Ethio Fm 107.8
በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام Ethio Fm 107.8
کانال Ethio Fm 107.8 (@ethiofm107dot8) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 18 595 مشترک است و جایگاه 12 273 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 1 808 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 18 595 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 14 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -127 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -8 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 9.95% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 6.76% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 1 851 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 1 257 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 5 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 15 ژوئن, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 15 ژوئن | +1 | |||
| 14 ژوئن | 0 | |||
| 13 ژوئن | +10 | |||
| 12 ژوئن | 0 | |||
| 11 ژوئن | 0 | |||
| 10 ژوئن | 0 | |||
| 09 ژوئن | +7 | |||
| 08 ژوئن | +3 | |||
| 07 ژوئن | +1 | |||
| 06 ژوئن | +1 | |||
| 05 ژوئن | +3 | |||
| 04 ژوئن | 0 | |||
| 03 ژوئن | +3 | |||
| 02 ژوئن | +8 | |||
| 01 ژوئن | 0 |
| 2 | አሜሪካ እና ኢራን የገቡበትን ጦርነት ለመቋጨት የሚያስችላቸው ስምምነት ላይ ደርሰዋል
ስምምነቱ ዐርብ የሚፈረም ሲሆን ከዛሬ ሰኞ ጀምሮ ኢራን ጥቃት ማድረሷን አንደምትገታ ገልፃለች።
የፓኪስታኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ሸህባዝ ሻሪፍ ሀገሬ በሁለቱ ኃይሎች መካከል የተፈጠረውን ልዩነት ለማጥበብ ስትሰራ ቆይታለች ብለዋል።
ዘላቂ ተኩስ አቁም ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ላይ ቴህራንና ዋሽንግተን መድረሳቸውን ያስታወሱት ሻሪፍ፥ ሊባኖስንም ያጠቃለለ ውል መሆኑን አረጋግጠዋል።
የኳታር አደራዳሪዎች ከ14 እስከ 15 ሰዓታት ከፍተኛ ውይይት አድርገው የመጣ ውጤት መሆኑም ታውቋል።
በስምምነቱ መሰረት ሆርሙዝ ሰርጥ ሙሉ ለሙሉ ይከፈታም ተብሏል።
አሜሪካም ሰርጡን በ30 ቀናት ውስጥ የመክፈት ግዴታ ይኖርባታል።
ስምምነቱ በአሜሪካ ቁርጠኝነት ልክ የሚመዘን መሆኑን ያስታወሰችው ቴህራን፥ዋሽንግተን የቤት ስራዋን መስራት እንዳለባትም አሳስባለች።
አሜሪካ በኢራን ዙሪያ ካሉ አካባቢዎች ጦሯን ማንሳትም ይኖርባታል።
በ60 ቀናት ውስጥ ኑክሌርን ጨምሮ ቁልፍ ጉዳዮች ውይይት እየተደረገባቸው መፍትሔ እየተሰጣቸው ይሄዳል ፤ለቀጣናውም ሰላም ይመጣል የሚል እምነት ተጥሏል።
ያም ሆኖ ግን ስምምነቱ ጥያቄ ያለበት መሆኑን የአሜሪካ ፖለቲከኞች ማንሳት ጀምረዋል።
ሪፐብሊካኑ ሴናተር ሊንዲሴይ ግርሃም እና የቀድሞው የትራምፕ ምክትል ፕሬዚዳንት ማይክ ፔንስ ተጠቃሽ ናቸው።
ጀርመን፣ጃፓን ፣ጣሊያን ፣ፈረንሳይ ፣እንግሊዝ፣ቱርክ እና ኒውዚላንድ ስምምነቱን በበጎ ከተመለከቱት አገራት መካከል ናቸው።
የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝም ለስምምነቱ የሰሩትን ሁሉ አመስግነዋል ሲሉ ዘ ዋሽንግተን ፖስትና ሲ ኤን ኤን ዘግበዋል።
ልዑል ወልዴ
ሰኔ 08/2018 ዓ.ም | 888 |
| 3 | እስራኤል በቤሩት ላይ የፈፀመችውን ጥቃት "ትርጉም የለሽ " ሲሉ ትራምፕ አጣጣሉ
