fa
Feedback
Ethio Fm 107.8

Ethio Fm 107.8

رفتن به کانال در Telegram

በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Ethio Fm 107.8

کانال Ethio Fm 107.8 (@ethiofm107dot8) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 18 533 مشترک است و جایگاه 12 141 را در دسته اخبار و رسانه‌ها و رتبه 1 817 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 18 533 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 05 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -92 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -1 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 8.93% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 6.82% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 1 655 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 264 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 4 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 06 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانه‌ها تبدیل کرده‌اند.

18 533
مشترکین
-124 ساعت
-37 روز
-9230 روز

در حال بارگیری داده...

ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
ژوئیه '26
ژوئیه '26
+18
در 0 کانال‌ها
ژوئن '26
+70
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '26
+78
در 2 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '26
+74
در 1 کانال‌ها
Get PRO
مارس '26
+26
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '26
+51
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '26
+45
در 1 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '25
+25
در 2 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '25
+51
در 3 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '25
+51
در 2 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '25
+35
در 4 کانال‌ها
Get PRO
اوت '25
+62
در 4 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '25
+52
در 2 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '25
+81
در 3 کانال‌ها
Get PRO
مه '25
+67
در 2 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '25
+88
در 3 کانال‌ها
Get PRO
مارس '25
+87
در 5 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '25
+60
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '25
+135
در 2 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '24
+279
در 5 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '24
+259
در 4 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '24
+312
در 2 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '24
+377
در 3 کانال‌ها
Get PRO
اوت '24
+470
در 3 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '24
+235
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '24
+202
در 3 کانال‌ها
Get PRO
مه '24
+429
در 1 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '24
+494
در 5 کانال‌ها
Get PRO
مارس '24
+533
در 1 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '24
+428
در 3 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '24
+529
در 5 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '23
+536
در 3 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '23
+223
در 2 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '23
+342
در 3 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '23
+160
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '23
+181
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '23
+167
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '23
+214
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '23
+191
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '23
+252
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '23
+235
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '23
+226
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '23
+260
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '22
+159
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '22
+231
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '22
+144
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '22
+165
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '22
+442
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '22
+191
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '22
+121
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '22
+98
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '22
+109
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '22
+140
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '22
+96
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '22
+103
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '21
+93
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '21
+139
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '21
+211
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '21
+230
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '21
+364
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '21
+341
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '21
+416
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '21
+410
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '21
+307
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '21
+319
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '21
+325
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '21
+310
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '20
+21 895
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
06 ژوئیه0
05 ژوئیه0
04 ژوئیه+15
03 ژوئیه0
02 ژوئیه+3
01 ژوئیه0
پست‌های کانال
📢የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት🎯 ነገ እሁድ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በጥቁር አንበሳ 132 ኪ.ቮ ሃይል አስተላላፊ መስመር ሰበታ ወጪ መስመር ላይ የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦                                          ✅ከንጋቱ 12፡00 እስከ ጠዋቱ 2፡00 ድረስ:-   👉በልደታ ክፍለ ከተማ ዙሪያ እና በጭድተራ ፊት ለፊት፣መላው የመርካቶ ዙሪያ፣ ፔፕሲ ፋብሪካ፣ የድሮው አትክልት ተራ፣ ኤሊያና ሆቴል፣ ሰባራ ባቡር፣ አዲስ ከተማ ቴሌ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) ኮል ሴንተር እና አካባቢው ፣ 👉በአምስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ዙሪያ፣ ሰንጋተራ፣ ጥቁር አንበሳ፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI)፣ የደም ባንክ፣ ፋና ሚዲያ፣  ንብ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት እና ጎላ ሚካኤል ሙሉ፣ በህንፃ ኮሌጅ ዙሪያ፣ ኮካ፣ አብነት፣ መድር-ኃይል፣ 👉ጦር ኃይሎች ሆስፒታል እና ቶሎሳ ሰፈር፣ በልደታ ደሴ ሆቴል ዙሪያ፣ መላው ብስራተ ገብርኤል ዙሪያ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት (Commercial Bank of Ethiopia HQ)፣ ፍልውሃ፣ ዘውዲቱ ሆስፒታል፣ 👉ጋንዲ ሆስፒታል፣ የሳይንስ ሙዚየም፣ አራት ኪሎ (ባሻ ወልዴ፣1080)፣ ቅድስት ማርያም፣ አንድነት ፓርክ፣ መላው የጨርቆስ ዙሪያ፣ ፌደራል ፖሊስ፣ በልደታ ፀበል ዙሪያ፣ በልደታ ኮንዶሚኒየም ዙሪያ እና አካባቢው ፣  👉ኮሜርስ  ኮሌጅ (Commerce)፣ ጥቁር አንበሳ፣ ቴሌ ዳታ ሴንተር፣ አድዋ ዜሮ ዜሮ (Adwa 00)፣ ወዳጅነት ፓርክ እና አካባቢያቸው የኃይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል፡፡ ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪ መለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን። #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት ሰኔ 27/2018 ዓ.ም

2
بدون متن...
