Ethio Fm 107.8
በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!
Показати більше📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Ethio Fm 107.8
Канал Ethio Fm 107.8 (@ethiofm107dot8) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 18 511 підписників, посідаючи 12 334 місце в категорії Новини і ЗМІ та 1 830 місце у регіоні Ефіопія.
📊 Показники аудиторії та динаміка
З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 18 511 підписників.
За останніми даними від 24 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -43, а за останні 24 години на 5, загальне охоплення залишається високим.
- Статус верифікації: Не верифікований
- Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 9.25%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 7.23% реакцій від загальної кількості підписників.
- Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 1 712 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 339 переглядів.
- Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 3.
📝 Опис та контентна політика
Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
“በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!”
Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 25 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Новини і ЗМІ.
Триває завантаження даних...
| Дата | Залучення підписників | Згадування | Канали | |
| 25 липня | +1 | |||
| 24 липня | +8 | |||
| 23 липня | +2 | |||
| 22 липня | +1 | |||
| 21 липня | +6 | |||
| 20 липня | 0 | |||
| 19 липня | 0 | |||
| 18 липня | +4 | |||
| 17 липня | 0 | |||
| 16 липня | +1 | |||
| 15 липня | +2 | |||
| 14 липня | +3 | |||
| 13 липня | +5 | |||
| 12 липня | +1 | |||
| 11 липня | 0 | |||
| 10 липня | +11 | |||
| 09 липня | +2 | |||
| 08 липня | +1 | |||
| 07 липня | 0 | |||
| 06 липня | +2 | |||
| 05 липня | 0 | |||
| 04 липня | +15 | |||
| 03 липня | 0 | |||
| 02 липня | +3 | |||
| 01 липня | 0 |
| 2 | እስራኤል የተኩስ አቁም ቢኖርም በደቡብ ሊባኖስ ፍንዳታዎችን እየፈጸመች ነው ተባለ
የእስራኤል ጥቃቶች የተፈጸሙት በሁለቱ ሀገራት መካከል ሰላም ለማውረድ ከሊባኖስ ባለስልጣናት ጋር ውይይት እየተደረገ ባለበት ወቅት ነው።
