ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን። YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8 Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR
显示更多📈 Telegram 频道 ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit 的分析概览
频道 ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit (@ortodoxmezmur) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 167 745 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 145,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 141 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 167 745 名订阅者。
根据 21 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 288,过去 24 小时变化为 47,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 12.82%。内容发布后 24 小时内通常能获得 6.14% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 21 498 次浏览,首日通常累积 10 295 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 143。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ።
ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን።
YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8
Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR”
凭借高频更新(最新数据采集于 22 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
数据加载中...
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 21 七月 | +47 | |||
| 20 七月 | +28 | |||
| 19 七月 | +37 | |||
| 18 七月 | +22 | |||
| 17 七月 | +10 | |||
| 16 七月 | +11 | |||
| 15 七月 | 0 | |||
| 14 七月 | +23 | |||
| 13 七月 | +13 | |||
| 12 七月 | +45 | |||
| 11 七月 | +33 | |||
| 10 七月 | +3 | |||
| 09 七月 | +10 | |||
| 08 七月 | +47 | |||
| 07 七月 | +22 | |||
| 06 七月 | +42 | |||
| 05 七月 | +44 | |||
| 04 七月 | +26 | |||
| 03 七月 | +49 | |||
| 02 七月 | +52 | |||
| 01 七月 | +43 |
ሐምሌ ፲፬ /14/በዚች ቀን የጌታ ክርስቶስ ጭፍራ ቅዱስ አብሮኮሮንዮስ በሰማዕትነት አረፈ። የዚህም ቅዱስ ትውልዱ ከኢየሩሳሌም ነው የአባቱ ስም ክርስቶፎሮስ ነው ትርጓሜውም ክርስቶሰን የለበሰ ማለት ነው ። ክርስቲያንም ነበረ የእናቱም ስም ቴዎዶስያ ነው እርሷ ግን ጣዖታትን ታመልክ ነበረች። አባቱም በአረፈ ጊዜ እናቱ ወስዳ ለዲዮቅልጥያኖስ ሰጠችው እርሱም ክርስቲያኖችን እንዲያሳድድ አዘዘው። በመንገድም ሳለ ከሰማይም ክርስቲያኖችን ካሳደደ ክፉ አሟሟት እንደሚሞት ሰማ። ክርስቶስም እራሱን ገለጸለት። ከዚህ በኋላ በክርስቶስ አምኖ የወርቅ መስቀል አሰርቶ ወደ እስክንድርያ ተጓዘ። በመንገድም በመስቀሉ ድል አደረገበት። በመጨረሻ ለዲዮቅልጥያኖስ ስለ እርሱ ነገሩት እርሱም በብዙ አሰቃየው እግዚአብሔር ከሁሉ አዳነው። በዚያ የነበሩ ሕዝቡም አይተው እጅግ አደነቁ እንዲህም እያሉ ጮኹ እኛ በግልጥ ክርስቲያን ነን በቅዱስ አብሮኮሮንዮስ አምላክ እናምናለን። ከእነርሱም ጋራ ሁለት መኳንንትና ዐሥራ ሁለት ሴቶች እናቱ ቴዎዶስያም ነበሩ መኰንኑም ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጧቸው አዘዘ። እነርሱም ቆረጡአቸው። በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ሐምሌ ስድስት ቀን ተቀበሉ። ቅዱስ አብሮኮሮንዮስን ግን እንደገና ብዙ ከአሰቃዩት በኋላ መኰንኑ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጡት በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
