ru
Feedback
ገድለ ቅዱሳን

ገድለ ቅዱሳን

Открыть в Telegram

@Gedelat ለተለያዩ አስተያየት እና ጥቆማ ማድረስ ከፈለጉ በአድራሻችን ቢያደርሱን ይደርሰናል፡፡ በአድራሻችን ✍ @Mnfesawi_bot

Больше
6 493
Подписчики
+524 часа
+17 дней
+630 день

Загрузка данных...

Облако тегов
Нет данных
Возникли проблемы? Пожалуйста, обновите страницу или обратитесь к нашему support-менеджеру .
Входящие и исходящие упоминания
---
---
---
---
---
---
Привлечение подписчиков
июнь '26
июнь '26
+83
в 1 каналах
май '26
+63
в 2 каналах
Get PRO
апрель '26
+77
в 2 каналах
Get PRO
март '26
+58
в 1 каналах
Get PRO
февраль '26
+44
в 1 каналах
Get PRO
январь '26
+59
в 1 каналах
Get PRO
декабрь '25
+98
в 2 каналах
Get PRO
ноябрь '25
+91
в 1 каналах
Get PRO
октябрь '25
+77
в 1 каналах
Get PRO
сентябрь '25
+56
в 1 каналах
Get PRO
август '25
+103
в 1 каналах
Get PRO
июль '25
+85
в 1 каналах
Get PRO
июнь '25
+99
в 1 каналах
Get PRO
май '25
+96
в 1 каналах
Get PRO
апрель '25
+96
в 2 каналах
Get PRO
март '25
+140
в 1 каналах
Get PRO
февраль '25
+107
в 1 каналах
Get PRO
январь '25
+190
в 1 каналах
Get PRO
декабрь '24
+198
в 2 каналах
Get PRO
ноябрь '24
+66
в 1 каналах
Get PRO
октябрь '24
+109
в 3 каналах
Get PRO
сентябрь '24
+60
в 1 каналах
Get PRO
август '24
+89
в 1 каналах
Get PRO
июль '24
+129
в 2 каналах
Get PRO
июнь '24
+107
в 2 каналах
Get PRO
май '24
+109
в 1 каналах
Get PRO
апрель '24
+120
в 2 каналах
Get PRO
март '24
+94
в 2 каналах
Get PRO
февраль '24
+74
в 2 каналах
Get PRO
январь '24
+102
в 2 каналах
Get PRO
декабрь '23
+116
в 3 каналах
Get PRO
ноябрь '23
+81
в 1 каналах
Get PRO
октябрь '23
+98
в 7 каналах
Get PRO
сентябрь '23
+79
в 0 каналах
Get PRO
август '23
+73
в 0 каналах
Get PRO
июль '23
+94
в 0 каналах
Get PRO
июнь '23
+64
в 0 каналах
Get PRO
май '23
+75
в 0 каналах
Get PRO
апрель '23
+78
в 0 каналах
Get PRO
март '23
+84
в 0 каналах
Get PRO
февраль '23
+54
в 0 каналах
Get PRO
январь '23
+83
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '22
+62
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '22
+70
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '22
+54
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '22
+61
в 0 каналах
Get PRO
август '22
+48
в 0 каналах
Get PRO
июль '22
+73
в 0 каналах
Get PRO
июнь '22
+47
в 0 каналах
Get PRO
май '22
+61
в 0 каналах
Get PRO
апрель '22
+75
в 0 каналах
Get PRO
март '22
+91
в 0 каналах
Get PRO
февраль '22
+57
в 0 каналах
Get PRO
январь '22
+99
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '21
+55
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '21
+64
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '21
+141
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '21
+174
в 0 каналах
Get PRO
август '21
+223
в 0 каналах
Get PRO
июль '21
+245
в 0 каналах
Get PRO
июнь '21
+205
в 0 каналах
Get PRO
май '21
+161
в 0 каналах
Get PRO
апрель '21
+520
в 0 каналах
Get PRO
март '21
+395
в 0 каналах
Get PRO
февраль '21
+333
в 0 каналах
Get PRO
январь '21
+517
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '20
+9 090
в 0 каналах
Дата
Привлечение подписчиков
Упоминания
Каналы
26 июня+3
25 июня+7
24 июня+1
23 июня+1
22 июня+2
21 июня+7
20 июня+2
19 июня+3
18 июня+1
17 июня+4
16 июня+3
15 июня+3
14 июня+5
13 июня+7
12 июня+2
11 июня+4
10 июня+5
09 июня+2
08 июня+1
07 июня+7
06 июня+1
05 июня+1
04 июня+3
03 июня+7
02 июня0
01 июня+1
Посты канала
photo content
+1

2
❤#ታላቅ_የበዓለ_ንግሥ_ጥሪ_ነቢዩ_ኤልሳዕ_የዕረፍቱ_በዓል_በእንጦጦ_ደብረ_ኃይል_ቅዱስ_ራጉኤል_ወኤልያስ_ቤተ_ክርስቲያን_ለኦርቶዶክሳውያን_ምዕመናን_በሙሉ። #ነገ_ሰኔ_20_ቀን_2018 ዓ.ም። ይህ መልዕክት ለሁሉም ኦርቶዶክሳውያን ምዕመናን እንዲደርስ #share…………  #share………  #share……… ❤ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ታላቁ እና ታሪካዊው #የርእሰ_አድባራት_እንጦጦ_ደብረ_ኃይል #ቅዱስ_ራጉኤል_ወኤልያስ_ቤተ_ክርስቲያን በመላው ሀገራችን ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ #የታላቁ_ነብይ_ቅዱስ_ኤልያስ_ደቀ_መዝሙር_የባህታውያን_አባት_የተአምራት_ባለቤት_እና_ሙታንን_የማስነሳት_ታላቅ_የፈውስ_ባለቤት_የሆነው_ታላቁ_ነቢየ_እግዚአብሔር #የቅዱስ_ኤልሳዕ_ታቦት በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሆኖ በዚሁ ታላቅ ደብር ይገኛል። ድውያንን የፈወሰ፤ ምድሪቱን በበረከት ያትረፈረፈ፤ በሽታን ያስወገደ ሙታንን ያስነሳ #የታላቁ_ነብይ_የቅዱስ_ኤልሳዕ_ዓመታዊ_የንግስ_በዓል_ነገ_ቅዳሴ_ሰኔ_20_2017 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ስለሚከበር በዕለቱ በታላቁ ደብር ርእሰ አድባራት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተ ክርስቲያን ተገኝተው እንዲያከብሩ መንፈሳዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ይህ መልዕክት ለሁሉም ኦርቶዶክሳውያን ምዕመናን እንዲደርስ #share…………  #share………  #share………                 @Teamihokidusan
71
3
Нет текста...
