Ethio Fm 107.8
በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!
Больше📈 Аналитический обзор Telegram-канала Ethio Fm 107.8
Канал Ethio Fm 107.8 (@ethiofm107dot8) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 18 508 подписчиков, занимая 12 333 место в категории Новости и СМИ и 1 827 место в регионе Эфиопия.
📊 Показатели аудитории и динамика
С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 18 508 подписчиков.
Согласно последним данным от 22 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -52, а за последние 24 часа — 3, при этом общий охват остаётся высоким.
- Статус верификации: Не верифицирован
- Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 9.45%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 7.06% реакций от общего числа подписчиков.
- Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 1 748 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 306 просмотров.
- Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 4.
📝 Описание и контентная политика
Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
“በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!”
Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 23 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Новости и СМИ.
Загрузка данных...
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 23 июля | +2 | |||
| 22 июля | +1 | |||
| 21 июля | +6 | |||
| 20 июля | 0 | |||
| 19 июля | 0 | |||
| 18 июля | +4 | |||
| 17 июля | 0 | |||
| 16 июля | +1 | |||
| 15 июля | +2 | |||
| 14 июля | +3 | |||
| 13 июля | +5 | |||
| 12 июля | +1 | |||
| 11 июля | 0 | |||
| 10 июля | +11 | |||
| 09 июля | +2 | |||
| 08 июля | +1 | |||
| 07 июля | 0 | |||
| 06 июля | +2 | |||
| 05 июля | 0 | |||
| 04 июля | +15 | |||
| 03 июля | 0 | |||
| 02 июля | +3 | |||
| 01 июля | 0 |
| 2 | የኔታንያሁ የእስር ትእዛዝ በትራምፕ እና በኒውዮርክ ከንቲባ መካከል የፈጠረው ውዝግብ
የኒውዮርክ ከተማ የመጀመሪያው ሙስሊም ከንቲባ ዞህራን ማምዳኒ፣ የኢስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ለመካፈል ወደ ከተማዋ በሚመጡበት ወቅት በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ያቀረቡት ጥሪ፣ በሀገር ውስጥ ፖለቲካ እና በአለም አቀፍ ዲፕሎማሲ መካከል ከፍተኛ ፍጥጫ አነሳስቷል።
ማምዳኒ እና የከተማዋ የህግ መምሪያ ባደረጉት ግምገማ፣ የኒውዮርክ ከተማ ከአለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) የወጣውን የእስር ትእዛዝ በራሷ ስልጣን የመፈጸም ገለልተኛ የህግ አቅም እንደሌላት አረጋግጠዋል።
ሆኖም ከንቲባው የከተማዋ ፖሊስ በቀጥታ በቁጥጥር ስር ማዋል ባይችልም፣ የፌዴራል መንግስቱ ትእዛዙን እንዲያስፈጽም ጥሪ አቅርበዋል። ኔታንያሁ በኒውዮርክ ከተማ "የተጠሉ እና የማይፈለጉ" መሆናቸውን በመግለጽ፣ ነዋሪዎች በሚመጡበት ወቅት ህዝባዊ ተቃውሟቸውን እንዲያሰሙ አበረታተዋል።
