ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን። YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8 Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR
إظهار المزيد📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit
تُعد قناة ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit (@ortodoxmezmur) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 168 002 مشتركاً، محتلاً المرتبة 143 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 140 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 168 002 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 26 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 525، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 89، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 12.61%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 6.16% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 21 185 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 10 347 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 132.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ።
ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን።
YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8
Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 27 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
جاري تحميل البيانات...
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 27 يوليو | +10 | |||
| 26 يوليو | +89 | |||
| 25 يوليو | +53 | |||
| 24 يوليو | +45 | |||
| 23 يوليو | +46 | |||
| 22 يوليو | +38 | |||
| 21 يوليو | +47 | |||
| 20 يوليو | +28 | |||
| 19 يوليو | +37 | |||
| 18 يوليو | +22 | |||
| 17 يوليو | +10 | |||
| 16 يوليو | +11 | |||
| 15 يوليو | 0 | |||
| 14 يوليو | +23 | |||
| 13 يوليو | +13 | |||
| 12 يوليو | +45 | |||
| 11 يوليو | +33 | |||
| 10 يوليو | +3 | |||
| 09 يوليو | +10 | |||
| 08 يوليو | +47 | |||
| 07 يوليو | +22 | |||
| 06 يوليو | +42 | |||
| 05 يوليو | +44 | |||
| 04 يوليو | +26 | |||
| 03 يوليو | +49 | |||
| 02 يوليو | +52 | |||
| 01 يوليو | +43 |
አዝጸጋ በዝቶልኝ እዘምርልሃለው በምስጋና ላይ ምስጋና አብዛለው አለኝ ሺህ ቃላት አለኝ ብዙ ቋንቋ አንተን መግለጫ ለዓለም የሚበቃ
አዝየተናገርከው ያሰብክልኝ ሆነ የልቤ መሻት ይህንን ነበረ አስተካከልከኝ ከሃያላን ጋራ አማኑኤል ሆይ እፁብ ያንተ ሥራ
አዝበለምለሙ መስክ ኣሳድረኸኛል ያ የጭንቁ ቀን አሳልፈኸኛል የምስጋና እርሻ ሆነልኝ ደጅአፌ አባት ሆይ ስለው ማር ማር አለው አፌ
አዝባዝን ብደሰት ብወድቅ ብነሳ እስከ እሁን አለው በአንተ የተነሳ መርከቤን ጥዬ ተስፋ አደርገሃለሁ እንደምትሞላው እተማመናለሁ ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
| 2 | ሐምሌ ፳ /20/
በዚህች ቀን ለስም አጠራሯ ክብር ይሁንና እመ ብርሃን ድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ ገብታለች። በዓሉ ከሰላሳ ሦስቱ የእመቤታችን በዓላት እንደ አንዱ አይቆጠርም። ምክንያቱም ቅዱሳን ሊቃውንት በዓታ ከበዓታ ጋር ይስማማል ብለው የታኅሣሥ ሦስትን በዓል ከሰላሳ ሦስቱ ደምረውታል።
እመቤታችን ወደ ቤተ መቅደስ የገባችው ሁለት ጊዜ ሲሆን አንደኛው ዛሬ የምናከብረውና በተወለደች በሰማንያ ቀኗ የገባችበት ነው። (ከግንቦት 1 ጀምረን እናስላው 80 ቀን ይመጣል::) ኦሪት እንዳዘዘው ቅዱሳን ኢያቄምና ሐና ንጽሕት ሕፃን ድንግል ማርያምን ታቅፈው የርግብ ልጆች (ግልገሎች) ዋኖስም ይዘው ወደ ቤተ መቅደስ ሒደዋል። ካህናቱ ዘካርያስና ስምዖን ወጥተው በደስታ ተቀብለዋቸዋል። እመቤታችን ለወላጆቿ ማኅጸን የከፈተች በኩር ናትና በእግዚአብሔር ፊት አቅርበዋታል::
ሁለተኛው ከሦስት ዓመታት በኋላ እንደ ስዕለታቸው ወደ ቤተ መቅደስ ወስደው ለእግዚአብሔር ሰጥተዋት ተመልሰዋል።
እግዚአብሔር ዛሬ ያልቃል: ነገ ይደቃል የማይባለውን የድንግል እናቱን ፍቅር አብዝቶ ያድለን። በረከቷም በእኛ ላይ ጸንቶ ይኑር።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 6 747 |
