Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
#ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ #Orthodox 📜 #የዕለቱ #ስንክሳር (#የቅዱሳን_ታሪክ) 💡 የአባቶች ምክርና ትምህርት 📖 ሕይወትን የሚቀይሩ ጥልቅ የአባቶች ምክር እና ትምህርቶች ይተላለፋሉ። 📌 ማስታወቂያ ለማሰራት 👉 @tadilogos ያግኙን። Buy ads: https://telega.io/c/OrthodoxTewahedoTrue
Ko'proq ko'rsatish📈 Telegram kanali Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ analitikasi
Orthodox Tewahedo ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ (@orthodoxtewahedotrue) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 169 372 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 140-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 138-o'rinni egallagan.
📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika
невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 169 372 obunachiga ega bo‘ldi.
05 Sentabr, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -1 017 ga, so‘nggi 24 soatda esa -185 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.
- Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
- Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 3.79% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 2.69% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
- Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 6 428 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 4 555 ta ko‘rish yig‘iladi.
- Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 52 ta reaksiya keladi.
📝 Tavsif va kontent siyosati
Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“#ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ #Orthodox
📜 #የዕለቱ #ስንክሳር (#የቅዱሳን_ታሪክ)
💡 የአባቶች ምክርና ትምህርት
📖 ሕይወትን የሚቀይሩ ጥልቅ የአባቶች ምክር እና ትምህርቶች ይተላለፋሉ።
📌 ማስታወቂያ ለማሰራት 👉 @tadilogos ያግኙን።
Buy ads: https://telega.io/c/OrthodoxTewahedoTrue”
Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 06 Sentabr, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.
Ma'lumot yuklanmoqda...
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 06 Sentabr | 0 | |||
| 05 Sentabr | 0 | |||
| 04 Sentabr | 0 | |||
| 03 Sentabr | 0 | |||
| 02 Sentabr | 0 | |||
| 01 Sentabr | +196 |
| 2 | 🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
📌 ጳጒሜን ፩ (1) በዚች ቀን የተባረከው የጳጒሜን ወር ባተ።
በዚችም ዕለት የወንጌላዊው የቅዱስ ዮሐንስ ረድእ፣ ሐዋርያና ሰማዕት የሆነው የከበረ ቅዱስ ዑቲኮስ ዕረፍቱ ነው።