በአንጻሩ የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር የኔታንያሁን ደህንነት ማረጋገጥ ዋና አላማው አድርጎታል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኔታንያሁ በአሜሪካ ምድር በሚቆዩበት ወቅት በማንኛውም መልኩ በቁጥጥር ስር እንደማይውሉ ዋስትና ሰጥተዋል።
የስቴት ሰክሬታሪ ማርኮ ሩቢዮ ይህንን ጥረት የመንግስት አካላት የተሳተፉበት ዘመቻ ሲሉ የገለጹት ሲሆን፣ የትራምፕ አስተዳደር የአለም አቀፉን ፍርድ ቤት ህጋዊ ስልጣን ሙሉ በሙሉ በመቃወም በፍርድ ቤቱ ባለስልጣናት ላይ ማዕቀብ ጥሏል።
ይህ ፍጥጫ የተቀሰቀሰው በጋዛ ውስጥ ከ73,000 በላይ ሰዎች ህይወት ማለፉን የጤና ባለስልጣናት ባረጋገጡበት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሁኔታውን ከዘር ማጥፋት ጋር በደመደመበት ወቅት ነው። ከአለም አቀፉ የፍትህ ፍርድ ቤት (ICJ) እና ከአለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) የተሰጡ ውሳኔዎች ለከንቲባው አቋም መነሻ ሆነዋል።
የማምዳኒ መግለጫ በከተማዋ በሚገኙ የአይሁድ ማህበራት ዘንድ፣ በተለይም በ UJA-Federation እና በኢስራኤል አምባሳደር ዳኒ ዳኖን ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞ አስነስቷል። ተቃዋሚዎቹ ከንቲባው የኒውዮርክን ህዝብ ለማገልገል እንጂ ኢስራኤልን ለፖለቲካ መጠቀሚያ ለማድረግ እንዳልተመረጡ በመግለጽ፣ አቋማቸው በከተማዋ የፀረ-ሴማዊነት ጥቃት እንዲስፋፋ ያደርጋል ሲሉ ኮንነዋቸዋል።
ከንቲባ ማምዳኒ ኔታንያሁን የማሰር ህጋዊ ስልጣን እንደሌላቸው ቢቀበሉም፣ የሟቾችን ቁጥር ወደ ህዝብ መድረክ በማውጣት እና የፓለስቲና ደጋፊዎችን ድምጽ በማሰማት በፌዴራል መንግስቱ ላይ የፖለቲካ ተጽእኖ ማሳደር ችለዋል። በትራምፕ አስተዳደር በኩል ያለው አቋም ግን የፌዴራል ስልጣንን በመጠቀም ኔታንያሁን ሙሉ በሙሉ ከህግ ተጠያቂነት የመጠበቅ ጽኑ ፍላጎትን እንደሚያሳይ ተመላክቷል።
ለዓለም አሰፋ
ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም | 379 |
| 3 | Нет текста... | 366 |
| 4 | በወታደራዊ ጁንታ የሚመሩት ሶስቱ ሀገራት የአፍሪካ ዋንጫን ለማስተናገድ ጥያቄ አቀረቡ
ቡርኪና ፋሶ፣ ማሊ እና ኒጀር በ2032 የሚካሄደውን የአፍሪካ ዋንጫን በጋራ ለማዘጋጀት ጥያቄ አቀረቡ፡፡ ይሁንና በአካባቢው ካለው የፀጥታ ስጋት አንፃር ካፍ ዕድሉን እንዳይሰጣቸው ተቃውሟቸውን የሚያሰሙ አካላትም በርክተዋል፡፡
የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) በ2028፣ 2032 እና 2036 የሚካሄዱትን የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ለማዘጋጀት የሚፈልጉ ሀገራት እንዲወዳደሩ ጨረታ ማውጣቱ የሚታወስ ነው።
የማሊ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እንደገለጸው የሶስቱ ሀገራት የጋራ ማመልከቻ በ"ወንድማማችነት፣ ቀጣናዊ ትስስር እና በአፍሪካ እግር ኳስ ዘላቂ እድገት" ላይ ያተኮረ ነው። አክሎም ለአህጉራዊው ጨዋታ አዲስ ዕይታን ለማምጣት የሚያስችል "ጠንካራ እና ተአማኒነት ያለው ጥያቄ" ለማዘጋጀት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እንደሚሰራ አስታውቋል።
ሦስቱ ጎረቤታሞች የሳህል ሀገራት ህብረት (AES) የተሰኘውን የፀጥታ፣ የመሠረተ ልማት፣ የንግድ እና ኢኮኖሚ ልማት ትብብር ስምምነት በጋራ ከመሰረቱ በኋላ ባለፈው ዓመት ከምዕራብ አፍሪካ የኢኮኖሚ ማህበረሰብ (ECOWAS) በይፋ መውጣታቸው ይታወሳል።
ሆኖም በቡርኪና ፋሶ፣ ማሊ እና ኒጄር ውስጥ ያለው የፀጥታ ሁኔታ በታጣቂ ጂሃዲስቶች ጥቃት ምክንያት አሁንም በከፍተኛ ሁኔታ ያልተረጋጋ ነው። የሦስቱ ሀገራት ወታደራዊ መንግስታት ከምዕራባውያን የደህንነት አጋሮቻቸው በመራቅ ከሩሲያ ጋር ያላቸውን ግንኙነት አጠናክረዋል። ይህንን የሚቃወሙ የካፍ አባል ሀገራት ደግሞ የአፍሪካ ዋንጫው እንዳይሰጣቸው ይፈልጋሉ፡፡
