Ethio Fm 107.8
በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!
Больше📈 Аналитический обзор Telegram-канала Ethio Fm 107.8
Канал Ethio Fm 107.8 (@ethiofm107dot8) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 18 480 подписчиков, занимая 12 127 место в категории Новости и СМИ и 1 872 место в регионе Эфиопия.
📊 Показатели аудитории и динамика
С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 18 480 подписчиков.
Согласно последним данным от 04 сентября, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -23, а за последние 24 часа — 1, при этом общий охват остаётся высоким.
- Статус верификации: Не верифицирован
- Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 10.90%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 7.28% реакций от общего числа подписчиков.
- Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 2 015 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 345 просмотров.
- Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 3.
📝 Описание и контентная политика
Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
“በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!”
Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 05 сентября, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Новости и СМИ.
Загрузка данных...
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 05 сентября | +5 | |||
| 04 сентября | +4 | |||
| 03 сентября | +1 | |||
| 02 сентября | +3 | |||
| 01 сентября | 0 |
| 2 | በጃፓን ያኩሺማ ከተማ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከፍተኛው የመሬት መንሸራተት ማስጠንቀቂያ ተሰጠ።
የጃፓን የአየር ሁኔታ ኤጀንሲ በካጎሺማ ግዛት ስር በምትገኘው ያኩሺማ ከተማ ከፍተኛውን የመሬት መንሸራተት ወይም የናዳ አደጋ ማስጠንቀቂያ አውጥቷል።
ኤጀንሲው ይህንን ከፍተኛ ደረጃ ያለው ማስጠንቀቂያ ያወጣው፣ በአካባቢው ታሪክ የማይረሳውና ክብረ ወሰን የሰበረ የዝናብ መጠን መመዝገቡን ተከትሎ ነው።
በከባድ ዝናቡ ምክንያት ሊከሰት የሚችለውን የመሬት መንሸራተት አደጋ ለመከላከል ነዋሪዎች አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉና የደህንነት መመሪያዎችን እንዲከተሉ ጥሪ ቀርቧል።