1 353
3
የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽንና ቴክኖ ኢትዮጵያ የሀገርን ገፅታ በቴክኖሎጂ ለመገንባት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙ የሀገርን ገፅታ ለመገንባትና የቱሪዝም መዳረሻዎችን በቴክኖሎጂ የታገዘ የማስተዋወቅ
የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽንና ቴክኖ ኢትዮጵያ የሀገርን ገፅታ በቴክኖሎጂ ለመገንባት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙ የሀገርን ገፅታ ለመገንባትና የቱሪዝም መዳረሻዎችን በቴክኖሎጂ የታገዘ የማስተዋወቅ ስራ ለመስራት የሚያስችል ስልታዊ ስምምነት በዛሬው እለት ተፈርሟል ። ስምምነቱ የተፈረመው ቴክኖ ኢትዮጵያ ከአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን እና ከቦርድ ሴል ፎን አዲስ አበባ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው 3ኛው ዙር የፎቶ ኤግዚቢሽን መክፈቻ ላይ ነው። በሕፃናትና ወጣቶች ትያትር ኮምፕሌክስ በይፋ በተከፈተው በዚህ ኤግዚቢሽን ላይ የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን እና ቴክኖ ኢትዮጵያ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ውል ተፈራርመዋል። ይህም ሁለቱ ተቋማት በቱሪዝም እና በቴክኖሎጂ ዘርፎች ላይ በቅንጅት በመስራት፣ የሀገር ውስጥ የቱሪዝም መዳረሻዎችን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግና ማህበረሰቡ የሀገሩን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ እሴቶች እንዲያውቅ ለማስቻል ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ተብሏል። በኤግዚቢሽኑ ላይ አዳዲስ የካሜራ እና የሰው ሰራሽ አስተዋፅኦ ወይም AI ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የተነሱ ከ100 በላይ ልዩ ልዩ የፎቶግራፍ ስራዎች ለዕይታ ቀርበዋል። ቴክኖሎጂን ለሀገር ገፅታ ግንባታና ለኪነጥበብ እድገት ማዋል ላይ ትኩረት ያደረገው ይህ የፎቶ ኤግዚቢሽን፣ ለሚቀጥሉት 10 ቀናት ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን፤ ከ10 ሺህ በላይ ታዳሚዎች ይጎበኙታል ተብሎ ይጠበቃል። ድርጊቱ በዘርፉ ላሉ ባለሙያዎችና ለቱሪዝም ኢንዱስትሪው አዲስ መነቃቃትን እንደሚፈጥርም ተነግሯል። ልዑል ወልዴ ሰኔ 26/2018 ዓ.ም
1 800
4
ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ የ3 ቢሊዮን ዶላር የቡና ወጪ ንግድ ዕቅዷን ማሳካቷን አቶ አዲሱ አረጋ ገለጹ በባለፈው በጀት ዓመት 2.65 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የተገኘ ሲሆን፤ ይህን ቁጥር ዓመት ባልሞላ
ኢትዮጵያ በበጀት ዓመቱ የ3 ቢሊዮን ዶላር የቡና ወጪ ንግድ ዕቅዷን ማሳካቷን አቶ አዲሱ አረጋ ገለጹ በባለፈው በጀት ዓመት 2.65 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የተገኘ ሲሆን፤ ይህን ቁጥር ዓመት ባልሞላ ጊዜ ዉስጥ ማሻሻል መቻሉን ግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው አስታውቀዋል ፡፡ መንግሥት ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት የቡናውን ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ሥራዎች መሠራታቸው በተለይም ለቡና ምርት ጥራት ትኩረት መደረጉ ለዕቅዱ ስኬት ድርሻው ከፍተኛ ነው ብለዋል ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ፡፡ ሰኔ 26/2018 ዓ.ም
1 730
5
ዘምዘም ባንክ የ1.8 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማስመዝገቡንና በካፒታል ገበያ ታሪክ ከወለድ ነፃ ቀዳሚ ባንክ መሆኑን አስታወቀ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የሚሰጠው ዘ
ዘምዘም ባንክ የ1.8 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማስመዝገቡንና በካፒታል ገበያ ታሪክ ከወለድ ነፃ ቀዳሚ ባንክ መሆኑን አስታወቀ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የሚሰጠው ዘምዘም ባንክ፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 1.8 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማስመዝገቡን ገለጸ። ባንኩ ይህን የገለፀው፣ 6 ቢሊዮን ብር ዋጋ ያላቸውን 6 ሚሊዮን ነባርና አዳዲስ አክሲዮኖቹን በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን  አስመዝግቦ ያስፀደቀ የመጀመሪያው ከወለድ ነፃ የፋይናንስ ተቋም መሆኑን ይፋ ባደረገበት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው። እንደ ባንኩ መግለጫ፣ የተመዘገበው የ1.8 ቢሊዮን ብር