ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን። YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8 Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit
کانال ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit (@ortodoxmezmur) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 169 141 مشترک است و جایگاه 141 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 141 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 169 141 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 02 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 914 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 5 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 12.32% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 6.30% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 20 837 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 10 651 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 122 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ።
ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን።
YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8
Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 03 سپتامبر, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 03 سپتامبر | +14 | |||
| 02 سپتامبر | +9 | |||
| 01 سپتامبر | +3 |
አዝብሄድ ብርቅ ተለይቼ ንፁ ፍቅርን እረስቼ ጌታዬ ነህና አባቴ ራርተህ መልሰኝ ከቤቴ /2/
አዝምንም ብሆን በደለኛ ብበድልህም ዳግመኛ ጌታ ሞቴን አትፈልግም አንተ ፍቅር ነህ ዘላለም /2/
አዝከመንጋው ወጥቼ ብጣል በድካም በኃጢያት ብዝል የቀድሞ ትጋቴን ስጠኝ ፅናትና ብርታት ሁነኝ /2/
አዝቅዱስ ስጋህን ቆርሰህ ክቡር ደምህን አፍሰህ ሞተህ ህይወት የሰጠኸኝ አንተ ፈጥረህ የምትገዛኝ /2/ ሊቀ መዘምራን ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
| 2 | ከዘመናት በፊት
ከዘመናት በፊት አንተ ነበርክ
ሁሉን አሳልፈህ ትኖራለህ
እምቅደመ ዘመናት ዘመናዊ
ድህረ ዘመን ሃዲስ ኢየሱስ ናዝራዊ/2/
አዝ
ክብርህ ገናና ነው ባንተ ከብሬያለሁ
ዘላለማዊ ነው ባንተ እኖራለሁ
በሰልፉ መካከል አለህ ከእኔ ጋራ
የሰራዊት ጌታ እፁብ የአንተ ስራ
አዝ
ከላይ ከአርያም ከዙፋንህ ግርማ
ቅዱስ አለ ኪሩብ ምስጋናው ተሰማ
ውዳሴ ከበበው መንበሩን እልልታ
ባሪያህ ላመስግንህ ፍቀድልኝ ጌታ
አዝ
የአማልክት አምላክ የሚመስልህ የለም
አይኔ ያየው ሁሉ ያላንተ አልሆነም
አይኔ ያየው ገንዘብህ ነውና
አልፋና ኦሜጋ ይድረስህ ምስጋና
አዝ
የምድር ኃያላን አይቆሙም ከፊትህ
ይህን ሰራህ ብሎ የለም የሚወቅስህ
ሰማይ እና ምድርን ፈጥረህ የምትገዛ
እናመልክሃለን የህይወታችን ቤዛ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 12 448 |
| 3 | ነሐሴ ፳፯ /27/
በዚችም ቀን በሊቀ ካህናት ኤሊ ዘመን ነቢይ ሳሙኤል ለመጠራቱ መታሰቢያ ሆነ። ይህንንም ነቢይ ተኝቶ ሳለ እግዚአብሔር ጠራው በኤሊም ፈንታ ነቢይና ካህን አድርጎ ለእስራኤል ልጆች ሾመው በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
