ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን። YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8 Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR
Mostrar más📈 Análisis del canal de Telegram ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit
El canal ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit (@ortodoxmezmur) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 168 124 suscriptores, ocupando la posición 144 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 140 en la región Etiopía.
📊 Métricas de audiencia y dinámica
Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 168 124 suscriptores.
Según los últimos datos del 30 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 557, y en las últimas 24 horas de 47, conservando un alto alcance.
- Estado de verificación: No verificado
- Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 13.27%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 6.13% de reacciones respecto al total de suscriptores.
- Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 22 308 visualizaciones. En el primer día suele acumular 10 308 visualizaciones.
- Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 133.
📝 Descripción y política de contenido
El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ።
ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን።
YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8
Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR”
Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 31 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.
Carga de datos en curso...
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 31 julio | +45 | |||
| 30 julio | +47 | |||
| 29 julio | +37 | |||
| 28 julio | +39 | |||
| 27 julio | +18 | |||
| 26 julio | +89 | |||
| 25 julio | +53 | |||
| 24 julio | +45 | |||
| 23 julio | +46 | |||
| 22 julio | +38 | |||
| 21 julio | +47 | |||
| 20 julio | +28 | |||
| 19 julio | +37 | |||
| 18 julio | +22 | |||
| 17 julio | +10 | |||
| 16 julio | +11 | |||
| 15 julio | 0 | |||
| 14 julio | +23 | |||
| 13 julio | +13 | |||
| 12 julio | +45 | |||
| 11 julio | +33 | |||
| 10 julio | +3 | |||
| 09 julio | +10 | |||
| 08 julio | +47 | |||
| 07 julio | +22 | |||
| 06 julio | +42 | |||
| 05 julio | +44 | |||
| 04 julio | +26 | |||
| 03 julio | +49 | |||
| 02 julio | +52 | |||
| 01 julio | +43 |
| 2 | ሐምሌ ፳፬ /24/
በዚች ቀን ከደቡባዊ ግብጽ ከታችኛው ምድር አውራጃ ከንሒሳ ከተማ ቅዱስ አባ ኖብ ሰማዕት ሆኖ ሞተ ።
የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ ቅዱሳን ንጹሐንና የሚራሩ ነበሩ ። ይህንንም ቅዱስ ኖብን በወለዱት ጊዜ ዐሥራ ሁለት ዓመት እስኪሆነው ፈሪሀ እግዚአብሔርን እያስተማሩ አሳደጉት ።
አንድ ቀን ቄሱንም ምእመናንን እንዲህ እያለ ሲያስተምራቸውና ሲያበረታቸው “ጣዖታትን ከምታመልኩ ክብር ይግባውና ስለ መድኃኒታችን ስለ ክርስቶስ ነፍሳችሁን ለሞት አሳልፋችሁ ብትሰጡ ለእናንተ መልካም ነው” ሲላቸው ሰማው። ከዚህ በኋላ ያለውን ሁሉ ለድኆችና ለችግረኞች ሰጠ ።
