ru
Feedback
ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

Открыть в Telegram

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን። YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8 Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

Канал ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit (@ortodoxmezmur) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 169 217 подписчиков, занимая 141 место в категории Религия и духовность и 140 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 169 217 подписчиков.

Согласно последним данным от 05 сентября, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 871, а за последние 24 часа — 33, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 11.97%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 6.21% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 20 253 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 10 506 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 114.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን። YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8 Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 06 сентября, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

169 217
Подписчики
+3324 часа
+897 дней
+87130 дней

Загрузка данных...

Облако тегов
Нет данных
Возникли проблемы? Пожалуйста, обновите страницу или обратитесь к нашему support-менеджеру .
Входящие и исходящие упоминания
---
---
---
---
---
---
Привлечение подписчиков
сентябрь '26
сентябрь '26
+134
в 6 каналах
август '26
+1 378
в 34 каналах
Get PRO
июль '26
+1 075
в 22 каналах
Get PRO
июнь '26
+769
в 28 каналах
Get PRO
май '26
+562
в 34 каналах
Get PRO
апрель '26
+1 144
в 51 каналах
Get PRO
март '26
+878
в 24 каналах
Get PRO
февраль '26
+1 112
в 26 каналах
Get PRO
январь '26
+727
в 30 каналах
Get PRO
декабрь '25
+613
в 28 каналах
Get PRO
ноябрь '25
+765
в 47 каналах
Get PRO
октябрь '25
+611
в 36 каналах
Get PRO
сентябрь '25
+475
в 35 каналах
Get PRO
август '25
+1 063
в 36 каналах
Get PRO
июль '25
+638
в 30 каналах
Get PRO
июнь '25
+710
в 49 каналах
Get PRO
май '25
+589
в 35 каналах
Get PRO
апрель '25
+1 793
в 48 каналах
Get PRO
март '25
+2 355
в 25 каналах
Get PRO
февраль '25
+13 101
в 29 каналах
Get PRO
январь '25
+2 277
в 41 каналах
Get PRO
декабрь '24
+2 258
в 28 каналах
Get PRO
ноябрь '24
+2 634
в 33 каналах
Get PRO
октябрь '24
+3 003
в 22 каналах
Get PRO
сентябрь '24
+10 013
в 21 каналах
Get PRO
август '24
+591
в 32 каналах
Get PRO
июль '24
+262
в 15 каналах
Get PRO
июнь '24
+292
в 20 каналах
Get PRO
май '24
+1 151
в 37 каналах
Get PRO
апрель '24
+1 532
в 30 каналах
Get PRO
март '24
+1 639
в 35 каналах
Get PRO
февраль '24
+486
в 26 каналах
Get PRO
январь '24
+992
в 28 каналах
Get PRO
декабрь '23
+1 222
в 47 каналах
Get PRO
ноябрь '23
+725
в 28 каналах
Get PRO
октябрь '23
+225
в 19 каналах
Get PRO
сентябрь '23
+1 307
в 0 каналах
Get PRO
август '23
+279
в 0 каналах
Get PRO
июль '23
+425
в 0 каналах
Get PRO
июнь '23
+493
в 0 каналах
Get PRO
май '23
+751
в 0 каналах
Get PRO
апрель '23
+1 505
в 0 каналах
Get PRO
март '23
+332
в 0 каналах
Get PRO
февраль '23
+1 312
в 0 каналах
Get PRO
январь '23
+802
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '22
+456
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '22