በዚችም ቀን የእስክንድራዊ ፊቅጦርና የእናቱ ሣራ መታሰቢያቸው ነው በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
በዚችም ቀን ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አራተኛ የሆነ የመላእክት አለቃ የሱርያል የበዓሉ መታሰቢያ ነው ። አማላጅነቱም ከኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን።
በዚችም ቀን ዳግመኛ አባቶቻችን ዐሥራ ሁለቱን የያዕቆብን ልጆች ያስቧቸዋል ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በረከታቸውም ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 13 021 |
| 4 | ☦️የሮሜ መልእክት የመጨረሻው ማብራሪያ ይሰጣል ☦️
✔️መ/ር ነቢዩ ኤልያስ
Telgram ፦ https://t.me/Terha_Tsion
Youtube፦ https://youtube.com/@tserhatsion?si=qh_eLZt0L3sAkacr | 12 785 |
| 5 | ደጅሽ ላይ ቆሜ
ደጅሽ ላይ ቆሜ ስለምንሽ
ባርኪኝ እናቴ ማርያም ስልሽ
ተደላደለልኝ ህይወቴ
በአንቺ በእናቴ በእመቤቴ
አዝ
እንቺ በመሆንሽ የሕይወቴ ፋና
አልፈራም ጨለማ ብርሃን አለኝና
አይጠፋም ዘላለም ፍቅርሽ ከአንደበቴ
አለ በደሜ ውስጥ ፍቅርሽ በሕይወቴ
አልቀርም ደጅሽ ለዘላለም /2/
ከአንቺ የሚለየኝ ማንም የለም /2/
አዝ
እጅግ የተገፋ ደካማ ሰው አለ
መቅደስሽ የቆመ አማልጂኝ እያለ
ይቁም ይሄ ልጅሽ ሃዘን የሰበረው
ከአንቺ በቀር ወገን መጠጊያ የሌለው
ያነሳው ኪዳንሽ ከውድቀቱ/2/
ያርግ በእጆሽ ያ ፀሎቱ/2/
አዝ
ፅልመት የለበሰ ፈታኝ ያደከመኝ
የምቋቋምበት ጉልበት አስፈለገኝ
በርትቼ እንድጸና ሳትጎዳ ነፍሴ
ሁኚኝ እናቴ ሆይ ግርማዬ ሞገሴ
ልፅና ደግፊኝ እመቤቴ/2/
ይውለቅ ከእጄ ላይ ሰንሰለቴ/2/
አዝ
አበው የለበሱሽ የክብራቸው ካባ
መአዛሽ የሚስብ የሮማን አበባ
ለውጪው በምልጃሽ የሕይወቴን ቃና
ባዶ ጋኔን ምልጃሽ ወይን ያስሞላውና
አፅጂልኝ በእጅሽ ማድጋዬን/2/
በወይን አስሞይው እንስራዬን/2/
ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 14 452 |
| 6 | ነሐሴ ፳፮ /26/
በዚችም ቀን ለአብርሃም ሚስት ለተመሰገነች ሣራ መታሰቢያዋን እናደርግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አባቶች አዘዙ።
ይቺንም ክብርተ ማሕፀን የሆነች ጡቶቿም የተባረኩ ክብርት ሣራን የጌራራ ንጉሥ አቤሜሌክ ባል እንዳላት ሳያውቅ በወሰዳት ጊዜ እንዳይቀርባት እግዚአብሔር ገሠጸው በደዌም ቀሠፈው ባሏ አብርሃምም በጸለየለት ጊዜ ከደዌው ተፈወሰ ከዚህም በኋላ ከብዙ ገንዘብ ጋራ ወደ ባሏ መለሳት።
ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር በሦስትነቱ ተገልጦ ወደ ቤቷ እንግድነት በመጣ ጊዜ ለአብርሃምም የይስሐቅን መወለድ በነገረው ጊዜ ሣራም በድንኳኑ ውስጥ ሳቀች እንዲህ ስትል እስከ ዛሬ ገና ነኝን ጌታዬም አርጅቷል።
እግዚአብሔርም አብርሃምን እንዲህ አለው ሣራን ለብቻዋ ምን አሳቃት እስከ ዛሬ ገና ነኝን ጌታዬም አርጅቷል እኔም አሁን አርጅቻለሁ ብላ በውኑ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር አለን። ከዚህም በኋላ ሣራ ፀንሳ እግዚአብሔር ባለው ወራት በርጅናዋ ለአብርሃም ወንድ ልጅን ወለደች።
ከዚህም በኋላ በበጎ እርጅና በአረፈች ጊዜ ከኬጢያዊ ኤሞርልጆች በገዛው ቦታ ቀበራት።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበረች እናታችን ሣራ በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 14 047 |
| 7 | በብዙ አገራት እንዳይታተሙ ታግደው የነበሩ፣ አነጋጋሪና አደገኛ ምስጢራትን የያዙ ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፎች በPdf የሚገኙበትን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ!