180
4
🕊                       †                         🕊   [ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ] 🩵                                                  🩵 [    ትንሣኤውንም እናምናለን  !    ] ▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬ ❝ እኛ ግን የዳንበትን አዳኛችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቀበለውን ሕማሙን በፈቃዱ ስለእኛ በሥጋ ያደረገውን ሞቱን እናስተምራለን ፤ ትንሣኤውንም እናምናለን ወደ ሰማይ ማረጉንም እናስተምራለን ፤ በሙታን በሕያዋን ይፈርድ ዘንድ የሚመጣበትን ዳግመኛ ምጽአቱን ፤ እርሱ የሚያወርሳት ለዘለዓለም የማታልፍ መንግሥተ ሰማያት እንዳለች እናምናለን። [ ማቴ.፲፥፳፰-፮ ። ግብ.ሐዋ.፩፥፲፩ ] በኦሪት የተጻፈውን ቃል ምክንያት አድርገው ለእግዚአብሔር ቀድሞ ሥጋ እንደ ነበረው የሚናገሩ ስለዚህም እግዚአብሔር ሰውን በእኛ አምሳል እንፍጠር አለ በእኛ አምሳል ያለውም ስለሰው ሥጋ ነው የሚሉ አሉ። [ዘፍ.፩፥፳፮ ] ነገር ግን እንዲህ አይደለም እርሱ ስለ ውሳጣዊ ሰውነታችን [ ነፍስ ] ተናገረ እንጂ እርሱ ሁልጊዜ በመታደስ ጸንቶ ይኖራልና። አፍአዊ ሰውነታችን [ ሥጋ ] ይሞት ዘንድ እስኪነሣ ድረስም ይፈርስ ይበሰብስ ዘንድ እንዳለው ነገሩ የታወቀ ነው ፤ ውሳጣዊው ግን አይሞትም አይፈርስም አይበሰብስም። [ ፪ቆሮ.፬፥፲፮ ] የበቃ ቢሆን ወደ መንግሥተ ሰማያት ይወስዱታል ፤ መውጣት ሳይኖር ሁል ጊዜ በዚያ ይኖራል።የበቃ ባይሆን ግን ወደገሀነም ይወስዱታል ፤ ፍጻሜ ሳይኖረው ለዘለዓለም በዚያ ይኖራል። [ ማቴ.፳፭፥፵፮ ] ሰው እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ በጎ ሥራን ቢሠራ እግዚአብሔርን እንደሚመስል እግዚአብሔር ገልጦልን ይኸን ቃል እንተረጕማለን ፤ ምድራዊ አዳምን መምሰል ገንዘብ እንደ አደረግን ሰማያዊ ክርስቶስን መምሰልን ገንዘብ እናደርጋለን ተብሎ እንደ ተጻፈ። [ ፩ቆሮ.፲፭፥፮-፵፱ ] ውሳጣዊ ሰውነት ግን የማይለወጥ ዕውቀት ያለው ነፍስ ነው ፤ ዳግመኛም እግዚአብሔር በሥጋ ተሰውሮ ያለ ነፍስን በቸርነቱ እግዚአብሔርን የሚመስል አድርጎ ፈጠረው ፤ እግዚአብሔር ጥንቱን ሥጋ አይደለምና አይወሰንምና ጌታ እሳት ነው ፤ ብርሃንም ነው ፤ ማንም ማን አይቀርበውም ፤ ሕሊናም መርምሮ አያገኘውም አይመረመርም ከላይ ሆኖ ሰማይን ፡ ይሸፍናል ፤ ከታች ሆኖ ምድርን ይሸፍናል። ፍጥረት ሁሉ ፤ ሰማያት በውስጣቸውም ያለው ሁሉ ፤ ምድርም ፤ በምድር ላይ ያለ ሰው ሁሉ ከብቱም አውሬውም ሁሉ የሚንቀሳቀሱትም ወፎችም ፤ የምድረ በዳ ዛፎችም ሁሉ ባሕርም ፤ ፈሳሾችም በውስጣቸውም ያሉ ሁሉ በእርሱ ጸንተው ይኖራሉ መጽሐፍ እንደ ተናገረ ሁሉም በእርሱ ተፈጥሮአልና። [ መዝ.፻፵፰፥፩—፲፬ ። ዮሐ.፩፥፫ ቆላ.፩፥፲፭-፲፰ ] ❞ [    🕊   ቅዱስ ቄርሎስ   🕊     ] ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን። ════════════════                            †††                ✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟ 🕊                        💖                       🕊
164
5
+2
Нет текста...
