Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
#ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ #Orthodox 📜 #የዕለቱ #ስንክሳር (#የቅዱሳን_ታሪክ) 💡 የአባቶች ምክርና ትምህርት 📖 ሕይወትን የሚቀይሩ ጥልቅ የአባቶች ምክር እና ትምህርቶች ይተላለፋሉ። 📌 ጥያቄ ለመጠየቅና ማስታወቂያ ለማሰራት 👉 @tadilogos ያግኙን። Buy ads: https://telega.io/c/OrthodoxTewahedoTrue
Больше📈 Аналитический обзор Telegram-канала Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
Канал Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ (@orthodoxtewahedotrue) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 171 166 подписчиков, занимая 136 место в категории Религия и духовность и 133 место в регионе Эфиопия.
📊 Показатели аудитории и динамика
С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 171 166 подписчиков.
Согласно последним данным от 28 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -1 674, а за последние 24 часа — -206, при этом общий охват остаётся высоким.
- Статус верификации: Не верифицирован
- Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 3.64%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 2.86% реакций от общего числа подписчиков.
- Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 6 231 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 4 900 просмотров.
- Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 58.
📝 Описание и контентная политика
Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
“#ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ #Orthodox
📜 #የዕለቱ #ስንክሳር (#የቅዱሳን_ታሪክ)
💡 የአባቶች ምክርና ትምህርት
📖 ሕይወትን የሚቀይሩ ጥልቅ የአባቶች ምክር እና ትምህርቶች ይተላለፋሉ።
📌 ጥያቄ ለመጠየቅና ማስታወቂያ ለማሰራት 👉
@tadilogos ያግኙን።
Buy ads: https://telega.io/c/OrthodoxTewahedoTrue”
Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 29 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.
Загрузка данных...
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 28 июля | 0 | |||
| 27 июля | 0 | |||
| 26 июля | 0 | |||
| 25 июля | +107 | |||
| 24 июля | 0 | |||
| 23 июля | +132 | |||
| 22 июля | +176 | |||
| 21 июля | +26 | |||
| 20 июля | +153 | |||
| 19 июля | +115 | |||
