Ethio Fm 107.8
前往频道在 Telegram
በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!
显示更多📈 Telegram 频道 Ethio Fm 107.8 的分析概览
频道 Ethio Fm 107.8 (@ethiofm107dot8) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 18 525 名订阅者,在 新闻与媒体 类别中位列第 12 101,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 819 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 18 525 名订阅者。
根据 12 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -65,过去 24 小时变化为 -6,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 9.00%。内容发布后 24 小时内通常能获得 6.76% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 1 667 次浏览,首日通常累积 1 253 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 4。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!”
凭借高频更新(最新数据采集于 13 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 新闻与媒体 类别中的关键影响点。
18 525
订阅者
-624 小时
-77 天
-6530 天
数据加载中...
吸引订阅者
七月 '26
七月 '26
+35
在0个频道中
六月 '26
+70
在0个频道中
Get PRO
五月 '26
+78
在2个频道中
Get PRO
四月 '26
+74
在1个频道中
Get PRO
三月 '26
+26
在0个频道中
Get PRO
二月 '26
+51
在1个频道中
Get PRO
一月 '26
+45
在1个频道中
Get PRO
十二月 '25
+25
在2个频道中
Get PRO
十一月 '25
+51
在3个频道中
Get PRO
十月 '25
+51
在2个频道中
Get PRO
九月 '25
+35
在4个频道中
Get PRO
八月 '25
+62
在4个频道中
Get PRO
七月 '25
+52
在2个频道中
Get PRO
六月 '25
+81
在3个频道中
Get PRO
五月 '25
+67
在2个频道中
Get PRO
四月 '25
+88
在3个频道中
Get PRO
三月 '25
+87
在5个频道中
Get PRO
二月 '25
+60
在1个频道中
Get PRO
一月 '25
+135
在2个频道中
Get PRO
十二月 '24
+279
在5个频道中
Get PRO
十一月 '24
+259
在4个频道中
Get PRO
十月 '24
+312
在2个频道中
Get PRO
九月 '24
+377
在3个频道中
Get PRO
八月 '24
+470
在3个频道中
Get PRO
七月 '24
+235
在1个频道中
Get PRO
六月 '24
+202
在3个频道中
Get PRO
五月 '24
+429
在1个频道中
Get PRO
四月 '24
+494
在5个频道中
Get PRO
三月 '24
+533
在1个频道中
Get PRO
二月 '24
+428
在3个频道中
Get PRO
一月 '24
+529
在5个频道中
Get PRO
十二月 '23
+536
在3个频道中
Get PRO
十一月 '23
+223
在2个频道中
Get PRO
十月 '23
+342
在3个频道中
Get PRO
九月 '23
+160
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+181
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+167
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+214
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+191
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+252
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+235
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+226
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+260
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+159
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+231
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+144
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+165
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+442
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+191
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+121
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+98
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+109
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+140
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+96
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+103
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+93
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+139
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+211
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+230
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+364
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+341
在0个频道中
Get PRO
六月 '21
+416
在0个频道中
Get PRO
五月 '21
+410
在0个频道中
Get PRO
四月 '21
+307
在0个频道中
Get PRO
三月 '21
+319
在0个频道中
Get PRO
二月 '21
+325
在0个频道中
Get PRO
一月 '21
+310
在0个频道中
Get PRO
十二月 '20
+21 895
在0个频道中
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 13 七月 | 0 | |||
| 12 七月 | +1 | |||
| 11 七月 | 0 | |||
| 10 七月 | +11 | |||
| 09 七月 | +2 | |||
| 08 七月 | +1 | |||
| 07 七月 | 0 | |||
| 06 七月 | +2 | |||
| 05 七月 | 0 | |||
| 04 七月 | +15 | |||
| 03 七月 | 0 | |||
| 02 七月 | +3 | |||
| 01 七月 | 0 |
频道帖子
የከተማ አስተዳደሩ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ለአከራዩች የሰጠዉን መብት ግምት ዉስጥ እንዲያስገባ ተጠየቀ
በተከራይ እና በአከራይ መካከል የሚኖርን ሰላማዊ ግንኙነት ታሳቢ ያደረገ ስርአት እንዲኖርም ተጠይቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ ከዛሬ ሐምሌ 05/2018 ዓ.ም ጀምሮ ማካሄድ ጀምሯል።
በጉባኤው ከንቲባ አዳነች አቤቤ የአስተዳደራቸውን የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል። ሪፖርቱን ተከትሎ የምክር ቤት አባላት ምላሽ እና ማብራሪያ ያስፈልጓቸዋል ያሏቸዉን ጥያቄዎች አንስተዋል።
የምክር ቤት አባሉ ዶ/ር ሲሳይ መንግስቴ መኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር ዙሪያ ያሉ ክፍተቶችን የተመለከተ ጥያቄ አቅርበዋል።
ዶ/ር ሲሳይ "አዋጁ ክፍተቶች ያሉት ይመስለኛል። በፍጥነት የወጣ በመሆኑ የአከራዩንም ሆነ የተከራዩን ህብረተሰቡን ፍላጎት በማገናዘብ አማካኝ የሆነ ነገር ይዞ መቷል ብዬ አላምንም" ብለዋል።