| 2 | አዳነኝ ጌታ
አዳነኝ ጌታ አዳነኝ
ፈወሰኝ ጌታ ፈወሰኝ /2/
እግዚአብሔር አዳነኝ ኃጢአተኛውን ወደደኝ
አዝ
ያልፋል ያላልኩት አልፎልኝ አይቼ
በእንባ ታጠብኩኝ ከድቅድቅ ወጥቼ
እንግዲህ ላንተ ምስክር ሆኛለሁ
ሥራህን ለዓለም ሁሌም እነግራለሁ /2/
ክንድህ ብርቱ ነው ደካማን ለመርዳት
ታውቅበታለህ የዛለን ማበርታት
አይኔን ከሰዎች ማራቄ ጠቅሞኛል
ደጅህ ወድቄ መኖር ተሽሎኛል
አዝ
የሀዘኔን ማቅ አውልቀህ ጣልክልኝ
ሞቴን ስጠብቅ ዕድሜ ጨመርክልኝ
ከአልጋዬ ላይ አነሱኝ እጆችህ
ተፈውሻለሁ ዛሬ በምህረት /2/
ቃልህ ፅኑ ነው ዳግም ይጠግናል
ጎባጣ አቅንቶ ሽባውን ተርትሯል
ሕይወቴ ባንተ ዛሬ አዲስ ሆናለች
በክብር መዝገብ በእጅህ ተፅፋለች
አዝ
የሀሰትን ፍርድ ጌታ ቀለበስከው
ተጽናንቷል ባንተ ያ የተገፋ ሰው
የግፍን ጽዋ አራከው ከፊቱ
በእጁ ላይ የለም ዛሬ ሰንሰለቱ /2/
በሃማ መስቀል መርዶኪዮስ የለም
የናቡቴ ደም በከንቱ አልቀረም
የእውነት ዳኛ ጌታ ስትመጣ
የሀሰቱ ሰው ግፈኛው ተቀጣ
ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 11 568 |
| 3 | ሐምሌ ፲፫ /13/
በዚች ቀን ከግብጽ ደቡብ ከቡና አውራጃ ጡሕ ከሚባል አገር ቅዱስ አሞን ምስክር ሁኖ አረፈ። ለዚህም ቅዱስ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ተገለጸለት ከእርሱ የሚሆነውንም ሁሉ ነገረው።
ከዚህ በኋላ ወደ እንዴናው ከተማ ሒዶ አውግስጦስ በሚባል መኰንን ፊት ክብርይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ። መኰንኑም በመንኰራኵር ውስጥ በእሳት ላይ በመጣል በእሳት በአጋሉት በብረት ዐልጋ ላይ በማጋደም ከላም ቆዳ በተሠራ ጅራፍ በውሽባ ቤት ማንደጃ ውስጥ በመጨመር ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃዩት።
የራሱንም ቆዳ ገፈው በራሱ ላይ የእሳት ፍም አኖሩ እግዚአብሔርም ያጸናው ነበር ያለ ምንም ጉዳት ጤነኛ አድርጎ ያስነሣው ነበር ። ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና እግዚአብሔር ክርስቶስ በጐልማሳ አምሳል በብርሃን ሠረገላ ላይ ሁኖ ተገለጠለትና አጽናናው እንዲህም አለው ወዳጄ አሞን እኔ ከአንተ ጋራ እኖራለሁ ስምህን የሚጠራውን፣ መታሰቢያህን የሚደርግውን ሁሉ ወይም ገድልህን የሚጽፈውን ሁሉ እኔ በመንግሥቴ ውስጥ አስበዋለሁ ኃጢአቱንም እደመስሳለሁ ሀገርህንም እጠብቃለሁ ይህንንም ብሎ ሰላምታ ሰጥቶት ከእርሱ ዘንድ ዐረገ።
ይህም ቅዱስ በሥጋው ሳለ ታላላቅ ተአምራቶችንና ድንቆችን አደረገ ወዲያውኑም በሰይፍ ራሱን ቆረጡት የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበለ ። ቅዱስ ዮልዮስም በዚያ ነበረ ሥጋውን ወስዶ በመልካም ልብስ ገነዘው ከሁለት አገልጋዮቹም ጋራ ወደ አገሩ ላከው በላይኛው ግብጽም ታላላቅ የሆኑ ድንቆችንና ተአምራቶችን እያሳየ እስከ ዛሬ አለ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ጻድቅ ሰማዕት ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 11 717 |
| 4 | ይለይብኛል
ጠብቆ አሳድጎ ከልጅነቴ
አባት እየሆነኝ ሚካኤል አባቴ
ይለይብኛል ሚካኤል ይለይብኛል
በክንፉ ሸፍኖ በቤቱ አሳድጎኛል /2/
አዝ
አያምርብኝ ብዘነጋው ታሪኬን
ሚካኤል ነው ያስጌጠልኝ ህይወቴን
አልረሳብኝ እርሱ አትርሳብኝ ያልኩትን