ትርፍ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ35 በመቶ ዕድገት አሳይቷል። በተመሳሳይ የባንኩ ጠቅላላ ገቢ ከ2.2 ቢሊዮን ብር ወደ 3 ቢሊየን ብር በማደግ የ36 በመቶ ጭማሪ ማስመዝገቡ ተጠቅሷል። በተያያዘም የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ መሊካ በድሪ ዘምዘም ባንክ በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ታሪክ አክሲዮኖቹን በይፋ አስመዝግቦ ያስፀደቀ ቀዳሚው ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ ተቋም በመሆን ታሪክ  ሰርቷል ብለዋል። ባንኩ ከግብይት አማካሪው ወጋገን ኢንቨስትመንት ባንክ ጋር በመሆን በካፒታል ገበያ መመሪያ በተቀመጠው መሠረት ነባርና አዳዲስ አክሲዮኖቹን አስመዝግቧል። ባንኩ የባለአክሲዮኖችን መብት በማስጠበቅና አዳዲስ አክሲዮኖችን ለሕዝብ በማቅረብ፣ አጠቃላይ ካፒታሉን ወደ 15 ቢሊዮን ብር ለማድረስ አቅዶ እየሠራ እንደሚገኝ ተገልጿል። አዲስዓለም አበበ ሰኔ 26/2018 ዓ.ም
1 704
6
በሰሜናዊ ናይጄሪያ ከ17 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለከፋ ረሃብ መጋለጣቸው ተገለጠ በሰሜናዊ ናይጄሪያ በተከሰተ የጸጥታ ችግር እና በእርዳታ አቅርቦት መቋረጥ ምክንያት ከ17 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለከፋ የረ
በሰሜናዊ ናይጄሪያ ከ17 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለከፋ ረሃብ መጋለጣቸው ተገለጠ በሰሜናዊ ናይጄሪያ በተከሰተ የጸጥታ ችግር እና በእርዳታ አቅርቦት መቋረጥ ምክንያት ከ17 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለከፋ የረሃብ አደጋ መጋለጣቸውን የዓለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) አስታወቀ። ተቋሙ ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው፣ በአካባቢው ያለው አለመረጋጋት በርካታ ቤተሰቦችን ከቤት ንብረታቸው ከማፈናቀሉም በላይ ገበሬዎች ወደ እርሻቸው እንዳይሰማሩ እንቅፋት ሆኖባቸዋል። ይህም በክልሉ ያለውን የምግብ ዋስትና ችግር ይበልጥ አባብሶታል። በተለይም የቦርኖ ግዛት የችግሩ ዋነኛ ሰለባ መሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን፣ በዚሁ ግዛት ብቻ ከ3 ሚሊዮን በላይ ሰዎች አጣዳፊ ለሆነ የምግብ እጥረት ተጋልጠዋል። የዓለም የምግብ ፕሮግራም በአሁኑ ወቅት ሰብአዊ ድጋፍ ለማቅረብ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ቢሆንም፣ የጸጥታው ሁኔታ እርዳታውን ለተቸገሩ ወገኖች ለማድረስ አስቸጋሪ እንዳደረገው ገልጿል። ተቋሙ በክልሉ የጀመረውን የምግብ እና የሥርዓተ-ምግብ ድጋፍ አጠናክሮ ለማስቀጠል በአስቸኳይ 89 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልገው ጥሪ አቅርቧል DW Africa እንደዘገበው። ልዑል ወልዴ ሰኔ 26/2018 ዓ.ም
1 481
7
የኢራኑ ጠቅላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ከዛሬ ጀምሮ ለሰባት ቀናት በኢራን እና በኢራቅ ከተሞች እንደሚከናወን ተገለፀ ባለፈው መጋቢት ወር ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው የቀብር ሥነ-ሥርዓት በአሜሪካ-እስራኤል እና በኢራን መካከል ባለው ጦርነት ምክንያት እንዲራዘም ተደርጓል። የ86 ዓመቱ አሊ ኻሜኒ ጦርነቱ በፈነዳበት የመጀመሪያ ቀን የካቲት 28 በመኖሪያ ግቢያቸው ላይ በተሰነዘረ የጋራ የአሜሪካ እና የእስራኤል የአየር ጥቃት ከቤተሰቦቻቸው ጋር መገደላቸው ይታወሳል። ከ1989 ጀምሮ ኢራንን የመሩት ኻሜኒ የአገሪቱን ወታደራዊ መዋቅር የቀረጹ መሪ ነበሩ። ይህ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ከሕዝብ ዕይታ ተሰውረው የቆዩት ልጃቸው እና ተተኪያቸው ሞጅታባ ኻሜኒ ሥልጣን ከያዙ በኋላ የሚከናወን የመጀመሪያው ትልቅ የመንግሥት ሥነ-ሥርዓት ነው። የሰባት ቀናት የቀብር ሥነ-ሥርዓት መርሃ-ግብሩ ከዛሬ ከፈረንጆቹ ሐምሌ 3 ጀምሮ በዋና ከተማው ቴህራን የሚጀምር ሲሆን፥የዓለም መሪዎችና ከፍተኛ ባለሥልጣናት ክብራቸውን ይገልጻሉ። በመቀጠልም በሐምሌ 4 እና 5 የሟቹ አስከሬን ሕዝቡ የመጨረሻ ስንብት እንዲያደርግለት በቴህራኑ ግራንድ ሞሳላ መስጊድ የሚቆይ ሲሆን፥በሐምሌ 6 እና 7 የሽኝት ሰልፉ ወደ ታዋቂው የሺዓ ሃይማኖታዊ ትምህርት ማዕከል ቆም ከተማ ይጓዛል። በመቀጠልም አስከሬኑ ወደ ጎረቤት አገር ኢራቅ በመጓዝ በሐምሌ 8 ቀን በናጃፍ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ይፋዊ አቀባበል ከተደረገለት በኋላ ታሪካዊ በሆኑት ናጃፍ እና ካርባላ ከተሞች የሕዝብ የሽኝት ሰልፍ ይካሄዳል። በመጨረሻም በሐምሌ 9 ቀን አስከሬኑ ወደ ኢራን ተመልሶ በኻሜኒ የትውልድ ስፍራ እና የሺዓ እስልምና እጅግ የተቀደሰ ከተማ በሆነችው መሻድ በሚገኘው የኢማም ሬዛ መቅደስ የቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ይፈጸማል ሲል አልጄዚራ ዘግቧል። ሳራ ዮሐንስ ሰኔ 26/2018 ዓ.ም
1 462
8
بدون متن...