📌 ይህ ቅዱስ አስቀድሞ ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስን ሲያገለግልና ሲታዘዝ የኖረ ሲሆን፣ በኋላም ከሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ጋር በመሆን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በአረማውያንና በዮናናውያን ዘንድ ወንጌልን ሰበከ፤ ብዙዎችንም አሳምኖ አጠመቀ።
📌 የጣዖታትን ቤቶች በማፍረስ አብያተ ክርስቲያናትን ያነጸ ሲሆን፣ ስለ ጌታችን ስም ከከሀዲያን ዘንድ መታሠርና ጽኑዕ ግርፋትን ተቀብሏል።
የእግዚአብሔርም መልአክ ወደ እስር ቤት እየመጣ ይመግበውና ያጸናው ነበር።
📌 ከዚህም በኋላ ወደ እሳትና ወደ አንበሶች ጉድጓድ ቢጥሉትም እሳቱ አልነካውም፤ አንበሶቹም እንደ በጎች የዋሃን ሆኑለት።
📌 በኋላም በእግዚአብሔር መልአክ መሪነት ወደ ቍስጥንጥንያ አገር ሄዶ ተጋድሎውን ፈጽሞ በመልካም ሽምግልና አርፏል።
"ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሐዋርያው ጸሎት ይማረን፤ በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።"
ምንጭ፦📖📖#መጽሐፈ_ስንክሳር
"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"
(የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል)
✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📖)
📌 የወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ረድእና የሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ባልንጀራ የሆነውን የቅዱስ ዑቲኮስን ተጋድሎና በረከት Share በማድረግ የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ❕ | 3 269 |
| 3 | 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
🌼💧 ጳጉሜን
ጳጉሜን በቅድስት ቤተክርስቲያናችን ዕለተ ምጽአት የሚታሰብበትና ከሁለቱ የፈቃድ አጽዋማት አንዱ የሚጾምበት ወር ነው።
💧 ጳጉሜን ማለት ምን ማለት ነው❔
ትርጉሙ፦ “ጭማሪ” ማለት ሲሆን በዓመቱ መጨረሻ ላይ 5 ወይም 6 ቀን ሆና የምትመጣ ወር ናት።
የዘመን አቆጣጠር፦ በየ4 ዓመቱ (በዘመነ ሉቃስ) 6 ቀን ስለምትሆን አገራችን ኢትዮጵያ “የ13 ወራት ጸጋ” በመባል ትታወቃለች።
የገና ጾም፦ ጳጉሜን 6 በምትሆንበት ዓመት ጾመ ነቢያት ሕዳር 15 ቀን ገብቶ ታኅሣሥ 28 ቀን ይፈታል።
✝️ጾመ ዮዲት (የጳጉሜን የፈቃድ ጾም)
ዮዲት ማን ናት❔ በታሪክ የምትታወቀው ዮዲት ጉዲት እንዳልሆነች ልብ ይሏል።
የጾሙ ታሪክ፦ የፋርስ ንጉሥ ናቡከደነፆር በላከው ሠራዊት አማካኝነት በእስራኤላውያን ላይ ታላቅ መከራ በደረሰ ጊዜ፣ ባሏ ሞቶባት በንጽሕና የምትኖረው ዮዲት ማቅ ለብሳና አማድ ነስንሳ ወደ አምላክ አለቀሰች።
ውጤቱ፦ በ3ኛው ቀን እግዚአብሔር በገለጸላት መመሪያ መሠረት በጾምና በጸሎት ባገኘችው ኃይል ጠላታቸውን አሸንፈዋል።
ምእመናንም ጥንተ ጠላታችን ሰይጣንንና ፈቃደ ሥጋን ለማሸነፍ ጳጉሜን በፈቃድ ይጾማሉ።
🎺 ዕለተ ምጽአት የሚታሰብበት ወር
ጳጉሜን ከክረምት ወደ አዲስ ዓመት መሸጋገሪያ እንደሆነች ሁሉ፣ ምጽአትም ከጊዜያዊው ወደ ዘለዓለማዊና ከምድራዊ ወደ ሰማያዊ ሕይወት መሸጋገሪያ በመሆኑ ዕለተ ምጽአት ይታሰብበታል።
አምላካችን እግዚአብሔር አዲሱን ዓመት የተባረከ ያድርግልን❕ አሜን።
ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩ‼️
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ | 4 463 |
| 4 | ✝ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር ይፈልጋሉ? | 625 |
| 5 | 💒 የአለማየሁ ዋሴ መፅሐፍት📚
▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰
➱ 1, እመጓ📚
➱ 2, ዝጓራ 📚
➱ 3, መርበብት 📚
➱ 4, ሰበዝ 📚
➱ 5, ሜተራሊዮን📚
➲ ኦርቶዶክሳዊ መፅሐፍ ማውጫ 📖
| 828 |
| 6 | 📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ነሐሴ ፴ (30)
🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
📌 በዚች ቀን ከ፲፮ቱ (16ቱ) ታላላቅ ነቢያት አንዱ የሆነው ታላቁ ነቢዩ ሚልክያስ ዕረፍቱ ነው።
📌 ይህ ነቢይ የእስራኤል ልጆች ከባቢሎን ምርኮ ከተመለሱ በኋላ የእግዚአብሔርን ሕግና ትእዛዝ በመተላለፋቸው፣ ስለ አሥራትና በኵራትም ጉድለት ገሥጿቸዋል።
📌 እግዚአብሔርም በነቢዩ ሚልክያስ አንደበት፦ "ዐሥራቴንና በኵራቴን አስገቡና እስቲ ፈትኑኝ፤ የሰማይን መስኮት ባልከፍትላችሁ፣ በረከትንም አትረፍርፌ ባላፈስስላችሁ፣ የምድራችሁንም ፍሬ ከነቀዝ ባልጠብቅላችሁ" በማለት መናገሩን አስተምሯል።
📌 ዳግመኛም ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በፊት መጥምቁ ዮሐንስ በነቢዩ ኤልያስ መንፈስና ኃይል አስቀድሞ ስለመጣቱ፣ ስለ አይሁድ ክህነት መሻርና በአሕዛብ መካከል ንጹሕ መሥዋዕት የሚቀርብበት አዲስ የክህነት ሥርዓት እንደሚተካ ትንቢት ተናግሯል።
📌 ነቢዩ ሚልክያስ መልካሙን ተጋድሎ ፈጽሞ እግዚአብሔርን በቅንነት ካገለገለ በኋላ በሰላም አርፏል።
"ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በነቢዩ ጸሎት ይማረን፤ በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።"
ምንጭ፦📖📖#መጽሐፈ_ስንክሳር
"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"
(የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል)
✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📖)
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
📌 ስለ አሥራትና በኵራት እንዲሁም ስለ መጥምቁ ዮሐንስ ታላቅ ትንቢት የተናገረውን የታላቁን ነቢይ የቅዱስ ሚልክያስን ገድልና በረከት Share በማድረግ የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ❕ | 5 475 |
| 7 | ☎️ስልኩን ስትነኩት የሚወስዳችሁ ቻናል ለህይወታችሁ ጠቃሚ ስለሆነ ስልኩን ይጫኑ
/Start
╭━━━━━━━╮
┃ ● ══ ▪
┃███████┃
┃███████┃
┃███████┃
┃███████┃
┃███████┃
┃███████┃
┃███████┃
┃███████┃
┃███████┃
┃ 🔘 ┃
╰━━━━━━━╯ | 891 |
| 8 | https://www.youtube.com/live/ZXoCizVhXUo?si=dK3pBFTgsWeyxCaO | 1 100 |
| 9 | 💡በመምህር ዶ/ር ዘበነ ለማ የተፃፈው መጽሐፈ አሜን ወሥርዓት ልታነቡት የሚገባ ድንቅ መፅሐፍ ነው❕
🔒መፅሐፉ ከሌላችሁ በPDF ለማግኘት
👉@EOTC_Library✅
👉@EOTC_Library✅ | 1 534 |
| 10 | 📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ነሐሴ ፳፱ (29)
🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
📌 በዚች ቀን የታላቁና የትሑቱ አባታችን የአባ ዮሐንስ ሐጺር (አጭሩ) ቅዱስ ሥጋ ከአንጦንዮስ ገዳም (ከቊልዝም) ወደ አስቄጥስ ገዳም የተፈለሰሰበት (የሥጋው ፍልሰት) በዓል ነው።
📌 በ፬፹፰ኛ (48ኛ) የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት በአባ ዮሐንስ ዘመን፣ የአስቄጥስ ገዳም መነኰሳት የቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር ሥጋ በመካከላቸው ይሆን ዘንድ ስለ ተመኙ፣ ሊቀ ጳጳሳቱና የቊልዝም አገር መኰንን በጋራ በመተባበር ቅዱስ ሥጋውን በታላቅ ጥንቃቄ ከቊልዝም አፍልሰው አመጡት።