የእስራኤል ጦር በደቡብ ሊባኖስ አል ማንሱሪ ከተማን ማጥቃቱን እና ማጅዳል ዙን መንደር ውስጥ ፍንዳታዎችን ማድረሱን የሊባኖስ ብሔራዊ የዜና ወኪል ዘግቧል።
ባለፈው ሐሙስ እስራኤል በአምቡላንስ ላይ በሰነዘረችው ጥቃት ሁለት የህክምና ባለሙያዎች የቆሰሉ ሲሆን፥ የሊባኖስ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ድርጊቱን ‹‹ዓለም አቀፍ ሰብአዊ ህጎችን በግልጽ የጣሰ›› ነዉ ብሎታል።
እስራኤል የደህንነት ቀጣና ለመፍጠር በድንበር አቅራቢያ ያሉ ሙሉ መንደሮችን እየመታች ሲሆን፥ ውጊያው ከተጀመረ ጀምሮ ከ4 ሺህ በላይ ሰዎችን ገድላ የአገሪቱን አንድ አምስተኛ ግዛት ይዛለች።
እስራኤል ዓላማዬ ሄዝቦላህን ማስቆም ነው ብትልም፥ የመብት ተሟጋቾች ግን ስልቱ ጋዛን ለኑሮ የማይመች ለማድረግ ከተሄደበት መንገድ ጋር ተመሳሳይ ነው ይላሉ።
የአሜሪካዉ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሊባኖስ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ አውን ጋር በዋይት ሃውስ ሲገናኙ ሊባኖስን ለመርዳት ቃል ገብተዋል።
እስራኤል ስለምትወጣበት የጊዜ ሰሌዳ ሲጠየቁም ‹‹በሂደት ላይ ናቸው፤ ወደ ሌላ ክፍል እየተሰማሩ ነው›› ብለዋል።
ቀጣዩ የባለስልጣናቱ ውይይት ለነሐሴ 4 በጣሊያን ተቀጥሯል።
የሄዝቦላህ መሪ ናኢም ቃሲም ስምምነቱን ‹‹ውድቅ እና ዋጋ ቢስ›› በማለት የትጥቅ ትግል ጥሪ አቅርበዋል።
ሳራ ዮሐንስ
ሐምሌ 17/2018 ዓ.ም | 1 548 |
| 3 | የአዲስ አበባ ፖሊስ በክረምት ወቅት ለሚከሰቱ የወንጀል ድርጊቶች ህብረተሰቡ ልዩ ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳሰበ
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮማንደር ቶማስ እሸቴ ከጣቢያችን ጋር በነበራቸዉ ቆይታ፤የክረምት ወቅት መግባቱን ተከትሎ የወንጀል ድርጊቶች ሊጨምሩ እንደሚችሉ ገልጸዋል።
በክረምት ወቅት የሰዎች እንቅስቃሴ የሚገደብ በመሆኑ፤ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም ወንጀለኞች ስርቆትና መሰል ድርጊቶችን ሊፈጽሙ እንደሚችሉ ተጠቁሟል።
በተለይም የመኖሪያ ቤት ሰብሮ መግባትና የቤት ውስጥ ንብረቶችን የመስረቅ ወንጀሎች በዚህ ወቅት ሊያጋጥሙ እንደሚችሉ ኮማንደሩ አስረድተዋል።
ከመኖሪያ ቤቶች በተጨማሪ በተለያዩ ተቋማትና መጋዘኖች ላይ ያነጣጠሩ የስርቆት ድርጊቶች ሊከሰቱ እንደሚችሉ በመረዳት ተገቢው ጥበቃ ሊደረግ እንደሚገባ ገልፀዋል።
በተጨማሪም የተሽከርካሪዎች መለዋወጫ ዕቃዎችን መዝረፍና ከተሽከርካሪ ውስጥ ንብረቶችን መስረቅ በክረምት ወቅት በስፋት የሚታዩ የወንጀል አይነቶች መሆናቸውን አስታውቀዋል።
እነዚህን የወንጀል ድርጊቶች ለመከላከል ፖሊስ ከማህበረሰቡና ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል።
ፖሊስ ወንጀልን አስቀድሞ ለመከላከል የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥልና ለዚህም የህዝቡ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ኮማንደር ቶማስ አፅንኦት ሰጥተዉ ተናግረዋል ።
ሊዲያ ደሳለኝ
ሐምሌ 17/2018 ዓ.ም | 1 624 |
| 4 | የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቡና ጥራት መውረድና የዋጋ ንረት ላይ የሚነሱ ቅሬታዎችን ለመፍታት በርካታ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ገለፀ
