ru
Feedback
Ethio Fm 107.8

Ethio Fm 107.8

Открыть в Telegram

በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Ethio Fm 107.8

Канал Ethio Fm 107.8 (@ethiofm107dot8) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 18 595 подписчиков, занимая 12 273 место в категории Новости и СМИ и 1 808 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 18 595 подписчиков.

Согласно последним данным от 14 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -127, а за последние 24 часа — -8, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 9.95%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 6.76% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 1 851 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 257 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 5.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 15 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Новости и СМИ.

18 595
Подписчики
-824 часа
-257 дней
-12730 день
Архив постов
በዩክሬን በተሰነዘሩት የሩሲያ ጥቃቶች የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ፤ በታዋቂው የኪቭ ካቴድራል ላይ የእሳት አደጋ ተከሰተ የሩሲያ ጦር በተለያዩ ዋና ዋና ከተሞች ላይ በሰነዘረው ተከታታይ ጥቃት በዩክሬን ቢያንስ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት ማለፉን የክልሉ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። የኪቭ ወታደራዊ አስተዳደር ኃላፊ ቲሙር ትካቼንኮ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ‹‹በኪቭ አንድ ሕፃንን ጨምሮ 23 ሰዎች ቆስለዋል በሚያሳዝን ሁኔታም የሟቾች ቁጥር ወደ አራት አድጓል›› ብለዋል። ቀደም ሲል የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ኢጎር ክሊሜንኮ እንደገለጹት፤በሰሜን ምስራቅ ዩክሬን በምትገኘው ካርኪቭ ከተማ ‹‹የእሳት ማጥፋት ሥራ ላይ የነበሩ አምስት የሀገር ውስጥ ድንገተኛ አደጋ አገልግሎት አባላት ተገድለዋል።›› ክሊሜንኮ በቴሌግራም ገጻቸው ላይ ‹‹ቢያንስ ሌሎች 5 ሰዎች ቆስለዋል›› ሲሉ የጻፉ ሲሆን፤ ጉዳቱ የደረሰው ሩሲያ በድጋሚ በሰነዘረችው ጥቃት መሆኑን አንስተዋል። የከተማዋ ከንቲባ ቪታሊ ክሊ ሰኞ ዕለት እንደተናገሩት በታዋቂው የኪቭ ፔቸርስክ ላቭራ የኦርቶዶክስ ገዳማት ግቢ ውስጥ የሚገኘው ዶርሚሽን ካቴድራል በሩሲያ ጥቃቶች ምክንያት የእሳት አደጋ ደርሶበታል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ከሞስኮ በስተደቡብ 200 ኪሎ ሜትር ያህል ርቃ በምትገኘው ቱላ በተባለችው የሩሲያ ከተማ ላይ የዩክሬን ሰው አልባ አውሮፕላን በሰነዘረው ጥቃት ሦስት ሰዎች ሲገደሉ፤ ሌሎች ሦስት ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የክልሉ ገዥ ሰኞ ዕለት አስታውቀዋል። ዲሚትሪ ሚልዬቭ ‹‹ዛሬ ምሽት የቱላ ከተማ የመኖሪያ መንደር በሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት ደርሶበታል›› ብለዋል፡፡ አክለውም ‹‹በጣም የሚያሳዝነው በደረሰን የመጀመሪያ ደረጃ መረጃ መሠረት ሦስት ሰዎች ተገድለዋል የአንድ ዓመት ሕፃንን ጨምሮ ሌሎች ሦስት ሰዎች ቆስለዋል›› ሲሉ ገልጸዋል። ሀና ሰይፉ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

