fa
Feedback
ገድለ ቅዱሳን

ገድለ ቅዱሳን

رفتن به کانال در Telegram

@Gedelat ለተለያዩ አስተያየት እና ጥቆማ ማድረስ ከፈለጉ በአድራሻችን ቢያደርሱን ይደርሰናል፡፡ በአድራሻችን ✍ @Mnfesawi_bot

نمایش بیشتر
6 515
مشترکین
-424 ساعت
-147 روز
+2430 روز

در حال بارگیری داده...

ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
اوت '26
اوت '26
+109
در 1 کانال‌ها
ژوئیه '26
+127
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '26
+97
در 1 کانال‌ها
Get PRO
مه '26
+63
در 2 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '26
+77
در 2 کانال‌ها
Get PRO
مارس '26
+58
در 1 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '26
+44
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '26
+59
در 1 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '25
+98
در 2 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '25
+91
در 1 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '25
+77
در 1 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '25
+56
در 1 کانال‌ها
Get PRO
اوت '25
+103
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '25
+85
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '25
+99
در 1 کانال‌ها
Get PRO
مه '25
+96
در 1 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '25
+96
در 2 کانال‌ها
Get PRO
مارس '25
+140
در 1 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '25
+107
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '25
+190
در 1 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '24
+198
در 2 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '24
+66
در 1 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '24
+109
در 3 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '24
+60
در 1 کانال‌ها
Get PRO
اوت '24
+89
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '24
+129
در 2 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '24
+107
در 2 کانال‌ها
Get PRO
مه '24
+109
در 1 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '24
+120
در 2 کانال‌ها
Get PRO
مارس '24
+94
در 2 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '24
+74
در 2 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '24
+102
در 2 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '23
+116
در 3 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '23
+81
در 1 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '23
+98
در 7 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '23
+79
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '23
+73
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '23
+94
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '23
+64
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '23
+75
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '23
+78
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '23
+84
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '23
+54
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '23
+83
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '22
+62
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '22
+70
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '22
+54
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '22
+61
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '22
+48
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '22
+73
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '22
+47
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '22
+61
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '22
+75
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '22
+91
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '22
+57
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '22
+99
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '21
+55
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '21
+64
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '21
+141
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '21
+174
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '21
+223
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '21
+245
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '21
+205
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '21
+161
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '21
+520
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '21
+395
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '21
+333
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '21
+517
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '20
+9 090
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
29 اوت0
28 اوت+1
27 اوت+1
26 اوت+3
25 اوت0
24 اوت+6
23 اوت+2
22 اوت+7
21 اوت+1
20 اوت+3
19 اوت+8
18 اوت+3
17 اوت+2
16 اوت+11
15 اوت+6
14 اوت+3
13 اوت+3
12 اوت+8
11 اوت+7
10 اوت+4
09 اوت+4
08 اوت+3
07 اوت+6
06 اوت+2
05 اوت+3
04 اوت+1
03 اوت+3
02 اوت+3
01 اوت+5
پست‌های کانال
photo content

2
[ ስንክሳር ነሐሴ - ፳፫ - ] .mp3
208
3
