Ethio Fm 107.8
前往频道在 Telegram
በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!
显示更多📈 Telegram 频道 Ethio Fm 107.8 的分析概览
频道 Ethio Fm 107.8 (@ethiofm107dot8) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 18 527 名订阅者,在 新闻与媒体 类别中位列第 12 186,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 819 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 18 527 名订阅者。
根据 30 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -111,过去 24 小时变化为 2,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 9.04%。内容发布后 24 小时内通常能获得 6.59% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 1 675 次浏览,首日通常累积 1 221 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 5。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!”
凭借高频更新(最新数据采集于 01 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 新闻与媒体 类别中的关键影响点。
18 527
订阅者
+224 小时
-287 天
-11130 天
数据加载中...
吸引订阅者
六月 '26
六月 '26
+70
在0个频道中
五月 '26
+78
在2个频道中
Get PRO
四月 '26
+74
在1个频道中
Get PRO
三月 '26
+26
在0个频道中
Get PRO
二月 '26
+51
在1个频道中
Get PRO
一月 '26
+45
在1个频道中
Get PRO
十二月 '25
+25
在2个频道中
Get PRO
十一月 '25
+51
在3个频道中
Get PRO
十月 '25
+51
在2个频道中
Get PRO
九月 '25
+35
在4个频道中
Get PRO
八月 '25
+62
在4个频道中
Get PRO
七月 '25
+52
在2个频道中
Get PRO
六月 '25
+81
在3个频道中
Get PRO
五月 '25
+67
在2个频道中
Get PRO
四月 '25
+88
在3个频道中
Get PRO
三月 '25
+87
在5个频道中
Get PRO
二月 '25
+60
在1个频道中
Get PRO
一月 '25
+135
在2个频道中
Get PRO
十二月 '24
+279
在5个频道中
Get PRO
十一月 '24
+259
在4个频道中
Get PRO
十月 '24
+312
在2个频道中
Get PRO
九月 '24
+377
在3个频道中
Get PRO
八月 '24
+470
在3个频道中
Get PRO
七月 '24
+235
在1个频道中
Get PRO
六月 '24
+202
在3个频道中
Get PRO
五月 '24
+429
在1个频道中
Get PRO
四月 '24
+494
在5个频道中
Get PRO
三月 '24
+533
在1个频道中
Get PRO
二月 '24
+428
在3个频道中
Get PRO
一月 '24
+529
在5个频道中
Get PRO
十二月 '23
+536
在3个频道中
Get PRO
十一月 '23
+223
在2个频道中
Get PRO
十月 '23
+342
在3个频道中
Get PRO
九月 '23
+160
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+181
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+167
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+214
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+191
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+252
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+235
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+226
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+260
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+159
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+231
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+144
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+165
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+442
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+191
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+121