+214
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '22
+164
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '22
+276
в 0 каналах
Get PRO
август '22
+742
в 0 каналах
Get PRO
июль '22
+360
в 0 каналах
Get PRO
июнь '22
+235
в 0 каналах
Get PRO
май '22
+209
в 0 каналах
Get PRO
апрель '22
+1 529
в 0 каналах
Get PRO
март '22
+323
в 0 каналах
Get PRO
февраль '22
+160
в 0 каналах
Get PRO
январь '22
+266
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '21
+229
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '21
+668
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '21
+917
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '21
+502
в 0 каналах
Get PRO
август '21
+3 491
в 0 каналах
Get PRO
июль '21
+1 305
в 0 каналах
Get PRO
июнь '21
+452
в 0 каналах
Get PRO
май '21
+1 455
в 0 каналах
Get PRO
апрель '21
+5 707
в 0 каналах
Get PRO
март '21
+3 749
в 0 каналах
Get PRO
февраль '21
+2 802
в 0 каналах
Get PRO
январь '21
+4 695
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '20
+174 539
в 0 каналах
Дата
Привлечение подписчиков
Упоминания
Каналы
06 сентября+21
05 сентября+44
04 сентября+43
03 сентября+14
02 сентября+9
01 сентября+3
Посты канала
አዲስ ዓመት አዲስ ዘመን አዲስ አመት አዲስ ዘመን  የሰጠኸን ጌታ ክበር ተመስገን/2/
አዝ
ምድርን በአበባ አጊጠህ አሳምረህ ክረምትና በጋን ታፈራርቃለህ የማታንቀላፋ ሳተፍ እንኳ ለአፍታ ተመስገን አዲስ ቀን በሰጠኸን ጌታ 2 እንኳን ለዚህ ቀን አደረሳችሁ እንኳን እግዚአብሔር አብሮ አደረሰን 2
አዝ
የመከራ ዘመን ታለፈና ዛሬ ለአዲስ አመት በቃን ይኸውና ዛሬ ዘመን ለፍስሃ ሰተኸናልና የዘመናት ጌታ ይድረስህ ምስጋና 2 እንኳን ለዚህ ቀን አደረሳችሁ እንኳን እግዚአብሔር አብሮ አደረሰን 2
አዝ
በአመቱ ያድርሰን ብለን ተመራርቀን የዓመታት ባለቤት ይኸው አደረሰን እድሜ ጤና ሰጥተህ ለዚህ ቀን ደርሰናል የጊዜ ባለቤት በብዙ ረድቶናል 2 እንኳን ለዚህ ቀን አደረሳችሁ እንኳን እግዚአብሔር አብሮ አደረሰን 2
አዝ
ከሩቅ ሀገር ያለው ላገሩ አብቃውና የአባቶች ምርቃት ያግኝ እንደገና ውዳሴ ምስጋና ለአንተ እናቀረባለን 2 እንኳን ለዚህ ቀን አደረሳችሁ እንኳን እግዚአብሔር አብሮ አደረሰን 2
አዝ
የመከራ ዘመን ታለፈና ዛሬ ለአዲስ አመት በቃን ይኸውና ዛሬ ዘመን ለፍስሃ ሰተኸናልና የዘመናት ጌታ ይድረስህ ምስጋና 2 እንኳን ለዚህ ቀን አደረሳችሁ እንኳን እግዚአብሔር አብሮ አደረሰን 2 ዘማሪ ዳግማዊ ደርቤ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️

2
​​​​ጳጉሜን ጳጉሜን የሚለው ስያሜዋ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙ ጭማሪ ማለት ነው፡፡ በግእዝ ተውሳክ ማለት ሲሆን ተውሳክ ማለት ተጨማሪ ማለት ነው፡፡ “ወሰከ - ጨመረ” ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ነው፡፡ ከኢትዮጵያ ውጭ ያሉ ሌሎች ሀገሮች ጳጉሜን የወር ተጨማሪ ያደርጓታል፡፡ ይኸውም ይታወቅ ዘንድ እኛ የወርን ቁጠር 30 ስናደርግ እነርሱ 31 ብለው የሚቆጥሩት ወር አላቸው፡፡ ይኹን እንጂ ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ጳጉሜን የወር ተጨማሪ ሳያደርጉ የዓመት ተጨማሪ አድርገዋታል፡፡ ጳጉሜን በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ትመጣለች፡፡ በአራት ዓመት አንዴ ማለትም በዘመነ ሉቃስ መጨረሻ በዘመነ ዮሐንስ መግቢያ ጳጉሜን ስድስት ቀን ትሆናለች፡፡ በዚህም ሀገራችን ኢትዮጵያ የአስራ ሦስት ወራት ጸጋ /Thirty months of sunshine/ በመባል ትታወቃለች፡፡ ጳጉሜን ስድስት በምትሆንበትም ጊዜ ጾመ ነቢያት /የገና ጾም/ ህዳር 14 ቀን ይገባና ታህሳስ 28 ቀን ጾሙ ተፈትቶ የልደት በዓል ይከበራል፡፡ በቅድስት ቤተክርስቲያን ካሉት ሁለት የፈቃድ አጽዋማት መካከል አንዱ በዚህ በጳጉሜን ወር የምንጾመው የፈቃድ ጾም ነው። ይህም ጾመ ዮዲት በመባል ይታወቃል፡፡ ይህ ግን እንደ አንደኛው የፈቃድ ጾም /ጽጌ ጾም/ በብዙዎች ዘንድ የታወቀ አይደለም፡፡ የዮዲት ጾም የሚባለውም እርሷ ስለ ጾመችው ነው፡፡ እዚህ ላይ ዮዲት ተብላ የተጠቀሰችው በቤተክርስቲያን ታሪክ ትምህርት ላይ በጥፋት ሥራዋ በተደጋጋሚ የምትጠቀሰው ዮዲት ጉዲት እንዳልሆነች ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡ ወደ ታሪኩ ስንመለስ የፋርስ ንጉስ ናቡከደነጾር በሠራዊቱ ተመክቶ ሹም ጠላት አጥፋ ድንበር አስፋ ካመነው እጅ መንሻ እየተቀበልህ ያላመነውን እያሳመንህ ና ብሎ ለጦር አበጋዙ ለሆሎፎርኒስ ትዕዛዝ ሰጠ፡፡ ዮዲ 2፥2-7፡፡ እርሱም እንደታዘዘው በኃይላቸው የታመኑ 12ሺህ እግረኞችንና በፈረስ የተቀመጡ 12ሺህ ጦረኞችን እየመራ ዘምቶ ካመነው እጅ መንሻ እየተቀበለ ያላመነውን እያሳመነ ብዙ ሀገሮችን እያጠፋ ሲሔድ ከአይሁድ ከተማ ደረሰ በዚህም ብዙ ጥፋት በመድረሱ የእስራኤል ልጆች አለቀሱ፡፡ ዮዲት ባሏ ሞቶባት ከወንድ ርቃ ንጽሕናዋን ጠብቃ በጾም በቀኖና በሀዘን ተወስና ትኖራለች በተፈጠረው ጥፋት ህዝቡ ላይ ለመጣው መከራ ማቅ ለብሳ በራስዋ ላይ ትብያ ነስንሳ ወደ እግዚአብሔር አለቀሰች፡፡ የፍጥረቱን ጥፋት የማይሻ እግዚአብሔር አምላክም ሕዝቡን የሚያድኑበትን መንገድ ለመጠየቅ ሱባኤ በገባች በሦስተኛው ቀን ገለፀላት፡፡ ዮዲ 8፥2፡፡ ከዚህ በኋላ ጠላታቸውን በዮዲት ምክንያት እስራኤላውያን እስከ ዮርዳኖስ እየተከተሉ አጥፍተዋቸዋል፡፡ ዮዲት ጠላቷን ለማጥፋት የቻለችው በጾምና በጸሎት ከእግዚአብሔር አምላክ ኃይል አግኝታ ነው፡፡ ስለዚህ ምዕመናን ጥንተ ጠላታችን ሰይጣንን ፈቃደ ሥጋን ለማሸነፍ በጾም ከፈጣሪያችን ኃይልን መጎናጸፍ አለብን ብለው ጳጉሜን በፈቃድ ይጾማሉ፡፡ የጳጉሜን ወር ዕለተ ምጽአት የሚታሰብባትም ወር ነች፡፡ ይህም ጳጉሜን የዓመታት መሸጋገሪያ ጨለማው የክረምት ወቅት ወደ ማብቂያው የምናልፍባት እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም ከጊዜያዊው ወደ ዘላለማዊ ከምድራዊ ወደ ሰማያዊ ከዚህ ዓለም ወደ ወዲያኛው መሸጋገሪያ ነውና፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
7 899
3
አንድ ዓመት 365 ¼ የተባለው ለምንድን ነው? ፣ ጷጉሜ የተባለችው ወርስ ከየት መጣች? ::::::::::::::::::::::: (በአለቃ ዕፁብ ማናዬ)::::::::::: :::::::: ሼር በማድረግ የበኩልዎን ይወጡ ብዙዎቻችን ስለ ዓመት ስንናገርና ለልጆቻችን ስናስተምር አንድ ዓመት 365 ¼ ቀንት፣ 52 ሳምንታት እና 12 ወራት በማለት እንናገራለል፡፡ እውነትም ልክ ነው፤ ነገር ግን 365 ¼ ማለት ምን ማለት ነው? ¼ የሚባል ቀን አለን? 12 ወራት በሠላሳ በሠላሳ ቀናት የተከፋፈሉ ሆነው ድምራቸው 12X30 = 360 ነው፡፡ ታዲያ 5ቀናት እና ¼ የተባለው ከየት መጣ? ጷጉሜስ የተባለችው ወርስ ከየት መጣች? ለሚባሉትን ጥያቄዎች አስተዋዮች ይጠይቃሉ፡፡ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ግን እንደሚከተለው ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ አስቀምጠውልናል፡፡(ይህ መልስ ብዛት ካላቸው የብራና ጽሑፎች ተውጣቶ ቀለል ባለ ዘዴ የቀረበ ነው፡፡) ይህ ትምህርት የሚገኘው አቡሻኽር በተባለው የቤተክርስቲያን ትምህርት ነው፡፡ ትምህርቱ ሰፊ ነው፡፡ አብዛኛውም የሒሳብ ስሌት ያለበትም ነው፡፡ ከላይ የቀረቡትን ጥያቄ መልስ ለማስረዳት ብዛት ያለውን የትምህርቱ ስሌት ማሳየት ይጠይቃል ነገር ግን ሁሉንም በሚመጥን መልኩ ለማቅረብ እንሞክራለን፡፡ ወደተነሳንበት ስንመለስ ስንት ወቅቶች አሉን ከተባለ አራት ናቸው፡፡ እነሱም ክረምት(ከሰኔ26- መስከረም25)፣ መፀው/መከር(ከመስከረም26- ታኅሣሥ25)፣ በጋ/ሐጋይ (ከታኅሣሥ26 - መጋቢት25)፣ ጸደይ/በልግ (ከመጋቢት26 - ሰኔ25) ነው፡፡ እያንዳንዱ ወቅት ደግሞ ሦስት ወራትን ይዟል፡፡ 3X30=90 ነው፡፡ 90 ሲባዛ በ4 ደግሞ 360 ነው፡፡ እንግዲህ የስሌቱ ነገር የሚጀምረው እዚህ ላይ ነው፡፡ ::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::: ከላይ አንድ ወቅት 90 ቀን ሳይሆን 91 ቀን 7ሰዓት እና 30 ደቂቃ ነው፡፡ ይህ የሚሆነው የየወሩ ቀን ማጠር እና መርዘምን ተከትሎ በሚመጣ ልዩነት ነው፡፡ ለምሳሌ መስከረም ላይ 12 ሰዓት አይመሽም ብርሃን ነው፡፡ ታኅሣሥ ላይ ግን 12 ሰዓት ጭልምልም ይላል፡፡ ሌሊቱም ረዥም ነው፡፡ ለምሳሌ እነዚህ ቀረቡ እንጂ እያንዳንዱ ወር የተለያየ ልዩነት አለው፡፡ ስለዚህ ጠቅላላውን አራቱንም ወቅቶች ስንደምራቸው የምናገኘው ውጤት አንድ ዓመትን ያስገኙልናል፡፡ ክረምት 91 ቀን 7 ሰዓት ከ30 ደቂቃ መፀው 91 ቀን 7 ሰዓት ከ30 ደቂቃ በጋ/ሐጋይ 91 ቀን 7 ሰዓት ከ30 ደቂቃ ጸደይ 91 ቀን 7 ሰዓት ከ30 ደቂቃ ::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::: ጠቅለል አድርገን ስንደምረው ዘጠና ዘጠናው ቀን ስንደምረው 90 X 4 = 360 ይሆናል፡፡ ይህ የአሥራሁለት ወሩን ያዘ ማለት ነው፡፡ ::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::: የየወቅቱን አንዳንድ ቀን ስንደምር 1 X 4 = 4 ይሆናል፡፡ ይህ የጷጉሜ አራቱ ቀናት ናቸው፡፡ ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡ የቀሩትን 7 ሰዓት እና 30 ደቂቃዎች ስንደምራቸው 30 ሰዓት ይመጣል፡፡ ወደ ዕለት ሲቀየር 1 ቀን እና 6 ሰዓት ይሆናል ማለት ነው፡፡ ከላይ ካገኘነው 4 ጋር ሲደመር 5 ቀናት እና 6 ሰዓት ይሆናል ማለት ነው፡፡ :::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::: በጠቅላላ አንድ ዓመት 365 ከ6ሰዓት ወይም ¼ የሚባለው ለዚህ ነው ይህ ስድስት ሰዓት በአራት ዓመት አንድቀን ሆኖ ጷጉሜ ስድስት እንድትሆን ያደርገዋል፡፡ ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡ ጷጉሜ የግሪክ ቃል ነው በእና ተውሣከ ውርኅ ትባላለች ማለት የወር ጭማሪ ወይንም ትርፍ ወር የተባለችው ለዚህ ነው፡፡ ይህቺ ወር በ600 ዓመት 7 ትሆናለች ነገር ግን ሊቃውንት ይቺን የትርፍ ትርፍ ናትና ከስሌት ውጪ የማይኖርባት በማለት ይገልጧታል፡፡ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur
7 256
4
ነሐሴ ፴ /30/ በዚህች ዕለት ከዐሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ የሆነው ታላቁ ነቢይ ሚልክያስ አረፈ። እግዚአብሔር አምላክ በነቢዩ አንደበት አድሮ እንዲህ ይለናል። ሰው እግዚአብሔርን ይሰርቃልን?
