fa
Feedback
Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

رفتن به کانال در Telegram

#ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ #Orthodox ​📜 #የዕለቱ #ስንክሳር (#የቅዱሳን_ታሪክ) 💡 የአባቶች ምክርና ትምህርት 📖 ​ሕይወትን የሚቀይሩ ጥልቅ የአባቶች ምክር እና ትምህርቶች ይተላለፋሉ። ​ከቅዱሳት መጻሕፍት የተቀሰሙ ለነፍስ ምግብ የሚሆኑ ቁምነገሮች ይገኛሉ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

کانال Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ (@orthodoxtewahedotrue) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 171 513 مشترک است و جایگاه 139 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 132 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 171 513 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 13 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -3 264 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -173 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 3.68% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 2.48% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 6 310 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 4 258 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 53 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
#ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ #Orthodox ​📜 #የዕለቱ #ስንክሳር (#የቅዱሳን_ታሪክ) 💡 የአባቶች ምክርና ትምህርት 📖 ​ሕይወትን የሚቀይሩ ጥልቅ የአባቶች ምክር እና ትምህርቶች ይተላለፋሉ። ​ከቅዱሳት መጻሕፍት የተቀሰሙ ለነፍስ ምግብ የሚሆኑ ቁምነገሮች ይገኛሉ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 14 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

171 513
مشترکین
-17324 ساعت
-8857 روز
-3 26430 روز

در حال بارگیری داده...

ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
ژوئیه '26
ژوئیه '26
+297
در 72 کانال‌ها
ژوئن '26
+527
در 89 کانال‌ها
Get PRO
مه '26
+987
در 90 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '26
+1 819
در 96 کانال‌ها
Get PRO
مارس '26
+3 830
در 155 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '26
+1 497
در 91 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '26
+1 638
در 92 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '25
+2 131
در 95 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '25
+2 940
در 101 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '25
+2 233
در 101 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '25
+3 122
در 95 کانال‌ها
Get PRO
اوت '25
+5 714
در 91 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '25
+3 189
در 87 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '25
+7 256
در 88 کانال‌ها
Get PRO
مه '25
+9 492
در 20 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '25
+11 161
در 30 کانال‌ها
Get PRO
مارس '25
+9 101
در 75 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '25
+9 362
در 5 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '25
+13 003
در 78 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '24
+12 895
در 25 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '24
+11 669
در 90 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '24
+14 156
در 82 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '24
+18 424
در 86 کانال‌ها
Get PRO
اوت '24
+20 997
در 87 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '24
+19 885
در 91 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '24
+16 756
در 91 کانال‌ها
Get PRO
مه '24
+18 029