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+98
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+109
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+140
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+96
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+103
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+93
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+139
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+211
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+230
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+364
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+341
在0个频道中
Get PRO
六月 '21
+416
在0个频道中
Get PRO
五月 '21
+410
在0个频道中
Get PRO
四月 '21
+307
在0个频道中
Get PRO
三月 '21
+319
在0个频道中
Get PRO
二月 '21
+325
在0个频道中
Get PRO
一月 '21
+310
在0个频道中
Get PRO
十二月 '20
+21 895
在0个频道中
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 30 六月 | +2 | |||
| 29 六月 | 0 | |||
| 28 六月 | 0 | |||
| 27 六月 | 0 | |||
| 26 六月 | 0 | |||
| 25 六月 | +4 | |||
| 24 六月 | 0 | |||
| 23 六月 | +4 | |||
| 22 六月 | 0 | |||
| 21 六月 | +7 | |||
| 20 六月 | +3 | |||
| 19 六月 | 0 | |||
| 18 六月 | 0 | |||
| 17 六月 | +13 | |||
| 16 六月 | 0 | |||
| 15 六月 | +1 | |||
| 14 六月 | 0 | |||
| 13 六月 | +10 | |||
| 12 六月 | 0 | |||
| 11 六月 | 0 | |||
| 10 六月 | 0 | |||
| 09 六月 | +7 | |||
| 08 六月 | +3 | |||
| 07 六月 | +1 | |||
| 06 六月 | +1 | |||
| 05 六月 | +3 | |||
| 04 六月 | 0 | |||
| 03 六月 | +3 | |||
| 02 六月 | +8 | |||
| 01 六月 | 0 |
频道帖子
የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር በሱዳን ምዕራብ ኮርዶፋን ግዛት የኮሌራ ወረርሽኝ መከሰቱን አስታወቁ
ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም እንዳሉት፤‹‹እስከ ሰኔ 20 ቀን 2026 ድረስ የክልሉ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር 8መቶ38 የተጠረጠሩ የኮሌራ ተጠቂዎችን፣ 7 የተረጋገጡ ታካሚዎችን እና 1መቶ17 ሞቶችን ሪፖርት አድርጓል፡፡
ወረርሽኙ የተከሰተው ‹‹በግጭት ምክንያት የጤና አገልግሎቶች መቋረጥ››በሰፈነበት ወቅት መሆኑን ገልጸዋል።
‹‹የህዝብ መፈናቀል መሰረታዊ የጤና አገልግሎቶችን ማግኘት ይበልጥ አስቸጋሪ እያደረገው ነው። በተመሳሳይ ጊዜ የጸጥታ ችግር እና የመንገድ ተደራሽነት ውስንነቶች የምላሽ ሰጪ ቡድኖችን ለማሰማራት እንዲሁም የሕክምና ቁሳቁሶችን እና ሰብአዊ ድጋፎችን ለማድረስ መዘግየትን እየፈጠሩ ነው››ብለዋል።
ዶክተር ቴዎድሮስ አክለውም የዓለም ጤና ድርጅት ከሌሎች ድርጅቶች ጋር በመሆን የኮሌራ ሕክምና መስጫ ማዕከላትን እና በአፍ የሚወሰድ የሰውነት ፈሳሽ መተኪያ ጣቢያዎችን በማስፋፋት፣ የኮሌራ መከላከያ ቁሳቁሶችን በማቅረብ፣ የእጅ መታጠቢያ ጣቢያዎችን በመገንባት፣ የጤና ባለሙያዎችን በማሰልጠን እንዲሁም የማህበረሰብ ጤና ትምህርትን በመደገፍ የጤና ምላሹን በማስተባበር ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
እስከዳር ግርማ
ሰኔ 23/2018 ዓ.ም
| 2 | የትራምፕ ቡድን በኢራንና በሊባኖስ ጉዳይ ተከፋፍሏል
ቫንስ ከሩቢዮ ጋር በኢራን እና ሊባኖስ ጉዳይ ተከፋፍለዋል ተባለ
ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የደረሱበትን የመግባቢያ ሰነድ በተመለከተ በውስጥ እና በውጭ ትችት እየተሰነዘረበት ባለበት ወቅት የአሜሪካዉ ምክትል ፕሬዚዳንት ጄዲ ቫንስ ስምምነቱን በይፋ ለመከላከል በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ቀርበዋል።