በማህበረሰቡ ዘንድ የሚነሳውን የቡና ጣዕም መለወጥና የጥራት መጉደል ቅሬታዎችን ለመፍታት በጥራት ማሻሻል ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ይገኛል ያሉት የቡናና ሻይ ባለስልጣን የዋና ዳይሬክተር ፅህፈት ቤት ሀላፊ ዶ/ር ሰፊሳ አባቡ ናቸው።
ጥራትን ለማስጠበቅ እና የቡና ጥራትን ከተቀመጠው ደረጃ በታች የሚያወርዱ አሰራሮችን ለማስቀረት የባለስልጣኑ ባለሙያዎች ወደ አምራቾች ዘንድ በአካል በመሄድ በምርት አሰባሰብና ዝግጅት ሂደት ላይ አስፈላጊውን ማሳሰቢያና ክትትል እያደረጉ ይገኛል ብለዋል፡፡
እንዲሁም ደግሞ ቡና ከለቀማ ጀምሮ በምድር ላይ እንዳይሰጣና የጥራት ደረጃው በተጠበቀ አልጋ ላይ ብቻ እንዲሰጣ የማድረግ ጥብቅ መመሪያ እየተተገበረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም በጥራት መጉደልና ባልተገባ መንገድ በሚካሄዱ የማቀናበር ሂደቶች ላይ የሚሳተፉ አካላትን በህግ የመጠየቅና የቁጥጥር ስራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን አንስተዋል፡፡
በገበያው ላይ የነበረውን የዋጋ ንረት ለማረጋጋት ከመሸጫ ጊዜው በፊት ከአምራቾችና ከገዢዎች ጋር የግንዛቤ ፈጠራና የማስጠንቀቂያ መልዕክቶች መተላለፋቸውን ያነሱት ሀላፊው፤ በገዢዎች መካከል የሚደረጉ አላስፈላጊ የሽሚያ ምክንያቶች የዋጋ ጭማሪ እንዲኖር እያደረጉ መሆናቸውን አክለዋል፡፡
ሀና ሰይፉ
ሐምሌ 17/2018 ዓ.ም | 1 374 |
| 5 | አሜሪካ እና ሳዑዲ አረቢያ ያደረጉት የሲቪል ኒውክሌር ስምምነት ይጸድቅ ዘንድ፤ ሪያድ ለእስራኤል ዕውቅና የሚሰጠውን የ‘አብርሃም አኮርድስ’ ስምምነት መቀላቀል እንዳለባት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ገለጹ።
ትራምፕ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት፤ ወታደራዊ ላልሆነ አገልግሎት የሚውለው ይህ የኒውክሌር ስምምነት የሚጸድቀው ሳዑዲ አረቢያ የአብርሃም ስምምነቶችን ለመቀላቀል ስትስማማ ብቻ እንደሆነ አስታውቀዋል።
ቀደም ሲል ሳዑዲ አረቢያ የፍልስጤም መንግሥት ሳይመሠረት ለእስራኤል ዕውቅና እንደማትሰጥ ገልጻ የነበረ ቢሆንም፣ እስካሁን ለትራምፕ ቅድመ ሁኔታ የሰጠችው ምላሽ የለም።
በሌላ በኩል፤ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ጽሕፈት ቤት በሰጠው መግለጫ፣ ሳዑዲ አረቢያ ስምምነቱን ተቀብላ የእስራኤል ወዳጅ መሆኗ በመካከለኛው ምሥራቅ ሰላምን ለማስፈን ትልቅ ታሪካዊ እርምጃ እንደሚሆን በመጥቀስ የትራምፕን ሃሳብ እንደሚደግፉ አስታውቀዋል።
ሐምሌ 17/2018 ዓ.ም | 1 354 |
| 6 | «አሜሪካ በ60 አገራት ላይ አዲስ የንግድ ታሪፍ ጣለች።»
ዩናይትድ ስቴትስ «የግዴታ የጉልበት ብዝበዛ የተካሄደባቸውን ምርቶች ለማገድ በቂ እርምጃ አልወሰዱም» ባለቻቸው 60 አገራት ላይ ከ10 እስከ 12 ነጥብ 5 በመቶ የሚደርስ አዲስ የንግድ ታሪፍ ጥላለች።
ከአርብ ጀምሮ ስራ ላይ የሚውለው ይህ አዲስ ታሪፍ፤ ብሪታንያ፣ ቻይና፣ የአውሮፓ ህብረት፣ ካናዳ፣ ጃፓን እና ህንድን ጨምሮ በርካታ የአሜሪካ ዋና ዋና የንግድ አጋሮችን ያካተተ ነው ይላል የቢቢሲ ዘገባ።
የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር እንደሚለው፤ የጉልበት ብዝበዛን ለመግታት ቃል የገቡ አገራት 10 በመቶ፣ የተቀሩት ደግሞ 12 ነጥብ 5 በመቶ ታሪፍ ይጣልባቸዋል።
የአሜሪካ የንግድ እንደራሴ ጄሚሰን ግሪር በሰጡት መግለጫ፤ ውሳኔው «የሰብአዊ መብት ጥሰትን ለማረም እና የሰራተኞችን ደህንነት ለማሻሻል ያለመ ነው» ብለዋል።
ሐምሌ 17/2018 ዓ.ም | 1 165 |
| 7 | ከ61 በላይ ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ የሚችል የፓርኪግ ስፍራ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ።
የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን በ3ኛው ዙር የኮሪደር ፕሮጄክት ልማት አካል በሆነው ከ22 ጎላጉል አደባባይ አንስቶ እስከ ኤምባሲዉ መጋጠሚያ ድረስ ባለው መስመር ከ61 በላይ አሽከርካሪዎች ማስቆም የሚያስችል የፓርኪንግ ስፍራ ላይ የቀለም ቅብ ስራ መከናወኑን አስታዉቋል።
በከተማዋ የሚከናወኑ የፓርኪንግ ስፍራዎች የትራፊክ ፍሰቱ እና እቅስቃሴው ሰላማዊ ደህንነቱም የተጠበቀ እንዲሆን የራሱን ጉልህ ሚና ይጫዎታል ተብሏል።
የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሰልጣን በከተማዋ በሚከናወኑ መደበኛ እና ደራሽ ፕሮጀክቶች፣ የኮሪደር ልማቶች እና ወንዝ ዳር ፕሮጀክቶች ፣በመንገድ ቀለም ቅብ ስራ፣ በምልክትና ማመላከቻዎች ተከላ ተሳታፊ እንደሆነም አስታዉቋል።
መረጃው የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ ነው።
ሐምሌ 18/2018 ዓ.ም | 1 057 |
| 8 | የህጻናት ማቆያ አገልግሎት የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎ ለማሳደግ ወሳኝ ሚና እንዳለዉ ተገለፀ
በኢትዮጵያ የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎ ለማሳደግ እና የህጻናትን ቀደምት እድገት ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ፣ የህጻናት ማቆያ አገልግሎትን እንደ ትልቅ ሀገራዊ አጀንዳ አድርጎ የመቅረጽ እና የማስፋፋት ስራዎች ተጠናክረው እየተከናወኑ እንደሚገኝም ሰምተናል።
ዘርፉ ለረጅም አመታት ትኩረት ተነፍጎት እና እንደ ቅንጦት ሲታይ የቆየ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት ግን መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች እና ከግል ባለሀብቶች ጋር በመተባበር የተለያዩ የህጻናት ማቆያ ሞዴሎች በተግባር ላይ እየዋሉ መሆናቸው ተመልክቷል።
በጉዳዩ ላይ የማርኬት ሲስተም አማካሪ የሆኑት አቶ ተስፋየሱስ አለማየሁ እንዳብራሩት፣ ቀደም ሲል በዘርፉ በቂ የግንዛቤ እጥረት እንደነበረ እና ህጻናትን ማቆየት እንደ ቅንጦት ይታይ ስለነበር የፖሊሲ አጀንዳ ለማድረግ ተደጋጋሚ ጥረቶች ሲደረጉ ቆይተዋል።
ይህም እናቶች ልጆቻቸውን የሚከባከብላቸው በማጣታቸው ምክንያት ከስራ ገበታቸው እንዲቀሩ ወይም ምርታማነታቸው እንዲቀንስ ዋነኛ ምክንያት ሆኖ እንደቆየ ገልጸዋል።
ሆኖም ግን ባለፉት ጥቂት አመታት ውስጥ በተደረጉ የገበያ ጥናቶች እና የፖሊሲ እንቅስቃሴዎች አዎንታዊ የግንዛቤ ለውጥ መምጣቱ ተጠቅሷል።
አሁን ላይ አገልግሎቱን በጥራት እና በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ አዳዲስ የመንግስት፣ የግል እና የማህበረሰብ አቀፍ የዴይ-ኬር ሞዴሎች ተቀርጸው ወደ ተግባር እየገቡ ይገኛሉ።
በተጨማሪም የህጻናት ተንከባካቢዎችን (ናኒዎችን) የሙያ ጥራት ለማረጋገጥ የሚያስችል ብሄራዊ የስልጠና ካሪከለም ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዲሁም የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ተዘጋጅቶ ሲጠናቀቅ፣ በቀጣይ በቴክኒክና ሙያ ተቋማት በኩል በስፋት የሚሰጥ ይሆናል።
ለአለም አሰፋ
ሐምሌ 18/2018 ዓ.ም | 1 285 |
| 9 | Немає тексту... | 1 309 |
| 10 | የኢራን ጦር ከቀድሞው ጊዜ በተሻለ ሁኔታ መዘጋጀቱን ቃል አቀባዩ ገለጹ
