General Wingate Polytechnic college-Official channel
ራዕይ:- በ2022 በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መሆን። የአይሶ 9001፡2015 የጥራት አመራር ስርዓት ሰርተፍኬት ባለቤት።
Больше📈 Аналитический обзор Telegram-канала General Wingate Polytechnic college-Official channel
Канал General Wingate Polytechnic college-Official channel (@wingetpolytechniccollege) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 12 605 подписчиков, занимая 15 721 место в категории Образование и 2 691 место в регионе Эфиопия.
📊 Показатели аудитории и динамика
С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 12 605 подписчиков.
Согласно последним данным от 14 сентября, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 315, а за последние 24 часа — 48, при этом общий охват остаётся высоким.
- Статус верификации: Не верифицирован
- Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 44.77%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 18.72% реакций от общего числа подписчиков.
- Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 5 640 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 359 просмотров.
- Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 21.
📝 Описание и контентная политика
Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
“ራዕይ:- በ2022 በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መሆን።
የአይሶ 9001፡2015 የጥራት አመራር ስርዓት ሰርተፍኬት ባለቤት።”
Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 15 сентября, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Образование.
Загрузка данных...
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 15 сентября | +6 | |||
| 14 сентября | +48 | |||
| 13 сентября | +23 | |||
| 12 сентября | +8 | |||
| 11 сентября | +20 | |||
| 10 сентября | +7 | |||
| 09 сентября | +6 | |||
| 08 сентября | +11 | |||
| 07 сентября | +10 | |||
| 06 сентября | +16 | |||
| 05 сентября | +13 | |||
| 04 сентября | +12 | |||
| 03 сентября | +25 | |||
| 02 сентября | +7 | |||
| 01 сентября | +14 |
| 2 | Нет текста... | 3 563 |
| 3 | Нет текста... | 1 |
| 4 | ማክሰኞ:- ጳጉሜ 3 ቀን 2018 ዓ∙ም
ኮሌጁ የ«ጽናት ቀን»ን ምክንያት በማድረግ የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር አካሄደ!!
ከ200 በላይ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የኮሌጁ ሰራተኞች እና በቋሚነት ድጋፍ ለሚደረግላቸው 13 ህፃናት ቤተሰቦች የበዓል መዋያ ስጦታ ተበርክቷል፡፡
ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ «የጽናት ቀን»ን እና መጪውን የ2019 አዲስ ዓመት በዓል ምክንያት በማድረግ በተቋሙ ውስጥ የመተሳሰብ፣ የመረዳዳት እና የደግነት ባህልን የሚያጎላ አርአያነት ያለው የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር አከናውኗል።
በዚሁ መርሃ ግብር ላይ በኮሌጁ ውስጥ ዝቅተኛ የደመወዝ መጠን ላላቸው ከ200 በላይ ሰራተኞች እንዲሁም ኮሌጁ በየወሩ በቋሚነት ድጋፍ እያደረገ ለሚያሳድጋቸው 13 ህፃናት ቤተሰቦች የበዓል መዋያ የሚሆን የዘይት እና የዱቄት ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።
የዚህ የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር ዋና ዓላማ ወቅታዊውን የኑሮ ውድነት ጫና ግምት ውስጥ በማስገባት በኢኮኖሚ ጫና ውስጥ ያሉ የሥራ ባልደረቦችን መደገፍ፣ በስራ ቦታ ላይ የመተሳሰብና የመረዳዳት ባህልን ማጠናከር እንዲሁም «የአንዱን ችግር ሌላው በመጋራት» የጽናትና የአንድነት መንፈስን ማጎልበት እንደሆነ ተገልጿል።
በዕለቱ እንደተገለፀው «ጽናት» በፈተናዎች ፊት ተስፋ አለመቁረጥና ወደፊት መጓዝ ብቻ ሳይሆን እጅ ለእጅ ተያይዞ አብሮ ማደግ፣ እርስ በርስ መደጋገፍና አብሮነትን ማጠናከር ጭምር በመሆኑ በተቋሙ ማህበረሰብ መካከል ያለውን ወንድማማችነትና አብሮነት የበለጠ ያጠናከረና ለመጪው አዲስ ዓመት አዲስ ተስፋንና ተነሳሽነትን ይፈጥራል ተብሏል።
የስጦታው ተጠቃሚ የሆኑ የኮሌጁ ሰራተኞችና የህፃናት ቤተሰቦችም በተደረገላቸው ድጋፍና በተቸራቸው ወንድማማችነታዊ ፍቅር የተሰማቸውን ጥልቅ ደስታ ገልጸው ለኮሌጁ አመራሮችና ማህበረሰብ ምስጋናቸውን አቅ | 1 |
| 5 | ሰኞ:- ጳጉሜ 2 ቀን 2018 ዓ∙ም
ኮሌጁ ጳጉሜ 3 «የጽናት ቀን»ን በደመቀ ሁኔታ አከበረ!!
ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የጳጉሜን ወር የስያሜ መገለጫ አስመልክቶ በአገር አቀፍ ደረጃ እየተከበሩ ከሚገኙት ሁነቶች መካከል ጳጉሜ 3 «የጽናት ቀን»ን በኮሌጁ ግቢ ውስጥ በልዩ ሁኔታ አክብሯል።
ዕለቱ የሀገር ፍቅር፣ የአንድነት እና የጽናት ተምሳሌትና ወካይ መገለጫ በሆነው የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ የመስቀል ስነ-ስርዓት የተጀመረ ሲሆን የኮሌጁ አመራሮችና ሰራተኞች በጋራ በመሆን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ሕዝብ መዝሙር ዘምረዋል።
ጽናት የትልቅ ራዕይ መሠረት፣ የለውጥ ኃይል እና የዘላቂ ስኬት መንገድ መሆኑ በዕለቱ መርሃ ግብር ላይ ተነስቷል። የኮሌጁ ማህበረሰብም እስካሁን ያለውን ትጋት በጽናት በማስቀጠል ለተቋሙ ሁሉን አቀፍ ለውጥ በማምጣት በሀገራዊ ዕድገት ላይ ጉልህ ሚናውን መወጣት እንዳለበት ተገልጿል።
ኮሌጁ ተቋማዊ አቅሙን አጠናክሮ ብቁና የላቀ ክህሎት ያላቸውን ባለሙያዎች በማፍራት የትውልድ ግንባታ ሀላፊነቱን በጽናት ሲወጣ የቆየ አንጋፋ ተቋም ነው።
በዛሬው ዕለትም በ2018 ዓ.ም የነበሩ ስኬቶችን በጽናት አስቀጥሎ ጥራት ያለው ስልጠናን ለመስጠት፣ ተቋሙን ለማዘመን፣ እንዲሁም በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ አምራች ኢንተርፕራይዞች ሐብት እንዲፈጥሩ ለማድረግ ሁሉም በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ቃል ኪዳኑን አድሷል።
በመጪው 2019 ዓ.ም አዲስ የስልጠና ዘመንም የጀመርነውን የለውጥ ጉዞ በበለጠ ቁርጠኝነት፣ በጽናትና በትብብር አጠናክረን መቀጠል እንዳለብን ተገልጿል፡፡ ጽናት በፈተና ፊት አለመቆም፤ ራዕይን ይዞ ወደፊት መጓዝ ነው!
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት" | 3 779 |
| 6 | ሰኞ:- ጳጉሜ 2 ቀን 2018 ዓ∙ም
የነባር ሰልጣኞች ምዝገባ ማስታወቂያ
እንኳን ለ2019 ዓ.ም የሥልጠና ዘመን በሰላም አደረሳችሁ!!!
በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2019 ዓ.ም ስልጠናችሁን የምትከታተሉ የቀን፣ የማታ እና የዊኬንድ ነባር (ተሻጋሪ) ሰልጣኞች በሙሉ አዲሱ ዓመት የስኬት፣ የዕድገት እና የላቀ ውጤት የምታስመዘግቡበት የተግባር ዘመን እንዲሆንላችሁ እየተመኘን ከዚህ ጋር በተያያዘው የምዝገባ ጊዜ ሰሌዳ መሠረት በኮሌጁ ግቢ ተገኝታችሁ ምዝገባ እንድታከናውኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
የቀን እና ማታ ሰልጣኞች የምዝገባ ፕሮግራም ከመስከረም 4ቀን እስከ መስከረም 8 ቀን 2019 ዓ.ም እንዲሁም የዊኬንድ ሰልጣኞች የምዝገባ ጊዜ ደግሞ ከመስከረም 9 እስከ መስከረም 10 ቀን 2019 ዓ.ም እንድትመዘገቡ እናሳስባለን። ከተጠቀሰው ጊዜ አልፎ ለሚመጣ ማንኛውም ሰልጣኝ የቅጣት ክፍያ የሚኖር መሆኑን እናሳውቃለን።
ጥብቅ ማሳሰቢያ፡
ምዝገባውን ለማከናወን የመመዝገቢያ ክፍያ በመክፈል የከፈላችሁበትን ደረሰኝ ማቅረብና ማስመዝገብ አለባችሁ።
ማንኛውም ሰልጣኝ ወደ ኮሌጁ ሲመጣ የኮሌጁን መታወቂያ ይዞ መምጣትና ማሳደስ ይጠበቅበታል።
የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሬጅስትራር ጽ/ቤት | 5 490 |
| 7 | Нет текста... | 4 106 |
| 8 | 🚀 ጳጉሜ 1የ'ዕምርታ ቀን' 🌟
ከተቋማዊ ደማቅ ስኬቶች መካከል በማንኪያ!