ቫንስ በስዊዘርላንድ የተካሄዱትን ከኢራን ጋር ድርድሮች መርተው እንደነበር በመግለጽ የመግባቢያ ሰነዱ ጥሩ እመርታ መሆኑንና ለመጨረሻ ስምምነት ጠንካራ መሠረት መጣሉን ተናግረዋል።
በተጨማሪም ቫንስ እስራኤል በስምምነቱ ላይ ያቀረበችውን ተቃውሞ በጥብቅ በመተቸት ዘጠኝ ሚሊየን ሕዝብ ያላት ሀገር ሁሉንም የብሔራዊ ደኅንነት ችግሮቿን በግድያ ብቻ መፍታት አትችልም ብለዋል።
በሌላ በኩል የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ እስራኤልን በይፋ ከመተቸት ተቆጥበው ትኩረታቸውን በኢራን መንግሥት ላይ አድርገዋል።
ስለ ቫንስ አስተያየት በተጠየቁ ጊዜም ቀጥተኛ መልስ ከመስጠት ይልቅ ሄዝቦላህ በሳምንቱ መጀመሪያ በእስራኤል የፍተሻ ጣቢያ ላይ ስለፈጸመው ጥቃት አንስተዋል።
ይሁን እንጂ የኋይት ሀውስ ኃላፊዎች በቫንስና በሩቢዮ መካከል የፖሊሲ ክፍፍል እንዳለ የሚነሱትን ወሬዎች በማስተባበል ሁለቱም በአስፈላጊ የውጭ ጉዳይ ጉዳዮች ላይ በአንድነት እየሠሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ትዕግስት ግርማ
ሰኔ 23/2018 ዓ.ም | 1 381 |
| 3 | የኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የአዕምሮ እና አካላዊ ህክምናን አጣምሮ እየሰጠ መሆኑ ተገለጸ
የኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የአዕምሮ እና አካላዊ ህክምናን አጣምሮ የሚሰጥ ሆስፒታል ሲሆን፤ከየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ለሚመጡ ታካሚዎች አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል ተብሏል፡፡
የሆስፒታሉ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መገርሳ ዓለሙ፥በኮቪድ-19 ወረርሽኝ እና በሰሜኑ ግጭት ወቅት በደረሰበት ጫና ምክንያት በጤና ሚኒስቴር አማካኝነት በ85 ሚሊየን ብር ወጪ የተደረገለት እድሳት ተጠናቆ አሁን ላይ ወደ ስራ መግባቱን አመልክተዋል።
ተቋሙ በአሁኑ ወቅት የኦፕሬሽን ክፍሎቹን ከ5 ወደ 10 ያሳደገ ሲሆን፥የሱስ ተጠቃሚዎች ተኝተው የሚታከሙበት ማዕከል፣ ዘመናዊ የጭቅላ ህጻናት ህክምና እና አዲስ የማይክሮ ባዮሎጂ ላቦራቶሪ አደራጅቷል።
ሆስፒታሉ በሚቀጥሉት 5 እስከ 10 ዓመታት ውስጥ የአዕምሮ፣ የነርቭ እንዲሁም የአንጎል እና የነርቭ ቀዶ ህክምናን በማቀናጀት የኒውሮ ሳይንስ ኢንስቲትዩት ለመሆን እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
የሚታየውን የሰው ኃይል ውስንነት እና የህክምና ግብዓቶች ዋጋ መጨመርን ለመቋቋም አገልግሎቱን በእጥፍ የሚያሳድግ አዲስ ህንፃ ለመገንባት የዝግጅት ሂደቶች ወደ መጨረሻው ምዕራፍ እንደደረሱም አመልክተዋል።
ሊዲያ ደሳለኝ
ሰኔ 23/2018 ዓ.ም | 1 146 |
| 4 | በደቡብ አፍሪካ ፀረ-ስደተኛ ተቃውሞዎች ወደ ሁከት ሊቀየሩ ይችላሉ ከሚል ስጋት ከፍተኛ የፀጥታ ኃይል ተሰማራ
ብዙዎች ከሁከትና ከጥቃት ለማምለጥ አስቀድመው ከአገሪቱ ተሰደዋል። የደቡብ አፍሪካ ፖሊስ እስካሁን 25,000 የሚሆኑ ስደተኞች ወደ አገራቸው መመለሳቸውን ገልጿል። አብዛኞቹ ከሌሎች የአፍሪካ አገራት የመጡ ናቸው።
ፀረ-ስደተኛ ተቃውሞዎች ወደ ሁከት ሊቀየሩ ይችላሉ ከሚል ስጋት የተነሳ በደቡብ አፍሪካ ከፍተኛ የፀጥታ አካላት የተሰማሩ ሲሆን፤ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ በተቃውሞው ላይ ለመሳተፍ ያቀዱ ወገኖች ያለምንም "ማስፈራሪያ፣ ዛቻ ወይም የአስቸኳይ ጊዜ ማስጠንቀቂያ " ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲያደርጉት አሳስበዋል።
የታቀዱት ተቃውሞዎች፣ ዘመቻ አድራጊዎች ሕጋዊ ሰነድ የሌላቸው የውጭ አገር ዜጎች በሙሉ ከአገር እንዲወጡ ያስቀመጡትን መደበኛ ያልሆነ የጊዜ ገደብ የሚያመለክቱ ናቸው።
ሕጋዊ ሰነድ የሌለው አንድ የማላዊ ዜጋ ለቢቢሲ እንደተናገረው "ወደ አገሩ በመመለሱ ደስተኛ" ቢሆንም፣ አራት ታዳጊ ልጆቹን ጥሎ በመሄዱ ግን "ልቡ እንደተሰበረ" ገልጿል።
ከተቃውሞዎቹ አንዱ የታቀደባት ጆሃንስበርግ ከተማ ባልተለመደ ሁኔታ ፀጥ ብላለች።
ሰልፈኞቹ ይሰበሰቡባቸዋል ተብለው በሚጠበቁባቸው አካባቢዎች ያሉ ሱቆች በሙሉ የተዘጉ ሲሆን፣ በከተማዋ ዋና ዋና ጎዳናዎች ላይም ከፍተኛ የፖሊስ ቁጥጥር ይታያል።
ፖሊስ እንደገለጸው ከሆነ በጆሃንስበርግ ትልቁ የከተማ መንደር (ታውንሺፕ) በሆነው ሶዌቶ ውስጥ የውጭ ዜጋ ንብረት የሆነን ሱቅ ዘርፈዋል ተብለው የተጠረጠሩ አምስት ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
