Ethio Fm 107.8
በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!
Mostrar más📈 Análisis del canal de Telegram Ethio Fm 107.8
El canal Ethio Fm 107.8 (@ethiofm107dot8) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 18 514 suscriptores, ocupando la posición 12 210 en la categoría Noticias y medios y el puesto 1 822 en la región Etiopía.
📊 Métricas de audiencia y dinámica
Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 18 514 suscriptores.
Según los últimos datos del 17 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -75, y en las últimas 24 horas de -13, conservando un alto alcance.
- Estado de verificación: No verificado
- Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 8.94%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 7.07% de reacciones respecto al total de suscriptores.
- Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 1 656 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 309 visualizaciones.
- Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 4.
📝 Descripción y política de contenido
El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!”
Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 18 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Noticias y medios.
Carga de datos en curso...
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 17 julio | 0 | |||
| 16 julio | +1 | |||
| 15 julio | +2 | |||
| 14 julio | +3 | |||
| 13 julio | +5 | |||
| 12 julio | +1 | |||
| 11 julio | 0 | |||
| 10 julio | +11 | |||
| 09 julio | +2 | |||
| 08 julio | +1 | |||
| 07 julio | 0 | |||
| 06 julio | +2 | |||
| 05 julio | 0 | |||
| 04 julio | +15 | |||
| 03 julio | 0 | |||
| 02 julio | +3 | |||
| 01 julio | 0 |
| 2 | https://www.youtube.com/watch?v=ZRG6yrhl1zs | 1 315 |
| 3 | የአሜሪካ ጥቃት ሰባት ሰዎችን መግደሉን ኢራን ገለጸች
አሜሪካ ለስድስተኛ ተከታታይ ምሽት በኢራን ላይ ጥቃት ማድረሷን ተከትሎ ቴህራን በርካታ ሰዎች መሞታቸውን የዘገበች ሲሆን፥ ጥቃቱ የሀገሪቱ ደቡባዊ ክፍል የመሠረተ ልማት አውታሮች ላይ ያነጣጠረ ነበር ተብሏል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ እዝ ጥቃቱ «የኢራንን ወታደራዊ አቅም ለማዳከም» የተደረገ ጥረት ነዉ ብሏል፡፡
እነዚህ ጥቃቶች ሁለቱ ሀገራት ባለፈው ወር የተፈራረሙት ጊዜያዊ ስምምነት አደጋ ላይ መውደቁን ያሳያሉ።
የአሜሪካ ወታደራዊ ክፍል በኦማን ባሕረ ሰላጤ ላይ የእገዳ ጥሰት የሞከሩ ሶስት የንግድ መርከቦችን አቅጣጫ ማስቀየሩን እና አንዷን መርከብ ከጥቅም ውጭ ማድረጉን አስታውቋል።