መሻሻል የነበረባቸው ጉዳዩች ያሉ ቢሆንም ስልጣኑ የፌደራል መንግስት ስለሆነ ብዙ ልንል ባንችልም ያሉት ዶ/ር ሲሳይ፤ አፈፃፀሙ ግን በደንብ መታየት ያለበት ነገር መሆኑን ማንሳት አለብን ሲሉ ለምክር ቤቱ ገልፀዋል።
የምክር ቤት አባሉ በቀረበዉ ሪፖርት መሠረት 5 መቶ ሺህ የአከራይ ተከራይ ዉል ተደርጓል የሚለዉን በማስታወስ ይህ 5 መቶ ሺህ አባወራ አለ እንደማለት መሆኑን ይገልፃሉ።
"ይህ 5 መቶ ሺህ አባወራ በስሩ አራት ሰዉ አለ ብንል ሁለት ሚሊዮን ህዝብ ማለት ነዉ፤ እያወራን ያለነዉ ስለዚህ ህዝብ ነዉ ትኩረት ሰጥተን ማየት አለብን" ብለዋል።
የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ በየአመቱ የኪራይ መጠን እየተጠና ሊጨምር እንደሚችል ያስቀምጣል።
ዶ/ር ሲሳይ ይህንን በማስታወስ" ዘንድሮ ተጠንቶ ቀረበ የተባለዉ ጭማሪ በሁለት አመቱ ነዉ፤ አዋጁ እንኳን ለአከራዩች የሰጠዉን መብት እኛ እየነፈግን ነዉ።" ሲሉ አስረድተዋል።
ይህ የሚመለከተው የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ጥናቱን በየአመቱ መስራት ይገባዋል ሲሉም አክለዋል።
አሁን ለዚህ በጀት አመት ተሰራ የተባለዉ ጥናት ምን ያህል መሠረታዊ ችግርን ይፈታል ወይ? የሚል ሀሳብ አለኝ ሲሉም ጠይቀዋል።
የማዕከላዊ ስታስቲክስ አገልግሎት በየአመቱ ከኑሮ ዉድነት እና የዋጋ ጭማሪዎች ጋር አያይዞ የሚያወጣዉን ጥናት መሠረት አድርጎ ሌላ ጥናት ሳያስፈልግ ጭማሪውን መወሠን ይቻላል ያሉት ዶ/ር ሲሳይ ለሌላ ጥናት ሀብት ማባከን አያስፈልግም ይላሉ።
ከተማ አስተዳደሩ ስለ ተከራዩች ብቻ ሳይሆን የአከራዩችን መብት ግምት ዉስጥ ማስገባት ይኖርበታል ተብሏል።
ለምክር ቤት አባሉ "አሁን ላይ በሁለት አመት ነዉ እያሰብን ያለነዉ ፤ አንድ አመት በዝምታ ነዉ የታለፈዉ ያ ማለት የአከራዩን መብት ከአዋጁ አንፃር የሚጥስ ነዉ" ሲሉ ገልጸዋል።
በምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ሀላፊ ወ/ሮ ቅድስት ወ/ጊዩርጊስ የስታትስቲክስ አገልግሎት ጥናት የሀገር አቀፍ ጥናት በመሆኑ ለከተማዉ ቤቶች ጥናቱን ለዋጋ ጭማሪ መሠረት በማድረግ መጠቀም አንችልም ብለዋል።
የከተማዋ አስተዳደሩ በዚህ አመት ለኪራይ ዋጋ ጭማሪ ያስጠናዉ ጥናት የስታቲስቲክስ አገልግሎት ያስጠናዉንም ያካተተ መሆኑን በመግለፅ ለሁለቱም አካላት እኩል ሊጠቅም የሚችል ነዉ ብለዋል።
ቁምነገር አየለ
ሐምሌ 05/2018 ዓ.ም
| 2 | 没有文字... | 1 321 |
| 3 | የአሜሪካው ሴናተር ሊንድሴ ግራሃም በ71 ዓመታቸው ‹‹በድንገተኛ ህመም›› ማለፋቸውን ቢሯቸዉ አስታወቀ
ከደቡብ ካሮላይና የሪፐብሊካን ፓርቲ አባል የሆኑት ግራሃም ከ2003 ጀምሮ በሴኔት ውስጥ አገልግለዋል
ቢሯቸዉ ባወጣው መግለጫ፤ ‹‹ቅዳሜ ምሽት የአሜሪካው ሴናተር ሊንድሴ ግራሃም በአጭር እና በድንገተኛ ህመም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል›› ብሏል።
ከደቡብ ካሮላይና ግዛት የመጡት የሪፐብሊካን ፓርቲ አባሉ ግራሃም፤ በ2002 ለሴኔት የተመረጡ ሲሆን በ2008፣ 2014 እና 2020 በድጋሚ ተመርጠዋል።
የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቅርብ ወዳጅ የነበሩት ግራሃም፤ የሴኔት የበጀት ኮሚቴ ሰብሳቢ ሆነው ያገለገሉ ሲሆን፤ በህዳር ወር ምርጫ ለአምስተኛ ጊዜ ለስድስት ዓመት የሴኔት የሥራ ዘመን ለመወዳደር በዝግጅት ላይ ነበሩ።
ግራሃም በቅርቡ ወደ ኪቭ ተጉዘው የተመለሱ ሲሆን፤ ባለፈው አርብ ከዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር ተገናኝተው ነበር።
እስከዳር ግርማ
ሐምሌ 05/2018 ዓ.ም | 1 546 |
| 4 | የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሞሪሸስ የጀመረው አዲስ በረራ አህጉራዊ የንግድና የቱሪዝም ትስስርን እንደሚያጠናክር ተገለጸ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ አበባን ከሞሪሸስ መዲና ፖርት ሉዊስ ጋር የሚያገናኘውን የቀጥታ በረራ ነገ ይጀምራል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው በምርቃቱ ወቅት እንደገለጹት፥አዲሱ መዳረሻ አየር መንገዱ አፍሪካን እርስ በእርስ የማስተሳሰር ስትራቴጂው አንድ አካል ነው።
ሞሪሸስን ከአየር መንገዱ 1መቶ45 የዓለም
መዳረሻዎች ጋር የሚያገናኘው ይህ መስመር፥በሁለቱ ሀገራት መካከል ለረጅም ጊዜ የነበረውን የቀጥታ የአየር ትራንስፖርት ክፍተት የሚሞላና የንግድ እንቅስቃሴውን የሚያቀላጥፍ መሆኑን ጠቁመዋል።
በኢትዮጵያ የሞሪሸስ አምባሳደር ራሻድ ዳውሪያዎ በበኩላቸው፥አየር መንገዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ሞሪሸስ የበረረው እ.ኤ.አ በ1976 በወቅቱ የነበረውን "የአፍሪካ አንድነት ድርጅት"(የኦኤዩ) ጉባኤ ለማስተናገድ እንደነበር አስታውሰዋል።
ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ በረራው በቋሚነት መጀመሩ በሁለቱ ሀገራት ግንኙነት አዲስ ታሪክ መጻፉን የገለጹት አምባሳደሩ፥ይህም ሞሪሸስን ከዋናው የአፍሪካ ምድር ጋር በቱሪዝምና በኢንቨስትመንት ይበልጥ እንደሚያስተሳስራት ገልጸዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዴኤታ አምባሳደር አደራ አበራ ባስተላለፉት መልዕክት፥የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአፍሪካን ሰማያት በማገናኘት ረገድ የሚጫወተው ሚና የሚደነቅ መሆኑን ጠቅሰዋል።
አዲሱ የበረራ መስመርም የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ስምምነትን ተግባራዊ ለማድረግና የአህጉሪቱን የኢኮኖሚ ውህደት ለማፋጠን ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አብራርተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ነገ ሐምሌ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ወደ ሞሪሸስ የሚያደርገውን የመክፈቻ በረራ የሚያከናውን ሲሆን፥በረራው በየሳምንቱ ለሦስት ቀናት የሚከናወን ይሆናል።
ልዑል ወልዴ
ሐምሌ 04/2018 ዓ.ም | 1 788 |
| 5 | 没有文字... | 1 547 |
| 6 | ጎልደን ስፖርት በኢትዮ ኤፍኤም 107.8 ዛሬ ምሽት ኖርዌይ ከ እንግሊዝ እንዲሁም አርጀንቲና ከ ስዊዘርላንድ የሚያደርጉትን የአለም ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ከምሽቱ 5 ሰዓት ጀምሮ የሚያስተላልፍ ይሆናል። | 1 572 |
| 7 | ከሁሉም ክፍለከተሞች ለተውጣጡ ከ50 በላይ ተማሪዎች ለአንድ አመት የሞዴስ ድጋፍ ተደረገ
ከ10 በላይ የመንግስት ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ከ50 በላይ ሴቶች ተጠቃሚ መሆናቸው ተገልጿል።
ይህን ያደረገው ኢቭ የንፅህና መጠበቂያ ምርቶች ማኑፋክቸሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ነው።
የተቋሙ ማርኬቲንግ እና ሴልስ ማናጀር ልዩ ደንድር እንዳሉት፥ ተማሪዎቹ በትምህርት ደረጃቸው ጥሩ ውጤት ያስመዘገቡ እና በትምህርት ቤቱ ተመርጠው የተላኩ ናቸው።
ኢቭ የንፅህና መጠበቂያ ምርቶች ማኑፋክቸሪንግ ፒኤልሲ በዛሬው ዕለት ባካሄደው ዝግጅት ፀደይ የተሰኘ የሴቶች የንፅህና መጠበቂያ ሞዴስ ወደ ገበያ ማስገባቱንም ገልጿል።
በዕለቱ የተለያዩ ስፖርታዊ እንዲሁም የጥያቄ እና መልስ ውድድሮች የተካሄዱ ሲሆን፥አሸናፊ ለሆኑ ተማሪዎች የገንዘብ እና የሞዴስ ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።
በተጨማሪም ከ1-3 የወጡ አሸናፊ ተማሪዎች የወከሏቸው ትምህርት ቤቶች ላይ የሚቀመጥ ሞዴስም ለየትምህርት ቤቶቹ ተሰጥቷል።
ከደጃዝማች ወንድይራድ፣ ፋና፣ አቡነ ባስሊዮስ፣ ቀጨኔ መድኃኔዓለም እና ሌሎች የመንግስት ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ተማሪዎች ናቸው በዕለቱ የተገኙት።