በተጨማሪም በኳዙሉ-ናታል ግዛት በሀማርስዴል አካባቢ በሚገኝ አንድ አነስተኛ ሱቅ ሰብረው በመግባት የተጠረጠሩ አምስት ሰዎች ተይዘዋል። በዚሁ ግዛት ዋና ከተማ በሆነችው በደርባን መሃል ከተማ የሚገኙ በርካታ የንግድ ተቋማት ተዘግተዋል።
ራማፎሳ ተቃዋሚዎች በሰላማዊ እና በኃላፊነት ስሜት እንዲንቀሳቀሱ በተደጋጋሚ ያስጠነቀቁ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ የስደተኞች ህግ ማሻሻያ እንደሚያስፈልግ አምነዋል።
በሳምንታዊ የዜና መጽሔታቸው ላይ ለዜጎች ባስተላለፉት መልዕክት "በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ አንዳንድ የውጭ አገር ዜጎች እዚህ ያሉት በሕጋዊ መንገድ ነው" በማለት አሳስበዋል።
"እነሱ ይሰራሉ፣ ይማራሉ፣ ቤተሰብ ይመሰርታሉ፣ በኢኮኖሚያችን ላይ መዋዕለ ንዋይ ያፈሳሉ እንዲሁም ለህብረተሰባችን አዎንታዊ አስተዋፅዖ ያበረክታሉ። እነሱም ቢሆኑ በሕጎቻችን እና በሕገ-መንግስታችን የመጠበቅ መብት አላቸው።"
"የመቃወም መብት እና የመናገር ነፃነት ሰዎችን ለማስፈራራት ወይም ለማሸበር፣ ወይም ደግሞ በንብረት ውድመትና በሁከት ድርጊቶች ላይ ለመሳተፍ ፈቃድ አይሰጥም" ሲሉ ጽፈዋል።
እንደ ኦፊሴላዊ መረጃዎች ከሆነ በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ከሦስት ሚሊዮን በላይ ሕጋዊ ሰነድ ያላቸው የውጭ አገር ዜጎች ይኖራሉ።
የተቀመጠው የጊዜ ገደብ ከመድረሱ በፊት፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች ለደህንነታቸው በመስጋት በጊዜያዊ ካምፖች ውስጥ ጉዳያቸው እስኪታይ ድረስ ለበርካታ ሳምንታት ሲጠባበቁ ቆይተዋል።
ሰኔ 23/2018 ዓ.ም | 951 |
| 5 | 没有文字... | 807 |
| 6 | በዘንድሮው ዓመት የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ከፍ ያለ ውጤት ያመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል አሉ ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)
የተፈጥሮ ሳይንስ የመጀመሪያ ዙር ተፈታኞች በኦንላይን ፈተና መውሰድ ጀምረዋል።
በዘንድሮው ዓመት የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ከፍ ያለ ውጤት ያመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ፡፡
በአዲስ አበባ 131 የፈተና ጣቢያወች ያሉ ሲሆን ፈተናው በበይነ መረብ ከሰኔ 23 እስከ ሃምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም በስድስት ዙር ይሰጣል።
የወረቀት ተፈታኞች ከሃምሌ አንድ ጀምሮ ፈተና መውሰድ እንደሚጀምሩ የተገለጸ ሲሆን ዘንድሮ 563 ሺህ 501 ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ ተመዝግበዋል።
ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በማስጀመርያ መርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልእክት፣ ለፈተናው የማጠናከሪያ ትምህርትን ጨምሮ በርካታ ዝግጅት ሲደረግ መቆየቱን ተከትሎ በዘንድሮ ዓመት የተሻለ ውጤት ይጠበቃል ብለዋል።
ተማሪዎች በራሳቸው፣ በብቃት በልበ ሙሉነት ተፈትነው ለሀገር ጠቃሚ ዜጋ እንዲሆኑ መልእክት አስተላልፈዋል።
ባለፈው ዓመት 20 በመቶ ብቻ በበይነ መረብ እንደተሰጠ አስታውሰው ዘንድሮ 62 በመቶ በበይነ መረብ ፈተናውን መስጠት እንደተቻለ አንስተዋል፡፡
በቀጣይ ዓመት ሙሉ በሙሉ በበይነ መረብ ለመስጠት መታቀዱምን አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ዘግቧል።
የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ እንደ አዲስ አበባ 58 ሺህ 309 ተማሪዎች በ131 የፈተና ጣቢያወች ፈተናውን እንደሚወስዱ ገልፀዋል።
በፈተና ማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ጨምሮ የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) እንዲሁም የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ሰኔ 23/2018 ዓ.ም | 861 |
| 7 | የኡጋንዳ ቀዳሚ የሚዲያ ተቋማት በጦር ኃይሉ አዛዥ ተዘጉ
የኡጋንዳ ቀዳሚው ገለልተኛ የሚዲያ ቡድን፣ የፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ልጅ በሆኑት በጦር ኃይሉ አዛዥ ትእዛዝ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች፣ ጋዜጦች እና የሬዲዮ ጣቢያዎች እንዲዘጉ ከተደረገ በኋላ “በወታደራዊ ከበባ” ስር መሆኑን ገለጸ።