🕊 [  †  እንኳን ለሰላሳ ሺ ግብጻውያን ሰማዕታት ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †   ] † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! † [ † 🕊  ሠለስቱ እልፍ ሰማዕታት  🕊 † ] † ዘመነ ሰማዕታት አርባ ሰባት ሚሊየን ክርስቲያኖችን በአርባ ዓመታት ከበላ በኋላ በ፫፻፭ [305] (312) ዓ/ም ቢጠናቀቅም ስለ ሃይማኖት መሞት ግን እስከ ምጽዓት ድረስ ይቀጥላል:: ለእያንዳንዱ ክርስቲያን ከሚቀርቡ ፈተናዎች ሁሉ እጅግ ከባዱ ይሔው ሰማዕትነት ነውና ሊቀበለው ያለው [ያደለው] ይቀበለዋል:: ቤተ ክርስቲያን በባሕር ላይ ያለች መርከብ ናትና ዘወትር በፈተና ውስጥ መኖሯ የሚጠበቅ ነው:: ዘመነ ሰማዕታትን ተከትሎ የመጣው የመናፍቃን ዘመን ሲሆን ለመቶ ሃምሳ ዓመታት ያህል መናፍቃን እንደ አሸን ፈልተዋል:: በዚያው ልክ ከዋክብት ቅዱሳን ሊቃውንት ነበሩና በየጊዜው ጉባኤያትን እየሠሩ: መናፍቃንን አሳፍረዋል:: ምዕመናንንም አጽንተዋል:: በ፬፻፶፩ [451] ዓ/ም የተፈጸመው ድርጊት ግን ዛሬም ድረስ ጠባሳው የሚለቅ አልሃነም:: ንጉሡ መርቅያንና ጳጳሱ ልዮን የንስጥሮስን ትምሕርት አለባብሰው ሊያስተምሩ ሲሞክሩ ግጭት በመፈጠሩ ቤተ ክርስቲያን ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ሁለት ተከፈለች:: በጉባኤው የነበሩ ስድስት መቶ ሰላሳ ስድስት ጳጳሳት ስቃይና ሞትን ፈርተው በኑፋቄ መጽሐፍ ላይ በመፈረማቸው "መለካውያን" [ከእግዚአብሔር ይልቅ ለንጉሥ የሚታዘዙ] ተባሉ:: ጉባኤውም "ጉባኤ ከለባት" [የውሾች ስብሰባ] : "ጉባኤ አብዳን" [የሰነፎች ጉባኤ] ተብሏል:: የወቅቱ የእስክንድርያ ፓትርያርክ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ግን "በኑፋቄው ላይ አልፈርምም::" ከማለቱ አልፎ መናፍቃኑን አወገዛቸው:: በዚህ ምክንያት ጽሕሙን ነጭተው: ጥርሱንም አርግፈው: ወደ ጋግራ ደሴት ከሰባት ደቀ መዛሙርቱ ጋር አሳደዱት:: በዚያም ለሦስት ዓመታት ቆይቶ በ፬፻፶፬ [454] ዓ/ም ዐረፈ:: እግዚአብሔር ፈርዶባቸው ንጉሡ መርቅያን እና ንግሥቲቱ ብርክልያ [ክፉ ሴት ናት] ድንገት ሞቱ:: ፈተናው ግን በዚህ አላበቃም:: በዙፋኑ የተተካው ሌላኛው ጨካኝ ልዮን ነበር:: መንፈሳዊውን አርበኛ አባ ዲዮስቆሮስን በሞት ያጡት የግብጽ ክርስቲያኖች ደቀ መዝሙሩን "አባ ጢሞቴዎስን እንሾማለን::" ቢሉ ንጉሡ ከለከለ:: የሚሾመው መለካዊ ነው ብሎ አብሩታርዮስ የሚባል መናፍቅ ጳጳስ በላያቸው ላይ ሾመባቸው:: ይህንን መታገስ ለሕዝቡና ለካህናቱ ከባድ ነበር:: ተኩላ እንኳን በበጐች ላይ በይፋ ተሹሞ: ተደብቆም ቢሆን እየነጠቀ መብላት ልማዱ ነው:: መናፍቁ ጳጳስ በተለያየ መንገድ ሕዝቡን ለመሳብ ሞክሮ ነበር:: ለምሳሌ አውጣኪን [የክርስቶስን ሰው መሆን ምትሐት የሚል 'የቱሳሔ' አስተማሪ መናፍቅ ነው::] አወገዘው:: እነሱ ግን ተረድተውታልና ቦታ አልሰጡትም:: ምክንያቱም አውጣኪ ከቀድሞም የተወገዘ መናፍቅ ነውና:: የሚገርመው ከሕዝቡ አንድስ እንኳ ከመናፍቁ ጳጳስ የሚባረክ አልነበረም:: ሥጋውን ደሙንም ከእውነተኛ ካህናት በድብቅ ይቀበሉ ነበር:: አንድ ቀን ግን መናፍቁ ጳጳስ አብሩታርዮስ ተገድሎ ተገኘ:: [መልአክ ቀሥፎት ነው የሚሉ አሉ:: እስካሁን ድረስ የገዳዩ ማንነት አልታወቀም::] ግብጻውያን ክርስቲያኖች ግን የእርሱን ሞት ሲሰሙ ደጉን እረኛ አባ ጢሞቴዎስን ሾሙ:: ችግሩ የመጣው ከዚህ በኋላ ነው:: የመናፍቁ ተከታዮች ለንጉሡ ልዮን "አንተን ንቀው: የሾምከውን ገደሉ:: ሌላ ጳጳስም ሾሙ::" ብለው መልዕክት ላኩለት:: በዚህ የተበሳጨው ልዮን ኦርቶዶክሳውያንን ባገኛችሁበት ሁሉ ግደሉ የሚል አዋጅ አወጣ:: ይህን አዋጅ ተከትሎ ሰላሳ ሺ ሰዎች በእስክንድርያ ከተማ ተጨፈጨፉ:: ገዳዮቹ ወንድ: ሴት: ሕፃን: ሽማግሌ ሳይመርጡ የክርስቲያኖችን ደም አፈሰሱ:: ለሦስት ቀናትም ግድያው ቀጥሎ እንደ ነበር ይነገራል:: ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት "ወኀጥኡ ዘይቀብሮሙ" እንዳለ ቀባሪም አጡ:: ገዳዮቹ ቀጥለውም አባ ጢሞቴዎስን አስረው አጋዙት:: ለአሥር ዓመታትም አሰቃዩት:: ከእነዚህ ዓመታት በኋላ ግን ንጉሡ ተጸጽቶ አባ ጢሞቴዎስን ወደ መንበሩ መልሶታል:: ወገኖቻችን የግብጽ ክርስቲያኖች እንኳን ያኔ ዛሬም በጽናታቸው አብነት ልናርጋቸው የሚገቡ ናቸው:: † አምላከ ሰማዕታት በቸርነቱ ይጠብቀን:: ከበረከታቸውም ያድለን:: [  † ነሐሴ ፳፫ [ 23 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ] ፩. ሰላሳ ሺ የእስክንድርያ [ግብጽ] ሰማዕታት ፪. ቅዱስ ድምያኖስ ሰማዕት [  † ወርኀዊ በዓላት  ] ፩. ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት ፪. ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት ፫. ነቢየ ጽድቅ ቅዱስ ሰሎሞን (ንጉሠ እሥራኤል) ፬. አባ ጢሞቴዎስ ገዳማዊ ፭. ቅዱስ ዳንኤል ነቢይ ፮. አባ ሳሙኤል ፯. አባ ስምዖን ፰. አባ ገብርኤል † " በጐንም ለማድረግ ብትቀኑ የሚያስጨንቃችሁ ማን ነው? ነገር ግን ስለ ጽድቅ እንኳ መከራን ብትቀበሉ ብጹዓን ናችሁ:: ማስፈራራታቸውንም አትፍሩ: አትናወጡም:: ዳሩ ግን ጌታን እርሱም ክርስቶስን በልባችሁ ቀድሱት:: በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ:: ነገር ግን በየውሃነትና በፍርሃት ይሁን:: " † [፩ጴጥ. ፫፥፲፫-፲፮] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
198
4
+3
بدون متن...
343
5
😭 #በምስራቅ_ወለጋ_ዞን_ጊዳ_አያና_ወረዳ በተለይ መንደር 22 ተብሎ በሚጠራው አከባቢ በተፈፀመ ጭፍጨፋ እስካሁን #ከ40 በላይ ንጹን ወገኖች ተገድለዋል። 😭 ከነዚህ መካከል በአሰቃቂ ሁኔታ በስለታማ መሣሪያ ተቆራርጠው የተገደሉት የ85 ዓመት አዛውንቱ አባ አየለ አረጋ እና ባለቤታቸው እማሆይ እስከዳር ገላው ይገኙበታል። 😭 መረብ ሚዲያ ያነጋገራቸው ከጥቃቱ የተረፉ የዓይን እማኞች እንደገለፁት፡ በአከባቢው አስከሬን መቅበር አልተቻለም፣ መከላከያ ሠራዊቱና ገዳ ኮማንዶ እንዲሁም በነዚኽ ኃይሎች ስር ተጠርንፈውና ስለታማ የጦር መሣሪያ ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ የቄሮ ቡድኖች በአከባቢው በመስፈራቸው በጥቃቱ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ቁስለኞችን ማንሳትም ሆነ በጥቃቱ የተገደሉ ንፁኋኖችን አስከሬን መቅበር እንዳልተቻለ ገልፀዋል። 😭 የአይን እማኞቹ አክለውም፡ ጨፍጫፊዎቹ  ከአከባቢው ለቀው እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ተከታትለን ቁስለኞችን ለማንሳትና አስከሬን ለመቅበር ሞክረን የነበረ ቢሆንም፡ ነገር ግን ወዲያውኑ በመመለሳቸው ጨርሰን ሳናነሳና ሳንቀብር ለመሸሽ ተገድደናል ብለዋል። #ሸዋ_ጎንደር_ወሎ_ጎጃም💚💛❤_አንድአማራ_አንድ_ኢትዮጵያ #ethiopian_tik_tok
318
6
+1
بدون متن...
264
7
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #ነሐሴ ፳፪ (22) ቀን። ❤ እንኳን #ከዐሥራ_ሁለቱ_ደቂቀ_ነቢያት አንዱ ለሆነው ለታላቁ ለሞራት ልጅ ለነቢዩ #ለቅዱስ_ሚክያስ ለዕረፍት በዐል እግዚአብሔር አምላክና በሰላም አደረሰን።                                                      ✝ ✝ ✝ ❤ #የሞራት_ልጅታላቁ_ነቢይ_ቅዱስ_ሚክያስ፦ ይህም ነቢይ በይሁዳ ነገሥታት በኢዮአታም፣ በአካአዝና በሕዝቅያስ ዘመን ትንቢት በመናገር አስተማረ። ❤ ስለጌታችን መውረድም እንዲህ አለ። "እነሆ እግዚአብሔር ከልዑል መንበሩ ወደዚህ ዓለም ይወርዳል"። ❤ ሁለተኛም ስለ ልደቱ እንዲህ ብሎ ተናገረ "የኤፍራታ ዕጣ የምትሆኚ አንቺ ቤተ ልሔም የእስራኤል ነገሥታት ከነገሡባቸው አገሮች አታንሺም ወገኖቹን የሚጠብቃቸው የእስራኤል ንጉሥ ከአንቺ ይወጣልና"። ❤ ስለ ምኵራብ መቅረት፤ ስለ ቤተ ክርስቲያን በዓለም ሁሉ መታነፅ ትንቢት ተናግሮአል። ዳግመኛም ስለ ሕገ ወንጌል መሠራት "ከጽዮን የእግዚአብሔር ቃል ከኢየሩሳሌም ይወጣል" አለ። የትንቢቱም ወራት ሲፈጸም ወደ በጎ ሽምግልና ደርሶ ወደ ወደደው እግዚአብሔር  ሔደ። ❤ የትንቢቱ ዘመን ከጌታችን መምጣት በፊት በስምንት መቶ ዓመት ነው። ማርታ በምትባልም ቦታ ተቀበረ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን የነቢዩ የቅዱስ ሚክያስ በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የነሐሴ 22 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለሚክያስ_ነባቢተ_ትንቢት_ልሳኑ። ዘይከውን በበዘመኑ። እንዘ ይብል ከመዝ ኂሩተ አምላክ ይዜኑ። መኑ ከማከ እግዚኦ አምሳለ አማልክት ዘኮኑ። አበሳ ርስቱ ዘይትነሐይ መኑ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የነሐሴ_22።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወገሠፀ ነገሥተ በእንቲአሆሙ። ወኢትግሥሡ መሲሐንየ። ወኢታሕስሙ ዲበ ነቢያትየ"። መዝ 104፥14-15። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 11፥25-ፍ.ም፣ 2ኛ ጴጥ 1፥19-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 7፥51-54። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 2፥1-7። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን ማርያም ወይም የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ቅዳሴ ነው። መልካም የነቢዩ የቅዱስ ሚክያስ የዕረፍትበዓል። ለሁላችን ይሁንልን።                  @Teamihokidusan
270
8
🕊 ከስንክሳር በተጨማሪ ሲቀርቡ የነበሩ ሌሎች ተከታታይ መርሐ-ግብሮች ከዘመን መለወጫ ዋዜማ ጀምሮ እንደ እግዚአብሔር በጎ ፈቃድ መቅረብ የሚጀምሩ ይሆናል ! 🌸 🌸 † ስንክሳር † ምክረ ቅዱሳን
🕊 ከስንክሳር በተጨማሪ ሲቀርቡ የነበሩ ሌሎች ተከታታይ መርሐ-ግብሮች ከዘመን መለወጫ ዋዜማ ጀምሮ እንደ እግዚአብሔር በጎ ፈቃድ መቅረብ የሚጀምሩ ይሆናል ! 🌸                                                  🌸 † ስንክሳር † ምክረ ቅዱሳን † የቅዱሳን ታሪክ † ዕቅበተ እምነት † ቤተ ክርስቲያንን እንወቅ † እናታችን ጽዮን † ከቅዱሳት መጽሐፍት ቅኝት † ድምፀ ተዋሕዶ † መዝሙረ ተዋሕዶ .... ❝ ወንድሞች ሆይ ፥ መጠራታችሁንና መመረጣችሁን ታጸኑ ዘንድ ከፊት ይልቅ ትጉ ፤ እነዚህን ብታደርጉ ከቶ አትሰናከሉምና። ❞ [ ፪ጴጥ.፩፥፲ ] 🌸                                                  🌸                            †††                ✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟ 🕊                        💖                        🕊
244
9
بدون متن...