ይህ ከፍተኛው ደረጃ ላይ የሚገኝ ማስጠንቀቂያ ነዋሪዎች ሕይወታቸውን ለመታደግ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስዱ የሚያሳስብ መሆኑም ተገልጿል።
በአካባቢው ያለው የዝናብ ሁኔታ አሁንም አሳሳቢ በመሆኑ፣ የሚመለከታቸው አካላት ሁኔታውን በቅርበት እየተከታተሉ ይገኛሉ ሲል አናዶሉ ዘግቧል።
ልዑል ወልዴ
ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም | 1 422 |
| 3 | የኩላሊት ታካሚዎች በመድኃኒት ዋጋ መናር እና በትራንስፖርት እጥረት እየተፈተኑ መሆኑን ገለጹ
የተስፍ የኩላሊት የታካሚወች ማህበር የፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ አቶ ባህይሉ እረና እንደገለፁት የኩላሊት ታካሚዎች ከሕመማቸው በተጨማሪ በመድኃኒት ዋጋ መጨመር እና በትራንስፖርት ችግር ከፍተኛ እንግልት እየደረሰባቸው መሆኑን ተናግረዋል
በተለይም ለሕክምናቸው ወሳኝ የሆነው የ"ሄፓሪን" መድኃኒት ዋጋ በአሁኑ ወቅት እስከ 800 ብር ድረስ መድረሱ ታካሚዎችን ለከፍተኛ ችግር ዳርጓቸዋል ብለዋል።
ማህበሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለታካሚዎች በማህበሩ መታወቂያ ነፃ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት እንዲያመቻች ጥሪ አቅርቧል።
በተጨማሪም ከትግራይ እና ከአማራ ክልሎች የሚመጡ ታካሚዎች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን የገለጸው ማህበሩ፣ በነዚህ አካባቢዎች የበሽታው መስፋፋት መንስኤ ላይ ጥናት እንዲደረግና መንግስት ለመድኃኒት አቅርቦትና ለቦታ አቅርቦት ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቋል።
ሊዲያ ደሳለኝ
ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም | 1 311 |
| 4 | የየመን የመንግስት ጦር በሁቲ አማፂያን ይዞታዎች ላይ የአየር ጥቃት መፈጸሙ ተሰማ።
የየመን የጦር ኃይል በሀገሪቱ ታኢዝ እና አል-ሁዳይዳ ግዛቶች በሚገኙ የሁቲ አማፂያን ይዞታዎች ላይ 15 የአየር ጥቃቶችን መፈጸሙ ተገልጿል።
ይህ ጥቃት ባለፈው ሐምሌ ወር በየመን ያለው ግጭት ዳግም ካገረሸ ወዲህ፣ የመንግስት ጦር በቀጥታ በውጊያው ውስጥ ተሳትፎ ያደረገበት የመጀመሪያው አጋጣሚ መሆኑ ተነግሯል።
እንደ አናዶሉ ኤጄንሲ የዜና ምንጮች ዘገባ፣ የአየር ጥቃቱ ያነጣጠረው በአማፂያኑ ወታደራዊ ይዞታዎች እና የስትራቴጂክ ቦታዎች ላይ ነው።
ጥቃቱ በሁቲ አማፂያን ላይ ስላደረሰው ሰብአዊና ቁሳዊ ጉዳት እስካሁን በዝርዝር የወጣ መረጃ የለም።
በየመን ያለው ውጥረት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በመጣበት በዚህ ወቅት፣ መንግስት የወሰደው ይህ እርምጃ በግጭቱ ሂደት ላይ አዲስ ምዕራፍ ሊከፍት እንደሚችል ተገምቷል።
የየመን መንግስትም ሆነ የሁቲ አማፂያን ስለ ጥቃቱ የሰጡት ተጨማሪ ማብራሪያ የለም።
ልዑል ወልዴ
ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም | 1 390 |
| 5 | የሰራተኞች ማህበራት መደራጀት እንደ ተቃዉሞ እና ችግር ፈጣሪ ተደርጎ መታየት የለበትም ሲል ኢሰማኮ ተናገረ