243
6
❤ ከዚህ በኋላ በዚያች ቀንና በዚያች ሌሊት በሥጋው ላይ እሳትን አነደዱ እሳቱም በላዩ እየነደደ ምንም ምን አልነካውም ወስደውም በገበያ ውስጥ ጣሉት ከዚያም አንሥተው በባሕር ውስጥ ጣሉት በእግዚአብሔርም ፈቃድ ወደ ደሴቱ ወደብ ዳር ደረሰ እናቱም ጠብቃው ነበርና ወስዳ ገነዘችው ለጥቂት ወራትም በቤቷ ውስጥ ሸሸገችው። ❤ ከዚህም በኋላ ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያን ሠሩለት ሥጋውንም በውጧ አኖሩ ከእርሱም ታላላቅና ብዙዎች ድንቆችና ተአምራት ተገለጡ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕቱ በሐዲስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን።                            ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #አባ_ብሶይ_አኖብ፦ የስሙ ትርጓሜውም የጠራ ወርቅ ማለት ነው። ይህም ቅዱስ ከድምያጥ አውራጃ ስሟ ባኖስ ከሚባል አገር ከአቅራብ መኰንን ከቆጵርያኖስ ጭፍሮች ውስጥ ከከተማዋ ታላላቅ ሰዎች ልጆች ወገን ነበር በዚህም ቅዱስ በመኰንኑ ዘንድ ነገር ሠሩበት። ቅዱሱም ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም በፊቱ ታመነ። ❤ ወደ እንዴናውም ወሰዱት በመኰንኑ አርያኖስ ፊት ቁሞ በጌታችን ታመነ አርያኖስም በእርሱ ላይ ተቆጣ "ለአማልክትም ሠዋ" አለው። አልታዘዘለትም ሥቃዩንም አልፈራም መኰንኑም ወስዶ ጽኑዕ ሥቃይ አሠቃየው ከዚያም ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡት አዘዘ ወደሚገድሉበት ቦታም ሊወስዱት አወጡት ብዙ ሕዝብም ይከተሉት ነበር እነሆ ከዚያም የአርያኖስ መኰንን አንበሶች ነበሩ። የሚጠብቃቸውም ሰው ነበር እነርሱም በብረት ሰንሰለት ታሥረው ነበር ከእነርሱም አንዱ አንበሳ የብረት ሰንሰለቱን በጥሶ ሩጦ ወደ ቅዱስ ደረሰ። የእግዚአብሔርም መልአክ ቅዱሱን በአንበሳው ጀርባ ላይ አወጣውና ዐይነ ፀሐይ ወደሚባል አገር እስከሚያደርሰው በረረበት ቅዱሱ ግን ዐይኑን ሸፍኖ ስለ ነበር ውዴት እንዳለ አላወቀም በዚያም ራሱን በሰይፍ ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ብሶይ አኖብ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሰኔ 19 ስንክሳር።                           ✝️ ✝️ ✝️ ❤ "#ሰላም_ለጻድቃን_እለ_በቋዓት"። ትርጉም፦ በቋዓት ያሉ ለኾኑ #ጻድቃን_ሰላምታ_ይገባል። #ሊቁ_አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ_በተአምኆ_ቅዱሳን ላይ።                                                        ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወይርአዩ አሕዛብ በቅድመ አዕይንቲነ። በቀለ ደሞሙ ለአግብርቲከ ዘተክዕወ። ይባዕ ቅድሜከ ገዐሮሙ ለሙቁሓን"። መዝ 78፥10-11። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ተሰ 1፥1-8፣ 1ኛ ዮሐ 2፥14-20 እና የሐዋ ሥራ 19፥11-18። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 24፥8-13። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ቄርሎስ ወይም የቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ቅዳሴ ነው። መልካም በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።                  @Teamihokidusan
220
7