ከዚህም በኋላ ወደ ሀገረ ገምኑዲ ሔደ በዚያም ላለው መኮንን ስለ ጌታችን አምላክነት መሰከረ። በዚህም ብዙ አሰቃየው የእግዚአብሔርመልአክተገልጦ አጽናናው።
ከዚህም በኋላ መኰንኑ ወደ ሰሜን አገር ሲጓዝ የከበረ ኖብን ከእርሱ ጋራ በመርከብ ወሰደው በመርከቡም ምሰሶ ላይ ዘቅዝቆ ሰቀለው የእግዚአብሔር መልአክም አዳነው። በዚህም ወታደሮቹ አምነው ሰማዕትነትን ተቀበሉ። መኮንኑ ግን በብዙ አሰቃየው አቅፋሐስ ከሚባል አገርም ዮልዮስ መጣ ከእርሱም እንደ ተረዳ ገድሉን ጻፈ ። መኰንኑም ማሠቃየቱን በሰለቸ ጊዜ አንገቱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ። እንዲሁም አደረጉበትና ሰማዕትነትን ተቀበለ። ጌታችንም ተገልጾ ብዙ ቃል ኪዳን ገባለት።
ሥጋውንም ቅዱስ ዮልዮሰ አንሥቶ ከሁለት አገልጋዮቹ ጋራ ንሒሳ ወደ ሚባል አገሩ ላከው።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 9 093 |
| 3 | አቤቱ ጉልበቴ ሆይ
አቤቱ ጉልበቴ ሆይ እወድሃለሁ /2/
አንተ ካሻገርከኝ ሁሉን አልፋለሁ /2/
አዝ
ክንድህን እንዳላየሁ ኃይልህን እንዳላየሁ
ሲመሽና ሲነጋ ዘወትር እጨነቃለሁ
አንተ ግን ለሰላሜ ለእረፍቴ ቆመሃል
ያዘነውን ልቤን ውስጤን አሳርፈሃል
አዝ
ሁልጊዜ ጠያቄ ነኝ መልስ የለኝም ጌታዬ
አንተ ግን መፍትሄ ነህ ስደክም ለብቻዬ
አይዞህ ስትል ስማውኝ ቃልህ ሲናገረኝ
ዘወትር አምላኬ ነህ የማትተወኝ
አዝ
የብርቱዎች አምላክ ነህ አውቃለሁ የእኔ ጌታ
ለደካማው አንተ ነህ ኃይሉን ምታበረታ
የተሸከመኝ ክንድህ ዝሎ አያውቅም ፍፅም
የማምለጫ አለት ነህ ለነፍሴ ዘላለም
አዝ
በፈረሰው ግድግዳ ሙሉ ሆነህ ቆመሃል
ባለቀስኩኝ ጊዜ ጉልበቴን አግኝተሃል
ልናገረው በሰው ፊት ሌላ ምን እከፍላለሁ
አይነ ስውር ነበርኩኝ ዛሬ ግን አይቻለሁ
ቀሲስ አሸናፊ ገ/ማርያም
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 11 856 |
| 4 | ሐምሌ ፳፫ /23/
በዚችም ቀን ከቀጰዶቅያ አገር ለንጊኖስ ሰማዕት ሆነ። ይህም ቅዱስ ከጲላጦስ ጭፍሮች ውስጥ ነበር ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ዓለም ደኅንነት መከራ እንዲቀበል የፈቀደበት ሰዓት በደረሰ ጊዜ በእርሱ ላይ የፈለጉትን ያደርጉ ዘንድ ለዐመፀኞች ፈቅዶላቸው ነበር። ይህም ለንጊኖስ ጌታን ይሰቅሉት ዘንድ ጲላጦስ ከአዘዛቸው ወታደሮች ውስጥ ነበር።
በመስቀል ላይ ከሞተ በኋላ ጌታችንን የቀኝ ጐኑን ወጋው ከጐኑም ደምና ውኃ ፈሰሰ። ይህንንም አይቶ እጅግ አደነቀ ከዚህም በፊት ፀሐይ እንደ ጨለመ፣ ጨረቃ ደም እንደሆነ፣ ዐለቱም እንደተሠነጠቀ፣ ሙታንም እንደተነሡ አይቶ ነበር።
ጌታችንም በተነሣ ጊዜ ስለ ትንሣኤው የሆነውን ሰምቶ ይህን ምሥጢር ይገልጽለት ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ። ሐዋርያው ጴጥሮስንም ላከለት እርሱም ነቢያት ስለ ጌታችን፣ ስለ መከራው፣ ስለ መሰቀሉ፣ ስለ መሞቱ፣ ስለ መነሣቱ፣ ስለ ዕርገቱም ትንቢት እንደተናገሩ ነገረው ። እርሱም ከቅድስት ድንግል በሥጋ ተወልዶ ዓለምን ለማዳን የመጣ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ እንደሆነ አስረዳው።
ያን ጊዜም በቅዱስ ጴጥሮስ ቃል አመነ የምድራዊ ንጉሥ አገልግሎትንም ትቶ ወደ ቀጰዶቅያ ሔደ በውስጧም ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንደ ሐዋርያት ሰበከ።
አይሁድም በጠላትነት ተነሡበት በመሳፍንትም ዘንድ ከሰሱት በላዩም የሐሰት ምስክርአስነሡበት ስለዚህም ራሱን በሰይፍ አስቆረጡት የሰማዕትነትንም አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 12 437 |
| 5 | ሐምሌ ፳፪ /22/
በዚችም ቀን ቅዱስ ለውንትዮስ በሰማዕትነት አረፈ። ይህም ቅዱስ ክርስቲያን ከሀድያን ከሆኑ ሠራዊት ጋር ይኖር ነበር ሀገሩም ጠራብሎስ ነው መልኩም ያማረ በገድሉም ፍጹም የሆነ ነበር። አምላክ ያስጻፋቸው መጻሕፍትንም ያነብ ነበር። ይልቁንም የዳዊትን መዝሙር ሁልጊዜ ያነብ ነበር። ባልንጀሮቹ ለሆኑ ወታደሮችም ያስተምራቸው ይመክራቸውም ነበር። እግዚአብሔርንም እንዲፈሩ ያስገነዝባቸው ነበር።
የማይጠቅሙ የረከሱ የአማልክትንም ሸክም ከትከሻችሁ ጣሉ ይላቸው ነበር። ከስሕተትም ተመልሰው ክብር ይግባውና በጌታችን ያመኑ አሉ። ከእነርሱም ወደ መኰንኑ ሒደው የከሰሱት አሉ።መኰንኑም በሰማ ጊዜ ወደርሱ አስቀርቦ ጠየቀው እርሱ ግን ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስን እንደሚያመልከው በመኰንኑ ፊት ታመነ።
መኰንኑም ጭካኔውን አይቶ ሥጋው እስከ ሚቆራረጥ ደሙም እንደ ውኃ በምድር ላይእስኪፈስ ድረስ ሥቃዩን እጥፍ ድርብ አደረገበት ። ከዚህም በኋላ በውኃ እንዲዘፍቁት በእግሩም እንዲጐትቱትና በወህኒ ቤት እንዲጥሉት አዘዘ በዚያም ነፍሱን አሳለፈ ገድሉንም ፈጸመ።