በሌላ በኩል እንደ ኳታር፣ ዮርዳኖስ እና ባህሬን ያሉ የባሕረ ሰላጤው ሀገራት የመሠረተ ልማት ጥበቃቸውን እና ወታደራዊ ዝግጁነታቸውን እያጠናከሩ ነው።
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ጦር በአህቫዝ ከተማ ለሚገኝ የሕፃናት ካንሰር ሆስፒታል መፈናቀል ምላሽ ለመስጠት በባህሬን በሚገኝ የአሜሪካ አየር ኃይል ጣቢያ ላይ ጥቃት መፈጸሙን አስታውቋል።
የኢራን ጦር ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄኔራል መሐመድ አክራሚኒያ የአሜሪካ ጥቃቶች ከቀጠሉ የኢራን እርምጃ «ወደ አዳዲስ አካባቢዎች እንደሚስፋፋ» አስጠንቅቀዋል።
አሜሪካ ኢራን ወደ ድርድሩ እንድትመለስ ስትፈልግ፥ ኢራን ደግሞ አሜሪካ መጀመሪያ እገዳውን እንድታነሳ ትፈልጋለች።
የዋይት ሀውስ ፕሬስ ሴክሬተሪ ካሮሊን ሌቪት፤ ትራምፕ ኢራንን ተጠያቂ እንደሚያደርጉ ነገር ግን ሁልጊዜ ለዲፕሎማሲ ክፍት መሆናቸውን ገልጸው፥ መርከቦች ላይ የሚሰነዘር ጥቃትን ግን እንደማይፈቅዱ ተናግረዋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ግን በአሁኑ ወቅት ከዋሽንግተን ጋር ለመነጋገር ምንም ዓይነት እቅድ እንደሌለውና ትኩረቱ ሀገሪቱን መከላከል ላይ ብቻ መሆኑን አስታውቋል።
ሳራ ዮሐንስ
ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም | 1 407 |
| 4 | Sin texto... | 1 111 |
| 5 | አዲስ አስመጪዎችና ላኪዎች የብሔራዊ ባንክ የሂሳብ ቁጥርን በአንድ መስኮት አገልግሎት እንዲያገኙ ፍቃድ ተሰጠ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አዲስ አስመጪዎችና ላኪዎች የብሔራዊ ባንክ የሂሳብ ቁጥርን በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የአንድ መስኮት አገልግሎት በኩል እንዲያገኙ ፍቃድ ሰጥቷል፡፡
ባንኩ ከኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ጋር በመተባበር አዲስ ፍቃድ ላወጡ አስመጪዎችና ላኪዎች የብሔራዊ ባንክ የሂሳብ ቁጥር አሰጣጥን የሚያቀል አዲስ የዲጂታል አገልግሎት አስተዋውቋል፡፡
አገልግሎቱ የባንኩ የሂሳብ ቁጥሮች በጉምሩክ ኮሚሽን አንድ መስኮት አገልግሎት በኩል ያለምንም ውጣ ውረድ እንዲሰጥ በማስቻል አስተዳደራዊ ሂደቶችን የሚቀንስና ፈጣን የንግድ አሰራርን የሚደግፍ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
አዲሱ አገልግሎት የሚመለከተው ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሂሳብ ቁጥር ለሚያወጡና አዲስ ፍቃድ ላገኙ አስመጪዎችና ላኪዎች ብቻ መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡
ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሂሳብ ቁጥር ያላቸው የንግድ ተቋማት ለሁሉም የገቢና የወጪንግድ ግብይቶቻቸው ይጠቀሙበት በነበረው ነባር ቁጥር መጠቀም እንደሚችሉ ባንኩ ገልጿል፡፡
ይህ አሰራር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከገቢና ወጪ ንግድ ጋር የተያያዙ አገልግሎቶችን ለማዘመን፣ የንግድ አሰራርን ምቹ ለማድረግ እንዲሁም የዲጂታል የሕዝብ አገልግሎት አሰጣጥን ለማጠናከር እያከናወነ ያለው ጥረት አካል መሆኑንም አመልክቷል፡፡
ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም | 1 126 |
| 6 | ቻይና በትራምፕ የምርጫ ጣልቃገብነት አስተያየት ላይ ያላትን ተቃውሞ ገለጸች
ቻይና የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ያቀረቡትን የምርጫ ጣልቃገብነት ክስ ውድቅ ማድረጓን ገልፃ ክሶቹንም መሰረተ ቢስ ናቸው ብላለች፡፡