| 18 июля | +134 | |||
| 17 июля | +76 | |||
| 16 июля | 0 | |||
| 15 июля | +93 | |||
| 14 июля | 0 | |||
| 13 июля | 0 | |||
| 12 июля | +85 | |||
| 11 июля | 0 | |||
| 10 июля | 0 | |||
| 09 июля | 0 | |||
| 08 июля | 0 | |||
| 07 июля | 0 | |||
| 06 июля | 0 | |||
| 05 июля | +58 | |||
| 04 июля | 0 | |||
| 03 июля | +13 | |||
| 02 июля | +45 | |||
| 01 июля | +96 |
| 2 | ናታኔም ነኝ
ናታኔም ነኝ አገልግሎቴ
አይከፋኝም ታናሽነቴ
እጠርጋለሁ ደጅህን ጌታ
ዝቅ ብዬ ላንተ ውለታ
አዝ
ከነገደ ሌዊ ባልሆን
ባልሾምም እንደ አሮን
የዜማ እቃ ባልይዝ በገና
ላመስግንህ በትህትና
ደጅ ሆኜ ካንተ በር ተሰፋ አድርጌ ስዘምር
ቆጥረህልኝ እንደዋጋ አከበርከኝ ባንተ ፀጋ
አዝ
ከረኝነት ከታናሽ ስፍራ
ለንግሥና ምንም ብጠራ
ከቀንዲሉ ቀርቧል ሀሣቤ
ልቀኝለት ተነጥፎ ልቤ
ደጅ ሆኜ ካንተ በር ተስፋ አድርጌ ስዘምር
ቆጥረህልኝ እንደዋጋ አከበርከኝ ባንተ ፀጋ
አዝ
ሳይከብድኝ የአለም ዝና
ተንበርክኬ ልሥጥህ ምሥጋና
ምክንያት አለኝ ለማዘንበሌ
ናታኔም ነኝ ይቺ ናት ቃሌ
ደጅ ሆኜ ካንተ በር ተስፋ አድርጌ ስዘምር
ቆጥረህልኝ እንደዋጋ አከበርከኝ ባንተ ፀጋ
አዝ
እንኳን ልቆሞ በፍታን ለብሼ
አፍርሀለው እኔ አጎንብሼ
የትመክኸት ካባዬን ጥዬ
ከመቅደስህ ልግባ ጌታዬ
ደጅ ሆኜ ካንተ በር ተስፋ አድርጌ ስዘምር
ቆጥረህልኝ እንደዋጋ አከበርከኝ ባንተ ፀጋ
መዝሙር
🎙️ዘማሪ ገ/ዮሐንስ ገ/ጻድቅ🎤
❖═@OrthodoxTewahedoTrue═❖
❖═@OrthodoxTewahedoTrue═❖
❖═@OrthodoxTewahedoTrue═❖ | 629 |
| 3 | 📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ ፳፪/22
🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
📌በዚች ቀን የጭፍሮች አለቃ የፋሲለደስ ልጅ ታላቁ ቅዱስ መቃርስ ሰማዕት አረፈ።
📌ቅዱስ መቃርስን ከሐዲው ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ዘንድ "ለጣዖት አይሰግድም" ብለው ቢከሰሱት፣ ወደ እስክንድርያ አስወስዶ እንዲያሠቃዩት አዘዘ።
ቅዱሱም ቤተሰቦቹንና ድሆችን አደራ ብሎ ሲወጣ፣ ጌታችን ተገልጦ አጸናው።
📌በእስክንድርያው መኰንን በኅርማኖስ ፊት በጽናት በመቆሙ አካሉ እስኪቀልጥ ድረስ ታላቅ ሥቃይ አደረሱበት፤ በሥቃይም ውስጥ ሳለ ጌታችን የሰማያዊውን ማደሪያና የወላጆቹን ክብር አሳየው።
ከዚያም ወደ ኒቅዮስ ሰደዱት፤ ምላሱንና ክንዱን ቢቆርጡ፣ በእሳት የጋሉ የብረት ችንካሮች በጎኑ ቢሰኩበትም ጌታችን ያለ ጉዳት ፈወሰው።
📌 እግዚአብሔር በእጁ ታላቅ ተአምር አደረገ፤ ቅዱስ መቃርስ ወደ ጌታ ጸልዮ የተቀበረን ምውት ካስነሣ በኋላ፣ ያ በድን ተነሥቶ ክርስቶስ እውነተኛ አምላክ መሆኑን መሰከረ።
ይህን ያዩ ብዙዎች አምነው በሰማዕትነት አረፉ።
📌 ከዚህ በኋላ ገዥው አርያኖስ ይዞት ሲሄድ ሰጥኑፍ በሚባል ቦታ መርከቧ ቆመች፤ ጌታችንም በዚያ ተጋድሎውን እንደሚያጠናቅቅ ነገረው።
በመጨረሻም አንገቱን በሰይፍ ተቆርጦ የሰማዕትነትን አክሊል ተቀዳጀ።
📌ጻድቁ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ በነገሠ ጊዜ አውሎጊዮስ ለተባለ ምእመን ቅዱስ መቃርስ በራእይ ተገልጦ ሥጋው ያለበትን በመንገሩ፣ ሥጋውን አግኝተው በስሙ በተሠራችው ቤተ ክርስቲያን አኖሩት፤ ከእርሱም ታላላቅ ድንቆችና ተአምራት ተገለጡ።
"ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ሰማዕት ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።"
ምንጭ፦📖#መጽሐፈ_ስንክሳር
"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"
(የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል)
✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📔)
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
📌ስለ አምላኩ ፍቅር ልዩ ልዩ መከራን የተቀበለውን የደጉን ሰማዕት የቅዱስ መቃርስን ገድል Share በማድረግ የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ❕ | 1 286 |
| 4 | ➡️ክርስቲያናዊ ሕይወት መርሃ ግብር ተጀምሯል ግቡ LIVE ! 👈
➡️ይህ ትምህርት በዕለት ተዕለት ሕይወታችን ክርስቶስን እንዴት መምሰል እንደምንችል የምንማርበት ልዩ መረሃ ግብር ነው።
ሼር ሼር ሼር 📎👇👇👇
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12?videochat=7cb7619bb19da1ffa8
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12 | 369 |
| 5 | 🔴አስተምህሮው ወደ ኢትዮጵያ እንዴት ገባ❔ (ታሪካዊ ዳሰሳ)
ክፍል(፭) 5
በሀገራችን በኢትዮጵያ በነባሩ የቤተክርስቲያን ትምህርትና ሊቃውንት ዘንድ ስለ አጽራረ ክርስቶስ (የክርስቶስ ተቃዋሚ) እና ስለ ዘመን መጨረሻ ሰፊና ጥልቅ ትምህርት ቢኖርም፣ "666" የሚለውን ቁጥር ከዕለት ተዕለት ቁሳቁሶች ጋር የማያያዝ አመለካከት ግን የቅርብ ጊዜ ክስተት ነው።
የ20ኛው ክፍለ ዘመን ማጠቃለያ፦ በ1980ዎቹ እና 1990ዎቹ ዓ.ም አካባቢ ከምዕራቡ ዓለም የተቀዱ የሴራ ትንተና (Conspiracy Theory) መጻሕፍት ወደ አማርኛ ተተርጉመው በስፋት ተሰራጩ።
እነዚህ መጻሕፍት አብዛኞቻቸው የራሳቸውን መላምትና ስጋት የያዙ ነበሩ።
የመረጃ ክፍተት፦ መጻሕፍቱ ታሪካዊውን እና አውደ-ጽሑፋዊውን የዮሐንስ ራእይ ትርጓሜ ከመግለጽ ይልቅ፣ የዓለምን የፋይናንስ ሥርዓት፣ የውጭ ድርጅቶችን አርማ፣ ኮምፒውተሮችን እና አዳዲስ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን በሙሉ ከ666 ጋር አያይዘው አቀረቡ።
የፍርሃት ባህል ማደግ፦ ይህ አቀራረብ በህብረተሰቡ ዘንድ ሰፊ ስጋትና ፍርሃትን የፈጠረ ሲሆን፣ ሰዎች አዳዲስ አሰራሮችን፣ የካርድ አገልግሎቶችን፣ ባርኮዶችን እና የቴክኖሎጂ እድገቶችን በጥርጣሬ እንዲያዩ ምክንያት ሆኗል።
ይህ አካሄድ አማንያን ትኩረታቸውን ከእውነተኛው መንፈሳዊ ህይወት፣ ከጸሎት እና ከፍቅር አውጥተው፣ ቁሳቁሶችንና ቁጥሮችን ወደ መፍራት እንዲያዘነብሉ አድርጓቸዋል።
ነገር ግን ነባሩ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ የሚያስተምረን አጽራረ ክርስቶስ በግብሩ፣ በስራው እና በክህደቱ የሚገለጥ እንጂ ድንገት በስህተት በምናይበት ወይም በምንጠቀምበት ቁሳቁስ የሚተላለፍ እንዳልሆነ ነው።
✍️አዘጋጅ፦ Orthodox Tewahedo True
🌀ይቀጥላል🔴
💡ማህበረሰባችንን ከስህተት አስተሰብ ለመጠበቅ አሁኑኑ ለሁሉም Share (ሼር) ያድርጉ❕
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ | 2 902 |
| 6 | ይቺን ዓመት ተወኝ
ከአመት እስከ አመት ፍሬን ሳላፈራ ደረቅ እንደሆንኩኝ
በራድ ወይም ትኩስ ሁለቱንም ሳልሆን እንዲያው ለብ እንዳልኩኝ አለሁኝ በቤትህ ለሙን መሬትህን እንዳጎሳቆልኲኝ
አውቃለሁ አምላኬ ፍሬን ለመቀበል እንዳመላለስኩሁህ