የምታምን ሀብታም ሴት መጥታ ለወታደሮች ብዙ ገንዘብ ሰጥታ የቅዱሱን ሥጋ ወሰደች በአማሩ ልብሶችም ገነዘችው የወርቅ ሣጥንም አሠርታ በውስጡ አኖረችው ። ሥዕሉንም አሣለች በፊቱም ሁልጊዜ የሚያበራ ፋና አኖረች ። ለዚችም ሴት ቅዱሱ ያደረገላት የድካም ዋጋዋ ሰኔ አንድ ቀን ተጽፎ አለ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ቅዱስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 13 169 |
| 6 | መራሄ ብርሃን
መራሄ ብርሃን ረድኤትህ የበዛ
ወደ ግብፅ ስትሄድ ድንግል ልጇን ይዛ
አብረህ የተራዳህ መልዐከ ልዑል
የእግዚአብሄር አገልጋይ ቅዱስ ዑራኤል
አዝ
አበው ሠባስገል ዑራኤል
ከምስራቅ ሲመጡ ዑራኤል
ሆነህ ቆመህ የመራህ ዑራኤል
አምሃ እንዲሠጡ ዑራኤል
ህይወቴን አቅናልኝ ዑራኤል
ከኃጥያት አውጣና ዑራኤል
በብርሃን ምራኝ በፅድቅ ጎዳና
አዝ
ፈጥነህ የምትደርስ ዑራኤል
ስምህን ለጠራ ዑራኤል
ፅዋህ አድርጎናል ዑራኤል
ያጠጣህ ለዕዝራ ዑራኤል
ጥበብ መንፈሳዊ ዑራኤል
በውስጤ እንዲዘራ ዑራኤል
በርሃናዊው መላክ ልቦናዬን አብራ
አዝ
ለሔኖክ የገለፅክ ዑራኤል
ረቀቀ ምስጢር ዑራኤል
በገፀ ሰማይ ላይ ዑራኤል
የፊደላት ቁጥር ዑራኤል
ማስተዋል አግኝቼ ዑራኤል
በፍቅር እንድሞላ ዑራኤል
ምልጃህ አይለየን ሁነኝ ከለላ
አዝ
አምላክ ስለሰው ልጅ ዑራኤል
ቀራንዮ ሲሰዋ ዑራኤል
ደመ መለኮቱን ዑራኤል
በብርሃን ፅዋ ዑራኤል
ተቀብለህ ረጭተህ ዑራኤል
አለምን የቀደስክ ዑራኤል
ለምስጋና አንቃኝ በነግህና በሰርክ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 11 702 |
| 7 | እንዲህ በአራት ነጥብ
እንዲህ በአራት ነጥብ ሊዘጋ ምዕራፉ
እግዚአብሔር ሊያሸንፍ የእርሱ ሆኖ ሰልፉ
መልካም ለመናገር አፉ ባይታደል
ይህን እስኪያይ ጠላት ምን አለ ዝም ቢል/2/
አዝ
መልካሙን ደብቆ ክፉን እያሳየ
ይለኝ ነበር ጠላት እግዚአብሔር ዘገየ
ግን ሁሉን በጊዜው ውብ አግድጎ ሲሰራ
አፍሮአል ለዘላላም ደንቆት የእርሱ ሥራ/2/
አዝ
በቃ ልጅ የለህም አትወልድም ሣራ
ላይሰማህ እግዚአብሔር ጮኸ ብትጣራ
እያለ ጠላቴ መስሎት ያሸነፈ
ይስሃቅ ተወለደ ያ ቀንም አለፈ /2/
አዝ
ፍፃሜዬን ሳያይ ገና ከጅምሩ
ጠላት በእሱ ግምት ብዙ መናገሩ
አስብሎታል ቴቄል ተቀይሮ ስሙ
የዘገየ መስሎ ጌታ በመቅደሙ/2/
አዝ
ድንጋይ ያሸከመን ውሃ ተሸከመ
ለእኛ ቀን ወጣልን ለእርሱ ግን ጨለመ
ገዳይ ቢዘገይም ሟች በመገስገሱ
ፈረሰኛው ሞተ እስከነ ፈረሱ/2/
አዝ
ቢመስለንም ሌሊቱ ፍፁም የማይነጋ
ተቆልፎ የሚቀር በሩ እንደተዘጋ
እርሱን ተስፋ አድርገው ባመንክበት ፅና
ቀን አለው እግዚአብሔር ያደርግሃል ቀና/2/
ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 15 180 |
| 8 | ሐምሌ ፳፩ /21/
በዚችም ቀን ቅድስት ኄራኒ የስሟ ትርጓሜ ሰላም ፍቅር የሆነ ለንጉሥ ሉክያኖስ ልጁ ምስክር ሁና ሞተች። እርሱም አባቷ ያማረ አዳራሽ እና የሚያስፈልጋትን እንዲሁም የሚያስተምራትም አንድ ሽማግሌ ሰው አድርጎ ሠራላት።
ዕድሜዋም ሰባት ዓመት ሆናትና ያን ጊዜ ራእይን አየች ለመምህሯም ስትነግረው በክብር ባለቤት በሆነ ክርስቶስ ስለ ስሙ ትጋደዪ ዘንድ አለሽ አላት።
ከግዜ በኋላም አባቷ ወደርሷ መጣና ላጋባሽ እኔ እሻለሁ አላት ከዚህም በኋላ ወደ እግዚአብሔር ጸለየችና ከጳውሎስ ደቀ መዛሙርት አንዱ ወደዚች ሀገር መቶ ያጠምቅሻል
አላት።በማግሥቱም ያ ሐዋርያ መጥቶ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃት። በዚህ ጊዜ አባቷ አሰቃያት እግዚአብሔርም ሲያድናት አይተው ቤተሰቦቿ አመኑ። ቊጥራቸውም ሦስት መቶ ሆነ።
እርሷን ያጠመቀ ሐዋርያ አጠመቃቸው። የጎረቤት ሀገር ንጉስም ይሕን ሰምቶ ብዙ አሰቃያት። እግዚአብሔር ግን ከሁሉ አዳናት። ያም ኑማርያኖስ ሙቶ በርሱ ፈንታ ሳፎር ነገሠ።
እርሱም በታላቅ ጦር ወጋትና ነፍሷን አሳለፈች የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ከሞተ አስነሣት። ንጉሥ ሳፎርም በአየ ጊዜ እጅግ አደነቀ ሰገደላትም በጌታችን ኢየሱስም አመነ። ከእርሱም ጋራ ከሀገር ሰዎች ብዙ ወገኖች አመኑ ቁጥራቸውም ሠላሳ አንድ ሺህ ሆነ። ከዚህ በኋላም ብዙ ሀገራትም እየዞረች ትመሰክር እና ተአምራትን ታደርግ ጀመር። በመጨረሻም የድልና የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለች።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋራ ይኑርለዘላለሙ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 15 212 |
| 9 | ጸጋህ ይብዛልኝ
ጸጋህ ይብዛልኝ ምህረት አይራቀኝ
አማኑኤል ሆይ ስራህ ደነቀኝ
ተመስገን ልበል ላቅርብ ምስጋና
በአንተ ቸርነት ቁምያለሁና
አዝ
ጸጋ በዝቶልኝ እዘምርልሃለው
በምስጋና ላይ ምስጋና አብዛለው
አለኝ ሺህ ቃላት አለኝ ብዙ ቋንቋ
አንተን መግለጫ ለዓለም የሚበቃ
አዝ
የተናገርከው ያሰብክልኝ ሆነ
የልቤ መሻት ይህንን ነበረ