የካፍ ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሞሴፔ ከሀገራቱ የቀረበውን “የ2032ቱን የአፍሪካ ዋንጫ በጋራ እናዘጋጅ” ጥያቄ አስመልክቶ የአህጉሪቱ እግር ኳስ መሪ አካል ማመልከቻውን ከመገምገሙ በፊት የደህንነት ዋስትና ያስፈልገው እንደሆነ ተጠይቀው “ሦስቱ ሀገራት ውድድሩን ለማዘጋጀት እንደማንኛውም የአህጉሪቱ ሀገራት እኩል እድል ይኖራቸዋ” ብለዋል።
"በወታደራዊ መንግስታት በመመራታቸው ምክንያት ምንም ዓይነት አሉታዊ ተፅዕኖ ወይም ጥላቻ አይደርስባቸውም፤ ነገር ግን የሰላም እና የደህንነት ጥያቄዎች ግድ ይላል፡፡ እሱ በእርግጠኝነት ትኩረት ሰጥተን የምንገመግመው ጉዳይ ነው። ነገር ግን የ2032 አፍሪካ ዋንጫ የት እንደሚካሄድ እስካሁን የተወሰነ ውሳኔ የለም። በእርግጥ ዲሞክራሲ፣ የመናገር ነፃነት እና መደበኛ ምርጫዎች የመደራደሪያ ነጥቦች አይደሉም፤ ከዛ ይልቅ በጣም ወሳኝ ናቸው፡፡ ነገር ግን በእግር ኳሱ በኩል ለመነጋገር ወደ እነዚያ ሀገራት እጓዛለሁ" ሲሉም አብራርተዋል።
በምስጋናው ታደሰ
ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም | 514 |
| 5 | Нет текста... | 441 |
| 6 | በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የ"አሜሪካን ስፔስ" ማዕከል ተመረቀ
የአሜሪካው አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የ"አሜሪካን ስፔስ" ማዕከል መረቁ።
ኤምባሲው ለጣቢያችን በላከው መግለጫ ማዕከሉ በኢትዮጵያ 7ኛው፣ በሀገሪቱ ደቡብ ክፍል ደግሞ የመጀመሪያው ነው።
ማዕከሉ ለሁሉም ክፍትና ነፃ ሲሆን፤ ኮምፒውተሮችን ለመጠቀም፣ የ3D ህትመት ልምምድ ለማድረግ፣ ለትምህርት ዕድሎች ለመዘጋጀትና በቴክኖሎጂ እንዲሁም በእንግሊዝኛ ቋንቋ ስልጠናዎች ላይ ለመሳተፍ የሚያስችል መድረክ ነው ተብሏል።
አምባሳደሩ በጉብኝታቸው ወቅት ከክልሉና ከከተማው ከፍተኛ አመራሮች ጋር በብሔራዊ የምክክር ሂደትና በኢኮኖሚ ዕድሎች ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን፤ ከ22 ሺህ በላይ ሰራተኞችን የያዘውን የሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክም ጎብኝተዋል።
ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም | 441 |
| 7 | Нет текста... | 377 |
| 8 | ኢትዮ ቴሌኮም በተጠናቀቀው 2018 በጀት ዓመት 215 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ገቢ አገኘሁ አለ
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ የተቋሙን የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም አስመልክተው በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
በመግለጫቸውም በበጀት ዓመቱ የገቢ ምንጭን በማስፋት በርካታ ሥራዎች መከናወናቸውን አብራርተዋል፡፡
በዓመቱ 215 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ገቢ መገኘቱን ጠቅሰው ÷ በዚህም የእቅዱን 99 ነጥብ 7በመቶ ማሳካት ተችሏል ነው ያሉት፡፡
ከባለፈው ተመሳሳይ ዓመት ጋር ሲነጻጸርም የ33 ነጥብ 2 በመቶ እድገት ማሳየቱን ነው የተናገሩት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ።
ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም | 388 |
| 9 | ለተጨዋቾቹ የተበረከተው አስገራሚ ስጦታ
ሎስ ፓላሲዮስ ኢ ቪያፍራንካ በስፔን ከሲቪያ በስተደቡብ አቅጣጫ የምትገኝ አነስተኛ ከተማ ናት፤ 400 ሺህ ህዝብ ብቻ ይኖርባታል፡፡ ስፔን የዘንድሮውን የዓለም ዋንጫ ስታነሳ ታዲያ የቡድኑ አባላት ከነበሩት መካከል ፋቢያን ሩይዝ እና ጋቪ ከዚህች አነስተኛ ከተማ ነው የተገኙት፡፡
ሁለቱ ተጨዋቾች ትናንትና ወደ ትውልድ ከተማቸው ሎስ ፓላሲዮስ ኢ ቪያፍራንካ ሲመለሱ ታዲያ በነዋሪዎቿ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡ ከዚህም በላይ ግን ነገሩን አስገራሚ ያደረገው ጉዳይ ላስመዘገቡት ድል የተበረከተላቸው ሽልማት ነው፡፡ የከተማዋ ማዘጋጃ ቤት ሃላፊ ከተማቸው በቲማቲም ምርቷ የምትታወቅ መሆኗንና በተለያዩ አጋጣሚዎች ታሪክ ለሚሰሩ ጀግኖቻቸው ይህንን ምርት በሽልማት መልክ እንደሚየጣበረክቱ ጠቅሰው ለሁለቱ ተጨዋቾችም ይሄንኑ ሽልማት አበርክተውላቸዋል፡፡