ነሐሴ ፴ /30/ በዚህች ዕለት ከዐሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ የሆነው ታላቁ ነቢይ ሚልክያስ አረፈ። እግዚአብሔር አምላክ በነቢዩ አንደበት አድሮ እንዲህ ይለናል። ሰው እግዚአብሔርን ይሰርቃልን? እናንተ ግን እኔን ሰርቃችኋል። እናንተም። የሰረቅንህ በምንድር ነው? ብላችኋል። በአሥራትና በበኵራት ነው። ትንቢተ ሚልክያስ 3:8 እንዴት አድርጌ ነው ከ5ሺህ ብር ደሞዝ በዛ ላይ የኑሮ ውድነቱ ተጨምሮበት አስራት የማወጣው? ብላችሁ ብትጠይቁም እግዚአብሔር በነቢዩ አድሮ እንዲህ ይለናል። በቤቴ ውስጥ መብል እንዲሆን አሥራቱን ሁሉ ወደ ጎተራ አግቡ፤ የሰማይንም መስኮት ባልከፍትላችሁ፥ በረከትንም አትረፍርፌ ባላፈስላችሁ በዚህ ፈትኑኝ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። ትንቢተ ሚልክያስ 3:10 ቅዱስ ሚልክያስም በበጎ ተጋድሎው እግዚአብሔርን ከአገለገለ በኋላ በዛሬዋ ዕለት ከዚህ ዓለም በመፍለስ በሰላም አረፈ። ሚልክያስ ማለት መልዐክ አንድም የተላከ ማለት ነው። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
12 279
5
በስምህ ታምኛለሁ በስምህ ታምኛለሁ እንዳትተወኝ ለሚያሳድደኝ ጠላት ለሞት አትስጠኝ ፀጥታዬ ነህ ጌታ ሰላም ዕረፍቴ ጉዞዬን አንተ አቅናልኝ ቅደም ከፊቴ አዝ በለስም ባታፈራ ዘይትም ባይኖር የህሊና ሰላም አለኝ ካንተ ጋር ስኖር በአባቶቼ በረከት የባረከኝ የእስራኤል ታዳጊያቸው ክበርልኝ ዘላለም ተመስገን ከፍ በልልኝ አዝ የፈተናዬ መውጫ መልሴ ነህ አንተ ጨለማውን አሻግረኝ እልፍኙን ከፍተህ ስታፅናናኝ ኖሬአለሁ ለብዙ ዘመን ተገፍቶ መች ይወድቃል በአንተ የሚታመን አይሞትም ይኖራል በአንተ የሚታመን አዝ ይቅርታና ምህረትህ እነሱ ይምሩኝ ወጥመድና እንቅፋቱ እንዳያደክሙኝ በጽድቅህ ሀሴት ላድርግ በአንተ ልበርታ መተከዝ ማልቀስ ይብቃኝ አፅናናኝ ጌታ ተነግሮ አያልቅም የአምላኬ ውለታ ዘማሪት ጽጌረዳ ጥላሁን 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
13 541
6
ነሐሴ ፳፱ /29/ በዚህች ዕለት በትሕትናው፣ በትዕግስቱ ይበልጡንም ደግሞ በመታዘዙ የሚታወቀው አባት ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር የፍልሰቱ ዕለት ናት። በአንድ ወቅት አባ ባይሞይ ቅዱስ ዮሐንስን ጠራውና ተፈ
ነሐሴ ፳፱ /29/ በዚህች ዕለት በትሕትናው፣ በትዕግስቱ ይበልጡንም ደግሞ በመታዘዙ የሚታወቀው አባት ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር የፍልሰቱ ዕለት ናት። በአንድ ወቅት አባ ባይሞይ ቅዱስ ዮሐንስን ጠራውና ተፈልጦ የወደቀ ደረቅ እንጨት ሠጠው ከዚያም "ትከለውና እንዲያፈራ አድርገው። ከዚያ አምጥተህ አብላኝ" አለው። ይህ ነገር ከተፈጥሮ ሥርዓት ውጪ መሆኑን እያወቀ ቅዱስ ዮሐንስ "እሺ" ብሎ ወስዶ ተከለው።  ከ10ኪ.ሜ በላይ እየተጓዘ ወሃ እየቀዳ ለ2 ዓመታት ሳይታክት አጠጣው። በሦስተኛው ዓመት ግን ለመለመ ወስዶም ለመምህሩ "አባቴ እንካ ብላ " ብሎ ሰጠው። መምህሩም ወዲያው ያን ፍሬ ታቅፎ ወስዶ ለገዳሙ መነኮሳት:- "ንሱ ብሉ: በረከትንም አግኙ:: ይህ የዛፍ ሳይሆን የመታዘዝ ፍሬ ነው አላቸው::" ቁመቱ እጅግ ያጠረ: ጽድቁ ግን ከሰማይ የደረሰ ቅዱስ ዮሐንስን ሰላም ሰላም እንለዋለን። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን: እኛንም በዚህ የጻድቅ ጸሎት ይማረን። በረከቱም ትድረሰን: ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚@ortodoxmezmur💚 💛@ortodoxmezmur💛 ❤️@ortodoxmezmur❤️