در 99 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '24
+9 737
در 94 کانال‌ها
Get PRO
مارس '24
+5 719
در 97 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '24
+7 644
در 121 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '24
+5 472
در 58 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '230
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '230
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '230
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '23
+6
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '23
+22
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '23
+7
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '23
+23
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '23
+35
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '23
+14
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '23
+18
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '23
+21
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '23
+11
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '22
+10
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '22
+18
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '22
+46
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '22
+35
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '22
+65
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '22
+76
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '22
+63
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '22
+33
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '22
+35
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '22
+27
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '22
+24
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '22
+54
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '21
+24
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '21
+60
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '21
+116
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '21
+164
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '21
+190
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '21
+201
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '21
+220
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '21
+153
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '21
+215
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '21
+397
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '21
+431
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '21
+303
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '20
+2 667
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
14 ژوئیه0
13 ژوئیه0
12 ژوئیه+85
11 ژوئیه0
10 ژوئیه0
09 ژوئیه0
08 ژوئیه0
07 ژوئیه0
06 ژوئیه0
05 ژوئیه+58
04 ژوئیه0
03 ژوئیه+13
02 ژوئیه+45
01 ژوئیه+96
پست‌های کانال
ምስጋና አምልኮ ምስጋና አምልኮ ስግደት ውዳሴ ይገባል በሉ ሰዎች ለቅድስት ስላሴ ዘላለም አለም ቅዱስ ነህ አምሳያም  ወደር የሌለህ መተማመኛም ሆነኸኛል ሥላሴ ባንተ ደስ ይለኛል
አዝ
የታመነ ነው የተፈራ የጽድቅን ፀሐይ የሚያበራ ዓለሙ ፀንታል በሥላሴ ትዘምርለት ለእርሱ ነፍሴ
አዝ
ዘመናት በእጁ በመዳፉ ሁሌም የእርሱ ነው ድሉ ሰልፉ የእሳት መድረኮች ያሉት ጌታ የማያልፍ ነው የማይረታ
አዝ
አብርሃም አምኖ ተሰደደ በእርጅናው ወራት ልጅ ወለደ የተስፋውን ቃል ፈፀመለት ሥላሴ በሉ በቀን በለሊት መዝሙር ዘማሪት ጸዳለ ጎበዜ ❖═@OrthodoxTewahedoTrue═❖ ❖═@OrthodoxTewahedoTrue═❖  ❖═@OrthodoxTewahedoTrue═❖

2
​📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ ፯/7 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌በዚች ቀን የባሕታውያንና የቁምተኞች አለቃ፣ የታላቁና የቅዱስ አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን አለቃ)
​📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ ፯/7 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌በዚች ቀን የባሕታውያንና የቁምተኞች አለቃ፣ የታላቁና የቅዱስ አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን አለቃ) የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው። ​📌ይህ ቅዱስ በታችኛው ግብጽ አክሚም አውራጃ ስንላል ከምትባል አገር የተገኘ ሲሆን፣ ገና ሳይወለድ የመላእክት አምሳል የሆነው አባ ሐርስዮስ "ዜናው በዓለም የሚሰማ የስሙ መዓዛ የሚጥም ፍሬ ከማኅፀንሽ ይወጣል" ብሎ ለእናቱ ትንቢት ተናግሮላት ነበር። በግንቦት ፯ ቀን ተወልዶ ካደገ በኋላ የአባቱን በጎች እየጠበቀ ምሳውን ለእረኞች ሰጥቶ እስከ ማታ ይጾም ነበር፤ በሌሊትም በውኃ ዐዘቅት ውስጥ ቁሞ እስኪነጋ ይጸልይ ነበር። ​📌አባቱ ወደ እናቱ ወንድም ወደ አባ አብጎል ዘንድ ለበረከት በወሰደው ጊዜ፣ አባ አብጎል "ለብዙ ሕዝብ ታላቅ አባት ትሆናለህ" ብሎ ትንቢት ተናገረለት። በኋላም አባ አብጎል ከሰማይ ድምፅ ሰምቶ፣ የእግዚአብሔር መልአክ ያመጣለትን የኤልያስን አስኬማና የመጥምቁ ዮሐንስን ቅናት ለቅዱስ ሲኖዳ አለበሰው። ቅዱስ ሲኖዳም ለመነኰሳት፣ ለመኳንንትና ለሰዎች ሁሉ የሚሆን ሥርዓትን ሠራ። ​📌በኤፌሶን የ፪፻ (200) ሊቃውንት ጉባኤ ስለ ንስጥሮስ ክህደት በተደረገ ጊዜ ከሊቀ ጳጳሳቱ ከቅዱስ ቄርሎስ ጋር አብሮ ሄደ። ሲመለሱም መርከበኞች አብሮ እንዳይሳፈር ቢከለክሉት፣ በጸሎቱ ደመና መጥታ ተሸክማ መርከቡ ካለበት በላይ አድርሳዋለች። ወደ ገዳሙም ደርሶ በተጋድሎ ሲኖር ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብዙ ጊዜ እየመጣ ያነጋግረው ነበር፤ እርሱም የጌታን እግር አጥቦ እጣቢውን ይጠጣ ነበር። ​📌ዕድሜው ፻፳ (120) ዓመት ከሁለት ወር በሆነው ጊዜ ጌታችን መጥቶ ሊያሳርፈው ሲያረጋጋው፣ እርሱ ግን "የልዩ ሦስትነትህን ክብር የሚነቅፉትን ለመከራከር ወደ ጉባኤ ልሂድን?" ብሎ ጠየቀው። ጌታችንም "ድካምህ ይብቃህ" ብሎ በክብር ዐረገ። ቅዱስ ሲኖዳም ለልጆቹ አባ ዊዳን ጠባቂ አድርጎ ከሾመላቸው በኋላ ነፍሱን በክብር ለእግዚአብሔር ሰጠ። ​"ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ጻድቅ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን።" ምንጭ፦📖#መጽሐፈ_ስንክሳር ​"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን" (የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል) ✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📔)   ​❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖   ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ​📌የባሕታውያንን አለቃ የታላቁን የቅዱስ አባ ሲኖዳን ገድልና የበረከት ታሪክ ለወዳጅ ዘመድዎ Share በማድረግ የመንፈሳዊ አገልግሎቱ ተካፋይ ይሁኑ❕
1 495
3
😇መምህር ገብተዋል 📖📖 📚🏆ምስጢረ ቁርባን 🏆📚 📔 ትምህርት ተጀምሯል ላይቭ ግቡ 🙏 ከታቺ ባለው ሊንክ ግቡ ቭኦይስ ቻት ግቡ 👇👇 https://t.me/Bete_kidus_Michael_12?videochat=132ae57e1a061a7502 https://t.me/Bete_kidus_Michael_12
832
4
የዘማሪ አቤል መክብብን ድንቅ የዝማሬዎችን ስራዎችን ማግኘት ይፈልጋልሉ ⁉️ለማግኘት ይቀላቀሉ።🙏🙏
የዘማሪ አቤል መክብብን ድንቅ የዝማሬዎችን ስራዎችን ማግኘት ይፈልጋልሉ ⁉️ለማግኘት ይቀላቀሉ።🙏🙏
413
5
☎️ስልኩን ስትነኩት የሚወስዳችሁ ቻናል ለህይወታችሁ ጠቃሚ ስለሆነ ስልኩን  ይጫኑ /Start ╭━━━━━━━╮ ┃   ● ══  ▪       ┃███████┃ ┃███████┃ ┃███████┃ ┃███████┃ ┃███████┃ ┃███████┃ ┃███████┃ ┃███████┃ ┃███████┃ ┃        🔘       ┃ ╰━━━━━━━╯
727
6
🕊️ 🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷 🕊️ 🕯 🕊️ ዘላለም ሥላሴ 🕊️ 🕯 🕊️ 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 🕊️ እንኳን ለአጋእዝተ ዓለም ሥላሴ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ 🕊️ 🕯 🕊️
🕊️ 🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷🌷  🕊️ 🕯    🕊️   ዘላለም  ሥላሴ    🕊️   🕯 🕊️    🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿                                           🕊️   እንኳን ለአጋእዝተ ዓለም ሥላሴ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ  🕊️                        🕯                       🕊️      ❝   እ  ም  ነ  ታ  ች  ን  ❞  🕯  ከሃይማኖተ አበው የተወሰደ  🕯 * የሥላሴ አንድነትና ሦስትነት፦    "እምነታችን በባሕርይ በመለኮት አንድ፤ በአካልና በገጽ ሦስት ብለን ማመን ነው። እነዚህም አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ናቸው።" * የሐዋርያት ትምህርት፦    "ይህ ከሐዋርያት ሲያያዝ የመጣልን፣ ቅዱሳን ሊቃውንት የገለጡልንና በእውነት የምናምንበት እውነተኛ ሃይማኖታችን ነው።" * የድኅነት መንገድ፦    "በንጹሕ ልቡና፣ በአፋችንና በልባችን ያለ ጥርጥር በዚህ ሃይማኖት እንመን፤ በዚህ እንድንድን መንግሥተ ሰማያትንም እንድንወርስ እንረዳለን።" 