Ethio Fm 107.8
በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام Ethio Fm 107.8
کانال Ethio Fm 107.8 (@ethiofm107dot8) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 18 485 مشترک است و جایگاه 12 078 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 1 847 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 18 485 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 31 اوت, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -10 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -7 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 9.92% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 7.42% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 1 835 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 1 371 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 3 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 01 سپتامبر, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 01 سپتامبر | 0 |
7መቶ 8ሺህ 266 ኩንታል ቀይ ሽንኩርትእንደሚቀርብ የተናገሩት የቢሮዉ ሀላፊ ሀቢባ ሲራጅ ፤ 227 ሺህ 8 መቶ 85 ኩንታል የጤፍ ምርት ለማቅረብ መታቀዱን በመግለጫቸው ገልፀዋል። ከ3.7 ሚሊዮን ሊትር በላይ ፈሳሽ የምግብ ዘይት ለኅብረተሰቡ ለማቅረብ ዝግጅት መጠናቀቁን የቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ሃላፊ ሀቢባ ሲራጅ ተናግረዋል። ለህብረተሰቡ በጥራትና በበቂ ሁኔታ ለማዳረስ ሲባል የሰብል፣ የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የፋብሪካ ምርቶች መሸጫ ማዕከላት አገልግሎቱ እንዲሰጡ ይደረጋል ተብሏል። 5 የቀንድ እንስሳት መሸጫ ማዕከላት እና 2መቶ 64 የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች በሳምንቱ ሙሉ ክፍት ሆነው አገልግሎት እንዲሰጡ መወሰኑን ሀላፊዋ ጠቁመዋል። ሊዲያ ደሳለኝ ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም
| 2 | بدون متن... | 385 |
| 3 | በኔፓል የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከ1,000 በላይ መድረሱ ተገለጸ
በኔፓል በተከሰተው ከባድ የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር 1,003 መድረሱን የአገሪቱ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ባለስልጣን አስታወቀዋል።
ባለስልጣኑ ዛሬ ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው፣ከሟቾቹ በተጨማሪ በርካታ ሰዎች የደረሱበት ያልታወቀ ሲሆን፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
የነፍስ አድን ሰራተኞች አሁንም አስከሬኖችን ፍለጋ እና በጎርፍ የተከበቡ ሰዎችን የማውጣት ስራቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል።