📌 ቅዱስ ሥጋው ወደ አስቄጥስ ገዳም በደረሰ ጊዜ መነኰሳቱ መስቀል፣ ወንጌል፣ ማዕጠንትና መብራት ይዘው በታላቅ ዝማሬ ተቀበሉት፤ በአባ መቃርስም ሥጋ አጠገብ አኖሩት።
በቅዳሴ ጊዜም ወንጌል ሲነበብ ቤተ ክርስቲያኒቱ በሰማያዊ ብርሃን በራች፣ እጅግ የበዛ መልካም መዓዛም ቦታውን ሞላው።
📌 በኋላም ሊቀ ጳጳሳቱ አባ ማርቆስ ከብዙ ኤጲስቆጶሳት ጋር ወደ አባ ዮሐንስ ሐጺር ቤተ ክርስቲያን ገብተው ቅዱስ ሥጋውን ሲገልጡና ሲሳለሙ መብረቅና ነጐድጓድ ሆነ፤ በዚያ የነበሩትም ሁሉ ደንግጠው ወደቁ።
📌 ቅዱስ አባታችን አባ ዮሐንስ ሐጺር በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ኃይል በዓለም ሁሉ ተዘዋውሮ የጣዖታትን ቤቶች ያፈረሰ፣ ሃይማኖትን የሰበከ፣ ድውያንን የፈወሰና አጋንንትን ያሳደደ ታላቅ የትሕትና አባት ነው።
የሥጋውም ፍልሰት በሰማዕታት ዘመን በ፭፻፳ (520) ዓመት ሆነ።
"ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ጻድቅ ጸሎት ይማረን፤ በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።"
ምንጭ፦📖📖#መጽሐፈ_ስንክሳር
"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"
(የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል)
✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📖)
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
📌የታላቁ አባታችን የታላቁና የትሑቱ የአባ ዮሐንስ ሐጺርን (አጭሩ) የሥጋውን ፍልሰትና የተደረገውን አምላካዊ ተአምር Share በማድረግ የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ❕ | 6 593 |
| 11 | ፠ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መንፈሳዊ መዝሙራት፣ ቅዳሴዎች እና የጸሎት መጻሕፍት በአንድ ቦታ! ፠
የዜማ ተዋሕዶ (Zema Tewahedo) መተግበሪያን በመጫን መንፈሳዊ ሕይወትዎን ያበልጽጉ።
🎵 የመዝሙራት ስብስብ፦ ⛪️ ቅዳሴ እና ጸሎት 📅 የዕለቱ ስንክሳር እና በዓላት
📲 አሁኑኑ ዳውንሎድ ያድርጉ፦
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.zema.tewahedo
ለወዳጅ ዘመድዎ በማጋራት የመንፈሳዊ በረከቱ ተካፋይ ያድርጉ! | 5 402 |
| 12 | 🕊️ ም ክ ረ ቅ ዱ ሳ ን 🕊️
❝ ም ን ፍ ሬ አ ፈ ራ ን ❔ ❞
🕊️ 🍒 🕊️
የልምምድና የእድገት ምሳሌ፦
አንድ የሚታገል ሰው በየጊዜው ተጋጣሚውን እንዴት ማሸነፍ እንዳለበት ልምምድ የሚያደርግ ከሆነ ክህሎቱ ይዳብራል፤ በየጊዜው የሚያነብና ራሱን የሚያሻሽል ሐኪምም ጎበዝና ሕመምተኞችን በአግባቡ የሚረዳ ይሆናል።
በየቀኑ ቃሉ የሚነገረን እኛስ ምን ለውጥ አመጣን? ምንስ ፍሬ አፈራን❔
የዘመናት ምልልስና ፍሬ፦
እየተናገርኩ ያለሁት ለአንድ ዓመት ብቻ በቤተ ክርስቲያን ስለቆዩት ሳይሆን ከልጅነታችን ጀምረን በቤቱ ለምንመላለሰው ነው።
ይህን ያህል ዘመን በቤቱ እየተመላለስን ፍሬ ካላፈራን ቤተ ክርስቲያን ደርሰን ብንመጣ ምን ጥቅም አለው❔
የቤተ ክርስቲያን እውነተኛ ዓላማ፦
አባቶቻችን አብያተ ክርስቲያናትን ያነጹልን ዝም ብለን እንድንሰባሰብ አይደለም፤ መሰባሰቡንማ በሌላም ስፍራ እንሰበሰባለን።
ያነጹልን ቃሉን እንድንማርበት፣ በቃሉም የንስሐ ፍሬ እንድናፈራበት፣ ሥጋወ ደሙን እንድንቀበልበትና እርስ በርሳችን እንድንተራረምበት ነው።
ታዲያ እኛ ምን ፍሬ አፈራን❔
😇😇😇
😇😇😇
😇😇😇
😇😇😇ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ☦️
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ | 6 065 |
| 13 | በብዙ አገራት እንዳይታተሙ ታግደው የነበሩ፣ አነጋጋሪና አደገኛ ምስጢራትን የያዙ ኦርቶዶክሳዊ እና ዓለም አቀፍ መጽሐፎች በPdf የሚገኙበትን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ!