ይህ ሁነት የመጀመሪያው ሲሆን፥በየአመቱ ለማከናወን ዕቅድ መያዙን ገልፀው ወደፊት ወደ ክልል ከተሞችም የማስፋት ሀሳብ መኖሩን አንስተዋል።
እስከዳር ግርማ
ሐምሌ 04/2018 ዓ.ም | 1 644 |
| 8 | ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ምክር ቤት ሊቀመንበርነትን ከግብፅ ተረከበች
በአዲስ አበባ በተካሄደው 22ኛው የሚኒስትሮች ጉባኤ ማጠናቀቂያ ላይ ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ምክር ቤትን በሊቀመንበርነት ለመምራት ከግብፅ ኃላፊነቱን በይፋ ተረክባለች።
ይህ ሽግግር ቀጣናዊ የኤሌክትሪክ ገበያን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ላይ ትልቅ መነቃቃትን ይፈጥራል ተብሏል።
በሁለት ቀናቱ ጉባኤ የኃይል አውታሮችን ማስተሳሰር፣ የኃይል ንግድን ማስፋፋት እና በዓለም ባንክ የሚደገፈውን የ1.6 ቢሊዮን ዶላር የሪትሬድ-ኢኤ (RETREP-EA) ፕሮጀክት ማፋጠን በሚሉ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ሀብታሙ ኢተፋ እንደገለጹት፤ የኃይል ገበያ ማዕከሉን ዋና መቀመጫ ከመወሰን ጋር ተያይዞ ከግብፅ ጋር የነበሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት ሰፊ ድርድር የተደረገ ሲሆን፣ ልዩነቶች ቀጣናዊ አንድነቱን እንዳይጎዱ ጠንካራ የህግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት ላይ መግባባት ተፈጥሯል።
ኢትዮጵያ በሊቀመንበርነት ዘመኗ ካላት ሰፊ የታዳሽ ኃይል አቅም በመነሳት፣ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የጀመረችውን የኃይል ኮሪደር ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የቀጣናውን የኃይል ደህንነት ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እንደምትሰራ አስታውቃለች።
ሐምሌ 04/2018 ዓ.ም | 1 725 |
| 9 | Conversation with Gemini
አሳጥረህ ማራኪ አድርገህ እንደገና ጻፍልኝ
ጽሑፉን ይበልጥ ማራኪ እና አጭር ለማድረግ፣ እባክዎ እንደገና እንዲጻፍ የሚፈልጉትን ዋና ጽሑፍ ያጋሩኝ።
ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ምክር ቤት ሊቀመንበርነትን ከግብፅ ተረከበች
በአዲስ አበባ በተካሄደው 22ኛው የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር የሚኒስትሮች ምክር መጠናቀቁን ተከትሎ ኢትዮጵያ የተቋሙን የሊቀመንበርነት መንበር ከግብፅ በይፋ ተረክባለች።
ይህ የሥልጣን ሽግግር ቀጣናዊ የኤሌክትሪክ ገበያን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ላይ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተገልጿል።
ለሁለት ቀናት በተካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ የአባል ሀገራቱን የኃይል አውታሮች ማስተሳሰር፣ የኃይል ንግድን ማስፋፋት እና የታዳሽ ኃይል ልማትን ማበረታታት በሚሉ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል። በተለይም በዓለም ባንክ የሚደገፈው የ1.6 ቢሊዮን ዶላር የሪትሬድ-ኢኤ ፕሮጀክት ቀጣናዊ የኃይል ግብይትን ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ተጠቁሟል።
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ እንደተናገሩት፣ በጉባኤው ላይ የኤሌክትሪክ የኃይል ገበያ ማዕከል ዋና መቀመጫን ከመወሰን ጋር ተያይዞ ከግብፅ ጋር የነበሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት ሰፊ ድርድር መደረጉን ገልጸዋል።
ሚኒስትሩ ልዩነቶች የአባል ሀገራቱን አንድነት እንዳይከፋፍሉ የህግ ማዕቀፎችን ማጠናከርና በጋራ መግባባት ላይ መድረስ ወሳኝ መሆኑን አሳስበዋል።