የአሜሪካ እና የኢራን ስምምነት መቃረቡን ተከትሎ ትራምፕ በቤሩት የተፈጸሙ ጥቃቶችን በመኮንን ሁሉም ወገኖች እንዲቆጠቡ አሳሰቡ
ፕሬዚዳንት ትራምፕ በዛሬው ዕለት እስራኤል በቤሩት የሰነዘረችውን ጥቃት በመኮነን በሊባኖስ የሚደረጉ ጥቃቶች በአስቸኳይ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።
ትራምፕ በትሩዝ ሶሻል ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት ጥቃቱ “ሊፈጸም የማይገባው ነበር” በማለት፤ ማንም ሰው ላልተገደለበት ወይም ላልቆሰለበት ክስተት የተሰጠ “ኢምንትና ትርጉም የለሽ” ምላሽ ሲሉ ገልጸውታል።
ቀጣይ መካካር ዲፕሎማሲያዊ መፍትሔን ሊያደናቅፍ እንደሚችል ያስጠነቀቁት ትራምፕ፤ ቀጣናዊ ስምምነቱ “በጣም መቃረቡን” እና ሊባኖስንም በዚሁ ሰፊ የሰላም ማዕቀፍ ውስጥ ሊያካትት እንደሚችል አጽንኦት ሰጥተዋል።
ሰኔ 07/2018 ዓ.ም | 1 544 |
| 4 | ትራምፕ የአሜሪካ-ኢራን ስምምነት እሁድ ዕለት እንደሚፈረም ሲናገሩ፣ ቴህራን ግን በጊዜው ላይ ጥርጣሬ አላት
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለውን ውጊያ ለማቆም የተዘጋጀው ስምምነት እሁድ ዕለት እንዲፈረም ቀጠሮ መያዙን ሲናገሩ ፤ ኢራን ግን በፊርማው ጊዜ ላይ ጥርጣሬ እንዳላት ገልፃለች ።
የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባቃኢ ስለ ስምምነቱ ጊዜ ጥንቃቄ የተሞላበት አስተያየት የሰጡ ሲሆን፥ "የመግባቢያ ሰነዱ የሚፈረምበትን ትክክለኛ ቀን በትዕግስት መጠባበቅ ይኖርብናል፣ ሆኖም ግን ነገ [እሁድ] አይሆንም" ብለዋል።
ትራምፕ በማህበራዊ ሚዲያ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ስምምነቱ አንዴ ተቀባይነት ካገኘ በኋላ ቁልፍ የባህር ትራንስፖርት መስመር የሆነው የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ "ለሁሉም ክፍት" እንደሚሆን ገልጸዋል።
ቅዳሜ ዕለት፣ ዋና አገናኝ የሆነችው ፓኪስታንም ስምምነቱ በ24 ሰዓታት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ "በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጠበቅ" እና "ለዲጂታል (የኤሌክትሮኒክስ) ፊርማ ዝግጅት እያደረጉ" መሆኑን አስታውቃለች።
ከዶናልድ ትራምፕ አስተያየት በፊት የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባቃኢ ስለ ስምምነቱ ጊዜ ጥንቃቄ የተሞላበት አስተያየት የሰጡ ሲሆን፥ "የመግባቢያ ሰነዱ የሚፈረምበትን ትክክለኛ ቀን በትዕግስት መጠባበቅ ይኖርብናል፣ ሆኖም ግን ነገ [እሁድ] አይሆንም" ብለዋል።
በንግግሩ ውስጥ ሌላኛዋ አገናኝ የሆነችው የኳታር ልዑካን ቡድን እሁድ ዕለት ቴህራን መድረሱን የኢራን መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
የዋሽንግተን ፖስት ዘገባ እንዳስነበበው ይህ ጉብኝት ኢራን ስምምነቱን ትፈርማለች ተብሎ በሚጠበቅበት ጊዜ ላይ ተፅዕኖ ይኑረው አይኑረው በግልጽ የታወቀ ነገር የለም።
ትራምፕ ቅዳሜ ዕለት በትሩዝ ሶሻል ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ፡ "ስምምነቱ ነገ እንዲፈረም ቀጠሮ ተይዟል፣ ከተፈረመ በኋላ ወዲያውኑ የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ለሁሉም ክፍት ይሆናል" ብለዋል።
ትራምፕ የኢራንን የዳበረ ዩራኒየም ክምችት ለመጠቆም በፈለጉበት ግልጽ በሆነ ንግግራቸው "በትክክለኛው ጊዜ፣ ሁሉም ነገር ሲረጋጋ፣ እኛ ገብተን 'የኑክሌር ብናኙን' (Nuclear Dust) እንወስዳለን" ያሉ ሲሆን፣ ከጊዜ በኋላም እንደሚወድም አክለው ገልጸዋል።
ሰኔ 07/2018 ዓ.ም | 1 869 |
| 5 | بدون متن... | 1 657 |
| 6 | “ኢትዮጵያ ከኃይል ፖለቲካ ወጥታ ወደ “የሃሳብ ልዕልና” የታሸጋገረችበት አዲስ የፖለቲካ ባህል እየተገነባ ነው” አሉ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ስላሴ