የኢራን ጦር ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄኔራል አሚር መሀመድ ኢራን ወታደራዊ ኃይሎች ከቀድሞው ጊዜ በበለጠ የዝግጅት አቅም ላይ መድረሳቸውን ገልጸዋል።
ለኢራን የመከላከያ ፕሬስ የዜና ወኪል በሰጡት ቃለ ምልልስ፤በተኩስ ማቆም ወቅት የተገኘውን ዕድል በመጠቀም የውጊያ ዝግጅታቸውንና የመዋጋት አቅማቸውን ማጠናከራቸውን ተናግረዋል።
ቃል አቀባዩ እንዳሉት፤ የኢራን ጦር ለማንኛውም ሊፈጠር ለሚችል ሁኔታ ዝግጅቱን አሻሽሎ እንደሚገኝ ገልጸው፣ በጠላት ሊወሰድ የሚችለውን ማንኛውንም እርምጃ ቀላል በማድረግ እንደማይመለከቱት አስታውቀዋል።
አክለውም ጠላት በመሬት ኃይል ወረራ ቢፈጽም ከአየር ወይም ከሚሳኤል ጥቃቶች የበለጠ ተጋላጭ እንደሚሆን ገልጸው፤የመሬት ውጊያዎች በተቃዋሚው ላይ ከፍተኛ ጉዳት ለማድረስ ሰፊ እድል እንደሚሰጡ ተናግረዋል።
የኢራን ጦር በመሬት ላይ በሚደረጉ ወታደራዊ ዘመቻዎች ውጤታማነቱና ፈጣን ምላሽ የመስጠት አቅሙ ከፍተኛ እንደሚሆን አስረድተዋል ሲል አልጀዚራ ዘግቧል።
ትዕግስት ግርማ
ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም | 1 770 |
| 11 | ትራምፕ ከሳዑዲ ጋር ያደረጉት የኒውክሌር ስምምነት የረጅም ጊዜ የሁኔታዎች መጠየቂያ መስፈርትን ውድቅ ያደረገ ነዉ ተባለ
የትራምፕ አስተዳደር ከሳዑዲ ዐረቢያ ጋር የደረሰው የኒውክሌር ስምምነት ከመካከለኛ ምስራቅ ጋር የነበረውን የዓመታት አቋም የቀየረ ሆኗል፡፡
የቀደሙት የአሜሪካ ፕሬዚዳንቶች ሳዑዲ ዐረቢያ ለሲቪል የኃይል ማመንጫ ፕሮግራሞች የሚሆን የአሜሪካን የኒውክሌር ቴክኖሎጂ ለማግኘት ከእስራኤል ጋር ያላትን ግንኙነት ማስተካከል አለባት በሚለው አቋም ላይ ይጸኑ ነበር፡፡
ከነዚህ መሪዎች በተቃራኒ ግን ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ስምምነቱ በስፍራው የኒውክሌር የጦር መሳሪያ ሽሚያ ሊቀሰቅስ ይችላል በሚል ከተሰነዘሩ ተቃውሞዎች ባሻገር፣ ለእስራኤል ምንም ዓይነት የፖለቲካ ጥቅም ሳይጠይቁ ለሳዑዲ ዐረቢያ የፈለገችውን ሰጥተዋታል፡፡
ይህ ስምምነት ትራምፕ እስራኤልን ማዕከል ያደረገውን እና ለእስራኤል እና ፍልስጤም ግጭት የሁለት ሀገራት መፍትሔ የመፈለግ ልማዳዊ የአሜሪካ የመካከለኛው ምስራቅ አካሄድን ውድቅ ማድረጋቸውን የሚያሳይ የቅርብ ጊዜ ማሳያ ነው፡፡
ትራምፕ በሁለተኛው የሥልጣን ዘመናቸው ከቻይና እና ከሌሎች ተፎካካሪዎች ጋር ለመወዳደር የአሜሪካን ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖ በማጠናከር ላይ ትኩረት አድርገዋል፡፡
ተነታኞች እንደሚያስረዱት ከሳዑዲ ዐረቢያ ጋር የተደረገው የኒውክሌር ስምምነት አሜሪካ እስራኤልን ብታስቀይም እንኳ ቀጣናዊ ወዳጆቿን በጉያዋ አጥብቃ መያዝ እንደምትፈልግ መልዕክት ያስተላለፈ ነዉ፡፡
«በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ ሀገራት የኒውክሌር መሰረተ ልማታቸውን ማልማት ይፈልጋሉ፤ አሜሪካ ባትሳተፍበት እንኳ ይህን ማድረጋቸው አይቀርም ዋሽንግተን ደግሞ አሁን ላይ ይህን እውነታ እየተቀበለች ይገኛል» ሲሉ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡
ጥቅምን መሠረት ያደረገ የውጭ ሀገር ፖሊሲ የትራምፕ ሁለተኛው የሥልጣን ዘመን መለያ ሆኗል፡፡
ሀና ሰይፉ
ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም | 1 583 |
| 12 | Немає тексту... | 1 250 |
| 13 | ሪከርዶቹ ፀድቀዋል
🏃♀️🏃♂️🏃♀️🏃♂️
የዓለም አትሌቲክስ በዛሬው ዕለት ሰባት የአዋቂዎችና የአንድ ከ20 ዓመት በታች ሪከርዶችን ያፀደቀ ሲሆን አንዱ የኢትዮጵያዊቷ ትዕግስት አሰፋ ሪከርድ ሆኖ ተመዝግቧል።