photo content

የአሜሪካ እና ኢራን ስምምነት የነዳጅ ዋጋን ቀነሰ አሜሪካ እና ኢራን የሆርሙዝ የባህር መስመርን ለመክፈትና ጦርነቱን ለማቆም የስምምነት ማዕቀፍ ላይ መድረሳቸውን ተከትሎ በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ከፍ
የአሜሪካ እና ኢራን ስምምነት የነዳጅ ዋጋን ቀነሰ አሜሪካ እና ኢራን የሆርሙዝ የባህር መስመርን ለመክፈትና ጦርነቱን ለማቆም የስምምነት ማዕቀፍ ላይ መድረሳቸውን ተከትሎ በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ከፍተኛ ለውጥ ታይቷል። ስምምነቱን ተከትሎ የጃፓንና የደቡብ ኮሪያ አክሲዮን ገበያዎች እስከ 5.7 በመቶ የደረሰ ታሪካዊ ጭማሪ አሳይተዋል። በአንጻሩ የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ በ4.5 በመቶ በመቀነስ በአንድ በርሜል ከ83.40 ዶላር በታች ወርዷል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ የተጣለው የባህር ኃይል እገዳ እንዲነሳ ማዘዛቸውን ያስታወቁ ሲሆን፤ ይፋዊው የፊርማ ሥነ-ሥርዓት አርብ ዕለት በስዊዘርላንድ እንደሚካሄድ ተገልጿል። ስምምነቱ ሊባኖስን ጨምሮ የተኩስ አቁም ማድረግን፣ የማዕቀብ መነሳትን እና የ24 ቢሊየን ዶላር የኢራን ሀብት መልቀቅን ያጠቃልላል ተብሏል። የባህር መስመሩ መከፈቱ የዓለምን የነዳጅ እጥረት የሚያቃልል ቢሆንም፤ የተከማቹ መርከቦችን ለማፅዳትና የባህር ውስጥ ፈንጂዎችን ስጋት ለመቅረፍ ግን ወራትን ሊወስድ እንደሚችል ባለሙያዎች አስታውቀዋል። ሳራ ዮሐንስ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና እየተሰጠ ነው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኙ 1መቶ99 የፈተና ጣቢያዎች፣ የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መል
+2
የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና እየተሰጠ ነው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኙ 1መቶ99 የፈተና ጣቢያዎች፣ የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በዛሬው ዕለት በይፋ መሰጠት መጀመሩን የከተማዋ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። ከዛሬ ሰኔ 8 ጀምሮ እስከ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ ሦስት ቀናት የሚቆየውን ይህንን ከተማ አቀፍ ፈተና ለመውሰድ 85 ሺህ 17 ተማሪዎች ተመዝግበው ዝግጅት ሲያደርጉ መቆየታቸው ተገልጿል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ በሰጡት መግለጫ፤ ፈተናው በስኬት እንዲጠናቀቅ በየደረጃው የኮማንድ ፖስት አደረጃጀቶች መዋቀራቸውን ገልጸዋል። ለፈተናው ሂደት ጥራትና ተዓማኒነት ሲባልም፣ ልምድ ያላቸው የፈተና አስፈጻሚዎች ተመልምለው በየጣቢያዎቹ እንዲመደቡ መደረጉን ጠቁመዋል። ከጸጥታ አኳያም ፈተናው ያለምንም ችግር እንዲከናወን አስፈላጊው የጸጥታ አካላት ጥበቃና የክትትል ሥራ መመቻቸቱ ተመላክቷል። በአሁኑ ሰዓት በሁሉም የፈተና ጣቢያዎች ሂደቱን የሚከታተሉ የቢሮው አመራሮችና ባለሙያዎች በሥራ ላይ እንደሚገኙ ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመላክታል። ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው (ሰሜ ባላገሩ) ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው የተለያ
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው (ሰሜ ባላገሩ) ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው የተለያዩ ባህላዊ እና ሌሎች ይዘቶቸ ያሏቸው የሙዚቃ ሥራዎችን ለአድማጭ ተመልካች አበርክቷል፡፡ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ባለትዳር እና የአራት ልጆች አባት እንደነበር ፋና ዲጂታል ከቤተሰቦቹ ያገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡ ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹና ለአድናቂዎቹ መጽናናትን ይመኛል፡፡ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

