ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን። YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8 Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR
显示更多📈 Telegram 频道 ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit 的分析概览
频道 ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit (@ortodoxmezmur) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 169 182 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 141,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 140 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 169 182 名订阅者。
根据 04 九月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 922,过去 24 小时变化为 32,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 11.81%。内容发布后 24 小时内通常能获得 6.20% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 19 974 次浏览,首日通常累积 10 484 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 112。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ።
ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን።
YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8
Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR”
凭借高频更新(最新数据采集于 05 九月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
数据加载中...
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 05 九月 | +20 | |||
| 04 九月 | +43 | |||
| 03 九月 | +14 | |||
| 02 九月 | +9 | |||
| 01 九月 | +3 |
ነሐሴ ፴ /30/በዚህች ዕለት ከዐሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ የሆነው ታላቁ ነቢይ ሚልክያስ አረፈ። እግዚአብሔር አምላክ በነቢዩ አንደበት አድሮ እንዲህ ይለናል። ሰው እግዚአብሔርን ይሰርቃልን? እናንተ ግን እኔን ሰርቃችኋል። እናንተም። የሰረቅንህ በምንድር ነው? ብላችኋል። በአሥራትና በበኵራት ነው። ትንቢተ ሚልክያስ 3:8 እንዴት አድርጌ ነው ከ5ሺህ ብር ደሞዝ በዛ ላይ የኑሮ ውድነቱ ተጨምሮበት አስራት የማወጣው? ብላችሁ ብትጠይቁም እግዚአብሔር በነቢዩ አድሮ እንዲህ ይለናል። በቤቴ ውስጥ መብል እንዲሆን አሥራቱን ሁሉ ወደ ጎተራ አግቡ፤ የሰማይንም መስኮት ባልከፍትላችሁ፥ በረከትንም አትረፍርፌ ባላፈስላችሁ በዚህ ፈትኑኝ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። ትንቢተ ሚልክያስ 3:10 ቅዱስ ሚልክያስም በበጎ ተጋድሎው እግዚአብሔርን ከአገለገለ በኋላ በዛሬዋ ዕለት ከዚህ ዓለም በመፍለስ በሰላም አረፈ። ሚልክያስ ማለት መልዐክ አንድም የተላከ ማለት ነው። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
| 2 | በስምህ ታምኛለሁ
በስምህ ታምኛለሁ እንዳትተወኝ
ለሚያሳድደኝ ጠላት ለሞት አትስጠኝ
ፀጥታዬ ነህ ጌታ ሰላም ዕረፍቴ
ጉዞዬን አንተ አቅናልኝ ቅደም ከፊቴ
አዝ
በለስም ባታፈራ ዘይትም ባይኖር
የህሊና ሰላም አለኝ ካንተ ጋር ስኖር
በአባቶቼ በረከት የባረከኝ
የእስራኤል ታዳጊያቸው ክበርልኝ
ዘላለም ተመስገን ከፍ በልልኝ
አዝ
የፈተናዬ መውጫ መልሴ ነህ አንተ
ጨለማውን አሻግረኝ እልፍኙን ከፍተህ
ስታፅናናኝ ኖሬአለሁ ለብዙ ዘመን