14 099
7
እንደምትወደኝአውቀዋለሁ እንደምትወደኝ አውቀዋለው እንደማትተወኝ ማረኝ ይቅር በለኝና ያንተ አድርገኝ/2/ አዝ ብሄድ ብርቅ ተለይቼ ንፁ ፍቅርን እረስቼ ጌታዬ ነህና አባቴ ራርተህ መልሰኝ ከቤቴ /2/ አዝ ምንም ብሆን በደለኛ ብበድልህም ዳግመኛ ጌታ ሞቴን አትፈልግም አንተ ፍቅር ነህ ዘላለም /2/ አዝ ከመንጋው ወጥቼ ብጣል በድካም በኃጢያት ብዝል የቀድሞ ትጋቴን ስጠኝ ፅናትና ብርታት ሁነኝ /2/ አዝ ቅዱስ ስጋህን ቆርሰህ ክቡር ደምህን አፍሰህ ሞተህ ህይወት የሰጠኸኝ አንተ ፈጥረህ የምትገዛኝ /2/ ሊቀ መዘምራን ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
15 496
8
ከዘመናት በፊት ከዘመናት በፊት አንተ ነበርክ ሁሉን አሳልፈህ ትኖራለህ እምቅደመ ዘመናት ዘመናዊ ድህረ ዘመን ሃዲስ ኢየሱስ ናዝራዊ/2/ አዝ ክብርህ ገናና ነው ባንተ ከብሬያለሁ ዘላለማዊ ነው ባንተ እኖራለሁ በሰልፉ መካከል አለህ ከእኔ ጋራ የሰራዊት ጌታ እፁብ የአንተ ስራ አዝ ከላይ ከአርያም ከዙፋንህ ግርማ ቅዱስ አለ ኪሩብ ምስጋናው ተሰማ ውዳሴ ከበበው መንበሩን እልልታ ባሪያህ ላመስግንህ ፍቀድልኝ ጌታ አዝ የአማልክት አምላክ የሚመስልህ የለም አይኔ ያየው ሁሉ ያላንተ አልሆነም አይኔ ያየው ገንዘብህ ነውና አልፋና ኦሜጋ ይድረስህ ምስጋና አዝ የምድር ኃያላን አይቆሙም ከፊትህ ይህን ሰራህ ብሎ የለም የሚወቅስህ ሰማይ እና ምድርን ፈጥረህ የምትገዛ እናመልክሃለን የህይወታችን ቤዛ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
17 666
9
ነሐሴ ፳፯ /27/ በዚችም ቀን በሊቀ ካህናት ኤሊ ዘመን ነቢይ ሳሙኤል ለመጠራቱ መታሰቢያ ሆነ። ይህንንም ነቢይ ተኝቶ ሳለ እግዚአብሔር ጠራው በኤሊም ፈንታ ነቢይና ካህን አድርጎ ለእስራኤል ልጆች ሾ
ነሐሴ ፳፯ /27/ በዚችም ቀን በሊቀ ካህናት ኤሊ ዘመን ነቢይ ሳሙኤል ለመጠራቱ መታሰቢያ ሆነ። ይህንንም ነቢይ ተኝቶ ሳለ እግዚአብሔር ጠራው በኤሊም ፈንታ ነቢይና ካህን አድርጎ ለእስራኤል ልጆች ሾመው በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። በዚችም ቀን የእስክንድራዊ ፊቅጦርና የእናቱ ሣራ መታሰቢያቸው ነው በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። በዚችም ቀን ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አራተኛ የሆነ የመላእክት አለቃ የሱርያል የበዓሉ መታሰቢያ ነው ። አማላጅነቱም ከኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን። በዚችም ቀን ዳግመኛ አባቶቻችን ዐሥራ ሁለቱን የያዕቆብን ልጆች ያስቧቸዋል ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በረከታቸውም ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
17 780
10
☦️የሮሜ መልእክት የመጨረሻው ማብራሪያ ይሰጣል ☦️ ✔️መ/ር ነቢዩ ኤልያስ Telgram ፦ https://t.me/Terha_Tsion Youtube፦ https://youtube.com/@tserhatsion?