| 3 | አበርታኝ ገብርኤል
አንተ የልቤ ወዳጂ ከአንተ ጋር አለኝ ጉዳይ
አንተ የእኔ ድጋፍ ከአንተ ጋር አለኝ ጉዳይ
አበርታኝ ገብርኤል በምድር በሰማይ
ምስራች አሰማኝ ናልኝ ከአርያም ላይ
አዝ
ሀዋርያ ልደት ፅድቅን ምታሰማ
ከጥንት ጀምሮ የሆንክ የኔ ግርማ
ስወጣ አይሀለሁ ሆነህ ከፍታዬ
ክንፍህ ተዘርግቶ ለምህረት በላዬ
አዝ
ገብርኤል ፀሀይ ወጣ በማለዳ
ማእረግ ልትሆነኝ እኔን ልትረዳ
የእሳቱ ወላፈን ሀይሉ ቀዘቀዘ
ኩራት አለው ልቤ በአንተ እየታገዘ
አዝ
መልአከ አድኖ ተልከህ ከጌታ
የመከራዬ ክንድ ጉልበቱ ተመታ
ከእንግዲህ ሚያሰጋኝ ማነው በህይወቴ
እያለኝ ማምለጫ ገብርኤል አባቴ
አዝ
ማንም የማይፈታው የህይወት ቋጠሮ
ሰም ወርቅ የሆነብኝ የነፍስ እንጉርጉሮ
ብዙ የምነግርህ በውስጤ አለ እና
ነፍሴን ልታዳምጥ ገብርኤል ቶሎ ና
ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 5 978 |
| 4 | የመላእክት አለቃ
የመላእክት አለቃ ገብርኤልን ላከው
ኃያሉ እግዚአብሔር በሰማያት ያለው
የባህሪይ ልጄ ወዳንቺ ይመጣል
ብለህ ለጽዮን ልጅ ንገራት ለድንግል
አዝ
ኃይለ ልዑል ወልድም ሥጋሽን ይለብሳል
በተለየ አካሉ ወዳንቺ ይመጣል
ከሥጋሽም ሥጋን ከነፍስሽም ነፍስ
ነስቶ ይዋሃዳል በግዕዘ ሕፃናት ካንቺ ይወለዳል
አዝ
ደንቆሮ ሊሰማ ዲዶች ሊናገሩ
በጌታ ተአምራት እውራን ሊበሩ
ሙታን ይነሱ ዘንድ በማሕፀንሽ ፍሬ
ከእግዚአብሔር ወዳንቺ ተልኬአለው ዛሬ
አዝ
ደስ አሰኛት አለው በልዩ ሰላምታ
ሐሴት እንድታደርግ ምስራቹን ሰምታ
ድዳ እንዳደረከው ካህን ዘካርያስን
እንዳታሳዝናት ከእርሷጋር ስትደርስ
አዝ
ገብርኤል በደስታ ምስራቹን ይዞ
ከሰማይ ወረደ በአምላኩ ታዞ
በሊባኖስ መንደር እስኪሰማ ድረስ
ክንፉን እያማታ መጣ ሲገሰግስ
አዝ
ደስ ይበልሽ አላት እየተሳለማት
ሐርን ከወርቅ ጋር ስትፈትል አግኝቷት
እውነተኛው ንጉሥ ካንቺ ይወለዳል
ላንቺ ፍቅርና አንድነት ይገባል
ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 11 439 |
| 5 | ገብርኤል መልአከ ራማ
ገብርኤል
ገብርኤል መልአከ ራማ /2/
ስንጠራህ ፈጥነህ ድረስ ድምጽህን እንስማ
አዝ
ትንቢቱ ሲፈጸም ዘመኑ ሲያበቃ
ከቀናት ሳትዘግይ ሳይጎድል ደቂቃ
ወደ ድንግል መጥተህ ደስታን አበሰርክ
የአምላክን ሰውን መሆን ለአለሙ ሰበክ/2/
አዝ
ከውኃ እና ከእሳት ከሞት አመለጡ
በእሳቱ መካከል ለጥፋት ቢሰጡ
አንተ ባለህበት በየትኛውም ስፍራ
ምንም ቦታ የለው ሞትና መከራ/2/
አዝ
የመንገዴ መሪ ፈውስ ነህ ለህመሜ
ገብርኤል ስትመጣ በዛልኝ ሰላሜ
ደስታን አብሳሪ ተሸክመህ ዜና
ዛሬም ለሀገራችን ምስራች ይዘህ ና/2/
አዝ
አንጌቤናይቱ ቅድስት ኢየሉጣ
ስለአንተ ትመስክር እስከ ልጇ ትምጣ
እሳት ነህ ገብርኤል ነበልባል አስወጋጅ
የአምላክን መወለድ ለአለም ምታውጅ/2/
ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 12 927 |
| 6 | ሐምሌ ፲፱ /19/
በዚችም ቀን ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ በሰማዕትነት መከራ ተቀበሉ ። ይህም ሕፃን ዕድሜው ሦስት ዓመት ሲሆነው ከሮሜ አገር ወደሌላ ሀገር እናቱ ይዛው ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኰንን አገኘችው ።
ሰዎችም ነገር ሠሩባት ወደርሱ አስቀረባትና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኰንን ሆይዕድሜው ሦስት ዓመት የሆነው ሕፃን አለ እርሱን ጠይቅ አለችው ።
ሕፃኑም በተጠየቀ ጊዜ ስለ እግዚአብሔር አምላክነት እና ስለ ጣዖታቱ ከንቱነት ተናገረ። ወዳለበት ጭፍራውን ልኮ ወደርሱ አስመጣው ሕፃኑንም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ሕፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው። ሕፃኑም መልሶ አዎ ለእኔ ደስታ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ኀዘንና ልቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው መጽሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏልና አለው እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስከ አስደነገጣቸው ድረስ ንጉሡን መኳንንቱንና ጣዖታቱን ረገማቸው ከብርታቱም የተነሣ አደነቁ።
መኰንኑም በአፈረ ጊዜ በዚህም ሕፃኑን እና እናቱንን በብዙ አሰቃያቸው እግዚአብሔርም ያለምንም ጉዳት ያነሣቸው ነበር። ብዙዎች አሕዛብም ይህን አይተው በሰማዕትነት ሞቱ። በሕፃኑ ላይም የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት። ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው።
ከዚህም በኋላ በፈላውሀ ውስጥ በገቡ ጊዜም የውኃው ፍልሐት እንደ ንጋት ጊዜ ውርጭ ቀዘቀዘ ከእግዚአብሔር የታዘዘ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ የእሳቱን ኃይል አቀዝቅዞታልና።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 13 119 |
| 7 | 👆የቀጠለ
እኒኽም ቅዱሳን ይኽንን በሚነጋገሩበት ጊዜ በውስጡ አንገትን የሚቆለምም ልብንም የሚያቀልጥ ሆድን የሚሰነጥቅ ሥርን የሚበጣጥስ መሳሪያ ካለበት የብረት ጋን ውስጥ ጨመራቸው፡፡ ከዚህ በኋላ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወረደና የብረቱን ጋን እሳት አጠፋው፡፡ ከቅዱሳኑም አንዳቸውንም ሳያቃጥላቸው የብረቱ ጋር ማቃጠሉና መፍላቱ ጸጥ አለ፡፡
ወንድሞቻችን ሆይ እንግዲህ በጭንቃቸው ጊዜ ገድላቸውን እስኪፈጽሙ ድረስ ይህ መልአክ ከሰማእታትና ከጻድቃን ጐን እንደማይለይ እወቁ ለኃጥአንም ኃጢአታቸውን ይቅር ይላቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ይጸልይላቸዋል፡፡ እኛም የዚህ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል በዓሉን እያከበርን አማላጅና ወዳጅ እናድርገው። በዚህም በሚመጣውም ዓለም ሊረዳን ይችላልና፡፡
ዳግመኛም መስፍኑ ሐሳቡ ሳይሳካለት ስለቀረ 14 የሾሉና የጋሉ የብረት ችንካሮች አምጥተው ሰባቱን በእናቱ በኢየሉጣ አካል ሰባቱን በራሱ በቂርቆስ አካል ማለት ሁለቱን በጆሮዎቹ ሁለቱን በዐይኖቹ ሁለቱን በአፍንጫዎቹ አንዱን በልቡ ይቸነክራቸው ዘንድ ጭፍሮቹን አዘዘ፡፡ ዳግመኛም የህፃኑን የእራስ ቆዳ ገፈው እሳት ውስጥ ይጨምሩ ዘንድ አዘዘ፡፡
አሁንም መልአኩ መጥቶ ይህንን መከራ ከእርሱ አራቀለት፡፡ ቀጥሎም በመቃን ውስጥ ጨምረው በገመድ እንዲጎትቱት አዘዘ፡፡ በዚህም ጊዜ መልአኩ አዳነው፡፡ ሕዝቡም ይህንን ሁሉ ተአምር ባዩ ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገኑት ቅዱስ ገብርኤልንም አከበሩት፡፡ ቅዱስ ቂርቆስና ቅድስት እየሉጣ ብዙ መከራ ከተቀበሉ በኋላ ጥር 15 በሰይፍ ተመትተው ስማትነትን ተቀብለዋል።
የሊቀ መላእክት የቅዱስ ገብርኤል ፣ ቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ የቅድስት እየሉጣ ተራዳኢነት ጸሎት አይለየን። ከዚህ በኋላ ሕፃኑን አስፈልገው ቢጠይቁት ነቢዩ ዳዊት የተናገረው ኃይለ ቃል መንፈስ ቅዱስ ተገልጾለት፤ ‹‹የአሕዛብ ጣዖታት የወርቅና የብር የሰው እጅ ሥራዎች ናቸው፡፡ የሚታመኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ›› መዝ. ፻፴ በማለት ሲዘልፏቸው አገር ገዥው ሰምቶ ተቆጣና የብረት ጋን አስመጥቶ ውኃ ሞልቶ ከዕቶን እሳት ላይ ጥዶ ልዩ ልዩ ማገዶዎች በመጨመር ነበልባሉ ከመጠን በላይ ሆነ፡፡ የብረት ጋኑም ድምፅ እንደ ክረምት መብረቅና ነጎድጓድ እስኪያስፈራ ድረስ አስነድዶ ሕፃኑን ከነእናቱ ወስዳችሁ ጨምሩአቸው ብሎ አዘዘ፡፡
በዚህ ጊዜ ቅድስት ኢየሉጣ በጣም ፈራች፡፡ የእግዚአብሔር ሥራ እፁብ ድንቅ ግሩም ረቂቅ ነው፡፡ ገና አፉን ያልፈታ የሦስት ዓመት ሕፃን ‹‹እናቴ ሆይ! ገድላችን እንፈጽም ዘንድ ጨክኝ በርቺ›› አላት፡፡ ቅድስት ኢየሉጣም ‹‹ልጄ የነፍስ አባት ሁነኝ›› አለችው፡፡ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስም ከዘመናቸው ሳይደርስ፣ ታሪካቸውን ሳይማር የሠለስቱ ደቂቅን ታሪክ መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት ‹‹አናንያን፣ አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ ያድነናል›› ቢላት ፍርሃቱ ሊለቃት ባለመቻሉ፣ ወደ እግዚአብሔር እንዲህ ሲል ጸለየ፡፡
‹‹ጌታ ሆይ! የወይኑን ፍሬ ስትሻ ግንዱን ታጠፋለህን? እንደዚህስ ሁሉ እኔን አድነህ እናቴን ታጠፋታለህን?›› ብሎ በጸለየጊዜ መንፈስ ቅዱስ አደረባትና መንግሥተ ሰማያትን በዓይነ ሥጋ እንድታይ አደረጋት፡፡ ከዚህ በኋላ ፍርሃቱ ለቀቃትና ‹‹ልጄ ሆይ! ከዛሬ ጀምሮ መምህሬ፣ አባቴ፣ መካሪዬ እልሃለሁ እንጂ ልጄ አልልህም›› ብላ በጭካኔ ከልጅዋ ጋር ወደ ፈላው የብረት ጋን ገባችበት፡፡
በዚህ ጊዜ ሕፃኑ ቂርቆስ አናንያን፣ አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ ያድነናል ያለውን ቃል ለመፈጻም እግዚአብሔር አምላክ መልአኩ
ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው፡፡ መልአኩም በትእምርተ መስቀል እሳቱን ቢባርከው እንደ በረዶ ቀዝቅዞላቸዋል፡፡ በመልካቸውም እንደ ፀሐይ አበራ፡፡ ከእግር ጥፍራቸው እስከ ራስ ጠሩራቸው አንድም ሳይጎዳቸው በደህና ወጡ፡፡
በመጨረሻም ሕፃኑ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ እንዲህ አለ፡፡ ይህን ያህል ገድል ተጋድዬ ምን ዋጋ ትሰጠኛለህ ቢለው፣ ጌታ በልብህ ያለውን ሁሉ እሰጥሃለሁ አለው፡፡ ዳግመኛም ሥጋህ በምድር ላይ እንዳይፈርስ እንዳይበሰብስ በኤልያስ ሠረገላ ላይ አኖርሃለሁ አለው፡፡
ስለሆነም በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያናችን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለእናታችን ለቅድስት ኢየሉጣ እና ለሕፃኑ ለቅዱስ ቂርቆስ ያደረገውን ይህን ታላቅ ተአምር ድንቅ ሥራ በማሰብ ከዋዜማው ጀምራ እግዚአብሔርን ስታመሰግን ትውላለች ታድራለች፡፡
የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤል በረከት ተራዳኢነት ከሁላችን ጋር ይኑር አሜን፡፡
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 12 369 |
| 8 | ሐምሌ 19
ቅዱስ ገብርኤል
እንኳን ለታላቁ መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን!!!
በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት ሐምሌ 19 የቅዱስ ገብርኤል አመታዊ በዓል ነው፡፡ ይህ ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት እየሉጣንና ልጇን ቅዱስ ቂርቆስን ከሞት አደጋ እንደታደገበት የሚታሰብበት ዕለት ነው። የሐምሌ 19 ስንክሳርና የሐምሌ ወር ድርሳነ ገብርኤል እንዲህ ተርከውታል፡፡
በዘመነ ሰማእታት ከሐድያን ነገሥታትና መኳንንት በክርስቲያኖች ላይ መከራ አጽንተውባቸው ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት ብዙዎች ሰማእትነትን ሲቀበሉ የተቀሩት አገር ጥለው ተሰደዱ። እየሉጣም የሦስት ዓመት ህፃን የነበረውን ቅዱስ ቂርቆስን ይዛ ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኮንን አገኘችው ሰዎችም ነገር አሰሩባት ወደእርሱ አስቀረባት እና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኮንን ሆይ ዕድሜው ሦስት አመት የሆነው ህፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እሱን ጠይቅ አለችው፡፡
ህፃኑም ወዳለበት ጭፍራውን ልኮ ወደእርሱ አስመጣው ህፃኑም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ህፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው፡፡ ህፃኑም መልሶ አዎ ለኔ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ሐዘንና ለቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው፡፡ መጻሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏል እና አለው፡፡ እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስካስደነገጣቸው ድረስ ንጉሱን መኳንንቱንና ጣኦታቱን ረገማቸው፡፡ከብርታቱም የተነሳ አደነቁ፡፡
መኮንኑም በአፈረ ጊዜ በያይነቱ በሆነ ስቃይ ታላላቆች የማይችሉትን ታላቅና አስጨናቂ የሆነ ስቃይን አሰቃየው እናቱንም ከእርሱ ጋር አሰቃያት፡፡ እግዚአብሔርም ያለ ምንም ጉዳት ያነሳቸው ነበር፡፡ ብዙዎች አህዛብም ይኸንን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስም አምነው በሰማእትነት አረፉ፡፡ የሰማእትነትንም አክሊል ተቀበሉ፡፡ በህፃኑም ላይ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት፡፡ ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው፡፡
መስፍኑም በውስጡ ሰም፣ ጨው፣ ባሩድ፣ ሙጫ የዶሮ ማር፣ እርሳስ፣ ብረት፣ ቅንጭብ፣ ቁልቋል ጨምራችሁ ታላቅ የብረት ጋን አንጡልኝ ብሎ ጭፍሮቹን አዘዛቸው፡፡ ጭፍሮቹም እንዳዘዛቸው ካአደረጉ በኋላ ያዘዝከንን ሁሉ ፈጽመን እሳቱ ነዶ ፈልቷል፡፡ ድምፁ እንደነጐድጓድ ይጮኸል ወላፈኑም እንደጸሐይ ነጸብራቅ በሩቁ ይጋረፋል፡፡ የፍላቱም ኃይል በ14 ክንድ ያኽል ከፍታ ወደ ላይ ይዘላል፡፡ እንግዲህ በውስጡ የሚጣሉትን እዘዝ አሉት በዚህ ጊዜ ህፃን ቂርቆስና እናቱ እየሉጣ በክርስቶስ ስም ስለሚያምኑ አስረዋቸው ነበርና ከፍላቱ ሊጨምሯቸው ከእስር ቤት አወጧቸው፡፡