ተገፍቶ መች ይወድቃል በአንተ የሚታመን
አይሞትም ይኖራል በአንተ የሚታመን
አዝ
ይቅርታና ምህረትህ እነሱ ይምሩኝ
ወጥመድና እንቅፋቱ እንዳያደክሙኝ
በጽድቅህ ሀሴት ላድርግ በአንተ ልበርታ
መተከዝ ማልቀስ ይብቃኝ አፅናናኝ ጌታ
ተነግሮ አያልቅም የአምላኬ ውለታ
ዘማሪት ጽጌረዳ ጥላሁን
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 10 233 |
| 3 | ነሐሴ ፳፱ /29/
በዚህች ዕለት በትሕትናው፣ በትዕግስቱ ይበልጡንም ደግሞ በመታዘዙ የሚታወቀው አባት ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር የፍልሰቱ ዕለት ናት።
በአንድ ወቅት አባ ባይሞይ ቅዱስ ዮሐንስን ጠራውና ተፈልጦ የወደቀ ደረቅ እንጨት ሠጠው ከዚያም "ትከለውና እንዲያፈራ አድርገው። ከዚያ አምጥተህ አብላኝ" አለው። ይህ ነገር ከተፈጥሮ ሥርዓት ውጪ መሆኑን እያወቀ ቅዱስ ዮሐንስ "እሺ" ብሎ ወስዶ ተከለው። ከ10ኪ.ሜ በላይ እየተጓዘ ወሃ እየቀዳ ለ2 ዓመታት ሳይታክት አጠጣው። በሦስተኛው ዓመት ግን ለመለመ ወስዶም ለመምህሩ "አባቴ እንካ ብላ " ብሎ ሰጠው።
መምህሩም ወዲያው ያን ፍሬ ታቅፎ ወስዶ ለገዳሙ መነኮሳት:- "ንሱ ብሉ: በረከትንም አግኙ:: ይህ የዛፍ ሳይሆን የመታዘዝ ፍሬ ነው አላቸው::"
ቁመቱ እጅግ ያጠረ: ጽድቁ ግን ከሰማይ የደረሰ ቅዱስ ዮሐንስን ሰላም ሰላም እንለዋለን።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን: እኛንም በዚህ የጻድቅ ጸሎት ይማረን። በረከቱም ትድረሰን: ለዘላለሙ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚@ortodoxmezmur💚
💛@ortodoxmezmur💛
❤️@ortodoxmezmur❤️ | 11 212 |
| 4 | እንደምትወደኝአውቀዋለሁ
እንደምትወደኝ አውቀዋለው እንደማትተወኝ
ማረኝ ይቅር በለኝና ያንተ አድርገኝ/2/
አዝ
ብሄድ ብርቅ ተለይቼ
ንፁ ፍቅርን እረስቼ
ጌታዬ ነህና አባቴ
ራርተህ መልሰኝ ከቤቴ /2/
አዝ
ምንም ብሆን በደለኛ
ብበድልህም ዳግመኛ
ጌታ ሞቴን አትፈልግም
አንተ ፍቅር ነህ ዘላለም /2/
አዝ
ከመንጋው ወጥቼ ብጣል
በድካም በኃጢያት ብዝል
የቀድሞ ትጋቴን ስጠኝ
ፅናትና ብርታት ሁነኝ /2/
አዝ
ቅዱስ ስጋህን ቆርሰህ
ክቡር ደምህን አፍሰህ
ሞተህ ህይወት የሰጠኸኝ
አንተ ፈጥረህ የምትገዛኝ /2/
ሊቀ መዘምራን ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 13 847 |
| 5 | ከዘመናት በፊት
ከዘመናት በፊት አንተ ነበርክ
ሁሉን አሳልፈህ ትኖራለህ
እምቅደመ ዘመናት ዘመናዊ
ድህረ ዘመን ሃዲስ ኢየሱስ ናዝራዊ/2/
አዝ
ክብርህ ገናና ነው ባንተ ከብሬያለሁ
ዘላለማዊ ነው ባንተ እኖራለሁ
በሰልፉ መካከል አለህ ከእኔ ጋራ
የሰራዊት ጌታ እፁብ የአንተ ስራ
አዝ
ከላይ ከአርያም ከዙፋንህ ግርማ
ቅዱስ አለ ኪሩብ ምስጋናው ተሰማ
ውዳሴ ከበበው መንበሩን እልልታ
ባሪያህ ላመስግንህ ፍቀድልኝ ጌታ
አዝ
የአማልክት አምላክ የሚመስልህ የለም
አይኔ ያየው ሁሉ ያላንተ አልሆነም
አይኔ ያየው ገንዘብህ ነውና
አልፋና ኦሜጋ ይድረስህ ምስጋና
አዝ
የምድር ኃያላን አይቆሙም ከፊትህ
ይህን ሰራህ ብሎ የለም የሚወቅስህ
ሰማይ እና ምድርን ፈጥረህ የምትገዛ
እናመልክሃለን የህይወታችን ቤዛ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 15 905 |
| 6 | ነሐሴ ፳፯ /27/
በዚችም ቀን በሊቀ ካህናት ኤሊ ዘመን ነቢይ ሳሙኤል ለመጠራቱ መታሰቢያ ሆነ። ይህንንም ነቢይ ተኝቶ ሳለ እግዚአብሔር ጠራው በኤሊም ፈንታ ነቢይና ካህን አድርጎ ለእስራኤል ልጆች ሾመው በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
በዚችም ቀን የእስክንድራዊ ፊቅጦርና የእናቱ ሣራ መታሰቢያቸው ነው በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