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ታዬ አፅቀ ስላሴ፣ የሀገር ግንባታም ሆነ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ከስሜታዊነትና ከደመነፍሳዊ አካሄድ የጸዱ መሆን እንዳለባቸው አሳሰቡ።
ፕሬዝዳንቱ ይህንን ያሉት የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ካውንስል፣ የሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ማጠቃለያ አስመልክቶ ባዘጋጀው ይፋዊ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ነው።
ፕሬዝዳንት ታዬ በንግግራቸው የሀገሪቱን የፖለቲካ ታሪክ ወደ ኋላ መለስ ብለው የቃኙ ሲሆን፣ ቀደም ሲል በውይይትና በጠረጴዛ ዙሪያ መፈታት የነበረባቸው ልዩነቶች በኃይል አማራጭ ለመፍታት በመሞከራቸው ምክንያት ሀገሪቱ ለከፍተኛ የዲሞክራሲና የእድገት መጓተት መዳረጓን ገልጸዋል።
ሆኖም በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ከኃይል ፖለቲካ ወጥታ ወደ “የሃሳብ ልዕልና” የታሸጋገረችበት አዲስ የፖለቲካ ባህል እየተገነባ መሆኑን በጽኑ አስምረውበታል።
ወቅታዊ ሁኔታዎችን በተመለከተም፣ የተወሰኑ የውጭ ሚዲያዎችና አካላት በኢትዮጵያ ውስጥ ግጭት እንዲቀሰቀስና እንዲባባስ ሆን ብለው ጥረት ማድረጋቸውን ፕሬዝዳንቱ በንግግራቸው ወቅሰዋል።
ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ ህዝብ የእነዚህን አካላት ፍላጎት ያከሸፈ የበሰለ የፖለቲካ ስልጣኔ ማሳየቱን ገልጸዋል።
ህዝቡ በትዕግስትና በጨዋነት ረጅም ሰልፎችን በመጠበቅ ድምፁን መስጠቱ፣ ለሀገራዊ ሰላምና አንድነት ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየበትና ታሪካዊ ፍርዱን የሰጠበት መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ በኩራት ተናግረዋል።
ምርጫው በሰላም መጠናቀቁን ተከትሎ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፉት ፕሬዝዳንቱ፣ ምርጫውን ላሸነፉ አካላትም ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።
ምርጫ ማሸነፍ የክብርና የድል መግለጫ ብቻ ተደርጎ መወሰድ እንደሌለበት የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፣ ይልቁንም ድሉ የሀገርን ህልውና የማስጠበቅና የህዝብን ህይወት የመለወጥ እጅግ ከባድ “የቤት ስራ” መሆኑን አስገንዝበዋል።
በመሆኑም አሸናፊዎች የህዝብን ድምፅ በትህትና በማዳመጥ፣ በታማኝነትና በንጽህና ሀገሪቱን ወደ ተሻለ የልማት ምዕራፍ ሊመሩ እንደሚገባ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
በመጨረሻም ፕሬዝዳንት ታዬ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ ለጸጥታ አካላትና ለሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የምርጫ ሂደቱን በነጻነትና በገለልተኝነት ለመምራት ላሳዩት ቁርጠኝነት ከፍተኛ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በዚህ ታሪካዊ መርሃ ግብር ላይ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀገር መከላከያና የፖሊስ ከፍተኛ መኮንኖች፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እንዲሁም የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት መገኘታቸው ታውቋል።
ልዑል ወልዴ
ሰኔ 06/2018 ዓ.ም | 2 011 |
| 7 | بدون متن... | 1 654 |
| 8 | የኃይል አቅርቦት ለተወሰኑ ሰዓታት በአዲስ አበባ ፣ በአዳማ እና መቀሌ የሚቋረጥባቸው ቦታዎች
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ነገ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ፣ በአዳማ እና በመቀሌ ከተሞች በሚገኙ የተለያዩ አካባቢዎች ላይ የጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል የኃይል አቅርቦት ለተወሰኑ ሰዓታት እንደሚቋረጥ አስታወቀ።