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤               ❤ #ሰኔ ፲፱ (19) ቀን። ❤ እንኳን #ለሰማዕቱ_ሐዲስ_ቅዱስ_ጊዮርጊስ፣ #ለአባ_ብሶይ_አኖብ ሰማዕትነት ለተቀበሉት #ለዕረፍታቸው_በዓልና_ለአምስት_ጭፍሮች እሊህም #ለአርሶፎኒስ_ለጴጥሮስ_ለአስኪርዮን #ለአርጌንዮስ_ለቢልፍዮስ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት #ለዕረፍታቸው_መታሰቢያ_በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከደብረ_ቋዓት ቅዱሳን አባቶቻችን ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                         ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #አምስቱ_ጭፍሮች፦ እሊህም ስማቸው አርሶፎኒስ፣ ጴጥሮስ፣ አስኪርዮስ፣ አርጌንዮስና ቢልፍዮስ ነው። በዲዮስጲልዮስ ቅጽር ውስጥ ይኖሩ ነበር። መኰንኑም ለጣዖታት እንዲሠው በአስገደዳቸው ጊዜ "እኛስ የንጉሣችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ትእዛዝ እንፈጽማለን ለእርሱም እንሰዋለን" አሉት መኰንኑም ሰምቶ ተቆጣ በአንድ ቤት ውስጥም እንዲዘጉባቸውና እስከ ሁለት ቀን ያህል ውኃ እንዳይሰጧቸው አዘዘ። ❤ ከዚህም በኋላ እንዲያመጧቸው አዘዘ በፊቱም በቆሙ ጊዜ "ለአማልክት ሠዉ" አላቸው እነርሱም በአንድ ቃል "እኛስ ለፈጣሪያችን ለክርስቶስ እንሠዋለን ለረከሱ አጋንንትን ግን አንሠዋም" አሉት። አንገታቸውንም አሥረው ወደ ሌላ አገር ይወስዱአቸው ዘንድ አዘዘ። አርጌንዮስም ወንድሞቹን "እኔ እውነትን እነግራችኋለሁ የእግዚአብሔር መልአክ አምስታችንንም በስማችን ሲጠራን ሸምቼዋለሁና" አላቸው። ❤ ዳክስ ወደሚባል መኰንንም በአደረሷቸው ጊዜ መኰንኑ አስቀድሞ አርሶፎኒስን ወስዶ "ለአማልክት ሠዋ" አለው እምቢ በአለውም ጊዜ በፈረስ ጅራት ላይ አሥረው በከተማ ውስጥ እንዲጎትቱትና እንዲአዞሩት አዘዘ። በመለሱትም ጊዜ በውሽባ ቤት ማንደጃ ውስጥ ፊቱን እንዲአጠወልጉት አዘዘ ሁለተኛም እስከ ሚጨነቅ ድረስ በሠረገላ ውስጥ አሥረው ቊልቊል ሰቀሉት ሃይማኖቱንም ጠብቆ ክብር ይግባውና ለጌታችን ነፍሱ ሰጠ። ❤ ሁለተኛም ጴጥሮስን አቀረቡት ዳክስም "ለአማልክት ሠዋ" አለው ትእዛዙንም ባልተቀበለው ጊዜ እንዲአሠቃዩትና እንጨት ተክለው ዘቅዝቀው እንዲሰቅሉት አዘዘ ሁለተኛም ምድሩን ቆፍረው ከትከሻው በታች ቀብረው በቅሎዎችን በላዩ እንዲነዱበት አዘዘ ይህንንም እግዚአብሔር እየረዳው ታገሠ ከጉድጓድም በአወጡት ጊዜ ከሥቃዩ ብዛት የተነሣ ሥጋው ጠወለገ መናገርም ተሣነው በግንድ ውስጥም አሥረው ጣሉት። ❤ ከዚህም በኋላ አርጌንዮስን አቀረቡት ዳክስም "ለአማልክት ሠዋ" አለው እምቢ ባለውም ጊዜ እስከሚገድሉት ድረስ ያሠቃዩት ዘንድ አዘዘ ያለ መብልና መጠጥም በተበሳ ግንድ ውስጥ አሥረው ዘቅዝቀው ሰቀሉት። ❤ ዳግመኛም አስኪርዮንን አቀረቡት ዳክስም "ለራስህ እዘን በክፉ አሟሟትም እንዳትሞት ለአማልክት ሠዋ" አለው እምቢ ባለውም ጊዜ እንዲሰነጥቁት አዘዘ ወታደሮችም ተረከቡትና በጽኑ ሥቃይ አሠቃዩት በትዕግሥቱም በአሸነፋቸው ጊዜ ለመኰንኑ ነገሩት በረኃብና በጽም ይሞት ዘንድ በግንድ ውስጥ አሥረው በባዶ ቤት እንዲዘጉበት አዘዘ እንዲሁም አደረጉበት። ❤ ደግመው ዲያቆን ቢፍዮስን አቀረቡት መኰንን ዳክስሞ "እንዳትሞት ለአማልክት ሠዋ" አለው ባልሰማውም ጊዜ እስከሚገድሉት ድረስ እንዲአሠቃዩት አዘዘ ሥጋውን ሠነጣጥቀው በከተማው አደባባይ ጎተቱት እንጨት ተክለውም ቊልቊል ሰቀሉት በአንገቱም ከባድ ደንጊያ አንጠለጠሉ ከሃይማኖቱም ባልተናወጸ ጊዜ በረኃብና በጽምዕ እንዲሞት በግንድ ውስጥ አሥረው በላዩ መዝጊያ ሠርተው ዘጉበት። በየዕለቱም ወንድሞች ምእመናን ከውጭ ሆነው ይጎበኙት ነበር ጳሔን የተባለው የሰኔ ወር በባተ በሠላሳ ጴጥሮስ ነፍሱን ሰጠ። እርሱንም አውጥተው ደጁን በሌሎቹ ላይ ዘጉ። ❤ የከበረ አርጌንዮስም ከአምስት ቀን በኋላ ዐረፈ እርሱን አውጥተው በቀሩት ላይ ደጁን ዘጉ። ብፁዕ አስኪርዮንም ከዐሥራ ሁለት ቀን በኋላ ዐረፈ። እርሱንም አውጥተው በቅዱስ ቢልፍዮስ ላይ ደጃፍ ሠርተው ዘጉበት እርሱም የሚያርፍባት ቀን ስትደርስ ወንድሞቼ ታገሡኝ በዚች ሌሊት እወጣለሁና አላቸው። ከዐሥራ ዘጠኝ ቀን በኋላ በዚያች ልሊት ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእሊህ ገድለኞች ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                            ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #ሰማዕቱ_ሐዲስ_ቅዱስ_ጊዮርጊስ፦ የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም መዛሕዝም ነው ትርጓሜውም ድንገተኛ ማለት ነው። እርሱም እስላም ነበር ከግብጽ ደቡብ ድምራ ከሚባል አገር ክርስቲያን ሴት አግብቶ ከእርሷም ሦስት ልጆችን ወለደ ከሦስቱም አንዱ ይህ ቅዱስ ነው። ከእናቱም ጋራ ወደ ቤተ ክርስቲያን ይሔድ ነበር ቅዱስ ቁርባንንም ይቀበል ዘንድ እናቱን ለመናት እርሷም ማንም የክርስትናን ጥምቀት ሳይጠመቅና ንጹሕ ሳይሆን ቁርባን ሊቀበል አይችልም አለችው። ❤ ከዚህም በኋላም ከተረፈ መሥዋዕቱ ሰጠችው በጎረሳትም ጊዜ ጣዕሟ በአፉ ውስጥ እንደ ማር ሆነ "የዚች የቁራሿ ጣዕም በአፌ ውስጥ እንዲህ የሆነ የዋናው የቁርባኑ ኅብስት ጣዕም ምን ያህል ይሆን" ብሎ በልቡ አሰበ ከዚች ጊዜ ጀምሮ ክርስቲያን ይሆን ዘንድ ወደደ። ❤ በአደገም ጊዜ ክርስቲያን ሴት አገባ ክርስቲያን ይሆን ዘንድ መፈለጉንም ነገራት እርሷም ወደሌላ አገር ሒዶ የክርስትናን ጥምቀት እንዲጠመቅ መከረችው እርሱም ወደ ሌላ አገር ሒዶ ተጠመቀ ስሙንም ለውጦ ጊዮርጊስ ተባለ። እስላሞችም በአዩት ጊዜ ይዘው ታላቅ ሥቃይን አሠቃዩት ከዚያም አምልጦ ሳፍጥ ወደሚባል አገር ሸሸ በዚያም ሦስት ዓመት ኖረ። ወሬውም በተገለጠ ጊዜ ቀጡር ወደ ሚባል አገር ሒዶ የልዳዊው ሰማዕት የቅዱስ ጊዮርጊስን ቤተ ክርስቲያን እያገለገለ ኖረ። ❤ ከዚህ በኋላ ወደ አገሩ ድምራ ተመለሰ እስላሞችም ሰሙ ይዘውም ለመኰንኑ ሰጡት የመኰንኑም ሚስት ክርስቲያን ነበረች ለመኰንኑም "አታሠቃየው" አለችው መኰንኑም አሥሮ በወህኒ ቤት ዘጋበት። እስላሞችም ተሰብሰቡ የወህኒ ቤቱንም ደጅ ሰብረው ታላቅ ግርፋት ገረፉት አካላቱም ቈራርጠው በሕይወትና በሞት መካከል ጣሉት። ሲነጋም ክርስቲያኖች የሞተ መስሏቸዋልና ሊቀብሩት መጡ ነገር ግን በሕይወት አገኙት። ❤ ከዚህም በኋላ እስላሞች ተሰብስበው "ከዚህ ምክርህ ካልተመለስክ እኛ ጽኑ ሥቃይ አሠቃይተን እንገድልሃለን" አሉት የመዛሕዝም ልጅ የከበረ ጊዮርጊስም "ሰማይና ምድርን የፈጠረ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስን አልክደውም የፈለጋችሁትን አድርጉ" አላቸው። እጅግም ተቆጡ በመርከብ ምሰሶ ላይም ሰቅለው ታላቅ ሥቃይን አሠቃዩት መኰንኑም ከስቅላት አውርደው በእሥር ቤት እንዲአሥሩት አዘዘ እንደዚሁም አደረጉ። ሚስቱም ታጽናናውና እንዲታገሥ ታደርገው ነበር ሰይጣንም እንዳያስተውና የደከመበትን ዋጋ እንዳያጣ በልቡ ወደ ክርስቶስ ያስብ ዘንድ ትመክረው ነበር። ❤ ከዚህም በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጸለትና አረጋጋው አበረታታውም ከሰማዕታትም ጋራ እንደ ተቈጠረ በማግሥቱም ራሱን በሰይፍ እንደሚቆርጡት ነገረው። በነጋም ጊዜ እስላሞች ወደ መኰንኑ ተሰብስበው ጊዮርጊስን ይሰጣቸው ዘንድ ፈለጉ መኰንኑም የወደዱትን ያደርጉበት ዘንድ እንዲሰጧቸው አዘዘ። ❤ ከዚህም በኋላ ከእሥር ቤት አወጡት ድምራ በምትባል አገር በከበረ የመላእክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ራሱን በሰይፍ ሰኔ 19 ቀን ቆረጡ የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ።
185
8
Нет текста...
234
9
[ ስንክሳር ሰኔ - ፲፱ - ] .mp3
222
10
🕊 †  እንኩዋን ለሐዲስ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ  † 🕊  †  ቅዱስ ጊዮርጊስ ሐዲስ  †  🕊 ሰማዕቱ የተወለደው በምድረ ግብጽ አሕዛብ [ተንባላት] በሰለጠኑበት የመጀመሪያው ዘመን ነበር:: በተለይ ተንባላቱ ግብፅና ሶርያን ከያዙ በሁዋላ ባልተጠበቀ ፍጥነት በኃይልም በሰውም ተደራጅተው ነበር:: ቅዱስ ጊዮርጊስ [ልብ በሉልኝ ሊቀ ሰማዕታት አይደለም] የተወለደው በዚህ አስቸጋሪ ጊዜ ነበር:: እናቱ የተመሠከረላት ክርስቲያን ብትሆንም እንዳለመታደል አባቱ ተንባላታዊ [አሕዛብ] ነበር:: ስሙንም መዛሕዝም ይሉታል:: ሕጻኑ እንደተወለደ ያወጡለት ስም አሕዛባዊ ከመሆኑ ባለፈ በሰዓቱ መጠመቅ አልቻለም:: የወቅቱ ሕግ ከወላጆቹ አንዱ አሕዛባዊ ከሆነና አጠምቃለሁ ቢባል የሚከተለው ሰይፍ ነበር:: በዚሕ ምክንያት ሳይጠመቅ ፯ [7] ዓመት ሞላው:: እናቱ ግን ሕጻን ቢሆንም ፍቅረ ክርስትናን ታስተምረው ነበር:: ባይጠመቅም ጸበሉን: እመቱን ትቀባው ነበር:: ደብቃ ቅዳሴ ታሰማውም ነበር:: አንድ ቀን ግን ሕጻናት ሲቆርቡ አይቶ ካልቆረብኩ ብሎ አለቀሰ:: ምን ታድርገው? ወደ ውጪ አውጥታ ከአውሎግያ [የሰንበት በረከት] አበላችው:: "ጌታየ! ልጄን እርዳው" አለች:: ልክ በአፉ ሲቀምሳት መዓዛ መንፈስ ቅዱስ አደረበትና ፍጹም ተደሰተ:: ትንሽ ከፍ ሲል ለምን እንደማይጠመቅና እንደማይቆርብ እናቱን ጠየቃት:: "ልጄ ሆይ! ይገድሉሃል" አለችው:: ከዚህች ቀን ጀምሮ የሚጠመቅበትን ዘዴ ይፈልግ ጀመር:: አስቀድሞ ትምሕርተ ክርስትናን ተማረ:: ለአካለ መጠን ሲደርስ አፈላልጐ ጠንካራ ክርስቲያን የሆነች ሴት አገባ:: ጥቂት ጊዜ ከቆየ በሁዋላ ሚስቱን ስለ መጠመቅ አማከራት:: "ሌላ ሃገር ሒደህ ተጠመቅ" አለችው:: ከግብፅ ተነስቶ ሶርያ ገባ:: አባቶችን አፈላልጎ ተጠመቀ:: ቀጥሎም መንገዱን ወደ ልዳ አደረገ:: ወደ ደብሩ ተጠግቶ አባቶችን "ስም አውጡልኝ" ቢላቸው መንፈስ ቅዱስ አናግሯቸው "ጊዮርጊስ" አሉት:: እሱም ደስ እያለው: ባጭር ታጥቆ የልዳውን ቅዱስ ጊዮርጊስ ያገለግለው ገባ:: ትንሽ ቆይቶ ሁከት መንፈሳዊ ተሰማው:: ማለትም ስለ ሃይማኖቱ ደሙን ማፍሰስ ፈለገና ወደ ግብፅ ተመለሰ:: በዚያ ያሉ አሕዛብ በክርስትና ስም: ልብስና ሞገስ ሲመለከቱት ተበሳጩ:: ዕለቱኑ አሠሩት:: ሌሊት እናቱና ሚስቱ መጥተው አሉት:- "አደራ! ፍቅረ ዓለም እንዳያታልልህ:: ሰማዕት ብትሆን ላንተም ክብር: ለእኛም ሞገስ ነው" ብለውም አጽናኑት:: [ እንዲሕ ያሉ እናትና ሚስት ማግኘትም ታላቅ እድል ነው!!! ] ሐዲስ ጊዮርጊስም ጸና:: ከዚያች ቀን ጀምሮ ለተከታታይ ቀናት ደበደቡት: አካሉን ቆራረጡት: ደሙንም መሬት ላይ አንጠፈጠፉት:: በየመንገዱ እየጎተቱ ተሳለቁበት:: እርሱ ግን ክርስቶስን ወዷልና ሁሉን ታገሰ:: ሌሊት በሆነ ጊዜም ጌታችን ተገልጦ "ከሰማዕታት ተቆጠርህ" አለው:: በማግስቱ በአደባባይ አንገቱን በሰይፍ ቆረጡት:: ክፋታቸው የጸና ነውና ሥጋውን በእሳት አቃጠሉት:: ወደ ባሕርም ጣሉት:: እናቱ ከባሕር ስታወጣው ግን ምንም አላገኘውም ነበር:: በዚሕች ቀን እናቱና ሚስቱ በክብር ቀብረውታል:: ቸሩ አምላክ ከሰማዕቱ ጽናትን: ትእግስትን: ጸጋ በረከትን ይክፈለን:: 🕊 † ሰኔ ፲፱ [ 19 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ፩. ቅዱስ ጊዮርጊስ ሐዲስ ሰማዕት ፪. አባ ብሶይ አኖብ ሰማዕት [ በአንበሳ ጀርባ ላይ የተቀመጠ አባት ] ፫. ቅዱሳን ፭ቱ "5ቱ" ጭፍሮች [ በብዙ ስቃይ ሰማዕት የሆኑ ባልንጀሮች ] ፬. አባቶቻችን የደብረ ቁዋዐት ጻድቃን [ †  ወርሐዊ በዓላት ] ፩. ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት ፪. ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት ፫. አቡነ ዓቢየ እግዚእ ጻድቅ ፬. አቡነ ስነ ኢየሱስ ፭. አቡነ ዮሴፍ ብርሃነ ዓለም " ስለዚሕ ወንድሞቼ ሆይ ! ጣዖትን ከማምለክ ሽሹ:: ልባሞች እንደመሆናችሁ እላለሁ:: በምለው ነገር እናንተ ፍረዱ:: የምንባርከው የበረከት ጽዋ ከክርስቶስ ደም ጋር ኅብረት ያለው አይደለምን? የምንቆርሰውስ እንጀራ ከክርስቶስ ሥጋ ጋር ኅብረት ያለው አይደለምን ? . . . እኛ ብዙዎች ስንሆን አንድ ሥጋ  ነን:: ሁላችን ያን አንዱን እንጀራ እንካፈላለንና:: " [፩ቆሮ.፲፥፲፬-፲፰] (10:14-18) † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
235
11
Нет текста...
210
12
[ በኃጢዓት መዋጥ + ] .mp3
206
13
🕊 💖 🕊 🩵 [ ምክረ ቅዱሳን ] 🩵 ════════════════ ▷ " በ ኃ ጢ ዓ ት መ ዋ ጥ ! " [ 💖 በቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ 💖 ] ▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬ ❝ ነፍሴ ሆይ ፥ ለም
🕊                        💖                        🕊     🩵       [   ምክረ ቅዱሳን   ]        🩵 ════════════════ ▷     " በ ኃ ጢ ዓ ት    መ ዋ ጥ  ! "  [  💖 በቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ 💖  ]  ▬▬▬▬▬▬   ♱    ▬▬▬▬▬▬ ❝ ነፍሴ ሆይ ፥ ለምን ታዝኛለሽ ? ለምንስ ታውኪኛለሽ ? የፊቴን መድኃኒት አምላኬን አመሰግነው ዘንድ በእግዚአብሔር ታመኚ። ❞ [ መዝ.፵፫፥፭ ] ════════════════                            †††                ✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟ 🕊                         💖                        🕊
249
14
+2
Нет текста...