ዛሬም ሳላፈራ እሾህን አብቅዬ ደርቄ ጠበኩህ
ያልተደረገልኝ ያላፈሰስክብኝ ያልሰጠኸኝ የለም
ነገር ግን ይህ ሁሉ አላርምህ አለኝ አለየኝም ከዓለም
አዝ
የማትሰለቸኝ ሆይ ተነስቼ እስክቆም እባክህ ታገሰኝ
የኔን ክፋት ተወው መላክህን ሰምተህ ይቺን ዓመት ተወኝ
አዝ
አውቃለሁ ታውቃለህ ቀጠሮን ሰጥቼ እንደማላከብር
ብዙ ጊዜ አቅጄ ብዙ ጊዜ ዝቼ በወሬ እንደምቀር
ዘንድሮስ እንዳልኩኝ አምና ይሔን ጊዜ ሰምተኸኝ ነበር
ምንም ሳልለወጥ ዘንድሮዬ አልፎ በአዲስ ተቀየረ
አዝ
ፍሬ የማይወጣኝ እኔን በመኮትኮት እጆችህ ደከሙ
እኔ ግን አለሁኝ ዛሬም አልበቃኝም በኃጢአት መታመሙ
የቃልህን ውሃ በድንጋይ ልጅህ ላይ ሳታክት ስታፈስ ዘመን ተቆጠረ
ወደ ልቤ ሳይሰርግ ሕይወቴን ሳይለውጥ እንዲያው ፈሶ ቀረ
አዝ
ቃልህን ጠግቤ እያገሳሁት ነው ሌሎች እስኪሰሙ
በቃልህ መኖር ግን አልያዝህ አለኝ ከበደኝ ቀለሙ
ብዙ ጥቅስ አገኘው ከቅዱስ መጽሐፍህ ገልጬ አይቼ
ከራሴ ላይ ብቻ አንድ ጥቅስ አጣሁኝ በበደል ተኝቼ
አዝ
ውጤቴ ደካማ ትምህርት የማይሰርፀኝ ተማሪ ብሆንም
ይቺን ዓመት ተወኝ ደግሞ ትንሽ ልማር ታገሰኝ አሁንም
እባክህ አልቆረጥ በቅዱስ መሬትህ ልቆይ ፍቀድልኝ
ያፈሩት ቅዱሳን የፍሬያቸው ሽታ መዓዛ እንዲደርሰኝ
አዝ
የተሸከምከኝ ሆይ ዛሬም ተሽከመኝ አትሰልቸኝ አደራ
ማን ይታገሰኛል ጠላት እየሆንኩት አይሰሩ ስሰራ
አታውጣኝ ከቤትህ ብዙ ቦታ አልይዝም ፍሬ ስለሌለኝ
ስፍራ የማያሻኝ ቤት የማላጣብብ ፍሬ አልባ በለስ ነኝ
አዝ
ቦታስ የሚይዙ ባለምግባሮቹ ቅዱሳንህ ናቸዉ
ልክ እንደ ዘንባባ የተንዥረገገ ተጋድሎ ፅድቃቸው
ከሊባኖስ ዝግባ እጅጉን የበዛ ገድል ትሩፋታቸው
አዝ
እኔ አይደለሁም ቦታስ የሞትይዘው ያንተው እናት ናት
ስሮቿ በምድር ጫፎቿ በሰማይ ሲደርሱ ያየናት
ይቺን ዓመት ተወኝ ከስሯ ሆናለው ባፈራ ምናልባት
አዝ
ይቺን ዓመት ተወኝ እባክህ አምላኬ አንድ ዓመት ምንህ ናት
ሺ ዓመት አንድ ቀን አይደለም ወይ ላንተ ዓመት ኢምንት ናት
ይሔ ዓመት አልፎ ዳግም ዓመት ስጠኝ እስከምልህ ድረስ
እባክህን ጌታ ይቺን ዓመት ተወኝ የወጉን እንዳደርስ
መዝሙር
🎙ዘማሪ ዲያቆን ቀዳሚ ጸጋ🎤
❖═@OrthodoxTewahedoTrue═❖
❖═@OrthodoxTewahedoTrue═❖
❖═@OrthodoxTewahedoTrue═❖ | 4 205 |
| 7 | 📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ ፳፩/21
🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
📌በዚች ቀን አምላክን በሥጋ የወለደች የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የበዓሏ መታሰቢያ (ወርሃዊ በዓል) ነው።
📌እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስለ ይቅርታና ስለ ምሕረት ሁልጊዜ በልጇና በአምላኳ ፊት ስለ እኛ ድኅነት ታማልዳለች።
📌እግዚአብሔር አምላክ ለሰው ልጅ የሕይወትና የድኅነት ወደብ ትሆነን ዘንድ ቅድስት እናቱን ስለሰጠን ስሙ የተባረከና የተመሰገነ ይሁን።
"ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ የሕይወትና የድኅነት ወደብ ትሆነን ዘንድ እርሷን እናቱን ስለሰጠን፤ በረከቷም በሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ላይ ይደር ለዘላለሙ አሜን።"
ምንጭ፦📖#መጽሐፈ_ስንክሳር
"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"
(የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል)
✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📔)