ኢትዮጵያ በአዲሱ የሊቀመንበርነት ዘመኗ ካላት የኃይል ትርፍ በመነሳት፣ እንደ ኬንያ፣ ሱዳንና ጅቡቲ ካሉ የጎረቤት ሀገራት ጋር የጀመረችውን የኮሪደር ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የቀጣናውን የኃይል ደህንነት ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እንደምትሰራ አስታውቃለች።
ዜናውን አጭር፣ ሳቢ እና ቀጥተኛ በማድረግ እንደሚከተለው ተዘጋጅቷል፦
ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ምክር ቤት ሊቀመንበርነትን ከግብፅ ተረከበች
በአዲስ አበባ በተካሄደው 22ኛው የሚኒስትሮች ጉባኤ ማጠናቀቂያ ላይ ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ምክር ቤትን በሊቀመንበርነት ለመምራት ከግብፅ ኃላፊነቱን በይፋ ተረክባለች።
ይህ ሽግግር ቀጣናዊ የኤሌክትሪክ ገበያን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ላይ ትልቅ መነቃቃትን ይፈጥራል ተብሏል።
በሁለት ቀናቱ ጉባኤ የኃይል አውታሮችን ማስተሳሰር፣ የኃይል ንግድን ማስፋፋት እና በዓለም ባንክ የሚደገፈውን የ1.6 ቢሊዮን ዶላር የሪትሬድ-ኢኤ (RETREP-EA) ፕሮጀክት ማፋጠን በሚሉ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ሀብታሙ ኢተፋ እንደገለጹት፤ የኃይል ገበያ ማዕከሉን ዋና መቀመጫ ከመወሰን ጋር ተያይዞ ከግብፅ ጋር የነበሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት ሰፊ ድርድር የተደረገ ሲሆን፣ ልዩነቶች ቀጣናዊ አንድነቱን እንዳይጎዱ ጠንካራ የህግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት ላይ መግባባት ተፈጥሯል።
ኢትዮጵያ በሊቀመንበርነት ዘመኗ ካላት ሰፊ የታዳሽ ኃይል አቅም በመነሳት፣ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የጀመረችውን የኃይል ኮሪደር ትስስር ይበልጥ በማጠናከር የቀጣናውን የኃይል ደህንነት ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እንደምትሰራ አስታውቃለች።
ሐምሌ 04/2018 ዓ.ም | 1 |
| 10 | 没有文字... | 1 523 |
| 11 | በባለስልጣኑ ፈቃድ ያገኙ የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ቁጥር 21 ደረሰ
የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ለሶስት አዳዲስ የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ መስጠቱን ገለጸ።
ፈቃድ ከተሰጣቸው ተቋማት መካከል ፕራይዝዎርዝ ኢንቨስትመንት ባንክ አ.ማ በኢንቨስትመንት ባንክ ዘርፍ የተሰማራው አንዱ ሲሆን፤ ብሉፊን ካፒታል አድቫይዘሪ እና ሉሚና ካፒታል ኃ.የተ.የግ.ማ ደግሞ በሰነደ ሙዓለንዋይ ኢንቨስትመንት ማማከር ዘርፍ የተሰማሩ ናቸው።
አዲሶቹን ጨምሮ በሀገሪቱ በህጋዊ መንገድ ፈቃድ አግኝተው የሚንቀሳቀሱ የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች አጠቃላይ ቁጥር 21 ደርሷል።
ከፈቃድ አሰጣጡ ጎን ለጎንም የድርጅቶቹ 10 ተሿሚ እንደራሴዎች እንዲሁም የ15 የቦርድ አባላት ሹመት በባለስልጣኑ መጽደቁ ታውቋል።
ባለስልጣኑ አያይዞም አገልግሎት ሰጪዎቹ ስራቸውን ሲያከናውኑ ሁሉንም ባለሃብቶች እኩል ባማከለ መልኩ፤ በዕውቀት፣ በታማኝነትና በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ ጥሪ አቅርቧል።
ሐምሌ 03 ቀን 2018 ዓ.ም | 1 749 |
| 12 | 没有文字... | 1 610 |
| 13 | የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች የኑሮ ውድነትን እያቃለሉ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ ገለጹ