☦️የሮሜ መልእክት የመጨረሻው ማብራሪያ ይሰጣል ☦️ ✔️መ/ር ነቢዩ ኤልያስ Telgram ፦ https://t.me/Terha_Tsion Youtube፦ https://youtube.com/@tserhatsion?si=qh_eLZt0L3sAkacr
14 482
11
ደጅሽ ላይ ቆሜ ደጅሽ ላይ ቆሜ ስለምንሽ ባርኪኝ እናቴ ማርያም ስልሽ ተደላደለልኝ ህይወቴ በአንቺ በእናቴ በእመቤቴ አዝ እንቺ በመሆንሽ የሕይወቴ ፋና አልፈራም ጨለማ ብርሃን አለኝና አይጠፋም ዘላለም ፍቅርሽ ከአንደበቴ አለ በደሜ ውስጥ ፍቅርሽ በሕይወቴ አልቀርም ደጅሽ ለዘላለም /2/ ከአንቺ የሚለየኝ ማንም የለም /2/ አዝ እጅግ የተገፋ ደካማ ሰው አለ መቅደስሽ የቆመ አማልጂኝ እያለ ይቁም ይሄ ልጅሽ ሃዘን የሰበረው ከአንቺ በቀር ወገን መጠጊያ የሌለው ያነሳው ኪዳንሽ ከውድቀቱ/2/ ያርግ በእጆሽ ያ ፀሎቱ/2/ አዝ ፅልመት የለበሰ ፈታኝ ያደከመኝ የምቋቋምበት ጉልበት አስፈለገኝ በርትቼ እንድጸና ሳትጎዳ ነፍሴ ሁኚኝ እናቴ ሆይ ግርማዬ ሞገሴ ልፅና ደግፊኝ እመቤቴ/2/ ይውለቅ ከእጄ ላይ ሰንሰለቴ/2/ አዝ አበው የለበሱሽ የክብራቸው ካባ መአዛሽ የሚስብ የሮማን አበባ ለውጪው በምልጃሽ የሕይወቴን ቃና ባዶ ጋኔን ምልጃሽ ወይን ያስሞላውና አፅጂልኝ በእጅሽ ማድጋዬን/2/ በወይን አስሞይው እንስራዬን/2/ ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
21 077
12
ነሐሴ ፳፮ /26/ በዚችም ቀን ለአብርሃም ሚስት ለተመሰገነች ሣራ መታሰቢያዋን እናደርግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አባቶች አዘዙ። ይቺንም ክብርተ ማሕፀን የሆነች ጡቶቿም የተባረኩ ክብርት ሣራ
ነሐሴ ፳፮ /26/ በዚችም ቀን ለአብርሃም ሚስት ለተመሰገነች ሣራ መታሰቢያዋን እናደርግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አባቶች አዘዙ። ይቺንም ክብርተ ማሕፀን የሆነች ጡቶቿም የተባረኩ ክብርት ሣራን የጌራራ ንጉሥ አቤሜሌክ ባል እንዳላት ሳያውቅ በወሰዳት ጊዜ እንዳይቀርባት እግዚአብሔር ገሠጸው በደዌም ቀሠፈው ባሏ አብርሃምም በጸለየለት ጊዜ ከደዌው ተፈወሰ ከዚህም በኋላ ከብዙ ገንዘብ ጋራ ወደ ባሏ መለሳት። ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር በሦስትነቱ ተገልጦ ወደ ቤቷ እንግድነት በመጣ ጊዜ ለአብርሃምም የይስሐቅን መወለድ በነገረው ጊዜ ሣራም በድንኳኑ ውስጥ ሳቀች እንዲህ ስትል እስከ ዛሬ ገና ነኝን ጌታዬም አርጅቷል። እግዚአብሔርም አብርሃምን እንዲህ አለው ሣራን ለብቻዋ ምን አሳቃት እስከ ዛሬ ገና ነኝን ጌታዬም አርጅቷል እኔም አሁን አርጅቻለሁ ብላ በውኑ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር አለን። ከዚህም በኋላ ሣራ ፀንሳ እግዚአብሔር ባለው ወራት በርጅናዋ ለአብርሃም ወንድ ልጅን ወለደች። ከዚህም በኋላ በበጎ እርጅና በአረፈች ጊዜ ከኬጢያዊ ኤሞርልጆች በገዛው ቦታ ቀበራት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበረች እናታችን ሣራ በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
20 835
13
በብዙ አገራት እንዳይታተሙ ታግደው የነበሩ፣ አነጋጋሪና አደገኛ ምስጢራትን የያዙ ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፎች በPdf የሚገኙበትን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ! 👇👇 @Bemnet_Library 📚 @B
በብዙ አገራት እንዳይታተሙ ታግደው የነበሩ፣ አነጋጋሪና አደገኛ ምስጢራትን የያዙ ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፎች በPdf የሚገኙበትን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ! 👇👇 @Bemnet_Library 📚 @Bemnet_Library 📚
10 668
14
​​ያየኽብኝን ያላሳየኽብኝ ያየኽብኝን ያላሳየኽብኝ ደግሞም በደሌን የረሳኽልኝ አስገረመኝ ለእኔ ያለህ አስደመመኝ ለእኔ ያለህ ብበድልህ /4/ እየቻለኝ ያ ትከሻህ አዝ እጄን በአፌ እያስጫነ አስገረመኝ ደጉ ልብህ ፊትህ አይጠቁር በኃጢአቴ እንዳላየህ ታልፈዋለህ ሳታሳጣኝ በሰው መሐል የእኔ ከዳኝ የልቤ ጥግ አላነስኩም ካየኽልኝ ከከፍታህ ከዚያ ማዕረግ አዝ በእርሱ ምሕረት ከድቅድቁ ከወጣሁኝ ከጨለማ ለይሁዳ ክፉ ወሬ ልቤ አይሰጋ ለዓለም ዜማ በነበልባል ሲያቃጥለኝ የስምዖን አንደበቱ የእሳት ልሳን ሆነኽልኝ በአንተ አለፈ ያ ክረምቱ አዝ ከበለስ ሥር የሠራሁት ዓለም ተፍቶ ያቃለለው ረሳሁት ትቼዋለሁ እንዳንተ ያለኝ ከቶ ማነው ሰው ሲሸሸኝ የቀረብከኝ አንተ እኮ ነህ መድኃኒቴ ዐይንህ ዐይቶኝ መች አለፍከኝ አነሳኸኝ ቸር አባቴ አዝ መክሮ መክሮ ሲታክተው ውጣ ብሎ እየጣለ ስንቱ አለፈ በመከራ ሰው ወገኑን ስላልቻለ የኔ ጌታ ፍቅሩ ችሎኝ ሰፊው ክንዱ አሻገረኝ ለውለታው ከእንባ በላይ የሚያረካው ምን ቃል አለኝ ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
21 640
15
ዛሬ [ ሰኞ ] ምሽት 2:00 እንገናኝ 12ኛው ዙር Graphics Design ሥልጠና ላይ Day 1 + 2 + 3 ኮርስ በነጻ እንድትከታተሉ ተጋብዛችኋል 🎉 ቀድማቹ ማወቅ ያለባችሁን እና ከየት ወደየ
ዛሬ [ ሰኞ ] ምሽት 2:00 እንገናኝ 12ኛው ዙር Graphics Design ሥልጠና ላይ Day 1 + 2 + 3 ኮርስ በነጻ እንድትከታተሉ ተጋብዛችኋል 🎉 ቀድማቹ ማወቅ ያለባችሁን እና ከየት ወደየት መሄድ እንደምትችሉ ጥንቅቅ አድርገን እናሳያችኋለን ። @greenbirdtechnology ላይ ~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~ « I want to attend Day 1+2+3 of Graphics Design Course » ~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~ ብላቹ ለምትልኩልን link እንሰጣችኋለን ___________________________ @greenbirdtechs @greenbirdtechs የለውጥዎ ክንፍ 🔑 🐥
17 308
16
ነሐሴ ፳፭ /25/ በዚችም ቀን ቅዱሱ አባት አባ ቢጻርዮን አረፈ። የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ምእመናን ነበሩ። በአደገም ጊዜ የምንኵስና ልብስን ለብሶ እግዚአብሔርን ሊአገለግል ወደደ