382
15
[ ስንክሳር ሰኔ - ፲፰ - ] .mp3
342
16
🕊 † እንኳን ለጻድቅ ሊቀ ጳጳሳት አባ ድምያኖስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን። † † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! † 🕊  †  አባ ድምያኖስ   †   🕊 †  አባ ድምያኖስ ተወልደው ያደጉት ግብጽ ውስጥ ነው:: ቤተሰቦቻቸው ክርስቲያኖች በመሆናቸው ገና በልጅነት ዕድሜአቸው ቅዱሳት መጻሕፍትንና በጐ ምግባራትን ተምረዋል:: ዕድሜአቸው ወደ ወጣትነቱ ሲጠጋ ሥርዓተ መነኮሳትን ለማጥናት ወደ ገዳመ አባ ዮሐንስ ሔዱ:: በዘመኑ ማንኛውም ሰው ተገቢውን ፈተና ሳያልፍ እንዲመነኩስ አይፈቀድለትም ነበር:: አንድ ሰው ሊመነኩስ ካሰበ በትክክል መናኝ መሆኑ ቢያንስ ለሦስት ቢበዛ ደግሞ ለአሥራ ሁለት ዓመታት እንዲፈተን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታዝዛለች:: ይኸውም "ሥርዓተ አመክሮ" ይባላል:: ከአሥራ ሁለት ዓመታት በላይ መቆየት ከፈለገ ግን ይፈቀድለታል:: በዚህም መሠረት አባ ድምያኖስ ለአሥራ ሰባት ዓመታት በአጭር ታጥቀው ገዳሙን አገልግለዋል:: ገዳሙም ይገባሃል በሚል ዲቁና እንዲሾሙ አድርጓል:: ከዚህ በኋላ ከአባቶች ተባርከው: ገዳሙንም ተሰናብተው ወጡ:: ነገር ግን የወጡት ወደ ዓለም ሳይሆን ራቅ ወዳለ ገዳም ነው:: የረድዕነት ዘመናቸውን ጨርሰዋልና አዲስ በሔዱበት ገዳም ወደ መደበኛው ገድል ተሸጋገሩ:: ያም ማለት በጾም: በጸሎት: በስግደት: በትሕርምት: በትሕትናና በፍቅር ሙሉ ጊዜአቸውን ማሳለፍ ጀመሩ:: በእንዲሕ ያለ ግብርም ዘመናት አለፉ:: የወቅቱ የግብጽ ፓትርያርክ አባ ጴጥሮስ በእረኝነት ሥራ የሚያግዛቸው ሰው እንዲፈለግላቸው በጠየቁት መሠረት ትምሕርትም: ጽሕፈትም: በጐ ምግባራትም የተሟላለት ሰው እንደ አባ ድምያኖስ አልተገኘምና ያለፈቃዳቸው ወደ እስክንድርያ ተወስደው የፓትርያርኩ ረዳት ሆነው ተሾሙ:: በረዳትነት በቆዩበት ጊዜ በወንጌል አገልግሎትና በመንኖ ጥሪት ሕዝቡንና ሊቀ ጳጳሳቱን አስደስተዋል:: ልክ አባ ጴጥሮስ ሲያርፉ ሕዝቡና ሊቃውንቱ በአንድ ድምጽ አባ ድምያኖስን ለፓትርያርክነት መርጧቸዋል:: ጻድቁ ሊቀ ጳጳሳት በዘመነ ፕትርክናቸው ከግል የቅድስና ሕይወታቸው ባለፈ እነዚህን ፈተናዎች በመወጣታቸው ይመሰገናሉ:: ፩. ሕዝቡ ከሃይማኖታቸው እንዳይወጡና በምግባር እንዳይዝሉ ተግተው አስተምረዋል:: ፪. በአካል ያልደረሱባቸውን በጦማር [በመልዕክት] አስተምረዋል:: ፫. በዘመናቸው የተነሱትን መናፍቃን ተከራክረው : የተመለሰውን ተቀብለው : እንቢ ያሉትን አውግዘዋል:: ፬. ከአንጾኪያ ፓትርያርክ የመጣውን የኑፋቄ ጦማር [መልዕክት] በይፋ ተቃውመው አውግዘዋል:: ለአርባ ሦስት ዓመታት የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ሆነው ያገለገሉት አባ ድምያኖስ ከብዙ ትጋት በኋላ በመልካም ሽምግልና በዚህች ቀን ዐርፈዋል:: ከግብጽ አበው ሊቃነ ጳጳሳት ዝርዝር ውስጥም አርባ አምስተኛ ሆነው ተመዝግበዋል:: † ልመናቸው : ክብራቸው : ጸጋ ረድኤታቸው አይለየን:: 🕊 [ †  ሰኔ ፲፰ [ 18 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ] ፩. አባ ድምያኖስ ጻድቅ ሊቀ ጳጳሳት ፪. ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት [ †  ወርኀዊ በዓላት ] ፩. ቅዱስ ፊልጶስ ሐዋርያ ፪. አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ሰባኬ ሃይማኖት [ረባን] ፫. አቡነ አኖሬዎስ ዘደብረ ጽጋጋ ፬. ማር ያዕቆብ ግብጻዊ † " ስለዚህ በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያንን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት : ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ:: ከሄድሁ በኋላ ለመንጋው የማይራሩ ጨካኞች ተኩላዎች እንዲገቡባችሁ እኔ አውቃለሁ:: ስለዚህ ሦስት ዓመት ሌሊትና ቀን በእንባ እያንዳንዳችሁን ከመገሰጽ እንዳላቋረጥሁ እያሰባችሁ ትጉ:: " † [ሐዋ. ፳፥፳፰] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
349
17
Нет текста...