👇👇
@Bemnet_Library 📚
@Bemnet_Library 📚 | 10 668 |
| 8 | ያየኽብኝን ያላሳየኽብኝ
ያየኽብኝን ያላሳየኽብኝ
ደግሞም በደሌን የረሳኽልኝ
አስገረመኝ ለእኔ ያለህ
አስደመመኝ ለእኔ ያለህ
ብበድልህ /4/ እየቻለኝ ያ ትከሻህ
አዝ
እጄን በአፌ እያስጫነ አስገረመኝ ደጉ ልብህ ፊትህ አይጠቁር በኃጢአቴ እንዳላየህ ታልፈዋለህ
ሳታሳጣኝ በሰው መሐል የእኔ ከዳኝ የልቤ ጥግ
አላነስኩም ካየኽልኝ ከከፍታህ ከዚያ ማዕረግ
አዝ
በእርሱ ምሕረት ከድቅድቁ ከወጣሁኝ ከጨለማ
ለይሁዳ ክፉ ወሬ ልቤ አይሰጋ ለዓለም ዜማ
በነበልባል ሲያቃጥለኝ የስምዖን አንደበቱ
የእሳት ልሳን ሆነኽልኝ በአንተ አለፈ ያ ክረምቱ
አዝ
ከበለስ ሥር የሠራሁት ዓለም ተፍቶ ያቃለለው
ረሳሁት ትቼዋለሁ እንዳንተ ያለኝ ከቶ ማነው
ሰው ሲሸሸኝ የቀረብከኝ አንተ እኮ ነህ መድኃኒቴ
ዐይንህ ዐይቶኝ መች አለፍከኝ አነሳኸኝ ቸር አባቴ
አዝ
መክሮ መክሮ ሲታክተው ውጣ ብሎ እየጣለ
ስንቱ አለፈ በመከራ ሰው ወገኑን ስላልቻለ
የኔ ጌታ ፍቅሩ ችሎኝ ሰፊው ክንዱ አሻገረኝ
ለውለታው ከእንባ በላይ የሚያረካው ምን ቃል አለኝ
ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 16 105 |
| 9 | ዛሬ [ ሰኞ ] ምሽት 2:00 እንገናኝ
12ኛው ዙር Graphics Design ሥልጠና ላይ
Day 1 + 2 + 3 ኮርስ በነጻ እንድትከታተሉ
ተጋብዛችኋል 🎉
ቀድማቹ ማወቅ ያለባችሁን እና
ከየት ወደየት መሄድ እንደምትችሉ ጥንቅቅ
አድርገን እናሳያችኋለን ።
@greenbirdtechnology ላይ
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
« I want to attend Day 1+2+3 of
Graphics Design Course »
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ብላቹ ለምትልኩልን link እንሰጣችኋለን
___________________________
@greenbirdtechs
@greenbirdtechs
የለውጥዎ ክንፍ 🔑 🐥 | 15 211 |
| 10 | ነሐሴ ፳፭ /25/
በዚችም ቀን ቅዱሱ አባት አባ ቢጻርዮን አረፈ። የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ምእመናን ነበሩ። በአደገም ጊዜ የምንኵስና ልብስን ለብሶ እግዚአብሔርን ሊአገለግል ወደደ ዓለምንም ንቆ ወደ ኣባ እንጦንስ ሔደ ለእርሱም ደቀ መዝሙር ሆኖ ብዙ ዘመናት አገለገለው።
ከዚህም በኃላ ወደ አባ መቃርስ ሒዶ ቅዱሳን አረጋውያን መነኰሳትንም አገለገላቸው። በአስቄጥስም ገዳም ይዘዋወር ነበር በቤት ውስጥም አያድርም ነበር ። አባቶችም ጭንቅ የነበረ ተጋድሎውን ስለርሱ ይናገሩ ነበር። እርሱ አርባ መዓልትና አርባ ሌሊት ከቶ ሳይተኛ ቁሞ ኖሮአልና።
በምንኩስናውም ወራት ብዙ ጊዜ በየአርባ ቀን ጾመ እነሆ እንዲህ እየተጋደለ ድንቆችንም እያደረገ ኀምሳ ሰባት ዓመታት ኖረ። ቅዱሳን አባ ዱላስና አባ ዮሐንስም ከተአምራቱ ተናገሩ እነርሱ ከርሱ ጋር ወደ ኤርትራ ባሕር ዳርቻ ሔዱ። እጅግም በተጠሙ ጊዜ እንደተጠሙ አውቆ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ መራራውንም ውኃ ጣፋጭአድርጎላቸው ጠጥተዋል።
የዚህም ቅዱስ ተአምራቶቹ ከነገርናችሁ የበዙ ናቸው እግዚአብሔርንም አገልገሎ በሰላም አረፈ ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ጻድቅ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 15 337 |
| 11 | በነጻ 🤗
ነገ ሰኞ ምሽት 2:00 በሚጀመረው 12ኛው
ዙር Graphics Design ሥልጠና ላይ
Day 1 + 2 + 3 ኮርስ በነጻ እንድትከታተሉ
ተጋብዛችኋል 🎉
ቀድማቹ ማወቅ ያለባችሁን እና
ከየት ወደየት መሄድ እንደምትችሉ ጥንቅቅ
አድርገን እናሳያችኋለን ።
@greenbirdtechnology ላይ
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
« I want to attend Day 1+2+3 of Graphics Design Course »