ነሐሴ ፳፭ /25/ በዚችም ቀን ቅዱሱ አባት አባ ቢጻርዮን አረፈ። የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ምእመናን ነበሩ። በአደገም ጊዜ የምንኵስና ልብስን ለብሶ እግዚአብሔርን ሊአገለግል ወደደ ዓለምንም ንቆ ወደ ኣባ እንጦንስ ሔደ ለእርሱም ደቀ መዝሙር ሆኖ ብዙ ዘመናት አገለገለው። ከዚህም በኃላ ወደ አባ መቃርስ ሒዶ ቅዱሳን አረጋውያን መነኰሳትንም አገለገላቸው። በአስቄጥስም ገዳም ይዘዋወር ነበር በቤት ውስጥም አያድርም ነበር ። አባቶችም ጭንቅ የነበረ ተጋድሎውን ስለርሱ ይናገሩ ነበር። እርሱ አርባ መዓልትና አርባ ሌሊት ከቶ ሳይተኛ ቁሞ ኖሮአልና። በምንኩስናውም ወራት ብዙ ጊዜ በየአርባ ቀን ጾመ እነሆ እንዲህ እየተጋደለ ድንቆችንም እያደረገ ኀምሳ ሰባት ዓመታት ኖረ። ቅዱሳን አባ ዱላስና አባ ዮሐንስም ከተአምራቱ ተናገሩ እነርሱ ከርሱ ጋር ወደ ኤርትራ ባሕር ዳርቻ ሔዱ። እጅግም በተጠሙ ጊዜ እንደተጠሙ አውቆ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ መራራውንም ውኃ ጣፋጭአድርጎላቸው ጠጥተዋል። የዚህም ቅዱስ ተአምራቶቹ ከነገርናችሁ የበዙ ናቸው እግዚአብሔርንም አገልገሎ በሰላም አረፈ ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ጻድቅ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
18 872
17
በነጻ 🤗 ነገ ሰኞ ምሽት 2:00 በሚጀመረው 12ኛው ዙር Graphics Design ሥልጠና ላይ Day 1 + 2 + 3 ኮርስ በነጻ እንድትከታተሉ ተጋብዛችኋል 🎉 ቀድማቹ ማወቅ ያለባችሁን እና ከየት
በነጻ 🤗 ነገ ሰኞ ምሽት 2:00 በሚጀመረው 12ኛው ዙር Graphics Design ሥልጠና ላይ Day 1 + 2 + 3 ኮርስ በነጻ እንድትከታተሉ ተጋብዛችኋል 🎉 ቀድማቹ ማወቅ ያለባችሁን እና ከየት ወደየት መሄድ እንደምትችሉ ጥንቅቅ አድርገን እናሳያችኋለን ። @greenbirdtechnology ላይ ~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~ « I want to attend Day 1+2+3 of Graphics Design Course » ~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~ ብላቹ ለምትልኩልን link እንሰጣችኋለን ___________________________ @greenbirdtechs @greenbirdtechs የለውጥዎ ክንፍ 🔑 🐥
6 783
18
ቁጥርህ ከመላእክት ቁጥርህ ከመላእክት ተስተካክሏል ከኪሩቤል መሐል ገብተህ አጥነሃል ተክለሃይማኖት በጸሎትህ  ብዙ ድውያን ፈውሰሃል አዝ ባሕር ሳያሰጥመን ደርሶልን  አለፍን በደረቅ ከፍሎልን  ኢትዮጵያዊው ሙሴ ተክለሃይማኖት  የሚሳነው የለም በሃይማኖት አዝ ጸሎቱ ምህላው ቅዳሴው  ገብቷል ከቤታችን መዓዛው ጸጋ በረከትህ በዝቶልናል በአማላጅነትህ ተምረናል አዝ ድካም በሌለበት በምስጋና አምላኩን ያከብራል በትህትና ስለ እኛም ዝም አይልም ይማጸናል የአባታችን አምላክ ይሰማናል አዝ ዘመናችን ሲረክስ መንገዳችን  ፈጥኖ ደረሰልን አባታችን  ተክለሃይማኖት እርዳን ልጆችህን  አታርቀው ከእኛ ኪዳንህን ዘማሪት ጸዳለ ጎበዜ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
20 916
19
​​እንኳን ለታላቁ ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ልደት መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ ጸጋ ዘአብ ካህኑና እግዚእ ኃረያ ናቸው። እርሱ በክህነቱ እርሷ በደግነቷ በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል። በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ ቢደርስባቸው ቅዱስ ሚካኤል ጸጋ ዘአብን ከሞት እግዚእ ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል። በሁዋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል። ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የጸነሱት መጋቢት 24 ቀን በ1206 ዓ/ም ሲሆን የተወለዱት ደግሞ ታሕሳስ 24 ቀን በ1207 ዓ/ም ነው። በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል። ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል። ዕድገት የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው "ፍሥሃ ጽዮን" ይሰኛል። ይሕንን ስም ይዘው አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው አድገዋል። በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን (ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል። በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል። ዲቁናም ከወቅቱ ዻዻስ አባ ጌርሎስ ተቀብለዋል። መጠራት አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮስ ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ። የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ። "ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን። ከዚህ በሁዋላ አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ። ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ በግርማ ዐረገ። ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በሁዋላ ሰዓትን አላጠፉም። ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ። አገልግሎት ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል አገልግሎትን ጀመሩ። በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ። ያን ጊዜ ኢትዮዽያ 2 መልክ ነበራት። 1ኛ. ዮዲት (ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል ወይም በባዕድ አምልኮ ተጠምዷል። 2ኛው. ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር። ግማሹ ሃገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ። ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን (ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል:: ገዳማዊ ሕይወት ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል። እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል። እነዚህም በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት: በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ ዳሞ ከአቡነ ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26 ዓመታት አገልግለዋል። በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በሁዋላም ወደ ምድረ ሽዋ (ዞረሬ) ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል። በተሰበረ እግራቸውም 6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል። ስድስት ክንፍ ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት ተባርከዋል። ጻድቁ ምድረ እሥራኤል የገቡት በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር:: የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሚካኤል ጋርም ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል። ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ በሁዋላ ነው ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር። ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም። በገሃድ:- -በቤተ መቅደስ ብስራቱን -በቤተ ልሔም ልደቱን -በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን -በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን -በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር። የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደ ሆነው ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ። በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ እመቤታችን ድንግል ማርያም ፈጥና ደርሳ ተክልየን ወደ ሰማይ አሳረገቻቸው። በዚያም :- -የብርሃን ዐይን ተቀብለው -6 ክንፍ አብቅለው -የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው -ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው -ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው -ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው -"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል። ተአምራት የተክልየ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው። ሙት አንስተዋል ድውያንን ፈውሰዋል አጋንንትን አሳደዋል እሳትን ጨብጠዋል በክንፍ በረዋል ደመናን ዙፋን አድርገዋል። ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን መሥርተዋል። በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት አብረው ኑረዋል። በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና:: ዕረፍት ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: እልፍ አእላፍ ፍሬን አፍርተው: በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24 ቀን በ1306 ዓ/ም ዐርፈዋል። ጌታ: ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል። 10 ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል። 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
20 515
20
ነሐሴ ፳፬ /24/ በዚች ቀን የክርስቶስ ምስክሩና ሐዋርያው የሆነ የመርዓስ ኤጲስቆጶስ ተጋዳይ ቅዱስ አባት ቶማስ አረፈ። ይህም አባት የመርዓስ አገር ኤጲስቆጶስ ነበር። በከሀዲ ዲዮቅልጥያኖስም ዘመን
ነሐሴ ፳፬ /24/ በዚች ቀን የክርስቶስ ምስክሩና ሐዋርያው የሆነ የመርዓስ ኤጲስቆጶስ ተጋዳይ ቅዱስ አባት ቶማስ አረፈ። ይህም አባት የመርዓስ አገር ኤጲስቆጶስ ነበር። በከሀዲ ዲዮቅልጥያኖስም ዘመን ይህን አባት መኳንንት እየደበደቡት ወሰዱት። ከዚህም በኃላ መኮንኑ ቅዱስ ቶማስን ለአማልክት ስገድ አለው ቅዱሱም ለጣዖት እንደማይሰግድ ነገረው። በዚህም በብዙ አሰቃዩት። ከዚህም በኋላ በጨለማ ቦታ ጣሉት በዚያም ሃያ ሁለት ዓመት ኖረ። በዚያም አካላቱን ይቆርጡት ነበር። መንጋዎቹም ያረፈ መስሏቸው በየዓመቱ መታሰቢያውን ሲያደርጉ ኖሩ። ነገር ግን አንዲት ሴት አይታው ስለነበር በድብቅ ትመግበው ነበር። ጻድቅ ቁስጠንጢኖስም እስከ ነገሠና የቀናች የክርስቶስን ሃይማኖት ክብር እስከ ገለጠ ድረስ እንዲህ ሲሠቃይ ኖረ። ይቺም ሴትስለ ቅዱሱ ለካህናቱ ነገረቻቸው በውስጡ ወደሚኖርበትም ቦታ መራቻቸው። እነርሱም አንሥተው ተሸከሙት እየዘመሩና እያመሰገኑ ወደ ቤተ ክርስቲያን አደረሱት በቤተ መቅደሱም ፊት ለፊት በወንበሩ ላይ አስቀመጡት ምእመናንም ሁሉ ወደርሱ እየመጡ ከእርሱ ይባረኩና የተቆረጡ ሕዋሳቱን ይሳለሙ ነበር። ይህም ቅዱስ ከ318ቱ ሊቃውንት አንዱ ነው። ንጉሱም ስለ ቅዱሱ በሰማ ጊዜ ሰገደለት። ከዚህም በኃላ ቅዱስ ቶማስ ወደ መንበረ ሢመቱ ሔደ ካህናቱንና መንጋዎቹን ሁሉ ሰብስቦ አነበበላቸው እርሱንም እንዲአስተውሉት እንዲጠብቁትም በመጠበቅም እንዲጸኑ አዘዛቸው። ጥቂት ዘመናትም ከኖረ በኃላ በሰላም በፍቅር አረፈ የሹመቱም ዘመን አርባ ዓመት ነው በዚህም እግዚአብሔርን አገለገለው። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
18 200