ተቋሙ በዕቅድ ለሚያከናውነው ለዚህ የጥገና ሥራ ደንበኞች አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉና በትዕግስት እንዲጠብቁም አሳስቧል።
የኤሌክትሪክ አገልግሎት በሰጠው መግለጫ መሠረት የኃይል መቋረጡ ነገ ጠዋት የሚጀምር ሲሆን፣ በተለያዩ አካባቢዎች እንደየሥራው ስፋትና ዓይነት ከስድስት እስከ ስምንት ሰዓታት ከግማሽ የሚቆይ ይሆናል።
በዚህም መሠረት በአዲስ አበባ ከተማ ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት እስከ ቀኑ ስምንት ሰዓት ከግማሽ ድረስ በአፍንጮ በር መስጊድ፣ ደጃች ውቤ፣ ጊዮርጊስ እሳት አደጋ፣ ችሎት አደባባይ፣ ዘበኛ ሰፈር፣ ሾላ፣ በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ በሰሜን ሆቴል ጫፍ፣ በቀለመወርቅ ትምህርት ቤት፣ በዶሮ ተራ፣ በራስ ደስታ አካባቢ፣ በአርበኞች ትምህርት ቤት እና በዕንቁላል ፋብሪካ አደባባይ ዙሪያ የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል።
በተመሳሳይ ሁኔታ ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ከግማሽ ድረስ በጎፋ ካምፕ ኮንዶሚኒየም፣ ጀርመን አደባባይ፣ ጉራጌ ሰፈር፣ ትግሬ ሰፈር፣ ካፍ ነዳጅ ማደያ ጀርባ፣ ሀግቤስ አራት መንታ፣ ጎጃም በረንዳ ጫፍ፣ ጅንአድ፣ አበበች ጎበና፣ ቄጤማ ተራ፣ ፓስተር አደባባይ፣ አቤት ሆስፒታል፣ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን፣ ዳትሰን ሰፈር፣ ሰን ሆቴል፣ 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ እና አዲስ አበባ ሜዲካል ኮሌጅ አካባቢዎች መብራት የማይኖር መሆኑ ታውቋል።
ከዚህ በተጨማሪም ከጠዋቱ ሶስት ሰዓት እስከ ቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ከግማሽ ባለው ጊዜ ውስጥ በድሬ ከአስፋልት በታች፣ ጉዳ፣ ኬላ፣ ጉዮ፣ በታጠቅ ኢንዱስትሪ መንደር በከፊል፣ ቶልቻ፣ ሰንጎታ እና በገፋርሳ ሰብስቴሽን ዙሪያ የጥገና ሥራው እንደሚከናወን ተገልጿል።
የአቅርቦት መቋረጡ ከአዲስ አበባ ውጭ ባሉ የክልል ከተሞችም የሚተገበር ሲሆን በአዳማ ከተማ የሚገኙት አዳማ ሆስፒታል፣ ፖስታ ቤት አካባቢ፣ ሁሩታ ከተማ እና ሰኞ ገበያ ከጠዋቱ ሶስት ሰዓት እስከ ቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ከግማሽ ድረስ የኃይል አቅርቦት ያጣሉ።
በመቀሌ ከተማ ደግሞ በኢትዮ-ሸዊት ብረት ሥራ እና በአካባቢው ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ አራት ሰዓት ከግማሽ ድረስ ሙሉ በሙሉ መብራት እንደሚቋረጥ ተቋሙ አስታውቋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ መደበኛ መስመር ላይ እስኪመለስ ድረስ ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠብቁ የጠየቀ ሲሆን፣ ለተፈጠረው ጊዜያዊ መስተጓጎልም አስቀድሞ ይቅርታ ጠይቋል።
ሰኔ 06/2018 ዓ.ም | 1 811 |
| 9 | بدون متن... | 1 643 |
| 10 | ኒጀር ግብረ-ሰዶማዊነትን በህግ ከከለከሉ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት ተርታ ተቀላቅላለች ።
የኒጀር ወታደራዊ ሁንታ ግብረ-ሰዶማዊነትን በወንጀል የሚቀጣ አዲስ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ማውጣቱን አስታወቀ።
ከሀገሪቱ የፍትህ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ አዲሱ ህግ ከትናንት በስቲያ ሐሙስ ጀምሮ ገቢራዊ ተደርጓል።
ስራ ላይ የዋለው አዲሱ ህግ ግብረ-ሰዶማዊነትን ወይም መሰል ድርጊቶችን የፈጸመ ወይም ለመፈጸም የሞከረ ማንኛውም ሰው ከ5 እስከ 10 ዓመት በሚደርስ እስራት እና በገንዘብ ይቀጣል።
ቅጣቱ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸውን ሰዎች ጋብቻ ያስፈጸሙ ሰዎችን፣ ምስክሮችን፣ ጋብቻው እንዲፈጸም ፍቃድ የሰጡትን እንዲሁም የሰርጉን አዘጋጆች በሙሉ ያጠቃልላል ነው የተባለው።
