Wazema Media / Radio
Wazema is Radio other contents are available either in our website/social media or FM radio stations in Ethiopia. www.wazemaradio.com
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام Wazema Media / Radio
کانال Wazema Media / Radio (@wazema_radio) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 48 620 مشترک است و جایگاه 5 398 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 692 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 48 620 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 05 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 658 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 8 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 39.62% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 17.93% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 19 265 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 8 719 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 91 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“Wazema is Radio other contents are available either in our website/social media or FM radio stations in Ethiopia. www.wazemaradio.com”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 06 سپتامبر, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 05 سپتامبر | +14 | |||
| 04 سپتامبر | +25 | |||
| 03 سپتامبر | +14 | |||
| 02 سپتامبر | +28 | |||
| 01 سپتامبر | +9 |
| 2 | ለቸኮለ! ዓርብ፣ ነሃሴ 29፣ 2018 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜና
1፤ ገዥው ብልጽግና ፓርቲ አዲስ በሚመሠርተው መንግሥት ውስጥ ከ70 እስከ 80 በመቶ የሚኾኑ ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታዎችን ለአዲስ ተሿሚዎች ለመስጠት መወሠኑን ዋዜማ ሠምታለች። የፓርቲው ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ፣ ረዘም ላሉ ዓመታት በአመራርነት ያገለገሉ ተሿሚዎች ራሳቸውን ለሌላ ተልዕኮ እንዲያዘጋጁ እንደነገሯቸው ምንጮች ገልጸዋል። በሥራ ላይ ከሚገኙ አመራሮች መካከል ባለፈው ጠቅላላ ምርጫ ወቅት በቂ ሥራ አልሠሩም በሚል ከሥራቸው የታገዱ ሹሞች መኖራቸውንም ምንጮች ተናግረዋል። በካቢኔ ምርጫ የሚንስትርነት ሹመት የሚሠጣቸው የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች የሚኖሩበት ዕድል አለ ያሉት ምንጮች፣ አዲስ በሚዋቀሩ የካቢኔ ድልድሎች ውስጥ ሹመት ማግኘት እንፈልጋለን የሚል ጥያቄ ያቀረቡ የፓርቲ አመራሮች መኖራቸውን ጭምር ሠምተናል። Link - https://cutt.ly/ZykaokpG
2፤ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ የሽብር ወንጀል ተጠርጣሪዎቹ የኢሕአፓ አመራር ይስሃቅ ወልዳይ፣ የፓርቲው አባል አበበ አካሉ እና የቀድሞው የሰላም ሚንስትር የዴኤታ ታዬ ደንደዓ ጠበቃ አበራ ንጉሥ እያንዳንዳቸው በ50 ሺሕ ብር ዋስትና ከእስር እንዲለቀቁ ፈቀደ። ችሎት፤ የፖሊስን ተጨማሪ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ጥያቄ ውድቅ በማድረግ፤ ተጠርጣሪዎቹ ጉዳያቸውን በውጭ እንዲከታተሉ መወሠኑን ዋዜማ ሠምታለች። ፖሊስ ምርመራውን እንዳላጠናቀቀ በመግለጽ ተጨማሪ 14 ቀናት እንዲፈቀድለት የተጠየቀው ትናንት በዋለው ችሎት ነበር።
3፤ ጣሊያን፣ ኢትዮጵያ እና ግብጽ በናይል ወንዝ ውዝግባቸው ዙሪያ እንዲነጋገሩ ሁኔታዎችን ለማመቻቸት ዝግጁ መሆኗን መግለጧ ተሠማ። የጣሊያን የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒዮ ታጃኒ ሰሞኑን ከግብጹ አቻቸው ባደር አብደላቲ ጋር ግብጽ ውስጥ በሠጡት መግለጫ፣ ኢትዮጵያ እና ግብጽ ፍላጎቱ ካላቸው ጣሊያን ድርድሩን ለማመቻቸት ዝግጁ መኾኗን መናገራቸውን ሚድል ኢስት ሞኒተር ጋዜጣ ዘግቧል። ሚንስትሩ፣ ግብጽ በዓለማቀፍ ሕግ መሠረት ከወንዙ ውሃ የድርሻዋን እንድታገኝ የሚያስችል ስምምነት ያስፈልጋል ማለታቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ኾኖም ግብጽ ለጣሊያን የአደራዳሪነት ሀሳብ ምን ምላሽ እንደሠጠች ዘገባው አልጠቀሠም።
4፤ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኩባንያ የ90 ቀናት ንቁ ደንበኞች ብዛት ከ15 ሚሊዮን አለፈ። ኩባንያው ከተመሠረተ ጀምሮ ከ3 ሺሕ 500 በላይ የኔትዎርክ ጣቢያዎችን በአገሪቱ ውስጥ ማቋቋሙንና ኔትዎርኩ ለ60 በመቶው የኢትዮጵያ ሕዝብ ተደራሽ መኾኑን ሃላፊዎቹ መናገራቸውን የኬንያው ዘ ስታር ጋዜጣ ዘግቧል። የኩባንያው እድገት ከአዲስ መሠረት ላይ ለሚጀምር ኩባንያ በዓለም ላይ ፈጣኑ እድገት መሆኑን ሃላፊዎቹ ጠቅሠዋል ተብሏል። ባለፉት አራት ዓመታት ለማኅበረሰብ ልማትና ድጋፍ 139 ወጪ ማድረጉን የጠቀሠው ኩባንያው፣ ባለድርሻ አካላትና አጋሮች ደሞ 545 ሚሊዮን ብር ለዚሁ ዓላማ ማዋጣታቸውን መግለጡን ዘገባው አመልክቷል።
5፤ የአማራ ክልል ፖሊስ፣ በባሕርዳር ከተማ በመንግሥት ተሽከርካሪ በመታገዝ ሰዎችን ያገቱ ግለሰቦችን ከነተሽከርካሪው ነሃሴ 29 ቀን ባሕርዳር ውስጥ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታወቀ። ተጠርጣሪዎቹ ታጋቾቹን አፍነው በመውሠድ ለ11 ቀናት አግተው እንዳቆዩዋቸው የገለጸው ፖሊስ፣ ታጋቾቹን ለመልቀቅ ሦስት ሚሊዮን 370 ሺሕ ብር ጠይቀው ገንዘቡን ከቤተሰቦቻቸው መቀበላቸውን ገልጧል። የእገታ ወንጀሉ የተፈጸመው በክልሉ የከተሞች ልማትና ፕላን ኢንስቲትዩት ቢሮ ተሽከርካሪ አማካኝነት መሆኑን ፖሊስ የጠቀሠ ሲሆን፣ የመንግሥት ተቋማት ለሥራ በተመደቡላቸው ተሽከርካሪዎችና አሽከርካሪዎች ላይ ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር እንዲያደርጉም አሳስቧል።
6፤ በሱዳን የተመድ ዓለማቀፍ አጣሪ ቡድን፣ ኢትዮጵያዊያን ከሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ጋር ወግነው ከሚዋጉ የውጭ ዜጎች መካከል እንደሚገኙበት አረጋግጫለሁ አለ። ቡድኑ፣ የኢትዮጵያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ቻድ ዜጎች ዳርፉርን ጨምሮ በተለያዩ ግንባሮች በውጊያ መሳተፋቸውን መለየት እንደተቻለ ገልጧል። ኾኖም የቡድኑ ምርመራ ከፈጥኖ ደራሹ ኃይል ጋር የተሠለፉ ኢትዮጵያዊያን ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ግንኙነት ያላቸው ስለመኾኑ አላመለከተም። ለሱዳን ተፋላሚ ወገኖች ድጋፍ ያደርጋሉ የሚል ውንጀላ የሚቀርብባቸው የተለያዩ አገራት መረጃ እንዲሠጡኝ ጠይቄያለሁ ያለው ቡድኑ፣ ከኢትዮጵያ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ሊቢያ ምላሽ እንዳላገኘ ገልጧል።
7፤ የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ፣ አፍሪካ "ሜርካተር" በተባለው ለበርካታ ክፍለ ዘመናት ሥራ ላይ ባለው የዓለም ካርታ ላይ ባነሳችው ቅሬታ ላይ ዛሬ ድምጽ ይሠጣል። በአፍሪካ ኅብረት ድጋፍ የቀረበው የውሳኔ ሀሳብ፣ መንግሥታት፣ ትምህርት ቤቶች፣ ዓለማቀፍ ድርጅቶችና የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ከነባሩ "ሜርካተር" ካርታ ይልቅ አዲሱን "ኢኳል ኧርዝ" የተሠኘውን ካርታ እንዲጠቀሙ ይጠይቃል። በአፍሪካ የውሳኔ ሀሳብ ላይ የተነሳው ዋነኛ ቅሬታ፣ ካርታው አሕጉሪቱን ከትክክለኛ ስፋቷ እርጅጉ አሳንሶ ያቀርባል የሚል ነው። በ16ኛው ክፍለ ዘመን የተሠራው ይሄው ካርታ፣ በምድር ወገብ አካባቢ የሚገኙትን አሕጉራት ስፋት በእጅጉ ያሳንሳል፤ በሰሜን ዋልታ አካባቢ ያሉትን ደሞ አግዝፎ ያቀርባል የሚል ትችት የካርታ ባለሙያዎች ያቀርቡበታል።
እንዲሁም፤
1፤ የእጅ ጥበብ ውጤቶች፣ የቤተ ውበት መገልገያ ጌጣጌጦችና የቆዳ ውጤቶች የሚቀርቡበት "የቅዳሜ ገበያ" ባዛር ቅዳሜ ነሐሴ 30 ከቤት እስከ ከተማ የከተማ ማዕከል ውስጥ ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 2 ሰዓት ይካሄዳል።
2፤ "እንቁጣጣሽ ማርኬት" የአዲስ ዓመት ባዛር በወዳጅነት ፓርክ (ቁጥር 2) ውስጥ ከነገ ቅዳሜ ነሐሴ 30 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን ድረስ ለተከታታይ ቀናት ይካሄዳል። [ዋዜማ] | 8 809 |
| 3 | የዐብይ አዲሱ ካቢኔ እየመጣ ነው፣ ተሰናባች ሚንስትሮች በዝግ ስብሰባ ላይ ናቸው - የዋዜማን ዝርዝር ዘገባ ያንብቡት-- https://cutt.ly/ZykaokpG | 10 693 |
| 4 | ለቸኮለ! ሐሙስ፣ ነሃሴ 28፣ 2018 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ የኢትዮጵያ መንግሥት በአገሪቱ የመጀመሪያውን የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችል የትብብር ማዕቀፍ ከዓለማቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ጋር ተፈራረመ። ኩባንያው በ100 ቢሊዮን ብር ካፒታል እንደሚቋቋምና ከኮርፖሬሽኑ 200 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያገኝ ተገልጧል። ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ፣ የሁለትዮሹ አጋርነት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገነቡ 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብ መንግሥት ያስቀመጥነውን ግብ የሚያሳካ ወሳኝ ርምጃ መኾኑን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ገልጸዋል።
2፤ የአማራ ክልል መንግሥት የጤና ባለሙያዎችን የትርፍ ሰዓት ክፍያ አፈጻጸምን አስመልክቶ አዲስ መመሪያ አወጣ። መመሪያው፣፣ የጤና ባለሙያዎች ደመወዝ ለ30 ቀናት እንዲሁም፣ ባንድ ቀን የሚያገኙት የገንዘብ መጠን ለ8 ሰዓታት ተካፍሎ ክፍያው እንዲፈጸምላቸው ይደነግጋል። ሌሎች ዝርዝር የክፍያ ስሌቶችም በመመሪያው ላይ ሠፍረዋል። ከደመወዝ የሚገኝ የትርፍ ሰዓት ክፍያ ለበረሃማና ለውርጭ አካባቢዎች የተፈቀደ አበል ክፍያ ተግባራዊ እንደሚደረግ ያሚያትተው መመሪያው፣ መመሪያው ጤና ባለሙያዎች በትርፍ ሰዓት ሥራ ያከናወኑትን ሥራ በዕለቱ ለአገልግሎት ጥራት ቁጥጥር ክፍል ሪፖርት ማድረግ እንዳለባቸውና ይህን ማድረግ ያላልቻሉ ክፍያውን እንደማያገኙ ደንግጓል።