🕊️                        🕯                     🕊️      ❝   የ  ሥ  ላ  ሴ    ፍ  ቃ  ር  ❞  🕯  አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ  🕯 * የማይበጠሰው ገመድ፦    "በሥላሴ ገመድ ፍጹም ታስረናል፤ ከልባችን በማይነቀል በቅንዋተ ፍቅሩ (በፍቅሩ ምስማር) ተቸንክረናል፤ እርሱ ወዶናልና አይጠላንም። እኛም በእምነት ይዘነዋል አንተወውም።"        🕊️    እንኳን  አደረሰን    🕊️                                              ☦️ ኦርቶዶክስ ☦️ 🕊️                         🕯                       🕊️    ​❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖   ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
5 303
7
ታላቅ በሆነው ታላቅ በሆነው እምነትሽ ታመንኩኝ     ካለሽበት ገስግሼ መጣሁኝ     እናቴ ክብርሽን አንግሼ     ቆምኩኝ እንደ ህፃን ታድሼ     እናቴ ቅድስት አርሴማ     ዝናሽ ለዓለም ተሰማ /2/ አዝ ስመጣ ባልጋ ነበረ     ተስፋዬም የተሰበረ     በእምነትሽ በፀበልሽ     ሰው ሆኜ ቆምኩኝ ደጅሽ    ልናገር ዝናሽን ላውራ     ይደነቅ የአምላክሽ ስራ     ተጋድሎሽ የእምነትሽ ፅናት     ሆኖኛል የእምነቴ መብራት     አዝ ደምግባት ከንቱ ብለሽ     ለሰማይ ክብር የታጨሽ     የእምነቴ ሐሰረ ፍኖት     በምልጃሽ አለሁኝ በህይወት  የልቡን ለነገረሽ     ፈጥኖ ይደርሳል መልስሽ     ዘንባባሽ ህይወት ይዘራል     የጠራሽ ማን አፍሮ ያውቃል     አዝ እርዳታሽ የደረሰለት     ያመጣል የልቡን ስለት     ላመኑሽ ፈውስሽ ቅርብ ነው     ባንቺ አፍሮ የሄደ ማነው የልቡን ለነገረሽ     ፈጥኖ ይደርሳል መልስሽ     ዘንባባሽ ህይወት ይዘራል     የጠራሽ ማን አፍሮ ያውቃል       አዝ ስመጣ ባልጋ ነበረ     ተስፋዬም የተሰበረ     በእምነትሽ በፀበልሽ     ሰው ሆኜ ቆምኩኝ ደጅሽ     ልናገር ዝናሽን ላውራ     ይደነቅ የአምላክሽ ስራ     ተጋድሎሽ የእምነትሽ ፅናት     ሆኖኛል የእምነቴ መብራት                 መዝሙር 🎙ዘማሪት ሲስተር ልድያ ታደሰ ❖═@OrthodoxTewahedoTrue═❖ ❖═@OrthodoxTewahedoTrue═❖  ❖═@OrthodoxTewahedoTrue═❖
4 103
8
​📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ ፮/6 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌 በዚች ቀን ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ የሆነውና ሐዋርያትን በትጋት ያገለገለው ቅዱስ መርቄሎ
​📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ ፮/6 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌 በዚች ቀን ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ የሆነውና ሐዋርያትን በትጋት ያገለገለው ቅዱስ መርቄሎስ (ጳውሎስ የተባለ) በሰማዕትነት አረፈ። ​📌ይህ ቅዱስ ረድእ ወንጌልን ለመስበክ ከሐዋርያት ጋር የሄደ፣ የቅዱስ ጴጥሮስን መልእክቶች ያደረሰና በመከራው ጊዜ ሁሉ አብሮት የነበረ ታማኝ አገልጋይ ነው። ወደ ሮሜ አገርም አብሮት በመግባት ብዙ አረማውያንን ወደ ቀናች ሃይማኖት መልሷል። ታላቁ ሐዋርያ ቅዱስ ጴጥሮስ በሰማዕትነት በሞተ ጊዜም፣ መርቄሎስ መጥቶ ከመስቀል ላይ አውርዶት በከበሩ ልብሶችና በሽቱ ገንዞ በሣጥን አድርጎ በምእመናን ቤት በክብር አኑሮታል። ​📌የቅዱስ ጴጥሮስ ደቀ መዝሙር መሆኑ በክፉው ንጉሥ በኔሮን ዘንድ በተከሰሰ ጊዜ፣ ንጉሡ ፊት ቀርቦ ስለ መምህሩና ስለ ጌታችን አምላክነት በግልጽ መሰከረ። ንጉሡም በጽኑ አስገረፈው፤ ዘቅዝቆም ሰቅሎ ከበታቹ ጢስ አጤሰበት። በኋላም ንጉሡ "በምን ዓይነት ሞት መሞት ትሻለህ?" ብሎ በጠየቀው ጊዜ፣ ቅዱሱ "እኔ በክርስቶስ ስም መሞትን እሻለሁ፤ አንተ በፈለግኸው ዓይነት ግደለኝ" በማለት በጽናት መለሰለት። ​📌ያን ጊዜም ንጉሡ ኔሮን እንደ መምህሩ እንደ ቅዱስ ጴጥሮስ ዘቅዝቀው እንዲሰቅሉት አዘዘ፤ እርሱም በታላቅ ትዕግሥት ተቀብሎ የሰማዕታትንና የሐዋርያትን የክብር አክሊል ተቀዳጀ። ​"ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሐዋርያት በጸሎታቸው ይማረን ለዘላለሙ አሜን።" ምንጭ፦📖#መጽሐፈ_ስንክሳር ​"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን" (የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል) ✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📔) ​  ​ ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖    ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ​📌እስከ ፍጻሜው ለመምህሩ የታመነውን የታላቁን የሐዋርያውና የሰማዕቱ የቅዱስ መርቄሎስን የበረከት ታሪክ ለወዳጅ ዘመድዎ Share በማድረግ የመንፈሳዊ አገልግሎቱ ተካፋይ ይሁኑ❕
4 101
9