ለካስ ሰምቶኝ ኖሯል የልጅነት ጸሎቴን
ሚካኤል ያን ሁሉ ዘመን የታገሰኝ
ሚካኤል ፍሬ ጠብቆ ያልቆረጠኝ
ሚካኤል የከፍታዬ መሰላል
ሚካኤል መነሻዬ ሆነሀል
አዝ
እንዳይከፋኝ አንዳልደፋ አንገቴን
እንዳላለቅስ እንዳላፈስ እንባዬን
እንዳይርቀኝ ደስታ በመንፈሴ እንዳልዝል
ካጠገቤ አይርቅም ያሳደገኝ ሚካኤል
ሚካኤል ቀኔም ቀን አይሆን ሳልጠራህ
ሚካኤል ና ድረስልኝ ሳልልህ
ሚካኤል እንዳስጀመርከኝ ጅማሬዬን
ሚካኤል አሳምረው ፍፃሜዬን
አዝ
ውድቅ አረገው የጠላቴ ክፉ እቅድ
አራመደኝ በከፍታዬ መንገድ
ሊያስቀረኝ አልቻለም ሊጎትተኝ ባላጋራ
ተጥሎ ስላለ በእግዚአብሔር ድንቅ ስራ
ሚካኤል እሳታዊ ነው ነበልባል
ሚካኤል ጠላቴ ፊትህ ይቀልጣል
ሚካኤል ለኔ ኃይሌ ነው መከታዬ
ሚካኤል የዘለዓለም ጠባቂዬ
ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 14 561 |
| 5 | ክረምቱን ለማንበብ የዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ መጽሐፎችን ጨምሮ ሌሎች ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፎች በPdf የሚገኙበትን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ!
👇👇
@Bemnet_Library 📚
@Bemnet_Library 📚 | 11 642 |
| 6 | ኃያል ነው እግዚአብሔር
ኃያል ነው እግዚአብሔር
ኃያል ነው ቅዱሱ /2/
አይቻለሁ በዓይኔ ሲቆም ማዕበሉ
አይቻለሁ በዓይኔ ሲታዘዝ ነፋሱ
አዝ
ሰረገላውን በእሳት ሠርቶታል
በደመና ላይ ይረማመዳል
በብርሃን ድንኳን በሰማይ ያለው
እርሱ ነው ጌታ የምናመልከው /2/
አዝ
እውነት በፊቱ ፍትሕ በእጁ
ሲኦልም ገነት አሉ በደጁ
ሥልጣን የእርሱ ነው አለቅነት
ማን እንደ ጌታ ከአማልክት /2/
አዝ
ታቦር ተራራ ተንቀጠቀጠ
ግርማው ሲገለጥ ሁሉ ቀለጠ
ድንቅን አድራጊ ተአምረኛ
ከማዳኑ ጋር ይምጣ ወደ እኛ /2/
አዝ
ምድር ጠፈሩ ታዟል ለእርሱ
እሳት ተፈትሎ ሆኗል ቀሚሱ
የክብርህ ብርሃን ይብራ በልቤ
አንተ ነህ ለእኔ ውድ ገንዘቤ /2/
ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 16 641 |
| 7 | ሐምሌ ፲፩ /11/
በዚች ቀን መርባስ የሚባል አገር ሰዎች የሆኑ ቅዱሳን ዮሐንስና የአባቱ ወንድም ልጅ ስምዖን በሰማዕትነት ሞቱ ። የዚህ ቅዱስ ዮሐንስ እናቱ መካን ነበረች አባቱም ልጅን ይሰጠው ዘንድ ክብር ይግባውና እግዚአብሔርን ይለምነው ነበር ከዚህም በኋላ ልጁን በሕይወቱ ዘመን ሁሉ ለእግዚአብሔር አገልጋይ ሊአደርገው ተሳለ ።
መጥምቁ ዮሐንስም እግዚአብሔር ልጅን እንደሚሰጠው በራእይ ተገልጦ ነገረው ። ይህን ቅዱስም በወለደው ጊዜ ዮሐንስ ብሎ ጠራው በመጥምቁ ዮሐንስም ስም ቤተ ክርስቲያን ሠራ ። ከዚህ በኋላ አድጎ ዐሥራ ሁለት ዓመት በሆነው ጊዜ አባቱ የበጎች እረኛ አደረገው ምሳውንም ለእረኞችና ለመንገደኞች ሁል ጊዜ ይሰጥ ነበር እርሱ ግን እስከ ምሽት ይጾም ነበር ።
አባቱም ይህን ነገር ሊአረጋግጥ ወደ ርሱ ሔደ አባቱንም በአየው ጊዜ ዮሐንስ ፈርቶ ሊሸሽ ወደደ ። አባቱም የዛሬ ምሳህን አሳየኝ አለው ቢመለከትም አገልግሉን ትኩስ እንጀራን ተመልቶ አገኘው እጅግም አደነቀ ከልጃቸው የሆነውንም ለሚስቱ ነገራት ።
ከዚህ በኋላ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እንዲማር አደረጉት እንጂ በጎችን የሚጠብቅ እረኛ እንዲሆን አልተዉትም። ከዚህም በኋላ አባቱ ሊአጋባው ወደደ ። እርሱ ግን ይህን አልወደደም ። ዐሥራ
ስምንት ዓመት በሆነውም ጊዜ ቅስና ተሾመ ከዚህም በኋላ ብዙ ተአምራትን አያደረገ። የአጎቱ ልጅ ስምዖንም ደቀ መዝሙሩ ነበር በመጨረሻም እግዚአብሔርን አገልግለው ከስምዖን ጋር ሰማዕት ሆኑ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 16 466 |
| 8 | 🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉
📍በፈለጉት ሰፈር ብቻ ይስሩ!