223
10
[ ስንክሳር ነሐሴ - ፳፪ - ] .mp3
195
11
🕊 [  † እንኳን ለታላቁ ነቢይ ቅዱስ ሚክያስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †  ] † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! † [ † 🕊  ቅዱስ ሚክያስ ነቢይ  🕊 † ] † ነቢይ ማለት በቁሙ ኃላፍያትን [አልፎ የተሠወረውን ምሥጢር] : መጻዕያትን [ገና ለወደ ፊት የሚሆነውን] የሚያውቅ ሰው ማለት ነው:: ሃብተ ትንቢት የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ሲሆን እርሱ ለወደደው ደግሞ በጸጋ ይሰጠዋል:: እነዚህም ከጌታ ሃብተ ትንቢት የተሰጣቸው አባቶችና እናቶች "ቅዱሳን ነቢያት" በመባል ይታወቃሉ:: ዘመነ ነቢያት ተብሎ የሚታወቀው ብሉይ ኪዳን ቢሆንም እስከ ምጽዓት ድረስ ጸጋውን እግዚአብሔር ለፈቀደላቸው አይነሳቸውም:: በሐዋርያት መካከልም ቅዱስ አጋቦስን የመሰሉ ነቢያት ነበሩ:: [ሐዋ.፲፩፥፳፯] (11:27) ቅዱሳን ነቢያት ከእግዚአብሔር እየተላኩ ሰውን ከፈጣሪው እንዲታረቅ ይመክራሉ: ይገስጻሉ:: ከበጐ ሃይማኖታቸውና ንጽሕናቸው የተነሳም እግዚአብሔርን በተለያየ አርአያና አምሳል አይተውታል:: "እስመ በአንጽሖ መንፈስ ርዕይዎ ነቢያት ለእግዚአብሔር: ወተናጸሩ ገጸ በገጽ" እንዳለ አባ ሕርያቆስ:: [ቅዳሴ ማርያም] የብዙ ነቢያት ፍጻሜአቸው መከራን መቀበል ነው:: እውነትን ስለ ተናገሩ: አንዳንዶቹም በእሳት: አንዳንዶቹም በሰይፍ: አንዳንዶቹም በመጋዝ ተፈትነዋል:: ሌሎቹ ለአናብስት ሲጣሉ ቀሪዎቹ ደግሞ በድንጋይ ተወግረዋል:: ስለዚህም መከራቸው ለቤተ ክርስቲያን መሠረት ተብለዋል:: ጌታም ለደቀ መዛሙርቱ "ሌሎች ደከሙ: እናንተ በድካማቸው ገባችሁ::" ብሎ የነቢያቱን መከራ ተናግሯል:: [ዮሐ.፬፥፴፮] (4:36) ነቢያት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እና ድንግል እናቱን ለማየት ብዙ ጥረዋል: ሽተዋልም:: "ብዙ ነቢያትና ጻድቃን እናንተ የምታዩትን ሊያዩ ሹ::" እንዳለ ጌታ በወንጌል:: [ማቴ.፲፫፥፲፮ (13:16), ፩ጴጥ.፩፥፲] (1:10) ዛሬ ግን በሰማያት ጸጋ በዝቶላቸው: ክብር ተሰጥቷቸው ሐሴትን ያደርጋሉ:: † ቅዱሳን ነቢያት በዋነኝነት ¤ አሥራ አምስቱ አበው ነቢያት: ¤ አራቱ ዐበይት ነቢያት: ¤ አሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያትና ¤ ካልአን ነቢያት ተብለው በአራት ይከፈላሉ:: † አሥራ አምስቱ አበው ነቢያት ማለት :- - ቅዱስ አዳም አባታችን - ሴት - ሔኖስ - ቃይናን - መላልኤል - ያሬድ - ኄኖክ - ማቱሳላ - ላሜሕ - ኖኅ - አብርሃም - ይስሐቅ - ያዕቆብ - ሙሴና - ሳሙኤል ናቸው:: † አራቱ ዐበይት ነቢያት ፦ - ቅዱስ ኢሳይያስ ልዑለ ቃል - ቅዱስ ኤርምያስ - ቅዱስ ሕዝቅኤልና - ቅዱስ ዳንኤል ናቸው:: † አሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት ፦ - ቅዱስ ሆሴዕ - አሞጽ - ሚክያስ - ዮናስ - ናሆም - አብድዩ - ሶፎንያስ - ሐጌ - ኢዩኤል - ዕንባቆም - ዘካርያስና - ሚልክያስ ናቸው:: † ካልአን ነቢያት ደግሞ :- - እነ ኢያሱ - ሶምሶን - ዮፍታሔ - ጌዴዎን - ዳዊት - ሰሎሞን - ኤልያስና - ኤልሳዕ . . . ሌሎችም ናቸው:: † ነቢያት በከተማም ይከፈላሉ:: - የይሁዳ [ኢየሩሳሌም]: - የሰማርያ [እሥራኤል]ና - የባቢሎን [በምርኮ ጊዜ] ተብለው ይጠራሉ:: † በዘመን አከፋፈል ደግሞ :- - ከአዳም እስከ ዮሴፍ [የዘመነ አበው ነቢያት]: - ከሊቀ ነቢያት ሙሴ እስከ ነቢዩ ሳሙኤል [የዘመነ መሳፍንት ነቢያት] - ከቅዱስ ዳዊት እስከ ዘሩባቤል ያሉት [የዘመነ ነገሥት ነቢያት] - ከዘሩባቤል ዕረፍት እስከ መጥምቁ ዮሐንስ ያሉት ደግሞ [የዘመነ ካህናት ነቢያት] ይባላሉ:: † ስለ ቅዱሳን ነቢያት በጥቂቱ ይህንን ካልን ወደ ዕለቱ በዓል እንመለስ:: ቅዱስ ሚክያስ ቁጥሩ ከአሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት ሲሆን ዘመነ ትንቢቱም ቅ.ል. ክርስቶስ በ፰ መቶ [800] ዓ/ዓ አካባቢ ነው:: "ደቂቀ ነቢያት" ማለት በጥሬው "የነቢያት ልጆች" ማለት ነው:: አንድም የጻፏቸው ትንቢቶች ሲበዙ አሥራ አራት ምዕራፍ: ሲያንስ አንድ ምዕራፍ ያላቸው ናቸውና ደቂቅ ይላቸዋል:: ሚክያስ አባቱ ሞራት [ሞሬት] ይባላል:: ሚክያስ ማለት "መኑ ከመ አምላክ - እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው!" ማለት ነው:: አንድም "መልአከ እግዚአብሔር" ማለት ነው:: የአባቶቻችን ሁሉ ስማቸው እግዚአብሔርን የሚሰብክ ነው:: ቅዱሱ ነቢይ ገና ልጅ እያለ መላእክት ያነጋግሩት ነበር:: በዚህ ምክንያት ከሰው አይቀርብም:: ትክ ብለው ሲያዩት በፊቱ ላይ ብርሃን ቦግ ቦግ እያለ ይታይ ነበር:: በወጣትነት ዘመኑ እግዚአብሔር ለትንቢት ሲጠራው በእሺታ ታዘዘ:: በሦስቱ ነገሥታት [በኢዮአታም: አካዝና ሕዝቅያስ] ዘመንም ትንቢቶችን ተናግሯል:: ሕዝቡን: መሣፍንቱን: ነገሥታቱን አስተምሮ ገስጿል:: አንድ ቀን በቤተ ልሔም ሲያልፍ የዳዊት ከተማ ፈት ሁና: ዳዋ በቅሎባት