አስተካከልከኝ ከሃያላን ጋራ
አማኑኤል ሆይ እፁብ ያንተ ሥራ
አዝ
በለምለሙ መስክ ኣሳድረኸኛል
ያ የጭንቁ ቀን አሳልፈኸኛል
የምስጋና እርሻ ሆነልኝ ደጅአፌ
አባት ሆይ ስለው ማር ማር አለው አፌ
አዝ
ባዝን ብደሰት ብወድቅ ብነሳ
እስከ እሁን አለው በአንተ የተነሳ
መርከቤን ጥዬ ተስፋ አደርገሃለሁ
እንደምትሞላው እተማመናለሁ
ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 19 186 |
| 10 | ሐምሌ ፳ /20/
በዚህች ቀን ለስም አጠራሯ ክብር ይሁንና እመ ብርሃን ድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ ገብታለች። በዓሉ ከሰላሳ ሦስቱ የእመቤታችን በዓላት እንደ አንዱ አይቆጠርም። ምክንያቱም ቅዱሳን ሊቃውንት በዓታ ከበዓታ ጋር ይስማማል ብለው የታኅሣሥ ሦስትን በዓል ከሰላሳ ሦስቱ ደምረውታል።
እመቤታችን ወደ ቤተ መቅደስ የገባችው ሁለት ጊዜ ሲሆን አንደኛው ዛሬ የምናከብረውና በተወለደች በሰማንያ ቀኗ የገባችበት ነው። (ከግንቦት 1 ጀምረን እናስላው 80 ቀን ይመጣል::) ኦሪት እንዳዘዘው ቅዱሳን ኢያቄምና ሐና ንጽሕት ሕፃን ድንግል ማርያምን ታቅፈው የርግብ ልጆች (ግልገሎች) ዋኖስም ይዘው ወደ ቤተ መቅደስ ሒደዋል። ካህናቱ ዘካርያስና ስምዖን ወጥተው በደስታ ተቀብለዋቸዋል። እመቤታችን ለወላጆቿ ማኅጸን የከፈተች በኩር ናትና በእግዚአብሔር ፊት አቅርበዋታል::
ሁለተኛው ከሦስት ዓመታት በኋላ እንደ ስዕለታቸው ወደ ቤተ መቅደስ ወስደው ለእግዚአብሔር ሰጥተዋት ተመልሰዋል።
እግዚአብሔር ዛሬ ያልቃል: ነገ ይደቃል የማይባለውን የድንግል እናቱን ፍቅር አብዝቶ ያድለን። በረከቷም በእኛ ላይ ጸንቶ ይኑር።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 17 491 |
| 11 | አበርታኝ ገብርኤል
አንተ የልቤ ወዳጂ ከአንተ ጋር አለኝ ጉዳይ
አንተ የእኔ ድጋፍ ከአንተ ጋር አለኝ ጉዳይ
አበርታኝ ገብርኤል በምድር በሰማይ
ምስራች አሰማኝ ናልኝ ከአርያም ላይ
አዝ
ሀዋርያ ልደት ፅድቅን ምታሰማ
ከጥንት ጀምሮ የሆንክ የኔ ግርማ
ስወጣ አይሀለሁ ሆነህ ከፍታዬ
ክንፍህ ተዘርግቶ ለምህረት በላዬ
አዝ
ገብርኤል ፀሀይ ወጣ በማለዳ
ማእረግ ልትሆነኝ እኔን ልትረዳ
የእሳቱ ወላፈን ሀይሉ ቀዘቀዘ
ኩራት አለው ልቤ በአንተ እየታገዘ
አዝ
መልአከ አድኖ ተልከህ ከጌታ
የመከራዬ ክንድ ጉልበቱ ተመታ
ከእንግዲህ ሚያሰጋኝ ማነው በህይወቴ
እያለኝ ማምለጫ ገብርኤል አባቴ
አዝ
ማንም የማይፈታው የህይወት ቋጠሮ
ሰም ወርቅ የሆነብኝ የነፍስ እንጉርጉሮ
ብዙ የምነግርህ በውስጤ አለ እና
ነፍሴን ልታዳምጥ ገብርኤል ቶሎ ና
ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 16 211 |
| 12 | የመላእክት አለቃ
የመላእክት አለቃ ገብርኤልን ላከው
ኃያሉ እግዚአብሔር በሰማያት ያለው
የባህሪይ ልጄ ወዳንቺ ይመጣል
ብለህ ለጽዮን ልጅ ንገራት ለድንግል
አዝ
ኃይለ ልዑል ወልድም ሥጋሽን ይለብሳል
በተለየ አካሉ ወዳንቺ ይመጣል
ከሥጋሽም ሥጋን ከነፍስሽም ነፍስ
ነስቶ ይዋሃዳል በግዕዘ ሕፃናት ካንቺ ይወለዳል
አዝ
ደንቆሮ ሊሰማ ዲዶች ሊናገሩ
በጌታ ተአምራት እውራን ሊበሩ
ሙታን ይነሱ ዘንድ በማሕፀንሽ ፍሬ
ከእግዚአብሔር ወዳንቺ ተልኬአለው ዛሬ
አዝ
ደስ አሰኛት አለው በልዩ ሰላምታ
ሐሴት እንድታደርግ ምስራቹን ሰምታ
ድዳ እንዳደረከው ካህን ዘካርያስን
እንዳታሳዝናት ከእርሷጋር ስትደርስ
አዝ
ገብርኤል በደስታ ምስራቹን ይዞ
ከሰማይ ወረደ በአምላኩ ታዞ
በሊባኖስ መንደር እስኪሰማ ድረስ
ክንፉን እያማታ መጣ ሲገሰግስ
አዝ
ደስ ይበልሽ አላት እየተሳለማት
ሐርን ከወርቅ ጋር ስትፈትል አግኝቷት
እውነተኛው ንጉሥ ካንቺ ይወለዳል
ላንቺ ፍቅርና አንድነት ይገባል
ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 18 359 |
| 13 | ገብርኤል መልአከ ራማ
ገብርኤል
ገብርኤል መልአከ ራማ /2/
ስንጠራህ ፈጥነህ ድረስ ድምጽህን እንስማ
አዝ
ትንቢቱ ሲፈጸም ዘመኑ ሲያበቃ
ከቀናት ሳትዘግይ ሳይጎድል ደቂቃ
ወደ ድንግል መጥተህ ደስታን አበሰርክ
የአምላክን ሰውን መሆን ለአለሙ ሰበክ/2/
አዝ
ከውኃ እና ከእሳት ከሞት አመለጡ
በእሳቱ መካከል ለጥፋት ቢሰጡ
አንተ ባለህበት በየትኛውም ስፍራ
ምንም ቦታ የለው ሞትና መከራ/2/
አዝ
የመንገዴ መሪ ፈውስ ነህ ለህመሜ
ገብርኤል ስትመጣ በዛልኝ ሰላሜ
ደስታን አብሳሪ ተሸክመህ ዜና
ዛሬም ለሀገራችን ምስራች ይዘህ ና/2/
አዝ
አንጌቤናይቱ ቅድስት ኢየሉጣ
ስለአንተ ትመስክር እስከ ልጇ ትምጣ
እሳት ነህ ገብርኤል ነበልባል አስወጋጅ
የአምላክን መወለድ ለአለም ምታውጅ/2/
ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 20 273 |
| 14 | ሐምሌ ፲፱ /19/
በዚችም ቀን ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ በሰማዕትነት መከራ ተቀበሉ ። ይህም ሕፃን ዕድሜው ሦስት ዓመት ሲሆነው ከሮሜ አገር ወደሌላ ሀገር እናቱ ይዛው ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኰንን አገኘችው ።