ዴይሊ ሞኒተር (The Daily Monitor) የተባለው ጋዜጣ እንደገለጸው፣ የታጠቁ ወታደሮች በዋና ከተማዋ ካምፓላ በሚገኘው የዋና መሥሪያ ቤቱ ደጃፍ ላይ የሰፈሩ ሲሆን፣ ኤንቲቪ (NTV) እና ስፓርክ ቲቪ (Spark TV) የተባሉት የቴሌቪዥን ጣቢያዎችም ከስርጭት ውጭ ሆነዋል። እነዚህ የሚዲያ ተቋማት በምስራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ተፅዕኖ ካላቸው የሚዲያ ኩባንያዎች አንዱ የሆነው የኔሽን ሚዲያ ግሩፕ (Nation Media Group) አካል ናቸው።
ለዚህ እርምጃ ዋናው መንስኤ ምን እንደሆነ እስካሁን በግልጽ ባይታወቅም፣ ጄኔራል ሙሆዚ ካይነሩጋባ በኤክስ (X) ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት፡ “በነጻ ፕሬስ አላምንም! ፕሬስ በለውጡ ካድሬዎች ሊመራ ይገባል” ብለዋል።
የተቃዋሚ እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ቡድኖች ጄኔራል ካይነሩጋባ በአባታቸው በሚመራው ከፍተኛ ጨቋኝ አገዛዝ ውስጥ ዋነኛ መሪ ተዋናይ መሆናቸውን በመጥቀስ ይከሷቸዋል።
በሌላ በኩል የፕሬዚዳንቱ እና የቤተሰባቸው ደጋፊዎች፣ በእነሱ አገዛዝ ስር በኡጋንዳ አስተማማኝ መረጋጋት እንደሰፈነና ኢኮኖሚው መሻሻል ማሳየቱን ይከራከራሉ።
ዕድሜያቸው 81 የሆኑት ፕሬዚዳንት ሙሴቬኒ፣ ከ40 ዓመታት በፊት ሥልጣን የያዙ የቀድሞ አማጺ መሪ ናቸው። ባለፈው ጥር ወር በተካሄደውና ውዝግብ ባስነሳው ምርጫ ለሰባተኛ ጊዜ አሸናፊ መሆናቸውን ያወጁ ሲሆን፣ አንድ ቀን እሳቸውን እንዲተካ ልጃቸውን እያዘጋጁት እንደሆነ በሰፊው ይገመታል።
በዘንድሮው ዓመት የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ከፍ ያለ ውጤት ያመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል አሉ ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)
የተፈጥሮ ሳይንስ የመጀመሪያ ዙር ተፈታኞች በኦንላይን ፈተና መውሰድ ጀምረዋል።
በዘንድሮው ዓመት የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ከፍ ያለ ውጤት ያመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ፡፡
በአዲስ አበባ 131 የፈተና ጣቢያወች ያሉ ሲሆን ፈተናው በበይነ መረብ ከሰኔ 23 እስከ ሃምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም በስድስት ዙር ይሰጣል።
የወረቀት ተፈታኞች ከሃምሌ አንድ ጀምሮ ፈተና መውሰድ እንደሚጀምሩ የተገለጸ ሲሆን ዘንድሮ 563 ሺህ 501 ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ ተመዝግበዋል።
ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በማስጀመርያ መርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልእክት፣ ለፈተናው የማጠናከሪያ ትምህርትን ጨምሮ በርካታ ዝግጅት ሲደረግ መቆየቱን ተከትሎ በዘንድሮ ዓመት የተሻለ ውጤት ይጠበቃል ብለዋል።
ተማሪዎች በራሳቸው፣ በብቃት በልበ ሙሉነት ተፈትነው ለሀገር ጠቃሚ ዜጋ እንዲሆኑ መልእክት አስተላልፈዋል።
ባለፈው ዓመት 20 በመቶ ብቻ በበይነ መረብ እንደተሰጠ አስታውሰው ዘንድሮ 62 በመቶ በበይነ መረብ ፈተናውን መስጠት እንደተቻለ አንስተዋል፡፡
በቀጣይ ዓመት ሙሉ በሙሉ በበይነ መረብ ለመስጠት መታቀዱምን አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ዘግቧል።
የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ እንደ አዲስ አበባ 58 ሺህ 309 ተማሪዎች በ131 የፈተና ጣቢያወች ፈተናውን እንደሚወስዱ ገልፀዋል።
በፈተና ማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ጨምሮ የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) እንዲሁም የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ሰኔ 23/2018 ዓ.ም | 1 |
| 8 | 没有文字... | 894 |
| 9 | በቬንዙዌላ በተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ የነፍስ አድን ስራው መዘግየት በነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ ቁጣን ቀሰቀሰ
በቬንዙዌላ የተከሰተውን አስከፊ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከትሎ የመንግስት ምላሽ መዘግየትና ቸልተኝነት ህዝቡን ለከፍተኛ ቁጣና ቅሬታ ዳርጓል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።