ቢመለከት አዘነ:: ወዲያውም ትንቢት ተናገረላት:: "ወአንቲኒ ቤተ ልሔም ምድረ ኤፍራታ: ኢትቴሐቲ እምነገሥተ ይሁዳ: እስመ እምኔኪ ይወጽዕ ንጉሥ: ዘይርዕዮሙ ለሕዝብየ እሥራኤል::" "አንቺም የኤፍራታ ምድር ቤተ ልሔም: የይሁዳ ነገሥታት ከነገሡባቸው ከተሞች ከቶ አታንሺም:: ወገኖቼን እሥራኤልን የሚጠብቃቸው ንጉሥ [መስፍን] ካንቺ ዘንድ ይወጣልና::" አለ:: ይኸውም አልቀረ ለጊዜው ከሚጠት በኋላ ደጉ ዘሩባቤል ነግሦባታል:: በፍጻሜው ግን የባሕርይ ንጉሠ ነግሥት ኢየሱስክርስቶስ ከንጽሕት ድንግል ማርያም ተወልዶባታል:: ቅዱስ ሚክያስ ወገኖቹን ሲያስተምርና ሲመራ ኑሮ: ሰባት ምዕራፎች ያሉትን ሐረገ ትንቢት ተናግሮ: በመልካም ሽምግልና: በንጉሡ ሕዝቅያስ ዘመን ዐርፏል:: ወገኖቹ ቀብረውታል:: ጌታም በክብረ ነቢያት ከልሎታል:: † ቸር አምላከ ነቢያት የነቢያቱን መከራ አስቦ ከመከራ: በእንባቸውም ከእንባ ይሰውረን:: ከተረፈ በረከታቸውም አያጉድለን:: [  † ነሐሴ ፳፪ [ 22 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ] ፩. ቅዱስ ሚክያስ ነቢይ [   † ወርኀዊ በዓላት   ] ፩. ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላእክት ፪. ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ ፫. ቅዱስ ደቅስዮስ [የእመቤታችን ወዳጅ] ፬. አባ እንጦንስ አበ መነኮሳት ፭. አባ ጳውሊ የዋህ † " ምን ይዤ ወደ እግዚአብሔር ፊት ልምጣና በልዑል አምላክ ፊት ልስገድ? የሚቃጠለውን መስዋዕትና የአንዱን ዓመት ጥጃ ይዤ በፊቱ ልምጣን? እግዚአብሔርስ በሺህ አውራ በጐች: ወይስ በእልፍ የዘይት ፈሳሾች ደስ ይለዋልን? . . . ሰው ሆይ! መልካሙን ነግሮሃል:: እግዚአብሔርም ከአንተ ዘንድ የሚሻው ምንድር ነው? ፍርድን ታደርግ ዘንድ: ምሕረትንም ትወድ ዘንድ: ከአምላክህም ጋር በትሕትና ትሔድ ዘንድ አይደለምን?" † [ሚክ. ፮፥፮] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
256
12
+1
بدون متن...
332
13
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #ነሐሴ ፳፩ (21) ቀን። ❤ እንኳን #አምላክ_ለወለደች_ለእመቤታች #ለቅድስት_ድንግል_ማርያም ለወራዊ መታሰቢያ በዐሏ፣ #ለትንሣኤዋና_ዕረገቷና_የጨረሻ_ቀን መታሰቢያ በዓልና የስሟ ትርጓሜ ሰላም ፍቅር ለሆነ ለንጉሥ ሉክያኖስ ልጅ ለሐዋርያዊቷ ሰማዕት #ለቅድስት_ኄራኒ ለዕረፍቷ መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በፍቅር አደረሰን።                                                                                 ✝ ✝ ✝ ❤ በዚች ቀን አምላክ በሥጋ የወለደች #የእመቤታችን_የድንግል_የማርያም_የበዓሏ መታሰቢያ ነው። እርሷ ስለእኛ ሁልጊዜ ትማልድልናለች። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን የሕይወትና የደኅነት ወደብ ትሆነን ዘንድ እርሷን እናቱን ስለሰጠን በረከቷም በሁላችን በክርስቲያን ወገኖች ላይ ይደር ለዘላለሙ አሜን።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #ሐዋርያዊቷ_ሰማዕት_ቅድስት_ኄራኒ፦ የስሟ ትርጓሜ ሰላም ፍቅር ማለት ነው። ለንጉሥ ሉክያኖስ ልጁ ነች እርሱም አባቷ ያማረ አዳራሽን ሠራላት መስኮቶቹንም ስምንት አደረገ ቅጽሩንም በዙሪያው ዐሥራ ሁለት አደረገ ማዕድንም ሠራላት። የወርቅና የብር የሆኑ ሣህኖችና ጽዋዎችንም አዘጋጀላት የሚያስተምራትም አንድ ሽማግሌ ሰው አደረገላት። ❤ ከዚህም በኋላ በዚያች አዳራሽ ውስጥ አኖራት የሚያገለግሏትም ሦስት አገልጋዮችን በእርሷ ዘንድ አድርጎ ደጃፎችን በላይዋ ዘጋ መምህርዋም በውጭ ሆኖ ያስተምራታል። ❤ ዕድሜዋም ሰባት ዓመት ሆናትና ያን ጊዜ ራእይን አየች በማዕዷ ላይ ርግብ ስትቀመጥ በአፍዋም የወይራ ቅጠል አለ ። በማዕዱም ላይ አኖረችው ሁለተኛም ንስር መጣ ከእርሱ ጋር አክሊል አለ በማዕዷ ላይም አኖረው። ደግሞ ቊራ መጣ ከእርሱ ጋራ ከይሲ አለ በማዕዷ ላይም አኖረው። ደነገጠችም ለመምህርዋም ነገረችው እርሱም እንዲህ ብሎ ተረጐመላት "ርግብ የሕግ ምልክት ናት የዘይቱም ቅጠል የክርስትና ጥምቀት ናት፣ ንስርም ድል አድራጊነት ነው አክሊልም ለሰማዕታት የሚሰጥ ክብራቸው ነው። ቊራ የንጉሥ ምሳሌ ነው ከይሲውም መከራ ነው አንቺም የክብር ባለቤት በሆነ ክርስቶስ ስለ ስሙ ትጋደዪ ዘንድ አለሽ" አላት። ❤ ከዚህም በኋላ ይጐበኛት ዘንድ አባቷ ወደርሷ መጣና "ልጄ ሆይ ከመንግሥት ታላላቆች ለአንዱ ላጋባሽ እኔ እሻለሁ" አላት እርሷ ግን ከልቡናዬ እስተምመክር ሦስት ቀኖችን አባቴ ሆይ ታገሠኝ" ብላ መለሰችለት። አባቷም በሔደ ጊዜ በጣዖታቱ መሠዊያ ፊት ተነሥታ ቆመችና ስለጋብቻ የሚሆነውን ይገልጡላት ዘንድ ለመነቻቸው እነርሱም ምንም ምን ከቶ አልመለሱላትም። ❤ ከዚህም በኋላ ዐይኖቿን ወደ ሰማይ አቅንታ "የክርስቲያን አምላክ ሆይ ወደምትፈቅደው ምራኝ" ብላ ጸለየች ያን ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ መጥቶ እንዲህ አላት። "እነሆ ነገ ከጳውሎስ ደቀ መዛመርት አንዱ ወደዚች አገር ይመጣል እርሱም የክርስትና ጥምቀትን ያጠምቅሻል። በማግሥቱም ያ ሐዋርያ መጥቶ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃት። በሦስተኛውም ቀን እንደቀጠረቻቸው አባቷና እናቷ መጡ እርሷም እንዲህ አለቻቸው "እኔ ሰማይና ምድርን በፈጠረ በሕያው እግዚአብሔር ልጅ በጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ የማምን ክርስቲያን ነኝ"። ❤ አባቷም ሰምቶ በእርሷ ላይ ተቆጣ ወደ ከተማው መካከልም አውጥተው በጐዳና ላይ እንዲጥሏትና በፈረሶች እግር እንዲአስረግጧት አዘዘ። ወታደሮችም ንጉሥ አባቷ እንዳዘዘ አደረጉባት ግን ምንም ምን ክፉ ነገር ከቶ አልደረሰባትም። ይህንንም ድንቅ ሥራ አባቷና እናቷ በአዩ ጊዜ የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ መንግሥታቸውንም ትተው ለርሷ ወደተሠራው አዳራሽ ሔደው በውስጡ ተቀመጡ። ❤ በጐረቤታቸው ያለ ንጉሥም ዜናቸውን በሰማ ጊዜ ወደ ርሳቸው መጥቶ ወደ መንግሥታቸው እንዲመለሱ ተናገራቸው። እነርሱም አልፈለጉም እርሱም መንግሥታቸውን ያዘ ቅድስት ኄራኒንም ይዞ አሠቃያት ከዚያም አንበሶችን፣ እባቦችን በላይዋ ሰደደ ምንም አልቀረቧትም ። ሁለተኛም በመጋዝ መገዛት በአንገቷም ውስጥ ታላቅ ደንጊያ አሥሮ ከባሕር ጣላት የክብር ባለቤት ጌታችንም ከዚህ ሁሉ አድኖ ያለ ጥፋት በጤና አሥነሣት። ❤ ከዚህም በኋላ እርሷን ያጠመቀ ሐዋርያን አባቷ ጠርቶ ከቤተሰቦቹ ሁሉ ጋር ተጠመቀ ቊጥራቸውም ሦስት መቶ ሆነ ከዘመዶቹና ከሀገር ሰዎችም ብዙዎች ተጠመቁ። ❤ ከዚህም በኋላ ከሀዲው ንጉሥ ኑማርያኖስ የቅድስት ኄራኒን ዜናዋን ሰማ ወደርሱም አስቀርቦ ቀላኒካ ወደሚባል አገር ወሰዳት። በዚያም ጽኑ ሥቃይን አሠቃያት በበሬ አምሳል በተሠራ የነሐስ በርሜል ውስጥ ዘጋባት የክብር ባለቤት ጌታችንም ያንን በሬ ሰብሮ ቅድስት ኄራኒን ያለ ጥፋት በጤና አወጣት። ❤ ከዚህም በኋላ ኑማርያኖስ ሙቶ በርሱ ፈንታ ሳፎር ነገሠ እርሱም የቅድስት ኄራኒን ዜና በሰማ ጊዜ ወደ ርሱ አስቀርቦ በእጁ ውስጥ በአለ በታላቅ ጦር ወጋትና ነፍሷን አሳለፈች የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ከሞተ አስነሣት። ንጉሥ ሳፎርም በአየ ጊዜ እጅግ አደነቀ ሰገደላትም በጌታችን ኢየሱስም አመነ ። ከእርሱም ጋራ ከሀገር ሰዎች ብዙ ወገኖች አመኑ ቁጥራቸውም ሠላሳ አንድ ሺህ ሆነ። ❤ ከዚህም በኋላ በዚያች አዳራሽ ውስጥ አባቷና እናቷ  ዐረፉ እርሷን ግን አምላካዊት ኃይል ተሸከመቻት ወደ ኤፌሶን አገርም አድርሳት በዚያ ታላላቅ የሆኑ ድንቆች ተአምራቶችን አደረገች። ✝ በፋርስ ነገሥታት በመቄዶንያ፣ በቀላኒካና በቊስጥንጥንያ ነገሥታት ፊት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ከመሰከረች በኋላ ወደ ወደደችው ክርስቶስ ሔደች። የድልና የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለች። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሐዋርያዊቷ ሰማዕት በቅድስት ኄራኒ በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የነሐሴ 21 ስንክሳር።                              ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለኄራኒ_ከመ_ትርጓሜሁ_ለስማ። ምሥጢረ ጥምቀት ዘርእየት አምሳለ ዕፀ ዘይት በንዋማ። ሶበ ነይሩ ኪያሃ በጽንዐ ሃይማኖት ቀዊማ። ወሶበ ኢክህለ ሙቃሔ ወእግረ ፈረስ ያሕምማ አሠረ ዚአሃ ተለው አቡሃ ወእማ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የነሐሴ_21።                             ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦"ወትቀውም ንግሥት በየማንከ።  በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወኊብርት። ስምዒ ወለትየ ወርእዪ ወአጽምዒ ዕዝነኪ"። መዝ44፥9-10። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 1፥39-57።                             ✝️ ✝️ ✝️ ❤ የዕለቱ የቅ ምስባክ፦ "አዋልደ ንግሥት ለክብርከ። ወትቀውም ንግሥት በየማንከ። በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወኊብርት"። መዝ 44፥9። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 7፥25-ፍ.ም፣ 2ኛ ዮሐ 1-1-7 እና የሐዋ ሥራ 16፥13-18። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 25፥1-14። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታች የማርያም ቅዳሴ ነው፡፡ መልካም በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።                  @Teamihokidusan                            
274
14
+1
بدون متن...