በጎርፉ ምክንያት በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ ሲሆን፣ በመሰረተ ልማቶችና በመኖሪያ ቤቶች ላይም ከፍተኛ ውድመት መድረሱ ተገልጿል።
የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ባለስልጣኑ የሟቾች ቁጥር አሁንም ሊጨምር እንደሚችል ስጋቱን ገልጿል።
ልዑል ወልዴ
ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም | 968 |
| 4 | በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚታየውን የሪፖርት መዛባት የሚቀርፍ አዲስ ስታንዳርድ ይፋ ሆነ
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን፣ የኮንስትራክሽን ማናጅመንት ኢንስቲትዩት እና የሚድሮክ ኮንሰልቲንግ አርክቴክትስና ኢንጅነርስ በመተባበር ያዘጋጁት አዲስ የግንባታ ፊዚካል አፈጻጸም መለኪያና የሪፖርት ማዕቀፍ ስታንዳርድ ይፋ ተደርጓል።
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መስፍን ነገዎ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ እስካሁን በዘርፉ ወጥ የሆነ የግንባታ አፈጻጸም መለኪያ ባለመኖሩ ምክንያት ፕሮጀክቶችን በጊዜ፣ በወጪና በጥራት ለመቆጣጠር አዳጋች ሆኖ ቆይቷል።
ይህ አዲስ ስታንዳርድ "ትክክለኛ መረጃ፣ ትክክለኛ መለኪያ፣ ተዓማኒነት ያለው ሪፖርት እና ትክክለኛ ውሳኔ" የሚለውን የሥራ ሰንሰለት በተግባር ለማዋል ያለመ ነው ተብሏል።
በተለይም በተለያዩ ተቋማትና ፕሮጀክቶች መካከል የሚታየውን የሪፖርት አለመጣጣም በመቅረፍ፣ የግንባታ አፈጻጸም ግምገማን ግልጽና ተነጻጻሪ ለማድረግ ከፍተኛ እገዛ እንደሚኖረው ተጠቁሟል።
በዝግጅቱ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ የክልልና የፌዴራል የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የዘርፉ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
አዲስዓለም አበበ
ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም | 918 |
| 5 | የሮቦት ማፅጃ ካሜራን በመጠቀም ሚስጥራዊ ምስል የቀረፀው የታይዋን ዜጋ በእስራትና በገንዘብ ተቀጣ
አንድ የታይዋን ዜጋ የባለቤቱን ሌላ የፍቅር ግንኙነት በሮቦት የቤት ማፅጃ ካሜራ አማካኝነት ያለፍቃዷ ቀርፆ በመያዙ በአምስት ወር የእስራት ፍርድ እና በ150,000 የታይዋን ዶላር መቀጮ ተቀጥቷል።
ግለሰቡ በ2023 በሁለተኛ መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ በተፈጠረ ጥርጣሬ ተነሳስቶ፣ በሞባይል መተግበሪያ የቤቱን ሮቦት ማፅጃ በርቀት በማስነሳት ባለቤቱ ከሌላ ወንድ ጋር ሆና በካሜራ ይዟታል።
ባል ምስሉን ለቀጣይ የሕግ ክስ እንደ ማስረጃ ለመጠቀም በማሰብ መቅረፁን የቀጠለ ሲሆን፣ በቪዲዮው ታግዞም ለደረሰበት የሞራል ጉዳት ከባለቤቱና ከፍቅር አጋሯ 500,000 የታይዋን ዶላር ካሳ አግኝቷል።
ሆኖም ግን፣ ስኬቱ ባለቤቱ ባቀረበችበት የመልስ ክስ ምክንያት ጥላ ያረፈበት ሆኗል።
በሮቦት ማፅጃው የተቀረፀው የቪዲዮ ማስረጃ የባለቤቱን አለመታመን ያረጋገጠ ቢሆንም፣ ሁለቱን ፍቅረኞች ያለፍቃዳቸው መቅረፁንም አረጋግጧል።
ባል ድርጊቱ ተገቢ እንደነበር ቢከራከርም፣ ፍርድ ቤቱ ግን የጋብቻ ግዴታዎች የሰዎችን የግል ሕይወት የመጠበቅ መብት አያልፉም በማለት ውድቅ አድርጎታል።