ደቡብ አፍሪካ በአንድ ሳምንት ውስጥ ከ2 ሺህ 7መቶ በላይ የውጭ ሀገር ዜጎችን ወደ ሀገራቸው መለሰች ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ በህገ-ወጥ ስደት ላይ ጠንከር ያለ እርምጃ እንደሚወስዱ ቃል ከገቡ በኋላ ባለው አንድ ሳምንት ውስጥ፤ደቡብ አፍሪካ 2 ሺህ 7መቶ45 የውጭ ሀገር ዜጎችን ወደ ሀገራቸው መመለሷን የሀገሪቱ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ገልጸዋል፡፡ ከአፍሪካ ግዙፍ ኢኮኖሚዎች አንዷ የሆነችው ደቡብ አፍሪካ፤ከመላው አህጉሪቱ በህጋዊም ሆነ በህገ-ወጥ መንገድ የሚመጡ ስደተኛ ሰራተኞችን ለረጅም ጊዜ ስትስብ ቆይታለች። ሆኖም ከ30 በመቶ በላይ በሆነ ከፍተኛ የስራ አጥነት መጠን የተጠመደችው ሀገሪቱ በቅርብ ሳምንታት የተከሰቱ አዳዲስ ግጭቶችን ጨምሮ ተደጋጋሚ በስደተኞች ላይ ያነጣጠሩ ብጥብጦች አስተናግዳለች። ዱላ፣ ጅራፍ እና ጋሻ የያዙ ደቡብ አፍሪካውያ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እየተዘዋወሩ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው የውጭ ሀገር ዜጎች እስከ ሰኔ 30 ድረስ ለቀው እንዲወጡ ትዕዛዝ ሲያስተላልፉ ሰንብተዋል። ንግዶች በመዘረፋቸው እና የውጭ ዜጎች ዒላማ በመደረጋቸው ምክንያት እየጨመረ የመጣው የደህንነት ስጋት የናይጄሪያ፣ ማላዊ፣ ጋና፣ ዚምባብዌ እና ሞዛምቢክ ዜጎች በመንግስታቶቻቸው አማካኝነት የተዘጋጀውን በፍቃደኝነት ወደ ሀገር የመመለስ ጥሪ እንዲቀበሉ አድርጓቸዋል። መንግስት እንደገለጸው ወደ ሀገራቸው ከተመለሱት መካከል አብዛኞቹ በሀገሪቱ ውስጥ በህገ-ወጥ መንገድ ይኖሩ የነበሩ ናቸው። መንግስት እሁድ ዕለት እንደገለጸው የስደተኛ መጠለያ ካምፖችን የማያስተዳድር ሲሆን፤ በጊዜያዊነትም ቢሆን የማቋቋም ዕቅድ የለውም። እንደ ሀገሪቱ የስታስቲክስ ኤጀንሲ መረጃ ከሆነ በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ከሦስት ሚሊየን በላይ የውጭ ሀገር ዜጎች ይኖራሉ፤ ይህም ከጠቅላላው የህዝብ ብዛት 5.1 በመቶ ያህሉ ነው። እስከዳር ግርማ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

photo content
+1

በደቡብ ምስራቅ እስያ በህገ-ወጥ ደላሎች ተታለው የነበሩ ከ1 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ በደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት በተለይም በሚያንማር፣ በካምቦዲያና በላኦስ ችግር ውስጥ የነ
በደቡብ ምስራቅ እስያ በህገ-ወጥ ደላሎች ተታለው የነበሩ ከ1 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ በደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት በተለይም በሚያንማር፣ በካምቦዲያና በላኦስ ችግር ውስጥ የነበሩ ከ1 ሺህ 3መቶ በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን ንጋት ግሎባል ኢኒሼቲቭ የተሰኘው ድርጅት አስታወቀ። ተመላሾቹ በህገ-ወጥ ደላሎች አማካኝነት "ከፍተኛ ክፍያ ያለው ስራ አለ" በሚል ተታለው ወደ ታይላንድ ከተጓዙ በኋላ፣ በግዳጅ ድንበር ተሻግረው በሚያንማር በሚገኙ የኢንተርኔት ማጭበርበሪያ ማዕከላት ውስጥ ታስረው እንዲሰሩ ይገደዱ እንደነበር ተገልጿል። ንጋት ግሎባል ኢኒሼቲቭ እንደገለጸው፥ እነዚህ ዜጎች በታጠቁ አካላት እየተጠበቁ ለወራት በሰው መብት ረገጣና በከፍተኛ ስቃይ ውስጥ ቆይተዋል። ድርጅቱ ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ከአለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት ጋር በመተባበር ዜጎቹን የማስመለስና የመልሶ ማቋቋም ስራ ሲሰራ መቆየቱን ገልጿል። ወደ ሀገር ቤት የተመለሱ ዜጎች የተጎዳ የስነ-ልቦና ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙና የጤና ሚኒስቴር ባወጣው መለኪያ መሰረት አብዛኞቹ ከተገቢው የአዕምሮ ጤና ደረጃ በታች መሆናቸው በጥናት መረጋገጡ ተጠቁሟል። ህብረተሰቡ በተለይም የተማሩ ወጣቶች በማህበራዊ ሚዲያ በሚለቀቁ ሀሰተኛ የስራ ማስታወቂያዎች እንዳይታለሉ ድርጅቱ አሳስቧል። ሊዲያ ደሳለኝ   ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