ከዚህ ቀደም በኒጀር ግብረ-ሰዶማዊነት በህግ የተከለከለ ባይሆንም፣ በህብረተሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ማግለል ይደርስበት ነበር።
ኒጀር ይህንን እርምጃ በመውሰድ ግብረ-ሰዶማዊነትን በህግ ከከለከሉ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት ተርታ ተቀላቅላለች ።
ግብረሰዶማዊነት በሴኔጋል፣ ኬንያ፣ ሴራሊዮን እና ታንዛኒያ እስከ 10 ዓመት እና ከዚያ በላይ በሆነ እስራት ያስቀጣል።
በሶማሊያ፣ ዩጋንዳ እና ሞሪታኒያ ደግሞ የወንጀሉ ቅጣት እስከ ሞት ፍርድ ሊደርስ እንደሚችል ዘገባው አመልክቷል።
ሰኔ 06/2018 ዓ.ም | 1 934 |
| 11 | በአዲሱ በጀት ዓመት የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ይደረግ እንደሆነ በግልጽ እንዲታወቅ ተጠየቀ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 5ኛ ዓመት 25ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የፌደራል መንግስትን የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት በተመለከተ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ጥያቄያቸውን ለምክር ቤቱ ካቀረቡት አባላት መካከል የአብን (የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ) ፓርቲን ወክለው የምክር ቤት አባል የሆኑት ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ይገኙበታል።
ዶክተር ደሳለኝ በጥያቄያቸው፤ መንግስት ለ2019 በጀት ዓመት ለመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ያደርጋል ወይ? የሚለው ጉዳይ በግልጽ እንዲታወቅ ጠይቀዋል።
የምክር ቤት አባሉ ጥያቄውን ባቀረቡበት ወቅት ባለፈው ዓመት የታዘቡትን አጋጣሚ በማስታወስ፤ "ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጥያቄ ለምክር ቤቱ አቅርቤ 'የደመወዝ ጭማሪ የለም' የሚል ምላሽ ከተሰጠኝ ከአንድ ወር በኋላ ጭማሪ ተደርጓል" ብለዋል። በመቀጠልም "ዘንድሮስ ጭማሪ የለም ካሉኝ ከአንድ ወር በኋላ ጭማሪ ይኖራል ወይ?" ሲሉ በሚኒስትሩ አገላለጽ ላይ ያላቸውን ጥርጣሬ በፈገግታ የታጀበ ጥያቄ በማስከተል ሰንዝረዋል።
ለቀረበው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፤ መንግስት ቀደም ሲል በሁለት ዙር የደመወዝ ጭማሪ ማድረጉን ጠቅሰዋል።
ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት በክልሎች በኩል በፐርሰንት ተሰርቶ የቀረበው የደመወዝ ጭማሪ ተመን እና ለጉዳዩ ከተመደበው በጀት ጋር ባለመመጣጠኑ ምክንያት፣ አሁንም ድረስ ተጨማሪ የማጥራትና የማስተካከል ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ሚኒስትሩ ለአባላቱ አስገንዝበዋል።
አቤል እስጢፋኖስ
ሰኔ06/2018 ዓ.ም | 2 038 |
| 12 | بدون متن... | 1 903 |
| 13 | ሀምሌ 8 ቀን 2018 ሀገራዊ ጉባኤ ይደረጋል አለ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮምሽን
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮምሽን ሀገራዊ ጉባኤዉን ሀምሌ 8 ቀን 2018 እንደሚያደርግ አሳወቀ
4 ሺህ ያህል ተሳታፊዎችን ያካተተዉ ይህ ጉባኤ ለሶስት ተከታታይ ሳምንታት በአዲስ አበባ ይደረጋል ተብሏል።
ተሳታፊዎች ጉባኤዉ ከመጀመሩ አንድ ሳምንት ቀደም ብለዉ ወደ አዲስ አበባ እንዲገቡ እንደሚደረግም የኮምሽኑ ዋና ኮምሽነር መስፍን አርአያ በዛሬዉ እለት በተሰጠ ላይ መግለጫ ተናግረዋል።
ቁምነገር አየለ
ሰኔ 05/2018 ዓ.ም | 2 018 |
| 14 | በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የከተማ አስተዳደሩ ገለጸ
በከተማዋ በአሁኑ ወቅት ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተነግሯል
በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ውስጥ ለስራው ደህንነት የሚሰጠው ትኩረት በማነሱ የሚደርሰውን ከፍተኛ የህይወት፣ የአካልና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የተቀናጀ የግንዛቤ ማስጨበጥና የቁጥጥር ስራ እየተከናወነ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታውቋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ፣ በሀገሪቱም ሆነ በአዲስ አበባ ከተማ የስራ ላይ ደህንነት ጉዳይ እንደ ሁለተኛ አጀንዳ መታየቱ፣ በግንባታ ሳይቶች ላይ ለሚጠፉ የበርካታ ዜጎች ህይወትና ለሚከሰቱ አካላዊ ጉዳቶች ዋነኛ ምክንያት ሆኗል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂና ማኔጅመንት ባለሙያዎች ማህበር ባዘጋጀው ዓለማቀፍ የኮንስትራክሽን ጤናና ደህንነት ኮንፍረንስ ላይ የተገኙት ኢ/ር ወንድሙ፣ ይህ ችግር ከግለሰብ አልፎ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ እያስከተለ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
በከተማዋ በአሁኑ ወቅት ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸውን የገለጹት ዋና ስራ አስኪያጁ፣ በእነዚህ ቦታዎች ላይ ከሩብ ሚሊዮን በላይ ዜጎች እንደሚሰማሩ ገልጸዋል። በመሆኑም በእነዚህ ሳይቶች ላይ የሚደርሰው የጥንቃቄ ጉድለት በሰራተኞች ላይ ብቻ ሳይሆን፤ በአካባቢው በሚንቀሳቀሱ ነዋሪዎችና መንግስት በከፍተኛ ወጪ በገነባቸው መሰረተ ልማቶች ላይ ጭምር ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን አመልክተዋል።
ኢንጅነር ወንድሙ አክለውም፣ የከተማ አስተዳደሩ ይህንን ችግር ለመቅረፍ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ፣ የባለሙያዎች ስምሪት፣ እንዲሁም ጥብቅ ቁጥጥርና ህጋዊ እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑን ገልጸዋል።
የግንባታ ደህንነትን መጠበቅ በሁሉም የስራ ቦታዎች ላይ ባህል ሆኖ እንዲቀጥል ለማድረግ ጥረቶች መጀመራቸውንና ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አጽንኦት ሰጥተዋል።
አዲስአለም አበበ
ሰኔ 05/2018 ዓ.ም | 2 080 |
| 15 | بدون متن... | 1 754 |
| 16 | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነው
እዉቅናን የሚያገኙት 100 ታዋቂ አፍሪካውያን የአመራር እና ቢዝነስ ጉባኤ ላይ ነዉ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ ማራኪሽ ላይ በሚካሄደዉ ታዋቂ አፍሪቃዉያን የአመራር እና ቢዝነስ ጉባኤ ላይ መሆኑ ተዘግቧል።
ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ጋር፤ የዛምቢያው ፕሬዝዳንት ሃካይንዴ ሂቺሌማ እና የቀድሞዋ የአፍሪቃ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ዶ/ር ንኮሳዛና ድላሚኒ ዙማ ዘንድሮ በሚካሄደው 100 ታዋቂ አፍሪቃውያን የአመራር እና ቢዝነስ ጉባኤ በሞሮኮ ማራኬሽ ላይ፤ ክብር እና እውቅና ከሚሰጣቸዉ ታዋቂ የአፍሪቃ መሪዎች እና ግለሰቦች መካከል ይገኙበታል።
ጉባኤዉ፤ በአህጉሪቱ እና ከአህጉሪቱ ዉጭ ባሉ ሀገራት መሪዎች፣ ባለሀብቶች፣ ዲፕሎማቶች እና ለውጥ ፈጣሪዎች ከፍተኛ ፍላጎት እያደገ የመጣ ተሳትፎን ተከትሎ በማራኬሽ ሞሮኮ ከሰኔ 19 እስከ ሰኔ 21 ቀን 2018 እንደሚካሄድ የዝግጅቱ አዘጋጆች አስታውቀዋል።
ይፋ በተደረገዉ ዘገባዉ መሰረት፤ በዳቭዳን የሰላም እና የጥብቅና ፋውንዴሽን እና በ100 በጣም ታዋቂ የሰላም ቁንጮ የአፍሪካ አጋሮች ጋር በመተባበር የሚዘጋጀው ይህ ዓመታዊ ጉባኤ፤ ልህቀትን ለማክበር፣ ፈጠራን ለማራመድ እና ኢኮኖሚያዊ እድገትን ለማስፈን፣ ድንበር ዘለል አጋርነቶችን ለማጠናከር እና ዘላቂ ልማትን ለማስፋፋት የሚሰራ የአፍሪቃ ግንባር ቀደም መድረኮች አንዱ ነው።
ሰኔ 05/2018 ዓ.ም | 1 932 |