ሽልማቱ የተበረከተላቸው በኪሏቸው መሰረት ነው፡፡ በዚህም መሰረት የፓሪስ ሴንት ዠርሜኑ ሩይዝ 85 ኪሎግራም እንዲሁም የባርሴሎናው ጋቪ 68.5 ኪሎ ግራም የቲማቲም ምርት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ የቀድሞው የስፔን ብሔራዊ ቡድን መስመር ተጫዋች ሄሱስ ናቫስ እ.ኤ.አ በ2010 የዓለም ዋንጫን በማንሳት ከሎስ ፓላሲዮስ ኢ ቪያፍራንካ ከተማ የተገኘ የመጀመሪያው ተጫዋች በነበረበት ወቅት ተመሳሳይ ሽልማት ተበርክቶለት ነበር። ከዚህ በተጨማሪም ናቫስ እና የአሁኑ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ሩይዝ ከስፔን ጋር የ2024 አውሮፓ ዋንጫን ካሸነፉ በኋላም ተመሳሳይ የቲማቲም ስጦታ ተበርክቶላቸው ነበር።
የከተማዋ የስፖርት ማዕከል በናቫስ ስም የተሰየመ ሲሆን፤ አሁን ደግሞ ለተቀዳጁት ስኬት እውቅና ለመስጠት የእግር ኳስ ሜዳዎች በሩይዝ እና በጋቪ ስም እንዲሰየሙ ከውሳኔ ላይ መደረሱን የከተማዋ ማዘጋጃ ቤት አስታውቋል።
ምስጋናው ታደሰ
ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም | 372 |
| 10 | Нет текста... | 317 |
| 11 | የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በቀበና ወንዝ ዳርቻ "ተስፋን እንተክላለን” በሚል መሪ ቃል የችግኝ ተከላ አከናወነ።
ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ በዛሬው ዕለት የመገናኛ ብዙኃን ባለድርሻ አካላትን በመጥራት ባዘጋጀው የችግኝ ተከላ መርሐ-ግብሩን አካሂዷል ፡፡
የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ''ተስፋን እንተክላለን” በሚል መሪ ቃል የባለሥልጣኑ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ቀበና ወንዝ ዳርቻ በጋራ አከናውኗል፡፡
በዕለቱም ክብርት ሃይማኖት ዘለቀ የመገናኛ ብዙሃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ፣ የክፍለ ከተማው አመራሮች እና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።
ኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በየዓመቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሚያከናውናቸው የልማት ሥራዎች አንዱ የሆነውን ይኸው ተግባር በየዓመቱ የሚያከናውነው ነው፡፡
በዕለቱም ክብርት ሃይማኖት ዘለቀ የመገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ችግኝ በመትከል ሁሉም ሰው ሀገራዊ ኃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።
ሊዲያ ደሳለኝ
ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም | 399 |
| 12 | የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና የዓለም ግዙፉን የንግድ ትስስር እየፈጠረ ነው – የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ
ሚኒስትር ደኤታው አምባሳደር ሃደራ አበራ፣ አፍሪካ በወሳኝ የኢኮኖሚ ሽግግር ላይ እንደምትገኝ በማንሳት፣ ነፃ የንግድ ቀጣናው ለአገራት አዳዲስ የንግድ፣ ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ዕድሎችን ይዞ መምጣቱን መናገራቸውን ተዘግቧል።
"አኅጉሪቱ ለዓለም አቀፍ ንግድ ጠቃሚ የሆነ የፈጠራ እና የኢንዱስትሪ ዕድገት ማዕከል እየሆነች ነው" ሲሉ ዲፕሎማቱ የመጀመሪያው የባህረ ሰላጤ እና የአፍሪካ ስልታዊ አጋርነት ከፍተኛ የውይይት መድረክ ላይ ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በ2019 የበጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ለኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች የሚሆን 500 ሚሊዮን የሜሪካን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ጨረታ መርሃ-ግብር ይፋ አደረገ
ባንኩ ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ የሀገር ውስጥ ገበያውንና የንግድ እንቅስቃሴውን ለማጠናከር የተዘጋጀው ይህ ጨረታ ከነሐሴ ወር ጀምሮ በየሁለት ሳምንቱ የሚካሄድ ይሆናል።
ግልጽነትን ለማስፈንና አስተማማኝ የፋይናንስ ፍሰት ለመፍጠር በየጨረታው 125 ሚሊዮን ዶላር ለንግድ ባንኮች ይቀርባልም ተብሏል።
በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ዘርፍ የታዩ የፖሊሲና የኢንቨስትመንት ክፍተቶችን ለመድፈን የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ስምምነት ተፈረመ
በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚስተዋሉ የአቅም፣ የኢንቨስትመንት እና የፖሊሲ ትስስር ማነቆዎችን በዘላቂነት ለመቅረፍ የሚያስችል አዲስ የስምምነት ምዕራፍ በዛሬው እለት ተከፍቷል።
የኢትዮጵያ ሪል እስቴት አልሚዎች ማህበር (EREDA) እና ዶክሳ ቢዝነስ ትሬዲንግ፣ የሀገር ውስጥና የአህጉር አቀፍ የቢዝነስ ትስስሮችን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ሁለት ስትራቴጂያዊ የመግባቢያ ሰነዶችን በይፋ ተፈራርመዋል።
ይህ ስምምነት በዘርፉ የሚንቀሳቀሱ አልሚዎችን፣ የፋይናንስ ተቋማትን፣ የፖሊሲ አውጪዎችን እና የቴክኖሎጂ አቅራቢዎችን በአንድ ወጥ መድረክ በማገናኘት፣ እስካሁን በዘርፉ ሲታይ የነበረውን የተቆራረጠ አሰራር ለማስቀረት ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።
እንደ ስምምነቱ መነሻ፣ ሁለቱ ተቋማት በቅርቡ በሚካሄዱ ዓመታዊ የሪል እስቴት ጉባኤዎች እና ቀጣናዊ የኤክስፖ መድረኮች ላይ በጋራ በመሰለፍ የኢንዱስትሪውን ተወዳዳሪነት ለማረጋገጥ ወስነዋል።
ተቋማቱ በጋራ በሰጡት መግለጫ እንዳመለከቱት፤ ትብብሩ በደፈናው የሚመራ ሳይሆን፣ የሁለቱን ወገኖች ኃላፊነት፣ የሥራ ጊዜ ሰሌዳ እና የሚጠበቁ ውጤቶችን በግልጽ በለየ ይፋዊ ስምምነት የሚመራ ነው።
ይህም የዘርፉን ዕድገት በዘፈቀደ ሳይሆን በሳይንሳዊ እና በተጠያቂነት መርህ ለመምራት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተመላክቷል።
የሪል እስቴት አልሚዎች ማህበር በዘርፉ ሙያዊ መመዘኛዎች እንዲከበሩና የባለድርሻ አካላት ቅንጅት እንዲጠናከር በትኩረት የሚሰራ ሲሆን፣ አጋር ድርጅቱ ዶክሳ ቢዝነስ ትሬዲንግ በበኩሉ ዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንቶችን በማሳብ እና የንግድ ትስስሮችን በመፍጠር ረገድ የድርሻውን ይወጣል ተብሏል።
ይህ ስምምነት በተለይም በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ዘርፍ አንገብጋቢ የሆኑትን የመሠረተ ልማት እና የፋይናንስ አቅርቦት ችግሮችን ለመፍታት እንዲሁም የሀገሪቱን የቤት ልማት እንቅስቃሴ ከአህጉራዊ የንግድ ትስስሮች ጋር ለማቀናጀት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተገልጿል።
ኢንዱስትሪው አሁን ካለበት ፈታኝ ሁኔታ ወጥቶ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ኢንቨስተሮች ምቹ እንዲሆን ለማድረግ ይህ ስምምነት እንደ ትልቅ የማሳያ እርምጃ ተወስዷል።
ልዑል ወልዴ
ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም | 813 |
| 13 | Нет текста... | 758 |
| 14 | አዲሱ የሐማስ መሪ ኻሊል አል-ሐያ የእስራኤል ጥቃት እንዲቆም እና ብሔራዊ አንድነት እንዲረጋገጥ ጥሪ አቀረቡ
ሰኞ ዕለት የሐማስ መሪ ሆነው የተሾሙት ኻሊል አል-ሐያ፣ ከተሾሙ ወዲህ የመጀመሪያ መግለጫቸውን ሰጥተዋል። መሪው በመግለጫቸው ድርጅታቸው በቀጣይ ትኩረት ሰጥቶ ስለሚሰራባቸው ዋና ዋና ጉዳዮች ተናግረዋል።
አል-ሐያ በመግለጫቸው ካሰፈሯቸው ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮች መካከል የመጀመሪያው በእስራኤል እየተካሄደ ያለው ጥቃት ሙሉ በሙሉ እንዲቆም ማድረግ መሆኑን ገልጸዋል።