በዚችም ቀን ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አራተኛ የሆነ የመላእክት አለቃ የሱርያል የበዓሉ መታሰቢያ ነው ። አማላጅነቱም ከኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን።
በዚችም ቀን ዳግመኛ አባቶቻችን ዐሥራ ሁለቱን የያዕቆብን ልጆች ያስቧቸዋል ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በረከታቸውም ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 15 410 |
| 7 | ☦️የሮሜ መልእክት የመጨረሻው ማብራሪያ ይሰጣል ☦️
✔️መ/ር ነቢዩ ኤልያስ
Telgram ፦ https://t.me/Terha_Tsion
Youtube፦ https://youtube.com/@tserhatsion?si=qh_eLZt0L3sAkacr | 14 482 |
| 8 | ደጅሽ ላይ ቆሜ
ደጅሽ ላይ ቆሜ ስለምንሽ
ባርኪኝ እናቴ ማርያም ስልሽ
ተደላደለልኝ ህይወቴ
በአንቺ በእናቴ በእመቤቴ
አዝ
እንቺ በመሆንሽ የሕይወቴ ፋና
አልፈራም ጨለማ ብርሃን አለኝና
አይጠፋም ዘላለም ፍቅርሽ ከአንደበቴ
አለ በደሜ ውስጥ ፍቅርሽ በሕይወቴ
አልቀርም ደጅሽ ለዘላለም /2/
ከአንቺ የሚለየኝ ማንም የለም /2/
አዝ
እጅግ የተገፋ ደካማ ሰው አለ
መቅደስሽ የቆመ አማልጂኝ እያለ
ይቁም ይሄ ልጅሽ ሃዘን የሰበረው
ከአንቺ በቀር ወገን መጠጊያ የሌለው
ያነሳው ኪዳንሽ ከውድቀቱ/2/
ያርግ በእጆሽ ያ ፀሎቱ/2/
አዝ
ፅልመት የለበሰ ፈታኝ ያደከመኝ
የምቋቋምበት ጉልበት አስፈለገኝ
በርትቼ እንድጸና ሳትጎዳ ነፍሴ
ሁኚኝ እናቴ ሆይ ግርማዬ ሞገሴ
ልፅና ደግፊኝ እመቤቴ/2/
ይውለቅ ከእጄ ላይ ሰንሰለቴ/2/
አዝ
አበው የለበሱሽ የክብራቸው ካባ
መአዛሽ የሚስብ የሮማን አበባ
ለውጪው በምልጃሽ የሕይወቴን ቃና
ባዶ ጋኔን ምልጃሽ ወይን ያስሞላውና
አፅጂልኝ በእጅሽ ማድጋዬን/2/
በወይን አስሞይው እንስራዬን/2/
ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 16 746 |
| 9 | ነሐሴ ፳፮ /26/
በዚችም ቀን ለአብርሃም ሚስት ለተመሰገነች ሣራ መታሰቢያዋን እናደርግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አባቶች አዘዙ።
ይቺንም ክብርተ ማሕፀን የሆነች ጡቶቿም የተባረኩ ክብርት ሣራን የጌራራ ንጉሥ አቤሜሌክ ባል እንዳላት ሳያውቅ በወሰዳት ጊዜ እንዳይቀርባት እግዚአብሔር ገሠጸው በደዌም ቀሠፈው ባሏ አብርሃምም በጸለየለት ጊዜ ከደዌው ተፈወሰ ከዚህም በኋላ ከብዙ ገንዘብ ጋራ ወደ ባሏ መለሳት።
ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር በሦስትነቱ ተገልጦ ወደ ቤቷ እንግድነት በመጣ ጊዜ ለአብርሃምም የይስሐቅን መወለድ በነገረው ጊዜ ሣራም በድንኳኑ ውስጥ ሳቀች እንዲህ ስትል እስከ ዛሬ ገና ነኝን ጌታዬም አርጅቷል።
እግዚአብሔርም አብርሃምን እንዲህ አለው ሣራን ለብቻዋ ምን አሳቃት እስከ ዛሬ ገና ነኝን ጌታዬም አርጅቷል እኔም አሁን አርጅቻለሁ ብላ በውኑ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር አለን። ከዚህም በኋላ ሣራ ፀንሳ እግዚአብሔር ባለው ወራት በርጅናዋ ለአብርሃም ወንድ ልጅን ወለደች።
ከዚህም በኋላ በበጎ እርጅና በአረፈች ጊዜ ከኬጢያዊ ኤሞርልጆች በገዛው ቦታ ቀበራት።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበረች እናታችን ሣራ በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 17 881 |
| 10 | በብዙ አገራት እንዳይታተሙ ታግደው የነበሩ፣ አነጋጋሪና አደገኛ ምስጢራትን የያዙ ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፎች በPdf የሚገኙበትን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ!
👇👇
@Bemnet_Library 📚
@Bemnet_Library 📚 | 10 668 |
| 11 | ያየኽብኝን ያላሳየኽብኝ
ያየኽብኝን ያላሳየኽብኝ
ደግሞም በደሌን የረሳኽልኝ
አስገረመኝ ለእኔ ያለህ
አስደመመኝ ለእኔ ያለህ
ብበድልህ /4/ እየቻለኝ ያ ትከሻህ