3፤ ዛሬ ረፋዱ 5 ሰዓት ገደማ ዎላይታ ሶዶ ዩንቨርስቲ የማኅበራዊ ሳይንስ ሕንጻ ላይ በእሳት ቃጠሎ ጉዳት ደረሠ። በቃጠሎው፣ በሕንጻው የጅአይኤስ ቤተመጽሃፍት፣ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ቤተመጽሃፍት እና በሌሎች የትምህርት ክፍሎች ንብረቶች ላይ ጉዳት ደርሷል ተብሏል። የዎላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር፣ የእሳት አደጋው ዎላይታን ተቋም አልባ ለማድረግ የተወጠነ የሴራ አካል ነው ብሏል። ፓርቲው፣ እሳቱ ከተነሳበት ሕንጻ ጋር ቀጥተኛ ግኑኝነት ያላቸው ግለሰቦችና የተቋሙ ተጠሪዎች ላይ ጥልቅ ምርመራ እንዲደረግ ጠይቋል።
4፤ አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ መቀሌ ውስጥ በተሠወረው የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹና የፎቶግራፍ ባለሙያው ፊሊሞን ገብረሂዎት ላይ የትግራይ ባለስልጣናት "ገለልተኛ"፣ "ጥልቅ" እና "ግልጽ" ምርመራ እንዲያደርጉ ጠየቀ። አምነስቲ፣ ፊሊሞን በነሃሴ 2017 ዓ፣ም መቀሌ ውስጥ በድንገት ከተሠወረ ጀምሮ እስካሁን ያለበት አይታወቅም ሲል ስጋቱን ገልጧል። የትግራይ ባለሥልጣናት እስካሁን በፊሊሞን ላይ ምርመራ ስለመጀመራቸው ምንም ያሉት ነገር የለም ያለው አምነስቲ፣ ባለስልጣናቱ ፊሊሞን ያለበትን ሁኔታና አድራሻውን ይፋ እንዲያደርጉ ጠይቋል። ፊሊሞን በቁጥጥር ሥር ውሎ ከሆነና ክስ ካልተመሠረተበት፣ ባስቸኳይ እንዲለቀቅም አምነስቲ አሳስቧል።
5፤ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ በኢሕአፓ አባላት ይስሃቅ ወልዳይ እና አበበ አካሉ እንዲሁም በቀድሞው የሰላም ሚንስትር ደኤታ ታዬ ደንደዓ ጠበቃ አበራ ንጉስ ላይ የዋስትና ብይን ለመስጠት ለነገ ነሐሴ 29 ቀጠሮ ሠጠ። ፖሊስ የምስክሮችን ቃል ለመቀበልና የሕክምና ማስረጃዎችን ከአርባ ምንጭ ለማስመጣት የ14 ተጨማሪ ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቆ፣ ተጠርጣሪዎቹ በዋስ ቢፈቱ ከአገር ሊወጡ ወይም ምስክሮችን ሊደልሉ ይችላሉ በማለት የዋስትና ጥያቄውን ተቃውሟል። የተጠርጣሪዎች ጠበቆች በበኩላቸው፣ የፖሊስን ጥያቄና ምክንያቶች ችሎቱ ውድቅ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
6፤ የናምቢያ መንግሥት የአገሪቱን አየር መንገድ መልሶ ለማቋቋም ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር የቴክኒክ ንግግር መጀመሩን አስታወቀ። ኾኖም በናምቢያ ላይ ሕጋዊ ግዴታ የሚጥል ስምምነት እስካሁን ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር እንዳልተደረሠና የቴክኒክ ንግግሩ የናምቢያን ብሄራዊ የሚያስጠብቅ እንደሚኾን ባለሥልጣናት መናገራቸውን የአገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኪሳራ የተዘጋውን የናምቢያ አየር መንገድ ወደ በረራ ለመመለስ ድርድር ላይ ስለመኾኑ ያወጣው መረጃ የለም።
በሌላ ዜና፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ 777-ኤፍ የሚባሉትን ጨምሮ 10 ያህል የጭነት ማጓጓዣ ቦይንግ አውሮፕላኖችን ለመግዛት መቃረቡን ሮይተርስ ዘግቧል። ኾኖም አየር መንገዱም ኾነ ቦይንግ ግዥውን እንዳላረጋገጡ ዘገባው ጠቅሷል። አየር መንገዱ ባሁኑ ወቅት 12 ቦይንግ 777-ኤፍ አውሮፕላኖች አሉት።
7፤ የተመድ የጸረ-ዘረኝነት ኮሚቴ፣ በባሪያ ንግድ የተሳተፉ አገራት ለተጎጂ ወገኖች ካሳ የመክፈልና ሌሎች የማካካሻ ርምጃዎችን የመውሠድ ግዴታ አለባቸው በማለት ወሠነ። ኮሚቴው፣ የአገራቱ ግዴታ የሚመነጨው እኤአ በ1965 ከጸደቀው ዘረኝነትን ለማጥፋት ከተረቀቀው አስገዳጅ ዓለማቀፍ ድንጋጌ መኾኑን ገልጧል። አንዳንድ ምዕራባዊያን አገራት በባሪያ ንግድ ወቅት ድርጊቱን ሕገወጥ የሚያደርግ ዓለማቀፍ ሕግ ስላልነበር፣ ላለፈ ድርጊት ተጠያቂ ልንኾን አንችልም ባይ ናቸው። የተመድ ኮሚቴ በበኩሉ፣ የባሪያ ንግድ የፈጠረው ተጽዕኖ እስካሁንም ስላለ፣ አገራቱ ተጽዕኖውን የሚቀርፉ ርምጃዎችን የመውሠድ ግዴታ አለባቸው ብሏል። [ዋዜማ] | 11 439 |
| 5 | ለቸኮለ! ረቡዕ፣ ነሃሴ 27፣ 2018 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ ከ230 በላይ ሥልጠና ያጠናቀቁ የሶማሊያ ወታደሮች ሰሞኑን የኢትዮጵያን ድንበር አቋርጠው ሶማሌ ክልል መግባታቸውንና በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው መኾኑን ዋዜማ ሠምታለች። ዋዜማ ያነጋገረቻቸው ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ አንድ የሶማሌ ክልል ከፍተኛ ባለሥልጣን፤ ወታደሮቹ ድንበር አቋርጠው የገቡት ሕጋዊ የጉዞ ሠነድ ሳይዙ መኾኑን ገልጸዋል፡፡ ወታደሮቹ፣ በአልሸባብ ስጋት ምክንያት ወደ ትውልድ ቦታቸው ለመሄድ ባለመቻላቸው የኢትዮጵያን ድንበር አቋርጠው ለማለፍ መሞከራቸውን በምርመራ ወቅት መናገራቸውን ባለሥልጣኑ ገልጸዋል፡፡
የሶማሊያ የብሄራዊ ደኅንነት አማካሪ አዌስ የሱፍ በበኩላቸው፣ ሠልጣኞቹ ወደ ኢትዮጵያ ያቀኑት፣ ሶማሌ ክልል ውስጥ የሚገኙ ዘመዶቻቸውን ለመጠየቅ መሆኑንና ከዚህ የተለየ ነገር ነገር ካለ ምርመራ እንደሚደረግ መናገራቸውን የሶማሊያ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። ጋልሙዱግ ግዛት ውስጥ በሳዑዲ ዓረቢያ ድጋፍ ሥልጠና ያጠናቀቁት ወታደሮች ወደ ኢትዮጵያ የገቡት፣ ወደየቤተሰባቸው እንዲሄዱ የአንድ ወር ፍቃድ ከተሠጣቸው በኋላ እንደኾነ ተነግሯል።
2፤ በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ በተከሠተው ድርቅ ሳቢያ፤ ከ3 ሺሕ 300 በላይ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ዋዜማ ከዞኑ አስተዳደር ሀላፊዎች ሠምታለች፡፡ ከወረዳው 24 ቀበሌዎች መካከል በ10ሩ እስካሁን የክረምት ዝናብ እንዳልዘነበ የገለጹት የዞኑ ሀላፊዎች፤ በጃንአሞራ፣ በበየዳ እና በደባርቅ ወረዳዎችም ድርቁ በመባባሱ ከ80 ሺሕ በላይ የቤት እንስሳት እንደሞቱ ወይም ለከባድ ጉዳት እንደተጋለጡ አስረድተዋል፡፡ ሀላፊዎቹ፣ ለድርቁ ተጎጂዎች አፋጣኝ እርዳታ ካልቀረበ ከጥቅምት እና ሕዳር በኋላ የከፋ የምግብ እጥረትና ሰብዓዊ ቀውስ ሊፈጠር እንደሚችል ስጋታቸውን ነግረውናል፡፡ በአካባቢው ያለው ጸጥታ፣ የመንግሥትም ሆነ ረድኤት ድርጅቶች እርዳታ በበቂ ሁኔታ እንዳያቀርቡ እንቅፋት መፍጠሩንም ሀላፊዎቹ ገልጸዋል።
3፤ አብን፣ መንግሥት በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ፣ በምሥራቅ አርሲ እና ሌሎች ዞኖች በንጹሃን ላይ የሚፈጸሙ "ማንነት" እና "እምነት" ተኮር ጥቃቶችን በታጣቂ ቡድኖች በማሳበብ ከተጠያቂነት ሊያመልጥ አይችልም አለ። አብን፣ መንግሥት በንጹሃን ላይ ለሚፈጸሙት ጥቃቶች የሕግም ሆነ የፖለቲካ ተጠያቂነት ያለባቸውን ባለስልጣናት ተጠያቂ ሳያደርግ ችግሩን በማድበስበስ ለማለፍ መሞከሩ ተቀባይነት የለውም በማለት ተችቷል። መንግሥት ሃላፊነታቸውን ያልተወጡ ባለሥልጣናትን ተጠያቂ እንዲያደርግ፣ በተጠቀሱት አካባቢዎች የጸጥታ ኃይሎች ስምሪት "ገለልተኛ" እና "ሕጋዊነትን" የተላበሰ መሆኑን የሚያረጋግጥ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶችንና ገለልተኛ አካላትን ያካተተ የምርመራና ክትትል ማዕቀፍ እንዲዘረጋም አብን ጠይቋል።
4፤ የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ፣ እድሜያቸው ከ5 ዓመት በላይ የሆናቸውና ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ያልወጣላቸው ሕጻናት በቀጣዩ የትምህርት ዘመን መመዝገብ እንደማይችሉ ማሳወቁን ዋዜማ ሠምታለች። ዋዜማ ከተለያዩ የዞንና የወረዳ ትምህርት ጽሕፈት ቤቶች የደረሳት መረጃ እንደሚያሳየው፣ ሕጻናቱ ለኢትዮ ቴሌኮም ቅርንጫፎች እና ውክልና ላላቸው ባንኮች አሻራ እየሠጡ መሆኑን ምንጮች ተናግረዋል። አሻራ በመስጠት ሂደቱ ፈታኝ ከሆኑ ጉዳዮች መካከል የምዝገባ ጊዜው መቃረብ፣ አሻራ የሚሰጡ ሕጻናት ቁጥር እጅግ ከፍተኛ መሆን፣ ማሽኖቹ የሕጻናቱን አሻራ በሚገባ መዝግበው ባለመያዛቸው በቤተሰቦች የእጅ ስልክ የሚላኩ መለያ ቁጥሮች መዘግየት ይገኙበታል ተብሏል። በዚህ ምክንያት፣ ሕጻናቱ ድጋሚ አሻራ እንዲሠጡ እየተገደዱና ለከፍተኛ እንግልት እየተዳረጉ መሆኑን ተረድተናል።
5፤ የሱዳን ወታደራዊ መንግሥት ከኢትዮጵያ ጋር ወደሚዋሠነው ብሉ ናይል ግዛት በርካታ ተዋጊዎችን በማንቀሳቀስ ላይ መኾኑን አስታወቀ። ወደ ብሉ ናይል ግዛት ደማዚን ከተማ አካባቢ የተንቀሳቀሱት ተዋጊዎች የፈጥኖ ደራሹን ኃይል ለመውጋት ከሱዳን ጦር ሠራዊት ጋር የወገኑ ኃይሎች እንደሆኑ የአገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። ከተያዘው ሳምንት መጀመሪያ ጀምሮ በግዛቲቱ በርካታ አካባቢዎች በመንግሥት ወታደሮችና በፈጥኖ ደራሹ ኃይል መካከል ውጊያ በመካሄድ ላይ መሆኑን ዘገባዎች ያመለክታሉ። ፈጥኖ ደራሹ ኃይል ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አቅራቢያ ስትራቴጂካዊቷን ኩርሙክ ከተማ ከአንድ ሳምንት በፊት ከሱዳን ጦር ሠራዊት መንጠቁ ይታወሳል።
6፤ የአሜሪካ ኮንግሬስ፣ የአሜሪካው የአፍሪካ የቀረጥ ነጻ ንግድ ስምምነት (አጎዋ) በሁለት ዓመት ከአራት ወራት እንዲራዘም ውሳኔ አሳለፈ። የሕግ መወሠኛው ምክር ቤቱ ከሳምንታት በፊት የአጎዋን ማራዘሚያ ረቂቅ ሕግ ማጽደቁ ይታወሳል። ኮንግሬሱ ለተያዘው ዓመት ብቻ ለጊዜው የአጎዋ ቆይታ እንዲራዘም ቀደም ሲል ወስኖ የነበረ ሲሆን፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕም ባለፈው የካቲት ወር ረቂቅ የውሳኔ ሀሳቡን ፈርመውበት እንደነበር ይታወሳል። የአሁኑ ማራዘሚያ እስከ ፕሬዝዳንቱ የሥልጣን ዘመን ማብቂያ የሚቀጥል ነው። ሁለቱ ምክር ቤቶች ያጸደቁት ረቂቅ ሕግ ተፈጻሚ የሚኾነው፣ አሁንም ፕሬዝዳንት ትራምፕ ሲፈርሙበት ነው። ኢትዮጵያ በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ተፈጽመዋል ከተባሉ የሰብዓዊ መብት ጥሠቶች ጋር በተያያዘ ከአጎዋ ተጠቃሚነቷ የታገደችበት ውሳኔ እስካሁን አልተነሳም።
እንዲሁም፤
1፤ በሐመረ ብርሃን የብራና መጻሕፍት ሥራ ድርጅት የተዘጋጀው "የምድር ጌጥ ኢትዮጵያ" የተሠኘ ዐውደ ርዕይ ለተከታታይ ቀናት ከነሐሴ 28 እስከ መስከረም 3 ቀን 2019 ዓ፣ም ድረስ በሆላንድ ፓርክ ይካሄዳል።
2፤ "ክሬቲቭ ማይንድ፤ አርት ፎር ሶሻል ቼንጅ" የሚል ርዕስ የተሠጠውና በፈጠራ ጥበብ ዘርፍ ውስጥ ያሉ የተለያዩ እንግዶች ሐሳቦቻቸውን የሚያጋሩበት መሰናዶ ነገ ነሐሴ 28 ቀን ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ በሂልተን ሆቴል ይካሄዳል። [ዋዜማ] | 11 961 |