ታላቅ በሆነው ታላቅ በሆነው እምነትሽ ታመንኩኝ     ካለሽበት ገስግሼ መጣሁኝ     እናቴ ክብርሽን አንግሼ     ቆምኩኝ እንደ ህፃን ታድሼ     እናቴ ቅድስት አርሴማ     ዝናሽ ለዓለም ተሰማ /2/ አዝ ስመጣ ባልጋ ነበረ     ተስፋዬም የተሰበረ     በእምነትሽ በፀበልሽ     ሰው ሆኜ ቆምኩኝ ደጅሽ    ልናገር ዝናሽን ላውራ     ይደነቅ የአምላክሽ ስራ     ተጋድሎሽ የእምነትሽ ፅናት     ሆኖኛል የእምነቴ መብራት     አዝ ደምግባት ከንቱ ብለሽ     ለሰማይ ክብር የታጨሽ     የእምነቴ ሐሰረ ፍኖት     በምልጃሽ አለሁኝ በህይወት  የልቡን ለነገረሽ     ፈጥኖ ይደርሳል መልስሽ     ዘንባባሽ ህይወት ይዘራል     የጠራሽ ማን አፍሮ ያውቃል     አዝ እርዳታሽ የደረሰለት     ያመጣል የልቡን ስለት     ላመኑሽ ፈውስሽ ቅርብ ነው     ባንቺ አፍሮ የሄደ ማነው የልቡን ለነገረሽ     ፈጥኖ ይደርሳል መልስሽ     ዘንባባሽ ህይወት ይዘራል     የጠራሽ ማን አፍሮ ያውቃል       አዝ ስመጣ ባልጋ ነበረ     ተስፋዬም የተሰበረ     በእምነትሽ በፀበልሽ     ሰው ሆኜ ቆምኩኝ ደጅሽ     ልናገር ዝናሽን ላውራ     ይደነቅ የአምላክሽ ስራ     ተጋድሎሽ የእምነትሽ ፅናት     ሆኖኛል የእምነቴ መብራት                 መዝሙር 🎙ዘማሪት ሲስተር ልድያ ታደሰ
1
10
🇪🇹 የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን አስተምህሮ ና ስርአትን የጠበቁ የትኞቹን መዝሙራት ማግኝት ይፈልጋሉ❓
1 694
11
የኦርቶዶክስ መዝሙር ይፈልጋሉ?
833
12
እኛም የክርስቶስ ተከታዮች የተባልን ምዕመናን፣ ከእነዚህ ብርሃናት ተቀብለን በቃላችንና በምግባራችን ለዓለም ብርሃን ልንሆን ይገባል። ጨለማውን ዓለም መለወጥ የሚቻለው በክፉ ፈንታ ክፉ በማድረግ ሳይሆ
እኛም የክርስቶስ ተከታዮች የተባልን ምዕመናን፣ ከእነዚህ ብርሃናት ተቀብለን በቃላችንና በምግባራችን ለዓለም ብርሃን ልንሆን ይገባል። ጨለማውን ዓለም መለወጥ የሚቻለው በክፉ ፈንታ ክፉ በማድረግ ሳይሆን፣ የእውነትንና የፍቅርን ብርሃን በማብራት ብቻ ነው። ​የቅዱሳን ሐዋርያት የጴጥሮስና የጳውሎስ በረከትና ረድኤት፣ በእነርሱ ላይ ያደረው የክርስቶስ ፍቅርና የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን ​✍️​ ​“ለግሪክ ሰዎችና ላልተማሩም፥ ለጥበበኞችና ለማያስተውሉም ዕዳ አለብኝ፤” በወንጌል አላፍርምና፤ አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም ለግሪክ ሰው፥ ለሚያምኑ ሁሉ የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ የእግዚአብሔር ጽድቅ ከእምነት ወደ እምነት በእርሱ ይገለጣልና። ሮሜ 1÷14 እግዚአብሔር ሆይ የሚሳንህ ነገር የለምና የራቀውን አቅርበህ የረቀቀውን አጉልተህ እየሰማነው ካለነው መርዶና ሰቀቀን ዕረፍተ ሥጋንና ዕረፍተ ነፍስን አትንሣን አሜን 🙏 ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖    ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
5 409
13
🌿እንኳን ለብርሃናተ ዓለም ለቅዱስ ጴጥሮስ፣ቅዱስ ጳውሎስ ለዕረፍታቸው መታሰቢያ ዓመታዊ በዓል አደረሳችሁ🌿 ብርሃናተ ዓለም ​ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቅዱስወንጌል «እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ» (ማቴ. ፭፥፲፬) ብሎ እንደተናገረ፥ ቅዱስ ጴጥሮስና ቅዱስ ጳውሎስ በሕይወታቸውና በትምህርታቸው፣ በደማቸውና በጭንቃቸው ዓለምን ከክህደትና ከውድቀት ጨለማ ወደ እውነተኛው የእግዚአብሔር መንግሥት ብርሃን የመለሱ የዓለም መብራቶች ናቸው ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ እነዚህ ቅዱሳን ሲመሰክር፦ «ጴጥሮስና ጳውሎስ የዓለም ዓይኖች፣ የቤተክርስቲያን ምሶሶዎች፣ የወንጌል ፈረሶችና የጽድቅ አርበኞች ናቸው» ይላቸዋል ዛሬ በዓለ ዕረፍታቸውን ስናስብ፣ እግዚአብሔር በእነርሱ ላይ የገለጠውን ድንቅ ጥበብና ፍቅር እንመለከታለን ​፩. የክርስቶስ ፍቅር፡ ቅዱስ ጴጥሮስን ከክህደት ወደ ንስሐ፣ ቅዱስ ጳውሎስን ከአሳዳጅነት ወደ ተሳዳጅነት መልሷቸዋል ​ሀ/ ቅዱስ ጴጥሮስ፦ ከክህደት በንስሐ ወደ መታመን ​ቅዱስ ጴጥሮስ በፍርሃት ምክንያት ጌታውን ሦስት ጊዜ ቢክደውም (ማቴ. ፳፮፥፷፱-፸፭)፣ የክርስቶስ ፍቅር ግን ፈጽሞ አልጣለውም። ጌታችን ዘወር ብሎ በተመለከተው ጊዜ፣ ያቺ የእይታ ፍቅር የጴጥሮስን ልብ ሰብራ ታላቅ ልቅሶንና ንስሐን ወለደች ​የማር አፍቅሮት የተባለው ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በትርጓሜ ወንጌሉ ላይ እንዲህ ይላል፦ «ጌታ ጴጥሮስን የተመለከተው በዓይኑ ብቻ ሳይሆን በቸርነቱ ብርሃን ጭምር ነው። ያ እይታ ጴጥሮስን ከውድቀቱ አንሥቶ የሐዋርያት አለቃ አደረገው።» ከትንሣኤ በኋላም ጌታችን «ትወደኛለህን?» እያለ ሦስት ጊዜ በመጠየቅ፣ በሦስቱ ክህደት ፋንታ ሦስት ጊዜ የፍቅር ቃል ኪዳን አጽንቶለታል (ዮሐ. ፳፩፥፲፭) ​የሰው ውድቀት የቱንም ያህል የከፋ ቢሆን፣ የእግዚአብሔር ምሕረትና የንስሐ በር ሁልጊዜ ክፍት ነው። ንስሐ የወደቀውን አንሥታ ከቀድሞው ክብር በላይ ታደርሳለች ፍርሃት ሲያሸንፈን፣ ወደ ክርስቶስ ቸርነት ዓይኖች መመልከት ይገባናል ​ለ/ ቅዱስ ጳውሎስ፦ ከአሳዳጅነት ወደ ተሳዳጅነት ​ሳውል (ጳውሎስ) ቤተክርስቲያንን የሚያሳድድ፣ ምዕመናንን የሚያስርና የሚገድል ኃያል ነበረ (ሐዋ. ፱፥፩-፪) ነገር ግን በደማስቆ መንገድ ላይ የወረደለት ሰማያዊ ብርሃንና «ሳውል ሳውል ስለ ምን ታሳድደኛለህ?» የሚለው ድምፅ ከአሳዳጅነት ወደ ክርስቶስ ምስክርነት አሻገረው። ​የቤተክርስቲያን መተርጉማን እንደሚያስተምሩት፣ ክርስቶስ «ስለ ምን