በዚህም መሠረት በታይዋን ሕግ የሰዎችን የግል እንቅስቃሴ ያለፍቃዳቸው መቅረፅ ወንጀል በመሆኑ፣ ባል የካሳ አሸናፊ ቢሆንም በወንጀሉ ምክንያት የእስራትና የገንዘብ መቀጮ ፍርድ ተፈርዶበታል።
ሐመረ ፍሬው
ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም | 877 |
| 6 | በሶሪያ ሱዌዳ ግዛት በተቀሰቀሰ ግጭት 10 የመንግስት የጸጥታ አባላት ቆሰሉ
በደቡባዊ ሶሪያ፣ አብዛኛው ነዋሪ የድሩዝ ማህበረሰብ በሆነባት ሱዌዳ ግዛት፣ በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች እና በአካባቢው ታጣቂ ቡድኖች መካከል ግጭት መከሰቱ ተነግሯል ።
የሶሪያ የመንግስት መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት ከሆነ፣ በዚህ ግጭት 10 የመንግስት የጸጥታ አባላት ላይ የመቁሰል አደጋ ደርሷል።
ግጭቱ የተቀሰቀሰው በጸጥታ ኃይሎች እና በአካባቢው ባሉ ታጣቂዎች መካከል በነበረ የቃላት ምልልስ እና አለመግባባት እንደሆነ ተገልጿል።
የሱዌዳ ግዛት ለዓመታት ከመንግስት ጋር በተያያዘ በተቃውሞዎች እና አልፎ አልፎ በሚከሰቱ ግጭቶች የምትታወቅ ሲሆን፣ የዛሬው ግጭትም በቀጠናው ያለውን ውጥረት ዳግም እንዳባባሰው ተዘግቧል።
ስለ ታጣቂዎቹ ጉዳት እስካሁን የተገለጸ መረጃ የለም።
ልዑል ወልዴ
ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም | 423 |
| 7 | በኔፓል በጭቃ በተሞሉ ዋሻዎች ዉስጥ ይገኛሉ የተባሉ ከ6መቶ በላይ ሠራተኞችን ለማዳን አደገኛ የፍለጋ ሥራ እየተከናወነ ነው
በኔፓል ትሪሹሊ ወንዝ ዳርቻ በተቆፈሩ እና በጭቃ በተሞሉ ረጅም ዋሻዎች ውስጥ ተቀርቅረዋል ተብለው የሚገመቱ ከ600 በላይ ሠራተኞች፤ ቤተሰቦች እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው በሕይወት ይገኛሉ የሚል ተስፋ ሰንቀዋል።
የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች የተረፉ ሰዎችን ለማዳን ያለው ወሳኝ ጊዜ እያለቀ ነው ከሚል ስጋት በመነሳት ወደ ትሪሹሊ-3ኤ ፕሮጀክት ቦታ አዉሮፕላን ለማስገባትና መንገድ ለመክፈት ኮረብታውን በፈንጂ በማፈንዳት የሕይወት አድን ጥረታቸውን ቀጥለዋል።
በኔፓል እና ቲቤት ድንበር ላይ በደረሰው የጎርፍ አደጋ የሞቱት ሰዎች ቁጥር 9መቶ39 መድረሱን የሀገሪቱ የአደጋ ስጋት አመራር ባለስልጣን አስታውቋል።
መሥሪያ ቤቱ የጠፉ ሰዎች ቁጥር 3ሺ9መቶ25 መድረሱን የገለጸ ሲሆን፤ከነዚህም መካከል 5መቶ92 ያህሉ የውጭ ሀገር ዜጎች እንደሆኑ አሳውቋል።
የኔፓል ጠቅላይ ሚኒስትር ባሌንድራ ሻህ እንደተናገሩት፤ በሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫዎች ውስጥ ይሠሩ ከነበሩ ሠራተኞች መካከል 2 መቶ79 ሰዎች መዳናቸውን ገልጸዋል።
የማዳን ሥራው በቻይና እና ኔፓል ወታደራዊ አባላት በተቋቋመ ዓለም አቀፍ ቡድን እየተመራ የሚገኝ ሲሆን፤በተጨማሪም የሕንድ፣ የኮሪያ እና የአውስትራሊያ ባለሙያዎች በሥራው ላይ በመሳተፍ ላይ ናቸው።
ነገር ግን ከነፍስ አድን ሰራተኞች መካከል አንድ ቡድን ሰኞ ዕለት ማለዳ ወደ አንዱ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ በሚወስደው ዋሻ ውስጥ መግባት የቻለ ቢሆንም ምንም ሰው ሳያገኝ ተመልሷል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደተናገሩት፤ የሕይወት አድን ሥራው ተጠናክሮ መቀጠሉን አንስተዉ፤ በሀገሪቱ ጎርፉ ‹‹የተለመደ›› ክስተት አለመሆኑንም ጠቁመው፤ ይህ አጋጣሚ በሂማላያ ክልል ውስጥ የሚገጥሙን አደጋዎች ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ እየጨመሩ መሆናቸውን ያሳያል ብለዋል።