| 6 | ለቸኮለ! ማክሰኞ፣ ነሃሴ 26፣ 2018 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ በቀጣዩ ዓመት በከተማዋ የኮሪደር ልማት የሚካሄድባቸው አካባቢዎች እንደተለዩ በከተማዋ አስተዳደር የ2019 በጀት ዓመትና የቀጣይ አምስት ዓመታት ዕቅድ የግምገማ መድረክ ላይ ተናገሩ። አዳነች የኮሪደር ልማት በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል። የወንዞችን ዳርቻ ማደስና "የወደቁ" ሠፈሮችን የማንሳት ሥራ በ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ውስጥ በቁጥር ተለይቶ መቀመጡን አዳነች ገልጠዋል። አዳነች አያይዘውም፣ ያረጁ ሠፈሮችን የማደስ ሥራ ነዋሪዎችን በንጽህና እንዲኖሩ ከመደገፉ ባሻገር፤ በተደጋጋሚ የሚከሠቱ ተላላፊ በሽታዎችን ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል፡፡
2፤ ኢትዮጵያ ከስምንት ዓመት በፊት ለተፈረመው የመጀመሪያው ዓለማቀፍ የፍልሠት ሠነድ አገራዊ የትግበራ ዕቅድ ረቂን አዘጋጀች። የሠነዱ አገር ዓቀፍ የትግበራ ዕቅድ ረቂቅ ዝግጅት በዓለማቀፉ የፍልሠት ድርጅት የፋይናንስ ድጋፍ አማካኝነት መከናወኑን ፍትሕ ሚንስቴር ገልጧል። ኢትዮጵያ ለሠነዱ የትግበራ ዕቅድ ከማውጣቷ በፊትም፣ ሁለት አገራዊ የትግበራ ሪፖርቶችን ለተመድ አቅርባለች። ኢትዮጵያ በ2018 ሞሮኮ ማራካሽ ውስጥ ዓለማቀፉ የፍልሠት ሠነድ በተፈረመበት ወቅት ከመጀመሪያዎቹ ፈራሚ አገራት መካከል አንዷ ነበረች። ዓለማቀፉ ሠነድ አገራት የፍልሠት አስተዳደራቸውን እንዲያሻሻሉና የፍልሠት ሥረ መሠረቶችን እንዲፈቱ የሚያግዝ ማዕቀፍ የዘረጋ ሠነድ ሲኾን፣ በአገራት ላይ አስገዳጅነት ግን የለውም።
3፤ በጋምቤላ ከተማ በተፈጸመ ጎሳ ተኮር ጥቃት በሁለት ታዳጊዎች ላይ ጉዳት እንደደረሠ ዋዜማ ሠምታለች፡፡ በአካባቢው ባለ ወንዝ ሲጫወቱ በነበሩ ታዳጊዎች ላይ ነሃሴ 24 ቀን በተፈጸመ ጥቃት የ11 እና የ13 ዓመት ታዳጊዎች ላይ ጉዳት መድረሱን ምንጮች ተናግረዋል። ጉዳት የደረሠባቸው ታዳጊዎች ለሕክምና እርዳታ ወደ ጋምቤላ ሆስፒታል እንደተወሰዱ ተነግሯል። የአካባቢው ምንጮች ጥቃቱን የፈጸሙት የአኝዋክ ታጣቂዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። በክልሉ ግጭት በተደጋጋሚ በሚከሠትባት ኢታንግ ልዩ ወረዳ፣ ካለፉት ጥቂት ቀናት ወዲህ ከልዩ ወረዳዋ ወደ ጋምቤላ ከተማ የተሸከርካሪ እንቅስቃሴ ተቋርጧል ተብሏል።
4፤ በሳዑዲ ገጠራማና በረሃማ ቦታዎች በኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞች መካከል በቅርቡ ከተካሄደ የቡድን ጸብ እና ግጭት ጋር በተያያዘ የግድያ ወንጀል የፈጸመ ግለሰብ ከአምስት ግብረ አበሮቹ ጋር በቁጥጥር ሥር መዋሉ ተገለጠ። በሳዑዲ የኢትዮጵያ ኢምባሲ፣ ጉዳዩን በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ሲያራግቡ የነበሩ ከ100 በላይ ግለሰቦችም በቁጥጥር ሥር እንደዋሉ አስታውቋል። ግለሰቦቹ ለሕግ እንዲቀርቡ ከሳዑዲ የጸጥታ አካላአካላትጋር በቅርበት እየሠራ መሆኑ ኢምባሲው ጠቅሷል።
5፤ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን፣ አባይ ቴሌቪዥን ባሠራጫቸው ዜናዎች እና ኘሮግራሞች ላይ ለተፈጸሙ የሕግና የጋዜጠኝነት ሙያ ስነ-ምግባር ጥሠቶች ማስጠንቀቂያ ሠጥቻለሁ አለ። ባለሥልጣኑ፣ የጣቢያው ሃላፊዎች ለተፈጠረው ስህተት ይቅርታ መጠየቃቸውን ገልጧል። በጣቢያው ፕሮግራሞች ላይ ከታዩ የስነምግባር ጥሠቶች መካከል፣ ከማኅበረሰቡ ባሕል ወግ እና እሴት ያፈነገጡ "ጸያፍ ንግግሮች" እና "አባባሎች"፣ በመልካም ባሕሪና በስነምግባር የታነጸ ወጣት ትውልድ በማፍራት ሂደት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ የሚፈጥሩ ይዘቶችን ማሠራጨት እንዲሁም የሴቶችን ክብር የሚነኩ ፕሮግራሞች ላይ የተፈጠሩ ግድፈቶች ይገኙበታል። ጣቢያው በሚያሠራጫቸው ዜናዎች ላይ ያልተረጋገጡ ምንጮቾን መጠቀም እንዲያቆምም ባለስልጣኑ አሳስቧል።
እንዲሁም፤
1፤ በኢትዮጵያ ከ11 ዓመታት በላይ የኖረችው አሜሪካዊቷ የቫዮሊን ተጫዋች ኬታ ሆስታተር ‘ወራጅ አለ’ የተሠኘ አዲስ የሙዚቃ አልበሟን ለአድማጮች አቅርባለች። ሆስታተር፣ አልበሙ በኢትዮጵያ ያሳለፈቻቸውን ትዝታዎች እና የሕይወት ቅጽበቶች በሙዚቃ የገለጸችበት እንደሆነ አስታውቃለች።
2፤ "የአጥቢያ ኮኮብ" የተሠኘ አዲስ ተውኔት ተመርቋል። ተውኔቱ ከያዝነው ሳምንት አንስቶ በቋሚነት ዘወትር ቅዳሜ ከምሽቱ 11 ሰዓት ተኩል ጀምሮ በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ለታዳሚያን ይቀርባል። [ዋዜማ] | 12 469 |
| 7 | ለቸኮለ! ሰኞ፣ ነሃሴ 25፣ 2018 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ፣ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅት ያዘጋጃቸውን አዲስ ዲጂታል መታወቂያ ያላወጡ የመንግሥት ሠራተኞች ከጳጉሜ 1 ጀምሮ የከተማ አሥተዳደሩ የሚሰጠውን ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት መጠቀም አይችሉም አለ። በከተማዋ ያሉ የመንግሥት ሠራተኞች ከተጠቀሰው ቀን ጀምሮ ከዚህ በፊት ባለው ነባር መታወቂያ አገልግሎቱን ማግኘት እንደማይችሉ አስተዳደር መግለጡን ዋዜማ ቢሮው ከጻፈው ደብዳቤ ላይ ተመልክታለች። ቢሮው፣ መታወቂያውን ባላወጡ የመንግሥት ሠራተኞች ላይ ለሚፈጠረው ችግር ተጠያቂ እንደማይሆን ገልጿል።
2፤ ሚድሮክ የወርቅ ማዕድን ኩባንያ፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ለሚያስገነባው የወርቅ ፋብሪካ የሚውሉ የግንባታ መሳሪያዎችን ለማግኘት የሚያስችለውን ስምምነት መቀመጫውን ኦስትሪያ ካደረገው ዓለማቀፉ የፋብሪካ መሳሪያዎች አምራች "ሴሜቴክ" ኩባንያ ጋር መፈራረሙን አስታወቀ። ስምምነቱ፣ "ሴሜቴክ" በዓመት 1 ሚሊዮን 250 ሺሕ ቶን ወርቅ አዘል ድንጋይ በፋብሪካ ውስጥ እንዲያልፍ የሚያስችል ማሽነሪ አምርቶ እንዲያቀርብ የሚያስችል መሆኑን ሚድሮክ ገልጧል። ሚድሮክ፣ "ሴሜቴክ" ኩባንያ አስፈላጊ የወርቅ ማምረቻ ምርቶችን አምርቶ ባንድ ዓመት ውስጥ ለሚድሮክ እንደሚያስረክብ ጭምር ጠቅሷል።
3፤ የሳዑዲ ዓረቢያ ድንበር ጠባቂ ፖሊስ ጫት እና ቁጥጥር የሚደረግባቸውን መድኃኒቶች ወደ አገሪቱ ሊያስገቡ ሞክረዋል ያላቸውን 18 ኢትዮጵያዊያን አሠረ። አራቱ ኢትዮጵያዊያን አሲር ግዛት ውስጥ 80 ኪሎ ግራም ጫት ሊያስገቡ ሲሞክሩ እንደታሠሩ ሳዑዲ ጋዜት ዘግቧል። 12ቱ ኢትዮጵያዊያን ደሞ ጃዛን ግዛት ውስጥ 240 ሊሎ ግራም ጫት ሊያስገቡ ሲሉ እንደተያዙ ዘገባው ጠቅሷል። በተመሳሳይ ግዛት ሁለት ኢትዮጵያዊያን 20 ሺሕ 800 ቁጥጥር የሚደረግባቸውን ክኒኖች ለማስገባት በመሞከር ተይዘዋል ተብሏል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚወጡ መረጃዎች እንደሚያሳዩት፣ ኢትዮጵያዊያን ጫት እና ቁጥጥር የሚደረግባቸውን ክኒኖች ሲያስገቡ የመያዛቸው ክስተት ተደጋጋሚ ኾኗል።
4፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሰባት ዓመታት በፊት በተከሠከሠው ቦይንግ ማክስ የመንገደኞች አውሮፕላን ሕይወታቸውን ያጡ ኬንያዊያን መንገደኞችን የወከሉ 32 ቤተሰቦች እያንዳንዳቸው 2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዶላር ካሳ ሊከፈል ነው። ቦይንግ በጠቅላላው ለኬንያዊያኑ ተጎጂ ቤተሰቦች 87 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዶላር እንዲከፍል ፍርድ ቤት ወስኖበታል። ለኬንያዊያኑ ቤተሰቦች የሚከፈላቸው ካሳ፣ ቦይንግ በወንጀል ላለመከሰስ ከአንድ ዓመት በፊት ከአሜሪካ ፍትሕ መስሪያ ቤት ጋር በደረሠበት ስምምነት መሠረት ካቋቋመው የ444 ሚሊዮን ዶላር የተጎጂዎች የካሳ ፈንድ ላይ ነው። ቦይንግ ከአደጋው ጋር በተያያዘ የቀረቡበትን የካሳ ክፍያ ክሶች 90 በመቶ ያህሉን የቋጫቸው ከፍርድ ቤት ውጭ ባሉ ድርድሮች ነው።
5፤ ሩዋንዳ ዳንጎቴ ኩባንያ ኬንያ ውስጥ በሚያስገነባው የነዳጅ ማጣሪያ የአክሲዮን ድርሻ ለመግዛት ከኩባንያው ጋር ድርድር ጀመረች። ኾኖም ድርድሩ ገና በመጀመሪያ ምዕራፍ ላይ እንደሚገኝ ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ ባለፈው ሳምንት ተናግረዋል። ኬንያ ከዳንጎቴ የነዳጅ ማጣሪያ የ10 በመቶ ድርሻ የመግዛት እቅድ እንዳላት ያስታወቀች ሲሆን፣ ኢትዮጵያም ድርሻ የመግዛት ፍላጎት እንዳላት እንደተዘገበ ይታወሳል። ዳንጎቴ ለምሥራቅ አፍሪካ አገራት እስከ 30 በመቶ የሚደርስ የአክሲዮን ድርሻ መድቧል። ነዳጅ ማጣሪያው የሚገነባባት ላሙ ወደብ፣ ኬንያን፣ ኢትዮጵያን እና ደቡብ ሱዳንን ያስተሳስረው የላፕሴት የመሠረት ልማት ፕሮጀክት አካል ናት።
6:
የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የፊልም ፌስቲቫል እና አፍሮፒክስ (AfroPix) የኢትዮጵያ ፊልሞችን ለዓለም አቀፍ ተመልካች ለማቅረብ የሚያስችል አጋርነት በይፋ መሥረታቸውን አስታወቁ። ይህ አዲስ መርሃ ግብር ዘመናዊ የኢትዮጵያ ፊልሞችን፣ ዶክመንተሪዎችንና አጫጭር ፊልሞችን በዓለም አቀፍ ደረጃ በዲጂታል አማራጭ ተደራሽ ለማድረግ ያለመ ነው ተብሏል። በዚህ መድረክ ላይ ፊልሞቻቸውን የሚያቀርቡ የፊልም ባለሙያዎች በየ 100,000 እይታ 3,000 ዶላር ክፍያ የሚያገኙበት ዘላቂ የገቢ ማስገኛ ሥርዓት ተዘርግቶላቸዋል። የአፍሮፒክስ መሥራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ታይሮን ሳችዌል አጋርነቱ ትክክለኛ የአፍሪካ ታሪኮችን ያለምንም ችግር ለዓለም ለማድረስ ትልቅ እምርታ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፤ የፌስቲቫሉ መሥራችና ዳይሬክተር ይርጋሸዋ ተሾመም ውሉ ለኢትዮጵያ የሲኒማ ባለሙያዎች ዓለም አቀፍ እውቅናንና የተሻለ የንግድ ገቢን እንደሚያስገኝ ጠቅሰዋል።
እንዲሁም፤
1፤ በከፈለኝ ኃይሉ (ኢ/ር) የተጻፈው "የደራ ገበያ ምሥጢር፤ በዲጂታል ዘመን" መጽሐፍ ለአንባቢያን ቀርቧል። መጽሐፉ ነባሩን የንግድ አሠራር ከአዲሱ ዲጅታል ዓለም ጋር አጣጥሞ መስራት ስለሚቻልበት መንገድ የሚያብራራ ነው።
2፤ በፖለቲከኛ ግርማ ሠይፉ የተዘጋጀውና በ280 ገፆች የቀረበው "ለውጥ እና ነውጥ" የተሠኘ መጽሐፍ ለንባብ በቅቷል። መጽሐፉ በ6 ዋና ዋና ክፍሎች የተዋቀረ ሲሆን፣ ሰላማዊ የዴሞክራሲ ሽግግርን፣ ምርጫን፣ የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ፣ ቀጣናዊ ጉዳዮችን እና ዘላቂ ሰላምን እንደሚዳስስ ተገልጿል። [ዋዜማ] | 14 405 |