ጳጉሜ 1 "የዕምርታ ቀንን" ስናስብ ኮሌጃችን በተሰናባቹ የበጀት ዓመት በቴክኖሎጂ ማምረት፣ በፈጠራ እና በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ዘርፍ ያስመዘገበውን አኩሪ ስኬት በስሱ እንቃኛለን፡፡
በዘንድሮው ዓመት ጉዟችን ምን አሳካን?
⚙️ቴክኖሎጂና ፈጠራ፡- በአሰልጣኞቻችንና ሰልጣኞቻችን የተሰሩ ዘመናዊ የማምረቻ ቴክኖሎጂዎችን እና ሀገር በቀል ፈጠራዎችን ወደ ገበያ ማስገባት ችለናል።
🤝 የገበያ ትስስር፡- ምርቶቻችንን በኤግዚቢሽኖች በማስተዋወቅ እኛን የሚያምኑ አዳዲስ አጋሮችን አፍርተናል፤ የደንበኞቻችንንም አድማስ በከፍተኛ ሁኔታ አስፍተናል።
🏭 የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን፡ አብዛኛዎቹ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለተሰማሩ ከ338 በላይ ኢንተርፕራይዞች በ4ቱ የድጋፍ አግባቦች መሰረት የቴክኒክና ሙያ እገዛ በማድረግ በሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ደማቅ አሻራ አሳርፈናል፡፡
ትናንት ያስመዘገብነው ስኬት ለዛሬ ጥንካሬያችን፣ ለነገው ደግሞ የላቀ ጥልቅ ልምዳችን ነው!!
መልካም የዕምርታ ቀን! | 4 451 |
| 9 | እሁድ:- ጵጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ∙ም
የኮሌጁ ዲራፍቲንግ ሰልጣኞች በጃይካ (JICA) አገር አቀፍ የአርክቴክቸራል ዲዛይን ውድድር የዓመቱ ምርጥ አሸናፊ ሆኑ!!
በጃፓን ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ (JICA) አስተባባሪነት በተካሄደው የ2026 ዓመታዊ የአርክቴክቸራል ዲዛይን ውድድር (Architectural Design Competition) የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሰልጣኞች በሁለቱም የውድድር ዘርፎችና በልዩ የዓመቱ ምርጥ ዲዛይን ዘርፍ የ1ኛ ደረጃ አንጸባራቂ ድልን በመቀዳጀት የዋንጫና የልዩ የልዩ እውቅና ባለቤት ሆኑ።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥር በሚገኙና የድራፍቲንግ የስልጠና ዘርፍ ባላቸው ሦስት የፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች (ጀነራል ዊንጌት፣ ተግባረ-እድ እና አቃቂ) መካከል በደረጃ 4 በተካሄደው በዚህ ውድድር የጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተወዳዳሪዎች የላቀ ብቃታቸውን በማስመስከር ከፍተኛ ውጤቶችን አስመዝግበዋል፡፡
ሰልጣኞቹ በቅልቅል አገልግሎት ህንፃ ዲዛይን (Mixed-Use Design) ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃ ያለውን እንዲሁም በሕዝባዊ አገልግሎት ቦታዎች ዲዛይን (Public Area Design) ደግሞ 1ኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ አሸናፊ ሆነዋል፡፡
የዓመቱ ልዩ የዲዛይን እውቅና (Best Perspectives Award 2026) ላይ ደግሞ የኮሌጁ ሰልጣኝ የሆነቺው ሜሮን ደገፉ የዓመቱ ምርጥ የዲዛይን አሸናፊ በመሆን የኮሌጁን ስም በደማቅ ቀለም አፅፋለች፡፡
በዛሬዋ ልዩ የእምርታ ቀን በሆነቺው ዕለት በ'ክሬቲቭ ሀብ ሴንተር' (Creative Hub Center) በተካሄደው የእውቅናና የሽልማት መርሃ-ግብር መድረክ ላይ የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞች፣ የዲፓርትመንት ኃላፊዎች፣ የጃይካ (JICA) አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ውድድሩ የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞችን የእውቀት ሽግግር ማፋጠን፣ የፈጠራ ክህሎታቸውን ማሳደግ እና የሥራ ፈጠራ እድሎችን ማጠናከር (Knowledge Sharing and Entrepreneurship Pathways for TVET Students) ዓላማ ያደረገ መሆኑ ተገልጿል።