ታሳድደኛለህ?» ያለው ራሱ ሰማይ ስላለ ሳይሆን፣ በምድር ያሉትን ምዕመናን ማሳደድ ራሱን ክርስቶስን ማሳደድ መሆኑን ለማወቅ ነው ጳውሎስ ከዚያን ዕለት ጀምሮ ስለ ክርስቶስ ስም መከራን የሚቀበል፣ የሚሰደድና የሚገረፍ ታላቅ የዓለም ሐዋርያ ሆነ እርሱ ራሱ «ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ ነው ወይስ ጭንቀት ወይስ ስደት?» (ሮሜ ፰፥፴፭) በማለት ያንን ፍቅር ገልጦታል ​ የእግዚአብሔር ፍቅር ጠላትን ወዳጅ፣ አሳዳጅን ወንጌላዊ የማድረግ መለኮታዊ ኃይል አለው። እግዚአብሔር ሰውን የሚመዝነው በያዘው ክፉ ታሪክ ሳይሆን ሊሆን በሚችለው ቅዱስ ማንነት ነው ​፪. በሐዋርያት ሥራ የተደረገላቸውና እነርሱም ያደረጓቸው ድንቅ ተአምራት ​የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ በሁለቱ ታላላቅ ብርሃናት ላይ የተደረጉትንና በእነርሱ እጅ የተፈጸሙትን ተአምራት በስፋት ይተርካል የቤተክርስቲያን ሊቃውንት «የሐዋርያት ሥራ የወንጌል ፍሬና የመንፈስ ቅዱስ ኃይል መገለጫ ነው» ይሉታል ​ሀ/ ለእነርሱ የተደረገላቸው ድንቅ ተአምር ​ለቅዱስ ጴጥሮስ፦ ሄሮድስ አግሪጳ በወህኒ ቤት አሳስሮት፣ በአራት ፈራቃ ወታደሮች እየተጠበቀ ሳለ፣ የእግዚአብሔር መልአክ በድንገት ወርዶ በብርሃን አበራው፤ ሰንሰለቱም ከእጁ ወደቀ፣ የብረቱም መዝጊያ በራሱ ተከፍቶለት ከሞት አምልጧል (ሐዋ. ፲፪፥፭-፲፩) ​ለቅዱስ ጳውሎስ፦ ከሲላስ ጋር በፊልጵስዩስ ወህኒ ቤት ተጥለው፣ እግራቸው በግንድ ታስሮ ሳለ፣ በመንፈቀ ሌሊት እግዚአብሔርን በቅኔና በምስጋና ሲያከብሩ ታላቅ የምድር መንቀጥቀጥ ሆኖ የወህኒው መሠረት ተናወጠ፤ ደጆቹም ተከፍተው ሰንሰለታቸው ተፈታ (ሐዋ. ፲፮፥፳፭-፳፮) ​ለ/ እነርሱ ያደረጉት ድንቅ ተአምር ​በቅዱስ ጴጥሮስ እጅ፦ በቤተ መቅደስ ደጅ (በመልካሟ በር) ይለምን የነበረውን ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ አንካሳ የሆነውን ሰው «ብርና ወርቅ የለኝም፤ ይህን ያለኝን ግን እሰጥሃለሁ፤ በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሣና ተመላለስ» ብሎ አስነስቶታል (ሐዋ. ፫፥፩-፲)። እንዲያውም የጴጥሮስ ጥላ እንኳ በሕመምተኞች ላይ ሲያርፍ ይፈወሱ ነበር (ሐዋ. ፭፥፲፭) ​በቅዱስ ጳውሎስ እጅ፦ በኤፌሶን ሳለ እግዚአብሔር በእጁ ታላቅ ተአምር ያደርግ ነበር። ከሰውነቱ ጨርቅ ወይም መጥረጊያ ወስደው በሕመምተኞች ላይ ቢያኖሩ ደዌያቸው ይለቃቸው፣ አጋንንትም ይወጡ ነበር (ሐዋ. ፲፱፥፲፩-፲፪) እንዲሁም ከአጥር ላይ ወድቆ የሞተውን አውጤክስን በጸሎት አስነስቶታል (ሐዋ. ፪፲፥፱-፲፪)። ቅዱሳኑ የእግዚአብሔር የጸጋ ዕቃዎች ናቸው ጥላና ጨርቃቸው እንኳ ሳይቀር ኃይልን ማድረጉ፣ እግዚአብሔር በቅዱሳኑ አጥንትና ንዋያት ላይ የሚያድረውን ጸጋ ያሳያል እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑ ነፍሳት ደግሞ በየትኛውም የወህኒና የጭንቅ ጨለማ ውስጥ ቢሆኑ ሰማያዊ ነፃነት አላቸው ​፫. ፍጻሜያቸው (የሰማዕትነት ክብር) ​የእነዚህ ቅዱሳን ፍጻሜ በምድር ላይ በደም የተፈጸመ፣ በሰማይ ግን በክብር አክሊል የተሸለመ ነበረ ሁለቱም በሮም ንጉሥ በኔሮን ዘመን በሰማዕትነት ዐረፉ ​ቅዱስ ጴጥሮስ፦ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን (እንደ አውሳቢዮስ ዘቂሣርያ ያሉ የታሪክ ጸሐፊዎች) እንደዘገቡት፣ ቅዱስ ጴጥሮስ ሊሰቅሉት በወሰዱት ጊዜ «ከጌታዬ ጋር እኩል ልሰቀል አይገባኝም፣ እርሱ ሰማይንና ምድርን የፈጠረ ጌታ ነውና እኔን ቁልቁል ስቀሉኝ» በማለት በትሕትና ራሱን ዝቅ አድርጎ ዘቅዝቀው ሰቅለውታል ​ቅዱስ ጳውሎስ፦ የሮም ዜግነት ስላለው እንዳይሰቀል ተከልክሎ፣ በሰይፍ ራሱን ተቆርጧል አንገቱ በተቆረጠ ጊዜ ከደሙ ጋር ወተት እንደፈሰሰና የተቆረጠው ራሱ ሦስት ጊዜ እየተንጠረጠረ «ክርስቶስ» የሚል ድምፅ እንደሰጠ ሊቃውንቱ በትርጓሜያቸው ይናገራሉ ቅዱስ ጳውሎስ አስቀድሞ «መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ፥ ሩጫውን ጨርሻለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤ ወደፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል» (፪ ጢሞ. ፬፥፯-፰) እንዳለ፣ የቃሉ ፍጻሜ ተፈጸመ የቅዱሳን ሕይወት ፍጻሜ ሞት ሳይሆን ወደ ዘለዓለም ክብር መሸጋገሪያ ድልድይ ነው። ቅዱስ ጴጥሮስ እስከ ሞት ድረስ ያሳየው ትሕትና፣ ቅዱስ ጳውሎስም ለአምላኩ ያፈሰሰው ደም እውነተኛ ክርስትና መስዋዕትነትን የምትጠይቅ መሆኗን ያስተምረናል ​፬. ብርሃናተ ዓለም (ዓለምን በስብከታቸውና በሕይወታቸው ማብራታቸው) ​ጌታችን «እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ» ሲል፣ ሐዋርያት በጨለማ ለነበረው ዓለም የእውነትን መብራት ይዘው እንደሚወጡ የተናገረው ትንቢት ነው ​ቅዱስ ጴጥሮስ፦ ለአይሁድ ወገን ሐዋርያ በመሆን፣ በበዓለ ኃምሳ በአንድ ስብከት ሦስት ሺሕ፣ በሌላም ጊዜ አምስት ሺሕ ሕዝብ ወደ ማመን በመመለስ (ሐዋ. ፪፥፵፩፣ ፬፥፬) የኦሪትን ጥላነት ገፎ የወንጌልን ብርሃን አብርቷል ​ቅዱስ ጳውሎስ፦ ከአሕዛብ ወገን እስከ ምዕራብ ዳርቻ («እስከ ምዕራብ ዳርቻ እስከ እስፔን ድረስ ») በመጓዝ፣ አራት ታላላቅ የስብከት ጉዞዎችን በማድረግ፣ ፲፬ቱን መልእክታት በመጻፍ፣ ጣዖት ያመልኩ የነበሩ አሕዛብን የእግዚአብሔር የጸጋ ልጆች አድርጓቸዋል
4 936
14