ሀና ሰይፉ
ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም | 879 |
| 8 | بدون متن... | 787 |
| 9 | ቴህራን በቂ የውጭ ምንዛሬ አላት ሲሉ የኢራን ማዕከላዊ ባንክ ገዢ ለትራምፕ ተናገሩ
ማዕከላዊ ባንኩ 2 ቢሊየን ዶላር ወደ ምንዛሬ ገበያው ለማስገባት ዝግጁ መሆኑ ተገልጿል፡፡
ምንም እንኳን የአሜሪካ ማዕቀብ እና የኢኮኖሚ ጫና ቢበረታም፤ኢራን በቂ የውጭ ምንዛሬ እንዳላት የማዕከላዊ ባንክ ገዢ አብዱልናስር ሄማቲ ተናግረዋል።
ተስኒም የዜና ወኪል እንደዘገበው፤ማዕከላዊ ባንኩ 2 ቢሊየን ዶላር ወደ ውጭ ምንዛሬ ገበያው ለማስገባት ዝግጁ ነው።
የአሜሪካን የኢኮኖሚ ውድቀት ክስ ውድቅ ያደረጉት ሄማቲ፤ኢራን የውጭ ምንዛሬ ገቢዎችን እና ተከፋይ ሂሳቦችን መሰብሰቧን እንደቀጠለች ገልጸው፤ዝርዝራቸው ሊገለጽ የማይችል የአገር ውስጥ ክምችትና ሌሎች ሀብቶች እንዳሏትም ተናግረዋል።
የአገሪቱ የኢኮኖሚ ሥርዓት በአዲሱ ማዕቀብ ውስጥም መስራቱን እንደቀጠለ የገለጹት ሄማቲ፤የሪያል ዋጋ በቅርቡ መውረድ በአብዛኛው ከሥነ-ልቦናዊ ሁኔታዎች ጋር የተያያዘ መሆኑን ጠቁመዋል።
ኢራን ወደ ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት ውስጥ ገብታለች የሚለውን ሀሳብ ውድቅ በማድረግ፤ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት እና ሰፊ የኢኮኖሚ ጫና ቢኖርም ይህ የመከሰቱ ዕድል አነስተኛ መሆኑን ተናግረዋል።
በጦርነቱ እና በአንዳንድ መሰረተ ልማቶች ላይ በደረሰው ውድመት ምክንያት የስራ አጥነት ቁጥር መጨመሩን ያመኑት ሄማቲ፤በሁለተኛው የኢራን ዓመት አጋማሽ ላይ ለአነስተኛ እና መካከለኛ ንግዶች የፋይናንስ ድጋፍ ቅድሚያ እንደሚሰጥ አክለዋል።
እነዚህ አስተያየቶች የተሰጡት የኢራን ሪያል ከአሜሪካ ዶላር ጋር ባለው ዋጋ ላይ አዲስ ተጽዕኖ እየገጠመው ባለበት እና በአሜሪካ-እስራኤል ጦርነት የኢኮኖሚ መዘዝ እንዲሁም በጠነከረው የአሜሪካ ማዕቀብ ወቅት ነው።
ዋሽንግተን በቅርቡ በቴህራን ላይ የምታደርገውን የኢኮኖሚ ጫና ዘመቻ ያሰፋች ሲሆን፤ ዋና ዋና የኢራን ገቢ ምንጮችን እና ዓለም አቀፍ ንግድን ኢላማ አድርጋለች።
ኢራን እና አሜሪካ በሰኔ ወር ጦርነቱን ለማቆም ያለመ ባለ 14 ነጥብ የመግባቢያ ስምምነት ቢፈራረሙም፤ ጊዜያዊ ስምምነቱ ግን በፍጥነት መፍረሱ ይታወሳል።
ሀና ሰይፉ
ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም | 845 |
| 10 | بدون متن... | 749 |
| 11 | በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ውጥረት በማገርሸቱ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አሳየ
ከሳምንታት አንጻራዊ ሰላም በኋላ፤ በዩናይትድ ስቴትስ እና በኢራን መካከል የተጀመረው አዲስ ወታደራዊ ፍጥጫ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ስጋት ዳግም ቀስቅሶታል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፤ኢራን በድርጊቷ የምትቀጥል ከሆነ ‹‹በከባድ ሁኔታ›› እንደሚያጠቋት መዛታቸውን ተከትሎ፤በዛሬው ዕለት በዓለም አቀፍ ገበያ የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል።
ይህ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተቀሰቀሰው ወታደራዊ ፍጥጫ እና የቃላት ምልልስ፤ሁኔታው ወደ ሰፊ ቀጣናዊ ጦርነት ሊያመራ ይችላል የሚል ስጋት በኢንቨስተሮች ዘንድ እንዲፈጠር አድርጓል።