በያንጎ የት መስራት እንዳለብዎ የሚወስኑት እርስዎ ነዎት።
በ My Area የፈለጉትን ሰፈር ብቻ በመምረጥ፣ ከቤትዎ ሳይርቁ በራስዎ ምርጫ ይስሩ።
የፈለጉትን ቦታ ይምረጡ፣ በራስዎ መንገድ ያትርፉ!🏡
📲 አሁኑኑ የያንጎ ፕሮ መተግበሪያን ያውርዱ
🔽🔽🔽ሊንኩን ይጫኑ🔽🔽🔽
https://ya.cc/t/3nVOkmT99fvrCa
ለበለጠ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ
💬 : https://t.me/YangoETH
❗️❗️❗️ | 13 557 |
| 9 | 视频消息 | 12 112 |
| 10 | ድንግል ሆይ
ድንግል ሆይ ወደኔ ትመጪ ዘንድ እንዴት ይሆናል
እመቤቴ ወደኔ ትመጪ ዘንድ እንዴት ይሆናል
ደካማ ነኝ እኔ ምግባር ይጎድለኛል/2/
አዝ
በሥጋዊ ሳይሆን በመንፈስ ዐይኖቼ
ለማየት እሻለሁ ከልቤ ጓጉቼ
ሥራዬ የከፋ መሆኑን አውቃለሁ
ስምሽንም መጥራት እጅግ እፈራለሁ
አዝ
ክብርሽ የበዛ ነው ቤዛዊተ ኵሉ
ምሕረት ታሰጫለሽ ላመነብሽ ሁሉ
ባንቺ የተመካ ምንም አያገኘው
የገሃነም እሳት ሲዖልም አይነካውም
አዝ
የልዑል ማደሪያ የሲና ዕፀ ጳጦስ
አንቺን ላመስግንሽ ከደዌ እንድፈወስ
ፍቀጂልኝ ድንግል ካንቺ ጋር እንድኖር
ልጅሽን ማልጂልኝ እንዲያበቃኝ ለክብር
አዝ
ምንም ተስፋ የለኝ ያላንቺ እናቴ
እመካብሻለሁ እስከ ዕለተ ሞቴ
የምስኪኖች አጽናኝ የጭንቅ ቀን ደራሽ
የልቤ ማረፊያ ምግብ መጠጤ ነሽ
አዝ
የጌታዬ እናት ድንግል እመቤቴ
ተጠብቃ ትኑር ካንቺ ዘንድ ሕይወቴ
የትኅትና ምንጭ የፍቅር ውቅያኖስ
ጠጥቼ ልርካብሸ ድንግል እንድፈወስ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 16 589 |
| 11 | ድንግል ሆይ
ድንግል ሆይ ወደኔ ትመጪ ዘንድ እንዴት ይሆናል
እመቤቴ ወደኔ ትመጪ ዘንድ እንዴት ይሆናል
ደካማ ነኝ እኔ ምግባር ይጎድለኛል/2/
አዝ
በሥጋዊ ሳይሆን በመንፈስ ዐይኖቼ
ለማየት እሻለሁ ከልቤ ጓጉቼ
ሥራዬ የከፋ መሆኑን አውቃለሁ
ስምሽንም መጥራት እጅግ እፈራለሁ
አዝ
ክብርሽ የበዛ ነው ቤዛዊተ ኵሉ
ምሕረት ታሰጫለሽ ላመነብሽ ሁሉ
ባንቺ የተመካ ምንም አያገኘው
የገሃነም እሳት ሲዖልም አይነካውም
አዝ
የልዑል ማደሪያ የሲና ዕፀ ጳጦስ
አንቺን ላመስግንሽ ከደዌ እንድፈወስ
ፍቀጂልኝ ድንግል ካንቺ ጋር እንድኖር
ልጅሽን ማልጂልኝ እንዲያበቃኝ ለክብር
አዝ
ምንም ተስፋ የለኝ ያላንቺ እናቴ
እመካብሻለሁ እስከ ዕለተ ሞቴ
የምስኪኖች አጽናኝ የጭንቅ ቀን ደራሽ
የልቤ ማረፊያ ምግብ መጠጤ ነሽ