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልሃኪም ሙሉ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ በንግድ ሥርዓቱ ላይ የደላሎችን ጣልቃ ገብነት በማስቀረት፣ ሸማቹንና አምራቹን በቀጥታ የሚያገናኙ የገበያ አማራጮችን ማስፋፋት የዋጋ ግሽበትን ለማረጋጋት ተጨባጭ ውጤት እያመጣ ይገኛል።
በበጀት ዓመቱ 804 አዳዲስ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች የተከፈቱ ሲሆን፣ በአገር አቀፍ ደረጃ አጠቃላይ የማዕከላቱ ቁጥር 2 ሺህ 369 ደርሷል ብለዋል።
ማዕከላቱ ከመደበኛው ገበያ ጋር ሲነጻጸር ከ15% እስከ 30% የሚደርስ ቅናሽ ያላቸው በመሆኑ፣ በተለይ መካከለኛና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን የማኅበረሰብ ክፍሎች በእጅጉ መደገፍ መቻሉን አንስተዋል።
የግብይት ሰንሰለቱን ይበልጥ ለማዘመን የሁለተኛ ደረጃ የገበያ ማዕከላትን የመገንባት ሥራ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። በአዲስ አበባ፣ ኦሮሚያና አማራ ክልሎች የተጀመረው ይህ ተሞክሮ ወደ ሌሎች ክልሎችም እየተስፋፋ መሆኑን ኃላፊው ጠቁመዋል።
ሐምሌ 03/2018 ዓ.ም | 1 624 |
| 14 | 没有文字... | 1 624 |
| 15 | ኢትዮጵያና ኬንያ የኃይል አቅርቦት ስምምነት አደረጉ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከኬንያው የኤሌክትሪክ ኃይል ኩባንያ (KPLC) ጋር አዲስ የኃይል ሽያጭ ስምምነት ተፈራረመ።
በስምምነቱ መሠረት ኬንያ በአንድ ኪሎ ዋት ሰዓት ኢነርጂ 24 ብር ከ07 ሳንቲም፣ እንዲሁም ለዲማንድ ቻርጅ 1,019 ብር ከ89 ሳንቲም ትከፍላለች።
አገልግሎቱ በላከልን መረጃ ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ጌቱ ገረመው እና የKPLC ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ኢ/ር ጆሴፍ ሲሮር በጋራ ፈርመውታል።
በድንበር አካባቢዎች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማስፋፋት፣ የሁለቱን ሀገራት የኢኮኖሚና ሰላም ትብብር ለማጠናከር እንዲሁም የምስራቅ አፍሪካን የተቀናጀ የኃይል አቅርቦት ሥርዓት (Regional Power Pool) እውን ለማድረግ ያለመ ነው።
ሐምሌ 03/2018 ዓ.ም | 1 587 |
| 16 | 没有文字... | 1 621 |
| 17 | አዲስ አበባ ለአስር ያህል የተፈጥሮ እና ሰዉሰራሽ አደጋዎች ተጋላጭ መሆኗ ተገለፀ
መዲናይቱ ለጎርፍ ፥ መሬት መንሸራተት ፥ የህንፃ መደርመስ እና እሳት ላሉ የአደጋ ክስተቶች ተጋላጭ መሆኗን ጥናት አሳይቷል።
በአዲስአበባ እሳት እና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮምሽን የአደጋ ቅነሳ ዘርፍ ሀላፊ የሆኑት አቶ ደሳለኝ ቱፋ የከተማዋን የአደጋ ስጋት በተመለከተ በኮተቤ ዩንቨርስቲ ጥናት መደረጉን ይገልፃሉ።
ሃላፊዉ ይህ ጥናት እንደገለፀዉ ከሆነም አዲስ አበባ አስር ለሚደርሱ የተፈጥሮ እና ሰዉሰራሽ የአደጋ ክስተቶች ተጋላጭ መሆኗን ጠቁሟል ብለዋል።
ከተማዋ በዋነኝነት ለጎርፍ ተጋላጭ መሆኗን የሚገልጹት ሀላፊዉ በመጪዉ የክረምት ወራት ዉስጥ ኮምሽኑ ተጋላጭ ቦታዎችን መለየቱን ተናግረዋል።
2 መቶ 38 አካባቢዎች ለጎርፍ እና ለመሬት መንሸራተት ተጋላጭ እንደሆኑ ተለይተዋል ያሉት አቶ ደሳለኝ ቱፋ 98 የሚሆኑን አካባቢዎች ለቅድመ አደጋ መከላከል ስራ እንዲሰራባቸዉ ለባለድርሻ አካላት ከምክረ ሀሳብ ጋር ተላልፎል ብለዋል።
የመሬት መንሸራተት ስጋት በታየባቸዉ አካባቢዎች እርምጃዎች እየወሰድን ነዉ የሚሉት ሀላፊዉ የጎርፍ ስጋት የሚያስከትሉ ክስተቶችን ለማስወገድ እየተሰራ ነዉ ይላሉ።
ከተማ አስተዳደሩ በአዲስ አበባ በመጪው የክረምት ወቅት ጎርፍ ቢያጋጥም ክፍለ ከተሞች ተጠያቂ እንደሚሆኑ መነገሩ ይታወሳል።