ሰራተኞችን የሀገሪቱን ኢኮኖሚ የሚያንቀሳቅሱ እንጂ ችግር ፈጣሪ አልያም ተቃዋሚ አድርጎ መመልከት አይገባም ያለዉ ኮንፌዴሬሽኑ፥ሰራተኞች በመደራጀታቸዉ እና ጥያቄ በማንሳታቸዉ የማህበር መሪዎች እየታሰሩ እንደሚገኙ ተገልጿል።
ከ3 መቶ በላይ ህጋዊ እዉቅና ያላቸዉ የሰራተኛ ማህበራት እንዲደራጁ ተደርጓል ሲል የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን ተናግሯል።
ኮንፌዴሬሽኑ በተጠናቀቀው የበጀት አመት 4መቶ 28 መሠረታዊ የሠራተኞች ማህበራት መደራጀታቸውን አስታዉቋል።
የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን ( ኢሰማኮ) የማህበር መሪዎች ያለ አግባብ የቦታ ዝዉዉር እርምጃ እና ሰራተኞች በመደራጀታቸዉ እስር እየገጠማቸው እንደሚገኝ ተናግሯል።
የኮንፌዴሬሽኑ ኘሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ፥እስከ ሰኔ 30 ድረስ ባለዉ ጊዜ 4መቶ 28 የሰራተኞች ማህበራት መደራጀታቸዉን ገልፀዉ፤3መቶ 45ቱ ህጋዊ እዉቅና ያገኙ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የሰራተኞች ማህበራት እና በድርጅቶች መካከል የሚፈጠሩ አለመግባባቶች በድርድር መፍትሄ እንዲያገኙ፤ መፍትሄ ማግኘት ያልቻሉትን ደግሞ በፍርድ ቤት መፍትሔ እንዲገኝላቸዉ የህግ ድጋፍ እየተሰጠ ይገኛል ተብሏል።
የማህበራት መደራጀትን እንደ ተቃዋሚ መመልከት አይገባም የሚሉት የኮንፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት፥ ሰራተኞች ኢኮኖሚውን ለማንቀሳቀስ አጋዥ እንጂ ችግር ፈጣሪ ሆነው መታየት የለባቸውም ብለዋል።
የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን ዝቅተኛ የደሞዝ ወለል እንዲወስን የሚያስችለው ቦርድ እንዲቋቋም ደንብ ቢዘጋጅም እስካሁን መፅደቅ አለመቻሉን ገልጿል።
በወር 1 ሺህ እና 2 ሺህ ብር ተከፍሎት የሚሰራ ሰራተኛ እየኖረ ነዉ ወይ? የሚሉት የኮንፌዴሬሽኑ ኘሬዝዳንት አቶ ካሳሁን፥ዝቅተኛ የደሞዝ ወለል መወሰኑ ግዴታ መሆኑን እና ይህን ለማድረግ ግን ችግሮች እንደበዙ ተናግረዋል።
ቁምነገር አየለ
ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም | 1 737 |
| 6 | Нет текста... | 1 496 |
| 7 | በገጠሩ የሀገሪቱ ክፍል ለሚገኙ ከ4.5 ሚሊየን በላይ ዜጎች የቴሌኮም አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ መዘጋጀቱን ኢትዮ ቴሌኮም አስታወቀ
ለዚህም ይረዳዉ ዘንድ 6መቶ5 ተጨማሪ የሞባይል ጣቢያዎችን ሊገነባ ነው
ኢትዮ ቴሌኮም ‹‹የቀጣዩ አድማስ›› የ3 ዓመት ስትራቴጂ 2ኛ ዓመት የስራ ዕቅዱን ለጋዜጠኞች ይፋ አድርጓል፡፡
ኩባንያዉ በቂ የቴሌኮም አገልግሎት ያላገኙ ማኅበረሰቦችን ለማስተሳሰር እና የዲጂታል ክፍተትን በተሳካ ሁኔታ ለማጥበብ በአዲሱ 2019 በጀት ዓመት ውስጥ 6መቶ5 ለገጠር የተለዩ ሳይቶችን ጨምሮ 1 ሺህ6መቶ85 ተጨማሪ የሞባይል ሳይቶችን ለመገንባት ማቀዱን ዋና ስራ አስፈጻሚዋ ፍሬሕይወት ታምሩ ገልጸዋል፡፡
ይህም ከ1 ሺህ 4መቶ በላይ ቀበሌዎች ለሚኖሩ ከ4.5 ሚሊየን በላይ ዜጎች ወሳኝ የቴሌኮም አገልግሎትን የሚያረጋግጥ ይሆናል ብለዋል፡፡
የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ፤ እስከ 2020 ዓ.ም በሚቆየው በዚህ ስትራቴጂ የሞባይል ጣቢያዎችን ቁጥር 13 ሺህ 2መቶ38 ለማድረስ፣ የ4ጂ ኢንተርኔት ሽፋን 97 በመቶ እንዲሁም የ5ጂ አገልግሎት የሚሰጡ ከተሞችን ቁጥር 1መቶ ለማድረስ መታቀዱን አንስተዋል፡፡
የስትራቴጂው የመጀመሪያ ዓመት በስኬት መጠናቀቁን የገለጹት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ፤ የሞባይል ደንበኞች ቁጥር 96 ነጥብ 2 ሚሊየን፣ የቴሌብር ተጠቃሚዎች ደግሞ 60 ሚሊየን መድረሳቸውን ገልጸዋል።
እስከዳር ግርማ
ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም | 1 623 |
| 8 | በአዲስ አበባ ከተማ በህገ-ወጥ የማዕድን ቁፋሮ ላይ የተሰማሩ አካላት እስከ ግማሽ ሚሊዮን ብር እንደሚቀጡ የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ።
ባለስልጣኑ እንደገለጸው፤ ያለፈቃድ ማዕድን የሚያመርቱ፣ ከፈቃድ ውጭ የሚንቀሳቀሱ እና የአካባቢ ጥበቃ ህጎችን የማይተገብሩ አካላት ተጠያቂ ይሆናሉ።
በዚህም መሰረት፡-ያለፈቃድ ማዕድን ሲያመርቱ የተገኙ አካላት ከ300,000 እስከ 400,000 ብር ቅጣት እንደሚጠበቅባቸው ተገልጿል።
ህገ-ወጥ ድርጊቱን የፈጸሙ አካላት የገንዘብ ቅጣቱ እንደ ጥፋቱ ክብደት እስከ 500,000 ብር ሊደርስ እንደሚችልና መሳሪያዎቻቸውም በመንግስት እንደሚወረሱ ተመላክቷል።
ከተማዋንና መሰረተ ልማቶችን ለመጠበቅ በማዕድን ማምረቻ ቦታዎች ላይ የሲሲቲቪ ካሜራዎችን የመግጠም ስራ የግዴታ እንደሚሆንና አልሚዎችም የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርት ማቅረብ እንዳለባቸው ተሳስቧል።
ይህ ጥብቅ የህግ ማዕቀፍ የከተማዋን ደህንነትና ሰላም ለማረጋገጥ የታለመ መሆኑ ተገልጿል።
ሊዲያ ደሳለኝ
ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም | 1 707 |
| 9 | በአንድ ጊዜ በርካታ ተማሪዎችን ማስተናገድ የሚችል አዲስ የትምህርት መተግበሪያ ይፋ ተደረገ
ዛሬ ነሐሴ 28 ቀን 2018 አ.ም የትምህርት ጥራትን ለማሻሻልና የዲጂታል ትምህርት ተዳራሽነትን ለማስፋት ያለመ “ማይ ሲድ አካዳሚ”የተሰኘ አዲስ የትምህርት የሞባይል መተግበሪያ በይፋ ተመርቋል።
ማይሲድ ኤድ ቴክ ፒኤልሲ (MySeed EdTech PLC) ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር ያቀረበው ይህ መተግበሪያ፥ በአዲሱ የሀገሪቱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት የተቀረፀ ሲሆን፥ በአንድ ጊዜ በሚሊየን የሚቆጠሩ ተማሪዎችን ማስተናገድ የሚችል ቴክኖሎጂን የያዘ መሆኑ ተገልጿል።
የማይሲድ ኤድ ቴክ ትምህርት ክፍል ሀላፊ አቶ ዳኛቸው (ቲቸር ዳኒ) እንደገለጹት፥መተግበሪያው ከ5ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉትን ሁሉንም የትምህርት አይነቶች በተፈጥሮ እና በማህበራዊ ሳይንስ ዘርፎች አካቶ ይዟል።
በተጨማሪም ይዘቶቹ ተማሪዎች ባሉበት ቦታ ሆነው በሀገሪቱ በሚነገሩ 5 የተለያዩ ቋንቋዎች ትምህርታቸውን በቀላሉ እንዲከታተሉ ታስበው የቀረቡ ናቸው ብለዋል።
አክለውም ላለፉት ዓመታት በህክምና፣ በስነ ህንጻ እና በኢንጂነሪንግ ዘርፎች ሀገራቸውን መጥቀም የሚፈልጉ በርካታ ተማሪዎች ፍላጎታቸው ሳይሳካ የቀረው በትምህርት ስርዓቱ ችግር ሳይሆን ትምህርቱ በሚቀርብበት አቀራረብ ምክንያት መሆኑን ጠቁመዋል።
የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ኢዘዲን ከማል በበኩላቸው፥መተግበሪያው እንደ ቲክቶክ፣ ኢንስታግራም እና ዩቲዩብ ባሉ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚለቀቁ ማራኪ ይዘቶችን ታሳቢ በማድረግ ተማሪዎች በትምህርታቸው ላይ ተመሳሳይ ሳቢና አዝናኝ አቀራረብ እንዲያገኙ ተደርጎ መዘጋጀቱን ገልጸዋል።
ተማሪዎች ይዘቶቹን በቪዲዮ መልክ እያዩ በተመጣጣኝ ዋጋ በወር በ3መቶ99 ብር የሁሉንም የትምህርት አይነቶች ማብራሪያ፣ የፒዲኤፍ (PDF) ማስታወሻዎች እና የማጠናከሪያ ጥያቄዎችን ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።
በተጨማሪም መተግበሪያው ተማሪዎች የትምህርት ቪዲዮዎችን አንድ ጊዜ ዳውንሎድ ካደረጉ በኋላ ያለ ምንም ተጨማሪ የኢንተርኔት ዳታ ዓመቱን ሙሉ መከታተል የሚያስችል አሰራርን ይዟል።
በመተግበሪያው ተምረው በዓመቱ መጨረሻ የተሻለ ውጤት ለሚያመጡ ተማሪዎች የመኪና ሽልማትም ተዘጋጅቷል።
ይህ አፕሊኬሽን በፕሌይ ስቶር (Play Store) እና አፕ ስቶር (App Store) ላይ የሚገኝ ሲሆን፥በገጠርም ሆነ በከተማ የሚገኙ ተማሪዎች በእጃቸው ባለው ስልክ በመጠቀም ህልማቸውን እውን እንዲያደርጉ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።
ሀና ሰይፉ
ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም | 1 714 |
| 10 | Нет текста... | 1 611 |
| 11 | በመኪና ሽያጭ ላይ የሚፈፀሙ የታክስ ስወራዎችንና ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴዎችን ለመግታት ጠንካራ የህግ ማስከበር እርምጃ ሊወሰድ ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የገቢዎች ቢሮ ባወጣው እንዳሳወቀው፤ በከተማዋ አንዳንድ የመኪና አስመጪዎችና የኮሚሽን ስራ ፈቃድ የሌላቸው ግለሰቦች በመቀናጀት ከፍተኛ የታክስ ስወራ ወንጀል እየፈፀሙ ይገኛሉ።
ህገ-ወጥ አሰራሩ በተለይም የመኪና አስመጪዎች የሚያስገቧቸውን ተሽከርካሪዎች መደበኛ የንግድ ፈቃድና አድራሻ ለሌላቸው ደላሎች አሳልፈው በመስጠት፣ ህጋዊ ደረሰኝ ሳይቆርጡ ዋጋን ቀንሰው በመሸጥ ግብር እንዳይከፈል የሚያደርጉበት እንደሆነ ተጠቅሷል።
ይህ ድርጊት በፌደራል የገቢ ግብር አዋጅ እና በተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ መሰረት በወንጀል የሚያስጠይቅ በመሆኑ፣ ቢሮው ከሚመለከታቸው የህግ አካላት ጋር በመቀናጀት ቁጥጥሩን እንደሚያጠናክር ገልጿል።
ቢሮው የኮሚሽን ንግድ ፈቃድ ያላቸውም ሆኑ የመኪና አስመጪዎች ከእንደዚህ አይነት ህገ-ወጥ አሰራር እንዲወጡ ያስጠነቀቀ ሲሆን፤ ማንኛውም የመኪና ሽያጭ በህጋዊ የንግድ ቦታ፣ በደረሰኝ እና መደበኛ ታክስ ተከፍሎበት ብቻ መከናወን እንዳለበት አሳስቧል።
ሀና ሰይፉ
ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም | 1 913 |
| 12 | በኢትዮጵያ የከተማ መሠረተ ልማትን በዲጂታል አማራጮች ለማዘመን የሚያስችሉ የቴክኖሎጂ መፍትሔዎች ይፋ መደረጋቸው ተገለፀ