አዝ
የጌታዬ እናት ድንግል እመቤቴ
ተጠብቃ ትኑር ካንቺ ዘንድ ሕይወቴ
የትኅትና ምንጭ የፍቅር ውቅያኖስ
ጠጥቼ ልርካብሸ ድንግል እንድፈወስ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 1 |
| 12 | ሐምሌ ፲ /10/
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሐምሌ ዐሥር በዚች ቀን ናትናኤል የተባለው ቅዱስ ሐዋርያ ስምዖን ቀለዮጳ በሰማዕትነት አረፈ ።
ይህንንም ሐዋርያ አይሁድ የጌታችንን ወንድም ያዕቆብን ከገደሉት በኋላ ለኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ አድርገው ሐዋርያት ሾሙት ። እርሱም ክብር ይግባውና ስለ ጌታችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ አስተምሮ ከአይሁድ ብዙዎችን ጌታችንን ወደማመን መለሳቸው ተአምራትንም አድርጎአልና በሽተኞችንም አድኗልና ።
ንጉሡ እንድርያስም ሴቶችን ከባሎቻቸው እንደሚለይ ንጽሕናቸውንም እንዲጠብቁ እንደሚአዝዛቸው ስለ እርሱ ሰማ ወደርሱም አስቀርቦ ጽኑ ሥቃይን አሠቃየው ማሠቃየቱንም በሰለቸ ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ ከእርሱም ጋር ቴዎና የምትባል አንዲት ድንግል ተገደለች ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት አባ ማቲያስና ከሁላችንም የክርስቲያን ወገኖች ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 18 880 |
| 13 | 1 ቀን ብቻ ቀረው
ብልሆች ይህ ኮርስ እንዲያመልጣቸው
አይፈልጉም ምክንያቱም በ2 ወራት ብቻ
ምንም Laptop ሳያስፈልግ
በስልካቸው ይህንን መሥራት እንደሚችሉ
ስለሚያውቁ 🤗
Video Editor ብቻ አይደለም የምናደርጋቹ
እሳት የላሰ Motion Designer ጭምር እንጅ 😊
ይህን ኮርስ ተምራቹ ስለ ሥራ ማጣት
ማሰብ የምታስቡት አይደለም ።
ለዚህ ነው እኛ ጋር ተማሩ የምንላቹ
ለዛውም ቤታቹ ሆናቹ
እጃቹ ላይ ባለው ስልክ ቤታቹ ሆናቹ
» ተማሩ
» ተሸለሙ
__________________________
✓ ሙያን መማር እንዲህ ቀላል
ሆኖ አያውቅም
✓ Capcut
✓ Alight Motion
✓ Inshot
✓ Kine Master
ሁሉንም አንድ ላይ
አሁኑኑ ተመዝገቡ
@greenbirdtechnology
_______________
Click Here For Details
.
.
.