ቤጂንግ ዋሽንግተን በዚህ አመት ከሚካሄደው የአሜሪካ የአጋማሽ ዘመን ምርጫ በፊት በቻይና ላይ የስም ማጥፋት ዘመቻ ለማካሄድ እየሞከረች ነው ስትል ከሳለች።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ሊን ጂያን እንደተናገሩት፥ የትራምፕ ክሶች ‹‹ምንም ዓይነት›› እውነተኛ መረጃ የሌላቸው እና ቻይናን ለማጠልሸት የታለሙ ናቸው።
በሌላ በኩል ትራምፕ ቻይና ከ2020 የምርጫ ዑደት ጀምሮ የ2መቶ20 ሚሊዮን አሜሪካውያን መራጮችን ፋይል ማግኘቷን ገልጸው ድርጊቱን "በታሪክ ውስጥ ትልቁ የምርጫ መረጃ ጥሰት" በማለት ገልጸውታል።
ቃል አቀባዩ አሜሪካን በዓለም አቀፍ ደረጃ ሰፊ ስለላ በማካሄድ እና በውጭ ሀገራት ጉዳይ ውስጥ ጣልቃ በመግባት ከሰዋል።
ትራምፕ በበኩላቸዉ የሲአይኤን ሪፖርት በመጥቀስ የቻይና አመራር በመጀመሪያው የስልጣን ዘመናቸው ወቅት ከ2020 ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በፊት የእርሳቸውን የድል እድል ለማዳከም መፈለጉን ጠቁመዋል።
ይህ የእርስ በርስ ውንጀላ የመጣው አሜሪካውያን ለአጋማሽ ዘመን ምርጫ ወደ ምርጫ ጣቢያ ከማምራታቸው ጥቂት ወራት ቀደም ብሎ ሲሆን፤ በአሜሪካ እና በቻይና መካከል ያለው ውጥረት በንግድ፣ በቴክኖሎጂ እና በብሔራዊ ደህንነት ዙሪያ አሁንም እንደበረታ ነው።
ሀና ሰይፉ
ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም | 1 026 |
| 7 | ከ4መቶ40 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ
የጉምሩክ ኮሚሽን ከሀምሌ 1 እስከ ሀምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረገው ክትትል 4መቶ29.7 ሚሊየን ብር የገቢ የኮንትሮባንድ እቃዎች እና 11.2 ሚሊየን ብር የወጭ፤ በድምሩ 4መቶ40.9 ሚሊየን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች በተለያዩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ተይዘዋል ብሏል፡፡
በቁጥጥር ስር ከዋሉት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል አዳዲስ እና ልባሽ ጨርቆች፣ ቡና፣ ኤሌክትሮኒክስ፣የግንባታ እቃዎች፣ ጥራጥሬ፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ፣ የመዋቢያ እቃዎች፣ ጫት፣ አደንዛዥ እጾች፣ መድኃኒት፣ ማዕድናት እና የውጭ ሀገር ገንዘቦች ይገኙበታል፡፡
በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ የገቢ እና የወጭ ኮንትሮባንድን በመቆጣጠር አዲስ አበባ ኤርፖርት፣ ጅግጅጋ እና አዋሽ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ቀዳሚውን ስፍራ ሲይዙ፤ በቅደም ተከተላቸውም 1መቶ18 ሚሊየን፣1መቶ11 ሚሊየን እና 82 ሚሊየን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎችን መያዝ ችለዋል፡፡
የኮንትሮባንድ እቃዎቹን ሲያዘዋውሩ የተገኙ 28 ተጠርጣሪዎች እና 15 ተሽከርካሪዎችም በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም | 1 249 |
| 8 | የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ከወጭ ንግድ ገቢ ከ2መቶ 60 ሚሊየን ዶላር በላይ መገኘቱን ገለጸ
ኮርፖሬሽኑ በ2018 በጀት ዓመት 2መቶ66.9 ሚሊየን ዶላር መገኘቱን አስታዉቋል
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በሚያስተዳድራቸው ልዩ ኢኮኖሚ ዞኖችና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ በሚንቀሳቀሱ ባለሀብቶች ተመርተው ወደ ውጭ አገራት ከተላኩ ምርቶች በ2018 በጀት ዓመት 2መቶ66.9 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ መገኘቱን አስታውቋል።
የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ፍሰሃ ይታገሱ እንደገለጹት፤በበጀት ዓመቱ የተገኘው የውጭ ምንዛሬ ገቢ ተቋሙ ከተቋቋመ ወዲህ የተመዘገበው ከፍተኛው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸሙን በሀዋሳ ከተማ በመገምገም ላይ ይገኛል።
ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም | 1 300 |
| 9 | በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ታ
የሥራ ዕድል ፈጠራና የትስስር መድረክ ተካሄደ
በቅርቡ የመቶኛ ዓመት መቶኛውን ያከበረውና ዓለም አቀፉን የ ISO 21001 የጥራት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ያገኘው አንጋፋው ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ፣ ለሰልጣኞቹ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ያለመ ታላቅ የአውደ ርዕይና የሥራ ትስስር (Job Fair) መድረክ አዘጋጀ።
በዕለቱ የሥራ ትስስር መድረኩን በይፋ የከፈቱት የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ዳግማዊት ግርማ ሲሆኑ ፣ የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ፣ ከተለያዩ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የመጡ አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም ከ30 በላይ ቀጣሪ ድርጅቶች በፕሮግራሙ ላይ ታድመዋል።
ይህ መድረክ ተመራቂ ሰልጣኞችን በቀጥታ ከቀጣሪ አካላት ጋር ለማገናኘት ታስቦ የተዘጋጀ ሲሆን፣ ሰልጣኞቹ የክህሎት ልውውጥ ከማድረጋቸውም በላይ በሆቴል፣ በኮምፒውተር ቴክኖሎጂ (ICT)፣ በፋይናንስ፣ በኤሌክትሪክ፣ በእንጨትና ብረታብረት ሥራ፣ በአረንጓዴ ቴክኖሎጂ፣ በጋርመንትና በሌሎችም የፈጠራ መስኮች ላይ ከተሰማሩ ተቋማት ጋር የሥራ ትስስር እንዲፈጥሩ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩ ተገልጿል።
የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ እንዲህ ያሉ የሥራ ትስስር መድረኮች ሰልጣኞች በቀጥታ ወደ ሥራ ዓለም እንዲገቡ ትልቅ እገዛ እያደረጉ መሆኑን ጠቅሰው፣ በዕለቱ በተፈጠረው ግንኙነት በርካታ ሰልጣኞች የሥራ ዕድል ማግኘታቸውን አብስረዋል። ዲኑ አክለውም መድረኩ ስኬታማ እንዲሆን ላገዙ አካላት በሙሉ፣ በተለይም ለኢዝ (EASE) ፕሮጀክት ልዩ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፣ በቀጣይም መሰል የሥራ ትስስር መድረኮች በቋሚነትና በሰፊው መዘጋጀታቸውን እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
ሐምሌ 09/2018 ዓ.ም | 1 644 |
| 10 | Sin texto... | 1 481 |
| 11 | ቻይና አሜሪካን በመብለጥ የኢትዮጵያ ቡና ሦስተኛዋ ግዙፍ ገዥ ሆነች - የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን
በተጠናቀቀው የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ኢትዮጵያ 47,836 ቶን ቡና ወደ ቻይና በመላክ፤ 347 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ገቢ አግኝታለች።
ይህም በቀደመው በጀት ዓመት ወደ እስያዊቷ ሀገር ከተላከው 34,284 ቶን ቡና እና ከተገኘው 219 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ጭማሪ አሳይቷል።