በዚህም ምክንያት የነዳጅ ዋጋ ዛሬም ጭማሪው ቀጥሏል፡፡
የነዳጅ ገበያ ተንታኞች እንደሚሉት ከሆነ፤በመካከለኛው ምስራቅ ያለው አለመረጋጋት በቀጠለ ቁጥር የነዳጅ አቅርቦት ላይ መስተጓጎል ሊፈጠር ይችላል የሚለው ስጋት የዋጋ ግሽበትን ሊያባብሰው ይችላል።
ልዑል ወልዴ
ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም | 859 |
| 12 | የስራና ክህሎት ሚኒስቴር በኢንተርፕራይዝ ልማት በኩል 2መቶ95 ቢሊየን ብር የገበያ ትስስር መፈጠሩን ገለፀ
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የዘርፉን የአምስት ዓመታት የልማትና የሪፎርም ጉዞን የሚገመግምበት እና የቀጣይ የልማት ዘመን አቅጣጫዎችን የሚያስቀጥበት ሀገር አቀፍ ጉባኤ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈርያት ካሚል፤ 1መቶ66 ቢሊየን ብር የመንግሥት የብድር ድጋፍ ለኢንተርፕራይዞች መቅረቡን እና 6መቶ23 ሺህ 26 ሄክታር መሬት ለኢንተርፕራይዞች እንዲዘጋጅ መደረጉን አብራርተዋል።
ወ/ሮ ሙፈሪያት ከ2014 እስከ 2018 ዓ.ም ድረስ በሀገር ውስጥ 19 ሚሊየን 40 ሺህ 6መቶ39 የሥራ ዕድሎች መፈጠራቸውን ገልጸዋል።
ሚኒስቴሩ በውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት በኩልም 1 ሚሊየን 6መቶ60 ሺህ 9መቶ81 ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረጉን ሚኒስትሯ አስረድተዋል።
በክህሎት ልማት ዘርፍ ደግሞ ከ20 ሚሊየን በላይ ዜጎች በአጭር ጊዜ ሥልጠና መሳተፋቸውን ገልጸዋል።
ሊዲያ ደሳለኝ
ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም | 841 |
| 13 | ዘለንስኪ ፑቲን ‹‹በግል›› ተጨማሪ ጦርነት ይፈልጋሉ ሲሉ ከሰሱ
የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት እንደተናገሩት አብዛኛው የሩሲያ ማህበረሰብ ጦርነቱ አሁን እንዲቆም ይስማማል፡፡
የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ እንደተናገሩት፤ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በሁለቱ ሀገራት መካከል አምስተኛ ዓመቱን የያዘውን ጦርነት ለመቀጠል ‹‹በግላቸው›› ፍላጎት አላቸው።
ዘለንስኪ ባስተላለፉት መልዕክት፤አብዛኛው የፑቲን የገዛ ማህበረሰብ ጦርነቱ አሁን ላይ እንዲቆም እንደሚስማማ ገልጸዋል።
ለጊዜው ግን በሚያሳዝን ሁኔታ የእኛም ሆነ የአጋሮቻችን መረጃዎች እንዲሁም ከሩሲያ የሚመጡ ምልክቶች ሁሉ እንደሚያመለክቱት የሩሲያው መሪ በግላቸው ተጨማሪ ጦርነት ይፈልጋሉ ብለዋል።
ዘለንስኪ አክለውም ከአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ እና የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አማች ከሆኑት ጃሬድ ኩሽነር ጋር በስልክ መነጋገራቸውን ገልጸዋል።
ውይይቱም ከሩሲያ ወገን ጋር ስለሚደረግ ስብሰባ እና ተጨማሪ ግንኙነት ዝግጅት፤ እንዲሁም ወደ ዩክሬን ሊያደርጉት ስለሚችሉት ጉብኝት የሚመለከት ነበር።
ሩሲያ ጦርነቱን ወደ ማቆም እንድትመጣ ምን መደረግ እንዳለበት ተወያይተናል ብለዋል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ተወካዮች ምን ማሳካት እንደሚችሉ እናያለን። መስከረም ወር ብዙ ነገሮችን ሊለውጥ ይችላል ሲሉ አክለዋል።
እስከዳር ግርማ
ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም | 1 029 |