| 8 | ለቸኮለ! ቅዳሜ፣ ነሃሴ 23፣ 2018 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ጌታቸው ረዳ፣ የሱዳን ጦር ሠራዊት በምዕራብ ኢትዮጵያ የድንበር አካባቢዎችንና መንደሮችን በከባድ መሳሪያ በመደብደብ ጉዳት እያደረሠ ይገኛል በማለት ለአልጀዚራ በሠጡት ቃል ከሰሱ። ጌታቸው፣ የሱዳን ወታደራዊ መንግሥት የኢትዮጵያን ተቃዋሚዎች ይረዳል በማለት ጭምር መወንጀላቸውን ዜና አውታሩ ማምሻውን ዘግቧል። የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ከኢትዮጵያ ግዛት እየተነሳ በሱዳን ጦር ሠራዊት ላይ ጥቃት ይፈጽማል የሚለውን የሱዳን ባለሥልጣናት ውንጀላ ያስተባበሉት ጌታቸው፣ ኢትዮጵያ የሱዳንን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት እንደምታከብር ተናግረዋል ተብሏል። ሱዳን ጦሯን ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጋር ወደሚዋሠነው ብሉናይል ግዛት ደማዚን ከተማ አካባቢ በብዛት እያንቀሳቀሰች መኾኗንም ዘገባው የሱዳን ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል።
2፤ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ በሽብር ወንጀል በተጠረጠሩት የኢሕአፓ አባላት ይስሃቅ ወልዳይ እና አበበ አካሉ እንዲሁም የቀድሞው የሰላም ሚንስትር ደዔታ ታዬ ደንደአ ጠበቃ አበራ ንጉስ ላይ መርማሪ ፖሊስ በሰባት ቀናት ውስጥ ምርመራውን አጠናቆ ለነሃሴ 28 እንዲያቀርብ አዘዘ። ፖሊስ ትናንት በዋለው ችሎት ላይ ምርመራውን ለማጠናቀቅ 14 ቀናት ተጨማሪ ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቆ ነበር። ችሎቱ ዛሬ ለመርማሪ ፖሊስ ተጨማሪ ሰባት ቀናት የፈቀደው፣ መርማሪ ፖሊስ የሚያቀርባቸውን ምስክሮች ቃል ለመስማት መኾኑን ገልጧል። ችሎቱ፣ ተጠርጣሪዎቹ ካኹን ቀደም ባቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ላይ ነሃሴ 28 ውሳኔ እሠጣለሁ ብሏል።
3፤ ጎጎት ፓርቲ፣ ከኦሮሚያ ክልል የተነሱ ታጣቂዎች በምሥራቅ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ሱተን ቀበሌ ነሃሴ 19 ቀን በፈጸሙት ጥቃት ሦስት የሚሊሺያ አባላትን ጨምሮ ሰባት ነዋሪዎች ተገድለዋል አለ። ፓርቲው፣ ታጣቂዎቹ ሌሎች አምስት ሰዎችን አፍነው እንደወሠዱ ገልጧል። በታጣቂዎቹ ጥቃት በርካታ የመንግሥትና የግል ተሽከርካሪዎች፣ መኖሪያ ቤቶችና የግል ንግድ ቤቶች መቃጠላቸውን ጭምር ፓርቲው ጠቅሷል። ታጣቂዎች በአካባቢው በተደጋጋሚ በሚፈጽሙት ጥቃት ላይ ግልጽ ምርመራ እንዲደረግና የምርመራ ውጤቱ ለሕዝብ ይፋ እንዲደረግ እንዲኹም የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ተጨማሪ የፌደራል የጸጥታ ኃይል ባስቸኳይ እንዲሠማራ ፓርቲው ጠይቋል።
4፤ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአርባ ምንጭ ከተማ ፖሊስ፣ "በሕገወጥ መንገድ" ሲዘዋወሩ ነበር ያላቸውን 32 ኤርትራዊያን በቁጥጥር ሥር አዋለ። በቁጥጥር ሥር የዋሉት ኤርትራዊያን፣ 14ቱ ሴቶች፣ 11ዱ ወንዶች እንዲኹም ሰባቱ ሕጻናት መኾናቸውን ፖሊስ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሠራጨው መረጃ ገልጧል። ሁለት የኤርትራዊያኑ አዘዋዋሪዎችና አንድ ሹፌር ጭምር በቁጥጥር ሥር ውለዋል ተብሏል። ኤርትራዊያኑና አዘዋዋሪዎቻቸው ከተማዋ ውስጥ የተያዙት፣ ሲያትል ከሚባል አልቤርጎ ምድር ቤት ላይ በሚገኝ አዳራሽ ተሸሽገው መኾኑን ፖሊስ ጠቅሷል። በርካታ ኤርትራዊያን ስደተኞች በደቡብ ኢትዮጵያ በኩል ድንበር አቋርጠው ኬንያ እንደሚገቡ የአገሪቱ ፖሊስ በተደጋጋሚ ገልጧል።
5፤ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚንስትር ፍራንክ ጋርሺያ ወደ ኢትዮጵያ ሊጓዙ ነው። ጋርሺያ ወደ ኢትዮጵያ የሚጓዙት፣ የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን ለማጠናከር እና የጋራ የጸጥታ እና ኢኮኖሚ አጋርነቶችን ለማጎልበት እንደኾነ መስሪያ ቤቱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ገልጧል። ኾኖም ጋርሺያ መቼ ኢትዮጵያ እንደሚገቡና ከየትኞቹ የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር እንደሚወያዩ የመስሪያ ቤቱ መረጃ አላመለከትም። ጋርሺያ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ለተመሳሳይ ዓላማ ወደ ኬንያ እና ዛምቢያ ጭምር ያቀናሉ ተብሏል።
6፤ ኡጋንዳ በፍልስጤሟ ጋዛ ሠርጥ እንዲሠማራ ለሚቋቋመው ዓለማቀፍ የማረጋጊያ ተልዕኮ 1 ሺሕ 200 ወታደሮች እንደምታዋጣ የአሜሪካ ባለሥልጣናት ማረጋገጣቸውን ዘ ኢስት አፍሪካ ጋዜጣ ዘገበ። የኡጋንዳ ወታደሮች በቀጣዩ ዓመት ጥቅምት በሠርጧ ይሠማራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ዘገባው ጠቅሷል። ቡሩንዲም ለተልዕኮው ወታደሮች ለማውጣት እየተነጋገረች መኾኑን ዘገባው ጠቅሷል። ሞሮኮ፣ በተልዕኮው ትሳተፋለች ተብላ የምትጠበቅ ሌላኛው አፍሪካዊት አገር ናት። በአሜሪካ ሀሳብ አመንጪነት የሚቋቋመው ዓለማቀፍ የማረጋጊያ ኃይል፣ ጋዛን የማረጋጋትና ለሰብዓዊ ዕርዳታ ሥራዎች ድጋፍ የመስጠት ሃላፊነት ይኖረዋል።
እንዲሁም፤
1፤ "ፍቅር እስከ መቃብር በሥዕል" የሚል ስያሜ የተሠጠውና በሠዓሊ ነጋልኝ ሉሌ የተዘጋጀው የሥዕል ዐውደ ርዕይ በተያዘው ሳምንት በፈንድቃ የባሕል ማዕከል ለዕይታ ቀርቧል። ይህ ዐውደ ርዕይ እስከ መስከረም 11 ቀን በዕይታ ላይ ይቆያል።
2፤ በመምህር መሠረት አበጀ የተዘጋጀው "ለምሳሌ፤ ውነተረት በመሠረት" የተሠኘ አዲስ መጽሐፍ በቅርቡ ለአንባቢያን ይቀርባል ተብሏል። [ዋዜማ] | 17 105 |
| 9 | ለቸኮለ! ዓርብ፣ ነሃሴ 22፣ 2018 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ በኦሮሚያ ክልል ምእራብ ሸዋ ዞን ኢልፈታ ወረዳ ዛሬ ዓርብ ማለዳ ላይ የአማጺው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት፣ የወረዳው የሚሊሺያ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሌሊሳ ወርቁን ጨምሮ ሌሎች የአካባቢው የአስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች መገደላቸውን ዋዜማ ሠምታለች። በጥቃቱ፣ በወረዳው የሃሩ ሲናኒ ቀበሌ ዋና አሥተዳዳሪ ጊቲማ አያንሳ፣ የጉቴ ቀበሌ የሠላምና ጸጥታ ጉዳዮች ኃላፊ ግርማ ጨዋቃ እና ሁለት የክልሉ ሚሊሺያ አባላት ሕይወታቸው ማለፉን ምንጮች ለዋዜማ ተናግረዋል። የአማጺ ቡድኑ አባላት ጥቃቱን ከፈጸሙ በኋላ ወደ ወረዳው አሥተዳደር ጽሕፈት ቤት አምርተው እንደነበርና ኾኖም የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ከስፍራው ሲደርሱ ታጣቂዎቹ ከተማዋን ለቅቀው እንደወጡ ምንጮች ነግረውናል።
2፤ በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መደበኛ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ተማሪዎች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሠጠው ዕድል መሠረት በከተማዋ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ትምህርታቸውን ለመቀጠል ቢያመለክቱም ማመልከቻቸው ውድቅ እንደተደረገ ዋዜማ ሠምታለች። የከተማዋ አስተዳደር ከ1 እስከ 8ኛ ክፍል በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ያልተማሩ አመልካቾችን አልቀበልም ማለቱን የተማሪዎች ቤተሰቦች ተናግረዋል። በእቴጌ መነን እና ገላን ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ለመማር ያመለከቱ ተማሪዎች ቤተሰቦች፣ ልጆቻቸው እስከ 8ኛ ክፍል ያለውን ትምህርት በአማርኛ ቋንቋ በመማራቸው ብቻ ማመልከቻቸው ተቀባይነት እንዳላገኘ ገልጸዋል። የከተማዋ አስተዳደር በእቴጌ መነን ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ሴት ተማሪዎችን የሚቀበል ሲኾን፣ በገላን ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ደሞ ወንዶችን ተቀብሎ ያስተምራል።
3፤ ብሄራዊ ባንክ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊ በሕገወጥ የሃዋላ ገንዘብ መላኪያ ዘዴዎች አማካኝነት ገንዘብ ከመላክ እንዲታቀቡ በድጋሚ አሳሰበ። ባንኩ ይህን ማሳሰቢያ በድጋሚ ያወጣው፣ ባሁኑ ወቅት በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ወደ አገር ውስጥ የሚልኩት ገንዘብ በመጨመሩ መኾኑን ገልጧል። ባንኩ ፍቃድ የላቸውም በማለት ከዘረዘራቸው የሃዋላ ገንዘብ አስተላላፊዎች መካከል፣ አዲስ መኒ ትራንስፈር፣ አማና ኤክስፕረስ፣ ባካል መኒ ትራንስፈር፣ ወርልድ ዳይሬክት ሊንክ፣ ጁባ ኤክስፕረስ፣ አዋሽ ዳይራክት እና ታጅ ፋይናንሻል ሠርቪስስ ይገኙበታል። ደንበኞች የገንዘባቸውን ደኅንነት ለመጠበቅና ገንዘባቸው አስተማማኝ በሆነ መንገድ ወደ አገር ቤት መድረሱን ለማረጋገጥ ሕጋዊ ፍቃድ የተሠጣቸውን የገንዘብ ማስተላለፊያ ወኪሎች ብቻ እንዲጠቀሙ ባንኩ መክሯል።
4፤ ትናንት በትግራይ ክልል ምሥራቅ ዞን ክልተ አውላሎ ወረዳ ሁለት የድሮን ጥቃቶች እንደተፈጸሙ የክልሉ ቴሌቪዥን ዘገበ። በአብርሃ ወአጽብሃ ቀበሌ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት ባንድ ትምህርት ቤቱ ሕንጻና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን ዘገባው ጠቅሷል። ኾኖም በጥቃቱ ወቅት በትምህርት ቤቱ ውስጥ ወይም በትምህርት ቤቱ አቅራቢያ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ይኑር አይኑር ዘገባው አይመለከተም። ከትናንት በስቲያም፣ በክልሉ ምሥራቃዊ ዞን ሰሃርቲ ጊጀት ከተማ ዓለም ባንክ ድጋፍ ያደረገለት አንድ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በድሮን ጥቃት ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሠበት የክልሉ ባለሥልጣናት ገልጠው ነበር።
5፤ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ በተያዘው የ2019 በጀት ዓመት የአገሪቱን የኃይል ማመንጨት አቅም ወደ 9 ሺሕ 770 ሜጋ ዋት ለማድረስ ማቀዱን አስታወቀ። በበጀት ዓመቱ እንዲመረት ከታቀደው ኃይል ውስጥ፣ ከ29 ሺሕ 884 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል ለአገር ውስጥ ፍጆታ እንዲሁም ከ2 ሺሕ 249 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ የሚኾነውን ለውጭ ገበያ ለማቅረብ መታቀዱን የኩባንያው ሥራ እስፈጻሚ አሸብር ባልቻ ዛሬ በሠጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል። ኩባንያው በዚሁ በጀት ዓመት በውጭ ምንዛሬ ከሚሸጠው ኤሌክትሪክ ኃይል ብቻ 278 ነጥብ 63 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ማቀዱን አሸብር ገልጸዋል። ኩባንያው የውጭ ምንዛሬ የሚያገኘው፣ በአገር ውስጥ በመረጃ ማቀነባበር ሥራ ለተሠማሩ የውጭ ኩባንያዎች እና ለጎረቤት አገራት ከሚሸጠው ኃይል ነው። ኾኖም የኤልኒኖ የአየር ንብረት ለውጥ በኩባንያው የኃይል ማመንጨት ሥራዎችና ከኃይል ሽያጭ በሚያገኘው ገቢ ላይ አሉታዊ ጫና ሊያሳድር እንደሚችል አሸብር ጠቁመዋል።