1 354
9
በታክስ አስተዳደር ለውጦች፣ ተግዳሮቶችና መልካም ተሞክሮዎች ላይ ያተኮረ  መድረክ ተካሄደ የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት (አዲስ ቻምበር) ከዓለም አቀፉ የግል ኢንተርፕራይዝ ማዕከል (ሳይፕ) ጋር በመተባበር 5ኛውን የመንግስትና የግሉ ዘርፍ የጋራ የምክክር መድረክ አካሄደ። በታክስ አስተዳደር ለውጦች፣ ተግዳሮቶችና መልካም ተሞክሮዎች ላይ ያተኮረው ይህ መድረክ የገንዘብ ሚኒስቴር እና የገቢዎች ቢሮ አመራሮችን ጨምሮ የንግዱን ማህበረሰብ አባላት አሳትፏል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ ቢሯቸው አገልግሎቱን ለማዘመን እየሰራ መሆኑን ገልጸው፣ የግሉ ዘርፍ የሚያነሳቸውን የግብር ቅሬታዎች ከአዲስ ቻምበር ጋር በተደራጀ መልኩ እየፈቱ መሆኑን ጠቅሰዋል። የአዲስ ቻምበር ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ዘሐራ መሐመድ በበኩላቸው፣ ጠንካራ ማክሮ ኢኮኖሚ ለመገንባት ፍትሐዊ፣ ቀልጣፋና ሊተነበይ የሚችል የግብር ሥርዓት መኖር ወሳኝ መሆኑን አሳስበዋል። በውይይቱ ወቅት ተሻሽሎ በወጣው የገቢ ግብር አዋጅ ላይ ድርጅቶች ቢከስሩ እንኳ ከዓመታዊ ሽያጫቸው 2.5 በመቶ ግብር እንዲከፍሉ የሚደነግገው ሕግና የደረጃ 'ሀ' እና 'ለ' ታክስ ከፋዮች የቅድሚያ ክፍያ ሥርዓት በንግዱ ማህበረሰብ ላይ ጫና እየፈጠረ መሆኑ እንደ ስጋት ተነስቷል። አዲስ ቻምበር በመድረኩ የተነሱትን ተግዳሮቶች በዝርዝር አጠናቅሮ ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት እንደሚያቀርብ አስታውቋል። ሐመረ ፍሬው ሰኔ 25/2018 ዓ.ም
1 708
10
+3
بدون متن...
1 615
11
ለምክክር ጉባኤዉ የቀረቡ አጀንዳዎች ላይ የተበታተኑ የሚመስሉ ይዘቶችን ኮሚሽኑ በድጋሜ ሊያያቸዉ ይገባል ተባለ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮምሽን ሀምሌ ስምንት በሚያካሂደው ጉባኤ ዙሪያ በምክክር ወቅት ሙያዊ ማብራሪያ ከሚያቀርቡት ባለሙያዎች ጋር በዛሬዉ ዕለት ዉይይት አካሂዷል። ኮሚሽኑ ለጉባኤዉ የመረጣቸዉ አጀንዳዎች ይፋ ከመሆናቸዉ አስቀድሞ በአጀንዳዎቹ ዙሪያ ከባለሙያዎች ጋር ዉይይት ማድረግ ነበረበት የሚል ሀሳብ በዚህ ዉይይት  ተንፀባርቋል። ኮሚሽኑ ለጉባኤው ስምንት ያህል አጀንዳዎች እንደሚቀርቡ ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን፥ እነዚህ የምክክር አጀንዳዎች ዙሪያ ባለሙያዎቹ ሀሳባቸውን ተናግረዋል። ከዚህ ዉስጥ የሆኑት ዶ/ር የማርሸት ታደሰ  አንዳንድ አጀንዳዎች የተበታተኑ የሚመስሉ ሆነዉ እንደሚታዩ ተናግረዋል። በእነዚህ አጀንዳዎች ዉስጥ ያሉ የተጠያቂነት፣የእርቅ እና የይቅርታ ይዘት ያላቸዉ ጉዳዩች የተበታተኑ ሆነዋልም ይላሉ። ለማሳያም የአጀንዳ 4፣5 እና 8 ላይ ያሉ ይዘቶችን ጠቅሰዋል። ዶ/ር የማርሸት የተበታተኑ የሚመስሉ አጀንዳዎች በመጨረሻዉ ምክረሀሳብን  ለመፃፍ እንደሚያስቸግር ይገልፃሉ። በዚህም የተበታተኑ ጉዳዮችን ሰብሰብ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። በዉይይት መድረኩ ሌላዉ ከተሳታፊ ባለሙያዎች የተነሳዉ ጥያቄ በአጀንዳ ሶስት ላይ የተቀመጠዉ የፌደራል ከተሞች ጉዳይን የተመለከተዉ ነዉ። በዚህ የአጀንዳ ክፍል ይዘት የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማን በተናጠል አጀንዳ አድርጎ ማቅረብ ያስፈለገበትን ምክንያት ኮሚሽኑ እንዲያስረዳ ተጠይቋል። ይህ የአጀንዳ ክፍል በአጀንዳ ሁለት ከተቀመጠዉ የመንግስት አወቀቀር ጉዳይ በሚለው አጀንዳ ስር  መካተት የነበረበት እንደሆነም ተነስቷል። የኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች በዚህ አጀንዳ ክፍል የተነሳዉን የባለሙያዎች ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡም፥በአዲስ አበባ እና ድሬደዋ ጉዳይ ዙሪያ ከህገመንግስት አቀራረፅ እስከ ስልጣን ክፍፍል ጥያቄ የሚነሳበት መሆኑን ገልፀዋል። በእነዚህ ከተሞች ዙሪያ ራሱን የቻለ አጀንዳ አድርጎ ለማስቀመጥ የነበሩ ጥያቄዎችን መሠረት ያደረገ በመሆኑ ራሳቸዉን ችለዉ በአጀንዳነት እንዲቀርቡ ሆኗል ሲሉም ኮሚሽነሮቹ ምላሽ ሰጥተዉበታል። ከዚህ ውጭ በምክክር ወቅት ሙያዊ ማብራሪያ ከሚያቀርቡ ባለሙያዎች ጋር በነበረዉ ዉይይት፥ሙስና እና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች የያዘዉ የአጀንዳ ክፍል በምክክሩ ወቅት ሊኖረዉ ስለሚችለዉ ጭብጥ እና ፋይዳ ተጠይቋል። የመካተቱ አስፈላጊነትም ጥያቄ የተነሳበት እና የሚታይበት ሌላ ሁኔታ ሊኖር እንደሚገባዉ ተነስቷል። ኮሚሽኑ ሙስናን በአጀንዳነት ማካተት ሙስናን የተመለከቱ ህጎች ተፈፃሚነት አነስተኛ የመሆን እና ያሉ ህጎችም በቂ ያለመሆን ነገር በአጀንዳነት ለመቅረቡ እንደምክንያት አቅርቧል። ኮሚሽኑ ለጉባኤዉ የሚሰይመዉ የባለሙያዎች ቡድን ቴክኒካዊ ምክር መስጠት፣ ጥናትና ትንተና ማካሄድ፣ የመነሻ ሰነዶችን ማዘጋጀት፣ ውስብስብ ፅንሰ ሀሳቦችን በቀላሉ ማብራራት የምክክር ቡድኖችን መደገፍ፣ እንዲሁም የመጨረሻ ምክረ ሐሳቦችን ማዘጋጀት የሚጠበቅበት ይሆናልም ተብሏል። ቁምነገር አየለ ሰኔ 25/2018 ዓ.ም
1 686
12
+1
بدون متن...
1 621
13
ገዳ ባንክ 1 ቢሊየን ብር በማትረፍ አጠቃላይ ሀብቱ 16.6 ቢሊየን ብር መድረሱን ገለፀ የገዳ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ወልዴ ቡልቱ ባንኩ በ2018 የበጀት ዓመት ያስመዘገበውን የሥራ አፈጻጸም ይፋ ባደ+2
ገዳ ባንክ 1 ቢሊየን ብር  በማትረፍ አጠቃላይ ሀብቱ 16.6 ቢሊየን ብር መድረሱን ገለፀ የገዳ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ወልዴ ቡልቱ ባንኩ በ2018 የበጀት ዓመት ያስመዘገበውን የሥራ አፈጻጸም ይፋ ባደረጉበት ወቅት፥ባንኩ በበጀት ዓመቱ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር ከሁለት እጥፍ በላይ ወይም የ1መቶ13 በመቶ ዕድገት በማሳየት ከታክስ በፊት 1 ቢሊየን ብር ማትረፍ መቻሉን አስታውቀዋል። እንደ ፕሬዝዳንቱ ገለፃ የባንኩ አጠቃላይ ሀብት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ64 በመቶ ከፍተኛ ዕድገት በማስመዝገብ 16.6 ቢሊየን ብር ደርሷል። በተመሳሳይ ሁኔታ የደንበኞች የተቀማጭ ሀብት በ64 በመቶ በማደግ 12.64 ቢሊየን ብር መድረስ ችሏል። ባንኩ በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ የቅርንጫፎቹን ቁጥር 1መቶ10 ማድረሱ የተገለፀ ሲሆን፥ ከነዚህም መካከል 10 ያህሉ ቅርንጫፎች በዘንድሮው የበጀት ዓመት የተከፈቱ  መሆናቸው ተጠቁሟል:: በተጨማሪም የባንኩን ዘላቂ ዕድገትና ጥንካሬ የሚያበስረው የዋና መሥሪያ ቤት ሕንፃ ግንባታ ሒደት በይፋ መጀመሩን አቶ ወልዴ ቡልቱ አንስተዋል። ባንኩ አሁን ላይ ለአምስት ዓመታት የሚያገለግሉ ስትራቴጂዎችን ቀርጾ ማጽደቅ ችሏል ያሉት ፕሬዝዳንቱ፥እነዚህ ስትራቴጂዎች በተለይም የባንኩን የውስጥና የቴክኖሎጂ ደህንነት ማጠናከር ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ገዳ ባንክ "የአዲሱ ትውልድ ባንክ" በሚለው መሪ ቃሉ መሰረት ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ቀልጣፋ የባንክ አገልግሎትን በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በማስፋፋት በአጭር ጊዜ ውስጥ ትልቅ የገበያ ድርሻ መያዝ መቻሉን በተግባር እንዳሳየም አንስተዋል። ሀና ሰይፉ ሰኔ 25/2018 ዓ.ም
1 846
14
ናይጀሪያ ዜጎቼ ላጡት ንብረት ካሳ እፈልጋለሁ አለች ናይጄሪያ ሕገ ወጥ ስደተኞችን ያነጣጠሩ የቅርብ ጊዜ ተቃውሞዎችን ተከትሎ አገሪቱን ለቀው ለወጡ ዜጎቿ ከደቡብ አፍሪካ መንግሥት ካሳ እንደምትጠይቅ+1