| 14 | የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 500 አዳዲስ የኤሌክትሪክ አዉቶብሶችን ሊያስገባ ነዉ።
ከኢትዮ ኤፍኤም ጋር ቆይታ ያደረጉት የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል የቢሮ ሀላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው፤የከተማዋን የትራንስፖርት ዘርፍ ወደ ቴክኖሎጂ ለማሸጋገር በተያዘዉ ዕቅድ 5መቶ አዳዲስ የኤሌክትሪክ አውቶቡሶችን ለመግዛት በሂደት ላይ መሆኑን አስታውቋል።
በአሁኑ ወቅት 1መቶ የኤሌክትሪክ አውቶቡሶች አገልግሎት መስጠት የጀመሩ ሲሆን፤ እነዚህ ተሽከርካሪዎች በዘመናዊ ካሜራዎችና በጂፒኤስ የተገጠሙ በመሆናቸው ስምሪታቸውን ከመሃል ሆኖ ለመቆጣጠር አመቺ ሆነዋል ብለዋል።
ይህ የቴክኖሎጂ ሽግግር አውቶቡሶች ከተመደበላቸው መስመር እንዳይወጡና የአገልግሎት ጥራታቸው እንዲጠበቅ ከፍተኛ እገዛ እያደረገ ነው ተብሏል።
አውቶቡሶቹ በውስጣቸው ባላቸው ካሜራ አማካኝነት የአሽከርካሪዎችን ስነ-ምግባርና የተሳፋሪዎችን ደህንነት ለመጠበቅ የሚያስችል አሰራር ተዘርግቶላቸዋል።
የቴክኖሎጂ አጠቃቀሙ በሰው ኃይል የሚደረገውን ቁጥጥር በማቀላጠፍና የህገ-ወጥ ድርጊቶችን ዕድል በማጥበብ ረገድ ትልቅ ለውጥ እያመጣ ነው።
አዲስ አበባ በኤሌክትሪክ ትራንስፖርት አጠቃቀም በአፍሪካ ግንባር ቀደም ከተማ ለመሆን በምታደርገው ጥረት እነዚህ አውቶቡሶች እንደ ትልቅ ምሰሶ እንደሚቆጠሩ ተመልክቷል።
ሊዲያ ደሳለኝ
ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም | 1 787 |
| 15 | አዲስ አበባ በየዓመቱ 100 ሺህ ቤቶችን ለመገንባት ማቀዷን አሳወቀች
አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፉት አምስት ዓመታት ከ496 ሺህ በላይ መኖሪያ ቤቶችን መገንባቱን ተገልጿል፡፡
አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ እንደዘገበው ቢሮው በቀጣዮቹ አምስት ዓመታትም በየዓመቱ 100 ሺህ ቤቶችን ለመገንባት ማቀዱን ገልጿል።
"ባለፉት አምስት ዓመታት በተከናወኑ ሁለገብ የቤት ልማት ሥራዎች ከ496 ሺህ በላይ መኖሪያ ቤቶችን መገንባት ተችሏል" ብለዋል የአዲስ አበባ ከተማ የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ቅድስት ወልደጊዮርጊስ፡፡
ኃላፊዋ እንዳሉት ማኅበራትን በማደራጀት፣ የ40/60 እና የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤት ተጠቃሚዎችን እንዲሁም የመንግሥት ሠራተኞችንና የተለያዩ ኅብረተሰብ ክፍሎችን በማቀፍ የቤት ልማት ሥራዎች ተከናውነዋል።
ነሐሴ 25 /2018 ዓ.ም | 1 611 |
| 16 | የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ገቢ በ2018 በጀት ዓመት 11.2 ቢሊዮን ዶላር ደረሰ
የመንግስትን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ ተከትሎ በ2018 በጀት ዓመት የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ስኬት አስመዝግቧል ብሏል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፡፡
ከወጪ ንግድ 11.2 ቢሊዮን ዶላር በማግኘት የዕቅዱን 119 በመቶ ማሳካት ተችሏል።