በቅርቡ በተካሄዱት የኮሪደር ልማት ስራዎች ወቅት ሳይታዩ የታለፉ ወይም የተዘጉ የጎርፍ መውረጃዎች ካሉ፣ ክረምቱ ከመግባቱ በፊት በፍጥነት መለየትና ምላሽ መስጠት እንደሚገባ ማሳሰቢያም ተሰጥቷል
በዛሬዉ እለት የ2018 የበጀት አመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርቱን የአዲስ አበባ የእሳት እና አደጋ ስጋት አመራር ኮምሽን አቅርቧል።
ቁምነገር አየለ
ሐምሌ 03/2018 ዓ.ም | 1 630 |
| 18 | በኢጣሊያዋ ፒሳ ከተማ ተማሪዎች የዓለማችንን ግዙፍ የወረቀት አውሮፕላን በመስራት አዲስ የጊነስ ክብረ ወሰን አስመዘገቡ
የወረቀት አውሮፕላን አጥፎ መስራት ማንኛውም ሰው ሊያደርገው ከሚችላቸው እጅግ ቀላል ነገሮች መሀል አንዱ ቢሆንም ይህ በተማሪዎች የተሰራው የዓለማችን ትልቁ የወረቀት አውሮፕላን ፈጽሞ ቀላል የሚባል አይደለም።
ከተለያዩ እና በርካታ ረጃጅም ወረቀቶች እና በርካታ ሊትር ሙጫ ብቻ የተሰራው ይህ ግዙፍ አካል 7 ሜትር ርዝመት እና 20.04 ሜትር የክንፍ ስፋት ያለው ሲሆን፤ ክብደቱም 28.49 ኪሎ ግራም ይመዝናል።
አውሮፕላኑ ምንም እንኳን ግዙፍ መጠንና ከባድ ክብደት ቢኖረውም፤ በጊነስ የዓለም ክብረ ወሰን ደንብ መሰረት እውቅና ለማግኘት በአንድ ሰው እጅ ብቻ ተወርውሮ ቢያንስ 15 ሜትር ርቀት በአየር ላይ መንሳፈፍ አለበት።
ይህ ክስተት ከሚወራው በላይ በተግባር ከባድ ቢሆንም ከኢካሩስ ፕሮጀክት በስተጀርባ ያሉ ተማሪዎች የአውሮፕላኑን መረጋጋት፣ ጥንካሬ፣ ክብደትና የበረራ ሳይንስ ህጎችን ለማስተካከል በከፍተኛ ጥንቃቄ ለወራት ሰርተዋል።
ቡድኑ ውጤታማ ንድፍ ላይ ለመድረስ ባደረገው የወራት ሙከራ በአጠቃላይ 300 ኪሎ ግራም ያህል ወረቀት እና 60 ኪሎ ግራም ሙጫ ተጠቅሟል።
የቀድሞው ክብረ ወሰን ተይዞ የቆየው እ.ኤ.አ. ከ2013 ጀምሮ የጀርመኑ ብራውን ሽዋይግ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ ቡድን 5 ሜትር ርዝመት፣ 24 ኪሎ ግራም ክብደት እና 18 ሜትር የክንፍ ስፋት ያለውን የወረቀት አውሮፕላን 18 ሜትር ያህል ርቀት ማብረር ችሎ በነበረበት ወቅት ነበር።
ይህ ክብረ ወሰን ከመመዝገቡ ከአንድ ወር በፊት፣ የቻይናውያን የተማሪዎች ቡድን በሪሞት መቆጣጠሪያ በሚሰራው የዓለማችን ትልቁ የወረቀት አውሮፕላን አዲስ የዓለም ክብረ ወሰን ማስመዝገባቸው የሚታወስ ነው።
ሀና ሰይፉ
ሐምሌ 03/2018 ዓ.ም | 1 582 |
| 19 | 没有文字... | 1 407 |
| 20 | አሜሪካ ለዲፕሎማሲ ዕድል ለመስጠት በኢራን ላይ የምታደርገውን ጥቃት አቁማለች ተባለ
በአሁኑ ወቅት በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለውን ውጥረት ለማርገብ በስተጀርባ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑን አንድ ባለስልጣን ለሲኤንኤን ገልጸዋል።
ሲኤንኤን የአሜሪካ ባለስልጣናትን ጠቅሶ እንደዘገበው፤በአሜሪካ እና በኢራን ግጭት ውስጥ ያለውን ውጥረት ለማርገብ በአሁኑ ጊዜ በስተጀርባ ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴዎች እየተከናወኑ ነው።
ውጥረቱ እንዳይባባስ እና ዲፕሎማሲው ውጤታማ እንዲሆን አሜሪካ ሆን ብላ ጥቃት በመሰንዘር እና ከዚያም ጥቃቱን በማቆም ላይ እንደምትገኝ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን ተናግረዋል።
በተጨማሪም እንደ መደራደሪያ ለመጠቀም የታለመላቸውን የጥቃት ቦታዎች ዝርዝር ይዛ ትገኛለች።
አስፈላጊ ከሆነ ዛሬ ምሽት ሊሰነዘሩ ለሚችሉ ጥቃቶች ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን በርካታ ባለስልጣናት ቢናገሩም፤በአሁኑ ወቅት ግን ለዲፕሎማሲው ቅድሚያ እየተሰጠ መሆኑ ተገልጿል።
ተጨማሪ የአሜሪካ ጥቃቶች ተፈጽመዋል የሚለው የኢራን ወገኖች ይገባኛል ጥያቄ ስህተት መሆኑን የአሜሪካ ባለስልጣናት ተናግረዉ፤ ሁኔታው ተለዋዋጭ መሆኑን እና አስፈላጊ ከሆነ ጥቃቶቹ ዳግም ሊጀምሩ እንደሚችሉ ጨምረው ገልጸዋል።
ሳራ ዮሐንስ
ሐምሌ 03/2018 ዓ.ም | 1 439 |