በዚያም ፍላቱ ወደላይ በሚዘል ብረት ጋን ውስጥ ለመጨመር ሲወስዷቸው የነዚህን ቅዱሳን አሟሟት ያዩ ዘንድ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች እንዲሰበሰቡ አዘዛቸው፡፡ በዚህን ጊዜ ቅድስት እየሉጣ የፍላቱን ጩኸት በሰማችና ባየች ጊዜ ተሸበረች፡፡ ተዘጋጅቶላት ከነበረው ክብር ልታፈገፍግ ሞከረች፡፡ ልጇ ቅዱስ ቂርቆስ ግን እናት ሆይ ከዚህ የብረት ጋን ግርማ የተነሳ አትፍሪ ድንጋጼም አይደርብሽ አናንያንና አዛርያን ሚሳኤልንም እግዚአብሔር ከእቶነ እሳት እንዳወጣቸው ሁሉ እኛንም ከዚህ ከብረት ጋን ሊያወጣን ችሎታ ያለው መሆኑን አትጠራጠሪ፡፡
እናት ሆ ከዚህ ከሚያልፈው ዓለም ጭንቅና መከራ ለመዳን ስትይ በማያልፈው ዘላለማዊ እሳት ለመቀጣት ትመርጫለሽን ይኽስ አይሆንም ይቅርብሽ፡፡ በአሁኑ ጊዜ እግዚአብሔር በመካከላችን አለና ይረዳናል፡፡ እናት ሆይ ሶስናን ከእደ ረበናት /መምህራነ አይሁድ/ ዳንኤልን ከአፈ አናብስት ያዳነ እርሱ እኛንም ከጋን ፍላት ያወጣናል፡፡ ይልቁንም እግዚአብሔር በዚህ የብረት ጋን ውስጥ ግዳጃችንን ልንፈጽም ፈቅዶ ከሆነ ኢዮብ ንብረቱንና ገንዘቡን ልጆቹንና ሚስቱን በመጨረሻም የተፈጥሮ አካሉን ባሳጣው ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ እግዚአብሐር ሰጠ እግዚአብሔር ነሳ እግዚአብሔርም እንደወደደ አደረገ ከማለት በስተቀር ምንም የተናገረው ነገር እንደሌለ ሁሉ እኛም የሱን ዓላማ በመከተል ይኽንን መከራ ልንታገስ ይገባናል፡፡
ነገር ግን እናቱ በዚህ ምክር ልትጽናና ባለመቻሏ ቅዱስ ቂርቆስ ዐይኑን ወደ ሰማይ አቅንቶ አቤቱ አምላክ ሆይ ይችን ባሪያህን ከርስትህ የምትለያት ከሆነ ከባለሟልነትህ መጽሐፍ ፋቀኝ፤ አቤቱ አዝመራውን አቃጥለ ፍሬውን ልትባርክ ትወዳለህን ይኽን እንዳታደር ግን ቸርነትህ ትከለክልኸለች አቤቱ እንጨቱን ቆርጣችሁ አንድዱት ቅጠሉን ግን ጠብቁት ብለኽ ልታዝ መለኮታዊ ባሕሪህ አይደለም፡፡ ነገር ግን እንጨቱንም ቅጠሉንም በአንድ ጠብቁት ብለኽ ታዝዛለኽ እንጂ፡፡ እንግዲህ በዚህ ምክንያት ይኽንን ያየ ሁሉ ማዳን የሚችል አምላክ ቢኖራቸውስ ኖሮ ከእሳት ባልሸሹም ነበር ብሎ አይጠራጠር፡፡
አቤቱ ዲያብሎስም ከባለስልጣኑ ይልቅ እኔ በረታሁ ቅዱሳኖቹንም ድል ነሳኋቸው ብሎ እንዳይመካ ከመንጋውም አንድ በግ ቀማው በማለት እንዳይደነፋ ለእናቴ ጽኑ የሆነ ኃይለ መንፈስ ቅዱስን ስጣት ብሎ በጸለየ ጊዜ ዲያብሎስ ከእየሉጣ አጠገብ ብን ብሎ ጠፋ፡፡ ከዚህ በኋላ ቅድስት እናቱ በሰማያዊ መንግሥት አባት የሆንከኝ ልጄ ሆይ ጌታኽ ኃይልን ሰጥቶኛልና የሚጠብቀንን ገድላችንን ፈጽመን ድል እናድርግ እነሆ በብረት ጋን ውስጥ የሚነደውን እሳት በማይበት ጊዜ በለምለም /በምንጭ/ ላይ እንደሚወርድ ጠል ሆኖ አይቸዋለሁና አለችው፡፡
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 12 975 |
| 9 | የፍቅር እናት
የፍቅር እናት የሰላም /2/
ይናፍቀኛል ስምሽ ሳልጠራው ስቀር ማርያም
አዝ
በሂወቴ ውስጥ በኑሮዬ
ቅደሚ ከፊት ከሀኅላዬ
ተደላደለ ልቤ
አንቺ አለሽና ካጠገቤ
አዝ
ምኞቴም ይስመር ትልቅ ህልሜ
ልለፍ ወደፊት ተቋቁሜ
የጌታዬ እናት ነሽ
ሀይልን ያረጋል ፀሎትሽ
አዝ
እንዴት ቀራለው ከመንገድ
አደራ እናቴ አስቢኝ
ከሚያስጨንቀኝ ጠላት
ለሚያሳድደኝ አትስጪኝ
አዝ
ትላንትም ዛሬም አመስጋኝ ነኝ
የለም ለነገየሚያስፈራኝ
ሜዳይሆናል ተራራ
ልጅሽ ስላለ ከኔ ጋራ
ሊቀ መዘምራን ቴድሮስ ዮሴፍ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 17 607 |
| 10 | ጥቆማ ስጡን‼️
የ 2018 ዓ.ም ጾመ ፍልሠታ ከመግባቱ በፊት ልክ በየአመቱ እንደምናደርገው ብዛት ላላቸው የገጠር ቤተ ክርስቲያኖች እየዞርን ጾሙ ሳይስተጓጎል ስርአተ ቅዳሴ እንዲቀደስ ማስቀደሻ ንዋየ ቅዱሳት ብዛት ላላቸው የገጠር ቤተ ክርስቲያኖች ድጋፍ እናደርጋለን ።
በአሁኑ የት አካባቢ እንምጣ ጠቁሙን እጥረት ያለባቸው ቦታ ካሉ ጠቁሙን ?