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
📌የዓለም ሁሉ አማላጅና የድኅነት ወደብ የሆነችውን የእመቤታችንን የበረከት መታሰቢያ ታሪክ ለወዳጅ ዘመድዎ Share በማድረግ የበረከቷ ተካፋይ ይሁኑ❕ | 4 292 |
| 8 | 😇መምህር ገብተዋል 📖📖
📚ቅዱስ ቁርባን ለምን እንቀበላለን📖📚
📔 ትምህርት ተጀምሯል ላይቭ ግቡ 🙏
ከታቺ ባለው ሊንክ ግቡ ቭኦይስ ቻት ግቡ 👇👇
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12?videochat=132ae57e1a061a7502
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12 | 716 |
| 9 | ✝ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር ይፈልጋሉ? | 213 |
| 10 | ✝ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር ይፈልጋሉ? | 884 |
| 11 | 📍 ለመሆኑ በቴሌግራም ትልቁን የኦርቶዶክስ መዝሙር ቻናል ተቀላቅለዋል ? የሰርግ ፣ የሀዘን ፣ የንግስ መዝሙራት ፣ የተለያዩ ወረባት ፣ የመዝሙር ግጥሞችን ያገኛሉ ። አብረውንም መዝሙራትን ያጠናሉ ። # ይቀላቀሉን 👇👇
https://t.me/+_R21gL_5brU5MDRk
https://t.me/+_R21gL_5brU5MDRk | 706 |
| 12 | 🔴ታሪካዊ አመጣጥ — የሮም ግዛት እና ንጉሥ ኔሮ
ክፍል (፬)4
የዮሐንስ ራእይ የተጻፈው በመጀመሪያው
ክፍለ ዘመን መጨረሻ አካባቢ፣ ክርስቲያኖች በሮም ነገሥታት እጅግ ዘግናኝ መከራ፣ ግፍ እና ስደት ይቀበሉ በነበረበት ታሪካዊ ወቅት ነው።
በዚያ ዘመን የነበረው የሮም ንጉሥ ቄሳር ኔሮ (Nero Caesar) ክርስቲያኖችን በእሳት ያቃጥል፣ ለአራዊት ይሰጥ እና በግፍ ይገድል ነበር። እራሱንም እንደ አምላክ በመቁጠር ሰዎች እንዲሰግዱለት ያስገድድ ነበር።
በሮም ግዛት ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ለንጉሡ ጣዖት ካልሰገዱና ካላጠኑ የመግዛትና የመሸጥ መብታቸውን ያጡ ነበር።
ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ይህንን መልእክት ለታደሙት ክርስቲያኖች ሲጽፍ፣ የሮም መንግሥት ምስጢሩን አውቆ ተጨማሪ ስደት እንዳያደርስ ሲል በምስጢራዊ የፊደል ስሌት (Gematria) ጻፈው።
"ቄሳር ኔሮ" የሚለው ስም በዕብራይስጥ ፊደላት ተጽፎ በፊደላቱ ቁጥር ሲደመር (ኔሮን ቄሳር)፦
ኑን (N) = 50
ሬሽ (R) = 200
ቫቭ (O/U) = 6
ኑን (N) = 50
ቆፍ (Q) = 100
ሳሜክ (S) = 60
ሬሽ (R) = 200
አጠቃላይ ድምር = 666
ስለሆነም ለዚያ ዘመን ክርስቲያኖች 666 ማለት ቤተክርስቲያንን የሚያሳድደው፣ እራሱን እንደ አምላክ የቆጠረው እና ክርስቲያኖችን ያሰቃይ የነበረው የንጉሥ ኔሮ አምባገነናዊ መንፈስና አሰራር ነበር።
ይህ ታሪካዊ አውድ የሚያሳየን፣ የራእይ መጽሐፍ በወቅቱ ለነበሩት አማንያን ቀጥተኛና ተግባራዊ መልእክት የነበረው መሆኑን ነው።
አውሬው የተባለው እግዚአብሔርን የሚቃወም፣ አምልኮን ለእሱ የሚጠይቅ እና አማንያንን
የሚያሳድድ ማናቸውም አምባገነናዊና ሰይጣናዊ ሥርዓት ነው።
✍️አዘጋጅ፦ Orthodox Tewahedo True
🌀ይቀጥላል🔴
💡ታሪካዊ እውነታዎችን ለሌሎች ለማሳወቅ አሁኑኑ ይህንን ፅሁፍ Share (ሼር) ያድርጉት❕
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ | 5 105 |
| 13 | 📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ ፳/20
🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
📌በዚች ቀን ታላቁና ክቡሩ የሠራዊት አለቃ ቅዱስ ቴዎድሮስ መስፍን (ዘበናድልዮስ) በሰማዕትነት አረፈ።
📌"የቅዱሱ አባት ዮሐንስ የግብፅ ሰው ሲሆን፣ እናቱ አረማዊ ነበረች።"
ቅዱስ ቴዎድሮስ በአደገ ጊዜ ተጠምቆ ክርስቲያን ሆነ፤ በጀግንነቱም የንጉሡ የሠራዊት አለቃ ሆኖ ተሾመ።
የበርበር ሰዎች በሮማውያን ላይ በተነሡ ጊዜ፣ ቅዱሱ ከምድራዊ ጦር ይልቅ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ታምኖ ብቻውን ወደ ጦርነቱ በመግባት ጠላቶችን በሙሉ ድል አደረገ።
📌በተጨማሪም አውኪስጦስ በሚባል አገር በየዕለቱ ሰዎችን ይበላ የነበረውን ታላቅ ዘንዶ፣ የአንዲት መበለት ልጆችን ሊበላ ሲል በጸሎቱና በጦሩ ወግቶ በመግደል ሕዝቡንና ሕፃናቱን አዳነ።
📌ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስ ክርስቲያኖችን ማሠቃየት በጀመረ ጊዜ፣ ቅዱስ ቴዎድሮስ በንጉሡ ፊት በክርስቶስ አምላክነት በግልጥ መሰከረ።
ንጉሡም ተቆጥቶ በጋለ የብረት አልጋ ላይ ቢያስተኛውና እሳት ቢያነድድበትም፣ እግዚአብሔር እሳቱን እንደ ንጋት ቁር በማቀዝቀዝ አዳነው።
ይህንን ድቅ ተአምር ያየው የንጉሡ የጭፍራ አለቃ አምኖ በሰማዕትነት አረፈ።
📌መኰንኑ ማሠቃየቱ በሰለቸው ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ፤ ራሱም ሲቆረጥ ደምና ወተት ፈሰሰ።
ሥጋውን እሳት ውስጥ ቢጥሉትም እሳቱ አልነካውም።
እናቱ ወታደሮቹን ወርቅ መስጣ ሥጋውን ወስዳ በአባቱ አገር በሰጥብ በተሠራችው ቤተ ክርስቲያን አኖረችው፤ ከሥጋውም ታላቅ ድኅነትና ተአምራት ተገለጠ።
"ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።"
ምንጭ፦📖#መጽሐፈ_ስንክሳር
"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"
(የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል)
✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📔)
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
📌በአምላኩ ኃይል የታመነውንና ዘንዶውን የገደለውን የታላቁን ሰማዕት የቅዱስ ቴዎድሮስን ገድል Share በማድረግ የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ❕ | 5 760 |
| 14 | 🔴የቁጥሩ ምስጢራዊ ትርጉም እና የቁጥር-ፊደል (Gematria) ስሌት
ክፍል (፫)3
በጥንታዊው ዘመን (በዕብራይስጥ፣ በግሪክ እና በግዕዝ ቋንቋዎች) እንደ ዛሬው የዓረብኛ የቁጥር ምልክቶች (1, 2, 3...) አልነበሩም።
ይልቁንም እያንዳንዱ ፊደል የራሱ የቁጥር እሴት ነበረው።
ለምሳሌ በግዕዝ ቋንቋ "ሀ" 1፣ "ለ" 2፣ "ሐ" 3 እንደሆነው ሁሉ፣ በዕብራይስጥም "አሌፍ" 1፣ "ቤት" 2፣ "ጊመል" 3 እየተባለ ይቆጠራል። ይህ አሰራር በስነ-ጽሁፍና በቋንቋ ጥናት "ጌማትሪያ" (Gematria) ይባላል።
የቁጥሩ መንፈሳዊና ምስጢራዊ ምሳሌነት፦
ቁጥር 7 (ሰባት)፦ በመጽሐፍ ቅዱሳዊ የቁጥር ምስጢር የፍጹምነት፣ የቅድስና እና የመለኮታዊ እረፍት ምልክት ነው።
እግዚአብሔር ፍጥረታትን ፈጥሮ በ7ኛው ቀን አረፈ፤ በብሉይና በሐዲስ ኪዳን 7 ቁጥር የፍጹምነት ማሳያ ነው (7 የቤተክርስቲያን ምስጢራት፣ 7 ሊቃነ መላእክት ወዘተ)።
ቁጥር 6 (ስድስት)፦ የሰው ልጅ የተፈጠረበት ቀን (6ኛው ቀን) በመሆኑ የሰው ምልክት ነው፤ ነገር ግን ከፍጹምነት (ከ7) አንደኛ ጎድሎ የሚገኝ የቁጥር ደረጃ ነው።