ሰዎችም ነገር ሠሩባት ወደርሱ አስቀረባትና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኰንን ሆይዕድሜው ሦስት ዓመት የሆነው ሕፃን አለ እርሱን ጠይቅ አለችው ።
ሕፃኑም በተጠየቀ ጊዜ ስለ እግዚአብሔር አምላክነት እና ስለ ጣዖታቱ ከንቱነት ተናገረ። ወዳለበት ጭፍራውን ልኮ ወደርሱ አስመጣው ሕፃኑንም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ሕፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው። ሕፃኑም መልሶ አዎ ለእኔ ደስታ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ኀዘንና ልቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው መጽሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏልና አለው እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስከ አስደነገጣቸው ድረስ ንጉሡን መኳንንቱንና ጣዖታቱን ረገማቸው ከብርታቱም የተነሣ አደነቁ።
መኰንኑም በአፈረ ጊዜ በዚህም ሕፃኑን እና እናቱንን በብዙ አሰቃያቸው እግዚአብሔርም ያለምንም ጉዳት ያነሣቸው ነበር። ብዙዎች አሕዛብም ይህን አይተው በሰማዕትነት ሞቱ። በሕፃኑ ላይም የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት። ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው።
ከዚህም በኋላ በፈላውሀ ውስጥ በገቡ ጊዜም የውኃው ፍልሐት እንደ ንጋት ጊዜ ውርጭ ቀዘቀዘ ከእግዚአብሔር የታዘዘ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ የእሳቱን ኃይል አቀዝቅዞታልና።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 19 813 |
| 15 | 👆የቀጠለ
እኒኽም ቅዱሳን ይኽንን በሚነጋገሩበት ጊዜ በውስጡ አንገትን የሚቆለምም ልብንም የሚያቀልጥ ሆድን የሚሰነጥቅ ሥርን የሚበጣጥስ መሳሪያ ካለበት የብረት ጋን ውስጥ ጨመራቸው፡፡ ከዚህ በኋላ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወረደና የብረቱን ጋን እሳት አጠፋው፡፡ ከቅዱሳኑም አንዳቸውንም ሳያቃጥላቸው የብረቱ ጋር ማቃጠሉና መፍላቱ ጸጥ አለ፡፡
ወንድሞቻችን ሆይ እንግዲህ በጭንቃቸው ጊዜ ገድላቸውን እስኪፈጽሙ ድረስ ይህ መልአክ ከሰማእታትና ከጻድቃን ጐን እንደማይለይ እወቁ ለኃጥአንም ኃጢአታቸውን ይቅር ይላቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ይጸልይላቸዋል፡፡ እኛም የዚህ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል በዓሉን እያከበርን አማላጅና ወዳጅ እናድርገው። በዚህም በሚመጣውም ዓለም ሊረዳን ይችላልና፡፡
ዳግመኛም መስፍኑ ሐሳቡ ሳይሳካለት ስለቀረ 14 የሾሉና የጋሉ የብረት ችንካሮች አምጥተው ሰባቱን በእናቱ በኢየሉጣ አካል ሰባቱን በራሱ በቂርቆስ አካል ማለት ሁለቱን በጆሮዎቹ ሁለቱን በዐይኖቹ ሁለቱን በአፍንጫዎቹ አንዱን በልቡ ይቸነክራቸው ዘንድ ጭፍሮቹን አዘዘ፡፡ ዳግመኛም የህፃኑን የእራስ ቆዳ ገፈው እሳት ውስጥ ይጨምሩ ዘንድ አዘዘ፡፡
አሁንም መልአኩ መጥቶ ይህንን መከራ ከእርሱ አራቀለት፡፡ ቀጥሎም በመቃን ውስጥ ጨምረው በገመድ እንዲጎትቱት አዘዘ፡፡ በዚህም ጊዜ መልአኩ አዳነው፡፡ ሕዝቡም ይህንን ሁሉ ተአምር ባዩ ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገኑት ቅዱስ ገብርኤልንም አከበሩት፡፡ ቅዱስ ቂርቆስና ቅድስት እየሉጣ ብዙ መከራ ከተቀበሉ በኋላ ጥር 15 በሰይፍ ተመትተው ስማትነትን ተቀብለዋል።
የሊቀ መላእክት የቅዱስ ገብርኤል ፣ ቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ የቅድስት እየሉጣ ተራዳኢነት ጸሎት አይለየን። ከዚህ በኋላ ሕፃኑን አስፈልገው ቢጠይቁት ነቢዩ ዳዊት የተናገረው ኃይለ ቃል መንፈስ ቅዱስ ተገልጾለት፤ ‹‹የአሕዛብ ጣዖታት የወርቅና የብር የሰው እጅ ሥራዎች ናቸው፡፡ የሚታመኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ›› መዝ. ፻፴ በማለት ሲዘልፏቸው አገር ገዥው ሰምቶ ተቆጣና የብረት ጋን አስመጥቶ ውኃ ሞልቶ ከዕቶን እሳት ላይ ጥዶ ልዩ ልዩ ማገዶዎች በመጨመር ነበልባሉ ከመጠን በላይ ሆነ፡፡ የብረት ጋኑም ድምፅ እንደ ክረምት መብረቅና ነጎድጓድ እስኪያስፈራ ድረስ አስነድዶ ሕፃኑን ከነእናቱ ወስዳችሁ ጨምሩአቸው ብሎ አዘዘ፡፡