"የኮንስትራክሽን ደህንነት ቅንጦት አይደለም" ሲሉ የዘርፉ ባለሙያዎች አሳስበዋል፡፡ በኢትዮጵያ አደጋዎች ሲከሰቱ የመደበቅና መረጃዎችን በአግባቡ የመመዝገብ ችግር እንዳለ ተገለጸ። በኢትዮጵያ አደጋዎች ሲከሰቱ የመደበቅና መረጃዎችን በአግባቡ የመመዝገብ ችግር እንዳለ የተገለጸው በሀገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በተዘጋጀው ዓለም አቀፍ የኮንስትራክሽን ጤናና ደህንነት ኮንፈረንስ ላይ ነው፡፡ በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ውስጥ የሥራ ላይ ደህንነትና ጤና አጠባበቅን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያለመው ይህ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ በአዲስ አበባ ተካሂዷል። የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂና ማኔጅመንት ባለሙያዎች ማህበር ከጄኔቫው ዓለም አቀፍ የማህበራዊ ዋስትና ማህበር (ISSA) ጋር በመተባበር ባዘጋጁት በዚህ መድረክ ላይ፣ በዘርፉ የሚታዩ ክፍተቶችና መፍትሄዎቻቸው በስፋት ተመክሮባቸዋል፤ በዘርፉ የአስተሳሰብ ለውጥ እንዲመጣም ጥሪ ቀርቧል፡፡ የማህበሩ ፕሬዝዳንት ኢንጅነር ሶፎንያስ ደነቀ ከኢትዮ ኤፍ ኤም ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ ኢትዮጵያ እንዲህ ያለውን መድረክ በማዘጋጀት ከአፍሪካ ሶስተኛዋ ሀገር መሆን ችላለች ብለዋል። ፕሬዝዳንቱ በሀገሪቱ ያለው የኮንስትራክሽን እድገት ፈጣን ቢሆንም፣ ከደህንነትና ጤና አጠባበቅ አንጻር ግን አሁንም በጅማሮ ደረጃ ላይ መሆናችንን ጠቁመዋል። ኢንጅነር ሶፎንያስ "ቪዥን ዜሮ" (Vision Zero) የተሰኘውን ዓለም አቀፍ መርህ በማንሳት፣ ይህ መርህ በግንባታ ሂደት ላይ ምንም ዓይነት አደጋ እንዳይከሰት የማድረግ ግብ ያለው ቢሆንም፣ በኢትዮጵያ ግን አደጋዎች ሲከሰቱ የመደበቅና መረጃዎችን በአግባቡ የመመዝገብ ችግር እንዳለ ገልጸዋል። ይህንን ለመቅረፍም "ኒር ሚስ" (Near miss) የሚባሉ፣ ለጥቂት የተረፉ አደጋዎችን ጭምር መዝግቦ የሚይዝ የቴክኖሎጂ ሥርዓትና ዳታቤዝ ለመፍጠር ማህበሩ እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። በዘርፉ የሚታየውን ትልቁን ተግዳሮት ሲያስረዱም፣ "የኮንስትራክሽን ደህንነት እንደ ቅንጦት እና እንደ ተጨማሪ ወጪ የሚታይበት የተሳሳተ አመለካከት ሊቀየር ይገባል" ብለዋል። ግንባታዎች ከዲዛይን ጀምሮ እስከ ፍጻሜያቸው ድረስ ለባለሙያዎችና ለአካባቢው ማህበረሰብ ደህንነት ትኩረት መስጠት እንዳለባቸው፣ ለዚህም የባለሀብቶች፣ የኮንትራክተሮችና የሱፐርቫይዘሮች በጋራ ተጠያቂነት ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። በኮንፈረንሱ የአዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛ ባለስልጣናትን ጨምሮ ከጀርመን፣ ስዊዘርላንድ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ኦስትሪያና ናይጄሪያ የተውጣጡ ከፍተኛ ባለሙያዎች ተሳትፈውበታል፡፡ አዲስ አለም አበበ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

photo content

ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት አለፈ ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ
ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት አለፈ ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታውቋል። አደጋው የደረሰው በዛሬው ዕለት ከደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች መካከል በሚገኘው የሐረጎ መንገድ ላይ መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡ በአደጋው ከሞቱት ሰዎች በተጨማሪም በርካታ ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸው ፖሊስ ገልጿል፡፡ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪው በግምት 100 ሜትር ጥልቀት ወዳለው ገደል ውስጥ መግባቱን አሚኮ ዘግቧል፡፡ በሕይወት የተረፉትን ወደ ሕክምና ቦታ ለማድረስ ርብርብ እየተደረገ ሲሆን፥ የአደጋው ምክንያት በመጣራት ላይ ይገኛል፡፡ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