አዘጋጅ:- ማኅበረ ኤዶምያስ
ለመጠቆም በዚህ ያዋሩን
@Yetinieal_2725
@Yetinieal_2725 | 19 056 |
| 11 | አስምርልኝ መስዋዕቴን
አስምርልኝ መስዋዕቴን
ተቀበለኝ ምስጋናዬን
አምላከ አቤል እግዚአብሔር
ተቀበለኝ ምስጋናዬን
አዝ
ባይገባኝ ቅዱስ ስምህን መጥራት
እንደ ኃጢአቴ እንደ በደሌ ብዛት
ፍቀድልኝ ልሰዋ ምስጋናህን
ልመስክረው ፅድቅና ማዳንህን
በጥበቤ አይደለም በብቃቴ
ለምስጋና ስምህን መጥራቴ
አዝ
የምስጋናን ቅኔ ልሰጥ ሰጠኸኝ
የዜማ እቃ በአፌ አሰለጠንከኝ
እለት እለት ቸርነትህ ደንቆኛል
ለምስጋና ፍቅርህ ያበረታኛል
በጥበቤ አይደለም በብቃቴ
ለምስጋና ስምህን መጥራቴ
አዝ
ኮልታፋ ነው ያልበቃ አንደበቴ
ደካማ ነው ያልበረታ ጉልበቴ
ስለ ስምህ ዘወትር እቀናለሁ
ለዘላለም ጌታዬ እልሃለሁ
በጥበቤ አይደለም በብቃቴ
ለምስጋና ስምህን መጥራቴ
አዝ
ምስጉን ጌታ ስምህን ላመስግን
ስለምትወድ ንፁህ መስዋዕትን
በከበረ በያሬዳዊው ዜማ
ተቀበለው ምስጋናዬን በራማ
በጥበቤ አይደለም በብቃቴ
ለምስጋና ስምህን መጥራቴ
ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 21 384 |
| 12 | ሐምሌ ፲፮ /16/
በዚች ቀን ቅዱስ አባት ወንጌሉ ዘወርቅ የተባለ ዮሐንስ አረፈ ። ይህም ቅዱስ ከሮሜ አገርነበር አባቱም አጥራብዮስ የሚባል ባለጠጋ ነው ። የእናቱም ስም ብዱራ ይባላል ። እንዲማርም ለመምህር ሰጡት ቅዱሳት መጻሕፍትንም ተማረ ።
ከዚህም በኋላ አባቱ ገበታው የወርቅ የሆነ ወንጌልን አሰርቶ ሰጠው ከእርሱም አትለይም ነበር። በዚያም ወራት ወደ ኢየሩሳሌም የሚጓዝ መነኵሴ ወደ እነርሱ መጣ በእነርሱም ዘንድ አደረ ለቅዱስ ዮሐንስም ስለምንኩስና ነገር በዚህ ጊዜ ከእርሱ ጋር ወደ ገዳም ሔዶ መነኮሰ። በብዙ ተጋድሎም ተጋደለ።
በዚህ ተጋድሎም ሰባት ዓመት በሆነው ጊዜ ከእነርሱ በረከትን ትቀበል ዘንድ ከመሞትህ በፊት ወደ አባትህና እናትህ ሒድ የሚል ራእይ አየ ።
ወደ አባቱ ቤትም በደረሰ ጊዜ በትንሽ ጎጆ ውስጥ በአባቱ ደጅ በጾም በጸሎትና በስግደት እየተጋደለ ባሮች ከአባቱ ማዕድ የሚጥሉለትን ፍርፋሪ እየተመገበ ሰባት ዓመት ኖረ። ዕረፍቱም በቀረበ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ከሰባት ቀን በኋላ ከዚህ ዓለም ትወጣለህ ብሎ ነገረው። ከዚህም በኋላ እናቱን አስጠርቶ ማንነቱን ሳይነግራት የመሞቻው ቀን ስለደረሰ በለበሰው ጨርቅ እና በሚኖርበት መጠለያ እንዲቀብሩት አምሏት የወርቅ ወንጌሉን ሰጣት። ለባሏ ባሳየችውም ጊዜ የልጃቸው እንደሆነ አወቁ።
ቢጠይቁትም ነገራቸው። ሰባቱ ቀንም ሲፈጸም ቅዱስ ዮሐንስ አረፈ።
ከዚህም በኋላ በስሙ ያማረች ቤተ ክርስቲያን ሠርተው ሥጋውን በውስጧ አኖሩ ። ከእርሱም ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶች ተገለጡ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 19 726 |
| 13 | ሰላም ለኪ እያለ
ሰላም ለኪ እያለ /2/
ሐርና ወርቁን ስታስማማ
የገብርኤል ድምፅ ተሰማ
ተሰማ የመልአኩ ድምፅ ተሰማ
ተሰማ የገብርኤል ድምጽ ተሰማ
አዝ
ውሃ ስትቀጂ ክንፉን እያማታ
ሊያበስርሽ የመጣው በታላቅ ደስታ
ከሞገስሽ ብዛት /2/ ሲታጠቅ ሲፈታ
አቅርቦልሽ ነበር የክብር ሰላምታ
አዝ
የምሥራቹን ቃል ምስጢር ተሸክሞ
ገብርኤል ተላከ ሊያረጋጋት ደግሞ
እርጋታን ተሞልታ/2/ ነገሩን መርምራ
የመልአኩን ብሥራት ሰማችው በተራ
አዝ
ይደሰታል እንጂ መንፈሴ በአምላኬ
በምስጋና ሳድር ዘወትር ተንበርክኬ
ሃሳቤ ለቅፅበት/2/ሌላ መች ያስባል
ለእኔ ልጅን መውለድ እንዴት ይቻለኛል
አዝ
ከአንቺ የሚወለደው ልዑል ነው ክቡር
የተመሰገነ በሰማይ በምድር
ምስጢሩ ኃያል ነው /2/ ይረቃል ይሰፋል
ከአንቺ በቀር ይኼን ማን ይሸከመዋል
አዝ
እጹብ ነው ድንቅ ነው አንቺን የፈጠረ
አንቺን በመውደዱ ሰውን አከበረ
ዓለም ይባረካል /2/ በማሕፀንሽ ፍሬ
ክብርሽን አልዘልቅም ዘርዝሬ ዘርዝሬ
ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 22 545 |
| 14 | ሐምሌ ፲፬ /14/
በዚች ቀን የጌታ ክርስቶስ ጭፍራ ቅዱስ አብሮኮሮንዮስ በሰማዕትነት አረፈ። የዚህም ቅዱስ ትውልዱ ከኢየሩሳሌም ነው የአባቱ ስም ክርስቶፎሮስ ነው ትርጓሜውም ክርስቶሰን የለበሰ ማለት ነው ። ክርስቲያንም ነበረ የእናቱም ስም ቴዎዶስያ ነው እርሷ ግን ጣዖታትን ታመልክ ነበረች።