250
15
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #ነሐሴ ፳፩ (21) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊቷ_ንግሥት ታቦተ ጽዮንን ወደ አገራችን ላመጣ ለንጉሥ ምኒልክ ቀዳማዊ እናት #ለንግስት_ማክዳ _ለንግስተ_ሳባ (አዜብ) ለልደት በዓል፣ ለንጉሥ ቆስጠንጢኖስ እናት #ለንግሥት_እሌኒ የልደት በሰላም አደረሰን።                                                          ✝ ✝ ✝ ❤ #ንግሥት_ቅድስት_ዕሌኒ፦ ይቺም ቅድስት በፊት የአንድ ነጋዴ ሰው ሚስት ነበረች እርሱም በነገረ ሠሪ ንጽሕት ሁና ሳለች ወደ ባሕር ጣላት። የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን ፈቃድም ሮሐ ከሚባል አገር ደርሳ የበራጥያ ንጉሥ ቊንስጣ አገኛት። ውበቷንና ደምግባቷንም አይቶ አገባት። ለክርስቲያን ነገሥታት መጀመርያቸው የሆነውን ቈስጠንጢኖስን ወለደችው ምግባርንና ሃይማኖትን በማስተማር በመልካም አሳደገችው። ❤ ልጇም በነገሠ ጊዜ "ወደ ኢየሩሳሌም ሔደሽ የክብር ባለቤት የሆነ የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ግለጪ የከበሩ ቦታዎችንም ሥሪ" የሚላትን በሕልሟ አይታ እንዴት እንዳየች ይህን ለልጇ ነገረችው እርሱም ከብዙ ሠራዊቱ ጋራ ሰደዳት። በደረሰችም ጊዜ የክብር ባለቤት ስለሆነ ስለ ጌታችን መስቀል መረመች አዳኝ የሆነ መስቀሉንም ሁለት ወንበዴዎች ከተሰቀሉባቸው መስቀሎች ጋራ አገኘችው። የክብር ባለቤት የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል የትኛው እንደሆነ ታውቅ ዘንድ በወደደች ጊዜ ከራሱ በላይ "ይህ የናዝሬቱ ኢየሱስ የአይሁድ ንጉሥ ነው" የሚል በእንጨት የተቀረጸበት ጽሑፍ ያለው እንደሆነ የኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ ቅዱስ መቃርስ ነገራት። ❤ ከዚህም በኋላ ከእርሱ ምልክት ታይ ዘንድ ፈለገች የሞተ ሰውም አግኝታ መስቀሎችን በበድኑ ላይ አኖረች አልተነሣም። ከዚህ በኋላ ሦስተኛውን መስቀል በላዩ አኖረች። ያን ጊዜ ያ ምውት ተነሣ ሃይማኖቷም ጸና ደስታዋም በዛ። ❤ ከዚህ በኋላ ዜናቸው በመስከረም ወር በዐሥራ ሰባት የተጻፈ በከበሩ ቦታዎች ውስጥ አብያተ ክርስቲያናትን ትሠራ ዘንድ ጀመረች። ለአባ መቃርስም በከበሩ ቦታዎች ሁሉ አብያተ ክርስቲያናትን እንዲሠራ ብዙ ገንዘብ ሰጠችው። ❤ ከዚህ በኋላ ወደ ልጇ ተመልሳ የሆነውን ሁሉ ነገረችው የከበረ መስቀል በመገኘቱ እጅግ ደስ አለው። ይቺም ቅድስት በጎ ገድላሏን ከፈጸመችና እግዚአብሔርንም ከአገለገለች በኋላ ስለ ካህናትም ልብስና ቀለብ ለአብያተ ክርስቲያናትና ለገዳማት ብዙ ጉልቶችና ርስቶችን ለድኆችና ለምስኪኖችም እንዲሁ ከሠራችና ከተከለች በኋላ ግንቦት9 ቀን በሰላም ዐረፈች መላ ዕድሜዋም ሰማንያ ሆነ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት ዕለኔ በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ የግንቦት9 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #ንግሥተ_ሳባ፦ ይህቺ ኢትዮዽያዊት ንግሥት ከ3 ሺ ዘመናት በፊት የነበረች ደግ እናት ናት። በሥጋዊ ደረጃ ከታንዛንያ እስከ የመን ያስተዳደረች ስመ ጥር ንግሥት ስትሆን በመንፈሳዊው ደረጃ ደግሞ እግዚአብሔር የቀባውን ሰው ፍለጋ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዛለች። ❤ ከዚያውም አምልኮተ እግዚአብሔርን ከሥርዓተ ኦሪት ጋር አምጥታለች። ድንግልናዋን ለታላቁ ንጉሥ ሰሎሞን ሰጥታ ቀዳማዊ ምኒልክን ወልዳለች። ❤ ይህቺ ንግሥት በጌታችን (በፈጣሪ) አንደበትም ተመስግናለች። (ማቴ. 12፥42) በስምም ሳባ፣ አዜብና ማክዳ ተብላ ትታወቃለች። ዛሬ ዕለተ ልደቷ ነው። ምንጭ፦ ከዲያቆን ዮርዳኖስ አበበ።                    @Teamihokidusan
205
16
+2
بدون متن...
178
17
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #ነሐሴ ፳፩ (21) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊ_ጻድቅ ኤርትራ አገር የሚነኘው #ደብረ_ጥሉል_ገዳምን_ለመሰረቱ በዐፄ ሱስንዮስ ዘመን የነበረውን የቤተ ክርስቲያንን ጥፋት ላለማየት ሳይወለዱ በእናታቸው ማኅፀን 7 ዓመት ከ6 ወር ለቆዩት #ለታላቁ_አባት_አቡነ_አብራኒዮስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓላቸው በሰላም አደረሰን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #አቡነ_አብራኒዮስ፦ አባታቸው ወልደ ክርስቶስ እናታቸው ወለተ ትንሣኤ የሚባሉ ደጋግ ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ የተወለዱት በ1624 ዓ.ም ምሥራቅ ጎጃም አካባቢ ልዩ ስሙ እነብሴ ይሁን እንጂ ተጋድሏቸውን ያደረጉትና ገዳማቸውን የገደሙት በዛሬዋ ኤርትራ ውስጥ ነው፡፡ ገዳሙ ኤርትራ ውስጥ ዞባ ድባርዋ ደቂ ድግና በተባለ አካባቢ ይገኛል፡፡ የገደሙት ጻድቁ በ1705 ዓ.