ትዕግስት አሰፋ ባለፈው ሚያዚያ 18 (April 27/2026) በተካሄደው የለንደን ማራቶን 2 ሰዓት ከ15 ደቂቃ ከ41 ሴኮንድ በመግባት የሻምፒዮንነት ክብሯን ማስጠበቋ ይታወሳል። ይህም እሷው እራሷ ኤፕሪል 27/2025 በለንደን አስመዝግባው የነበረውን በሴቶች ብቻ የተሮጠ የማራቶን የዓለም ሪከርድ (2:15:50) በ9 ሴኮንዶች ያሻሻለችበት ነው።
ኢትዮጵያዊቷ አትሌት በመጨረሻዎቹ ማይሎች ከኬንያውያኑ ሔለን ኦቢሪ እና ጆይሲሊን ጄፕኮስጌይ ተነጥላ በመውጣት በድንቅ አጨራረስ ማሸነፍ ችላለች። ኦቢሪ በ2:15:53 የግል ምርጥ ሰዓቷን በማስመዝገብ ሁለተኛ ስትወጣ፣ ጄፕኮስጌይ ደግሞ በ2:15:55 ሶስተኛ ሆና አጠናቃለች። ይህም በአንድ የማራቶን ውድድር ሶስት ሴቶች ከ2 ሰዓት ከ16 ደቂቃ በታች ሲገቡ በታሪክ የመጀመሪያው ሆኗል።
በሌላ በኩል በዛው የለንደን ማራቶን ኬንያዊው ሰባስቲያን ሳዌ 1 ሰዓት ከ59 ደቂቃ ከ30 ሴኮንድ በሆነ ድንቅ ሰዓት በማጠናቀቅ በተመሳሳይ አዲስ የዓለም ሪከርድ መያዙ ይታወሳል። በዚህም የማራቶን ውድድርን ከሁለት ሰዓት በታች በመግባት የመጀመሪያው ሰው ሆኗል። በዚህም የሀገሩ ልጅ የሆነው ኬልቪን ኪፕቱም ኦክቶበር 8/2023 በቺካጎ ማራቶን ይዞት የነበረውን የ2 ሰዓት ከ00 ደቂቃ ከ35 ሴኮንድ የዓለም ሪከርድ በ65 ሴኮንዶች ማሻሻል ችሏል።
ሳዌ ከኢትዮጵያዊው ዮሚፍ ቀጀልቻ እና ከኡጋንዳው ጃኮብ ኪፕሊሞ ጋር ከፍተኛ ፉክክር ሲያደርግ ቆይቶ፣ ውድድሩን ለማጠናቀቅ አንድ ማይል ሲቀረው ቀድሞ በመውጣት በ1:59:30 አሸንፏል። ዮሚፍ ቀጀልቻም በ1:59:41 በማጠናቀቅ ከሁለት ሰዓት በታች መግባት የቻለ ሲሆን፣ ኪፕሊሞ ደግሞ በ2:00:28 ሶስተኛ ደረጃን አግኝቷል።
የሁለቱም ጀግና አትሌቶች የዓለም ሪከርድ በዛሬው ዕለት በይፋ መፅደቁን የዓለም አትሌቲክስ ማረጋገጫ ሰጥቷል።
በምስጋናው ታደሰ
ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም | 1 308 |
| 14 | Немає тексту... | 1 258 |
| 15 | በስደተኞች ጥቃት ምክንያት ደቡብ አፍሪካ በዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ተከሰሰች
የጃፓን ኩባንያ ለሰዎች የሚሆን አዲስና ለየት ያለ ፍሪጅ አስተዋወቀ
በጃፓን የሚገኘው ኤስ.ዲ.አር.ኤስ (SDRS) የተሰኘ ኩባንያ ለአንድ ሰው ብቻ የሚያገለግልና "ዶ ሂኤሞን ቦክስ" የተሰኘ ለየት ያለ የማቀዝቀዣ ሣጥን ለአለም አስተዋውቋል።
ይህ አዲስ ፈጠራ በይነመረብ ላይ "የሰው ልጅ ፍሪጅ" በሚል ቅጽል ስም ተሰጥቶት የበርካታ ሰዎችን ትኩረት እየሳበ ይገኛል።
የጃፓን የበጋ ወቅት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሞቀ መምጣቱ ለዜጎች ጤና አደገኛ እየሆነ በመምጣቱ በዚሁ ሐምሌ ወር ውስጥ ብቻ በቶኪዮ 48 ሰዎች በከፍተኛ ሙቀት ምክንያት ለህመም ተዳርገው ወደ ሆስፒታል ገብተዋል።
ይህንን ተከተሎ ግለሰቦችም ሆኑ ኩባንያዎች የሙቀቱን አደጋ ለመከላከል የሚያስችሉ አዳዲስ መንገዶችን ሲፈልጉ የቆዩ ሲሆን፣ ኤስ.ዲ.አር.ኤስ ኩባንያ ይህንን የማቀዝቀዣ ሣጥን ለመሥራት መነሻ የሆነውም ይህ እየጨመረ የመጣው ፍላጎት ነው።
"ዶ ሂኤሞን ቦክስ" ግልጽ የሆነ የመስታወት በር ያለው እና ለሰዎች ማቀዝቀዣነት ተብሎ የተሠራ ብረት ነክ ሣጥን ነው። ተጠቃሚዎች ወደ ውስጥ ገብተው አብሮ በተሠራው ወንበር ላይ ሲቀመጡ፣ ወደ ጭንቅላታቸው፣ አንገታቸው፣ ትከሻቸው እና ጀርባቸው የሚነፍሰውንና እስከ 5 ዲግሪ ሴልሺየስ የቀዘቀዘውን አየር ያገኛሉ።
እንደ አምራቹ ገለጻ፣ በሣጥኑ ውስጥ ለ10 ደቂቃ ያህል መቆየት የሰውነትን ሙቀት በፍጥነት ለመቀነስ እና በሙቀት ምክንያት የሚመጣን ድካም ወይም ህመም ለማስታገስ ይረዳል።