666 (ሦስት ጊዜ ስድስት)፦ በዕብራይስጥ ባህል አንድን ነገር ሦስት ጊዜ መደጋገም የነገሩን የመጨረሻ ደረጃና ማረጋገጫ ማሳያ ነው (ምሳሌ፡ "ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር" - ኢሳይያስ 6፡3)።
ስለዚህ 666 ማለት ፍጹም ለመሆን እና እግዚአብሔርን ለመሰልጠን የሚታገል፣ ነገር ግን ሁልጊዜ ከእግዚአብሔር ፍጹምነት (7) ጎድሎ የሚቀር የሰይጣናዊ ትዕቢት፣ የሐሰት አምልኮ እና የሰው ልጅ ውድቀት መገለጫ ነው።
አውሬው እራሱን እንደ አምላክ ለማድረግ ይሞክራል፤ ነገር ግን በምንም ተአምር የፍጹምነት ቁጥር ወደሆነው ወደ 7 መድረስ አይችልም።
ሁልጊዜ በ 6 ላይ ይቆማል።
ሦስት ጊዜ 666 መባሉ የውድቀቱን እና የእግዚአብሔርን ፍጹምነት ሊደርስበት አለመቻሉን በጥብቅ የሚያስረዳ የመጽሐፍ ቅዱስ ምስጢር ነው።
✍️አዘጋጅ፦ Orthodox Tewahedo True
🌀ይቀጥላል🔴
💡ወንድሞችና እህቶች ከውዥንብር እንዲድኑ ይህንን ጠቃሚ መልእክት አሁኑኑ Share (ሼር) ያድርጉ❕
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ | 5 449 |
| 15 | 💵P2P ወይም cryptocrrency እና blockchain በርካታ ተጠቃሚዎች አሉት።
በP2P ወይም በክሪብቶ ከረንሲ ተጠቅመን እንዴት ገንዘብ ማግኘት እንችላለን⁉️ | 648 |
| 16 | ስሙ ገብርኤል ነው
ስሙ ገብርኤል ነው
ከእሳት የሚያወጣ፤
ብስራትና ደስታን ለዓለም የሚያመጣ(፪)።
እንኳን ከነደደው ገና ከታሰበው፤
ያተርፋል ያድናል ፈጥኖ እእሚደርስ ነው(፪)።
ከትናንቱ ይልቅ ዛሬ እሚሳሳልኝ፤
በመንገዴ ቀድሞ ነገን ሚጠብቀኝ፤
አሊዝም ጋሻ ጦር አልሻም ወታደር፤
የገብርኤልን ስዕል እሰቅላለሁ ከበር።
ገብርኤል ገብርኤል የቤታችን ዘውድ፤
የእናት አባቶቼ መመኪያ ዘመድ።
አዝ
አራተኛ ሆኖ በእሳት ውስጥ ታያችሁ፤
እርሱ ገብርኤል ነው የሚታደጋቸው፤
ከሰው ጋር የሚቆም ለህዝብ የሚራራ፤
ይምጣ ለሀገራችን ከሚካኤል ጋራ ፤
ገብርኤል ገብርኤል ገብርኤል ለሚሉ፤
አበርቺ መልአክ ነው ስሙን ለሚጠሩ።
አዝ
ከመላእክቱ አለም ከራማ ይመጣል፤
ሁሉን ወደመዳን ወደፅድቅ ይመራል፤
ኃያል ነው ገብርኤል የነገዶች መሪ፤
የጽናት ሰባኪ እምነት አስተማሪ።
ገብርኤል ገብርኤል ኦ ልዑለ ራማ፤
ለተከዘችው ነፍስ ደስታን የሚያሰማ።
አዝ
በጓዳ ነግሬው በአደባባይ ረዳኝ፤
በሰዎች መካከል ምስክር አረገኝ፤
በምን ፍጥነት አየኝ ኧረ እንዴት ደረሰ፤
ወላፈን ሳይነካኝ እንባዬን አበሰ፤
ገብርኤል ገብርኤል ፀዋሪ ምሕረት፤
ከአደጋ ሚጋርድ ሚመራ ከፊት።
መዝሙር
🎙ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ🎤
❖═@OrthodoxTewahedoTrue═❖
❖═@OrthodoxTewahedoTrue═❖
❖═@OrthodoxTewahedoTrue═❖ | 6 744 |
| 17 | 📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ሐምሌ ፲፱/19
🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
📌በዚች ቀን ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ እና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ ስለ ክርስቶስ ስም የተቀበሉት ታላቅ የሰማዕትነት መከራ ይታሰባል።
📌ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ዕድሜው ገና ፫ (3) ዓመት ሳለ፣ እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ ከስደት አገር ለዚያው ለሸሸችው መኰንን አሳልፈው ሰጧት።
መኰንኑም ስለ አምልኮ በጠየቃት ጊዜ "ይህ ሦስት ዓመት የሆነው ሕፃን አማልክትህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን" ብላ ሕፃኑን አቀረበችው።