አመ አመ ሰበክሙ አመ አመ ሰበክሙ(፪) ቅዱሳን ሐዋርያት ቅዱሳን ሐዋርያት - - - ሐዋርያት የዓለም ብርሃን ናችሁ - - - ሐዋርያት መጀመሪያ ጴጥሮስ - - - ሐዋርያት አለና ጳውሎስ - - - ሐዋርያት     አዝ ብርሃናተ ዓለም - - - ሐዋርያት ጴጥሮስ ወጳውሎስ- - - ሐዋርያት በእውነት ተሰየፉ - - - ሐዋርያት ስለ ክርስቶስ - - - ሐዋርያት   አዝ ሐዋርያት ፈርተው - - - ሐዋርያት ሲለቅሙ በሻማ - - - ሐዋርያት ሰዎች አትለዩ - - -ሐዋርያት ከወንጌል አውድማ - - - ሐዋርያት      አዝ የዘላለም ሕይወት - - - ሐዋርያት ማደስ ካማራችሁ - - - ሐዋርያት የሐዋርያት ሥራ - - - ሐዋርያት ይሁን አላማችሁ - - - ሐዋርያት       አዝ ውኆች ቀለም ሆነው - - - ሐዋርያት እንጨቶች ብዕር - - - ሐዋርያት ቢፅፉት አያልቅም - - - ሐዋርያት የሐዋርያት ክብር - - - ሐዋርያት     አዝ ሐምሌ አምስት ቀን - - - ሐዋርያት ማኅበራችን - - - ሐዋርያት በክርስቶስ መስቀል - - - ሐዋርያት ተባረከልን - - - ሐዋርያት                  መዝሙር በጴጥሮስ ወ ጳውሎስ ቤ/ክ ሰ/ት/ቤት ዘማርያን 📖"ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን እንደሚታረዱ በጎች ተቆጠርን"              ሮሜ ፰ ፥ ፴፮   ​ ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖    ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
4 785
15
😇መምህር ገብተዋል 📖📖 📚😇ነገረ ክርስቶስ😇📖📚 📔 ትምህርት ተጀምሯል ላይቭ ግቡ 🙏 ከታቺ ባለው ሊንክ ግቡ ቭኦይስ ቻት ግቡ 👇👇 https://t.me/Bete_kidus_Michael_12?videochat=132ae57e1a061a7502 https://t.me/Bete_kidus_Michael_12
754
16
✝️ የዕለቱ ቅዱስ ወንጌል ቃል ✝️ ​« ማንም ሊከተለኝ የሚወድ ቢኖር፥ ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ። ነፍሱን ሊያድን የሚወድ ሁሉ ያጠፋታልና፤ ስለ እኔና ስለ ወንጌል ነፍሱን የሚያጠፋት
✝️ የዕለቱ ቅዱስ ወንጌል ቃል ✝️ ​« ማንም ሊከተለኝ የሚወድ ቢኖር፥ ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ። ነፍሱን ሊያድን የሚወድ ሁሉ ያጠፋታልና፤ ስለ እኔና ስለ ወንጌል ነፍሱን የሚያጠፋት ሁሉ ግን ያድናታል። ሰው ዓለምን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል❔ ሰውስ ስለ ነፍሱ ቤዛ ምን ይሰጣል❔ » ​✥ የማርቆስ ወንጌል ምዕራፍ 8 ÷ 34-37 ✥ ​💡ከቃሉ ምን እንማራለን❔ (ለዕለት ተዕለት ሕይወታችን) ​ለወጣቶችና ለልጆች፦ በዚህ ዓለም ላይ የምናሳድደው ዝና፣ ሀብት ወይም ጊዜያዊ ደስታ ሁሉ ከነፍሳችን መዳን ጋር ሊወዳደር አይችልም። እውነተኛ ስኬት ክርስቶስን አርአያ አድርጎ በቅንነትና በሥነ-ምግባር መኖር ነው። ​ለእናቶችና ለአባቶች፦ ልጆቻችን የዚህን ዓለም ትምህርትና እውቀት ብቻ ሳይሆን፣ የነፍሳቸውን ዋጋ እንዲያውቁና ሃይማኖታቸውን ጠብቀው እንዲያድጉ በትዕግሥትና በጸሎት መምራት ይገባናል። ​« ዓለምን ከማተርፍ ይልቅ ነፍሴን ማዳን ይሻለኛል❕ »   ​ ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖    ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
5 757
17
​📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ ፬/4 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌በዚች ቀን የከበሩ ታላላቅ ሰማዕታት የቅዱስ አቡቂርና ዮሐንስ የሥጋቸው ፍልሰት (ከቦታ ወደ ቦ
​📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ ፬/4 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌በዚች ቀን የከበሩ ታላላቅ ሰማዕታት የቅዱስ አቡቂርና ዮሐንስ የሥጋቸው ፍልሰት (ከቦታ ወደ ቦታ መፍለስ) ሆነ። ​📌እሊህ ቅዱሳን የካቲት ፮ ቀን በሰማዕትነት በሞቱ ጊዜ፣ ምእመናን ሥጋቸውን ወስደው በእስክንድርያ ከተማ በቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሥውር አኑረውት ነበር። እስከ ሊቀ ጳጳሳቱ እስከ ቅዱስ ቄርሎስ ዘመንም ድረስ በዚያው ቆየ። ​📌ከዚህ በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ ለሊቀ ጳጳሳቱ ለቅዱስ ቄርሎስ ተገልጦለት፣ የቅዱሳኑን የአቡቂርንና የዮሐንስን ሥጋ አውጥቶ እንዲያፈልስ አዘዘው። ቅዱስ ቄርሎስም ከብዙ ሕዝብ ጋር ሄዶ በጸሎት ምድሩን ሲቆፍሩ ሥጋቸው ያለበት ቦታ ተገለጠላቸው። የቅዱሳኑንም ሥጋ በታላቅ ክብር ተሸክመው በባሕር ዳርቻ ወደምትገኝ ሌላኛዋ የቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን አድርሰው አኖሩት። ​📌በዚያም ቦታ ላይ ቤተ ክርስቲያን የሠሩላቸው ሲሆን፣ በዚህች ቀን ታላቅ በዓል አደረጉ። ከቅዱሳኑ ሥጋ ብዙ ድንቅ ተአምራትና የበሽተኞች ፈውስ በመገለጡ፣ አረማውያኑ ሳይቀሩ ጣዖቶቻቸውን ትተው በጌታ አመኑ፤ ክርስቲያኖችም ሆኑ። የነበረችውም የጣዖት ቤት በአሸዋ ተከምራ ታላቅ ኮረብታ ሆነች። ​"ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።" ​ምንጭ፦📖#መጽሐፈ_ስንክሳር ​"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን" (የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል) ✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📔)   ​ ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖    ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ​ ​📌የታላላቆቹ ቅዱሳን ሰማዕታት የአቡቂርና የዮሐንስን የሥጋ ፍልሰት በዓል ታሪክ ለወዳጅ ዘመድዎ Share በማድረግ የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ❕