ሳዑዲ አረቢያ እና ጀርመን በ2018 ዓ.ም ቀዳሚ እና ሁለተኛ የኢትዮጵያ ቡና መዳረሻዎች ናቸው።
“ሀገሪቱ በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ትልቋ የኢትዮጵያ ቡና ገዥ ትሆናለች ብለን ተስፋ እናደርጋለን” ሲሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሻፊ ኡመር ተናግረዋል።
እንደ ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ገለጻ፤ የዕድገቱ ምክንያቶች፦ ተፈጥሯዊ (ኦርጋኒክ) የቡና ፣የተሻሻሉ የመላኪያ አገልግሎቶች፣ እያደገ የመጣው የሁለቱ ሀገራት የንግድ እና የዲፕሎማሲ ግንኙነት ናቸው።
“ጠንካራ የማስተዋወቅ ሥራዎችን በመሥራት እና የቻይናውያን ተጠቃሚዎችን በተለይም እያደገ የመጣውን የወጣቶች ፍላጎት ለማሟላት ኦርጋኒክ ቡና በመላክ በቻይና ያለውን ሰፊ የገበያ ዕድል ለመጠቀም እየጣርን ነው” ሲሉም አክለዋል።
ሐምሌ 09/2018 ዓ.ም | 1 562 |
| 12 | ያንጎ ራይድ በአሽከርካሪዎች እና በተሳፋሪዎች መካከል መተማመንን ለማሳደግ “የተሟላ መለያ” (Passenger Profile Badge) የተባለ አዲስ የደህንነት አገልግሎት በአዲስ አበባ አስተዋወቀ።
ተሳፋሪዎች ስም፣ ፎቶ እና ግላዊ መረጃቸውን በመሙላት “የተሟላ መለያ” ምልክት እንደሚያገኙ ተገልጿል።
አሽከርካሪዎችም የጉዞ ጥያቄ በሚደርሳቸው ጊዜ ይህንን ምልክት በቀጥታ መመልከት ይችላሉ ተብሏል።
በተለይ በሌሊትና ባልተለመዱ አካባቢዎች የሚፈጠርን ጥርጣሬ ያስወግዳል።
ተቋሞ በላከልን መረጃ በቅድመ ዳሰሳ ጥናት መሠረት፣ ይህ ምልክት ካላቸው ተሳፋሪዎች የሚላኩ የጉዞ ጥያቄዎችን አሽከርካሪዎች የመቀበል ፍላጎት በ40% ጨምሯል።
ይህ አዲስ አሠራር ያንጎ ከሚያቀርባቸው ከ25 በላይ የውስጥ መተግበሪያ የደህንነት አማራጮች (እንደ SOS፣ የጉዞ መስመር መከታተያ እና ሌሎች) መካከል አንዱ ነው።
የያንጎ የኢትዮጵያ ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር የቀናዓለም አበበ አዲሱ አሰራር በሁለቱ ወገኖች መካከል አስተማማኝና ግልጽ የጉዞ ልምድ ለመፍጠር ትልቅ እገዛ እንዳለው ገልጸዋል።
ሐምሌ 09/2018 ዓ.ም | 1 369 |
| 13 | የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በጎንደር ጉብኝት አደረጎ
የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ የንግድ ዲፕሎማሲን ለማሳደግ፣ የሰላምና መረጋጋትን አስፈላጊነት ለማጉላት እንዲሁም የሰብአዊና የጤና ድጋፎችን ውጤታማነት ለመገምገም በጎንደር ጉብኝት አድርገዋል።
ኢምባሲው በላከልን መግለጫ አምባሳደሩ ከአካባቢውና ከክልሉ ባለስልጣናት ጋር ባደረጉት ውይይት፣ በአሜሪካና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን የንግድ ግንኙነት ለማስፋፋት መረጋጋት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
የጎንደርን የቱሪዝም አቅም ለማሳየትም በዩኔስኮ የተመዘገበውን የፋሲል ግቢን ጎብኝተዋል።
ከጎንንደር ዩኒቨርሲቲ ጋር ያለውን የ70 ዓመታት አጋርነትም የተከበረ ሲሆን፣ በዩኒቨርሲቲው ሆስፒታል በመገኘት በአሜሪካ ድጋፍ የሚከናወኑ የቲቢ መከላከያ መርሃ ግብሮችን ጎብኝተዋል።
ይህ ድጋፍ በታህሳስ 2025 በተፈረመው የ1.466 ቢሊዮን ዶላር የጤና ስምምነት አካል ነው።
በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ የሰብአዊ ረዳት ድርጅቶች ጋር በመወያየት፣ አሜሪካ ፈጣንና ተጠያቂነት ያለው ሰብአዊ ምላሽ ለመስጠት ያላትን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።
ሐምሌ 09/2018 ዓ.ም | 1 324 |