እስካሁን በደረሰው አደጋ ቢያንስ 1ሺህ7መቶ ሰዎች ለህልፈት መዳረጋቸውን ባለስልጣናት የገለጹ ሲሆን፤ ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት ዴልሲ ሮድሪጌዝ ክስተቱን በሀገሪቱ ታሪክ ‹‹እጅግ አስከፊው የተፈጥሮ አደጋ››ሲሉ ጠርተውታል።
ሆኖም በፈራረሱ የሪል ስቴት እና የመኖሪያ ህንፃዎች ፍርስራሽ ስር የተረፉ ሰዎችን ለመታደግ የሚደረገው ጥረት እጅግ አዝጋሚ መሆን ነዋሪዎችን እያስቆጣ ይገኛል።
የመንግስት እርዳታ እና የማዳኛ ማሽነሪዎች በፍጥነት አለመድረሳቸውን ተከትሎ በቤሎ ሆሪዞንቴ እና መሰል መንደሮች የሚገኙ ነዋሪዎች የራሳቸውን ደህንነት ለአደጋ አጋልጠው በባዶ እጃቸውና በዶማ ፍርስራሹን እየቆፈሩ ሰዎችን ለማዳን ተገድደዋል።
ምንም እንኳን ከኮሎምቢያ፣ ኤል ሳልቫዶር እና አሜሪካ የመጡ የነፍስ አድን ቡድኖች ድጋፍ እያደረጉ ቢሆንም በአንዳንድ አካባቢዎች የፍለጋ ስራው በይፋ መቋረጡ ተገልጿል።
በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች አሁንም በፍርስራሹ ስር ተቀብረው በመቅረታቸው የአደጋው እውነተኛ የጉዳት መጠን ምን ያህል እንደሆነ ለማወቅ አስቸጋሪ ሆኗል ሲል ቢቢሲ በዘገባው አክሏል።
እድላዊት ብርሃኑ
ሰኔ 23/2018 ዓ.ም | 830 |
| 10 | ‹‹ፈረንሳይ ትንኮሳዎቿን እንድታቆም እንመክራለን››- ኢራን
ፈረንሳይ የሆርሙዝ ሰርጥን ከፈንጅ ለማፅዳት ያቀረበችውን ጥያቄ ነገሩን ለማባባስ የተደረገ ትንኮሳ ነው ስትል ኢራን ጥያቄዋን ውድቅ አደረገች።
በኢስላማባዱ የመግባቢያ ስምምነት መሰረት ፈንጂዎችን የማፅዳት ስራ የኢራን ብቻ ነው ያለች ሲሆን፤ ፈረንሳይ የባህር ላይ ደህንነትን ሊያወሳስቡ ከሚችሉ ትንኮሳዎች እንድትቆጠብ አስጠንቅቃለች።
ኢራን ይህንን ያለችው ፈረንሳይ ከኢራን ጋር በመሆን ፈንጂዎችን ከሰርጡ ለማስወገድ ያቀረበችውን የትብብር ጥያቄ ተከትሎ መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል።
በኢራን የሕግና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካዜም ጋሪባባዲ፤ በእስላማባድ የመግባቢያ ስምምነት መሠረት በዚህ ስልታዊ የባህር መስመር ላይ የሚከናወኑ የፈንጂ ማጽዳት ሥራዎች በኢራን ብቻ እንጂ በማንኛውም ሌላ አገር እንደማይከናወኑ ገልጸዋል።
አሁን ያለው የወሽመጡ ሁኔታ አደገኛና እና ውስብስብ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ማንኛውም ስምምነቶች ሆኑ የውጭ አካላት በፈንጅ ማጽዳት ሥራ ላይ የሚኖራቸው ተሳትፎ እንደማይፈቀድ አፅንዖት ሰጥተው አሳስበዋል።
‹‹ፈረንሳይ በትንኮሳዎቿ ሁኔታውን ይበልጥ እንዳታወሳስብ በጥብቅ እንመክራለን›› ብለዋል ጋሪባባዲ።
እርሳቸው ይህንን ያሉት የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኤክስ ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት፤ ፈረንሳይ እና ኦማን የባህር ላይ መስመሮችን ደህንነት ለመጠበቅ እና በዚህ ስልታዊ የውሃ መስመር ላይ ነፃ እና ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ማለፍን ለማረጋገጥ ከባልደረቦቻቸው ጋር በመቀናጀት በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ የፈንጅ ማጽዳት ሥራን በጋራ ለመሥራት መወሰናቸውን ከገለጹ በኋላ ነው።
ሃናን ሸምሱ
ሰኔ 23/2018 ዓ.ም | 918 |
| 11 | ኦማን በሆርሙዝ ባሕረ ሰላጤ ፈንጅ የማጽዳት ዋና ኃላፊነት የኢራን ነው አለች
ኦማን በሆርሙዝ ባሕረ ሰላጤ በባሕር ውስጥ ሊኖሩ የሚችሉ ፈንጂዎችን የማጽዳት ዋና ኃላፊነት በዋናነት በኢራን ላይ እንደሚወድቅ አስታዉቃለች።
ይህ መግለጫ የመጣው የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ከኦማን ጋር በመተባበር የሆርሙዝ ባሕረ ሰላጤን ከፈንጂ ለማጽዳት ዝግጁ መሆናቸውን ከገለጹ በኋላ ኢራን በጉዳዩ ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ ባሰማችበት ወቅት ነው።
የኦማን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር ቢን ሐመድ አልቡሳይዲ ለፈረንሳዩ ሞንቴ ካርሎ ዱዋሊያ ሬዲዮ በሰጡት ቃል፤በአሜሪካና ኢራን መካከል በተደረሰው የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ባሕረ ሰላጤና በዓለም አቀፍ እውቅና ባላቸው የመርከብ መጓጓዣ መስመሮች የፈንጅ አደጋ እንዳይኖር ማረጋገጥ በዋናነት የኢራን ኃላፊነት ነው ብለዋል።