5 887
18
​✝️ የዕለቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ✝️ ​« የአባትን ተግሣጽ ስሙ፥ ማስተዋልንም ታውቁ ዘንድ አድምጡ፤ መልካም ትምህርትን እሰጣችኋለሁና ሕጌን አትተዉ። ​እኔም አባቴን የምሰማ ልጅ ነበርሁና፥ በእናቴ
​✝️ የዕለቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ✝️ ​« የአባትን ተግሣጽ ስሙ፥ ማስተዋልንም ታውቁ ዘንድ አድምጡ፤ መልካም ትምህርትን እሰጣችኋለሁና ሕጌን አትተዉ። ​እኔም አባቴን የምሰማ ልጅ ነበርሁና፥ በእናቴም ዘንድ እወደድ ነበር። ያስተምረኝም ነበር እንዲህም ይለኝ ነበር፦ ልብህ ቃሌን ይቀበል፥ ትእዛዜን ጠብቅ በሕይወትም ትኖራለህ። ​ጥበብን አግኝ፥ ማስተዋልን አግኝ፤ አትርሳም፥ ከአፌም ቃል ፈቀቅ አትበል❕ » ​✥ መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ 4 ÷ 1-5 ✥ ​💡ከቃሉ ምን እንማራለን❔ (ለዕለት ተዕለት ሕይወታችን) ​ለወጣቶችና ለልጆች፦ የእግዚአብሔርን ቃልና የወላጆቻችንን ምክር (ተግሣጽ) መስማት የቅድስና፣ የጥበብና የረጅም ዕድሜ መሠረት ነው። የወላጅ ምክር ከክፉ መንገድ ይጠብቀናል። ​ለእናቶችና ለአባቶች፦ ልጆቻችንን በእግዚአብሔር ቃልና በጥሩ ስነ-ምግባር ኮትኩቶ ማሳደግ፣ ነገ በሕይወታቸው ስኬታማና ለሀገር የሚጠቅሙ ትውልድ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል። ​« ጥበብንና ማስተዋልን ፍለጋ ከቅዱሳት መጻሕፍት አንራቅ❕ »   ​ ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ ❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖    ❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
5 993
19
​📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ ፫/3 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌በዚች ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሃያ አራተኛ የሆነው፣ የዓለም ብርሃንና የቤተ ክርስቲያን ዓ
​📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ ፫/3 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ​📌በዚች ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሃያ አራተኛ የሆነው፣ የዓለም ብርሃንና የቤተ ክርስቲያን ዓምድ ታላቁ ቅዱስ አባት ቄርሎስ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት (ዓምደ ሃይማኖት) አረፈ። ​📌ይህ ቅዱስ አባት የእናቱ ወንድም በሆነው በሊቀ ጳጳሳቱ በአባ ቴዎፍሎስ ዘንድ ያደገ ሲሆን፣ ወደ አስቄጥስ (ቅዱስ መቃርስ) ገዳም ተልኮ አምላካውያን መጻሕፍትን ተምሯል። እግዚአብሔርም መጽሐፍን አንድ ጊዜ አንብቦ እስከሚያጸናው ድረስ ታላቅ ዕውቀትንና ማስተዋልን ሰጠው። በኋላም ለአባ ሰራብዮን ተሰጥቶ ትምህርቱን በፈጸመ ጊዜ ወደ አባ ቴዎፍሎስ ተመለሰ፤ እርሱም በሊቀ ጵጵስና ሥራ ውስጥ በመሾም ሁልጊዜ ሕዝቡን እንዲያስተምር አደረገው። ከትምህርቱ ጣዕም የተነሣም ሕዝቡ ዝም እንዲል አይፈልግም ነበር። ​📌አባ ቴዎፍሎስ ካረፈ በኋላ በእስክንድርያ መንበር ላይ ተሾመ፤ በዘመኑም በትምህርቱና በድርሳናቱ ቤተ ክርስቲያንን አበራት። የቁስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳሳት የነበረው ንስጥሮስ በካደ ጊዜ፣ በንጉሥ ቴዎዶስዮስ ዘመን በኤፌሶን ከተማ የ፪፻ (200) ኤጲስቆጶሳት ጉባኤ እንዲሰበሰብ አደረገ። ቅዱስ ቄርሎስም የዚህ ጉባኤ መሪ (ሊቀ ጉባኤ) በመሆን ንስጥሮስን ተከራክሮ ረታው፤ ከክህደቱም ለመመለስ ፈቃደኛ ባለመሆኑ አውግዞ ከመንበሩ አሳደደው። ​📌ይህ አባት የቀናች ሃይማኖትን የገለጠባቸውን ፲፪ (12) አንቀጾችን (የቄርሎስ መዓዛ/ሃይማኖት) የደረሰ ሲሆን፣ ከእነርሱም በኋላ ብዙ ድርሳናትን፣ ተግሣጻትንና መልእክቶችን ጥሏል። እግዚአብሔር ቃል ከሥጋ ጋር ከተዋሐደ በኋላ "ተዋሕዶ ዘእንበለ ፍልጠት" (ያለ መለየት) አንድ አካል አንድ ባሕርይ (አሐዱ አካል ወአሐዱ ባሕርይ) መሆኑን በሚገባ አስረድቷል። ክርስቶስን ወደ ሁለት ባሕርይ የሚከፍሉትን መናፍቃን ሁሉ አውግዞ ለይቷል። ​📌በወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ መንበር ላይ ፴፪ (32) ዓመታት በትጋት ካገለገለ በኋላ፣ መልካሙን ገድሉን ፈጽሞ በዚህች ዕለት በሰላም አረፈ። ​"ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።" ​ምንጭ፦📖#መጽሐፈ_ስንክሳር ​"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን" (የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል) ✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📔) ​ ​╭══✧•|❀:✧๑♡๑✧❀•✧══╮   @OrthodoxTewahedoTrue ╰══✧•ೋ•✧๑♡๑✧•✧══╯ ​📌የእምነት ጠበቃና የቤተ ክርስቲያን ጌጥ የሆነውን የታላቁን የቅዱስ አባ ቄርሎስን (ዓምደ ሃይማኖት) የበረከት ታሪክ ለወዳጅ ዘመድዎ Share በማድረግ የመንፈሳዊ አገልግሎቱ ተካፋይ ይሁኑ❕
6 933
20
🫶⛪️የኢኦተቤክ አስተምህሮ ና ስርአትን የጠበቁ መዝሙራት ማግኝት ይፈልጋሉ⁉️
1 204