በዕለቱ በተካሄደው የሽልማት ሥነ-ሥርዓት ላይ የዓመቱ ምርጥ የዲዛይን አሸናፊ ለሆነችው ሰልጣኝ ሜሮን ደገፉ የዋንጫ፣ የታብሌት፣ የእውቅና ሰርተፊኬትና የገንዘብ ሽልማት የተበረከተላት ሲሆን ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃ በመያዝ ላጠናቀቁ የኮሌጁ ሰልጣኞችም የዋንጫ፣ የገንዘብና የተለያዩ የስልጠና ቁሳቁስ ማበረታቻ ተሸላሚ ሆነዋል።
ይህ የተመዘገበው አንጸባራቂ ድል ኮሌጃችን ጥራት ያለውና በገበያው ዘንድ ተወዳዳሪ የሆነ የሰው ኃይል ለማፍራት የሚያደርገውን ጥረትና ለሙያ ስልጠና የሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት የሚያሳይ ነው ተብሏል።
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት" | 4 833 |
| 10 | Нет текста... | 4 107 |
| 11 | Нет текста... | 4 270 |
| 12 | ሐሙስ:- ነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ∙ም
በፋዌ (FAWE) እና ማስተርካርድ ፋውንዴሽን ዓመታዊ ጉባኤ ላይ የኮሌጁ አሰልጣኝና ሰልጣኝ እውቅና ተበረከተላቸው፡፡
ኮሌጃችን በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል (AICC) በተካሄደው የፋዌ (FAWE) እና ማስተር ካርድ ፋውንዴሽን 2ኛ ምዕራፍ የ2026 ዓመታዊ የሰልጣኞች ጉባኤ ላይ በዛሬው ዕለት ተሳትፏል።
የአፍሪካ ሴት የትምህርት ባለሙያዎች ፎረም (FAWE) ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር የሚተገብረው ይህ የትምህርትና ስልጠና ድጋፍ ፕሮግራም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከተተገበረባቸው ሁለት ተቋማት አንዱ ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሲሆን በአሁኑ ወቅት 59 የኮሌጁ ሰልጣኞች የዚህ ፕሮግራም ተጠቃሚ ናቸው።
በጉባኤው ላይ "የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞችን የተቅጣሪነት እና የስራ ፈጠራ እድሎች ማጠናከር" (Strengthening Employability and Entrepreneurship Pathways for TVET Students) በሚል ርዕስ የፓናል ውይይት የተካሄ ሲሆን በውይይቱ ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ ከማስተርካርድ ፋውንዴሽን፣ ከፋዌ፣ ከኢንዱስትሪው ዘርፍ እና ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የተውጣጡ አመራሮች ተሳትፈዋል።
ውይይቱ ሰልጣኞችን ከገበያው ፍላጎት ጋር የሚጣጣም ክህሎት በማስጨበጥ፣ የኢንዱስትሪ ትስስርን በማስፋት እና ለግል ስራ ፈጠራ ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ዙሪያ ያተኮረ ነበር።
ከዕለቱ መርሃ-ግብር ክንዋኔዎች መካከል አንዱ የእውቅና እና ሽልማት ስነ-ስርዓት ሲሆን በዚህም በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በላቀ ስራ ሰልጣኞችን በማብቃትና በመደገፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱት የኮሌጁ የፊዚኮ-ኬሚካል አሰልጣኝ ወ/ሮ ጸሐይ አህመድ የታብሌት ሽልማት ሲበረከትላቸው በተመሳሳይ ከተቋማችን ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገበቺው ሰልጣኝ ሀና ቢራራ የስማርት ፎን ማበረታቻ ተሰጥቷታል፡፡
ፋዌ (FAWE) ከማስተርካርድ ፋውንዴሽን በሚያገኘው የገንዘብ ድጋፍ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ በአማራ፣ በኦሮሚያና ሲዳማ ክልሎች በሚገኙ 6 ፖሊ ቴክኒኮች ላይ እየሰራ ያለ ድርጅት ነው፡፡
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት" | 7 459 |
| 13 | Нет текста... | 7 152 |
| 14 | ቅዳሜ:- ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ∙ም
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ!!
የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ መደረጉን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
በዘመኑ ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡ 563 ሺህ 960 ተማሪዎች መካከል 550 ሺህ 210 ተማሪዎች ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 12.8 በመቶ (70 ሺህ 544 ተማሪዎች) 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ በማምጣት ማለፍ ችለዋል።
50ከመቶ እና ከዚያ በላይ ካመጡ ተማሪዎች መካከል በተፈጥሮ ሳይንስ 16.5 በመቶ እንዲሁም በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ 8.33 በመቶ ናቸው።
የተመዘገቡ ከፍተኛ ውጤቶችን በተመለከተ ተፈጥሮ ሳይንስ በወንድ 591.6 ከ 600 እና በሴት 583 ከ 600 ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ በወንድ 576.2 እና በሴት 569.1 ነው።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እንደገለጹት የዘንድሮው ውጤት ከባለፉት ዓመታት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ በመሆኑ የሚቀበሉት የሬሚዲያል ተማሪዎች ቁጥር የሚቀንስ ሲሆን የመቁረጫ ነጥቡ ወደፊት የሚገለጽ ይሆናል።
ተማሪዎች ውጤታቸውን ከሰኞ ጠዋት ወይም ማክሰኞ ከሰዓት ጀምሮ መመልከት የሚችሉ ሲሆን ቅሬታ ያላቸው ተማሪዎችም ለ5 እና 6 ቀናት ቅሬታ ማቅረብ ይችላሉም ተብሏል።
የብሔራዊ ፈተና ውጤት መለቀቁን ተከትሎ ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅም የስራና ክህሎት ሚኒስቴር በሚቆርጠው የመግቢያ ነጥብ መሠረት የ2019 ዓ.ም አዲስ ሰልጣኞችን ለመቀበል ሙሉ ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቋል።
ኮሌጁ በ12 ዲፓርትመንቶች እና 30 በሚደርሱ የሙያ መስኮች በቀን፣ በማታ እና በቅዳሜና እሁድ መርሃ ግብሮች ለማሰልጠን ሰብዓዊና ቁሳዊ ግብዓቶችን በማሟላት አዲስ ሰልጣኞችን ለመቀበል ዝግጁ ነው።
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት" | 8 114 |
| 15 | ሐሙስ:- ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ∙ም
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ!!
የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ይፋ መደረጉን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
በዘመኑ ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡ 563 ሺህ 960 ተማሪዎች መካከል 550 ሺህ 210 ተማሪዎች ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 12.8 በመቶ (70 ሺህ 544 ተማሪዎች) 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ በማምጣት ማለፍ ችለዋል።
50ከመቶ እና ከዚያ በላይ ካመጡ ተማሪዎች መካከል በተፈጥሮ ሳይንስ 16.5 በመቶ እንዲሁም በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ 8.33 በመቶ ናቸው።
የተመዘገቡ ከፍተኛ ውጤቶችን በተመለከተ ተፈጥሮ ሳይንስ በወንድ 591.6 ከ 600 እና በሴት 583 ከ 600 ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ በወንድ 576.2 እና በሴት 569.1 ነው።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እንደገለጹት የዘንድሮው ውጤት ከባለፉት ዓመታት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ በመሆኑ የሚቀበሉት የሬሚዲያል ተማሪዎች ቁጥር የሚቀንስ ሲሆን የመቁረጫ ነጥቡ ወደፊት የሚገለጽ ይሆናል።
ተማሪዎች ውጤታቸውን ከሰኞ ጠዋት ወይም ማክሰኞ ከሰዓት ጀምሮ መመልከት የሚችሉ ሲሆን ቅሬታ ያላቸው ተማሪዎችም ለ5 እና 6 ቀናት ቅሬታ ማቅረብ ይችላሉም ተብሏል።
የብሔራዊ ፈተና ውጤት መለቀቁን ተከትሎ ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅም የስራና ክህሎት ሚኒስቴር በሚቆርጠው የመግቢያ ነጥብ መሠረት የ2019 ዓ.ም አዲስ ሰልጣኞችን ለመቀበል ሙሉ ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቋል።
ኮሌጁ በ12 ዲፓርትመንቶች እና 30 በሚደርሱ የሙያ መስኮች በቀን፣ በማታ እና በቅዳሜና እሁድ መርሃ ግብሮች ለማሰልጠን ሰብዓዊና ቁሳዊ ግብዓቶችን በማሟላት አዲስ ሰልጣኞችን ለመቀበል ዝግጁ ነው።
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት" | 1 |
| 16 | Нет текста... | 5 992 |
| 17 | ሐሙስ:- ነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ∙ም
አንጸባራቂ ድል ለጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ!!