"ለጋዛ ሕዝብ የምለው፤ በእናንተ ላይ የደረሰውን ጉዳት እና ስቃይ እስክናስወግድ ድረስ በሁሉም መንገድ እና አቅጣጫ መስራታችንን እንቀጥላለን" ያሉት መሪው፣ ለጋዛ ሕዝብ ሰብአዊ ክብር ያለው ኑሮን መመለስ ተፈጥሯዊ መብቱ መሆኑን አጽንዖት ሰጥተዋል።
ከጋዛ በተጨማሪም በወረራ ስር ያለውን የዌስት ባንክ (የምዕራብ ዳርቻ) ግዛት መከላከል፣ ስለ እየሩሳሌም እና ስለ እስረኞች መብት መታገል የድርጅታቸው ኃላፊነት እንደሆነና በሁሉም ግንባሮች እንቅስቃሴያቸውን እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።
ሌላው የአዲሱ መሪ ትኩረት "ብሔራዊ አንድነትን ማስፈን" ያሉት ሲሆን፣ ይህንን ግብ ለማሳካት ከሁሉም ፍልስጤማዊ አካላት ጋር በትብብር እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
አል-ሐያ በጋዛ ሰርጥ የሚፈሰውን ደም ለማስቆም እና ለተኩስ አቁም ድርድር ጥረት እያደረጉ ያሉትን እንደ ግብፅ፣ ኳታር እና ቱርክ ያሉ አካላትን አመስግነዋል። ሆኖም አስታራቂ አገራቱ እስራኤል ከዚህ ቀደም የተስማማችባቸውን ነጥቦች በተግባር እንድትተገብር እውነተኛ ጫና ያደርጉ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
አዲስዓለም አበበ
ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም | 1 569 |
| 15 | ሄዝቦላህን ማስፈታት የሚቻለው እስራኤል ከደቡብ ሊባኖስ ሙሉ በሙሉ ከወጣች በኋላ ነው ሲሉ የሊባኖሱ ፕሬዚዳንት ጆሴፍ አውን ተናገሩ
ፕሬዝዳንት ጆሴፍ አውን በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ በሊባኖስ አምባሳደር ናዳ ሐማዴህ ሞዋድ ለእርሳቸውና ለልዑካናቸው በተዘጋጀ እራት ግብዣ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ የሄዝቦላህ ትጥቅ መፍታት እስራኤል ከደቡብ ሊባኖስ ሙሉ በሙሉ ስትወጣ ብቻ እውን ሊሆን እንደሚችል ገልጸዋል።
ፕሬዝዳንቱ የሊባኖስ ልዩ ብሔራዊ አብሮነት ለሊባኖስ ብቻ ሳይሆን ለመላው ክልል ጥበቃ እንደሚያስፈልገው ጠቅሰው፤ይህም አሜሪካ የተመሠረተችበትን መሠረታዊ እሴቶች የሚጋራ መሆኑን አመልክተዋል።
አውን እንዳሉት፤ እስራኤል ወረራዋን ማቆም፣ የሊባኖስ ጦር መላ አገሪቱን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር እና የመልሶ ግንባታ ሥራዎች በመንግሥት ብቻ መመራት ከተሳካ፣ የሄዝቦላህ ትጥቅ መፍታት በተግባር ሊሳካ ይችላል ብለዋል።
ይህ አስተያየት በሊባኖስ የጸጥታና የፖለቲካ ሁኔታ ዙሪያ የሚካሄዱ ውይይቶች በቀጠሉበት ወቅት የተሰጠ መሆኑ ተጠቁሟል።
ትዕግስት ግርማ
ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም | 1 524 |
| 16 | በቬኔዙዌላ የመሬት መንቀጥቀጥ የሟቾች ቁጥር ከ5 ሺህ በላይ መድረሱ ተዘገበ
ባለፈው ወር በደረሰው አደጋ 16 ሺህ7መቶ40 ሰዎች መቁሰላቸውን የብሔራዊ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ገልጸዋል።
ባለፈው ወር በቬኔዙዌላ በተከሰቱት ተከታታይ የመሬት መንቀጥቀጦች የሟቾች ቁጥር 5 ሺህ3መቶ46 መድረሱን ተገልጿል።
ባለስልጣናት ለ1መቶ28 ሺህ3መቶ24 ቤተሰቦች ድጋፍ ማድረጋቸውን እና 21 ሺህ2መቶ35 ሰዎችን የሚይዙ 1መቶ7 ጊዜያዊ መጠለያ ካምፖችን ማቋቋማቸውን የገለጹ ሲሆን፣ 17 ሺህ9መቶ7 ሰዎች ደግሞ አሁንም ቋሚ መኖሪያ ቤት እንደሌላቸው አስታውቀዋል።
የመሬት መንቀጥቀጡ 8መቶ56 ህንፃዎች ላይ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን፣ ከእነዚህም ውስጥ 1መቶ90ዎቹ ሙሉ በሙሉ ፈርሰዋል።
በሬክተር ስኬል 7.2 እና 7.5 የተመዘገቡት ሁለቱ የመሬት መንቀጥቀጦች፣ የደቡብ አሜሪካዊቷን ሀገር የመቷት ሰኔ 24 ነበር።
እስከዳር ግርማ
ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም | 1 556 |
| 17 | ዩክሬን ባለፉት 48 ሰዓታት ውስጥ 13 የሩሲያ የባህር መርከቦችን መምታቷ ተገለፀ
ጥቃቱ የተፈጸመው ለቀናት የዘለቀውን ተቃውሞ ተከትሎ አዲስ የጦር አዛዥ ከተሾመ በኋላ ነው።
የዩክሬን ሰው አልባ ሲስተምስ ጦር አዛዥ ሮበርት ብሮቭዲ እንደተናገሩት፥የዩክሬን ድሮኖች ባለፉት 48 ሰዓታት ውስጥ በጥቁር ባህር እና በአዞቭ ባህር ላይ 13 የሩሲያ መርከቦችን መምታታቸውን ገልጸዋል።