| 17 | በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው የሰላም ስምምነት ሰነድ እሁድ ዕለት በጄኔቫ ሊፈረም እንደሚችል ተገለጸ
በፋርስ ባሕረ ሰላጤ ያለውን ጦርነት ለማቆም በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ምናልባት እስከ እሁድ ሊፈረም እንደሚችል አንድ የምዕራባዊ ምንጭ ለሮይተርስ ተናግሯል፡፡
ጄኔቫም ስምምነቱ የሚፈረምባት ዋነኛ ስፍራ ሆና ተለይታለች።
ምንጩ እንደገለጹት በስምምነቱ ላይ የሚሰፍሩ ቃላት አሁን በመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ናቸው፤ ኢራን ግን ስምምነቱ እስራኤል በኢራን ከሚደገፈው የሄዝቦላህ ታጣቂ ቡድን ጋር እየተዋጋች ባለችበት በሊባኖስ ያለውን ግጭት ማካተት አለበት በሚለው አቋሟ ጸንታለች።
ዓላማው የስምምነቱን ቃላት እስከ ቅዳሜ ድረስ በማጠናቀቅ በአሜሪካው ምክትል ፕሬዚዳንት ጄዲ ቫንስ እና በኢራን የፓርላማ አፈ ጉባኤ መሀመድ ባከር ቃሊባፍ እንዲፈረም ማድረግ ነው።
እስካሁን የተረጋገጠ ቦታ ባይኖርም ጄኔቫ ዋነኛዋ እጩ ሆናለች።
ትራምፕ እንደተናገሩት ስምምነቱ ዝግጁ በመሆኑ በኢራን ላይ ሊያካሂዱት የነበረውን አዲስ ጥቃት ሰርዘዋል።በኋይት ሀውስ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ "ከኢራን ጋር በጦርነቱ ላይ ትልቅ ስምምነት ላይ ደርሰናል" ብለዋል።
የኢራን ባለስልጣናት እንደገለጹት የስምምነቱ ውሎች ቴህራን እስካሁን የጠየቀቻቸውን አብዛኛዎቹን ጉዳዮች የያዙ ይመስላሉ፤ ትራምፕ ግን ኢራን በየካቲት ወር ከተፈጸሙ ጥቃቶች በኋላ የዘጋችውን የሆርሙዝ ሰርጥ ከማስከፈት ባለፈ ብዙም ያገኙት ነገር ያለ አይመስልም።
አንድ ከፍተኛ የኢራን ባለስልጣን ለሮይተርስ እንደገለጹት፤ የስምምነቱ ረቂቅ በኢራን ዘይት ላይ የተጣለውን ማዕቀብ የሚያነሳ፣ የታገዱ በቢሊየን የሚቆጠሩ ዶላሮችን የሚለቅ እና ሊባኖስን ጨምሮ በሁሉም ግንባሮች ግጭቶች እንዲቆሙ የሚያዝ ነው።
የኒውክሌር ጉዳዮች ለሌላ ጊዜ ለሚደረጉ ውይይቶች እንዲቆዩ ይደረጋል።
ዋሽንግተን ኢራን የኒውክሌር መሣሪያ በጭራሽ እንዳታበለጽግ ዋስትና የሚሰጥ ስምምነት ትፈልጋለች፤ ኢራን በበኩሏ የኒውክሌር መሣሪያ የመሥራት ፍላጎት እንደሌላት ትናገራለች።
ማዕቀቦችን ማንሳት፣ የኢራንን ሀብት መልቀቅ እና እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምታደርገውን ጥቃት ማቆም የኢራን መሠረታዊ ጥያቄዎች ናቸው።
ምንጩ ኢራን በምላሹ ምን ልታቀርብ እንደምትችል የጠቀሰው ነገር የለም። አሜሪካም እስካሁን የሰጠችው ፈጣን ምላሽ የለም።
የኢራኑ መህር ዜና አገልግሎት እንደገለጸው፤ ውሎቹ ሌሎች ዋና ዋና የአሜሪካ ቅናሾችን ያካተቱ ሲሆን፣ ይህም ኃይሏን ከኢራን አካባቢ ለማስወጣት እና የተጎዳውን የኢራን ኢኮኖሚ መልሶ ለመገንባት ዕቅድ ማቅረብን ይጨምራል።
የመህር ዘገባ አክሎም፤‹‹አሜሪካና አጋሮቿ ቢያንስ 3መቶ ቢሊየን ዶላር የሚያወጣ የኢራን መልሶ ግንባታ ዕቅድ ማቅረብ አለባቸው›› ብሏል።
ሊዲያ ደሳለኝ
ሰኔ 05/2018 ዓ.ም | 1 624 |
| 18 | بدون متن... | 1 501 |
| 19 | #በአዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ዋጋ ላይ የተሽከርካሪ ባለንብረቶች ቅሬታቸውን ገለጹ
"አንድ ጎማ ለመቀየር እቁብ እየገባ ያለን እና ነዳጅ ለመሞላት ተቸግሮ እያለቀስ ላለዉ አሽከርካሪ ለሰሌዳ ይሄን ያህል ዋጋ ማስቀመጥ ፍትሀዊነት የራቀዉ ነዉ " ብለዋል ኢትዮ ኤፍ ኤም ያናገራቸው የተሽከርካሪ ባለንብረቶች ፡፡
አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ዋጋ ጫና ዉስጥ ያለዉን የኢትዮጵያውያን ኑሮ ይበልጥ የሚያከብደዉ ያደርጋል ሲሉ የተሽከርካሪ ባለንብረቶች ተናገሩ
በኢትዮጵያ የዜጎች የኑሮ ጓዝ ከከፍተኛ የኑሮ መወደድ ጋር ትግል የገጠመ የሚመስልበት ሆኗል የሚለዉ ሀሳብ አብዛኞዉ ኢትዮጵያ ስለኑሮ ቢጠየቅ የሚመልሰዉ እየሆነ መጥቷል።
የዜጎች የገቢ አቅም ባለበት ቀጥሎ በተለያየ መልኩ ወጪ የሚደርገዉ የአገልግሎት የገንዘብ መጠን ከፍ ማለት ያልተጣጣመ እና የተሳከረ የኑሮ መልክን እንድንገፋ አድርጓል የሚሉ ኢትዮጵያውያን መኖራቸዉንም ጠቋሚ አድርጓል።