| 14 | በአዲስ አበባ በትምህርት ቤቶች አካባቢ የትራፊክ አደጋ ወደ ‘ዜሮ’ መውረዱና ከ60 ሺህ በላይ እግረኞችም መቀጣታቸው ተነገረ
በአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቤቶች አካባቢ በተሰራ የተቀናጀ የቁጥጥርና የደህንነት ስራ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ምንም ዓይነት የትራፊክ አደጋ አለመመዝገቡን የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን አስታወቀዋል ።
በሌላ በኩል ደንብ በተላለፉ ከ60 ሺህ በላይ እግረኞች ላይ አስተማሪ እርምጃ መወሰዱ ታውቋል።
የባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር ወይዘሮ ገነት ዲባባ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደገለጹት፤ በትምህርት ቤቶች አካባቢ የትራፊክ ደህንነትን ለማረጋገጥ በተሰራው ስራ ከ110 ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ 1 ሺህ 100 ተማሪዎች የትራፊክ ማስተናገድ ስልጠና ወስደው በትምህርት ማህበረሰቡ ላይ የደህንነት ስራዎችን ሲያከናውኑ ቆይተዋል።
ይህ ስራ በትምህርት ቤቶች አካባቢ ይከሰት የነበረውን አደጋ ሙሉ በሙሉ በመከላከል ረገድ ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገቡን ገልጸዋል።
በተያያዘ መረጃ በከተማዋ የትራፊክ ፍሰትን ለማሳለጥና ደህንነትን ለመጠበቅ በተደረገ ቁጥጥር፤ በእግረኞች ደንብ ቁጥር 557/2016 መሠረት ከ60 ሺህ በላይ እግረኞች ደንብ በመተላለፋቸው ተቀጥተዋል።
ከነዚህም መካከል ግማሽ ያህሉ በገንዘብ ሲቀጡ፣ ከ27 ሺህ በላይ የሚሆኑት ደግሞ በማህበራዊ አገልግሎት እንዲቀጡ ተደርጓል።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ተደራሽ ያደረጋቸው የመንገድ ደህንነት የግንዛቤ ስራዎች ቁጥር 20 ሚሊዮን ለሚደርሱ የመንገድ ተጠቃሚዎች መድረሱንም አስታውቋል።
ባለስልጣኑ በቀጣይም የክረምቱን ወራት ጨምሮ የትራፊክ አደጋን ለመቀነስና የከተማዋን የትራፊክ ፍሰት ይበልጥ ሰላማዊ ለማድረግ ቁጥጥሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
ልዑል ወልዴ
ሐምሌ 09/2018 ዓ.ም | 1 276 |
| 15 | Sin texto... | 1 275 |
| 16 | ባማኮን ሪልስቴት ያስገነባቸውን አፓርታማዎች ለባለቤቶቻቸው አስረከበ
ባማኮን ሪልስቴት በቦሌ ያስገነባቸውን ዘመናዊ አፓርታማዎች ለባለቤቶቻቸው አስረክቧል።
በግንባታው ዘርፍ ከ20 ዓመታት በላይ ተሻግሯል የተባለው ኩባንያው ያስረከባቸው እነዚህ አፓርታማዎች ከቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ፊት ለፊት የሚገኙ ሲሆን፥በተለይም ለአገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ ተጓዦች ተመራጭ መኖሪያዎች ናቸው ተብሏል።
ቤቶቹ በተመጣጣኝ ዋጋ ከመቅረባቸውም በላይ ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቁ በመሆናቸው ባለቤቶቹ በራሳቸው መኖር አሊያም በቀጥታ አከራይተው ከፍተኛ ገቢ ማግኘት የሚችሉባቸው እንደሆኑ ተጠቅሷል።
ባማኮን ሪልስቴት ግንባታዎቹን በታቀደላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ በራሱ በባማኮን ግሩፕ ሥር ካሉ እህት ኩባንያዎች ጋር በጥምረት እንደሚሰራ ገልጿል።
ከዚ ቀደም በካዛንችስ ፣ ባምቢስ አትላስ፣ፍሬንድሺፕ ፓርክ፣ቦሌ ኤርፖርት ቪው ፣በሜክሲኮ እና ቡልቡላ ሳይቶች ላይ የመኖሪያና የንግድ ቤቶች ግንባታዎችን አጠናቆ ለደንበኞች ማስረከቡ ተገልጿል።
ሀና ሰይፉ
ሐምሌ 09/2018 ዓ.ም | 1 496 |