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር በበኩሉ በኦዴሳ ክልል በሚገኙ የዩክሬን ወደቦች እና ወታደራዊ መሰረተ ልማቶች ላይ ጥቃት መሰንዘሩን አስታውቋል።
ሞስኮ በጥቃቱ ምክንያት ሁለት የባህር ኃይል መርከቦች እንዲሁም ወታደራዊ ጭነቶችን ለማውረድ እና ለማከማቸት የሚያገለግሉ የወደብ መሰረተ ልማቶች፣ የነዳጅ እና ቅባት ማከማቻ ታንኮች መመታታቸውን ተናግራለች።
ቅዳሜ ዕለት በዩክሬን ድሮኖች የተፈጸመው የቀድሞ ጥቃት ስምንት ሠራተኞችን የገደለ፣ የእሳት አደጋ ያስከተለ እና የዋይልድቤሪስን ሥራዎች ያስተጓጎለ ነበር ሲል ቲአርቲ ወርልድ ዘግቧል።
ሳራ ዮሐንስ
ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም | 1 474 |
| 18 | ነዳጅን በኮንትሮባንድ መንገድ ይዘናል በሚል ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ነዳጅ እና ተሽከርካሪዎችን መዉረስ አግባብነት የለዉም ሲሉ የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች ገለፁ
የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን በበኩሉ የታሸገ ነዳጅ እሽጉ ሳይፈታ ለተጠቃሚው እንዲደርስ ማድረግ የሕግ ግዴታ ሲሆን፣ በነዳጅ ላይ የሚፈጸም ቅሸባ በኢትዮጵያ የነዳጅ ንግድና ስርጭት ሕግ መሠረት ከባድ ወንጀል ተብሎ ሊቀጣ ይገባል ይላል።
በዚህ አመት ግንቦት ወር ጀምሮ እስከ ሰኔ መጨረሻ ባለዉ ጊዜ የአምስት ተሽከርካሪዎች መወረሱን ሪፖርት እንደተደረገለት የኢትዮጵያ የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች ማህበር አሳዉቋል።
የኢትዮጵያ የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች ሌብነት እያበረታታን አይደለም፤ ሆኖም በሀገሪቱ አንዳንድ ክልሎች ባሉ የመንግስት አካላት የነዳጅ ቅሸባ ሲደረግ ተገኝቷል እየተባለ የተጫነው ነዳጅ ኮንትሮባንድ ነዉ በሚል እየተወረሰ መሆኑ ሰርተን የማንከፍለዉ እዳ ዉስጥ ከቶናል ብለዋል።
ባለንብረቶች በህጋዊ መንገድ ቀረጥ ተከፍሎ እየገባ ያለ ነዳጅ ኮንትሮባንድ የሚሆንበት አግባብ በሌለበት ህጋዊ መሠረትን ሳይጠብቁ መዉረስ አይገባም ይላሉ።
ኢትዩ ኤፍም በጉዳዩ ዙሪያ ባለንብረቶችን አነጋግሯል።
አቶ የማነ ፀጋዬ የተባሉ ባለንብረት ከሶስት ወር በፊት አዋሽ አርባ አካባቢ ነዳጅ ጭኖ ቢጓዝ የነበረን ተሽከርካሪ አሽከርካሪዉ ነዳጅ ሲቀሽብ ተገኝቷል በማለት ነዳጁን ሰመራ ላይ በማራገፍ ነዳጁን ከነተሽከርካሪዉ እንደተወረሰ ያለምንም የፍርድ ቤት ዉሳኔ በደብዳቤ እንደተገለጸላቸው ተናግረዋል።
ባለንብረቱ አሁን ላይ ባለእዳ የሆኑበትን ክፍያ ለመክፈል የእርዳታ እና ድጋፍ ማሰባሰቢያ እየጠየቁ እንደሚገኝ የተመለከትን ሲሆን የኢትዮጵያ የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች ማህበር ጉዳዩን ከክልሉ እስከ ነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን በመዉሰድ ለማነጋገር ሙከራ ተደርጓል ተብሏል።
አቶ ጌትነት ማህመድ የኢትዩጵያ ፈሳሽ ጭነት ማህበር ምክትል ኘሬዝዳንት የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን እና ንግድ እና ቀጠናዊ ትስስርን ለማነጋገር እንደተሞከረ ነግረዉናል።
ለዚህ ምን ምላሽ እንደተሰጠ ሲገልፁም" ነዳጅ እጥረት በተፈጠረ ሰሞን የተቋቋመዉ ኮማድፖስት ዉረሱ ብሏቸዋል ፤ ምን ማድረግ አንችልም ሲሉ ምላሽ ሰጥተዉናል" ብለዋል።
ሌላኛዉ ባለንብረት አቶ ዳኛቸዉ አበበ ይባላሉ። ተሽከርካሪዎች እየተወረሱ እንደሚገኙ በመግለፅ አሽከርካሪዎች አጥፍተዉ ሲገኙ በጥፋት እነሱን መጠየቅ ሲገባ ለሀገር ጥቅም ሊዉል የተጫነን ነዳጅ እና ተሽከርካሪ መዉረስ ለወረሹ አካል ሌብነትን ማበረታታት ነዉ ይላሉ።
ሲቀሽብ ተያዘ የተባለዉን አሽከርካሪ በነፃ ለቆ ተሽከርካሪ መዉረስ ነገም ለተመሳሳይ ጥፋት አሽከርካሪን መጋበዝ እና ባለንብረትን ባለእዳ መድረግ ነዉ ብለዉናል።