አባቱም በአረፈ ጊዜ እናቱ ወስዳ ለዲዮቅልጥያኖስ ሰጠችው እርሱም ክርስቲያኖችን እንዲያሳድድ አዘዘው። በመንገድም ሳለ ከሰማይም ክርስቲያኖችን ካሳደደ ክፉ አሟሟት እንደሚሞት ሰማ። ክርስቶስም እራሱን ገለጸለት። ከዚህ በኋላ በክርስቶስ አምኖ የወርቅ መስቀል አሰርቶ ወደ እስክንድርያ ተጓዘ። በመንገድም በመስቀሉ ድል አደረገበት።
በመጨረሻ ለዲዮቅልጥያኖስ ስለ እርሱ ነገሩት እርሱም በብዙ አሰቃየው እግዚአብሔር ከሁሉ አዳነው። በዚያ የነበሩ ሕዝቡም አይተው እጅግ አደነቁ እንዲህም እያሉ ጮኹ እኛ በግልጥ ክርስቲያን ነን በቅዱስ አብሮኮሮንዮስ አምላክ እናምናለን። ከእነርሱም ጋራ ሁለት መኳንንትና ዐሥራ ሁለት ሴቶች እናቱ ቴዎዶስያም ነበሩ መኰንኑም ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጧቸው አዘዘ። እነርሱም ቆረጡአቸው። በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ሐምሌ ስድስት ቀን ተቀበሉ።
ቅዱስ አብሮኮሮንዮስን ግን እንደገና ብዙ ከአሰቃዩት በኋላ መኰንኑ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጡት በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 22 618 |
| 15 | አዳነኝ ጌታ
አዳነኝ ጌታ አዳነኝ
ፈወሰኝ ጌታ ፈወሰኝ /2/
እግዚአብሔር አዳነኝ ኃጢአተኛውን ወደደኝ
አዝ
ያልፋል ያላልኩት አልፎልኝ አይቼ
በእንባ ታጠብኩኝ ከድቅድቅ ወጥቼ
እንግዲህ ላንተ ምስክር ሆኛለሁ
ሥራህን ለዓለም ሁሌም እነግራለሁ /2/
ክንድህ ብርቱ ነው ደካማን ለመርዳት
ታውቅበታለህ የዛለን ማበርታት
አይኔን ከሰዎች ማራቄ ጠቅሞኛል
ደጅህ ወድቄ መኖር ተሽሎኛል
አዝ
የሀዘኔን ማቅ አውልቀህ ጣልክልኝ
ሞቴን ስጠብቅ ዕድሜ ጨመርክልኝ
ከአልጋዬ ላይ አነሱኝ እጆችህ
ተፈውሻለሁ ዛሬ በምህረት /2/
ቃልህ ፅኑ ነው ዳግም ይጠግናል
ጎባጣ አቅንቶ ሽባውን ተርትሯል
ሕይወቴ ባንተ ዛሬ አዲስ ሆናለች
በክብር መዝገብ በእጅህ ተፅፋለች
አዝ
የሀሰትን ፍርድ ጌታ ቀለበስከው
ተጽናንቷል ባንተ ያ የተገፋ ሰው
የግፍን ጽዋ አራከው ከፊቱ
በእጁ ላይ የለም ዛሬ ሰንሰለቱ /2/
በሃማ መስቀል መርዶኪዮስ የለም
የናቡቴ ደም በከንቱ አልቀረም
የእውነት ዳኛ ጌታ ስትመጣ
የሀሰቱ ሰው ግፈኛው ተቀጣ
ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 25 442 |
| 16 | ሐምሌ ፲፫ /13/
በዚች ቀን ከግብጽ ደቡብ ከቡና አውራጃ ጡሕ ከሚባል አገር ቅዱስ አሞን ምስክር ሁኖ አረፈ። ለዚህም ቅዱስ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ተገለጸለት ከእርሱ የሚሆነውንም ሁሉ ነገረው።
ከዚህ በኋላ ወደ እንዴናው ከተማ ሒዶ አውግስጦስ በሚባል መኰንን ፊት ክብርይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ። መኰንኑም በመንኰራኵር ውስጥ በእሳት ላይ በመጣል በእሳት በአጋሉት በብረት ዐልጋ ላይ በማጋደም ከላም ቆዳ በተሠራ ጅራፍ በውሽባ ቤት ማንደጃ ውስጥ በመጨመር ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃዩት።
የራሱንም ቆዳ ገፈው በራሱ ላይ የእሳት ፍም አኖሩ እግዚአብሔርም ያጸናው ነበር ያለ ምንም ጉዳት ጤነኛ አድርጎ ያስነሣው ነበር ። ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና እግዚአብሔር ክርስቶስ በጐልማሳ አምሳል በብርሃን ሠረገላ ላይ ሁኖ ተገለጠለትና አጽናናው እንዲህም አለው ወዳጄ አሞን እኔ ከአንተ ጋራ እኖራለሁ ስምህን የሚጠራውን፣ መታሰቢያህን የሚደርግውን ሁሉ ወይም ገድልህን የሚጽፈውን ሁሉ እኔ በመንግሥቴ ውስጥ አስበዋለሁ ኃጢአቱንም እደመስሳለሁ ሀገርህንም እጠብቃለሁ ይህንንም ብሎ ሰላምታ ሰጥቶት ከእርሱ ዘንድ ዐረገ።
ይህም ቅዱስ በሥጋው ሳለ ታላላቅ ተአምራቶችንና ድንቆችን አደረገ ወዲያውኑም በሰይፍ ራሱን ቆረጡት የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበለ ። ቅዱስ ዮልዮስም በዚያ ነበረ ሥጋውን ወስዶ በመልካም ልብስ ገነዘው ከሁለት አገልጋዮቹም ጋራ ወደ አገሩ ላከው በላይኛው ግብጽም ታላላቅ የሆኑ ድንቆችንና ተአምራቶችን እያሳየ እስከ ዛሬ አለ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ጻድቅ ሰማዕት ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 23 260 |