አዝ
እጄን በአፌ እያስጫነ አስገረመኝ ደጉ ልብህ ፊትህ አይጠቁር በኃጢአቴ እንዳላየህ ታልፈዋለህ
ሳታሳጣኝ በሰው መሐል የእኔ ከዳኝ የልቤ ጥግ
አላነስኩም ካየኽልኝ ከከፍታህ ከዚያ ማዕረግ
አዝ
በእርሱ ምሕረት ከድቅድቁ ከወጣሁኝ ከጨለማ
ለይሁዳ ክፉ ወሬ ልቤ አይሰጋ ለዓለም ዜማ
በነበልባል ሲያቃጥለኝ የስምዖን አንደበቱ
የእሳት ልሳን ሆነኽልኝ በአንተ አለፈ ያ ክረምቱ
አዝ
ከበለስ ሥር የሠራሁት ዓለም ተፍቶ ያቃለለው
ረሳሁት ትቼዋለሁ እንዳንተ ያለኝ ከቶ ማነው
ሰው ሲሸሸኝ የቀረብከኝ አንተ እኮ ነህ መድኃኒቴ
ዐይንህ ዐይቶኝ መች አለፍከኝ አነሳኸኝ ቸር አባቴ
አዝ
መክሮ መክሮ ሲታክተው ውጣ ብሎ እየጣለ
ስንቱ አለፈ በመከራ ሰው ወገኑን ስላልቻለ
የኔ ጌታ ፍቅሩ ችሎኝ ሰፊው ክንዱ አሻገረኝ
ለውለታው ከእንባ በላይ የሚያረካው ምን ቃል አለኝ
ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 20 531 |
| 12 | ዛሬ [ ሰኞ ] ምሽት 2:00 እንገናኝ
12ኛው ዙር Graphics Design ሥልጠና ላይ
Day 1 + 2 + 3 ኮርስ በነጻ እንድትከታተሉ
ተጋብዛችኋል 🎉
ቀድማቹ ማወቅ ያለባችሁን እና
ከየት ወደየት መሄድ እንደምትችሉ ጥንቅቅ
አድርገን እናሳያችኋለን ።
@greenbirdtechnology ላይ
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
« I want to attend Day 1+2+3 of
Graphics Design Course »
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ብላቹ ለምትልኩልን link እንሰጣችኋለን
___________________________
@greenbirdtechs
@greenbirdtechs
የለውጥዎ ክንፍ 🔑 🐥 | 17 308 |
| 13 | ነሐሴ ፳፭ /25/
በዚችም ቀን ቅዱሱ አባት አባ ቢጻርዮን አረፈ። የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ምእመናን ነበሩ። በአደገም ጊዜ የምንኵስና ልብስን ለብሶ እግዚአብሔርን ሊአገለግል ወደደ ዓለምንም ንቆ ወደ ኣባ እንጦንስ ሔደ ለእርሱም ደቀ መዝሙር ሆኖ ብዙ ዘመናት አገለገለው።
ከዚህም በኃላ ወደ አባ መቃርስ ሒዶ ቅዱሳን አረጋውያን መነኰሳትንም አገለገላቸው። በአስቄጥስም ገዳም ይዘዋወር ነበር በቤት ውስጥም አያድርም ነበር ። አባቶችም ጭንቅ የነበረ ተጋድሎውን ስለርሱ ይናገሩ ነበር። እርሱ አርባ መዓልትና አርባ ሌሊት ከቶ ሳይተኛ ቁሞ ኖሮአልና።
በምንኩስናውም ወራት ብዙ ጊዜ በየአርባ ቀን ጾመ እነሆ እንዲህ እየተጋደለ ድንቆችንም እያደረገ ኀምሳ ሰባት ዓመታት ኖረ። ቅዱሳን አባ ዱላስና አባ ዮሐንስም ከተአምራቱ ተናገሩ እነርሱ ከርሱ ጋር ወደ ኤርትራ ባሕር ዳርቻ ሔዱ። እጅግም በተጠሙ ጊዜ እንደተጠሙ አውቆ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ መራራውንም ውኃ ጣፋጭአድርጎላቸው ጠጥተዋል።
የዚህም ቅዱስ ተአምራቶቹ ከነገርናችሁ የበዙ ናቸው እግዚአብሔርንም አገልገሎ በሰላም አረፈ ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ጻድቅ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 16 917 |
| 14 | በነጻ 🤗
ነገ ሰኞ ምሽት 2:00 በሚጀመረው 12ኛው
ዙር Graphics Design ሥልጠና ላይ
Day 1 + 2 + 3 ኮርስ በነጻ እንድትከታተሉ
ተጋብዛችኋል 🎉
ቀድማቹ ማወቅ ያለባችሁን እና
ከየት ወደየት መሄድ እንደምትችሉ ጥንቅቅ
አድርገን እናሳያችኋለን ።
@greenbirdtechnology ላይ
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
« I want to attend Day 1+2+3 of Graphics Design Course »
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ብላቹ ለምትልኩልን link እንሰጣችኋለን
___________________________
@greenbirdtechs