አንጋፋውና በክህሎት ስልጠና ዘርፍ ግንባር ቀደም የሆነው ጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2018 በጀት ዓመት ባስመዘገበው የላቀ አፈፃፀም በከተማ አቀፍ ደረጃ የ2ኛ ደረጃን ድል ተቀዳጅቷል።
ኮሌጁ ይህንን ትልቅ ስኬት ያረጋገጠው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ሥር በሚገኙ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች መካከል በተካሄደው ምዘና ነው።
በቢሮው በተካሄደው የ2018 በጀት ዓመት የግብ ተኮር (KPI) እና የቁልፍ ተግባራት አፈፃፀም ምዘና መሠረት ኮሌጃችን 94.26% ከፍተኛ ውጤት ማምጣት ችሏል።
ይህ ምዘና የተቋማትን የመማር ማስተማር ጥራት፣ የአሰራር ቅልጥፍና፣ የተገልጋይ እርካታን እንዲሁም በተቋማዊ አቅም ግንባታ የተከናወኑ ዐበይት ተግባራትን በሚገባ የፈተሸ ሲሆን ኮሌጁ በሁሉም መለኪያዎች ልቆ መገኘት ችሏል።
ኮሌጁ ባስመዘገበው በዚህ የላቀ አፈጻጸም የዕውቅናና ሽልማት የምስክር ወረቀት የተሰጠው ሲሆን ይህ ክብር የተቋሙ አመራሮች፣ አሰልጣኝና የአስተዳደር ሠራተኞች ዓመቱን ሙሉ ላሳዩት ያላሰለሰ ጥረት፣ ቁርጠኝነት እና ጠንካራ የቡድን መንፈስ የተሰጠ እውነተኛ ማሳያ ነው።
ይህ አሸናፊነት ኮሌጁ ለጥራት ማረጋገጥ ስርዓት የሚሰጠውን ከፍተኛ ትኩረትና ተቋማዊ አሰራሩን ለማዘመን እያደረገ ያለውን ስኬታማ ጉዞ በጉልህ የሚያንፀባርቅ ነው።
የኮሌጁ ማህበረሰብ በዚህ በተገኘው ስኬት በመኩራት በቀጣይ የ2019 በጀት ዓመት ከዚህም ላቀ ደረጃ ለመድረስና የ1ኛ ደረጃ አሸናፊነትን ለመቀዳጀት በበለጠ ተነሳሽነት ዝግጅቱን ጀምሯል።
ለዚህ ታላቅ ስኬት መገኘት ከፍተኛ አስተዋፅዖ ላበረከታችሁ የኮሌጃችን ቤተሰቦች በሙሉ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታችንን እያስተላለፍን በቀጣይ የጀመርነውን የላቀ አፈፃፀም አጠናክረን እንድንቀጥል ጥሪያችንን እናቀርባለን።
"በላቀ አገልግሎት የመረጃ ተደራሽነት" | 5 619 |
| 18 | Нет текста... | 5 011 |
| 19 | Нет текста... | 8 418 |
| 20 | ኢትዮጵያ በአፍሪካ መድረክ ላይ! 🇪🇹🌍
PICE በASEB 2026 የTOP 5 የመጨረሻ ተወዳዳሪዎች ውስጥ መመረጡን በደስታ እንገልጻለን።
ይህ የሽልማት ውድድር ብቻ አይደለም።
ይህ የኢትዮጵያን የፈጠራ፣ የቴክኒክ ክህሎት፣ የሥራ ፈጠራ እና የምርታማነት አቅም ለአፍሪካ የምናሳይበት እድል ነው።
🗳️ ለPICE ድምጽዎን ይስጡ!
🙏 ይምረጡ
📲 ያጋሩ
👥 ጓደኞችዎን ያሳትፉ
🌍 የኢትዮጵያን ድምፅ በአፍሪካ ያሰሙ!
አንድ ድምፅ። አንድ ድምጽ ማሰማት። አንድ የአፍሪካ ተፅዕኖ። 🇪🇹🌍
VOTE ON;-
https://www.asebs.com/finalists/productivity-improvement-center-of-excellence-coworking-space | 7 034 |