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ብላቹ ለምትልኩልን link እንሰጣችኋለን
___________________________
@greenbirdtechs
@greenbirdtechs
የለውጥዎ ክንፍ 🔑 🐥 | 6 783 |
| 12 | ቁጥርህ ከመላእክት
ቁጥርህ ከመላእክት ተስተካክሏል
ከኪሩቤል መሐል ገብተህ አጥነሃል
ተክለሃይማኖት በጸሎትህ
ብዙ ድውያን ፈውሰሃል
አዝ
ባሕር ሳያሰጥመን ደርሶልን
አለፍን በደረቅ ከፍሎልን
ኢትዮጵያዊው ሙሴ ተክለሃይማኖት
የሚሳነው የለም በሃይማኖት
አዝ
ጸሎቱ ምህላው ቅዳሴው
ገብቷል ከቤታችን መዓዛው
ጸጋ በረከትህ በዝቶልናል
በአማላጅነትህ ተምረናል
አዝ
ድካም በሌለበት በምስጋና
አምላኩን ያከብራል በትህትና
ስለ እኛም ዝም አይልም ይማጸናል
የአባታችን አምላክ ይሰማናል
አዝ
ዘመናችን ሲረክስ መንገዳችን
ፈጥኖ ደረሰልን አባታችን
ተክለሃይማኖት እርዳን ልጆችህን
አታርቀው ከእኛ ኪዳንህን
ዘማሪት ጸዳለ ጎበዜ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 18 242 |
| 13 | እንኳን ለታላቁ ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ
ልደት
መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ ጸጋ ዘአብ ካህኑና እግዚእ ኃረያ ናቸው። እርሱ በክህነቱ እርሷ በደግነቷ በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል።
በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ ቢደርስባቸው ቅዱስ ሚካኤል ጸጋ ዘአብን ከሞት እግዚእ ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል። በሁዋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል።
ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የጸነሱት መጋቢት 24 ቀን በ1206 ዓ/ም ሲሆን የተወለዱት ደግሞ ታሕሳስ 24 ቀን በ1207 ዓ/ም ነው። በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል። ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል።
ዕድገት
የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው "ፍሥሃ ጽዮን" ይሰኛል። ይሕንን ስም ይዘው አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው አድገዋል። በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን (ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል። በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል። ዲቁናም ከወቅቱ ዻዻስ አባ ጌርሎስ ተቀብለዋል።
መጠራት
አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮስ ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ።
የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ። "ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን። ከዚህ በሁዋላ አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ። ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ በግርማ ዐረገ። ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በሁዋላ ሰዓትን አላጠፉም። ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ።
አገልግሎት
ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል አገልግሎትን ጀመሩ። በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ። ያን ጊዜ ኢትዮዽያ 2 መልክ ነበራት።