በትናንትናው እለት በአዲስ አበባ ተግባራዊ መሆን የጀመረዉን አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ(ታርጋ) ዋጋ ብዙ እያስባለ ይገኛል ።
ይህ አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ በአዲስ አበባ ተመዝግበው ሰሌዳ እየተጠባበቁ ባሉ አዳዲስ ተሽከርካሪዎች ላይ የተጀመረ ይሁን እንጂ በሁሉም ተሽከርካሪ በሂደት ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑ እየተገለፀ ነዉ።
ለመሆኑ በዚህ ዋጋ ዙሪያ የተሽከርካሪ ባለንብረቶች ምን እያሉ ይገኛል ?ሲል ኢትዩ ኤፌም ጠይቋል።
የሜትር ታክሲ የትራንስፖርት ዘርፍ ላይ የሚገኙ ባለንብረት እንደሚገለፁት " ለስራ በብድር ለገዛሁት መኪና 56 ሺህ ብር ለሰሌዳ ትከፍላለህ መባል በጣም ይከብዳል ፤ ለጎማ እቁብ እየገባን የምንቀይር ሰዎች አሁን ደግሞ ለታርጋም እቁብ እየገባን ልንቀየር ነዉ ማለት ነዉ" ሲሉ ተናግረዋል።
ሌላኛ ያነጋገርናቸው የግል ተሽከርካሪ ባለንብረት በዋጋዉ ላይ ያላቸዉን ቅሬታ ሲያስረዱ " የአለምአቀፍ ዋጋዎችን ምሳሌ እንኳን ለማድረግ ዋጋዉ ከ10 ዶላር እስከ 70 ዶላር የሆነ የዋጋ መጠን ያለ ነዉ። በኢትዩጵያ ለሰሌዳ ዋጋዉ መወደድ ምክንያት ሆኖ እየቀረበ ያለዉ የሰሌዳዉ ቴክኖሎጂ ከሆነም አቅማችን ያላገናዘበ ቴክኖሎጂ የእኛ መሆን አይገባዉም" ይላሉ ፡፡
ሲቀጥሉም" ድህነታችን ለማሳበብ ሳይሆን እንደ ህዝብ ኪሳችን ባዶ ነዉ፥ ነዳጅ ለመሙላት እያለቀሰ እና እየለመነ ያለን አሽከርካሪ ላይ እንደዚህ አይነት ጫና መቀመጡ የታሰበበት ነዉ ብዬ አላስብም" የሚል ሀሳብን ሰጥተዋል።
የንግድ መገልገያ ተሽከርካሪ እንዳላቸው የነገሩን ሌላኛዉ ያነጋገርናቸው ባለንብረት " በሰማነዉ ነገር ተገቢ ያልሆነ እና ህዝቡ ያለበትን ሁኔታ የማያማክል እና በጭራሽም የተደረገዉ ነገር መቼም በዚህ መልኩ ይሆናል ተብሎ የማይታሰብ ነዉ ፤ይሄ እንደዚህ ተብሎ ሊነገረንም አይገባም"ይላሉ።
" ለታርጋ 56 ሺህ ብር ነዉ ማለት የመኪና እቃ ዉድ በሆነበት ሰአት ፥ ኑሮ በተወደደበት ሰአት ታርጋዉ ከወርቅ ጥፍጥፍ ቢሰራ እንኳን ለእኛ አያዋጣንም በግዳጅ ካላደረጋችሁ ከተባለ ግን ምንም ማድረግ አንችልም" ሲሉ ተናግረዋል።
የህዝብ ታክሲ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ሰሌዳ ዋጋ የነዳጅ ከሆኑ 11ሺህ 700 በተቃራኒው ደግሞ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ደግሞ 9ሺህ 400 ብር የዋጋዉ ተመን መሆን መረጃዉ ጠቁሟል።
በሌላ በኩል የግል መገልገያ እና የንግድ ተሽከርካሪዎች ለነዳጅ 56ሺህ እንዲሁም ለኤሌክትሪክ 44ሺህ 500 የሰሌዳ መሸጫ ዋጋ ሆኖ ተቀምጧል።
ይፋ የተደረገዉ የአዲሱ ሰሌዳ የዋጋ ስሌት ዙሪያ እንደ ሀገሪቱ ዜጋ የአቅም ልክ ቃኝቷል የሚባል አይደለም ያሉት ባለንብረቶቹ ሀገሪቷ ዉስጥ ለሚወጡ አሰራሮች ተደርገዋል የሚባሉ ጥናቶች የሚከተሏቸው መስፈርቶች ከዜጎች ኑሮ ጋር የሚቃረን ይመስላል ይላሉ ባለንብረቶቹ።
የሜትር ታክሲ የትራንስፖርት ዘርፍ ላይ የሚገኙ ባለንብረት ይሄንን ሲያስረዱም" አንድ ታርጋ የዚህን ያህል ተአምር አይደለም የዚህን ያህል ዋጋ የሚቀመጥለት፤ ሰዉ የአቅሙን ያህል ከፍሎ ሰርቶ እንዲኖር ማድረግ ያስፈልጋል ፤ የህዝብ አቅም ያማከለ ህግ ለምን እንደማይወጣ ስመለከት ግራ ይገባኛል " ብለዋል።
ከዚህ ዉጪም ያነጋገርናቸው የግል ተሽከርካሪ ባለንብረት "ጥናት ማድረግ ማለት የህዝቡን አቅም ማገናዘብም አብሮ የሚያመጣ ስለሆነ ኢትዮጵያዊያን ሆነዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚኖሩ ሰዎች ያልሰሩት የሚመስል አይነት ዉሳኔዎች እየወጡ ነዉ" ሲሉ ሀሳባቸዉን ሰጥተዋል።
ሲቀጥሉም" መንግስት የህዝብ የኑሮ ጫና የማቅለል ሀላፊነት አለበት ፤ በተለይ ከትራንስፖርት እና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር ጋር ተያይዞ ከሰሞኑ እየወጡ ያሉ ነገሮች ህዝቡን የሚያማምሩ ይመስላል" ሲሉም ገልፀዋል።
ቁምነገር አየለ
ሰኔ 05/2018 ዓ.ም | 1 713 |
| 20 | بدون متن... | 1 465 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