| 17 | ይለይብኛል
ጠብቆ አሳድጎ ከልጅነቴ
አባት እየሆነኝ ሚካኤል አባቴ
ይለይብኛል ሚካኤል ይለይብኛል
በክንፉ ሸፍኖ በቤቱ አሳድጎኛል /2/
አዝ
አያምርብኝ ብዘነጋው ታሪኬን
ሚካኤል ነው ያስጌጠልኝ ህይወቴን
አልረሳብኝ እርሱ አትርሳብኝ ያልኩትን
ለካስ ሰምቶኝ ኖሯል የልጅነት ጸሎቴን
ሚካኤል ያን ሁሉ ዘመን የታገሰኝ
ሚካኤል ፍሬ ጠብቆ ያልቆረጠኝ
ሚካኤል የከፍታዬ መሰላል
ሚካኤል መነሻዬ ሆነሀል
አዝ
እንዳይከፋኝ አንዳልደፋ አንገቴን
እንዳላለቅስ እንዳላፈስ እንባዬን
እንዳይርቀኝ ደስታ በመንፈሴ እንዳልዝል
ካጠገቤ አይርቅም ያሳደገኝ ሚካኤል
ሚካኤል ቀኔም ቀን አይሆን ሳልጠራህ
ሚካኤል ና ድረስልኝ ሳልልህ
ሚካኤል እንዳስጀመርከኝ ጅማሬዬን
ሚካኤል አሳምረው ፍፃሜዬን
አዝ
ውድቅ አረገው የጠላቴ ክፉ እቅድ
አራመደኝ በከፍታዬ መንገድ
ሊያስቀረኝ አልቻለም ሊጎትተኝ ባላጋራ
ተጥሎ ስላለ በእግዚአብሔር ድንቅ ስራ
ሚካኤል እሳታዊ ነው ነበልባል
ሚካኤል ጠላቴ ፊትህ ይቀልጣል
ሚካኤል ለኔ ኃይሌ ነው መከታዬ
ሚካኤል የዘለዓለም ጠባቂዬ
ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 26 031 |
| 18 | ክረምቱን ለማንበብ የዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ መጽሐፎችን ጨምሮ ሌሎች ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፎች በPdf የሚገኙበትን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ!
👇👇
@Bemnet_Library 📚
@Bemnet_Library 📚 | 11 642 |
| 19 | ኃያል ነው እግዚአብሔር
ኃያል ነው እግዚአብሔር
ኃያል ነው ቅዱሱ /2/
አይቻለሁ በዓይኔ ሲቆም ማዕበሉ
አይቻለሁ በዓይኔ ሲታዘዝ ነፋሱ
አዝ
ሰረገላውን በእሳት ሠርቶታል
በደመና ላይ ይረማመዳል
በብርሃን ድንኳን በሰማይ ያለው
እርሱ ነው ጌታ የምናመልከው /2/
አዝ
እውነት በፊቱ ፍትሕ በእጁ
ሲኦልም ገነት አሉ በደጁ
ሥልጣን የእርሱ ነው አለቅነት
ማን እንደ ጌታ ከአማልክት /2/
አዝ
ታቦር ተራራ ተንቀጠቀጠ
ግርማው ሲገለጥ ሁሉ ቀለጠ
ድንቅን አድራጊ ተአምረኛ
ከማዳኑ ጋር ይምጣ ወደ እኛ /2/
አዝ
ምድር ጠፈሩ ታዟል ለእርሱ
እሳት ተፈትሎ ሆኗል ቀሚሱ
የክብርህ ብርሃን ይብራ በልቤ
አንተ ነህ ለእኔ ውድ ገንዘቤ /2/
ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 26 360 |
| 20 | ሐምሌ ፲፩ /11/
በዚች ቀን መርባስ የሚባል አገር ሰዎች የሆኑ ቅዱሳን ዮሐንስና የአባቱ ወንድም ልጅ ስምዖን በሰማዕትነት ሞቱ ። የዚህ ቅዱስ ዮሐንስ እናቱ መካን ነበረች አባቱም ልጅን ይሰጠው ዘንድ ክብር ይግባውና እግዚአብሔርን ይለምነው ነበር ከዚህም በኋላ ልጁን በሕይወቱ ዘመን ሁሉ ለእግዚአብሔር አገልጋይ ሊአደርገው ተሳለ ።
መጥምቁ ዮሐንስም እግዚአብሔር ልጅን እንደሚሰጠው በራእይ ተገልጦ ነገረው ። ይህን ቅዱስም በወለደው ጊዜ ዮሐንስ ብሎ ጠራው በመጥምቁ ዮሐንስም ስም ቤተ ክርስቲያን ሠራ ። ከዚህ በኋላ አድጎ ዐሥራ ሁለት ዓመት በሆነው ጊዜ አባቱ የበጎች እረኛ አደረገው ምሳውንም ለእረኞችና ለመንገደኞች ሁል ጊዜ ይሰጥ ነበር እርሱ ግን እስከ ምሽት ይጾም ነበር ።
አባቱም ይህን ነገር ሊአረጋግጥ ወደ ርሱ ሔደ አባቱንም በአየው ጊዜ ዮሐንስ ፈርቶ ሊሸሽ ወደደ ። አባቱም የዛሬ ምሳህን አሳየኝ አለው ቢመለከትም አገልግሉን ትኩስ እንጀራን ተመልቶ አገኘው እጅግም አደነቀ ከልጃቸው የሆነውንም ለሚስቱ ነገራት ።
ከዚህ በኋላ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እንዲማር አደረጉት እንጂ በጎችን የሚጠብቅ እረኛ እንዲሆን አልተዉትም። ከዚህም በኋላ አባቱ ሊአጋባው ወደደ ። እርሱ ግን ይህን አልወደደም ። ዐሥራ
ስምንት ዓመት በሆነውም ጊዜ ቅስና ተሾመ ከዚህም በኋላ ብዙ ተአምራትን አያደረገ። የአጎቱ ልጅ ስምዖንም ደቀ መዝሙሩ ነበር በመጨረሻም እግዚአብሔርን አገልግለው ከስምዖን ጋር ሰማዕት ሆኑ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 26 534 |