@greenbirdtechs
የለውጥዎ ክንፍ 🔑 🐥 | 6 783 |
| 15 | ቁጥርህ ከመላእክት
ቁጥርህ ከመላእክት ተስተካክሏል
ከኪሩቤል መሐል ገብተህ አጥነሃል
ተክለሃይማኖት በጸሎትህ
ብዙ ድውያን ፈውሰሃል
አዝ
ባሕር ሳያሰጥመን ደርሶልን
አለፍን በደረቅ ከፍሎልን
ኢትዮጵያዊው ሙሴ ተክለሃይማኖት
የሚሳነው የለም በሃይማኖት
አዝ
ጸሎቱ ምህላው ቅዳሴው
ገብቷል ከቤታችን መዓዛው
ጸጋ በረከትህ በዝቶልናል
በአማላጅነትህ ተምረናል
አዝ
ድካም በሌለበት በምስጋና
አምላኩን ያከብራል በትህትና
ስለ እኛም ዝም አይልም ይማጸናል
የአባታችን አምላክ ይሰማናል
አዝ
ዘመናችን ሲረክስ መንገዳችን
ፈጥኖ ደረሰልን አባታችን
ተክለሃይማኖት እርዳን ልጆችህን
አታርቀው ከእኛ ኪዳንህን
ዘማሪት ጸዳለ ጎበዜ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 20 276 |
| 16 | እንኳን ለታላቁ ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ
ልደት
መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ ጸጋ ዘአብ ካህኑና እግዚእ ኃረያ ናቸው። እርሱ በክህነቱ እርሷ በደግነቷ በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል።
በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ ቢደርስባቸው ቅዱስ ሚካኤል ጸጋ ዘአብን ከሞት እግዚእ ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል። በሁዋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል።
ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የጸነሱት መጋቢት 24 ቀን በ1206 ዓ/ም ሲሆን የተወለዱት ደግሞ ታሕሳስ 24 ቀን በ1207 ዓ/ም ነው። በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል። ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል።
ዕድገት
የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው "ፍሥሃ ጽዮን" ይሰኛል። ይሕንን ስም ይዘው አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው አድገዋል። በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን (ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል። በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል። ዲቁናም ከወቅቱ ዻዻስ አባ ጌርሎስ ተቀብለዋል።
መጠራት
አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮስ ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ።
የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ። "ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን። ከዚህ በሁዋላ አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ። ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ በግርማ ዐረገ። ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በሁዋላ ሰዓትን አላጠፉም። ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ።
አገልግሎት
ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል አገልግሎትን ጀመሩ። በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ። ያን ጊዜ ኢትዮዽያ 2 መልክ ነበራት።
1ኛ. ዮዲት (ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል ወይም በባዕድ አምልኮ ተጠምዷል።