👇👇
@EOTC_Library 📚
@EOTC_Library 📚 | 1 696 |
| 14 | 📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ነሐሴ ፳፰ (28)
🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
📌 በዚች ቀን የዓለም ሁሉ አባቶችና የእምነት ምሳሌዎች የሆኑት የአብርሃም፣ የይስሐቅና የያዕቆብ መታሰቢያቸውን እናደርግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት አባቶቻችን ያዘዙበት ታላቅ ቀን ነው።
📌 አባታችን አብርሃም በእግዚአብሔር ጥሪ ከአገሩና ከዘመዶቹ ተለይቶ ወጣ፤ እግዚአብሔርም "ታላቅ ሕዝብ አደርግሃለሁ፣ ስምህንም ከፍ አደርገዋለሁ" ሲል ቃል ኪዳን ገባለት።
📌 አብርሃም የ፺፱ (99) ዓመት አረጋዊ በሆነ ጊዜ እግዚአብሔር በወይራ ዛፍ ሥር በሦስት ሰዎች አምሳል (በቅድስት ሥላሴ) ተገለጠለት።
አብርሃምም እንግዳ ተቀባይ ነበርና መግቦ አስተናገዳቸው፤ በዚያም ሚስቱ ሣራ በ፺ (90) ዓመቷ ወንድ ልጅ (ይስሐቅን) እንደምትወልድ አበሠሩት።
📌 ዳግመኛም አብርሃም በጌራራ አገር ሳለ ንጉሡ አቤሜሌክ ሣራን በወሰዳት ጊዜ፣ እግዚአብሔር በሕልም ተገልጦ በመገሠጽ ከጥፋት ጠበቃት፤ አብርሃምም ሰማያዊ ነቢይ ነበርና ስለ አቤሜሌክና ስለ ቤተሰቡ ጸልዮ ፈወሳቸው፣ የማሕፀናቸውንም መዘጋት ከፈተላቸው።
📌 አባታችን አብርሃም ያለ እንግዳ ማዕድ የማይበላ ታላቅ የትሩፋትና የርኅራኄ አባት ነበር፤ መልካሙን ተጋድሎ ፈጽሞ በ፯፭ (175) ዓመቱ በሰላም አረፈ።
"ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባታችን አብርሃም ጸሎት ይማረን፤ በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።"
ምንጭ፦📖📖#መጽሐፈ_ስንክሳር
"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"
(የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል)
✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📖)
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
📌 የእምነትና የእንግዳ ተቀባይነት አባት የሆኑትን የከበሩ የአባቶቻችንን የአብርሃም፣ የይስሐቅና የያዕቆብን ታሪክና በረከት Share በማድረግ የበረከታቸው ተካፋይ ይሁኑ❕ | 7 036 |
| 15 | ፠ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መንፈሳዊ መዝሙራት፣ ቅዳሴዎች እና የጸሎት መጻሕፍት በአንድ ቦታ! ፠
የዜማ ተዋሕዶ (Zema Tewahedo) መተግበሪያን በመጫን መንፈሳዊ ሕይወትዎን ያበልጽጉ።
🎵 የመዝሙራት ስብስብ፦ ⛪️ ቅዳሴ እና ጸሎት 📅 የዕለቱ ስንክሳር እና በዓላት
📲 አሁኑኑ ዳውንሎድ ያድርጉ፦
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.zema.tewahedo
ለወዳጅ ዘመድዎ በማጋራት የመንፈሳዊ በረከቱ ተካፋይ ያድርጉ! | 4 079 |
| 16 | 🕊️ ም ክ ረ ቅ ዱ ሳ ን 🕊️
❝ ስ ለ ፍ ቃ ር ና ት ሕ ት ና ❕ ❞
🕊️ 🍒 🕊️
እውነተኛው የፍቅር ሚዛን፦
አጠገብህ ያለውን ወንድምህን ሳትወድና ሳታከብር እግዚአብሔርን እወደዋለሁ ብትል ፍቅርህ ውሸት ነው። ሰውን ስታከብር ፈጣሪን ታከብራለህ፤ ሰው የእግዚአብሔር አምሳል ነውና።
ስለ ትሕትናና አገልግሎት፦
በታናናሾችና በደካሞች ውስጥ ክርስቶስ አለ።
ሰውን በትሕትና ማገልገልና መሸከም አምላክን እንደ መሸከም ይቆጠራል።
ስለ ጸሎት ትጋት፦
በጸሎት ጊዜ እንቅልፍ እንዳይጥልህና አእምሮህ እንዳይበታተን ልብህን በፈጣሪ ፍቅር እሰራው።
ያለ ትጋትና ያለ ንቅሃት መንፈሳዊ እድገት አይገኝም።
☦️ አባ ብሾይ☦️
ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩ‼
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ | 7 052 |
| 17 | 💡 ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ድንቅ ምስጢራትና ክብር ማወቅ ይፈልጋሉ?
በእርሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ የተጻፈው «መጽሐፈ አሐቲ ድንግል»
እያንዳንዱ ኦርቶዶክሳዊ ሊያነበውና ሊይዘው የሚገባ፣ ልብ የሚያሞቅና እውቀት የሚያስጨብጥ ልዩ መንፈሳዊ ሀብት ነው! 📖✨
ይህንን ድንቅ መጽሐፍ አግኝተው እንዲያነቡት በእጅጉ እንጋብዝዎታለን❕
🛡 መፅሐፉ ከሌላችሁ በPDF ለማግኘት
👉@EOTC_Library💎
👉@EOTC_Library💎 | 1 528 |
| 18 | https://www.youtube.com/live/zuA5sp-y7LI?si=yBsuCEqPaj3UuH90 | 1 297 |
| 19 | « በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ። »
(የዮሐንስ ወንጌል📖📖 16 ፥ 33)
እንኳን ለቸሩ መድኃኔዓለም ወርሃዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ❕
ይህ ዕለት የኃጢአታችንን ዕዳ ደምስሶ በዕፀ መስቀል ላይ የከፈለልንን ታላቅ የፍቅርና የምሕረት ዋጋ የምናስብበት ነው፤ መድኃኔዓለም ማለት « የዓለም መድኃኒት » ማለት ነው።
💡 ከዕለቱ ትምህርት የምንወስደው አጭር መንፈሳዊ ምክር
በሕይወታችሁ ምንም ዓይነት ፈተና፣ ጭንቅና ተስፋ ማስቆረጥ ቢገጥማችሁ ወደ ዓለም ኃጢአት ከመሮጥ ይልቅ የመስቀሉን ባለቤት መድኃኔዓለምን አስቡት፤ እርሱ ዓለምን እንዳሸነፈ ሁሉ እናንተንም ያሸንፍላችኋል።
በቤተሰባችሁ ውስጥ የሚያጋጥሙ የመከራና የጭንቅ ጊዜያት ሲበዙ በሰዎች እርዳታ ሳይሆን በቸሩ መድኃኔዓለም ምሕረትና አባታዊ ርኅራኄ ተስፋ በማድረግ ቤታችሁን በጸሎትና በምስጋና ጠብቁ።
😇« የቸሩ መድኃኔዓለም ፍቅርና ምሕረት ከሁላችን ጋር ይሁን❕»
ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩ‼
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖ | 8 470 |
| 20 | 📖📖 ስንክሳር ዘወርኀ ነሐሴ 27 (፳፯)
🤩በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
📌 በዚች ቀን በሊቀ ካህናቱ በኤሊ ዘመን ታላቁና ጻድቁ ነቢዩ ሳሙኤል በእግዚአብሔር የተጠራበት ታላቅ የመታሰቢያ ቀን ነው።
📌 ይህ ነቢይ በታናሽነቱ በቤተ መቅደስ ያደገ ሲሆን፣ ተኝቶ ሳለ እግዚአብሔር በስሙ ጠርቶታል።
📌 እግዚአብሔር አምላክም በኤሊ ፈንታ ለእስራኤል ልጆች ታላቅ ነቢይና ካህን አድርጎ ሾመው፤ ሕዝቡንም በእውነትና በቅንነት መራ።
"ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በነቢዩ ጸሎት ይማረን፤ በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።"
ምንጭ፦📖📖#መጽሐፈ_ስንክሳር
"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"
(የቅዱሳንን ዜና/ታሪክ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል)
✍️አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር📖)
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
❖══ @OrthodoxTewahedoTrue ══❖
❖═ @OrthodoxTewahedoTrue ═❖
📌 በታናሽነቱ በእግዚአብሔር ተጠርቶ ለእስራኤል ካህንና ነቢይ ሆኖ የተሾመውን የታላቁን ነቢይ የቅዱስ ሳሙኤልን በረከትና መታሰቢያ Share በማድረግ የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ❕ | 7 621 |