አሜሪካ እና ኢራን የገቡበትን ጦርነት ለመቋጨት የሚያስችላቸው ስምምነት ላይ ደርሰዋል ስምምነቱ ዐርብ የሚፈረም ሲሆን ከዛሬ ሰኞ ጀምሮ ኢራን ጥቃት ማድረሷን አንደምትገታ ገልፃለች። የፓኪስታኑ ጠቅላይ
አሜሪካ እና ኢራን የገቡበትን ጦርነት ለመቋጨት የሚያስችላቸው ስምምነት ላይ ደርሰዋል ስምምነቱ ዐርብ የሚፈረም ሲሆን ከዛሬ ሰኞ ጀምሮ ኢራን ጥቃት ማድረሷን አንደምትገታ ገልፃለች። የፓኪስታኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ሸህባዝ ሻሪፍ ሀገሬ በሁለቱ ኃይሎች መካከል  የተፈጠረውን ልዩነት ለማጥበብ ስትሰራ ቆይታለች ብለዋል። ዘላቂ ተኩስ አቁም ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ላይ ቴህራንና ዋሽንግተን መድረሳቸውን ያስታወሱት ሻሪፍ፥ ሊባኖስንም ያጠቃለለ ውል መሆኑን አረጋግጠዋል። የኳታር አደራዳሪዎች ከ14 እስከ 15 ሰዓታት ከፍተኛ ውይይት አድርገው የመጣ ውጤት መሆኑም ታውቋል። በስምምነቱ መሰረት ሆርሙዝ ሰርጥ ሙሉ ለሙሉ ይከፈታም ተብሏል። አሜሪካም ሰርጡን በ30 ቀናት ውስጥ የመክፈት ግዴታ ይኖርባታል። ስምምነቱ በአሜሪካ ቁርጠኝነት ልክ የሚመዘን መሆኑን ያስታወሰችው ቴህራን፥ዋሽንግተን የቤት ስራዋን መስራት እንዳለባትም አሳስባለች። አሜሪካ በኢራን ዙሪያ ካሉ አካባቢዎች ጦሯን ማንሳትም ይኖርባታል። በ60 ቀናት ውስጥ ኑክሌርን ጨምሮ ቁልፍ ጉዳዮች ውይይት እየተደረገባቸው መፍትሔ እየተሰጣቸው ይሄዳል ፤ለቀጣናውም ሰላም ይመጣል የሚል እምነት ተጥሏል። ያም ሆኖ ግን ስምምነቱ ጥያቄ ያለበት መሆኑን የአሜሪካ ፖለቲከኞች ማንሳት ጀምረዋል። ሪፐብሊካኑ ሴናተር ሊንዲሴይ ግርሃም እና የቀድሞው የትራምፕ ምክትል ፕሬዚዳንት ማይክ ፔንስ ተጠቃሽ ናቸው። ጀርመን፣ጃፓን ፣ጣሊያን ፣ፈረንሳይ ፣እንግሊዝ፣ቱርክ እና ኒውዚላንድ ስምምነቱን በበጎ ከተመለከቱት አገራት መካከል ናቸው። የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝም ለስምምነቱ የሰሩትን ሁሉ አመስግነዋል ሲሉ ዘ ዋሽንግተን ፖስትና ሲ ኤን ኤን ዘግበዋል። ልዑል ወልዴ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

እስራኤል በቤሩት ላይ የፈፀመችውን ጥቃት "ትርጉም የለሽ " ሲሉ ትራምፕ አጣጣሉ የአሜሪካ እና የኢራን ስምምነት መቃረቡን ተከትሎ ትራምፕ በቤሩት የተፈጸሙ ጥቃቶችን በመኮንን ሁሉም ወገኖች እንዲቆጠቡ
እስራኤል በቤሩት ላይ የፈፀመችውን ጥቃት "ትርጉም የለሽ " ሲሉ ትራምፕ አጣጣሉ የአሜሪካ እና የኢራን ስምምነት መቃረቡን ተከትሎ ትራምፕ በቤሩት የተፈጸሙ ጥቃቶችን በመኮንን ሁሉም ወገኖች እንዲቆጠቡ አሳሰቡ ​ፕሬዚዳንት ትራምፕ በዛሬው ዕለት እስራኤል በቤሩት የሰነዘረችውን ጥቃት በመኮነን በሊባኖስ የሚደረጉ ጥቃቶች በአስቸኳይ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ​ትራምፕ በትሩዝ ሶሻል ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት ጥቃቱ “ሊፈጸም የማይገባው ነበር” በማለት፤ ማንም ሰው ላልተገደለበት ወይም ላልቆሰለበት ክስተት የተሰጠ “ኢምንትና ትርጉም የለሽ” ምላሽ ሲሉ ገልጸውታል። ​ቀጣይ መካካር ዲፕሎማሲያዊ መፍትሔን ሊያደናቅፍ እንደሚችል ያስጠነቀቁት ትራምፕ፤ ቀጣናዊ ስምምነቱ “በጣም መቃረቡን” እና ሊባኖስንም በዚሁ ሰፊ የሰላም ማዕቀፍ ውስጥ ሊያካትት እንደሚችል አጽንኦት ሰጥተዋል። ሰኔ 07/2018 ዓ.ም