1ኛ. ዮዲት (ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል ወይም በባዕድ አምልኮ ተጠምዷል።
2ኛው. ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር።
ግማሹ ሃገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ። ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን (ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል::
ገዳማዊ ሕይወት
ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል። እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል።
እነዚህም በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት: በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ ዳሞ ከአቡነ ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26 ዓመታት አገልግለዋል።
በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በሁዋላም ወደ ምድረ ሽዋ (ዞረሬ) ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል። በተሰበረ እግራቸውም 6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል።
ስድስት ክንፍ
ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት ተባርከዋል። ጻድቁ ምድረ እሥራኤል የገቡት በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር::
የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሚካኤል ጋርም ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል። ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ በሁዋላ ነው ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር።
ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም። በገሃድ:-
-በቤተ መቅደስ ብስራቱን
-በቤተ ልሔም ልደቱን
-በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን
-በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን
-በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር።
የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደ ሆነው ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ። በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ እመቤታችን ድንግል ማርያም ፈጥና ደርሳ ተክልየን ወደ ሰማይ አሳረገቻቸው።
በዚያም :-
-የብርሃን ዐይን ተቀብለው
-6 ክንፍ አብቅለው
-የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው
-ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው
-ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው
-ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው
-"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል።
ተአምራት
የተክልየ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው።
ሙት አንስተዋል
ድውያንን ፈውሰዋል
አጋንንትን አሳደዋል
እሳትን ጨብጠዋል
በክንፍ በረዋል
ደመናን ዙፋን አድርገዋል።
ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን መሥርተዋል። በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት አብረው ኑረዋል። በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና::
