ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። . #ዝማሬ_ዳዊት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት @zmaredawit_messengerbot ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል
Show more134 760Subscribers
+6224 hours
+1607 days
+93130 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
Show all...
❤ 19🕊 1
እውነት ስለሆነ
እውነት ስለሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ
ዋለ ባደባባይ ሲሰደብ ሲከሰስ
የሀሰት ዳኝነት አምላክን ወቀሰው
ህይወት ሰጠን እንጂ ጥፋቱ ምንድነው/2/
#አዝ
ከቃሉ እብለትን ባያገኙበትም
ዝምታውን አይተው አላዘኑለትም
ባላወቁት መጠን ጠሉት ካለበደል
ጥፋቱ ምን ይሆን የሚያደርስ ከመስቀል/2/
#አዝ
የልቡን ትህትና ፍቅሩን ሳያስተውሉ
ቸሩ ጌታችንን አቻኩለው ሰቀሉ
እሩህሩሁን ጌታ ቸንክረው ሰቀሉት
ሞትን አስውግዶ ቢሰጣቸው ህይወት/2/
#አዝ
ስለ ቸርነቱ ስድብን ከፈሉት
ስለ ርህራሄው የሾህ አክሊል ሰጡት
ሀሞትና ከርቤ ሆምጣጤ ደባልቀው
መራራ አስጎነጩት ጨክኖልባቸው/2/
#አዝ
ፈውስን ለሰጣቸው ልባቸውን ሞልተው
አሉት ወንበዴ ነው ስቀለው ስቀለው
ከጁ በረከትን የተሻሙ ሁሉ
ይጮሁ ነበረ ይገደል እያሉ/2/
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️
❤ 95🕊 10
#የሚጠብቀኝ_አይተኛም
የሚጠብቀኝ አይተኛም/2/
አያንቀላፋም
ቤት ባይኖረኝም እደጅ ባድርም
ቀን እና ለሊት ከኔ አይርቅም
ድምጸ አራዊት የለሊት ግርማ
ወደኔ አይቀርብም ድምጽህ ሲሰማ
አዝ
መሰናክልን ለእግሮቼ አይሰጥም
ይሰውረኛል በቀኙ ሰላም
ፀሐይም በቀን አይተኩሰኝም
የአጋንንትም ሀይል አያስፈራኝም
አዝ
ነፍሴን ጠበቃት ከጠላት ወጥመድ
ጌታዬ መራኝ በጽድቅ መንገድ
መውጣት መግባቴን እየጠበቀ
ለዚህ አበቃኝ እርሱ ባወቀ
አዝ
የሰማዩን ጠል እታገሳለው
ሰው ከጨከነ ምን እሆናለው
ለሊት በድብቅ ለሚጎበኙኝ
ለጻድቃኑ ክብር አምላክ ይስጥልኝ
አዝ
እንቅልፌን ባርኮ ለሰጠኝ የጌታ
በአለም ሀሳብ ሳልንገላታ
የእለት ምግቤንም ላልነሳኝ ፍጹም
ምስጋና ላቅርብ እስከ ዘለዓለም
መዝሙር
ሊቀ-መዘምራን ይልማ ኃይሉ
"እነሆ፥ እስራኤልን የሚጠብቅ
አይተኛም አያንቀላፋምም።"
👉 መዝሙረ ዳዊት 121:4
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️
❤ 60🥰 8🕊 3🔥 2🤬 2
በይስሐቅ ፈንታ
የበገና መዝሙር
በይስሐቅ ፈንታ ኢየሱስ ታረደ/2/
ደሙን ከፈለና አዳምን ታደገ/2/
ተጨነቀ ጌታ ተሰቃየ ጌታ
የኔ መድኃኔዓለም የአዳም ልጅ አለኝታ
እንደሚታረድ በግ ተነዳ ወደ ሞት
ንፁህ ኢየሱስ በደል የሌለበት
በማመን ሲሸከም የአዳምን መከራ
ስቃይ ተቀበለ ደሙ እየተዘራ
ለሚገርፋት ሁሉ ምህረትን ሲቸር
እርሱ ግን ሲገረፍ ብዙ ተቸገረ
የሰማነውን ድምፅ ማን ሰው እኮ አምኗል
የእግዚአብሔርስ ክንድ ለነማን ተገልጿል
ባየነው ጊዜ ህመም ተሸክሞ
ስለበደላችን ተገርፎና ታሞ
እጁ የታሰረው ይስሀቅ ተፈቶ
ኢየሱስ ቀረበ በሰው ልጆች ፈንታ
ንፁህ በግ ቀረበ በደል የሌለበት በደለኛ ሆኖ
ሊሰቀል ሊገደል መስቀሉን ተጭኖ
በእውነት ደዌያችንን እርሱ ተሰቀለ
በሰው ልጆች ፈንታ በእንጨት ተሰቀለ
እኛ ግን ከሰስነው እንደ ወንጀለኛ
ስለ እኛ ቢሰቀል ሰማያዊው ዳኛ
ለሰው ልጆች ህይወት የታሰበውን ሰይፍ
አይተናል ሰምተናል በኢየሱስ አንገት ሲያልፍ
የመስቀሉ ስዕል ኧረ እንዴት ይገርማል
እዩት ንፁህ በግ በአርምሞይነዳል
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️
❤ 25🥰 25🕊 4🤬 2
ይህን ያውቁ ኖሯል?