ትራምፕ የአሜሪካ-ኢራን ስምምነት እሁድ ዕለት እንደሚፈረም ሲናገሩ፣ ቴህራን ግን በጊዜው ላይ ጥርጣሬ አላት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለውን ውጊያ ለማቆም የተዘጋጀው ስምምነት እሁድ ዕለት እንዲፈረም ቀጠሮ መያዙን ሲናገሩ ፤ ኢራን ግን በፊርማው ጊዜ ላይ ጥርጣሬ እንዳላት ገልፃለች ። የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባቃኢ ስለ ስምምነቱ ጊዜ ጥንቃቄ የተሞላበት አስተያየት የሰጡ ሲሆን፥ "የመግባቢያ ሰነዱ የሚፈረምበትን ትክክለኛ ቀን በትዕግስት መጠባበቅ ይኖርብናል፣ ሆኖም ግን ነገ [እሁድ] አይሆንም" ብለዋል። ትራምፕ በማህበራዊ ሚዲያ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ስምምነቱ አንዴ ተቀባይነት ካገኘ በኋላ ቁልፍ የባህር ትራንስፖርት መስመር የሆነው የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ "ለሁሉም ክፍት" እንደሚሆን ገልጸዋል። ቅዳሜ ዕለት፣ ዋና አገናኝ የሆነችው ፓኪስታንም ስምምነቱ በ24 ሰዓታት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ "በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጠበቅ" እና "ለዲጂታል (የኤሌክትሮኒክስ) ፊርማ ዝግጅት እያደረጉ" መሆኑን አስታውቃለች። ከዶናልድ ትራምፕ አስተያየት በፊት የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባቃኢ ስለ ስምምነቱ ጊዜ ጥንቃቄ የተሞላበት አስተያየት የሰጡ ሲሆን፥ "የመግባቢያ ሰነዱ የሚፈረምበትን ትክክለኛ ቀን በትዕግስት መጠባበቅ ይኖርብናል፣ ሆኖም ግን ነገ [እሁድ] አይሆንም" ብለዋል። በንግግሩ ውስጥ ሌላኛዋ አገናኝ የሆነችው የኳታር ልዑካን ቡድን እሁድ ዕለት ቴህራን መድረሱን የኢራን መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። የዋሽንግተን ፖስት ዘገባ እንዳስነበበው ይህ ጉብኝት ኢራን ስምምነቱን ትፈርማለች ተብሎ በሚጠበቅበት ጊዜ ላይ ተፅዕኖ ይኑረው አይኑረው በግልጽ የታወቀ ነገር የለም። ትራምፕ ቅዳሜ ዕለት በትሩዝ ሶሻል ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ፡ "ስምምነቱ ነገ እንዲፈረም ቀጠሮ ተይዟል፣ ከተፈረመ በኋላ ወዲያውኑ የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ለሁሉም ክፍት ይሆናል" ብለዋል። ትራምፕ የኢራንን የዳበረ ዩራኒየም ክምችት ለመጠቆም በፈለጉበት ግልጽ በሆነ ንግግራቸው "በትክክለኛው ጊዜ፣ ሁሉም ነገር ሲረጋጋ፣ እኛ ገብተን 'የኑክሌር ብናኙን' (Nuclear Dust) እንወስዳለን" ያሉ ሲሆን፣ ከጊዜ በኋላም እንደሚወድም አክለው ገልጸዋል። ሰኔ 07/2018 ዓ.ም