ዕረፍት
ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: እልፍ አእላፍ ፍሬን አፍርተው: በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24 ቀን በ1306 ዓ/ም ዐርፈዋል።
ጌታ: ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል። 10 ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል።
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 17 630 |
| 14 | ነሐሴ ፳፬ /24/
በዚች ቀን የክርስቶስ ምስክሩና ሐዋርያው የሆነ የመርዓስ ኤጲስቆጶስ ተጋዳይ ቅዱስ አባት ቶማስ አረፈ። ይህም አባት የመርዓስ አገር ኤጲስቆጶስ ነበር። በከሀዲ ዲዮቅልጥያኖስም ዘመን ይህን አባት መኳንንት እየደበደቡት ወሰዱት።
ከዚህም በኃላ መኮንኑ ቅዱስ ቶማስን ለአማልክት ስገድ አለው ቅዱሱም ለጣዖት እንደማይሰግድ ነገረው። በዚህም በብዙ አሰቃዩት። ከዚህም በኋላ በጨለማ ቦታ ጣሉት በዚያም ሃያ ሁለት ዓመት ኖረ። በዚያም አካላቱን ይቆርጡት ነበር። መንጋዎቹም ያረፈ መስሏቸው በየዓመቱ መታሰቢያውን ሲያደርጉ ኖሩ። ነገር ግን አንዲት ሴት አይታው ስለነበር በድብቅ ትመግበው ነበር።
ጻድቅ ቁስጠንጢኖስም እስከ ነገሠና የቀናች የክርስቶስን ሃይማኖት ክብር እስከ ገለጠ ድረስ እንዲህ ሲሠቃይ ኖረ። ይቺም ሴትስለ ቅዱሱ ለካህናቱ ነገረቻቸው በውስጡ ወደሚኖርበትም ቦታ መራቻቸው። እነርሱም አንሥተው ተሸከሙት እየዘመሩና እያመሰገኑ ወደ ቤተ ክርስቲያን አደረሱት በቤተ መቅደሱም ፊት ለፊት በወንበሩ ላይ አስቀመጡት ምእመናንም ሁሉ ወደርሱ እየመጡ ከእርሱ ይባረኩና የተቆረጡ ሕዋሳቱን ይሳለሙ ነበር።
ይህም ቅዱስ ከ318ቱ ሊቃውንት አንዱ ነው። ንጉሱም ስለ ቅዱሱ በሰማ ጊዜ ሰገደለት። ከዚህም በኃላ ቅዱስ ቶማስ ወደ መንበረ ሢመቱ ሔደ ካህናቱንና መንጋዎቹን ሁሉ ሰብስቦ አነበበላቸው እርሱንም እንዲአስተውሉት እንዲጠብቁትም በመጠበቅም እንዲጸኑ አዘዛቸው።
ጥቂት ዘመናትም ከኖረ በኃላ በሰላም በፍቅር አረፈ የሹመቱም ዘመን አርባ ዓመት ነው በዚህም እግዚአብሔርን አገለገለው።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 15 204 |
| 15 | ፀሐይ ዘልዳ ጊዮርጊስ
እምነ ሠናይት ኩሉ እለ ውስተ ባሕር ወየብስ/2/
ሶበ ነጸርኩ በኃሢሥ ዘከማከ አልቦ ጊዮርጊስ/2/
አዝ
የመከራን ገፈት ቀምሳ ለሰጠችህ
ልጅ ሆነሀልና ለማርያም እናትህ
ስምዐ ክርስቶስ አርዓያ ሰማዕታት
ሆነህ የተሰየምህ የሰማዕታት አባት
አዝ
የገድልህን ነገር ጆሮአችን ሲሰማ
ልባችን ይቀልጣል በጽናትህ ዜና
የጌታህን ትእግስት ቀራንዮን እያሰብክ
በወጣትነትህ ተጋድሎህን ፈጸምክ
አዝ
በጭንቅ መከራ ጽናትህ ሲፈተን
ከአምላክ ተምረህ ቁጣ ሳትናገር
ሁሉን ስለጌታ ችለህ ታግሰሀል
የብርሃን አክሊልን በሰማይ ደፍተሃል
አዝ
ሥዕለ ገጽህን ዘወትር እያየን
ነገረ ገድልህን ሁልጊዜ እያደነቅን
ፍቅርህ በልባችን ስለተሣለብን
ይኸው እንዘምራለን ጊዮርጊስ እያልን
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 20 165 |
| 16 | ነሐሴ ፳፫ /23/
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ነሐሴ ሃያ ሦስት በዚችም ቀን ቅዱስ ድምያኖስ በሰማዕትነት አረፈ።
ይህንንም ቅዱስ የአንጾኪያ አገርመኰንን ብዙ ወራት አሠቃየው ከማሠቃየትም በሰለቸ ጊዜ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ።
በረከቱ ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 18 776 |
| 17 | በብዙ አገራት እንዳይታተሙ ታግደው የነበሩ፣ አነጋጋሪና አደገኛ ምስጢራትን የያዙ ኦርቶዶክሳዊ እና ዓለም አቀፍ መጽሐፎች በPdf የሚገኙበትን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ!