ይህ የሰው ልጅ ፍሪጅ በውስጡ በቋሚነት 15 ዲግሪ ሴልሺየስ አካባቢ የሚሆን የሙቀት መጠን የሚጠብቅ ሲሆን፣ ሦስት የማቀዝቀዣ እና የአየር ዝውውር አማራጮች ተገጥመውለታል።
በተጨማሪም ቅዝቃዜ እንዳይበዛ ከ20 ደቂቃ በኋላ በራሱ የሚጠፋ ሲሆን፣ መደበኛ ተንቀሳቃሽ ኤሲ ከሚወስደው የኤሌክትሪክ ኃይል ግማሽ ያህሉን ብቻ በመጠቀም ረገድ ኃይል ቆጣቢ ነው ተብሏል።
መሳሪያው ምንም ዓይነት ልዩ የገጠማ ሥራ የማያስፈልገው በመሆኑ፣ አብረው በተሠሩለት እግሮች አማካኝነት በቀላሉ ከቦታ ቦታ ማንቀሳቀስ ይቻላል ሲል ኦዲቲ ሴንትራል ዘግቧል።
ሐመረ ፍሬው
ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም | 1 012 |
| 16 | Немає тексту... | 1 134 |
| 17 | https://www.youtube.com/watch?v=Mx6DzEYkjbk | 1 237 |
| 18 | የኔታንያሁ የእስር ትእዛዝ በትራምፕ እና በኒውዮርክ ከንቲባ መካከል የፈጠረው ውዝግብ
የኒውዮርክ ከተማ የመጀመሪያው ሙስሊም ከንቲባ ዞህራን ማምዳኒ፣ የኢስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ለመካፈል ወደ ከተማዋ በሚመጡበት ወቅት በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ያቀረቡት ጥሪ፣ በሀገር ውስጥ ፖለቲካ እና በአለም አቀፍ ዲፕሎማሲ መካከል ከፍተኛ ፍጥጫ አነሳስቷል።
ማምዳኒ እና የከተማዋ የህግ መምሪያ ባደረጉት ግምገማ፣ የኒውዮርክ ከተማ ከአለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) የወጣውን የእስር ትእዛዝ በራሷ ስልጣን የመፈጸም ገለልተኛ የህግ አቅም እንደሌላት አረጋግጠዋል።
ሆኖም ከንቲባው የከተማዋ ፖሊስ በቀጥታ በቁጥጥር ስር ማዋል ባይችልም፣ የፌዴራል መንግስቱ ትእዛዙን እንዲያስፈጽም ጥሪ አቅርበዋል። ኔታንያሁ በኒውዮርክ ከተማ "የተጠሉ እና የማይፈለጉ" መሆናቸውን በመግለጽ፣ ነዋሪዎች በሚመጡበት ወቅት ህዝባዊ ተቃውሟቸውን እንዲያሰሙ አበረታተዋል።
በአንጻሩ የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር የኔታንያሁን ደህንነት ማረጋገጥ ዋና አላማው አድርጎታል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኔታንያሁ በአሜሪካ ምድር በሚቆዩበት ወቅት በማንኛውም መልኩ በቁጥጥር ስር እንደማይውሉ ዋስትና ሰጥተዋል።
የስቴት ሰክሬታሪ ማርኮ ሩቢዮ ይህንን ጥረት የመንግስት አካላት የተሳተፉበት ዘመቻ ሲሉ የገለጹት ሲሆን፣ የትራምፕ አስተዳደር የአለም አቀፉን ፍርድ ቤት ህጋዊ ስልጣን ሙሉ በሙሉ በመቃወም በፍርድ ቤቱ ባለስልጣናት ላይ ማዕቀብ ጥሏል።
ይህ ፍጥጫ የተቀሰቀሰው በጋዛ ውስጥ ከ73,000 በላይ ሰዎች ህይወት ማለፉን የጤና ባለስልጣናት ባረጋገጡበት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሁኔታውን ከዘር ማጥፋት ጋር በደመደመበት ወቅት ነው። ከአለም አቀፉ የፍትህ ፍርድ ቤት (ICJ) እና ከአለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) የተሰጡ ውሳኔዎች ለከንቲባው አቋም መነሻ ሆነዋል።
የማምዳኒ መግለጫ በከተማዋ በሚገኙ የአይሁድ ማህበራት ዘንድ፣ በተለይም በ UJA-Federation እና በኢስራኤል አምባሳደር ዳኒ ዳኖን ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞ አስነስቷል። ተቃዋሚዎቹ ከንቲባው የኒውዮርክን ህዝብ ለማገልገል እንጂ ኢስራኤልን ለፖለቲካ መጠቀሚያ ለማድረግ እንዳልተመረጡ በመግለጽ፣ አቋማቸው በከተማዋ የፀረ-ሴማዊነት ጥቃት እንዲስፋፋ ያደርጋል ሲሉ ኮንነዋቸዋል።