photo content

“ኢትዮጵያ ከኃይል ፖለቲካ ወጥታ ወደ “የሃሳብ ልዕልና” የታሸጋገረችበት አዲስ የፖለቲካ ባህል እየተገነባ  ነው”  አሉ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ስላሴ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ታዬ አፅቀ ስላሴ፣ የሀገር ግንባታም ሆነ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ከስሜታዊነትና ከደመነፍሳዊ አካሄድ የጸዱ መሆን እንዳለባቸው አሳሰቡ። ፕሬዝዳንቱ ይህንን ያሉት የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ካውንስል፣ የሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ማጠቃለያ አስመልክቶ ባዘጋጀው ይፋዊ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ነው። ፕሬዝዳንት ታዬ በንግግራቸው የሀገሪቱን የፖለቲካ ታሪክ ወደ ኋላ መለስ ብለው የቃኙ ሲሆን፣ ቀደም ሲል በውይይትና በጠረጴዛ ዙሪያ መፈታት የነበረባቸው ልዩነቶች በኃይል አማራጭ ለመፍታት በመሞከራቸው ምክንያት ሀገሪቱ ለከፍተኛ የዲሞክራሲና የእድገት መጓተት መዳረጓን ገልጸዋል። ሆኖም በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ከኃይል ፖለቲካ ወጥታ ወደ “የሃሳብ ልዕልና” የታሸጋገረችበት አዲስ የፖለቲካ ባህል እየተገነባ መሆኑን በጽኑ አስምረውበታል። ወቅታዊ ሁኔታዎችን በተመለከተም፣ የተወሰኑ የውጭ ሚዲያዎችና አካላት በኢትዮጵያ ውስጥ ግጭት እንዲቀሰቀስና እንዲባባስ ሆን ብለው ጥረት ማድረጋቸውን ፕሬዝዳንቱ በንግግራቸው ወቅሰዋል። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ ህዝብ የእነዚህን አካላት ፍላጎት ያከሸፈ የበሰለ የፖለቲካ ስልጣኔ ማሳየቱን ገልጸዋል። ህዝቡ በትዕግስትና በጨዋነት ረጅም ሰልፎችን በመጠበቅ ድምፁን መስጠቱ፣ ለሀገራዊ ሰላምና አንድነት ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየበትና ታሪካዊ ፍርዱን የሰጠበት መሆኑን ፕሬዝዳንት ታዬ በኩራት ተናግረዋል። ምርጫው በሰላም መጠናቀቁን ተከትሎ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፉት ፕሬዝዳንቱ፣ ምርጫውን ላሸነፉ አካላትም ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል። ምርጫ ማሸነፍ የክብርና የድል መግለጫ ብቻ ተደርጎ መወሰድ እንደሌለበት የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፣ ይልቁንም ድሉ የሀገርን ህልውና የማስጠበቅና የህዝብን ህይወት የመለወጥ እጅግ ከባድ “የቤት ስራ” መሆኑን አስገንዝበዋል። በመሆኑም አሸናፊዎች የህዝብን ድምፅ በትህትና በማዳመጥ፣ በታማኝነትና በንጽህና ሀገሪቱን ወደ ተሻለ የልማት ምዕራፍ ሊመሩ እንደሚገባ ጥሪያቸውን አቅርበዋል። በመጨረሻም ፕሬዝዳንት ታዬ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ ለጸጥታ አካላትና ለሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የምርጫ ሂደቱን በነጻነትና በገለልተኝነት ለመምራት ላሳዩት ቁርጠኝነት ከፍተኛ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በዚህ ታሪካዊ መርሃ ግብር ላይ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀገር መከላከያና የፖሊስ ከፍተኛ መኮንኖች፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እንዲሁም የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት መገኘታቸው ታውቋል። ልዑል ወልዴ ሰኔ 06/2018 ዓ.ም