በበጀት ዓመቱ መጀመሪያ 9.4 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ የነበረ ቢሆንም፣ የአፈፃፀሙ ውጤት ከቀደመው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በከፍተኛ ደረጃ አድጓል ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በማህበራዊ ትስስር ገጹ እንዳጋራው መረጃ የማዕድን ዘርፍ 5.07 ቢሊዮን ዶላር በማስመዝገብ ቀዳሚውን ስፍራ ሲይዝ፤ የግብርና ምርቶች 3.83 ቢሊዮን ዶላር፣ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ 493 ሚሊዮን ዶላር፣ እንዲሁም የኤሌክትሪክና ሌሎች ዘርፎች 425 ሚሊዮን ዶላር አስገኝተዋል።
ውጤታማ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ የአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ፣ በህገ-ወጥ ንግድ ላይ የተደረገ ጥብቅ ቁጥጥር፣ የዋጋ ተመን ክለሳ እንዲሁም የሎጀስቲክስና የትራንስፖርት መሻሻሎች ለዚህ ታሪካዊ ስኬት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ አበርክተዋል።
ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም | 1 487 |
| 17 | አሜሪካ እና ኢራን ከሳምንታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ተኩስ ተለዋወጡ
የአሜሪካ ኃይሎች በሆርሙዝ ሰርጥ በሚገኘው የላራክ ደሴት ባሉ ሁለት የሮኬት ማስወንጨፊያዎች ላይ ጥቃት ካደረሱ በኋላ ሁለቱ ሀገራት ተኩስ ተለዋውጠዋል።
ከሐምሌ መጨረሻ ወዲህ የመጀመሪያው በተባለው የአሜሪካ ጥቃት የሁለት ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ ሌሎች ሁለት ሰዎች መጎዳታቸውን የኢራን ኢስላማዊ አብዮታዊ ዘብ አስታውቋል፡፡
ቡድኑ «ምላሽ እና ቅጣት» እንደሚኖርም ዝቷል።
የዩኤስ ማዕከላዊ ዕዝ ሴንትኮም በሆርሙዝ ሰርጥ ውስጥ የተደቀነን አጣዳፊ ስጋት ለመከላከል በቦምብ አጥማጅ ኃይሎች ላይ የተወሰነ እና ትክክለኛ እርምጃ መውሰዱን ገልጿል።
ኢራን በበኩሏ ለዚህ ጥቃት ምላሽ ይሆን ዘንድ በዮርዳኖስ የሚገኙ የዩኤስ ወታደራዊ ቦታዎችን መምታቷን ገልፃለች።
በተመሳሳይ የዮርዳኖስ ጦር ሰኞ ማለዳ ስምንት ሚሳዔሎችን ማክሸፉን አስታውቋል።
የኢራን መንግሥት ቴሌቪዥን የኢራን ጦር በኤምሬትስ የሚገኝን የአየር ኃይል ጣቢያ በድሮን ኢላማ ማድረጉን ዘግቧል።
ነገር ግን የኤምሬትስ የመከላከያ ሚኒስቴር የአል-ሚንሃድ አየር ኃይል ጣቢያ ተመታ የተባለው ዘገባ «መሰረት የሌለው» ነው ብሏል፤ ሆኖም ኤምሬትስ አንድ ድሮን መትታ መጣሏን አረጋግጣለች።
ሀና ሰይፉ
ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም | 1 460 |
| 18 | የሩሲያ እና የቻይና መሪዎች በሻንጋይ ትብብር ድርጅት ጉባዔ ላይ ሊገናኙ መሆኑ ተገለፀ
የሩሲያው ቭላድሚር ፑቲን እና የቻይናው ዢ ጂንፒንግን ጨምሮ ሌሎች መሪዎች ለዓመታዊው የድርጅቱ ጉባኤ በኪርጊስታን ዋና ከተማ ቢሽኬክ ይሰበሰባሉ።
መሪዎቹ ይህንን መድረክ የባለብዙ-ዋልታ ዓለም ራዕያቸውን ለማራመድ እና በምዕራባውያን ላይ የተቀናጀ ግንባር ለማሳየት እንደሚጠቀሙበት ይጠበቃል።
ምንም እንኳን የድርጅቱ የምስረታ መግለጫ ቡድኑ በሌሎች አገሮች ላይ ያነጣጠረ ጥምረት አይደለም ቢልም፤ባለፈው ዓመት በተደረገው ስብሰባ ላይ ፑቲን ምዕራባውያንን የዩክሬንን ጦርነት በመቀስቀስ ሲከሱ፣ ዢ ጂንፒንግ ደግሞ በአሜሪካ እና በቻይና መካከል ያለውን ውጥረት በመጥቀስ የማስፈራራት ድርጊቶችን ኮንነዋል።
በዚህ ዓመት ከ10ሩ ቋሚ አባላት በተጨማሪ የሕንድ፣ የፓኪስታን፣ የኢራን እንዲሁም አባል ያልሆነችው የቱርክ መሪዎች በጉባዔው ላይ ይገኛሉ።