6፤ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን፣ ላለፉት ስድስት ወራት በሦስት የሮይተርስ የዜና ወኪል ዘጋቢዎች ላይ ጥሎት የቆየውን የሥራ ፍቃድ እገዳ አነሳ። ባለሥልጣኑ የሦስቱን የሮይተርስ ዘጋቢዎች የሥራ ፍቃድ የመለሠው፣ ከዜና ወኪሉ ኃላፊዎች ጋር ከተወያየ በኋላ መኾኑን ዛሬ ባወጣው መግለጫ ገልጧል። የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ኃይማኖት ዘለቀ፣ ሮይተርስ "የሚዛናዊነት"፣ "የትክክለኛነት"፣ "የተዓማኒነት" እና "የተጨባጭነት' ችግር ያለባቸውና ላንድ ወገን ያደሉ ዘገባዎችን ይሠራ ነበር በማለት በውይይቱ ወቅት መናገራቸውን ባለሥልጣኑ ጠቅሷል። ባለሥልጣኑ፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የሮይተርስ ቋሚ የዜና ወኪሎች ፍቃድ እንደታደሠላቸው አውቀው አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ ጠይቋል። ሮይተርስ በበኩሉ፣ በኢትዮጵያ ላይ "ነጻ"፣ "ገለልተኛ" እና "ተዓማኒ" ዘገባዎችን መስራት እንደሚቀጥል አረጋግጧል። የሮይተርስ የዘጋቢዎች ፍቃድ የታገደው፣ ሮይተርስ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ኢትዮጵያው ውስጥ ወታደራዊ ማሠልጠኛ አቋቁሟል የሚል ዘገባ መስራቱን ተከትሎ ነበር።
7፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቻይናዋ ቸንጉ ግዛት እና አዲስ አበባ መካከል በዛሬው ዕለት በቀጥታ ጭነት የማጓጓዝ አገልግሎት ጀመረ። አዲሱ የጭነት ማጓጓዣ አገልግሎት፣ በምዕራባዊ የቻይና ግዛቶች እና በአፍሪካ መካከል ያለውን የንግድ ልውውጥ ይበልጥ እንደሚያሳድገው አየር መንገዱ ባሠራጨው መረጃ ገልጧል። የአየር መንገዱ የጭነት አገልግሎት በተለይ እንደ ሌጎስ፣ አክራ፣ ዳካር፣ ኢንቴቤ እና ሉቡምባሺ ያሉ የአፍሪካ ከተሞች ከቻይና ጋር ያላቸው የንግድ ትስስር እንዲጠናከር ያስችላል ሲል የቻይናው ዥንዋ የዜና ወኪል ዘግቧል። አየር መንገዱ ይህንኑ የጭነት አገልግሎት በቦይንግ 777 አውሮፕላኖቹ በሳምንት ሁለት ቀናት እንደሚሠጥ ዘገባው አመልክቷል። የአየር መንገዱ የጭነት ማጓጓዝ አገልግሎት ወደፊት በሳምንት ወደ አራት ቀናት ሊያድግ ይችላል ተብሏል። አየር መንገዱ ባሁኑ ወቅት 12 ቦይንግ 777 የጭነት ማጓጓዣ አውሮፕላኖች አሉት።
እንዲሁም፤
1፤ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የተዘጋጀውና በ"አርት ቴራፒ" ዙሪያ የሚያተኩር እንዲሁም ባለሞያዎች ሀሳቦቻቸውን የሚያጋሩበት ዝግጅት ቅዳሜ ነሐሴ 23 ቀን ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ በብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነጥበባት ማዕከል ይካሄዳል።
2፤ ታዋቂው ፒያኒስት ግርማ ይፍራሸዋ ከአዲስ አበባ ዌስት ሮታሪ ክለብ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የበጎ አድራጎት የልገሳ መርሃ-ግብር ነገ ቅዳሜ ነሐሴ 23 ቀን ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ ሐያት 49 በሚገኘው የመቄዶንያ የአረጋዊያንና የአእምሮ ሕሙማን ማዕከል ይከናወናል። [ዋዜማ] | 17 143 |
| 10 | ለቸኮለ! ሐሙስ፣ ነሃሴ 21፣ 2018 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ ገንዘብ ሚንስቴር የማክሮ ኢኮኖሚ ትንበያ ማዕቀፉን ሊቀይር መኾኑን አንድ የዓለማቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይ ኤም ኤፍ) ሪፖርት አመለከተ። አሁን ያለው የሚንስቴሩ የምጣኔ ሀብት መለኪያ መንግሥት በቅርቡ የወሠዳቸው የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በኢኮኖሚው ውስጥ ያላቸውን ሥርጸት ማሳየት እንደማይችል ሪፖርቱ ገልጧል። አዲሱ የምጣኔ ሀብት የትንበያ ማዕቀፍ፣ የመንግሥት የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች፣ የፖሊሲ ውሳኔዎችና ድንገተኛ ለውጦች በኢኮኖሚውና በአገሪቱ ዕዳ ላይ የሚያሳድሩትን ተጽዕኖ በተሻለ መንገድ ለመገምገም እንደሚያስችል ሪፖርቱ ጠቅሷል። ተቋሙ ለሚንስቴሩ አዲስ የምጣኔ ሀብት ትንበያ ማዕቀፍ ለመፍጠር ገምጋሚ ቡድኖቹን በመላክ ጥናት ሲያደርግ መቆየቱን የጠቀሠው ሪፖርቱ፣ የግምገማው ግኝቶች ሚንስቴሩ እስካሁን የሚጠቀምበት የምጣኔ ሀብት መተንበያ ማዕቀፍ ክፍትቶች እንዳሉበት ማሳየቱን ገልጧል።
2፤ ዓለማቀፉ የገንዘብ ተቋም፣ ጠበቅ ያለ የገንዘብ ፖሊሲ ቢከተሉ ይሻላል ካላቸው ትላልቅ ምጣኔ ሀብት ካላቸው የአፍሪካ አገራት መካከል ኢትዮጵያን አካተተ። ተቋሙ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ማዕቀፎቹን ማጠናከር እንዳለበት ሰሞኑን ትላልቅ ኢኮኖሚ ባላቸው የአፍሪካ አገራት ዘላቂና አካታች ልማት ዙሪያ ባወጣው አንድ ሪፖርት ላይ ምክረ ሀሳቡን ሠጥቷል። ተቋሙ ይህን ምክረ ሀሳብ የሠጠው፣ በሚያዝያ ወር ላይ በነበረው የአገሪቱ የገንዘብ ፖሊሲ ሁኔታ ላይ ተመስርቶ መኾኑን ጠቅሷል። ብሄራዊ ባንክ ባለፈው ሐምሌ የፖሊሲ ተመኑን ከ15 በመቶ ወደ 16 በመቶ ማሳደጉ ይታወሳል።
3፤ ዛሬ በትግራይ ክልል ሰሃርቲ ወረዳ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት አንድ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሠበት የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። በጥቃቱ ኮምፒውተሮችን ጨምሮ ዓለም ባንክ የለገሳቸው የትምህርት ቤቱ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቁሳቁሶች እንደወደሙ ቢሮው ጠቅሷል። ቢሮው በጥቃቱ ወቅት በትምህርት ቤቱ አካባቢ አንዳችም ወታደራዊ እንቅስቃሴ አልነበረም ያለው ቢሮው፣ ጥቃቱ "ኾን ብሎ የክልሉን የትምህርት ተቋማት ለማውደም" ያለመ ነው በማለት ወንጅሏል። በተያዘው ሳምንት ብቻ በትንሹ አምስት የድሮን ጥቃቶች በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች እንደተፈጸሙ ከክልሉ የወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ።
4፤ የሳዑዲ ዓረቢያ ድንበር ጠባቂ ፖሊሶች ትናንት 12 ኢትዮጵያዊን በቁጥጥር ሥር አዋሉ። ኢትዮጵያዊያኑ ጃዛን እና አስሪ በተባሉ ግዛቶች ውስጥ በቁጥጥር ሥር የዋሉት፣ 290 ኪሎ ግራም ጫት፣ 33 ኪሎ ግራም ሐሺሽ እና ከ72 ሺሕ በላይ የሳዑዲ መንግሥት ቁጥጥር የሚያደርግባቸውን ክኒኖች ለማስገባት ሲሞክሩ መኾኑን ሳዑዲ ጋዜት ዘግቧል። በተያዘው ነሃሴ ወር ብቻ የተለያዩ ዕጾችን ወደ አገሪቱ ለማስገባት ሲሞክሩ ወይም አገሪቱ ውስጥ ሲያጓጉዙ ተገኝተዋል የተባሉ ከ60 በላይ ኢትዮጵያዊያን በፖሊስ ቁጥጥር ሥር መዋላቹውን መረጃዎች ያሳያሉ። የሳዑዲ ፍርድ ቤቶች ዕጾችን አዘዋውረዋል ባሏቸው ኢትዮጵያዊያን ላይ በተደጋጋሚ የሞት ቅጣት ውሳኔ እንደሚያሳልፉ ይታወቃል።
5፤ የሱዳን ወታደራዊ መንግሥት፣ ከኢትዮጵያ አቅጣጫ ወደ ሱዳን ግዛት ገብቷል ያለውን ድሮን ዛሬ ጧት መትቶ መጣሉን አስታወቀ፡፡ የሱዳን ጦር ኃይል ድሮኑን መትቶ የጣለው፣ ከኢትዮጵያው ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ጋር በሚዋሠነው ብሉ ናይል ግዛት ውስጥ መኾኑን እንደገለጠ የአገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። ኾኖም የሱዳን ጦር ኃይል መትቼ ጣልኩት ባለው ድሮን ዙሪያ ዝርዝር ማብራሪያ አንዳልሠጠ ዘገባዎቹ ጠቅሠዋል። የአገሪቱ ጦር ኃይል ከቀናት በፊትም በዚሁ ግዛት ውስጥ ኩርሙክ ከተማ አካባቢ ከኢትዮጵያ በኩል የገባ ድሮን መትቼ ጥያለሁ ማለቱ አይዘነጋም። የኢትዮጵያ መንግሥት ለሱዳን ወታደራዊ መንግሥት ውንጀላዎች ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ በይፋ ምላሽ አልሠጠም።
6፤ አፍሪካ ኅብረት፣ በመጪው መስከረም ወር ለአባል አገራት ብድር የመክፈል አቅም ደረጃ የሚያወጣ አሕጉራዊ ተቋም ሊያቋቁም ነው። ተቋሙ ሞሪሺዬስ ውስጥ በተያዘው ወር መጨረሻ በይፋ ይመሠረታል መባሉን ሮይተርስ ዘግቧል። በርካታ የአፍሪካ አገራት መሪዎች፣ እንደ ፊች፣ ሙዲስ እና ኤስ ኤንድ ፒ ያሉ ዓለማቀፍ የአገራት እዳ የመክፈል አቅም ደረጃ አውጭ የኾኑ ተቋማት አፍሪካ ላይ አድሏዊነት ያሳያሉ፤ በተለይ በግጭትና በወረርሽኝ ጊዜ የአፍሪካ አገራት ለእዳ ከፋይነት ያላቸውን አቅም ፈጥነው ዝቅ ያደርጉታል በማለት ሲከሱ ቆይተዋል። ኅብረቱ የአፍሪካ የገንዘብ ኢንስቲትዩትን አቡጃ ውስጥ በቀጣዩ ዓመት ጥቅምት ወር ለማቋቋም ዝግጅቱን መጨረሱንም የኅብረቱ ባለሥልጣናት መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል።
እንዲሁም፤
1፤ በደረጀ ትዕዛዙ የተዘጋጀውና በከያኒ ተስፋዬ ገሠሠ የሕይወት ታሪክ ላይ የሚያጠነጥን "ተስፋዬ ገሠሠ፤ ጎምቱ የጥበብ ባለሟል" የተሠኘ መጽሐፍ ለንባብ በቅቷል። መጽሐፉ በጃፋር መጽሐፍ መደብር ይገኛል።
2፤ ቅዳሜ ነሐሴ 23 ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ በሚካሄደው የ"ነገረ መጽሐፍት" ውይይት ላይ ሳይላለም ተሠማ በእንግድነት ተጋብዛለች። ለውይይት የተመረጠው፣ "ክብካቦት" የተሠኘው የደራሲዋ መጽሐፍ ነው። ውይይቱ የሚካሄደው፣ ቀበና አካባቢ በሚገኘው የማኅበራዊ ጥናት መድረክ አዳራሽ ነው። [ዋዜማ] | 16 357 |
| 11 | ለቸኮለ! ረቡዕ፣ ነሃሴ 20፣ 2018 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ እና በአፍሪካ ኅብረት የአሜሪካ መልዕክተኛ ዋልተር ፓርስ፣ በአፍሪካ ቀንድ የአፍሪካ ኅብረት ተወካይ ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ ሰሞኑን በመቀሌ ያደረጉት ጉብኝት ተስፋ እንደሠጣቸው ገለጡ። ከኦባሳንጆ ጋር በጉዳዩ ዙሪያ በመገናኘት መነጋገር እንደሚፈልጉ የጠቀሱት ዲፕሎማቶቹ፣ ኦባሳንጆ በድጋሚ ወደ መቀሌ ይመለሳሉ ብለው እንደሚጠብቁ በጋራ ባወጡት መግለጫ ገልጸዋል። የሁሉም መሪዎች ትኩረት ተፈናቃዮች ክብራቸውና ደኅንነታቸው ተጠብቆ ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ማድረግ ሊሆን እንደሚገባ ዲፕሎማቶች ያሠመሩበት ሲሆን፣ ይህን ለማሳካት ማመቻመች ያስፈልጋል ብለዋል።
በኢትዮጵያ የአውሮፓ ኅብረት ልዑክ፣ የፈረንሳይ፣ የጀርመን፣ የጣሊያን፣ የስዊድን፣ የአየርላንድ፣ የካናዳና ብሪታንያ ኤምባሲዎችን ጨምሮ የበርካታ አገራት ኤምባሲዎችም፣ በኢትዮጵያ ሁሉም ወገኖች የፕሮቶሪያውን የግጭት ማቆም ስምምነት ገንቢ በሆነ መንገድ እና በቅን መንፈስ ለመተግበር ግንኙነት እንዲያደርጉ ጠይቀዋል። በአፍሪካ ቀንድ የአፍሪካ ኅብረት ተወካይ ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ ከፌደራል መንግሥቱና ከትግራይ ባለሥልጣናት ጋር ውይይቶች ማድረግ መቀጠላቸውን በበጎ ጎኑ እንደሚመለከቱት የአገራቱ ኤምባሲዎች ገልጸዋል። በሰሜን ኢትዮጵያ ያለውን ሁኔታ በቅርበት እየተከታተሉ መኾኑን የጠቀሱት ኤምባሲዎቹ፣ በሰሜን ኢትዮጵያ በድጋሚ ጦርነት የሚቀሰቀስ ከኾነ ለአካባቢው ሕዝቦች እጅግ አውዳሚ ይሆናል በማለት አስጠንቅቀዋል።