ም ነው፡፡ ❤ አቡነ አብራኒዮስ የተፀነሱት በመልአኩ በቅዱስ ገብርኤል አብሳሪነት ነው፡፡ ነገር ግን ቀደም ብዬ እንደጠቀስኩት ጻድቁ በዐፄ ሱስንዮስ ዘመን የነበረውን የቤተ ክርስቲያንን ጥፋት ላለማየት ሳይወለዱ በእግዚአብሔር ፈቃድ በእናታቸው ማኅፀን 7 ዓመት ከ6 ወር ተቀምጠዋል፡፡ በዚህም ወቅት እሳት ልትጭር ከጎረቤቷ የመጣች አንዲት ሴት የአቡነ አብራኒዮስ እናት "የማትወልጂው ምን ሆነሽ ነው?" ብላ ስትናገር ጻድቁ በእናታቸው ማኅፀን ሆነው "…ለምን ክፉ ትናገሪያለሽ?" ብለው መልስ ሰጥተዋታል፡፡ ይህም ቅዱሳን ልክ እንደ ነቢዩ ኤርምያስ ገና በእናታቸው ማኅፀን ሳሉ እንደሚመረጡ አንድ ማሳያ ነው፡፡ ❤ በርካታ ምእመናንን በሰማዕትነት ከገደሉ በኋላ በመጨረሻም ዐፄ ሱስንዮስ በመቅሰፍት ተመተው ሊሞቱ ሲሉ "ሃይማኖት ይመለስ፣ ፋሲል ይንገሥ" ብለው የቤተ ክርስቲያን ሰላም መልሰው ንስሓ ገብተው ሞቱ፡፡ አቡነ አብራኒዮስም ይህ የቤተ ክክርስቲያን የመከራ ዘመን ሲያልፍና ሃይማኖት ሲመለስ ተወለዱ፡፡ ገና በ5 ዓመታቸው ከጥንቆላ መጻሕፍት በቀር ሁሉንም የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍትንና ምሥጢራትን ሁሉ ተምረው ዐወቁ፡፡ በ12 ዓመታቸው መነኰሱ፡፡ ዲቁና ሲሾሙም ጳጳሱ "ገና ሕፃን ነው፣ አሁን አልሾመውም" ሲሉ የሰማይ መላእክት "ይባዋል" ብለው መስክረውላቸዋል፡፡ ❤ በልጅነታቸውም መነኰሳቱ ወደ ጫካ ሔደው ዕንጨት እንዲሰብሩ ሲያዟቸው ጌታችን ግን ለአቡነ አብራኒዮስ ኃይል ሰጥቷቸው በነፋስ ሠረገላ እየሔዱ የ6 ሰዓቱን የእግር መንገድ እሳቸው ግን ዕንጨቱን ሰብረው በቶሎ ይመለሱ ነበር፡፡ ይህም ሲታወቅባቸው ውዳሴ ከንቱን ንቀው ከዚያ ገዳም ወጥተው ወደ አቡነ ተጠምቀ መድኅን ዘንድ ሔዱ፡፡ በዚያም በታላቅ ተጋድሎ ከኖሩ በኋላ አቡነ ተጠምቀ መድኅን "በአንተ ምክንያት ብዙ ነፍሳት ይድናሉ፣ ክፍልህ በዚያ ነው" ብለው አሁን ገዳማቸውን ወደገደሙበት ቦታ (ኤርትራ) ላኳቸው፤ ሲመጡም ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል እየመሯቸው እንደመጡ ገድላቸው ይናገራል፡፡ ጻድቁ ወደዚህ ገዳም ሲመጡ በፊት ይቀመጡባት የነበረችው ትልቅ ድንጋይ በተኣምር ከመሬት 7 ክንድ ከፍ ብላ አብራቸው መጥታለች፡፡ ድንጋይዋ ዛሬም ድረስ በገዳማቸው በክብር ስለተቀመጠች ምእመናን እየዳሰሷት ይባረኩባታል፣ መካኖች ይወልዱባታል፣ ሕሙማን ይፈወሱባታል፡፡ ❤ አቡነ አብራኒዮስ በቅዳሴ ጊዜ ጌታችንን በዕለተ ዐርብ እንደተሰቀለ ሆኖ ይመለከቱት ስለነበር በኀዘን በተመስጦ ሆነው ይቆዩም ስለነበር ሕዝቡም "በቅዳሴ ሰዓት ይተኛል" እያሉ ያሟቸው ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ጻድቁ ወደ አካለ ጉዛይ በመሔድ በዘንዶ ላይ አድሮ ይመለክ የነበረውን ሰይጣን በጸሎታቸው አጥፍተው ዘንዶውን ገድለው ሕዝቡንም አስተምረው በንስሓ መልሰው አጥምቀዋቸዋል፡፡ ወደ ታላቁ ገዳም ደብረ ቢዘንም ሲሔዱ 6400 አጋንንትን አግኝተው በጸሎታቸው አጥፍተዋቸዋል፡፡ በዚህም ምክንያት አቡነ አብራኒዮስ "ሰዳዴ አጋንንት-አጋንንት አባራሪ" ተብለዋል፡፡ ❤ አቡነ አብራኒዮስ ወደ ሌላ ቦታ ሔደው ሰለዳዋ የምትባል ቦታ ላይ ሆነው ሳለ አንድ ሰው ወደ ገዳማቸው ገብቶ አንዲትን ዛፍ ሲቆርጥ በመንፈስ ቅዱስ መነጽርነት አዩት፡፡ ቆራጩም ሰው "ተው አትቁረጥ" የሚል የአባታችንን ድምፅ ሰማ፣ በአካል የሉም ብሎ እምቢ አለ፣ ነገር ግን በመቅሠፍት ተመቶ ወዲያው ሞተ፡፡ በአንድ ዕለትም ልጃገረዶች እየዘፈኑ ሲሔዱ ብዙ አጋንንት በዘፈናቸው ተደስተው አብረዋቸው ሲጨፍሩ አባታችን በመንፈስ ተመልክተው ለልጃገረዶቹ ዘፈን የአጋንንት መሆኑን እንዳስተማሯቸው ገድላቸው ይናገራል፡፡ ❤ ለአቡነ አብራኒዮስ ለዕፍታቸው ሲደርስ ክብርት እመቤታችን ተገልጻ "ቤተ ክርስቲያን በስሜ አንጽልኝ" አለቻቸው፡፡ እርሳቸውም ውብ አድርገው በእመቤታችን ስም አነጹ ነገር ግን ፍጻሜውን ሳያዩ በዕለተ ቀኗ ነሐሴ 21 ቀን ዐረፉ፡፡ በዕረፍታቸውም ወቅት ጌታችን ተገልጦ ታላቅ ቃልኪዳን ሲሰጣቸው "...ዋስ እፈልጋለሁ፣ ዋስ ስጠኝ" አሉት፡፡ ጌታችንም "ሐዋርያት፣ ሰማዕታት፣ ከአንተ በፊት የነበሩ ጻድቃን ያልጠየቁኝን አንተ እንዴት ጠየከኝ?" አላቸው፡፡ እርሳቸውም "አምላኬ ሆይ! አንተ መሐሪና በጽድቅ ፈራጅ ቃልህም የማይለወጥ እንደሆንክ አውቃለሁ" አሉት፡፡ ጌታችም ፍግግ ብሎ "ይሁን የምትሻውን አላሳጣህም" በማለት ከፈጣሪ በታች ከፍጡራን በላይ የሆነች ክብርት እመቤታችንንና ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስን ዋስ አድርጎ ቃል ኪዳን ከገባላቸው በኋላ ነሐሴ 21 ቀን 1713 ዓ.ም በሰላም ዐረፉ። ከታላቁ ጻድቅ ከአባታች አቡነ አብራኒዮስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን፣ በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ ከገድላት አንደበት።                   @Teamihokidusan
190
18
+3
بدون متن...
316
19
[ ስንክሳር ነሐሴ - ፳፩ - ] .mp3
257
20
🕊 [  † ✝️ 🌻 እንኳን ለቅዱሳት አንስት ኄራኒ ሰማዕት: ንግሥተ ሳባ እና ንግሥት ዕሌኒ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ✝️ 🌻  ] † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! † [ † 🕊 ቅድስት ኄራኒ ሐዋርያዊት ሰማዕት 🕊 † ] † ይህቺ ቅድስት ወጣት መልክ ከደም ግባት ምግባር ከሃይማኖት ስም ከመልካምነት የተባበረላት ሰማዕት ናት:: ኄራኒ ማለት "ሰላማዊት: የተወደደች" ማለት ነው:: አንድም በጥሬው "ሰላምና ፍቅር" ማለት ነው:: ቅድስት ኄራኒ በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን በታናሽ እስያ የንጉሥ ሉክያኖስ ልጅ ናት:: ከተወለደች ጀምሮ ስለ ክርስትና ሰምታ አታውቅም:: ምክንያቱም አባቷ ጣዖት አምላኪ ከመሆኑ ባለፈ ክርስቲያኖችን ይቀጣ ስለ ነበር ነው:: ልጁን ማንም እንዳያገኛት ሲል ንጉሡ ለቅድስት ኄራኒ ቤተ መንግስት ሠራላት:: ማንም እንዳይገባ በዙሪያው ፲፪ [12] አጥር አጠረበት:: ጣዖቶቹን እንድታጥን አገልጋዮችንም ሾመላት:: ምናልባት አጥር ሰውን ሊከለክለው ይችላል:: እግዚአብሔር ግን እግዚአብሔር ነውና ምንም አይከለክለውም:: ጌታ ደግሞ ይህቺን ወጣት ለወንጌል አገልግሎት ይፈልጋታል:: አንድ ቀን አባቷ: ልጁ ምሑር እንድትሆንለት አለ የተባለ ሽማግሌ ፈላስፋ ቀጠረላት:: ጥበበ እግዚአብሔር ማለት ይሔ ነው:: አባቷ ይሕ ሽማግሌ ማንን እንደሚያመልክ አልተረዳም:: አረጋዊው እጅግ የተዋጣለት ክርስቲያን ነው:: ግን ማንም አያውቅበትም:: አረጋዊው ቅድስት ኄራኒን ዝም ብሎ ሊሰብካት አልወደደም:: መጀመሪያ በስነ ምግባር አነጻት:: ቀጥሎ ግን "ጌታ ሆይ! ጐዳናህን ምራት" እያለ ይጸልይላት ገባ:: ጌታችን ልመናውን ሰምቶታልና ቅድስቷ አንድ ቀን ግሩም ራዕይን አየች:: እርሷ ለማዕድ ተቀምጣ ሳለ: የምሥራቅና የምዕራብ መስኮቶቿም ተከፍተው ሳሉ: በምሥራቁ መስኮት ነጭ ርግብ በአፏ የወይራ ዝንጣፊ [ቆጽለ ዘይት] ይዛ ገባችና ማዕዷ ላይ አኑራው ሔደች:: እርሷን ተከትሎ ደግሞ ንስር በአፉ አክሊል ይዞ ገብቶ ማዕዷ ላይ ጥሎት ሔደ:: በ፫ [3]ኛው ግን ቁራ: እባብ በአፉ ይዞ በምዕራቡ መስኮት ገብቶ ማዕዷ ላይ ጥሎት ወጣ:: ቅድስት ኄራኒ ያየችው ራዕይ ቢጨንቃት ሽማግሌ መምሕሯን "ተርጉምልኝ" አለችው:: እርሱም "ልጄ ሆይ! ለዘመናት ስጠብቀው የነበረ ምኞቴን ነው ጌታ ያሳየሽ:: የሕልምሽ ትርጉም እንዲህ ነው :- ነጭ ርግብ የመንፈስ ቅዱስ [የሃይማኖት] ምሳሌ ናት:: የወይራ ዝንጣፊው ደግሞ ማሕተመ ጥምቀት [ሜሮን] ነው:: ቁራ የክፉ ነገሥታት ምሳሌ ሲሆን እባብ የመከራ ምሳሌ ነው:: ንስር ድል የመንሳት ምልክት ሲሆን አክሊል ደግሞ የመንግስተ ሰማያት ምሳሌ ነው:: ልጄ! ክርስቲያን ሆነሽ የሚደርስብሽን ሁሉ ጌታ አሳይቶሻል" ብሎ ተርጉሞላት ተሰናበታት:: እርሷም ወደ ምሥራቅ ዙራ ጸለየች :- "የማላውቅህ አምላክ ሆይ! ወደ እውነትህ ምራኝ" ስትል ለመነች:: በዚያች ሰዓት የእግዚአብሔር መልአክ መጥቶ አጽናናት:: የሚያጠምቃትም እንደሚልክላት ነገራት:: በዚያን ጊዜ አባቷ ገብቶ "ልጄ! ከመሣፍንቱ ላንዱ ልድርሽ ስለሆነ ምን ትያለሽ?" አላት:: "፫ [3] ቀን ስጠኝ" አለችውና ሰጣት:: ወደ ጣዖቶቹ ዕለቱኑ ወርዳ "ላግባ ወይስ ይቅርብኝ?" አለቻቸው:: ከቀድሞም በወርቅ የተለበጡ ድንጋዮች ናቸውና ዝም አሉ:: በሙሉ ቀጥቅጣ ሰባብራቸው ተመለሰች:: በዘመኑ ቅዱሳን ሐዋርያት [በተለይ እነ  ቅዱስ ዻውሎስ] በሕይወተ ሥጋ ነበሩና ከቅዱስ ዻውሎስ ደቀ መዛሙርት አንዱ ቤቷ እንደ ተዘጋ ገባ:: ክርስትናን ከጥንቱ እስከ ተፍጻሜቱ አስተምሮ አጠመቃት:: በ፫ [3]ኛው ቀን አባቷ "ምን መከርሽ?" ቢላት "የእኔ ምክር መርዓተ ክርስቶስ [ሰማያዊ ሙሽራ] መሆን ነው" አለችው:: አባቷ ደነገጠ:: እጅግ ስለ ተናደደ ወደ አደባባይ አውጥቶ አስሮ መሬት ላይ ጣላትና በመቶ የሚቆጠሩ ፈረሶች እንዲረግጧት አደረገ:: በወቅቱ ሰው የሚጠብቀው የአካሏን ቁርጥራጭ ነበር:: ነገር ግን ጌታ ከእርሷ ጋር ነበርና ልብሷ እንኩዋ ጭቃ አልነካም:: አባቷ ንጉሥ ሉክያኖስና ሠራዊቱ ያዩትን ማመን አልቻሉም:: ሁሉም ድምጻቸውን ከፍ አድርገው "ከክርስቶስ በቀር ሌላ አምላክ የለም" አሉ:: ቅድስት ኄራኒ ምንም ሳትናገር ይህንን ሁሉ ሰው ማረከች:: ወዲያውም ንጉሡ መልእክተኛ ልኮ የቅዱስ ዻውሎስ ደቀ መዝሙርን አስጠርቶ ከነ ቤተሰቦቹ ተጠመቀ:: የዚህን ዓለም ክብር ንቆም ንግሥናውን ተወ:: የጸሎት ሰውም ሆነ:: የቅድስት ኄራኒ ተጋድሎ ግን ቀጠለ:: በአካባቢው የነበረ ንጉሥ መጥቶ የአባቷን መንግስት ቀማ:: እርሷንም እጅግ አሰቃያት:: እርሱ አልፎ አርማንዮስ የሚባል ንጉሥ እንዲሁ አሰቃያት:: እርሱም አለፈ:: ከእርሱ ቀጥሎ የመጣው ንጉሥ ብዙ መከራዎችን በእርሷ ላይ አደረሰ:: በጦርም ጐኗን ወግቶ ገደላት:: ከጥቂት ሰዓታት በሁዋላ ግን ልክ ከእንቅልፉ እንደሚነቃ ሰው ተነስታ ጠራችው:: በጣም ደንግጦ "አምላክሽ አምላኬ ነው" ሲል አመነ:: ከ፴ ሺህ [30,000] በላይ ሠራዊቱን ይዞም ተጠመቀ:: ቅድስት ኄራኒ በቀረ ሕይወቷ በስብከተ ወንጌል እስያን አድርሳለች:: ጌታ አብርቶላት: እርሷም አብርታ: እልፍ ፍሬን አፍርታ: በዚህች ቀን ዐርፋለች:: የሐዋርያትንም: የሰማዕታትንም አክሊል ተቀዳጅታለች:: † ✝️ 🌻  ንግሥተ ሳባ  🌻  †  ✝️ † ይሕቺ ኢትዮዽያዊት ከ፫ [3] ሺ ዘመናት በፊት የነበረች ደግ እናት ናት:: በሥጋዊ ደረጃ ከታንዛንያ እስከ የመን ያስተዳደረች ስመ ጥር ንግሥት ስትሆን በመንፈሳዊው ደረጃ ደግሞ እግዚአብሔር የቀባውን ሰው ፍለጋ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዛለች:: ከዚያውም አምልኮተ እግዚአብሔርን ከሥርዓተ ኦሪት ጋር አምጥታለች:: ድንግልናዋን ለታላቁ ንጉሥ ሰሎሞን ሰጥታ ምኒልክን ወልዳለች:: ይህቺ ንግሥት በጌታችን [በፈጣሪ] አንደበትም ተመስግናለች:: [ማቴ.፲፪፥፵፪] (12:42) በስምም " ሳባ: አዜብና ማክዳ ተብላ ትታወቃለች:: ዛሬ ዕለተ ልደቷ ነው:: [ † 🕊 ቅድስት ዕሌኒ ንግሥት 🕊 † ] † ይሕቺ ቅድስት የቅዱስ ቆስጠንጢኖስ እናቱ የመስቀሉ ወዳጅ የቤተ ክርስቲያን ባለውለታ የሆነች ክብርት እናት ናት:: ይህቺም ቅድስት የተወለደቺው በዚሁ ዕለት ነው:: † የቅዱሳት እናቶቻችን አምላክ እህት እናቶቻችንን ከክፋትም ከጥፋትም ይሠውርልን:: ለሃገርም ለሃይማኖትም የሚጠቅሙ ሴቶችንም ጌታ አይንሳን:: በረከታቸውም ይደርብን:: [ † ነሐሴ ፳፩ [ 21 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ] ፩. ተዝካረ ፍልሠታ ለማርያም ድንግል [6ኛ ቀን] ፪. ቅድስት ኄራኒ ሐዋርያዊት [ሰማዕት] ፫. ቡርክት ንግሥተ ሳባ [ልደቷ] ፬. ቅድስት ዕሌኒ ንግሥት [ልደቷ] [  † ወርኀዊ በዓላት  ] ፩. ቅድስት ድንግል እግዝእትነ ማርያም ወላዲተ አምላክ ፪. አበው ጎርጎርዮሳት ፫. አቡነ ምዕመነ ድንግል ፬. አቡነ አምደ ሥላሴ ፭. አባ አሮን ሶርያዊ ፮. አባ መርትያኖስ ጻድቅ † " ንግሥተ አዜብ በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነስታ ትፈርድበታለች:: የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለችና:: እነሆም ከሰሎሞን የሚበልጥ ከዚህ አለ::" † [ማቴ.፲፪፥፵፪] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
357