የኢራኑ ፕሬዝዳንት መሱድ ፔዜሽኪያን ከፑቲን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት እንደሚያደርጉ የሚጠበቅ ሲሆን፤አገራቸው ከሩሲያ ጋር የጠበቀ ወታደራዊ ግንኙነት እንዲሁም ከቻይና ጋር የኃይል ትስስር አላት።
ይህ ስብሰባ የተዘጋጀው የአሜሪካው የገንዘብ ሚኒስትር ስኮት ቤሰንት የቻይናን የ1.2 ትሪሊየን ዶላር ዓለም አቀፍ የንግድ ትርፍ ዘላቂነት የሌለው ሲሉ በኮነኑ ማግስት ነው።
ቤሰንት የቻይና ኢኮኖሚ ደካማ በመሆኑ ምርቶቿን ወደ ውጭ ለመላክ እየሞከረች መሆኑን ገልጸው፤የጂ20 አባላት ከቤጂንግ ጋር ያላቸውን የንግድ ውል ድጋሚ እንዲፈትሹ እንደሚያበረታቱ ተናግረዋል።
ሳራ ዮሐንስ
ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም | 1 297 |
| 19 | ሕዝባችንን በጨለማ ውስጥ ትተን ለዳታ ማይኒንግ ተቋማት ኃይል አንለቅም አለ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የውሃ ግድቦች የውሃ መጠን በመቀነሱ ምክንያት ለሕዝብና ለሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች የኤሌክትሪክ አቅርቦት ቅድሚያ ለመስጠት ሲባል ለዳታ ማይኒንግ ኩባንያዎች የሚቀርበውን የኃይል መጠን በ75 በመቶ መቀነሱን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አስታውቀዋል።
ከተፈረመው ውል አንጻር የቀረበው የኃይል መጠን ወደ 23በመቶ ዝቅ ብሏል (የ75 በመቶ ቅናሽ ተደርጓል) ነው የተባለው፡፡
የውሳኔው ምክንያት ወደ ግድቦች የሚገባው የውሃ መጠን ቢያንስ በ20 በመቶ መቀነሱ እና የደረቃማ ወቅት ቅድመ ማስጠንቀቂያ መኖሩ መሆኑ ተገልጿል።
ዳታ ማይኒንግ ባለፈው የበጀት ዓመት 50.37 ቢሊየን ብር ገቢ ያስገኘ ቀዳሚ ዘርፍ ቢሆንም ለሕዝብ ጥቅም ሲባል አቅርቦቱ ገታ ተደርጓል።
ሆኖም በጥቅምት ወር (ከክረምቱ ማብቂያ በኋላ) በሚደረግ የውሃ መጠን ግምገማ መሠረት አቅርቦቱ የሚሻሻል ወይም የሚቀጥል ይሆናል ተብሏል።
ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም | 1 315 |
| 20 | የቤተክርስቲያኗ አስተዳዳሪ በሙስና ወንጀል የሁለት ዓመት እስራት ተፈረደባቸው
በደቡብ ኮሪያ ‹‹የዓለም ሰላምና አንድነት የቤተሰብ ፌዴሬሽን›› ወይም ‹‹ዩኒፊኬሽን ቸርች›› ተብሎ የሚጠራው የሃይማኖት ተቋም መሪ፣ በቀድሞዋ ቀዳማዊት እመቤት ላይ በፈጸሙት የጉቦ ወንጀል ጥፋተኛ ተብለው የሁለት ዓመት እስራት ተፈርዶባቸዋል።
የሴኡል ፍርድ ቤት የ83 ዓመቷን የቤተክርስቲያኑ መሪ ሀን ሀክ ጃን ጥፋተኛ ብሎ የፈረደባቸው የቀድሞዋን ቀዳማዊት እመቤት ኪም ኪዮን ሂን በውድ ስጦታዎች በማማለልና የፖለቲካ ጥቅሞችን ለማግኘት በመሞከር ወንጀል ነው።
መሪዋ በተለይም እንደ ዲዛይነር የእጅ ቦርሳዎች ያሉ የቅንጦት ዕቃዎችን በደላላ በኩል ለቀዳማዊት እመቤቷ አድርሰዋል የሚል ክስ ቀርቦባቸዋል።
ሀን ሀክ ጃ የቀረበባቸውን ክስ ያስተባበሉ ሲሆን፤ ጠበቆቻቸውም ለከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ ለማለት መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።
ይህ የፍርድ ውሳኔ የተሰማው በደቡብ ኮሪያ ከፍተኛ የፖለቲካ ቀውስ በነገሰበት ወቅት ነው ተብሏል።
የቀድሞዋ ቀዳማዊት እመቤት ኪም ኪዮን ሂ በሙስና ወንጀል ጥፋተኛ ተብለው የተፈረደባቸው ሲሆን፤ባለቤታቸውና የቀድሞው ፕሬዝዳንት ዩን ሱክ ዮልም ወታደራዊ አዋጅ ለማወጅ ባደረጉት ያልተሳካ ሙከራና በስልጣን አላግባብ መገልገያ ወንጀል በአሁኑ ወቅት በእስር ላይ ይገኛሉ ሲል የዘገበዉ ዶይቸ ቬሌ ነው።
ልዑል ወልዴ
ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም | 1 495 |