በዚህ ጊዜ ቅድስት ኢየሉጣ በጣም ፈራች፡፡ የእግዚአብሔር ሥራ እፁብ ድንቅ ግሩም ረቂቅ ነው፡፡ ገና አፉን ያልፈታ የሦስት ዓመት ሕፃን ‹‹እናቴ ሆይ! ገድላችን እንፈጽም ዘንድ ጨክኝ በርቺ›› አላት፡፡ ቅድስት ኢየሉጣም ‹‹ልጄ የነፍስ አባት ሁነኝ›› አለችው፡፡ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስም ከዘመናቸው ሳይደርስ፣ ታሪካቸውን ሳይማር የሠለስቱ ደቂቅን ታሪክ መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት ‹‹አናንያን፣ አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ ያድነናል›› ቢላት ፍርሃቱ ሊለቃት ባለመቻሉ፣ ወደ እግዚአብሔር እንዲህ ሲል ጸለየ፡፡
‹‹ጌታ ሆይ! የወይኑን ፍሬ ስትሻ ግንዱን ታጠፋለህን? እንደዚህስ ሁሉ እኔን አድነህ እናቴን ታጠፋታለህን?›› ብሎ በጸለየጊዜ መንፈስ ቅዱስ አደረባትና መንግሥተ ሰማያትን በዓይነ ሥጋ እንድታይ አደረጋት፡፡ ከዚህ በኋላ ፍርሃቱ ለቀቃትና ‹‹ልጄ ሆይ! ከዛሬ ጀምሮ መምህሬ፣ አባቴ፣ መካሪዬ እልሃለሁ እንጂ ልጄ አልልህም›› ብላ በጭካኔ ከልጅዋ ጋር ወደ ፈላው የብረት ጋን ገባችበት፡፡
በዚህ ጊዜ ሕፃኑ ቂርቆስ አናንያን፣ አዛርያንና ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ ያድነናል ያለውን ቃል ለመፈጻም እግዚአብሔር አምላክ መልአኩ
ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው፡፡ መልአኩም በትእምርተ መስቀል እሳቱን ቢባርከው እንደ በረዶ ቀዝቅዞላቸዋል፡፡ በመልካቸውም እንደ ፀሐይ አበራ፡፡ ከእግር ጥፍራቸው እስከ ራስ ጠሩራቸው አንድም ሳይጎዳቸው በደህና ወጡ፡፡
በመጨረሻም ሕፃኑ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ እንዲህ አለ፡፡ ይህን ያህል ገድል ተጋድዬ ምን ዋጋ ትሰጠኛለህ ቢለው፣ ጌታ በልብህ ያለውን ሁሉ እሰጥሃለሁ አለው፡፡ ዳግመኛም ሥጋህ በምድር ላይ እንዳይፈርስ እንዳይበሰብስ በኤልያስ ሠረገላ ላይ አኖርሃለሁ አለው፡፡
ስለሆነም በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያናችን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለእናታችን ለቅድስት ኢየሉጣ እና ለሕፃኑ ለቅዱስ ቂርቆስ ያደረገውን ይህን ታላቅ ተአምር ድንቅ ሥራ በማሰብ ከዋዜማው ጀምራ እግዚአብሔርን ስታመሰግን ትውላለች ታድራለች፡፡
የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤል በረከት ተራዳኢነት ከሁላችን ጋር ይኑር አሜን፡፡
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 18 377 |
| 16 | ሐምሌ 19
ቅዱስ ገብርኤል
እንኳን ለታላቁ መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን!!!
በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት ሐምሌ 19 የቅዱስ ገብርኤል አመታዊ በዓል ነው፡፡ ይህ ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት እየሉጣንና ልጇን ቅዱስ ቂርቆስን ከሞት አደጋ እንደታደገበት የሚታሰብበት ዕለት ነው። የሐምሌ 19 ስንክሳርና የሐምሌ ወር ድርሳነ ገብርኤል እንዲህ ተርከውታል፡፡
በዘመነ ሰማእታት ከሐድያን ነገሥታትና መኳንንት በክርስቲያኖች ላይ መከራ አጽንተውባቸው ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት ብዙዎች ሰማእትነትን ሲቀበሉ የተቀሩት አገር ጥለው ተሰደዱ። እየሉጣም የሦስት ዓመት ህፃን የነበረውን ቅዱስ ቂርቆስን ይዛ ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኮንን አገኘችው ሰዎችም ነገር አሰሩባት ወደእርሱ አስቀረባት እና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኮንን ሆይ ዕድሜው ሦስት አመት የሆነው ህፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እሱን ጠይቅ አለችው፡፡
ህፃኑም ወዳለበት ጭፍራውን ልኮ ወደእርሱ አስመጣው ህፃኑም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ህፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው፡፡ ህፃኑም መልሶ አዎ ለኔ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ሐዘንና ለቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው፡፡ መጻሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏል እና አለው፡፡ እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስካስደነገጣቸው ድረስ ንጉሱን መኳንንቱንና ጣኦታቱን ረገማቸው፡፡ከብርታቱም የተነሳ አደነቁ፡፡