ከንቲባ ማምዳኒ ኔታንያሁን የማሰር ህጋዊ ስልጣን እንደሌላቸው ቢቀበሉም፣ የሟቾችን ቁጥር ወደ ህዝብ መድረክ በማውጣት እና የፓለስቲና ደጋፊዎችን ድምጽ በማሰማት በፌዴራል መንግስቱ ላይ የፖለቲካ ተጽእኖ ማሳደር ችለዋል። በትራምፕ አስተዳደር በኩል ያለው አቋም ግን የፌዴራል ስልጣንን በመጠቀም ኔታንያሁን ሙሉ በሙሉ ከህግ ተጠያቂነት የመጠበቅ ጽኑ ፍላጎትን እንደሚያሳይ ተመላክቷል።
ለዓለም አሰፋ
ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም | 1 207 |
| 19 | Немає тексту... | 1 152 |
| 20 | በወታደራዊ ጁንታ የሚመሩት ሶስቱ ሀገራት የአፍሪካ ዋንጫን ለማስተናገድ ጥያቄ አቀረቡ
ቡርኪና ፋሶ፣ ማሊ እና ኒጀር በ2032 የሚካሄደውን የአፍሪካ ዋንጫን በጋራ ለማዘጋጀት ጥያቄ አቀረቡ፡፡ ይሁንና በአካባቢው ካለው የፀጥታ ስጋት አንፃር ካፍ ዕድሉን እንዳይሰጣቸው ተቃውሟቸውን የሚያሰሙ አካላትም በርክተዋል፡፡
የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) በ2028፣ 2032 እና 2036 የሚካሄዱትን የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ለማዘጋጀት የሚፈልጉ ሀገራት እንዲወዳደሩ ጨረታ ማውጣቱ የሚታወስ ነው።
የማሊ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እንደገለጸው የሶስቱ ሀገራት የጋራ ማመልከቻ በ"ወንድማማችነት፣ ቀጣናዊ ትስስር እና በአፍሪካ እግር ኳስ ዘላቂ እድገት" ላይ ያተኮረ ነው። አክሎም ለአህጉራዊው ጨዋታ አዲስ ዕይታን ለማምጣት የሚያስችል "ጠንካራ እና ተአማኒነት ያለው ጥያቄ" ለማዘጋጀት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እንደሚሰራ አስታውቋል።
ሦስቱ ጎረቤታሞች የሳህል ሀገራት ህብረት (AES) የተሰኘውን የፀጥታ፣ የመሠረተ ልማት፣ የንግድ እና ኢኮኖሚ ልማት ትብብር ስምምነት በጋራ ከመሰረቱ በኋላ ባለፈው ዓመት ከምዕራብ አፍሪካ የኢኮኖሚ ማህበረሰብ (ECOWAS) በይፋ መውጣታቸው ይታወሳል።
ሆኖም በቡርኪና ፋሶ፣ ማሊ እና ኒጄር ውስጥ ያለው የፀጥታ ሁኔታ በታጣቂ ጂሃዲስቶች ጥቃት ምክንያት አሁንም በከፍተኛ ሁኔታ ያልተረጋጋ ነው። የሦስቱ ሀገራት ወታደራዊ መንግስታት ከምዕራባውያን የደህንነት አጋሮቻቸው በመራቅ ከሩሲያ ጋር ያላቸውን ግንኙነት አጠናክረዋል። ይህንን የሚቃወሙ የካፍ አባል ሀገራት ደግሞ የአፍሪካ ዋንጫው እንዳይሰጣቸው ይፈልጋሉ፡፡
የካፍ ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሞሴፔ ከሀገራቱ የቀረበውን “የ2032ቱን የአፍሪካ ዋንጫ በጋራ እናዘጋጅ” ጥያቄ አስመልክቶ የአህጉሪቱ እግር ኳስ መሪ አካል ማመልከቻውን ከመገምገሙ በፊት የደህንነት ዋስትና ያስፈልገው እንደሆነ ተጠይቀው “ሦስቱ ሀገራት ውድድሩን ለማዘጋጀት እንደማንኛውም የአህጉሪቱ ሀገራት እኩል እድል ይኖራቸዋ” ብለዋል።
"በወታደራዊ መንግስታት በመመራታቸው ምክንያት ምንም ዓይነት አሉታዊ ተፅዕኖ ወይም ጥላቻ አይደርስባቸውም፤ ነገር ግን የሰላም እና የደህንነት ጥያቄዎች ግድ ይላል፡፡ እሱ በእርግጠኝነት ትኩረት ሰጥተን የምንገመግመው ጉዳይ ነው። ነገር ግን የ2032 አፍሪካ ዋንጫ የት እንደሚካሄድ እስካሁን የተወሰነ ውሳኔ የለም። በእርግጥ ዲሞክራሲ፣ የመናገር ነፃነት እና መደበኛ ምርጫዎች የመደራደሪያ ነጥቦች አይደሉም፤ ከዛ ይልቅ በጣም ወሳኝ ናቸው፡፡ ነገር ግን በእግር ኳሱ በኩል ለመነጋገር ወደ እነዚያ ሀገራት እጓዛለሁ" ሲሉም አብራርተዋል።
በምስጋናው ታደሰ
ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም | 1 273 |