የኦርቢክስ ቴክኖሎጂስ ኃ.የተ.የግ.ማ በኢትዮጵያ የከተማ መሠረተ ልማትን የሚያዘምኑ እና አገልግሎቶችን ዲጂታል የሚያደርጉ ሦስት የቴክኖሎጂ መፍትሔዎችን ይፋ አደረገ።
እነዚህ ቴክኖሎጂዎች አገሪቱ ከነደፈችው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ጋር ቀጥተኛ ትስስር አላቸው።
የመጀመሪያው ዘመናዊ የፓርኪንግ ሥርዓት ሲሆን፥ አሽከርካሪዎች ክፍት የፓርኪንግ ቦታዎችን በቀላሉ መረጃ አግኝተው አስቀድመው እንዲይዙ እና በጥሬ ገንዘብ ሳይገበያዩ በ30 ሰከንድ ውስጥ በዲጂታል መንገድ ክፍያ እንዲፈጽሙ ያስችላል።
ይህም በእጅ የሚሰራውን አሰራር ከማስቀረቱም በላይ ለከተማ ፕላነሮች የትራፊክ ፍሰትን በጥናት ለመረዳት ያግዛል።
ሁለተኛው ኦርቢክስ ኢቪ(Orbix EV) የተባለው መድረክ ሲሆን፥ አገሪቱ ለነደፈችው ብሔራዊ የኢ-ሞቢሊቲ ስትራቴጂ ስኬት የተዘጋጀ ነው።
መድረኩ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎችን፣ የቻርጂንግ ጣቢያዎችን እና የኃይል አቅራቢዎችን በአንድ ላይ ያገናኛል።
አሽከርካሪዎች በአቅራቢያቸው ያሉ ጣቢያዎችን በቀላሉ እንዲያገኙ፣ ሰልፍ ለማስቀረት አስቀድመው ሰዓት እንዲይዙ እና በራስ-አገዝ ቻርጅ እንዲያደርጉ የሚረዳ ሲሆን፥ አጠቃላይ መሠረተ ልማቱን በአንድ ማዕከል ለመቆጣጠር የሚያስችል ብሔራዊ የኢቪ ዕዝ ማዕከል ያካትታል።
ሦስተኛው አይ ሀብ (iHub) የተባለው የዜጎች ተሳትፎ መድረክ ሲሆን፥ በዜጎች እና በመንግሥት መካከል ቀጥተኛ ግንኙነት ይፈጥራል።
ነዋሪዎች እንደ የመንገድ መበላሸት፣ የትራፊክ አደጋ፣ የቆሻሻ መከማቸት እና የፍሳሽ መስመሮች መዘጋትን የመሰሉ የከተማ ችግሮችን በፎቶ፣ በቪዲዮ እና በሎኬሽን በመታገዝ በቀጥታ ለሚመለከተው ተቋም ጥቆማ ማድረስ ይችላሉ።
ይህም የመንግሥት ተቋማት ለችግሮች ፈጣን ምላሽ እንዲሰጡ እና የከተማዋን ሀብት በግልጽነት እንዲያስተዳድሩ ያግዛል።
ሳራ ዮሐንስ
ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም | 1 528 |
| 13 | Нет текста... | 1 474 |
| 14 | በቴሌብር ላይ የተቀመጠውን የዝውውር ገደብ ለማንሳት ከብሔራዊ ባንክ ጋር እንደሚነጋገር ኢትዮ ቴሌኮም ገለፀ
ደንበኞች ቴሌብርን አሁን ላይ ከጥቃቅን የገንዘብ ዝውውሮች በተጨማሪ ከፍ ላሉ ክፍያዎች ጭምር እየተጠቀሙ መሆናቸውን የኩባንያው ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገልፀዋል።
ከፍተኛ የገንዘብ እንቅስቃሴ ባለበት ሁኔታ ደግሞ የብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ዝውውር ገደብ መኖሩ አስቸጋሪ እንደሆነባቸው ኩባንያው ከደንበኞች ተደጋጋሚ ቅሬታ እንደደረሰው ተናግረዋል።
ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ይህንን ያሉት ኢትዮ ቴሌኮም “የቀጣዩ አድማስ”የ3 ዓመት ስትራቴጂ 2ኛ ዓመት የስራ ዕቅዱን ለጋዜጠኞች ይፋ ባደረገበት ወቅት ነው።
ዕቅዱ የደንበኞችን ቁጥር ከማሳደግ ባሻገር የኔትወርክና የአገልግሎት ጥራትን ማሳደግ ዋነኛ ግቡ ማድረጉን ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ተናግረዋል።
ከተያዙት ዕቅዶች መካከል የቴሌብር ደንበኞቹን ቁጥር ከ67 ሚሊየን በላይ ማድረስ አንዱ መሆኑን ገልፀዋል።
በቴሌብር የሚደረግ የገንዘብ ዝውውር መጠንን ደግሞ ወደ 7.40 ትሪሊየን ብር ለማሳደግ መታቀዱንም ፍሬሕይወት ታምሩ ተናግረዋል።