ሚኒስትሩ በተጨማሪም ኦማን ጥያቄ በሚቀርብላት ጊዜ ለክልላዊና ለዓለም አቀፍ ጥረቶች አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል።
ትዕግስት ግርማ
ሰኔ 23/2018 ዓ.ም | 964 |
| 12 | ታዋቂው የቻይና ባለሀብት በአሜሪካ በ30 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ
በአንድ ወቅት ከቻይና እጅግ ባለጸጋ ነጋዴዎች አንዱ እንደነበረ የሚነገርለት ጉዎ ዌንጉዊ በቢሊየን ዶላር በሚቆጠር የማጭበርበር ወንጀል በአሜሪካ ፍርድ ቤት የ30 ዓመት እስራት ተፈርዶበታል።
የቀድሞው የሪል እስቴት ባለሀብት በ2017 ከቻይና በመሰደድ ወደ አሜሪካ ያቀና ሲሆን፤እዚያም እራሱን የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ተቺ አድርጎ በመቅረጽ በርካታ የኢንተርኔት ተከታዮችን ማፍራት ችሎ ነበር።
ይሁን እንጂ ጉዎ ሲንቀሳቀስ በነበረበት ወቅት በማደራጀት፣ በማጭበርበር እና ህገ-ወጥ ገንዘብን ህጋዊ አድርጎ የማቅረብ ወንጀሎች ጥፋተኛ ሆኖ ተገኝቷል።
የኒውዮርክ ፍርድ ቤት ዳኛ አና ሊሳ ቶሬስ በሰጡት ውሳኔ፤ ጉዎ ‹‹በቻይና ዲሞክራሲ እንዲሰፍን የሚፈልጉ ሰዎችን እምነት በመበዝበዝ›› የሰበሰበውን ገንዘብ ለራሱ ቅንጡ ህይወት ማደላደያ ማዋሉን ገልጸዋል።
የአሜሪካው አቃቤ ህግ ሾን ኤስ ባክሌይ ለቢቢሲ በሰጡት መግለጫ፤ ‹‹ጉዎ ከተሰጡት በርካታ ህጋዊ እድሎች ጋር ከመስማማት ይልቅ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የጣሉበትን እምነት ለግል ስግብግብነቱ ተጠቅሞበታል›› ብለዋል።
አቃቤ ህጉ አክለውም፤‹‹የዛሬው ውሳኔ ዝና እና ሀብት ከህግ በላይ ሊያደርጉ እንደማይችሉ እና ቤተሰቦችን በመበዝበዝ እራሳቸውን የሚያበለጽጉ አጭበርባሪዎች ከባድ መዘዝ እንደሚጠብቃቸው ያሳየ ነው›› ሲሉ ተናግረዋል።
ሀና ሰይፉ
ሰኔ 23/2018 ዓ.ም | 1 135 |
| 13 | የህብረት ስራ ማህበራትን በማዘመን የግብርና ሽግግርን ለማረጋገጥ የሚያስችል የሪፎርም ስራ እየተከናወነ መሆኑ ተገለጸ
በኢትዮጵያ የግብርና ሽግግርን ለማረጋገጥና የምርት አሰባሰብና ግብይት ስርዓቱን ለማዘመን የህብረት ስራ ማህበራት ግንባር ቀደም ሚና እንዲጫወቱ ሰፊ የሪፎርም ስራ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ህብረት ስራ ኮሚሽን አስታወቀ።
የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አቶ ጌትነት ታደሰ፣ ግብርናው ከአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት ባለፈ ለሌሎች ዘርፎች መሰረት እንዲሆን የህብረት ስራ ማህበራትን ማጠናከር የግድ እንደሆነ ገልጸዋል። ለዚህም ይረዳ ዘንድ ከ8 ሺህ በላይ የቀበሌ የልማት አደራጆችና ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጥቷቸዋል ብለዋል።
ኮሚሽነሩ አክለውም፣ አዲሱ የግብርናና የገጠር ልማት ፖሊሲ ማህበራቱ በምርት ላይ እሴት በመጨመርና የንግድና የታክስ ስርዓቱን ግልጽነት በማስፈን ረገድ ትልቅ ድርሻ እንደሰጣቸው ተናግረዋል። ይህ የሪፎርም ስራ በግብርና ሚኒስቴር፣ በግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት እና በሌሎች ተጠሪ ተቋማት ቅንጅት እየተመራ መሆኑም ታውቋል።
በተለይም በበጋ ስንዴ፣ በአረንጓዴ አሻራና በዲጂታላይዜሽን ረገድ የተመዘገቡ ውጤቶችን ይበልጥ ለማሳደግ የህብረት ስራ ማህበራት የአሰራር ሪፎርም ማድረጋቸው ወሳኝ መሆኑ ተመላክቷል። ለሪፎርም ስራው መሳካትም የሚኒስትሮች ምክር ቤትና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስፈላጊውን የህግ ድጋፍ እያደረጉ መሆኑ ተገልጿል።
አዲስዓለም አበበ
ሰኔ 22/2018 ዓ.ም | 1 443 |
| 14 | 没有文字... | 1 273 |
| 15 | የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ነገ ሰኔ 23 ይጀምራል
የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም በመላ ሀገራችን በ6መቶ7 የፈተና ማዕከላት በስድስት ዙር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል።
ለፈተናው በድምሩ 5መቶ63 ሺህ 5መቶ1 ተፈታኞች የተመዘገቡ ሲሆን፤ 30መቶ ሺህ 4መቶ56 የተፈጥሮ ሳይንስ እና 2መቶ57 ሺህ 45 የማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ናቸው።
ተፈታኞች ወደ ፈተና ማዕከላት ሲቀርቡ የመፈተኛ መግቢያ ካርዳቸውን (Admission Card)፣ የተማሪ ወይም ህጋዊ መታወቂያ፣ በፈተና አስተዳደሩ የተፈቀደ እስክሪብቶ እና ባዶ ወረቀት ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል።