2ኛው. ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር።
ግማሹ ሃገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ። ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን (ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል::
ገዳማዊ ሕይወት
ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል። እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል።
እነዚህም በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት: በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ ዳሞ ከአቡነ ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26 ዓመታት አገልግለዋል።
በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በሁዋላም ወደ ምድረ ሽዋ (ዞረሬ) ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል። በተሰበረ እግራቸውም 6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል።
ስድስት ክንፍ
ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት ተባርከዋል። ጻድቁ ምድረ እሥራኤል የገቡት በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር::
የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሚካኤል ጋርም ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል። ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ በሁዋላ ነው ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር።
ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም። በገሃድ:-
-በቤተ መቅደስ ብስራቱን
-በቤተ ልሔም ልደቱን
-በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን
-በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን
-በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር።
የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደ ሆነው ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ። በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ እመቤታችን ድንግል ማርያም ፈጥና ደርሳ ተክልየን ወደ ሰማይ አሳረገቻቸው።
በዚያም :-
-የብርሃን ዐይን ተቀብለው
-6 ክንፍ አብቅለው
-የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው
-ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው
-ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው
-ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው
-"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል።
ተአምራት
የተክልየ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው።
ሙት አንስተዋል
ድውያንን ፈውሰዋል
አጋንንትን አሳደዋል
እሳትን ጨብጠዋል
በክንፍ በረዋል
ደመናን ዙፋን አድርገዋል።
ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን መሥርተዋል። በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት አብረው ኑረዋል። በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና::
ዕረፍት
ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: እልፍ አእላፍ ፍሬን አፍርተው: በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24 ቀን በ1306 ዓ/ም ዐርፈዋል።
ጌታ: ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል። 10 ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል።
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 19 865 |
| 17 | ነሐሴ ፳፬ /24/
በዚች ቀን የክርስቶስ ምስክሩና ሐዋርያው የሆነ የመርዓስ ኤጲስቆጶስ ተጋዳይ ቅዱስ አባት ቶማስ አረፈ። ይህም አባት የመርዓስ አገር ኤጲስቆጶስ ነበር። በከሀዲ ዲዮቅልጥያኖስም ዘመን ይህን አባት መኳንንት እየደበደቡት ወሰዱት።
ከዚህም በኃላ መኮንኑ ቅዱስ ቶማስን ለአማልክት ስገድ አለው ቅዱሱም ለጣዖት እንደማይሰግድ ነገረው። በዚህም በብዙ አሰቃዩት። ከዚህም በኋላ በጨለማ ቦታ ጣሉት በዚያም ሃያ ሁለት ዓመት ኖረ። በዚያም አካላቱን ይቆርጡት ነበር። መንጋዎቹም ያረፈ መስሏቸው በየዓመቱ መታሰቢያውን ሲያደርጉ ኖሩ። ነገር ግን አንዲት ሴት አይታው ስለነበር በድብቅ ትመግበው ነበር።
ጻድቅ ቁስጠንጢኖስም እስከ ነገሠና የቀናች የክርስቶስን ሃይማኖት ክብር እስከ ገለጠ ድረስ እንዲህ ሲሠቃይ ኖረ። ይቺም ሴትስለ ቅዱሱ ለካህናቱ ነገረቻቸው በውስጡ ወደሚኖርበትም ቦታ መራቻቸው። እነርሱም አንሥተው ተሸከሙት እየዘመሩና እያመሰገኑ ወደ ቤተ ክርስቲያን አደረሱት በቤተ መቅደሱም ፊት ለፊት በወንበሩ ላይ አስቀመጡት ምእመናንም ሁሉ ወደርሱ እየመጡ ከእርሱ ይባረኩና የተቆረጡ ሕዋሳቱን ይሳለሙ ነበር።
ይህም ቅዱስ ከ318ቱ ሊቃውንት አንዱ ነው። ንጉሱም ስለ ቅዱሱ በሰማ ጊዜ ሰገደለት። ከዚህም በኃላ ቅዱስ ቶማስ ወደ መንበረ ሢመቱ ሔደ ካህናቱንና መንጋዎቹን ሁሉ ሰብስቦ አነበበላቸው እርሱንም እንዲአስተውሉት እንዲጠብቁትም በመጠበቅም እንዲጸኑ አዘዛቸው።
ጥቂት ዘመናትም ከኖረ በኃላ በሰላም በፍቅር አረፈ የሹመቱም ዘመን አርባ ዓመት ነው በዚህም እግዚአብሔርን አገለገለው።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 17 528 |
| 18 | ፀሐይ ዘልዳ ጊዮርጊስ
እምነ ሠናይት ኩሉ እለ ውስተ ባሕር ወየብስ/2/
ሶበ ነጸርኩ በኃሢሥ ዘከማከ አልቦ ጊዮርጊስ/2/
አዝ
የመከራን ገፈት ቀምሳ ለሰጠችህ
ልጅ ሆነሀልና ለማርያም እናትህ
ስምዐ ክርስቶስ አርዓያ ሰማዕታት
ሆነህ የተሰየምህ የሰማዕታት አባት
አዝ
የገድልህን ነገር ጆሮአችን ሲሰማ
ልባችን ይቀልጣል በጽናትህ ዜና
የጌታህን ትእግስት ቀራንዮን እያሰብክ
በወጣትነትህ ተጋድሎህን ፈጸምክ
አዝ
በጭንቅ መከራ ጽናትህ ሲፈተን
ከአምላክ ተምረህ ቁጣ ሳትናገር
ሁሉን ስለጌታ ችለህ ታግሰሀል
የብርሃን አክሊልን በሰማይ ደፍተሃል
አዝ
ሥዕለ ገጽህን ዘወትር እያየን
ነገረ ገድልህን ሁልጊዜ እያደነቅን
ፍቅርህ በልባችን ስለተሣለብን
ይኸው እንዘምራለን ጊዮርጊስ እያልን
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 21 636 |
| 19 | ነሐሴ ፳፫ /23/
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ነሐሴ ሃያ ሦስት በዚችም ቀን ቅዱስ ድምያኖስ በሰማዕትነት አረፈ።
ይህንንም ቅዱስ የአንጾኪያ አገርመኰንን ብዙ ወራት አሠቃየው ከማሠቃየትም በሰለቸ ጊዜ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ።
በረከቱ ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 20 581 |
| 20 | በብዙ አገራት እንዳይታተሙ ታግደው የነበሩ፣ አነጋጋሪና አደገኛ ምስጢራትን የያዙ ኦርቶዶክሳዊ እና ዓለም አቀፍ መጽሐፎች በPdf የሚገኙበትን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ!
👇👇
@Bemnet_Library 📚
@Bemnet_Library 📚 | 11 200 |