መኮንኑም በአፈረ ጊዜ በያይነቱ በሆነ ስቃይ ታላላቆች የማይችሉትን ታላቅና አስጨናቂ የሆነ ስቃይን አሰቃየው እናቱንም ከእርሱ ጋር አሰቃያት፡፡ እግዚአብሔርም ያለ ምንም ጉዳት ያነሳቸው ነበር፡፡ ብዙዎች አህዛብም ይኸንን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስም አምነው በሰማእትነት አረፉ፡፡ የሰማእትነትንም አክሊል ተቀበሉ፡፡ በህፃኑም ላይ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት፡፡ ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው፡፡
መስፍኑም በውስጡ ሰም፣ ጨው፣ ባሩድ፣ ሙጫ የዶሮ ማር፣ እርሳስ፣ ብረት፣ ቅንጭብ፣ ቁልቋል ጨምራችሁ ታላቅ የብረት ጋን አንጡልኝ ብሎ ጭፍሮቹን አዘዛቸው፡፡ ጭፍሮቹም እንዳዘዛቸው ካአደረጉ በኋላ ያዘዝከንን ሁሉ ፈጽመን እሳቱ ነዶ ፈልቷል፡፡ ድምፁ እንደነጐድጓድ ይጮኸል ወላፈኑም እንደጸሐይ ነጸብራቅ በሩቁ ይጋረፋል፡፡ የፍላቱም ኃይል በ14 ክንድ ያኽል ከፍታ ወደ ላይ ይዘላል፡፡ እንግዲህ በውስጡ የሚጣሉትን እዘዝ አሉት በዚህ ጊዜ ህፃን ቂርቆስና እናቱ እየሉጣ በክርስቶስ ስም ስለሚያምኑ አስረዋቸው ነበርና ከፍላቱ ሊጨምሯቸው ከእስር ቤት አወጧቸው፡፡
በዚያም ፍላቱ ወደላይ በሚዘል ብረት ጋን ውስጥ ለመጨመር ሲወስዷቸው የነዚህን ቅዱሳን አሟሟት ያዩ ዘንድ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች እንዲሰበሰቡ አዘዛቸው፡፡ በዚህን ጊዜ ቅድስት እየሉጣ የፍላቱን ጩኸት በሰማችና ባየች ጊዜ ተሸበረች፡፡ ተዘጋጅቶላት ከነበረው ክብር ልታፈገፍግ ሞከረች፡፡ ልጇ ቅዱስ ቂርቆስ ግን እናት ሆይ ከዚህ የብረት ጋን ግርማ የተነሳ አትፍሪ ድንጋጼም አይደርብሽ አናንያንና አዛርያን ሚሳኤልንም እግዚአብሔር ከእቶነ እሳት እንዳወጣቸው ሁሉ እኛንም ከዚህ ከብረት ጋን ሊያወጣን ችሎታ ያለው መሆኑን አትጠራጠሪ፡፡
እናት ሆ ከዚህ ከሚያልፈው ዓለም ጭንቅና መከራ ለመዳን ስትይ በማያልፈው ዘላለማዊ እሳት ለመቀጣት ትመርጫለሽን ይኽስ አይሆንም ይቅርብሽ፡፡ በአሁኑ ጊዜ እግዚአብሔር በመካከላችን አለና ይረዳናል፡፡ እናት ሆይ ሶስናን ከእደ ረበናት /መምህራነ አይሁድ/ ዳንኤልን ከአፈ አናብስት ያዳነ እርሱ እኛንም ከጋን ፍላት ያወጣናል፡፡ ይልቁንም እግዚአብሔር በዚህ የብረት ጋን ውስጥ ግዳጃችንን ልንፈጽም ፈቅዶ ከሆነ ኢዮብ ንብረቱንና ገንዘቡን ልጆቹንና ሚስቱን በመጨረሻም የተፈጥሮ አካሉን ባሳጣው ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ እግዚአብሐር ሰጠ እግዚአብሔር ነሳ እግዚአብሔርም እንደወደደ አደረገ ከማለት በስተቀር ምንም የተናገረው ነገር እንደሌለ ሁሉ እኛም የሱን ዓላማ በመከተል ይኽንን መከራ ልንታገስ ይገባናል፡፡
ነገር ግን እናቱ በዚህ ምክር ልትጽናና ባለመቻሏ ቅዱስ ቂርቆስ ዐይኑን ወደ ሰማይ አቅንቶ አቤቱ አምላክ ሆይ ይችን ባሪያህን ከርስትህ የምትለያት ከሆነ ከባለሟልነትህ መጽሐፍ ፋቀኝ፤ አቤቱ አዝመራውን አቃጥለ ፍሬውን ልትባርክ ትወዳለህን ይኽን እንዳታደር ግን ቸርነትህ ትከለክልኸለች አቤቱ እንጨቱን ቆርጣችሁ አንድዱት ቅጠሉን ግን ጠብቁት ብለኽ ልታዝ መለኮታዊ ባሕሪህ አይደለም፡፡ ነገር ግን እንጨቱንም ቅጠሉንም በአንድ ጠብቁት ብለኽ ታዝዛለኽ እንጂ፡፡ እንግዲህ በዚህ ምክንያት ይኽንን ያየ ሁሉ ማዳን የሚችል አምላክ ቢኖራቸውስ ኖሮ ከእሳት ባልሸሹም ነበር ብሎ አይጠራጠር፡፡
አቤቱ ዲያብሎስም ከባለስልጣኑ ይልቅ እኔ በረታሁ ቅዱሳኖቹንም ድል ነሳኋቸው ብሎ እንዳይመካ ከመንጋውም አንድ በግ ቀማው በማለት እንዳይደነፋ ለእናቴ ጽኑ የሆነ ኃይለ መንፈስ ቅዱስን ስጣት ብሎ በጸለየ ጊዜ ዲያብሎስ ከእየሉጣ አጠገብ ብን ብሎ ጠፋ፡፡ ከዚህ በኋላ ቅድስት እናቱ በሰማያዊ መንግሥት አባት የሆንከኝ ልጄ ሆይ ጌታኽ ኃይልን ሰጥቶኛልና የሚጠብቀንን ገድላችንን ፈጽመን ድል እናድርግ እነሆ በብረት ጋን ውስጥ የሚነደውን እሳት በማይበት ጊዜ በለምለም /በምንጭ/ ላይ እንደሚወርድ ጠል ሆኖ አይቸዋለሁና አለችው፡፡
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 19 511 |
| 17 | የፍቅር እናት
የፍቅር እናት የሰላም /2/
ይናፍቀኛል ስምሽ ሳልጠራው ስቀር ማርያም
አዝ
በሂወቴ ውስጥ በኑሮዬ
ቅደሚ ከፊት ከሀኅላዬ
ተደላደለ ልቤ
አንቺ አለሽና ካጠገቤ
አዝ
ምኞቴም ይስመር ትልቅ ህልሜ
ልለፍ ወደፊት ተቋቁሜ
የጌታዬ እናት ነሽ
ሀይልን ያረጋል ፀሎትሽ
አዝ
እንዴት ቀራለው ከመንገድ
አደራ እናቴ አስቢኝ
ከሚያስጨንቀኝ ጠላት
ለሚያሳድደኝ አትስጪኝ
አዝ
ትላንትም ዛሬም አመስጋኝ ነኝ
የለም ለነገየሚያስፈራኝ
ሜዳይሆናል ተራራ
ልጅሽ ስላለ ከኔ ጋራ
ሊቀ መዘምራን ቴድሮስ ዮሴፍ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 22 708 |
| 18 | ጥቆማ ስጡን‼️
የ 2018 ዓ.ም ጾመ ፍልሠታ ከመግባቱ በፊት ልክ በየአመቱ እንደምናደርገው ብዛት ላላቸው የገጠር ቤተ ክርስቲያኖች እየዞርን ጾሙ ሳይስተጓጎል ስርአተ ቅዳሴ እንዲቀደስ ማስቀደሻ ንዋየ ቅዱሳት ብዛት ላላቸው የገጠር ቤተ ክርስቲያኖች ድጋፍ እናደርጋለን ።
በአሁኑ የት አካባቢ እንምጣ ጠቁሙን እጥረት ያለባቸው ቦታ ካሉ ጠቁሙን ?