👇👇
@Bemnet_Library 📚
@Bemnet_Library 📚 | 11 200 |
| 18 | ማርያም ማርያም ብዬ
ማርያም ማርያም ብዬ ስምሽን ልጥራው
አይደክመኝም እኔ ብደጋግመው
አሁንም ጠራሁሽ አላስችልህ ቢለኝ
አውቀዋለሁ ስምሽን እናቴ ስትወለደኝ/2/
ገና በማህፀን በእናቴ የምጥ ቀን
ደጋግሜ ሰማሁ ሲጠሩት ስምሽን
በሰከንዳት እድሜ የማውቃት አንዲት ቃል
ልቤላይ ያለው ስም ማርያም ማርያም ይላል
ማርያም...ማርያም
አዝ
ሔዋን ምጧ ቀሎ ልጆቿን ታቀፈች
በአመላጅነትሽ እናቴም ታመነች
በተወለድኩባት በመጀመሪያው ቀን
ስምሽን እየሰማሁ ወጣሁ ከማህፀን
ማርያም...ማርያም
አዝ
ከቃልኪዳን ስም ጋር አደኩኝ አብሬ
ምልጃሽ ሳይለየኝ አለሁ እስከዛሬ
የሕይወቴን ፈደል ካንቺ ላይ ቆጠርኩኝ
በልጅሽ አምኜ ዳግም ተወለድኩኝ
ማርያም...ማርያም
አዝ
የክፉ ቀን ስንቄ ያዘልኩሽ በልቤ
የሕይወቴ ምግብ እንጀራ መሶቤ
እንደትላንትናው ዛሬም እጠራሻለሁ
የመስቅል ስር ክብሬን እንዴት እረሳለሁ
የመስቅል ስር ክብሬን እንዴት እተዋለሁ
ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤️ | 22 563 |
| 19 | ነሐሴ ፳፪ /22/
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ነሐሴ ሃያ ሁለት በዚች ቀን ታላቅ ነቢይ የሞራት ልጅ ሚክያስ አረፈ። ይህም ነቢይ በይሁዳ ነገሥታት በኢዮአታም፣ በአካዝና በሕዝቅያስ ዘመን ትንቢት በመናገር አስተማረ።
ስለ ጌታችን መውረድም እንዲህ አለ። እነሆ እግዚአብሔር ከልዑል መንበሩ ወደዚህ ዓለም ይወርዳል።
ሁለተኛም ሰለ ልደቱ እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ የኤፍራታ ዕጣ የምትሆኚ አንቺም ቤተ ልሔም የእስራኤል ነገሥታት ከነገሡባቸው አገሮች አታንሺም ወገኖቼ እስራኤልን የሚጠብቃቸው ንጉሥ ከአንቺ ይወጣልና።
ስለ ምኵራብ መቅረት፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን በዓለም ሁሉ መታነፅ ትንቢት ተናግሮአል። ዳግመኛም ስለ ሕገ ወንጌል መሠራት ሕግ ከጽዮን የእግዚአብሔርም ቃል ከኢየሩሳሌም ይወጣል አለ ። የትንቢቱም ወራት ሲፈጸም ወደ በጎ ሽምግልና ደርሶ ወደ ወደደው እግዚአብሔር ሔደ።
የትንቢቱም ዘመን ከጌታችን መምጣት በፊት በስምንት መቶ ዓመት ነው ። ማርታ በምትባልም ቦታ ተቀበረ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 22 670 |
| 20 | ይህ እራሱ Youtube እንዳይመስላቹ 🤭
እኛጋ ስትማሩ የምትሠሩት Figma Web Design ነው
በምንም ተአምር በ2 ወራት ይህን አደርገዋለሁ ተብሎ አይታሰብም ነበረ
ምክንያቱም የዓመታት ጥረት ስለሚጠይቅ
አሁን ግን እኛጋ ስትማሩ እንደዛ አይደለም
እራሱን Youtubeን እንደገና ዲዛይን ታደርጉታላቹ ።
ሁሉም ቀላል ነው 🤗
የ500 ብር ቅናሹ ሊያበቃ የመጨረሻዋ ቀን
የመጨረሻዎቹ ሰዓታት ⏰
ባለሙያ መሆን እንድህ ቀላል ሆኗል
ከPhotoshop - Figma
~~~~~~~~~~~~~~~~~~
@Greenbirdtechnology ላይ
ተመዝገቡ ቤታቹ ሆናቹ ተማሩ።
Click here for Details
_______________
@greenbirdtechs
@greenbirdtechs
የለውጥዎ ክንፍ 🔑 | 10 211 |