በ2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ ምድር መስቀል አደባባይን መጠቀም ያልቻለችው የኛይቱ ውቧ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብቻ
🤬 111❤ 18🔥 12
#መከራው_ክርስትናዬን_አጣፈጠው ✞
መከራው ክርስትናዬን አጣፈጠው
ስደቱ ማህተቤን አጠበቀው
በሞት መንደር በሀዘን ውስጥ በመከራ
አየውት እግዚአብሔርን ከኔ ጋራ
ክርስትያን ተብለን በክርስቶስ ስም የተጠራነው
በጥልቁ ውስጥም በእግዚአብሔር እንድናምን ነው
ለጥቂት ግዜ ቢበረታብን ስደት ሀዘኑ
አምላክ ግን መውጫ ያዘጋጃል በዚህ ተፅናኑ
#አዝ
በስደት ሳለን ካፋችን ቢደርቅ የፅዮን ዜማ
ከወንዙ አጠገብ ቁጭ ብለን ሰለን ድምፁን ሳንሰማ
በእግዚአብሔር ጊዜ ከባቢሎን ምድር እንለቃለን
መሰንቆአችንን ከአርያም ዛፍ ላይ እናወርዳለን
#አዝ
ደካሞች ሲሉን በስሙ ያን ጊዜ እንበረታለን
ድሆች ስንባል ባለጠጎች እናደርጋለን
በምድር ቅዱስ ህዝብ አድርጎ ለእርሱ ለየን
ጨለማው አልፎ በቸርነቱ ብርሀን አሳየን
#አዝ
ከፀጋ በላይ እንዳንፈተን ይከልለናል
በቁስላችን ላይ የፈውስን ዘይት ያፈስልናል
በጊዜም ቢሆን ያለ ጊዜውም በእርሱ እንፅና
እንኳን ስደቱን ሞቱን ሊገታው ይችላልና
ሊቀ-መዘምራን
ዲያቆን ቴድሮስ ዮሴፍ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️
❤ 26🥰 5
#ክፋትን_ጥሉ
እግዚአብሔርን የምትወዱ
አምላኬ ነው የምትሉ
ክፋትን ጥሉ
....አዝ...
የታተማችሁ በቅዱስ ደሙ
የተጠራችሁ በሕያው ስሙ
ከፀብ እራቁ ሽሹ ከክፋት
ፍቅንር ልበሱ ቁሙ በእውነት
.... አዝ....
በቀልን ገንዘብ የምታደርጉ
ከወንድማችሁ የምትዋጉ
የጠራን በዚህ ስለማይከብር
እያመለክነው አንከራከር
.... አዝ.....
መገፋት እንጂ የኛ ግብራችን
እንደተማርነው ለአምላካችን
አትታወቁ ሰውን በመክሰስ
በእግረ ስጋ በመመላለስ
..... አዝ....
ማህተብ ያሰረ ከአንገቱ ላይ
የፍቅር ሰው ነው በምድሪቱ ላይ
መስቀልን እንጂ ሾተል አይዝም
የሚያጣፍጥ ነው አልጫን አለም
ዘማሪ ሊቀ መዘምራን
ቴዎድሮስ ዮሴፍ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️
❤ 32🔥 2😍 2🕊 1
Sign in and get access to detailed information
We will reveal these treasures to you after authorization. We promise, it's fast!