2፤ ኢዜማ፣ የአገራዊ የምክክር ኮሚሽን በአዲስ አበባ አጀንዳ ላይ ያዋቀረው የአሸማጋዮች ቡድን ያካሄደው ስብሰባ ከሕግና ከአሠራር ውጪ ነው በማለት ተቃወመ። ኢዜማ፣ ኮሚሽኑ የሥራ ቡድኖች በልዩነት ባቀረቧቸው ምክረ ሀሳቦች ላይ ውሳኔ የሚሠጡ ሌሎች አካላትን ማደራጀቱ ከማቋቋሚያ አዋጁ ጋር እንደሚጣረስ ገልጧል። የምክክር ቡድኖች ለብሄራዊ ምክክሩ ጠቅላላ ጉባኤ ያቀረቧቸውን ምክረ ሀሳቦች ብቻ እንደሚቀበል ያስታወቀው ፓርቲው፣ ተመካካሪዎች ያቀረቧቸው ምክረ ሀሳቦች ለሕዝብ ይፋ እንዲደረጉም ጠይቋል። የምክክር ጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች አተገባበር የሚከታተል ገለልተኛ እና ሕጋዊ አካል አንዲቋቋም ጭምር ፓርቲው ጠይቋል።
3፤ የኢትዮጵያ የሐምሌ ወር የዋጋ ግሽበት በሰኔ ወር ከነበረበት 13 ነጥብ 9 በመቶ ወደ 15 ነጥብ 3 በመቶ አሻቀበ። ባለፈው ሰኔ ከነበረበት 15 ነጥብ 1 በመቶ የነበረው የምግብ የዋጋ ግሽበት፣ በሐምሌ ወደ 15 ነጥብ 7 በመቶ ከፍ ማለቱን የስታትስቲክስ አገልግሎት ያወጣው መረጃ ያመለክታል። ባለፈው ሰኔ 15 ነጥብ 1 በመቶ የነበረው የምግብ የዋጋ ግሽበት በሐምሌ ወደ 15 ነጥብ 7 በመቶ ከፍ ብሏል። ምግብ ነክ ያልኾኑ ሸቀጦች የዋጋ ግሽበት ባንጻሩ በሰኔ ወር 11 ነጥብ 2 በመቶ የነበረ ሲሆን፣ በሐምሌ ወር 14 ነጥብ 8 በመቶ ደርሷል። የስጋ የዋጋ ግሽበት 21 ነጥብ 6፣ የዘይት የዋጋ ግሽበት 20 ነጥብ 3 እንዲሁም የፍራፍሬ የዋጋ ግሽበት 19 ነጥብ 2 መድረሱ ተገልጧል።
4፤ ብሄራዊ ባንክ ዛሬ ባካሄደው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ አምስት ባንኮች ብቻ ተሳተፉ። በጨረታው ከተሳተፉት ባንኮች መካከል ሁለቱ ብቻ የውጭ ምንዛሪ እንዳገኙ ባንኩ ገልጧል። በዛሬው ጨረታ አንድ ዶላር በ160 ብር ከ20 ሳንቲም እንደተሸጠ ባንኩ ጠቅሷል። በባለፈው ሳምንት ጨረታ፣ አንድ ዶላር የተሸጠው በ160 ብር ከ21 ሳንቲም ነበር። ተጫራች ባንኮች በዛሬው ጨረታ ላንድ ዶላር ያቀረቡት ከፍተኛ ዋጋ 160 ብር ከ20 ሳንቲም ሲሆን፣ ዝቅተኛው ዋጋ ደሞ 160 ብር ከ18 ሳንቲም ነው። ለጨረታው የቀረበው 125 ሚሊዮን ዶላር ሲኾን፣ የተጫራቾች ፍላጎት ግን ከ170 ሚሊዮን ዶላር በላይ እንደነበር ተገልጧል።
5፤ የአዲስ አበባ የመሬት አስተዳደር ቢሮ፣ የአርሶ አደሮች የይዞታ ማረጋገጫን ለሦስተኛ ወገን ማዘዋወር ላይ ተጥሎ የነበረውን እገዳ ከነሃሴ 14 ጀምሮ አነሳ። የከተማዋ አስተዳደር "አርሶ አደሮች መሬቱን እንዳይሸጡና ለኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ቀውስ እንዳይዳረጉ" በሚል ካለፈው ጥር ወር ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ አርሶ አደሮች የይዞታ ማረጋገጫዎችን ለሦስተኛ ወገን እንዳያስተላልፉ አግዶ ነበር። አሁን እገዳው የተነሳው፣ እገዳው በርካታ የመልካም አስተዳደር ችግሮች በማስከተሉና ተገልጋዮች ቅሬታ በማቅረባቸው መኾኑን ቢሮው ጠቅሷል።
6፤ የሶማሌ ክልላዊ መንግሥት፣ የተለየ ፍላጎት አላቸው ያላቸው አካላት ሰሞኑን በጅግጅጋ ከተማ የመድሃኒአለም ቤተክርስቲያን ያስገነባውን መቃኞ ማፍረሳቸውን ኮነነ። የድርጊቱ ፈጻሚዎች "የሐይማኖት ጸብ" ለማስነሳትና የክልሉን መልካም ገጽታ ለማጠልሸት ሞከረዋል በማለት የወነጀለው የክልሉ መንግሥት፣ ፖሊስ የድርጊቱን ፈጻሚ አካላት በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ መጀመሩን ገልጧል። መቃኞው የተገነባበት ቦታ፣ በግለሰብ ስም የተመዘገበ ይዞታ መኾኑን ማረጋገጡንም የክልሉ መንግሥት ጠቅሷል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሶማሌ አገረ ስብከት፣ በጅጅጋ ከተማ አዲስ የተሠራው የመድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን መቃኞ ቤት በኃይል መፍረሱ "ያልተጠበቀ" እና "አሳዛኝ" ድርጊት ነው በማለት አውግዟል። ድርጊቱ በአካባቢው ምዕመናን ዘንድ ከፍተኛ ሐዘን መፍጠሩን የገለጠው አገረ ስብከቱ፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት አስቸኳይ ሕጋዊ ማጣራት እንዲያደርጉ ትናንት ባወጣው መግለጫ ጠይቆ ነበር።
እንዲሁም፤
ከነገ ሐሙስ እስከ እሁድ በሀገር ፍቅር ቴአትር፣ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር እንዲሁም በዓለም ሲኒማ የሚቀርቡ ተውኔቶችን ዝርዝር እነሆ፥
ከነሐሴ 21 እስከ 24 ቀን 2018 ዓ፣ም
➤በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት
ሐሙስ ከምሽቱ 11 ሰዓት ተኩል፤ "የደመና ዳንኪረኞች"
እሁድ ከምሽቱ 11 ሰዓት፤ "የመጨረሻው ፍርድ" ተውኔቶች
➤ በዓለም ሲኒማ
ሐሙስ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ፤ "የኮኮቡ ሰው"
ዓርብ ከምሽቱ 12 ሰዓት፤ "አቧራው ጨሠ"
➤በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ቤት
ዓርብ ከምሽቱ 12 ሰዓት፤ "ዴጊያ"
ቅዳሜ ከቀኑ 7 ሰዓት ተኩል፤ "12ቱ እንግዶች"
ቅዳሜ ከምሽቱ 11 ሰዓት ተኩል፤ "በር የሌለው ቤት"
እሁድ ከቀኑ 7 ሰዓት ተኩል፤ "ንጉስ አርማህ"
እሁድ ከምሽቱ 11 ሰዓት ተኩል፤ "እምዬ ብረቷ" ይቀርባሉ [ዋዜማ] | 17 083 |
| 12 | ለቸኮለ! ማክሰኞ፣ ነሃሴ 19፣ 2018 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ ኢትዮጵያ፣ ደቡብ ሱዳን ውስጥ በተሠማሩ ሁለት ኢትዮጵያዊያን የተመድ ሰላም አስከባሪ አባላት ላይ የታጠቁ አካላት የፈጸሙትን ጥቃት አወገዘች። በጁባ የኢትዮጵያ ኢምባሲ፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት በክስተቱ ዙሪያ ባፋጣኝ ምርመራ እንዲያደርጉና ድርጊቱን የፈጸሙት አካላት በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። በአገሪቱ ጆንገሌ ግዛት ውስጥ የታጠቁ ወጣቶች ትናንት በፈጸሙት ጥቃት ሁለት ኢትዮጵያዊያን ሰላም አስከባሪዎች ተገድለው፣ ሌሎች ሰባት ሰዎች እንደቆሠሉ ተመድ አስታውቆ ነበር። ኢምባሲው፣ በአገሪቱ የሚካሄደው ግጭት በጥልቅ እንዳሳሰበው ጨምሮ ገልጧል።
2፤ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሊሴጎን ኦባሳንጆ ትናንት መቀሌ ውስጥ ሥልጣን በኃይል ከያዘው ሕወሃት-መራሹ የክልሉ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ አስተዳደሩ ከፌደራል መንግሥት ጋር ለመወያየት ቅድመ ሁኔታዎችን ማስቀመጡን ገለጠ። ቅድመ ሁኔታዎቹ፣ ፌዴራል መንግሥቱ በትግራይ ላይ ጥሎታል ያለውን የኢኮኖሚ ማዕቀብና እገዳ ማንሳት፤ ወታደራዊ ከበባን ማቆምና ውጥረት ማርገብ፤ የትግራይ ግዛቶችን ቀድሞ ወደነበሩበት መመለስ፤ ተፈናቃዮችን ደኅንነታቸውና ክብራቸው በተጠበቀ መንገድ መመለስ እና የሕወሓትን ፖለቲካዊና ሕጋዊ ማንነት መመለስ የሚሉ ናቸው። አስተዳደሩ፣ ትርጉም ያለው፣ ገንቢና ለውጥ የሚያመጣ የሰላም ውይይት በማንኛውም ጊዜና ሁኔታ ለማካሄድ ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጧል። በሰኔው ተመሳሳይ ውይይት መሠረት ኦባሳንጆ ትርጉም ያለው ክትትልና ቁጥጥር አላደረጉም በማለት የተቸው አስተዳደሩ፣ ኦባሳንጆ ከፌደራል መንግሥቱ ጋር ተወያይተው በአንድ ወይም ሁለት ሳምንት ውስጥ ወደ ትግራይ እንደሚመለሱ ገልጸዋል ብሏል።
3፤ በትግራይ ክልል መቐለ ቅርንጫፍ የፓስፖርት አገልግሎት ከየካቲት ጀምሮ በመቋረጡ ተገልጋዮች ለከፋ እንግልት እንደተጋለጡ ዋዜማ ሠምታለች፡፡ የፓስፖርት አገልግሎት ፈላጊዎች ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ከፍተኛ ወጪ እንደሚያወጡና የኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎትም የጊዜያዊ አስተዳደሩ ማኅተም ያላረፈባቸውን ሠነዶች አልቀበልም በማለት ለእንግልት እንደዳረጋቸው ገልጸዋል። ተገልጋዮች፣ ከመደበኛው መስፈርት ውጪ ተቋሙ ተጨማሪ ሠነዶችን እንዲያቀርቡ እንደሚጠይቃቸውም ተናግረዋል። ተቋሙ በበኩሉ፣ የኤርትራና የትግራይ ተወላጆች የባሕልና የቋንቋ መመሳሰል ስላላቸው ልዪ ጥንቃቄ እንደሚያደርግ አንድ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የተቋሙ ባልደረባ ለዋዜማ ገልጸዋል።
4፤ ኢትዮጵያ እኤአ በ2028 የሚካሄደውን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ ጥያቄ ማቅረቧን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ለመጨረሻ ጊዜ ያስተናገደችው ከ50 ዓመታት በፊት ነበር። በቀጣዩ ዓመት የሚካሄደውን የአፍሪካ ዋንጫ በጋራ የሚያዘጋጁት፣ ኬንያ፣ ታንዛኒያ እና ኡጋንዳ ናቸው። የኢትዮጵያ ብሄራዊ እግር ኳስ ቡድን፣ በዓለማቀፉ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ባወጣው የደረጃ ሠንጠረዥ ከ211 አገራት 143ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
5፤ አሜሪካ፣ የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት በሱዳን ላይ የጦር መሳሪያ ማዕቀብ እንዲጥል ጠየቀች። ማዕቀቡ ድሮኖችን ጭምር መሸፈን እንዳለበት አሜሪካ አሳስባለች። ጥያቄውን ያቀረቡት የፕሬዝዳንት ትራምፕ የዓረብና አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ማሳድ ቡሎስ፣ የሱዳኑ ጦርነት ከቀጠለ ጎረቤት አገራትን ጎትቶ ሊያስገባ ይችላል በማለት አስጠንቅቀዋል። ሱዳን እና ሩሲያ፣ መላዋን ሱዳን የሚሸፍን የጦር መሳሪያ ማዕቀብ መጣል የአገሪቱን ጦር ሠራዊት ይጎዳል በማለት ስጋታቸውን ገልጠዋል። የጸጥታው ምክር ቤት ከ20 ዓመት በፊት ዳርፉር ግዛት ላይ ብቻ ተፈጻሚ እንዲሆን የጣለው የጦር መሳሪያ ማዕቀብ የአሁኑ ዙር የቆይታ ጊዜው በቀጣዩ ወር ያበቃል።
እንዲኹም፤
1፤ የአንጋፋው ድምጻዊ መሐሙድ አህመድ የመጨረሻ ሥራ እንደሆነ የተነገረለት የሙዚቃ አልበም ለአድማጮች ሊቀርብ እንደሆነ ተሠምቷል። ይህ አልበም "ለታሪክ" የተሠኘ ርዕስ የተሠጠውና ከ6 ዓመታት በፊት የተጠናቀቀ እንደሆነ ተነግሯል። በአልበሙ ዙሪያ ነገ ረቡዕ ረፋድ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሠጥም ዋዜማ ከአዘጋጆቹ ሠምታለች።
2፤ የገጣሚ ምልዕቲ ኪሮስ "ደምፀ ቃል" የተሠኘ አዲስ መጽሐፍ ለአንባቢያን ሊቀርብ ነው። መጽሐፉ ነገ ከ11 ሰዓት ተኩል ጀምሮ በያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት የተለያዩ እንግዶች በተገኙበት ተመርቆ ለንባብ ይበቃል። [ዋዜማ] | 19 016 |
| 13 | የትግራይ ነዋሪዎች ፓስፖርት ለማውጣት አዲስ አበባ መምጣት ይገደዳሉ፣ እሱም ከተሳካ!