@greenbirdtechs
@greenbirdtechs
የለውጥዎ ክንፍ 🔑 🐥 | 12 882 |
| 14 | ሐምሌ ፱ /9/
በዚች ቀን የአምስቱ አህጉር ኤጲስቆጶስ ቅዱስ ቴዎድሮስ በሰማዕትነት አረፈ። ዲዮቅልጥያኖስም በካደና ጣዖትን በአመለከ ጊዜ ምእመናንን ያሠቃዩአቸው ዘንድ መኳንንቱን ወደ ሀገሮች ሁሉ ላከ። ለጣዖትም እንዲሰግዱ ያስገድዷቸው ነበር።
ስሙ ፍላጦስ የሚባል አንድ መኰንንም ወደ አፍራቅያ አገር መጣ። በዚህም ቅዱስ ለክርስቲያን ወገን መምህር እንደ ሆነ ነገር ሠሩበት መኰንኑም ወደርሱ አስቀርቦ ለአማልክት እንዲሠዋ አዘዘው።
ቅዱሱም እንዲህ ብሎ መለሰለት ሰማይና ምድርን የፈጠረ አምላክን ትተን ጣዖት ማምለክ አይግባንም። መኰንኑም በውኑ አርጤምስንና አጵሎንን አርዳሚስንም ሌሎች አማልክትንም ያይላቸዋልን ሌላ ነውን አንተ ይምትናገርለት አምላክ ካለ እነዚህስ አማልክት አይደሉምን አለው። ቅዱስ ቴዎድሮስም መልሶ አዎን አማልክት አይደሉም ክብር ይግባውና ከአንድ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር አምላክ የለም እርሱም ለፍጥረቶች ሁሉ ፈጣሪያቸው ነው አለው።
መኰንኑም ኃይለ ቃል ስለመመለሱ ተቆጥቶ አርባ ቀን በግርፋትና በስቅላት በእሥራትና በመንኰራኲራት እንዲአሠቃዩት አዘዘ። እርሱ ግን ትእዛዙን አልሰማም ከሥቃዩም የተነሣ አልፈራም። ከዚህም በኋላ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ። በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጀ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን ለዘላለሙ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 20 618 |
| 15 | ዛሬ የቅዱስ ዳዊት መዝሙር ማብቂያ ጉባኤ አለን !
"መዝሙር 1 ብለን 150ውን መዝሙር በትርጓሜ እና በማብራሪያ እንድንማር የፈቀደ ልዑለ ባሕሪይ እግዚአብሔር ይመስገን።"
ስለ ቅዱስ ዳዊት ታሪክ እንነጋገራለን እና የመጨረሻችን ጉባኤ ነው ስለዚህ አትቅሩ።
መ/ር ነቢዩ ኤልያስ
ለመማር፦ https://t.me/Terha_Tsion | 10 353 |
| 16 | 视频消息 | 17 252 |
| 17 | 🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉
በያንጎ የጥሪ ቡፌ ቀረበላችሁ! 📢
ከአዲሱ Order Pool ጋር ምርጫው ሙሉ በሙሉ በእርስዎ እጅ ነው!
ጉዞውን ከመቀበልዎ በፊት መነሻውን፣ መድረሻውን እና ትርፉን አስቀድመው ማየት ይችላሉ።
የጥሪ ቡፌውን ይቃኙ፣ የፈለጉትን መርጠው ይውሰዱ! 📈
📲 አሁኑኑ የያንጎ ፕሮ መተግበሪያን ያውርዱ!
🔽🔽🔽ሊንኩን ይጫኑ🔽🔽🔽
https://ya.cc/t/3nVOkmT99fvrCa
ለበለጠ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ
💬 : https://t.me/YangoETH
❗️❗️❗️ | 17 364 |
| 18 | ፍቅርህ ማረከኝ
ፍቅርህ ማረከኝ በሕይወቴ በዘመኔ/2/
እግዚአብሔር ለእኔ መድሃኒቴ
ፍቅርህ ማረከኝ በህይወቴ በዘመኔ/2/
አዝ
ተገዝቻለሁ በወርቅ ደምህ
ዓለምን ትቼ ላገለግልህ
ሞትህ ህይወቴ ለእኔ ሆኖኛል
በአንተ መከራ ሸክሜ እርቋል
ለክብርህ ቆሜ እዘምራለሁ