| 17 | መንግሥት ለኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዘመናዊነትና ለምርምር ሥራዎች ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥ ፕሬዝዳንት ታየ ገለጹ
የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታየ አፅቀስላሴ የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በቀጣዩ መቶ ዓመት ውጤታማና ተወዳዳሪ ሆኖ እንዲቀጥል መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልፀዋል።
ፕሬዝዳንቱ የተቋሙን 100ኛ ዓመት የምስረታ በዓል አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ተቋሙ በመሠረተ ልማትና በቴክኖሎጂ ዘርፍ እንዲጎለብት ምቹ የፖሊሲ መደላድል እንደሚፈጠር ተናግረዋል።
ፕሬዝዳንቱ ለተቋሙ አመራርና ሠራተኞች ለቀጣዩ የሥራ ዘመን ሦስት ዋና ዋና አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል።
እነዚህም የሳይንሳዊ ምርምር ብቃትን በማጎልበት የወረርሽኝ መከላከል ዝግጁነትን ማሳደግ፣ የዲጂታል ጤና መረጃ አያያዝን በማዘመን የበሽታዎችን ስርጭት አስቀድሞ መተንበይ የሚያስችል የቴክኖሎጂ አቅም መገንባት፣ እና ለውሳኔ ሰጪዎች ግብዓት የሚሆኑ ሳይንሳዊ ጥናቶችን በስፋት ማቅረብ የሚሉ ናቸው።
"የዜጎችን ጤንነት መጠበቅ የሀገር ልማትና የብሔራዊ ደኅንነት ዋነኛ መሠረት ነው" ያሉት ፕሬዝዳንት ታየ፣ ተቋሙ ያለፉትን ስኬቶች ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የውስጥ አቅሙን ማጠናከር እንዳለበት አሳስበዋል።
መንግሥት ለተቋማት ግንባታ የሰጠው ትኩረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም በንግግራቸው አፅንዖት ሰጥተዋል።
አዲስዓለም አበበ
ሐምሌ 09/2018 ዓ.ም | 1 444 |
| 18 | Sin texto... | 1 617 |
| 19 | ፕሬዝዳንት ታየ አፅቀስላሴ የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትን 100ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በይፋ አስጀመሩ
የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታየ አፅቀስላሴ የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የተመሠረተበትን 100ኛ ዓመት የምስረታ በዓልና አውደ ርዕይ በዛሬው ዕለት በይፋ ከፍተዋል።
ፕሬዝዳንቱ በመክፈቻ መርሐ ግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ተቋሙ ባለፉት መቶ ዓመታት የዜጎችን ጤና ለመጠበቅና ጠንካራ የጤና ሥርዓት ለመገንባት ያደረገው ጉዞ የኢትዮጵያ ብርቱ ትግል ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።
ፕሬዝዳንቱ በወጣትነት ዘመናቸው ተቋሙ "ፓስተር" ተብሎ በሚጠራበት ወቅት የነበረውን ትውስታ በማውሳት፣ ዛሬ ለደረሰበት ደረጃ የባለሙያዎች መስዋዕትነት ከፍተኛ እንደነበር ገልጸዋል።
"ይህ 100 ዓመት ቀላል አይደለም፤ በሂደቱ የታየው የባለሙያዎች ቁርጠኝነትና ታሪክ ጎልቶ ሊጻፍ ይገባል" ብለዋል።
የሀገር ሉዓላዊነትና ብሔራዊ ደኅንነት ከዜጎች ጤና ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት እንዳለው የገለጹት ፕሬዝዳንት ታየ፣ ኢንስቲትዩቱ እንደ ኮቪድ-19፣ ኤም-ፖክስና ማርበርግ ያሉ ወረርሽኞችን በመመከት ረገድ ያሳየው ሳይንሳዊ አመራር የሚደነቅ መሆኑን ጠቁመዋል።
ተቋሙ ያስመዘገባቸውን ስኬቶች ይበልጥ በማጠናከር ለቀጣዩ መቶ ዓመት ራሱን እንዲያዘጋጅም ጥሪ አቅርበዋል።
አዲስዓለም አበበ
ሐምሌ 09/2018 ዓ.ም | 1 187 |
| 20 | Sin texto... | 1 098 |