ቴሌብር ስራ ከጀመረበት በእነዚህ 5 ዓመታት ውስጥ 9 ትሪሊየን ብር የገንዘብ ዝውውር ተካሂዶበታል ያሉ ሲሆን፥ በዚህኛው ዕቅድ ግን በአንድ ዓመት ውስጥ 7.4 ትሪሊየን ብር ለማዘዋወር መታቀዱን አንስተዋል።
በዚህ ዓመት ከተገኘው 2መቶ15 ቢሊየን ብር ገቢ በ2019 በጀት ዓመት 2መቶ 95 ቢሊየን ብር ገቢ ለማግኘት መታቀዱን ተናግረዋል።
ለኩባንያው ገቢ የዳታ እና ኢንተርኔት አገልግሎት ከፍተኛውን ቦታ መያዛቸው የተነሳ ሲሆን፥ በቀጣይ ለተያዘው ዕቅድም ከፍተኛውን ቦታ የሚይዝ መሆኑ ተገልጿል።
አጠቃላይ የደንበኞቹን ቁጥር ወደ 96.2 ሚሊየን ለማሳደግ ዕቅድ መያዙንም ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ተናግረዋል።
እስከዳር ግርማ
ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም | 1 804 |
| 15 | Нет текста... | 1 499 |
| 16 | Нет текста... | 1 |
| 17 | ውዳሴ ዲያግኖስቲክ ማዕከል ለ5 ቀናት የሚቆይ ነፃ የሕክምና ዘመቻ ይፋ አደረገ
ውዳሴ ዲያግኖስቲክ ማዕከል፥ “ጳጉሜን ለጤና” በሚል መሪ ቃል ላለፉት 16 ዓመታት ሲያካሂድ የቆየውን ነፃ የሕክምና ምርመራ እና የበጎ አድራጎት መርሃ ግብር ዘንድሮም ለ17ኛ ጊዜ እንደሚያካሒድ አሳውቋል::
ዘመቻው በአቅም ማነስ ምክንያት የሕክምና ምርመራ ወጪ መሸፈን ለማይችሉ እና በሐኪም የታዘዘ የምርመራ ወረቀት በእጃቸው ለሚገኝ ዜጎች ታስቦ የተዘጋጀ ሲሆን፥ ከነሐሴ 28 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለ5 ተከታታይ ቀናት ይቆያል።
በዚህም መሰረት የCT Scan፣ MRI፣ X-ray እና Ultrasound (3D፣ 4D) ህክምና ምርመራዎች የልብ እና የልብ ምርመራ (Echo) እና ECG ምርመራዎች በነፃ ይሰጣሉ።
በተጨማሪም በ ISO የተረጋገጠ የላቦራቶሪ ምርመራዎች በተከታታይ ለ5 ቀናት ይሰጣሉ።
ከነፃ የሕክምና ምርመራዎቹ በተጨማሪ፥የውዳሴ ዲያግኖስቲክ ማዕከል የማህበረሰብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ አምስቱን የጳጉሜ ቀናት መሰረት ያደረጉ ልዩ ልዩ የበጎ አድራጎት ተግባራትን ለማከናወን ማቀዱም ታውቋል።
የዘንድሮ የ“ጳጉሜን ለጤና” 17ኛ ዓመት ክብረ በዓል የሕክምና አገልግሎትን “ከአባቶች ክብርና ቡራኬ” ጋር በማስተሳሰር የሚታሰብ ይሆናል ተብሏል።
ውዳሴ ዲያግኖስቲክ ማዕከል ለ24 ሰዓታት ክፍት በመሆን አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
የዚህ ነፃ የሕክምና ዕድል ተጠቃሚ ለመሆን የሚፈልጉ የሐኪም ትዕዛዝ በእጃቸው የሚገኝ ዜጎች፥ከነሐሴ 28 እስከ ጳጉሜ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት ቀናት በአጭር ስልክ ቁጥር 9888 ወይም በ0940-040404 / 0940-050505 በመደወል መመዝገብ እንደሚችሉ ማዕከሉ ገልጿል።
ሀና ሰይፉ
ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም | 1 712 |
| 18 | Нет текста... | 1 647 |
| 19 | Нет текста... | 1 |
| 20 | https://youtu.be/59FMd3AwtoA?si=FwoodeYrd614SkJ_ | 1 508 |