ለኢትዩ ኤፌም ሀሳባቸዉ የሰጡት ሌላኛዉ ግለሰብ አቶ ዘላለም ነጋሲ ናቸዉ። ነዳጅን ኮንትሮባንድ ነዉ በሚል መያዝ ህጋዊ አይደለም ይላሉ። ይህንንም ሲያስረዱ "ነዳጅን መንግስት ሁሉን ነገር ከፍሎ እስከ ጅቡቲ ድረስ ያመጣዉ ነዉ። ይሄን ቀሽቦ የተገኘ አሽከርካሪ በእምነት ማጉደል ወንጀል መጠየቅ ሲገባ ኮንትሮባንድ ነዳጅ በሚል ተሽከርካሪ ከነነዳጁ መዉረስ ኮንትሮባንድ ወንጀል የሚለዉ መረዳት እንዳልቻሉ ያሳያል" ብለዋል
ሲቀጥሉም"ነዳጅን ኮንትሮባንድ ማለት ምን ማለት ነዉ? የጉምሩክ ኮምሽን በየክልሉ ሀላፊነት ለሰጣቸው አስፈጻሚዎች በቂ ግንዛቤ መስጠት ይገባዋል። ያለፍርድ ቤት ትእዛዝ ወይም በአንድ መስሪያ ቤት ሀላፊ ትእዛዝ ንብረት መዉረስ ህገመንግስቱ የሰጠዉን መብትን መጣስ ነዉ" ሲሉም አክለዋል።
የኢትዮጵያ የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች ማህበር ዋና ኘሬዝደንት አቶ ፀጋ አሳመረ በጉዳዩ ዙሪያ በሰጡን ማብራሪያ ሌብነት እና ኮንትሮባንድ መለየት እንደሚያስፈልግ ይገልፃሉ።
ቀረጥ የተቀረጠበትን ነዳጅ ሲቀሸብ ተገኝቷል በሚል ኮንትሮባንድ ብሎ መዉረስ አግባብ አይደለም በሚል ለሚመለከተዉ አካል እስከ ጠቅላይ ሚኒስቴር በደብዳቤ አሳዉቀናል ብለዋል።
"አንዳንድ ጊዜም ተሽከርካሪዎቹ አንድ ሺህ ሊትር ቀድተዉ ከሆነ ግማሹ ተሳቢዉ ላይ ነዉ የሚደረገዉ። ከዛ ከተሳቢዉ ላይ ወደ መኪናው ሲገለብጡ ነዉ የሚይዟቸዉ ይሄ አይነቱ አሰራር ያለ ነዉ ። ይሄን እነሱ ቅሸባ ነዉ የሚሉ እንደዋዛ ሊባል አይችልም"ሲሉም አስረድተዋል።
በሌላ በኩል በነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን የነዳጅ አቅርቦት እና ስርጭት መሪ ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ መሠለች ወዳጆ የታሸገ ነዳጅ እሽጉ ሳይፈታ እንዲደርስ ይፈልጋል ይላሉ ። ቅሸባዉ ወንጀል ነዉ መባል ያለበት ሲሉ ይገልፃሉ።
የታሸገ ነዳጅ እሽጉ ሳይፈታ ለተጠቃሚው እንዲደርስ ማድረግ የሕግ ግዴታ ሲሆን፣ በነዳጅ ላይ የሚፈጸም ቅሸባ በኢትዮጵያ የነዳጅ ንግድና ስርጭት ሕግ መሠረት ከባድ ወንጀል ተብሎ ሊቀጣ ይገባል። በነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን የነዳጅ አቅርቦት እና ስርጭት መሪ ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ መሠለች ወዳጆ እንደገለፁት፣ የነዳጅ እሽግ ሳይፈታ ለተጠቃሚው መድረስ አለበት።
ባለሥልጣኑ በድንገተኛ ፍተሻ በመቅጃ ማሽኖች (ዲስፔንሰር) ላይ ትክክለኛ ያልሆነ ልኬትና ቅሸባ በፈጸሙ የነዳጅ ማደያዎች ላይ የማገጃ እርምጃዎችን የነዳጅ አቅርቦት፣ ስርጭትና ግብይት ወጥነትን ለመፍታት እና ቅሸባን ለመከላከል በዲጂታልና በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር እየተዘረጋ ይገኛል ብሏል።
ቁምነገር አየለ
ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም | 1 161 |
| 19 | Нет текста... | 1 055 |
| 20 | አሜሪካ በኢራን ላይ የምታካሂደውን ጥቃት አጠናክራ ቀጥላለች
አሜሪካ ለ11ኛ ተከታታይ ምሽት በኢራን ላይ የአየር ጥቃት የሰነዘረች ሲሆን፥ቴህራን በበኩሏ ዋሽንግተን በኑክሌር ተቋማቷ ላይ ከሚሰነዘር ጥቃት እንድትቆጠብ አጥብቃ አስጠንቅቃለች።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ እንደገለጸው፥የተሰነዘረው የጥቃት ማዕበል “ኢራን በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ በሚያልፉ የንግድ መርከቦች ላይ የምታደርሰውን ዛቻ የመቀነስ” አላማ ያለው ነው።
የኢራን መንግስት መገናኛ ብዙሃን በዋና ከተማዋ ቴህራን የአየር መከላከያ ስርአቶች መስራታቸውን ዘግበዋል።
በተጨማሪም በታብሪዝ፣ ቻባሃር፣ ኮናራክ እና የሀገሪቱ ብቸኛ የኑክሌር ሀይል ማመንጫ በሚገኝበት ቡሼህር ከተሞች የፍንዳታ ድምፆች ተሰምተዋል።
ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ በናታንዝ አቅራቢያ የሚገኘውን የመሬት ውስጥ የኑክሌር ተቋም በቅርቡ እንደምትመታ ከተናገሩ በኋላ፤ የበቀል እርምጃ እንደምትወስድ ያስጠነቀቀችው ኢራን በአሜሪካ እና በመካከለኛው ምስራቅ ወዳጆቿ ላይ አጸፋዊ ጥቃት እንደምትሰነዝር ገልጻለች።
ሀና ሰይፉ
ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም | 1 208 |