እንደ አቅሜ አገንሃለሁ/2/
አዝ
ምድርና ሰማይ እልል ይበሉ
ምስጋና ለአንተ ይድረስ እያሉ
መሳይ የለህም ለቅድስናህ
አቀርባለሁኝ ለአንተ ምስጋና
ጣቴ በገና ይደረድራል
በቀን በሌሊት ያመስግናል/2/
አዝ
ክብርህን አይተው ጠላቶች ፈሩ
ለጌትነትህ ወድቀው ተገዙ
እንዲህ ነህ አምላክ እንዲህ ነህ ጌታ
ሁሉን በፍቅር የምትረታ
በአንተ ተመካሁ በፈጣሪያችን
አዳኝ በሆንከው በንጉሳችን/2/
ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 21 223 |
| 19 | ሐምሌ ፰ /8/
በዚች ቀን በጎ ስም አጠራር ያለው የአባ መቃርስ ገዳምና የዓለም ሁሉ ኮከብ የሆነው ቅዱስ አባት አባ ብሶይ አረፈ።
ይህም ቅዱስ ከግብጽ አገር ስሟ ሰነስ ከምትባል አገር ነበር ሰባት ወንድሞችም ነበሩት እናቱም የእግዚአብሔር መልአክ እግዚአብሔር ያገለግለኝ ዘንድ ከሰባቱ ልጆችሽ አንዱን ስጪኝ ብሎሻል እያለ እንደሚያነጋግራት ራዕይን አየች።
እርሷም ጌታዬ ሆይ የወደድከውን ውሰድ ሁሉም ገንዘቦቹ ናቸውና አለችው። መልአኩም እጁን ዘርግቶ የብሶይን ራስ ይዞ ለእግዚአብሔር መልካም ሥራ የሚሠራ ይህ ልጅ ነው አለ። ከዚህም በኋላ ከእርሷ በአደገም ጊዜ የምንኵስና ልብስ ሊለብስ ወደደ ። ወደ አስቄጥስም ገዳም ሔደ በአባ ባይሞይ ዘንድም መነኰሰ። ከዚህም በኋላ እጅግ ጽኑ የሆነ ተጋድሎን መጋደል ጀመረ ምንም ምን ሳይቀምስ አርባ ቀን እስከ መጨረሻው ሦስት ጊዜ ጾመ።
በቀንና በሌሊት በጾምና በጸሎት እየተጋ ቅዱሳት መጻሕፍትን አዘውትሮ በማንበብ በመጻሕፍት ቃል ነፍሱን ያረካት ነበር ። የእግዚአብሔርን ቃል እጅግ ይወድ ነበርና ከማር ከስኳርም እጅግ ይጥመው ነበርና በውኃ ዳርም እንዳለች ተክል ሆነ። ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስንም ያየው ዘንድ የተገባው ሆኖ ነበር ጌታችንም ብዙ ጊዜ ይገለጽለት ነበር።
ከእርሱም ጋራ ይነጋገር ነበር። እርሱም እግሩን አጥቦ እጣቢውን ይጠጣው ነበር። እግዚአብሔርን አገልግሎአምሳ ሰባት አመት ኑሮ አረፈ። ከሥጋውም ብዙዎች ድንቆችና ተአምራቶች ተገለጡ በአስቄጥስም ገዳም እየተጋደለ ሀያ ሰባት ዓመት ኖረ። በእንዴናው ገዳም ዐሥር ዓመት ኖረ ከመመንኰሱም በፊት በዓለም ውስጥ ሃያ ዓመት ተቀመጠ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 19 968 |
| 20 | ሥላሴ መታመኛዬ
ሥላሴ መታመኛዬ
አምላኬ መጠለያዬ/2/
ጉልበቴ ነህ ማሸነፍያዬ
ሥላሴ መታመኛዬ
አዝ
ጠፈሩም እርሱ መሠረቱም እርሱ
ፍጥረታት በሙሉ ስሙን አውድሱ
ሱራፌልን ልክህ ከንፋሮቼን ዳሰኝ
ለምፄን ተመልክተህ አምላክ አትጣለኝ
ለምፄን ተመልክተህ ጌታዬ አትጣለኝ
አዝ
እንዴት ያለ አንደበት ስምህን ይጠራል
ግርማህን አይቼ ልቤ ተሸብሯል
ኦዝያን አለፈ ክፋት እጅግ በዝቶ
አምላኬን አየሁት በዙፋኑ ፀንቶ/2/
አዝ
አልአዛር ያንተ ነው መንገድ የወደቀ
ከእጅ ያላመለጠ ነዌ ባለፀጋ
ንገሥታትም ያንተ በሥልጣን ያሉት
ለስምህ ይንበርከክ ይህ ሁሉ ፍጥረት/2/
አዝ
በድቅድቅ ጨለማ ተስፋ በሌለበት
ብርሃን ሆኖ አየሁት የጌታዬን ምሕረት
ኃይል ማሸነፍን ጽናትንም ስጠኝ
ጠላት እንዳይጥለኝ ፀጋህን አልብሰኝ/2/
ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 22 063 |