photo content

የኃይል አቅርቦት ለተወሰኑ ሰዓታት በአዲስ አበባ ፣ በአዳማ እና መቀሌ የሚቋረጥባቸው ቦታዎች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ነገ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ፣ በአዳማ እና በመቀሌ ከተሞች በሚገኙ የተለያዩ አካባቢዎች ላይ የጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል የኃይል አቅርቦት ለተወሰኑ ሰዓታት እንደሚቋረጥ አስታወቀ። ተቋሙ በዕቅድ ለሚያከናውነው ለዚህ የጥገና ሥራ ደንበኞች አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉና በትዕግስት እንዲጠብቁም አሳስቧል። የኤሌክትሪክ አገልግሎት በሰጠው መግለጫ መሠረት የኃይል መቋረጡ ነገ ጠዋት የሚጀምር ሲሆን፣ በተለያዩ አካባቢዎች እንደየሥራው ስፋትና ዓይነት ከስድስት እስከ ስምንት ሰዓታት ከግማሽ የሚቆይ ይሆናል። በዚህም መሠረት በአዲስ አበባ ከተማ ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት እስከ ቀኑ ስምንት ሰዓት ከግማሽ ድረስ በአፍንጮ በር መስጊድ፣ ደጃች ውቤ፣ ጊዮርጊስ እሳት አደጋ፣ ችሎት አደባባይ፣ ዘበኛ ሰፈር፣ ሾላ፣ በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ በሰሜን ሆቴል ጫፍ፣ በቀለመወርቅ ትምህርት ቤት፣ በዶሮ ተራ፣ በራስ ደስታ አካባቢ፣ በአርበኞች ትምህርት ቤት እና በዕንቁላል ፋብሪካ አደባባይ ዙሪያ የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል። በተመሳሳይ ሁኔታ ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ከግማሽ ድረስ በጎፋ ካምፕ ኮንዶሚኒየም፣ ጀርመን አደባባይ፣ ጉራጌ ሰፈር፣ ትግሬ ሰፈር፣ ካፍ ነዳጅ ማደያ ጀርባ፣ ሀግቤስ አራት መንታ፣ ጎጃም በረንዳ ጫፍ፣ ጅንአድ፣ አበበች ጎበና፣ ቄጤማ ተራ፣ ፓስተር አደባባይ፣ አቤት ሆስፒታል፣ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን፣ ዳትሰን ሰፈር፣ ሰን ሆቴል፣ 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ እና አዲስ አበባ ሜዲካል ኮሌጅ አካባቢዎች መብራት የማይኖር መሆኑ ታውቋል። ከዚህ በተጨማሪም ከጠዋቱ ሶስት ሰዓት እስከ ቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ከግማሽ ባለው ጊዜ ውስጥ በድሬ ከአስፋልት በታች፣ ጉዳ፣ ኬላ፣ ጉዮ፣ በታጠቅ ኢንዱስትሪ መንደር በከፊል፣ ቶልቻ፣ ሰንጎታ እና በገፋርሳ ሰብስቴሽን ዙሪያ የጥገና ሥራው እንደሚከናወን ተገልጿል። የአቅርቦት መቋረጡ ከአዲስ አበባ ውጭ ባሉ የክልል ከተሞችም የሚተገበር ሲሆን በአዳማ ከተማ የሚገኙት አዳማ ሆስፒታል፣ ፖስታ ቤት አካባቢ፣ ሁሩታ ከተማ እና ሰኞ ገበያ ከጠዋቱ ሶስት ሰዓት እስከ ቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ከግማሽ ድረስ የኃይል አቅርቦት ያጣሉ። በመቀሌ ከተማ ደግሞ በኢትዮ-ሸዊት ብረት ሥራ እና በአካባቢው ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ አራት ሰዓት ከግማሽ ድረስ ሙሉ በሙሉ መብራት እንደሚቋረጥ ተቋሙ አስታውቋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ መደበኛ መስመር ላይ እስኪመለስ ድረስ ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠብቁ የጠየቀ ሲሆን፣ ለተፈጠረው ጊዜያዊ መስተጓጎልም አስቀድሞ ይቅርታ ጠይቋል። ሰኔ 06/2018 ዓ.ም

photo content

ኒጀር ግብረ-ሰዶማዊነትን በህግ ከከለከሉ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት ተርታ ተቀላቅላለች ። የኒጀር ወታደራዊ ሁንታ ግብረ-ሰዶማዊነትን በወንጀል የሚቀጣ አዲስ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ማውጣቱን አስታወ
ኒጀር ግብረ-ሰዶማዊነትን በህግ ከከለከሉ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት ተርታ ተቀላቅላለች ።  የኒጀር ወታደራዊ  ሁንታ  ግብረ-ሰዶማዊነትን በወንጀል የሚቀጣ አዲስ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ማውጣቱን አስታወቀ። ከሀገሪቱ የፍትህ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ አዲሱ ህግ ከትናንት በስቲያ ሐሙስ ጀምሮ ገቢራዊ ተደርጓል።  ስራ ላይ የዋለው አዲሱ ህግ  ግብረ-ሰዶማዊነትን ወይም መሰል ድርጊቶችን የፈጸመ ወይም ለመፈጸም የሞከረ ማንኛውም ሰው ከ5 እስከ 10 ዓመት በሚደርስ እስራት እና በገንዘብ ይቀጣል። ቅጣቱ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸውን ሰዎች ጋብቻ ያስፈጸሙ ሰዎችን፣ ምስክሮችን፣ ጋብቻው እንዲፈጸም ፍቃድ የሰጡትን እንዲሁም የሰርጉን አዘጋጆች በሙሉ ያጠቃልላል ነው የተባለው። ከዚህ ቀደም በኒጀር ግብረ-ሰዶማዊነት በህግ የተከለከለ ባይሆንም፣ በህብረተሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ማግለል ይደርስበት ነበር። ኒጀር ይህንን እርምጃ በመውሰድ ግብረ-ሰዶማዊነትን በህግ ከከለከሉ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት ተርታ ተቀላቅላለች ።  ግብረሰዶማዊነት በሴኔጋል፣ ኬንያ፣ ሴራሊዮን እና ታንዛኒያ እስከ 10 ዓመት እና ከዚያ በላይ በሆነ እስራት ያስቀጣል። በሶማሊያ፣ ዩጋንዳ እና ሞሪታኒያ ደግሞ የወንጀሉ ቅጣት እስከ ሞት ፍርድ ሊደርስ እንደሚችል ዘገባው አመልክቷል። ሰኔ 06/2018 ዓ.ም