አዘጋጅ:- ማኅበረ ኤዶምያስ
ለመጠቆም በዚህ ያዋሩን
@Yetinieal_2725
@Yetinieal_2725 | 26 503 |
| 19 | አስምርልኝ መስዋዕቴን
አስምርልኝ መስዋዕቴን
ተቀበለኝ ምስጋናዬን
አምላከ አቤል እግዚአብሔር
ተቀበለኝ ምስጋናዬን
አዝ
ባይገባኝ ቅዱስ ስምህን መጥራት
እንደ ኃጢአቴ እንደ በደሌ ብዛት
ፍቀድልኝ ልሰዋ ምስጋናህን
ልመስክረው ፅድቅና ማዳንህን
በጥበቤ አይደለም በብቃቴ
ለምስጋና ስምህን መጥራቴ
አዝ
የምስጋናን ቅኔ ልሰጥ ሰጠኸኝ
የዜማ እቃ በአፌ አሰለጠንከኝ
እለት እለት ቸርነትህ ደንቆኛል
ለምስጋና ፍቅርህ ያበረታኛል
በጥበቤ አይደለም በብቃቴ
ለምስጋና ስምህን መጥራቴ
አዝ
ኮልታፋ ነው ያልበቃ አንደበቴ
ደካማ ነው ያልበረታ ጉልበቴ
ስለ ስምህ ዘወትር እቀናለሁ
ለዘላለም ጌታዬ እልሃለሁ
በጥበቤ አይደለም በብቃቴ
ለምስጋና ስምህን መጥራቴ
አዝ
ምስጉን ጌታ ስምህን ላመስግን
ስለምትወድ ንፁህ መስዋዕትን
በከበረ በያሬዳዊው ዜማ
ተቀበለው ምስጋናዬን በራማ
በጥበቤ አይደለም በብቃቴ
ለምስጋና ስምህን መጥራቴ
ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 27 072 |
| 20 | ሐምሌ ፲፮ /16/
በዚች ቀን ቅዱስ አባት ወንጌሉ ዘወርቅ የተባለ ዮሐንስ አረፈ ። ይህም ቅዱስ ከሮሜ አገርነበር አባቱም አጥራብዮስ የሚባል ባለጠጋ ነው ። የእናቱም ስም ብዱራ ይባላል ። እንዲማርም ለመምህር ሰጡት ቅዱሳት መጻሕፍትንም ተማረ ።
ከዚህም በኋላ አባቱ ገበታው የወርቅ የሆነ ወንጌልን አሰርቶ ሰጠው ከእርሱም አትለይም ነበር። በዚያም ወራት ወደ ኢየሩሳሌም የሚጓዝ መነኵሴ ወደ እነርሱ መጣ በእነርሱም ዘንድ አደረ ለቅዱስ ዮሐንስም ስለምንኩስና ነገር በዚህ ጊዜ ከእርሱ ጋር ወደ ገዳም ሔዶ መነኮሰ። በብዙ ተጋድሎም ተጋደለ።
በዚህ ተጋድሎም ሰባት ዓመት በሆነው ጊዜ ከእነርሱ በረከትን ትቀበል ዘንድ ከመሞትህ በፊት ወደ አባትህና እናትህ ሒድ የሚል ራእይ አየ ።
ወደ አባቱ ቤትም በደረሰ ጊዜ በትንሽ ጎጆ ውስጥ በአባቱ ደጅ በጾም በጸሎትና በስግደት እየተጋደለ ባሮች ከአባቱ ማዕድ የሚጥሉለትን ፍርፋሪ እየተመገበ ሰባት ዓመት ኖረ። ዕረፍቱም በቀረበ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ከሰባት ቀን በኋላ ከዚህ ዓለም ትወጣለህ ብሎ ነገረው። ከዚህም በኋላ እናቱን አስጠርቶ ማንነቱን ሳይነግራት የመሞቻው ቀን ስለደረሰ በለበሰው ጨርቅ እና በሚኖርበት መጠለያ እንዲቀብሩት አምሏት የወርቅ ወንጌሉን ሰጣት። ለባሏ ባሳየችውም ጊዜ የልጃቸው እንደሆነ አወቁ።
ቢጠይቁትም ነገራቸው። ሰባቱ ቀንም ሲፈጸም ቅዱስ ዮሐንስ አረፈ።
ከዚህም በኋላ በስሙ ያማረች ቤተ ክርስቲያን ሠርተው ሥጋውን በውስጧ አኖሩ ። ከእርሱም ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶች ተገለጡ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 24 899 |