ናይጀሪያ  ዜጎቼ  ላጡት ንብረት ካሳ እፈልጋለሁ አለች ናይጄሪያ ሕገ ወጥ ስደተኞችን ያነጣጠሩ የቅርብ ጊዜ ተቃውሞዎችን ተከትሎ አገሪቱን ለቀው ለወጡ ዜጎቿ ከደቡብ አፍሪካ መንግሥት ካሳ እንደምትጠይቅ  አስታውቃለች። የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኪሚኢቢ ኢሞሞቲሚ ለቢቢሲ እንደተናገሩት፥ ይህ ጉዳይ በሁለቱ መንግሥታት መካከል በከፍተኛ ደረጃ ውይይት ይደረግበታል ብለዋል። በደቡብ አፍሪካ የናይጄሪያ ጊዜያዊ ከፍተኛ ኮሚሽነር አሌክሳንደር አጃዪ መንግሥት በናይጄሪያውያን የተተዉ የንግድ ተቋማትን እና ንብረቶችን መመዝገብ ጀምሯል ማለታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል። በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ከ600 በላይ ናይጄሪያውያን ወደ አገራቸው ተመልሰዋል። የደቡብ አፍሪካ ባለሥልጣናት ወደ አገራቸው የሄዱ ሰዎች በአገሪቱ ውስጥ በሕገ ወጥ መንገድ ይኖሩ የነበሩ ናቸው ቢሉም ናይጄሪያ ግን ነገሩን አስተባብላለች። አንዳንድ ስደተኞችን የሚቃወሙ ቡድኖች ሕገ ወጥ የውጭ አገር ዜጎችን የሚቃወሙ ሰልፎች በቀጣይ ሳምንታት እንደሚቀጥሉ የተናገሩ ሲሆን፥ ማክሰኞ ዕለትም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የተሳተፉበት ሰልፍ ተደርጎ ነበር። ሰልፎቹ በአብዛኛው ሰላማዊ የነበሩ ቢሆንም በውጭ አገር ዜጎች ላይ የተነጣጠሩ የተናጠል የጥቃት ክስተቶች ታይተዋል ሲል ቢቢሲ አክሎ አስነብቧል። ሀናን ሽምሱ ሰኔ 25/2018 ዓ.ም
1 804
15
ናይጀሪያ ዜጎቼ ላጡት ንብረት ካሳ እፈልጋለሁ አለች ናይጄሪያ ሕገ ወጥ ስደተኞችን ያነጣጠሩ የቅርብ ጊዜ ተቃውሞዎችን ተከትሎ አገሪቱን ለቀው ለወጡ ዜጎቿ ከደቡብ አፍሪካ መንግሥት ካሳ እንደምትጠይቅ+1
ናይጀሪያ  ዜጎቼ  ላጡት ንብረት ካሳ እፈልጋለሁ አለች ናይጄሪያ ሕገ ወጥ ስደተኞችን ያነጣጠሩ የቅርብ ጊዜ ተቃውሞዎችን ተከትሎ አገሪቱን ለቀው ለወጡ ዜጎቿ ከደቡብ አፍሪካ መንግሥት ካሳ እንደምትጠይቅ  አስታውቃለች። የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኪሚኢቢ ኢሞሞቲሚ ለቢቢሲ እንደተናገሩት፥ ይህ ጉዳይ በሁለቱ መንግሥታት መካከል በከፍተኛ ደረጃ ውይይት ይደረግበታል ብለዋል። በደቡብ አፍሪካ የናይጄሪያ ጊዜያዊ ከፍተኛ ኮሚሽነር አሌክሳንደር አጃዪ መንግሥት በናይጄሪያውያን የተተዉ የንግድ ተቋማትን እና ንብረቶችን መመዝገብ ጀምሯል ማለታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል። በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ከ600 በላይ ናይጄሪያውያን ወደ አገራቸው ተመልሰዋል። የደቡብ አፍሪካ ባለሥልጣናት ወደ አገራቸው የሄዱ ሰዎች በአገሪቱ ውስጥ በሕገ ወጥ መንገድ ይኖሩ የነበሩ ናቸው ቢሉም ናይጄሪያ ግን ነገሩን አስተባብላለች። አንዳንድ ስደተኞችን የሚቃወሙ ቡድኖች ሕገ ወጥ የውጭ አገር ዜጎችን የሚቃወሙ ሰልፎች በቀጣይ ሳምንታት እንደሚቀጥሉ የተናገሩ ሲሆን፥ ማክሰኞ ዕለትም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የተሳተፉበት ሰልፍ ተደርጎ ነበር። ሰልፎቹ በአብዛኛው ሰላማዊ የነበሩ ቢሆንም በውጭ አገር ዜጎች ላይ የተነጣጠሩ የተናጠል የጥቃት ክስተቶች ታይተዋል ሲል ቢቢሲ አክሎ አስነብቧል። ሀናን ሽምሱ ሰኔ 25/2018 ዓ.ም
1
16
በሰነዶች ማረጋገጫ ንብረት ገዝተው ስም ያላዛወሩ ዜጎች በአስቸኳይ ይዞታቸውን እንዲያስመዘግቡ ተጠየቀ ቀደም ባሉ ጊዜያት ከሪል እስቴት አልሚዎችም ሆነ ከግለሰቦች ጋር የቤት ወይም የመሬት ግብይት ፈጽ