ሞባይል ስልክ፣ ስማርት ሰዓት፣ ብሉቱዝ፣ ጆሮ ማዳመጫ፣ ፍላሽ ዲስክ፣ ሜሞሪ ካርድ፣ የግል ላፕቶፕ ወይም ታብሌት እና ሌሎች ያልተፈቀዱ መሳሪያዎችን ይዞ ወደ ፈተና ክፍል መግባት አይፈቀድም።
ፈተናው በበይነ መረብ በ6 ዙር የሚሰጥ ሲሆን፣ በወረቀት የሚፈተኑ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከሐምሌ 1 እስከ3፣ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ደግሞ ከሐምሌ 6 እስከ 8 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚፈተኑ ተገልጿል።
ሰኔ 22/2018 ዓ.ም | 1 359 |
| 16 | የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን የቁጥጥር ሥርዓቱን ለማዘመን ሦስት ዋና ዋና የሪፎርም አጀንዳዎችን ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን ገለጸ
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ምርት ላይ ያተኮረ ጠንካራ የቁጥጥር ሥርዓት ለመፍጠር በሕግ፣ በአደረጃጀትና በሲስተም ዝርጋታ ላይ ትኩረት አድርጎ እየሠራ መሆኑን አስታውቋል።
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሔራን ገርባ እንደገለጹት፣ ተቋሙ በአዋጅ ቁጥር 1112/2011 አዲስ ተግባርና ኃላፊነት ከተሰጠው በኋላ ሦስት ዋና ዋና የሪፎርም አጀንዳዎችን ሲተገብር ቆይቷል። እነዚህም የሕግ ማዕቀፎችን ማሻሻል፣ ጠንካራ የተቋም አደረጃጀት መፍጠር እና ዲጂታል አሠራርን ጨምሮ የጥራት አስተዳደር ሥርዓቶችን (ISO Standards) መዘርጋት ናቸው።
ዋና ዳይሬክተሯ ይህን የገለጹት፣ የባለስልጣኑ የመድኃኒት ጥራት ምርምራ ላቦራቶሪ ስለሚሠራቸው ሥራዎች ግንዛቤ ለመስጠትና የጋራ መግባባት ለመፍጠር የምክክር መድረክ እና የላቦራቶሪ የመስክ ጉብኝት በተከናወነበት ወቅት ነው፡፡
በአሁኑ ወቅት ባለሥልጣኑ በላቦራቶሪ ምርመራ እና በኢንስፔክሽን ዘርፎች ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃዎችን (ISO 17025 እና ISO 17020) ማሟላቱ ወ/ሪት ሔራን ገልጸዋል። ጤናን እንደ ኢንቨስትመንት በመቁጠር አምራቾችን የሚያበረታታ፣ ቀልጣፋና ግልጽ አገልግሎት ለመስጠት እየተሠራ መሆኑንም ተናግረዋል።
ባለሥልጣኑ በፌዴራል ደረጃ ከክልሎች ጋር በመቀናጀት ከውጭ የሚገቡና ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን፣ መድኃኒቶችን፣ የሕክምና መሣሪያዎችን፣ የመዋቢያ ምርቶችን እንዲሁም የትንባሆና አልኮል ቁጥጥርን በበላይነት እያከናወነ ይገኛል።
አዲስአለም አበበ
ሰኔ 22/2018 ዓ.ም | 1 189 |
| 17 | 没有文字... | 1 160 |
| 18 | https://www.youtube.com/watch?v=-4TMUZjG9EA | 1 280 |
| 19 | አፍሪካ በዓለም ንግድ ላይ ያላት ድርሻ 3 በመቶ መሆኑ ተገለፀ
አፍሪካ በዓለም አቀፍ የንግድ ሥርዓት ውስጥ ከሦስት አሥርተ ዓመታት በላይ ብትቆይም፣ አሁንም በዓለም ንግድ ያላት ድርሻ 3 በመቶ ብቻ መሆኑ ተገልጿል።
ይህ ቁጥር ደግሞ እንደ ቡና እና ማዕድናት ያሉ ጥሬ ዕቃዎች ሲወጡ፣ የአህጉሪቱ የንግድ ተሳትፎ ከዚሁ ከሦስት በመቶም በእጅጉ ዝቅ የሚል መሆኑ ነው የተጠቆመው።
ይህንን ዝቅተኛ ተሳትፎ ለመቀየርና አህጉሪቱን የንግድ ተጠቃሚ ለማድረግ፣ 22ኛው የአፍሪካ ከፍተኛ የንግድ ባለሥልጣናት ስብሰባ በናይጄሪያ አቡጃ መካሄድ ጀምሯል።
ባለሥልጣናቱ ለሦስት ቀናት በሚቆየው የሥራ ቆይታቸው፣ የቀረቡ የቴክኒክ ምክረ-ሃሳቦችን መርምረው ወደ ውሳኔ በመቀየር ለንግድ ሚኒስትሮች ምክር ቤት ያቀርባሉ ተብሏል።
የዚህ ስብሰባ ዋነኛ ግብ አፍሪካ ጥሬ ዕቃዎችን ብቻ ከመላክ ባለፈ፣ እሴት የተጨመረባቸውን ምርቶች ለዓለም ገበያ በማቅረብ ያላትን ድርሻ የምታሳድግበትን ስትራቴጂ መንደፍ እንደሆነ ተገልጿል።
ልዑል ወልዴ
ሰኔ 22/2018 ዓ.ም | 1 312 |
| 20 | ተማሪዎች ውጤታቸውን መመልከት ይችላሉ
በ2018 የትምህርት ዘመን በ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና 95.85በመቶ ተማሪዎች 50 እና ከዛ በላይ ውጤት ማስመዝገባቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤትን ይፋ ተደርጓል።
ተማሪዎች ውጤታቸውን ይህንን ማስፈንጠሪያ https://aa.ministry.et/#/result በመጫን መመልከት ይችላሉ።
ሰኔ 22/2018 ዓ.ም | 1 257 |
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