እግዚአብሔርም ለሕፃኑ ኃይልና ንግግርን ሰጥቶት ንጉሡን፣ መኳንንቱንና ጣዖታቱን ረገመ፤ መኰንኑንም "ላንተ ኀዘንና ልቅሶ፣ ጥርስ ማፋጨትም ነው" አለው።
📌መኰንኑም በማፈር ታላላቆች እንኳ የማይችሉትን አስጨናቂ ሥቃይ በሕፃኑና በእናቱ ላይ አደረሰ፤ እግዚአብሔር ግን ያለምንም ጉዳት ያነሣቸው ነበር።
በሕፃኑም ላይ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አድሮ ብዙ በሽተኞችን ፈወሰ፤ ይህንን ያዩ ብዙ አሕዛብም አምነው በሰማዕትነት አረፉ።
📌ከዚህ በኋላ መኰንኑ በታላቅ የናስ ጋን ውስጥ ውኃ አፍልተው እንዲጥሏቸው አዘዘ።
የፍላቱ ድምፅ እንደ ነጐድጓድ በሆነ ጊዜ በእናቱ ላይ ፍርሃት ቢገባባትም፣ ሕፃኑ ቂርቆስ ወደ እግዚአብሔር ጸልዮ ጌታችን የሰማያዊውን ክብር ስላሳያት ልቧ ጸና።
ወደ ጋኑም በገቡ ጊዜ የታዘዘው የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ የእሳቱን ኃይል አቀዘቀዘው፤ ውኃውም እንደ ንጋት ውርጭ ቀዘቀዘ።
📌መኰንኑ ሥጋቸው ተቆራርጦ እስኪወድቅ በመቃጥን ውስጥ እንዲጐትቷቸው ቢያደርግም መልአኩ አዳናቸው።
በወህኒ ቤትም በዘጋቸው ጊዜ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወርዶ አጽናናቸው፤ ስሙን ለሚጠራና መታሰቢያውን ለሚያደርግ ሁሉ ታላቅ ቃል ኪዳን ሰጠው።
"ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ቂርቆስና በኢየሉጣ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን።"
ምንጭ፦📖#መጽሐፈ_ስንክሳር
"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"
(የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል)
✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📔)
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
📌በሕፃንነቱ የእሳት ነበልባልን ያበረደውን የቅዱስ ቂርቆስንና የእናቱን የቅድስት ኢየሉጣን ገድል፣ እንዲሁም የሊቀ መላእክት የቅዱስ ገብርኤልን ተአምር Share በማድረግ የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ❕ | 7 373 |
| 18 | 😇መምህር ገብተዋል 📖📖
📔 ትምህርት ተጀምሯል ላይቭ ግቡ 🙏
online ያላቹ ላይቪ ግቡ የሚደንቅ ትምህርት በእውነት ለመምህራችን ቃል ሕይወት ያሰማልን ትምህርቱ እንዳያመልጣችሁ ላይቭ ግቡ
ከታቺ ባለው ሊንክ ግቡ ቭኦይስ ቻት ግቡ 👇👇
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12?videochat=132ae57e1a061a7502
https://t.me/Bete_kidus_Michael_12 | 530 |
| 19 | በሐምሌ 19 ቀን በሚከበረው የቅዱስ ገብርኤል በዓል፣ መልአኩ ከፈላው ድስት ያዳናቸው ቅዱሳን እነማን ናቸው⁉️ | 7 359 |
| 20 | እስኪ ለነፍስዎ ምን ያህል ጊዜ ሰጡ⁉️📚
የንባብ ባህልዎን የሚያሳድጉና እምነትዎን የሚያጸኑ ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍትን በቀላሉ በስልክዎ ያግኙ።
የዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ስብስቦችን ጨምሮ በርካታ መንፈሳዊ መጻሕፍት በPDF መልኩ በቻናላችን ቀርበውልዎታል።
አሁኑኑ Join በማድረግ የቤተሰባችን አባል ይሁኑ❕
👇👇
👉@EOTCblogs
👉@EOTCblogs
👉@EOTCblogs | 401 |