የዋዜማን ዝርዝር ዘገባ ያንብቡ- https://cutt.ly/UyghIjTX | 19 364 |
| 14 | ለቸኮለ! ሰኞ፣ ነሃሴ 18፣ 2018 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ ዛሬ ረፋዱ ላይ በደቡባዊ እና ሰሜን ምዕራብ የትግራይ አካባቢዎች የድሮን ጥቃቶች እንደተፈጸሙ የክልሉ የዜና ምንጮች ዘገቡ። በደቡብ ትግራይ ዞን ራያ አዘቦ ወረዳ ሁለት የድሮን ጥቃቶች እንደተፈጸሙ የዞኑ ባለሥልጣናት መናገራቸውን የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል። በጥቃቱ በሲቪሎች ንብረትና በመስኖ እርሻ ልማት ላይ ጉዳት መድረሱን ዘገባው ጠቅሷል። በሰሜን ምዕራብ ዞን እንዳባጉና ወረዳ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት ደሞ፣ በሲቪሎች መኖሪያዎች ላይ ጉዳት አድርሷል መባሉን ዘገባው አመልክቷል። ባለሥልጣናቱ ለጥቃቱ ፌደራል መንግሥቱን ተጠያቂ አድርገዋል ተብሏል። ጥቃቶቹ በተፈጸሙባቸው አካባቢዎች በሰዓቱ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ይኑር አይኑር ለጊዜው አልታወቀም።
2፤ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የደገም ወረዳ ዋና አሥተዳዳሪ ተፈራ ደሴ ትናንት እሁድ ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው አማጺ ቡድን በፈጸመው ጥቃት መገደላቸውን ዋዜማ ሠምታለች። በጥቃቱ ለጊዜው ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ የመከላከያ ሠራዊት፣ የኦሮሚያ ፖሊስ እና የክልሉ ሚሊሺያ አባላትም ሕይወታቸው ማለፉን ምንጮች ነግረውናል። ተፈራ የተገደሉት፣ ከመከላከያ ሠራዊት፣ ከክልሉ ፖሊስና ሚሊሺያ አባላት ጋር "ጋር ኢሌ" በተባለ ቦታ የጸጥታ ሥራ በማከናወን ላይ ሳሉ እንደኾነ ዋዜማ ተረድታለች።
3፤ በጋምቤላ ክልል አቦል ወረዳ ማነታቸ ያልታወቁ ታጣቂዎች ትናንት ጧት ባንድ የሕዝብ ማጓጓዣ አውቶቡስ ላይ በፈጸሙት ጥቃት አንድ ሰው ተገድሎ አራቱ መቁሠላቸውን ዋዜማ ሠምታለች። በክልሉ በተለይ በኢታንግ ልዩ ወረዳ ውስጥ በሕዝብ ትራንስፖርት ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች በተደጋጋሚ ይፈጸማሉ። ባለፈው ወር አጋማሽ ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች ወደ ኢታንግ ከተማ በተሽከርካሪ በመጓዝ ላይ የነበሩ የመንግሥት ሠራተኞች ላይ በፈጸሙት ጥቃት፣ እንድ የአካባቢውን ሹመኛ ገድለው ሁለቱን ማቁሠላቸውን ዋዜማ መዘገቧ ይታወሳል።
4፤ በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ደጀን ወረዳ፣ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሐይማኖት አባቶችና በ"ቅባት" እምነት አራማጆች መካከል የተፈጠረው አለመግባባት በእርቅ ተፈትቷል ተባለ። የ"ቅባት" እምነት አራማጅ አባቶች ያለ ቤተክርስቲያኗ ቤተ-ክህነት ፍቃድ ያሳተሟቸውን ማኅተሞችና የገቢ መሰብሰቢያ ደረሠኞች ለመመለስና አስተምህሯቸውንና ለመተው እንደተስማሙ የወረዳው አስተዳደር ገልጧል። ቤተክርስቲያኗ በእምነቱ አራማጆች ላይ የጣለቻቸው እግዶችም እንደተነሱ ተገልጧል። የ"ጸጋ" እና የ"ቅባት" እምነት ልዩነት፣ እየሱስ ክርስቶስ ቅዱስን ከተቀባበት ጊዜ ጋር የተያያዘ እንደኾነ ይታወቃል።
5፤ የሱዳን ወታደራዊ መንግሥት፣ "ከኢትዮጵያ ግዛት የተነሳ" ድሮን ትናንት ብሉ ናይል ግዛት ውስጥ መትቼ ጥያለሁ አለ። የሱዳን መከላከያ ሚንስቴር፣ ድሮኑ ተመትቶ የወደቀው የድንበር ከተማ በሆነችው ኩርሙክ አካባቢ መኾኑን ገልጧል። የድሮኑ ዒላማ ምን እንደነበር፣ የድሮኑ ባለቤት ወይም የድሮኑ ሥሪት የት አገር እንደኾነ መረጃ ይኑረው አይኑረው ሚንስቴሩ አልጠቀሠም። የኢትዮጵያ ጦር ሠራዊት በዚሁ ውንጀላ ዙሪያ ለጊዜው ያለው ነገር የለም። የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል፣ ኩርሙክ ከተማን ከሱዳን ጦር ሠራዊት በከሳምንት በፊት በማስለቀቅ መልሶ መቆጣጠሩ ይታወሳል።
6፤ የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ባድር አብደላቲ፣ በአፍሪካ ቀንድ ከዓለማቀፍ ሕግጋት ጋ በተጻረረ መንገድ የባሕር በር ለማግኘት ይደረጋሉ ያሏቸውን ጥረቶች አገራቸው እንደምትቃወም ለፕሬዝዳንት ትራምፕ የዓረብና የአፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ማሳድ ቡሎስ ተናገሩ። እነዚህ በኃይል የሚካሄዱ ጥረቶች መቆም አለባቸው ያሉት አብደላቲ፣ የቀጠናው አገራት "አንድነት"፣ "ሉዓላዊነት" እና "የግዛት አንድነት" ሊከበር ይገባል በማለት ከቡሎስ ጋር ትናንት በስልክ ባደረጉት ውይይት አጽንዖት እንደሠጡ የግብጽ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። የባሕር በር በኃይል ለማግኘት ይደረጋሉ ያሏቸው ጥረቶች የየትኛው አገር ጥረቶች እንደኾኑ አብደላቲ ባይጠቅሱም፣ ኢትዮጵያ ግን ቀይ ባሕር ላይ የባሕር በር ማግኘት የኅልውና ጉዳይ መኾኑን ደጋግማ ስትገልጥ ቆይታለች።
7፤ በደቡብ ሱዳን ጆንገሌ ግዛት በተመድ ሰላም አስከሪዎች ተሽከርካሪ ላይ የታጠቁ አካላት በዛሬው ዕለት በፈጸሙት ጥቃት ሁለት ሰላም አስከባሪዎች ተገደሉ። በጥቃቱ ሌሎች ሰባት ቆስለዋል ተብሏል። አሜሪካ፣ ጥቃቱን የፈጸሙት የታጠቁ ወጣቶች ናቸው በማለት ጁባ በሚገኘው ኢምባሲዋ በኩል ባወጣችው መግለጫ ድርጊቱን ክፉኛ አውግዛለች። በጥቃቱ ላይ ሙሉ እና ግልጽ ምርመራ እንዲደረግ ያሳሰበችው አሜሪካ፣ ለጥቃቱ ተጠያቂ የኾኑ አካላት ለፍርድ እንዲቀርቡም ጠይቃለች።
እንዲሁም፤
1፤ የሞሶብ ባንድ አባላት ልዩ የሙዚቃ ዝግጅታቸውን ዛሬ ከምሽቱ 2 ሰዓት ከ30 ጀምሮ በሞሶብ የሙዚቃ ማዕከል ያቀርባሉ።
2፤ በደራሲና አዘጋጅ ፉዓድ ሙስጠፋ የተዘጋጀው "ሐምራዊት" የተሠኘው አዲስ ፊልም ለዕይታ ሊበቃ ነው። ፊልሙ ነገ ነሐሴ 19 ቀን ከ11 ሰዓት ጀምሮ ፍላሚንጎ በሚገኘው አዲሱ ሕፃናትና ወጣቶች ቴአትር አዳራሽ ተመርቆ ለዕይታ እንደሚበቃ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል። [ዋዜማ] | 22 770 |
| 15 | ለቀሩ ስራዎች ፣ አዳዲስ የምክክር ኮምሽነሮች ይሾማሉ?
በየካቲት ወር 2014 ዓ.ም ሥራ የጀመረው ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን፤ ለሁለት ያህል ጊዜያት የሥራ ዘመኑ እንደተራዘመለት የሚታወስ ሲሆን፤ ከየካቲት 14 ቀንን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለስምንት ወራት ያህል የተራዘመለት የሥራ ጊዜ ጥቅምት 14 ቀን፣ 2019 ዓ.ም ይጠናቀቃል። ለቀሩ ስራዎች ፣ አዳዲስ የምክክር ኮምሽነሮች ይሾማሉ? የዋዜማን ዘገባ ያንብቡ - https://cutt.ly/1yfLf5fd | 21 832 |
| 16 | بدون متن... | 1 |
| 17 | ለቸኮለ! ቅዳሜ፣ ነሃሴ 16፣ 2018 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ጉባኤ ዛሬ የመዝጊያ ሥነ ሥርዓቱን አካሂዷል። ኾኖም የምክክር ጉባኤው ትናንት ምሽት የተካሄደው ምልዓተ ጉባኤ መሟላቱ ሳይረጋገጥ መኾኑን ዋዜማ ሠምታለች። ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ የክልል ተወካዮች ጉባኤ ያዋቀረው የሽምግልና ቡድን ያቀረበውን አዲስ አበባን የተመለከተ ምክረ ሀሳብ ለጠቅላላ ጉባኤው ሲያነቡ፣ የአማራ ክልል ተወካዮች ከአዳራሽ ወጥተው እንደነበርና የተወሠኑት በኮሚሽነሮች ልመና እንደተመለሱ ምንጮች ገልጸዋል። ተወካዮቹ፣ ኮሚሽነሮች በአዲስ አበባ ዙሪያ ያከራከረው ምክረ ሀሳብ ለጉባኤው የሚቀርበው በሥራ ቡድን ደረጃ የጸደቀው ምክረ ሀሳብ ብቻ ነው በማለት የሠጡንን ማረጋገጫ አፍርሠዋል በማለት ቅሬታ ማሠማታቸው ታውቋል።
የአሸማጋይ ኮሚቴው አማራጭ ምክረ ሀሳቦች፣ ሁሉም ክልሎች ዋና ከተማቸውን እንዲመርጡ በሕገመንግሥቱ እንዲደነገግ ወይም አዲስ አበባ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ ከተማ መኾኗ በሕገመንግሥቱ እንዲሠፍር የሚጠይቁ ናቸው።
2፤ እናት ፓርቲ፣ ለአገራዊ ምክክሩ ጉባኤ ውሳኔ ሙሉ በሙሉ እውቅና እንደማይሠጥ አስታወቀ። ፓርቲው፣ ምክክሩ ተጨባጭና አዎንታዊ ውጤት እንዳያስገኝና በአገሪቱ ቀውስ ላይ ተጨማሪ ቀውስ እንዲፈጠር ያደረጉት የኦሮሚያ ብልጽግና እና ገዢው ፓርቲ ናቸው በማለት ከሷል። ሕዝቡ ከአገራዊ የምክክር ጉባኤው የሚወጡ "አሳሳች" ውሳኔዎችንና ሠነዶችን እንዳይቀበልና እንዲቃወም ፓርቲው ጥሪ አድርጓል፡፡
አብን በበኩሉ፣ ለምክክር ሂደቱ ሙሉ በሙሉ ይሁንታ የሚሠጠው አገራዊ የምክክር ኮሚሽን በምክክር ጉባኤው ማጠቃለያ ላይ ስለተፈጸመው "ሕገወጥ ጣልቃ ገብነት"፣ ባለቀ ሰዓት በተጨመረው አጀንዳ አመጣጥና ዓላማ እንዲሁም "አድሏዊ" አቋም ባራመዱ አንድ ኮሚሽነር ዙሪያ ግልጽ ማብራሪያ ሲሠጥ መኾኑን አስታውቋል። ፓርቲው፣ በስምንቱ አጀንዳዎች ላይ በተያዙ ቃለጉባኤዎች መሠረተ ለጉባኤው ለተነበቡ የስምምነት ማጠቃለያዎች ብቻ ዕውቅና እንደሚሠጥም ገልጧል። የተወሠኑ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት እንዲኹም ጥቂት የኮሚሽኑ አባላትና ባለሙያዎች የምክክር ጉባኤው ስምምነት የደረሠባቸውን ውጤቶች ለማዛባት በግልጽ "ወገንተኝነት" አሳይተዋል በማለት ፓርቲው ከሷል።
3፤ የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከወሠዱ 550 ሺሕ 210 ተማሪዎች መካከል 70 ሺሕ 544ቱ ብቻ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ማለፊያ ውጤት አስመዘገቡ። ትምህርት ሚንስቴር፣ ማለፊያ ውጤት ያመጡት ከጠቅላላ ተፈታኞች 12 ነጥብ 8 በመቶዎቹ ብቻ መኾናቸውን ማምሻውን በሠጠው መግለጫ አስታውቋል። በመላ አገሪቱ ለፈተናው ተመዝግበው የነበሩት 563 ሺሕ 960 ተማሪዎች ነበሩ። ከማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች 8 ነጥብ 3 በመቶዎቹ ብቻ ሲያልፉ፣ ከተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ደሞ 16 ነጥብ 5 በመቶዎቹ ማለፊያ ውጤት አስመዝግበዋል ተብሏል።
ከተፈጥሮ ሳይንስ ወንድ ተፈታኞች ከ600 ከተያዘው ነጥብ 591 ነጥብ 6 ያስመዘገብው የአዳማ የኦዳ ስፔሻል ቦርዲንግ ተማሪ ሲኾን፣ ከሴት ተፈታኞች የእንጅባራ አገው ምድር ትምህርት ቤት ተማሪ 583 ነጥብ ማስመዝገቧ ተገልጧል።