በሰነዶች ማረጋገጫ ንብረት ገዝተው ስም ያላዛወሩ ዜጎች በአስቸኳይ ይዞታቸውን እንዲያስመዘግቡ ተጠየቀ   ቀደም ባሉ ጊዜያት ከሪል እስቴት አልሚዎችም ሆነ ከግለሰቦች ጋር የቤት ወይም የመሬት ግብይት ፈጽመው፣ በሰነዶች ማረጋገጫ ብቻ የያዙና እስካሁን የስመ-ንብረት ዝውውር ያላደረጉ አካላት በአስቸኳይ ሂደቱን እንዲያጠናቅቁ  ጥሪ ቀረበ ።   የከተማ አስተዳደሩ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ መኮንን ያኢ እንደገለጹት፤ ግዢ ፈጽመው የስም ዝውውር ያላደረጉ ወገኖች ለከፍተኛ ጉዳትና ለአደጋ እየተጋለጡ ይገኛሉ።   የስመ-ንብረት ዝውውር ዋና ዓላማ አንድ ግለሰብ ያፈራውን ንብረት ለሌላ አካል የሚያስተላልፍበት ሕጋዊ ሥርዓት መሆኑንና የመጨረሻው መዳረሻም የይዞታ ማረጋገጫ (ካርታ) ማግኘት መሆኑን ኃላፊው አስረድተዋል።   በመሆኑም ባለንብረቶች መብታቸውን ለማስከበርና ንብረታቸውን ከማንኛውም ሕጋዊ ስጋት ለመጠበቅ ሲሉ፣ ሳይዘገዩ ወደ መሬት ተቋማት በመቅረብ ሂደቱን እንዲያጠናቅቁ የከተማ አስተዳደሩ ጥሪ አቅርቧል።   ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም
1 539
17
ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት የማሊ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ኒጀር ከአባልነት መውጣት እንዳሳሰበዉ ገለጸ ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ማሊ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ኒጀር ከአባልነት መውጣታቸው ዓለ+1
ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት የማሊ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ኒጀር ከአባልነት መውጣት እንዳሳሰበዉ ገለጸ ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ማሊ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ኒጀር ከአባልነት መውጣታቸው ዓለም አቀፍ የፍትህ ሂደትን ያዳክማል በሚል ስጋቱን ገልጿል። መቀመጫውን በሄግ ያደረገው ፍርድቤቱ ፤በጦር ወንጀሎች እና በሰብአዊነት ላይ በሚፈጸሙ ወንጀሎች ግለሰቦችን የሚከስና ለፍርድ የሚያቀርብ ተቋም ነው። እነዚህ ሦስቱ በወታደራዊ አመራር የሚተዳደሩ የምዕራብ አፍሪካ አገራት ባለፈው ዓመት ከፍርድ ቤቱ የወጡ ሲሆን፤ ተቋሙን ‹‹በኢምፔሪያሊዝም እጅ ያለ አዲሱ የቅኝ አገዛዝ ጭቆና መሣሪያ›› ሲሉ ጠርተውታል። ሦስቱ የቀድሞ የኤኮዋስ አባላት በ2024 የሳህል አገራት ጥምረትን መመስረታቸዉ ይታወሳል፡፡ የፍርድ ቤቱን አባል አገራት የሚወክለው የICC አባል አገራት ጉባኤ፤ በአገራቱ መውጣት መጸጸቱን ገልጿል። ተቋሙ ባወጣው መግለጫ፤ አገራት ከፍርድ ቤቱ መውጣታቸው ‹‹የጋራ የፍትህ ፍለጋን አደጋ ላይ ይጥላል፤ እንዲሁም ወንጀል ሰርቶ ያለቅጣት የመቅረትን ባህል ለማስቆም የሚደረገውን ዓለም አቀፍ ጥረት ያዳክማል›› ብሏል። ፍርድ ቤቱ ቡርኪና ፋሶ፣ ማሊ እና ኒጀር በሮም ደንቡ አባልነታቸው እንዲቀጥሉ እና በአባል አገራት ጉባኤ ማዕቀፍ ውስጥ ገንቢ ተሳትፎ ማድረጋቸውን እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርቧል። ከሮም ደንብ መውጣት አንድ አገር የደንቡ አባል በነበረበት ወቅት የነበሩበትን ግዴታዎች እንደማያስቀር ፍርድቤቱ አስታውሷል። ፍርድ ቤቱ በአሁኑ ወቅት 1መቶ25 አባላት ያሉት ቢሆንም ቻይና፣ ህንድ፣ ሩሲያ፣ አሜሪካ እና እስራኤልን ጨምሮ በርካታ ዋና ዋና ኃያላን አገራት እስካሁን አባል አልሆኑም። እስከዳር ግርማ ሰኔ 25/2018 ዓ.ም
1 425
18
ኢራንና አሜሪካ በዶሀ የነበራቸው ስምምነት መጠናቀቁን ተከትሎ የነዳጅ ዋጋ በድጋሚ ቀነሰ ዩኤስ እና ኢራን በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ ትኩረት አድርገው የነበረበት የዶሃው ውይይት መጠናቀቁን ተከትሎ የነዳጅ ዋጋ ለተከታታይ ሶስት ቀናት መቀነሱን አለም አቀፍ ሚዲያዎች እየዘገቡት ይገኛሉ። ኢራን እና ዩናይትድ ስቴትስ በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ዙሪያ ባደረጉት ንግግር ላይ መሻሻል ማሳየታቸውን ኳታር ማስታወቋን ተከትሎ ነው የአቅርቦት መቋረጥ ስጋት በመቀነሱ የነዳጅ ዋጋ ሐሙስ ዕለት ለሶስተኛ ተከታታይ ቀን የቀነሰው። የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ የወደፊት ዋጋ በ66 ሳንቲም ወይም በ0.92 በመቶ ቅናሽ አሳይቶ በባሬል 70.91 ዶላር የደረሰ ሲሆን፣ የዩናይትድ ስቴትስ ዌስት ቴክሳስ ኢንተርሚዲየት ደግሞ በ59 ሳንቲም ወይም በ0.86 በመቶ በመቀነስ በባሬል 67.99 ዶላር ሆኗል። ይህም ካለፈው የካቲት 27 ጀምሮ የታየው ዝቅተኛው የዋጋ ደረጃ ነው ሲል ሮይተርስ በዘገባው አስነብቧል። የኳታር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ በኤክስ ማህበራዊ ገጽ ላይ ባሰፈሩት ጽሑፍ፣ ንግግሩ በሰኔ ወር ጦርነቱን ባቆመው የመግባቢያ ሰነድ ላይ ባሉ ጉዳዮች ዙሪያ "አዎንታዊ መሻሻል" አሳይቷል ማለታቸውን ነው የተነገረው። ሮይተርስ ባስነበበው ዘገባ እንዳለው ሁለቱ ወገኖች ዘላቂ ሰላም ለማምጣት መሻሻል ማሳየታቸውን የሚጠቁም ምንም ምልክት እስካሁን አልታየም። በኢራን እና በዩኤስ ተደራዳሪዎች መካከል የሚቀጥለው ስብሰባ ከሐምሌ 9 በኋላ የሚካሄድ ሲሆን ይህም በቅርቡ ከዚህ ዓለም በሞት ለተለዩት የኢራኑ ከፍተኛ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ ከሚደረገው የቀብር ሥነ ሥርዓት በኋላ መሆኑን የኳታሩ ሚኒስቴር አክሎ ገልጿል። ኢራን በባህር ወሽመጥ ላይ ያላትን ቁጥጥር እና ወደ ባሕረ ሰላጤው በሚገቡ ወይም በሚወጡ መርከቦች ላይ ክፍያ የመጣል አቅሟን በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ለማግኘት ቆርጣ የተነሳች መሆኗን ሁለት ከፍተኛ የኢራን ምንጮች ገልጸዋል። ይህንን ግብ ለማሳካት አስፈላጊ ከሆነ ኃይል የመጠቀም ፍላጎት እንዳላትም ጠቁመዋል። ሀናን ሸምሱ ሰኔ 25/2018 ዓ.ም
1 493
19
بدون متن...
1 342
20
ሩሲያ የሚሳኤል እና የሰው አልባ አውሮፕላን በመጠቀም በዪክሬን ዋና ከተማ በኪየቭ ላይ በፈጸመችው ጥቃት 13 ሰዎች ተገደሉ ። የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ሩሲያ ለ ትልቅ ጥቃት እየተዘጋጀ
ሩሲያ የሚሳኤል እና የሰው አልባ አውሮፕላን በመጠቀም በዪክሬን ዋና ከተማ በኪየቭ  ላይ በፈጸመችው ጥቃት 13 ሰዎች ተገደሉ ። የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ሩሲያ ለ ትልቅ ጥቃት እየተዘጋጀች መሆኗን ካስጠነቀቁ ከሰዓታት በኋላ በከተማው ውስጥ ያሉ ሕንፃዎችን እና በርካታ ሰፈሮች ፈርሰዋል ። የኪየቭ ወታደራዊ አስተዳደር ኃላፊ የሆኑት ቲሙር ተካቼንኮ እንደገለጹት ከሞቱ ሰዎች መካከል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ህጻናት ይገኙበታል ብለዋል። የዩክሬን አየር ሃይል በበኩሉ ሩሲያ 74 ሚሳኤሎችን እና 496 ሰው አልባ አውሮፕላኖችን በዋነኛነት በመዲናዋ ላይ ማስወንጨፏን አስታውቋል። የሀገሪቱ መከላከያ ሃይል ከእነዚህ ውስጥ አብዛኞቹን መመከት ሲችል 25 የባለስቲክ ሚሳኤሎች እና 12 ሰው አልባ አውሮፕላኖች አና 33 ቦታዎችን መትተዋል። በከተማዋ በርካታ የእሳት ቃጠሎዎች የተከሰቱ ሲሆን በከተማው በሚገኝ የአምቡላንስ ጣቢያ ላይ ጉዳት መድረሱን እና ይህም ቢያንስ በአንድ ሰው ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ማድረሱን ቢቢሲ ዘግቧል ። የሀገሪቱ የድንገተኛ አደጋ መከላከል አገልግሎት 13 ሰዎች መሞታቸውን እና ከ30 በላይ ሰዎች ቆስለዋል ብሏል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንድሪ ሲቢሃ የዩክሬን አጋሮች ተጨማሪ የአየር መከላከያ ዘዴዎችን እንዲልኩ ጠይቀው ሀገሪቱ የሩሲያ ሽብርን ለማስቆም የውግዘት ቃላት ብቻ ሳይሆን ተጨባጭ እርምጃ ያስፈልጋታል ሲሉ መናገራቸውን ቢቢሲ ገልጿል ። ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ህዝቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ፣ እራሱን እና ልጆቹንም እንዲጠብቅ አሳስበዋል።   ሰላማዊት ዲታ   ሰኔ 25/2018 ዓ.ም
1 661