4፤ የኢትዮጵያ አበዳሪ አገራት ኮሚቴ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት እና የ1 ቢሊዮን ዶላር ቦንድ ያዥ ዓለማቀፍ ኢንቨስተሮች የቦንዱን አከፋፈል እንደገና ለማዋቀር ባለፈው ሰኔ ወር በመርህ ደረጃ የደረሱበትን ስምምነት አጸደቀ። ኮሚቴው፣ ስምምነቱ 'ሁሉም አበዳሪዎች በእኩል መታየት አለባቸው' ከሚለው የቡድን 20 ማዕቀፍ መርህ ጋር የተጣጣመ መኾኑን ገልጧል። የአበዳሪ አገራት ኮሚቴ ስምምነቱን ማጽደቁ፣ ኢትዮጵያ ስምምነቱን ተግባራዊ ማድረግ እንድትጀምር ያስችላታል። ኾኖም ስምምነቱ ቦንድ ያዦች ወደፊት በገበያ በሚወሠን ወለድ ከኢትዮጵያ የ1 ቢሊዮን ዶላር ቦንድ እንዲገዙ መፍቀዱ፣ ቦንድ ያዦች ከአበዳሪ አጋራት በተለየ እንዲጠቀሙ ሊያደርግ ይችላል የሚል ስጋት እንዳለው ኮሚቴው ገልጧል።
5፤ ኢትዮጵያ ዳንጎቴ ኬንያ ውስጥ ከሚገነባው የነዳጅ ማጣሪያ ኩባንያ የአክሲዮን ድርሻ የመግዛት ፍላጎት እንዳላት ብሉምበርግ ዘገበ። ኩባንያው የምሥራቅ አፍሪካ አገራት በድምሩ የ30 በመቶ ድርሻ እንዲገዙ ፈቅዷል። ኬንያ፣ በግማሽ ቢሊዮን ዶላር የ10 በመቶ ድርሻ የመግዛት ፍላጎት እንዳላት ከወዲሁ አስታውቃለች። ነዳጅ ማጣሪያው ከኬንያና ኡጋንዳ ድፍድፍ ነዳጅ በመግዛት በቀን 700 ሺሕ በርሜል ድፍድፍ የማጣራት አቅም ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
እንዲሁም:-
1.ድምጻዊት ተዓምር ግዛው "በፍቅር" የተሰኘ የመጀመሪያ የሙዚቃ አልበሟን የፊታችን ቅዳሜ ነሐሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም በዓለም አቀፍ የሙዚቃ ማሰራጫ መተግበሪያዎች በኩል ለአድማጮች ልታቀርብ መሆኑን ይፋ አድርጋለች።
2.ዐውደ ፋጎስ 91ኛ ዙር ውይይት ነገ ነሐሴ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ በወመዘክር አዳራሽ ይካሄዳል።በዚህኛው ዙር ግዛቸው ጥጋቡ "የፊደል ፍልስፍና እና የመጽሐፍ አተረጓጎም ሳይንስ" በሚል ርዕስ የውይይት መነሻ ሀሳብ ያቀርባል። [ዋዜማ] | 22 249 |
| 18 | አዲስ አበባን በተመለከተ በሽምግልና የተጨመረው “ምክረ ሃሳብና” የቀጠለው ውዝግብ
......የክልሉ ተወካዮች ከአዳራሽ መውጣትን ተከትሎ የክልሉ አመራሮች ተወካዮቹን እንዳነጋገሩ የገለጡት የዋዜማ ምንጮች፤ በአመራሮቹ ጥረት “የተወሰኑ” ተመካካሪዎች ወደ አዳራሽ መመለሳቸውን ጠቁመዋል።
ጉዳዩ ውሳኔ የተሰጠበት አለመሆኑን የገለጡት የክልሉ አመራሮች፤ ኮሚሽኑ ለሀገር ይበጃል ያለውን ውሳኔ እንደሚያስተላልፍ ያላቸውን እምነት በመግለጥ ተመካካሪዎችን ለማግባባት መሞከራቸውንም ሰምተናል። በክልሉ ፕሬዝዳንት አረጋ ከበደ መሪነት ወደ ጉባኤው የተመለሱ ተመካካሪዎች የጉባኤውን ሂደት አጠናቅቀው መውጣታቸውንም ምንጮች ጠቁመዋል። የዋዜማን ዘገባ ያንብቡ- https://cutt.ly/ZyfkhEWA | 22 013 |
| 19 | ለቸኮለ! ዓርብ፣ ነሃሴ 15፣ 2018 ዓ፣ም የዋዜማ ዐበይት ዜናዎች
1፤ በአገራዊ ምክክር ጉባኤው 300 ያህል የኦሮሚያ ክልል ተመካካሪዎች፣ አዲስ አበባ የኦሮሚያ ክልል መቀመጫ መኾኗን የሚያረጋግጥ ድንጋጌ በሕገመንግሥቱ ይካተት የሚለው ጥያቄያችን አማራጭ የሌለው ምክረ ሀሳብ ኾኖ ካልተያዘ ከጉባኤው እንወጣለን በማለት ማስጠንቀቃቸውን ዋዜማ ሠምታለች። የአገራዊ ምክክር ኮሚሽንም፣ የጋራ ማረጋገጫ ቡድኑ ያመሳከራቸውን ምክረ ሀሳቦች ከማቅረቡ በፊት ስብሰባ ያልጠራውን የክልል ተወካዮች ጉባኤ ትናንት ሰብስቦ የኦሮሚያ ተመካካሪዎችን ቅሬታ አቅርቧል። የክልል ተወካዮች ጉባኤ፣ ቅሬታውን መርምሮ የመፍትሄ ሀሳብ የሚያቀርብ የ11 ክልሎች ፕሬዝዳንቶች፣ የሁለቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች፣ ሦስት የትግራይ ተወካዮች፣ አምስት የሃይማኖቶች ተወካዮች፣ ሦስት የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሁለት የወጣቶች ተወካዮች የተካተቱበት ኮሚቴ አቋቁሟል።
ኾኖም በርካታ ተመካካሪዎች፣ የኦሮሚያ ተመካካሪዎች ቅሬታ ከምክክር ሂደቱ የወጣና ሂደቱን ወደ ኋላ የሚመልስ ነው የሚል ተቃውሞ አሠምተዋል ተብሏል። ለሥራ ቡድኖች ከቀረቡት 476 ምክረ ሀሳቦች ውጭ አዲስ የሚጨመር ወይም የሚቀነስ ምክረ ሀሳብ ካለ፣ ራሳቸውን ከጉባኤው ለማግለል የወሠኑ ተመካካሪዎች መኖራቸውም ታውቋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን፣ የምክክር ጉባኤው በእያንዳንዱ አጀንዳ ላይ የተጠናቀሩትን የመጨረሻ ምክረ ሀሳቦች በማዳመጥ ላይ መኾኑን ዛሬ ማምሻውን ገልጧል። የምክክር ጉባኤው የተጠራው፣ የኦሮሚያ ተወካዮችን ቅሬታ ይመረምራል የተባለው የክልል ተወካዮች ገባኤ ምን መፍትሄ አቅርቦ እንደኾነ ግን ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ ማወቅ አልተቻለም።
2፤ ሥልጣን በኃይል የተቆጣጠረው ሕወሃት-መራሹ የትግራይ አስተዳደር፣ ትግራይ ሕዝቧንና ግዛቷን ከጥቃት ለመከላከል በቂ አቅም አላት አለ። የክልሉ አስተዳደር ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ እስካሁን ያሳየው ትዕግስት እንደ ድክመት ወይም የትግራይ ሕዝብ ራሱን መከላከል እንደማይችል ተደርጎ መቆጠር የለበትም በማለት አጽንዖት ሠጥቷል። በትግራይ ላይ የሚፈጸሙ ተደጋጋሚ ጥቃቶችን ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ እንዲያወግዝና ሁኔታው ተባብሶ ወደለየለት ጦርነት እንዳያመራ ጣልቃ እንዲገባም አስተዳደሩ ጠይቋል። አስተዳደሩ፣ ፖለቲካዊ ልዩነቶችን በንግግር ለመፍታት አሁንም ዝግጁ መኾኑን ገልጧል።
በሌላ በኩል፣ የትግራይ ትምህርት ቢሮ፣ ትናንት መቀሌ ውስጥ የድሮን ጥቃት የተፈጸመው በመምህራን መኖሪያ ላይ ነው በማለት ከሷል። ቢሮው፣ በጥቃቱ 14 መምህራን እና ቤተሰቦቻቸው የመቁሰል ጉዳት እና በመምህራን ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን ጠቅሷል። የክልሉ መምህራን ማኅበርም፣ የድሮን ጥቃቱ በመምህራን መኖሪያ ቤቶች ላይ እንደተፈጸመ በመግለጽ አውግዟል።
3፤ በኢትዮጵያ የወባ በሽታ አስተላላፊ ተሕዋሲያን ዘረ መላቸውን በመቀያየር መድሃኒት የመቋቋም አቅማቸው በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን ጤና ሚንስቴርና የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከአሜሪካ ተመራማሪዎች ጋር ባደረጉት ጥናት አረጋገጡ። በአገሪቱ ከስድስት ዓመት በፊት 1 ሚሊዮን የነበረው በወባ የተያዙ ሰዎች ቁጥር በአውሮፓዊያኑ 2024 ወደ 10 ሚሊዮን አሻቅቧል። መድሃኒቶችን የሚቋቋሙ በርካታ የወባ ተኅዋሲያን ዝርያዎች በስፋት መሠራጨታቸውን ጥናቱ አሳይቷል። ኾኖም መድሃኒቶችን የሚቋቋሙ ተሕዋሲያን መበራከት በአገሪቱ ውስጥ የወባ በሽታ ለመጨመሩ ዋነኛ ምክንያት አይደለም ያለው ጥናቱ፣ የወባ መቆጣጠሪያ ፕሮግራሞች መቋረጥና የአየር ንብረት ለውጥ አስተዋጽዖ እንዳደረጉ ገልጧል። በሽታውን በመከላከል ላይ ትልቅ ትኩረት ማድረግና የበሽታ ምርመራን ማስፋፋት ከፍተኛ ትኩረት እንዲሠጠው ጥናቱ አሳስቧል።
4፤ የኢትዮጵያና ቻይና ኩባንያዎች የ330 ሚሊዮን ዶላር ግምት ያላቸው 33 የትብብር ስምምነቶች ሰሞኑን ተፈራረሙ። አዲስ አበባ ላይ በተካሄደው የሁለቱን አገራት የወጪ ንግድ ለማሳደግ ባለመ መድረክ ላይ ከ200 በላይ የኢትዮጵያ እና ቻይና ኩባንያዎች ተሳትፈዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ኢትዮጵያ ወደ ቻይና የምትልከው የወጪ ምርት 369 ሚሊዮን ዶላር መድረሱን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስትር ካሳሁን ጎፌ በመድረኩ ላይ ተናግረዋል። ካሳሁን፣ ባለፉት አምስት ዓመታት ብቻ ኢትዮጵያ ወደ ቻይና ገበያ የምትልከው ምርት በ92 በመቶ ማደጉንም ገልጸዋል። ቻይና ያለ ታሪፍ በርካታ ምርቶቻቸውን እንዲልኩ ከፈቀደችላቸው የአፍሪካ አገራት አንዷ ናት።
5፤ ነገ ቅዳሜ በመቀሌ እንዲካሄድ ታቅዶ የነበረው የአሽንዳ ዓመታዊ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሠረዘ። የአሸንዳ በዓል ማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት የተሠረዘው፣ በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች በሚካሄደው የድሮን ጥቃት ሳቢያ መኾኑን የትግራይ ባሕልና ቱሪዝም ቢሮ ገልጧል። የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች አንቂዎች፣ በክልሉ በሴቶች ላይ የሚፈጸመሙ ተደጋጋሚ ጥቃቶችን በመቃወም ሴቶች በዓሉን ጥቁር በመልበስና "ጥቁር አሸንዳ" በሚል መሪ ቃል እንዲያከብሩት ቅስቀሳ ሲያደርጉ ነበር። ይህንኑ ተከትሎ፣ የክልሉ ቱሪዝም ቢሮ ከመደበኛው ባሕላዊ ስነ ሥርዓት ውጪ ሌላ እንቅስቃሴ ማድረግ አይቻልም ሲል ሰሞኑን ማስጠንቀቂያ አውጥቶ እንደነበር አይዘነጋም።
6፤ የተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች፣ በተለያዩ የሙያ መደቦች ለሚቀጠሩ የውጭ ዜጎች ዝቅተኛው ወርሃዊ ደመወዝ አራት ሺሕ ድርሃም ወይም 1 ሺሕ 80 ዶላር ገደማ እንዲኾን ወሠነች። የአገሪቱ መንግሥት የውጭ ዜጎች የሚሠማሩባቸውን ሁሉንም የሙያ መስኮች በዘጠኝ መደቦች ደልድሏቸዋል። የውጭ ዜጎች የሚቀጠሩባቸው የሙያ ዘርፎች በዘጠኝ መደቦች የተከፈሉት፣ የዓለም የሥራ ድርጅትን የሙያ ደረጃ መስፈርቶች መሠረት በማድረግ መሆኑን የአገሪቱ መንግሥት ገልጧል። ከዘጠኙ የሙያ መደቦች መካከል፣ ከድርጅት ማናጀርነት፣ ከኮንስትራክሽን፣ ከግብርና፣ ከአገልግሎትና ሽያጭ እና ከማዕድን ዘርፍ ጋር የተያያዙ ምድቦች ይገኙበታል። ኢትዮጵያ ከቤት ሠራተኞች በተጨማሪ በቅርቡ በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የሠለጠኑ ባለሙያዎችን ወደ ኢምሬቶች መላክ መጀመሯ ይታወሳል።
እንዲሁም፤
1፤ "ግራመር ኦፍ ሂሊንግ" የተሠኘና በሥነ-ልቦናዊ ጉዳት፣ በትዝታ እና በፈውስ ዙሪያ ያተኮሩ የሥነ-ጥበብ ሥራዎች የሚቀርቡበት ኤግዚቢሽን ከነገ ነሐሴ 16 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን ድረስ ቦሌ በሚገኘው ስቱዲዮ 11 የሥዕል ማሳያ ውስጥ ይካሄዳል።
2፤ "እቴጌ ጣይቱ እና ዳግማዊ ምኒልክ፤ ኢትዮጵያ ከ1883 እስከ 1910" በተሠኘው የትርጉም መጽሐፍ ዙሪያ የተዘጋጀ የመጽሐፍ ፊርማ ሥነ ሥርዓት ነገ ቅዳሜ ነሐሴ 16 ቀን ከቀኑ 8 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ድረስ በጃዕፈር መጽሐፍት መደብር ይካሄዳል። በመርሃ ግብሩ ላይ የመጽሐፉ ተርጓሚዎች ሕይወት ተፈራ እና ዮርዳኖስ አልማዝ ሠይፉ ይገኛሉ። [ዋዜማ] | 21 596 |
| 20 | ምክክሩ አጣብቂኝ ውስጥ ገብቷል
በምክክር ጉባዔው ማብቂያ የኦሮሚያ ክልል ተወካዮች አዲስ ምክረ ሃሳብ እንዲካተትላቸው ያቀረቡት ጥያቄ አጠቃላይ የምክክሩን አጀንዳዎች የማጠቃለያ ጉባዔ አራዝሞታል።
"በተዘጋ ጉዳይ ላይ" ለኦሮሚያ ጥያቄ ተብሎ አሰራሩ ከተጣሰ "ራሳችንን ከምክክሩ እናገላለን" ያሉ የአማራ ክልል ተወካዮች ጉዳዩን በአትኩሮት እየተከታተሉ ነው። የዛሬው ውሎ የጉባዔውን ቀጣይ ዕጣ ፈንታ ይወስናል። የዋዜማን ዘገባ ያንብቡ- https://cutt.ly/syfqEdNA | 20 445 |