269
18
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #ሰኔ_፲፰ (18) ቀን። ❤ እንኳን #ለእስክንድርያ_አርባ_አምስተኛው ሊቀ ጳጳስ #ለአባ_ድምያኖስ_ለዕረፍት_በዐል መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰው፦ #ከሰማዕቱ_ቅዱስ_ኤስድሮስ መታሰቢያው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                         ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #አባ_ድምያኖስ፦ ይህም አባት ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት አርባ አምስተኛ የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ነው። በአስቄጥስ በአባ ዮሐንስ ሐጺር ገዳም ከታናሽነቱ ጀምሮ መነኰሰ ዐሥራ ሰባት ዓመት ያህልም እየተጋደለ ኑሮ ዲቁና ተሾመ። ከዚህም በኋላ በታርን ወደተባለ ገዳም ሔደ ይኸውም የአባቶች ገዳም ማለት ነው እርሱም በእስክንድርያ ምዕራብ ያለ ነው። እንደ ገዳመውያንም ገድል በውስጡ ተጠምዶ እየተጋደለ ኖረ። ❤ ከእርሱ አስቀድሞ የነበረው አባ ጴጥሮስ ሊቀ ጵጵስና በተሾመ ጊዜ በሊቀ ጵጵስናው ሥራ የሚረዳውና በሥራው ሁሉ የሚአማክረው ስለ ቤተ ክርስቲያን ጥበቃ አዋቂ ሰው ፈለገ ይህንንም አባ ድምያኖስን ሰዎች በበጎ ሥራ ሁሉና በዕውቀቱ ያመሰግኑታል። ስለዚህም ወደርሱ ወሰደውና በሊቀ ጵጵስናው ሥራ እየተራዳው ከእርሱ ጋራ እንዲቀመጥ አደረገው እርሱም ትእዛዙን ተቀብሎ ከእርሱ ጋር ተቀምጠ ሰዎችም ሁሉ ወደዱት። ❤ አባ ጴጥሮስም በዐረፈ ጊዜ ኤጲስቆጶሳትና አዋቂዎች ሊቃውንት በአንድ ምክር ተስማምተው በእስክንድርያ ከተማ ይህን አባ ድምያኖስን ሊቀ ጵጵስና ሾሙት ለአገልግሎትም ፅሙድ ሆነ በመልካም ሥራ ሁሉ ጸንቶ ኖረ። ሁሉጊዜም ድርሰቶችንና መልክቶችን እየጻፈ ወደ አገሩ ሁሉና ወደ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ይልክ ነበር። ❤ በአስቄጥስም ገዳም በአባ መቃርስ ደብር ከነጣቂው ከሀዲ ወገን የሆኑ አርሲሳን የሚሉአቸው መናፍቃን ነበሩ እነርሱም በሚቆርቡበት ቀን ሌሊት ወይን ይጠጣሉ በማግሥቱም ቅዱስ ቁርባንን ይቀበላሉ። እነርሱ ጌታችን በመጀመሪያ ኅብስቱን ከመፈተቱ በፊት በኋላም ኅብስቱን ከሰጣቸው በኋላ ሁለት ጊዜ ጽዋን እንደሰጣቸው በሉቃስ ወንጌል ተጽፎ ያለውን ምክንያት ያደርጋሉና። ይህም አባት አባ ድምያኖስ ስሕተታቸውን ገለጠላቸው የፊተኛው ጽዋ የአለፈው ኦሪት ፋሳካ ምሳሌ እንደ ሆነም አስረዳቸው አዲሱ የአባቶቻችን ሐዋርያት ቀኖና ሕግ ግን የመድኃኒታችንን ሥጋውንና ደሙን የሚቀበል ሁሉ ከመብልና ከመጠጥ ይጠበቅ ዘንድ ከቁርባንም አስቀድሞ ምንም ምን እንዳይቀምስ ያዝዛል። ከእርሳቸውም ውስጥ ከስሕተታቸው ተመልሰው ንስሐ የገቡና የታዘዙለት አሉ ያልተመለሱትን ግን አውግዞ ከምእመናን አንድነት ለይቶ አባረራቸው። ❤ በዚህ በአባ ድምያኖስ ዘመንም የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት ቴዎድሮስ ዐረፈ። በእርሱ ፈንታም የሥላሴን ስም ፈጽሞ የማያወሳ አንድ እግዚአብሔር ብቻ ይላል እንጂ በልዩ ሦስትነት የማያምን መናፍቅ ሰው ተሾመ የከፋች ሃይማኖቱንም የምትገልጽ መልእክት ወደዚህ አባት ድምያኖስ ላከ። አባ ድምያኖስም በአነበባት ጊዜ እጅግ አዘነ በመልክቱ ውስጥ እግዚአብሔር አንድ ገጽ ብቻ እንደ ሆነ ያወሳል እንጂ የልዩ ሦስትነትን ስም የሚያወሳ አላገኘምና። ❤ ይህም አባት ድምያኖስ የሥላሴን በመለኮት አንድነታቸውን በገጽ በአካልና በግብር ሦስትነታቸውን ከቅዱሳን መጻሕፍትም ጠቅሶ ለዚህም መናፍቅ መልእክት ጻፈለት ደግሞም እንዲ አለው "ለእግዚአብሔር ዓለም ሳይፈጠር ከእርሱ ጋራ የነበረ ጥንትና ፍጻሜ የሌለው አካላዊ ቃል አካላዊ ሕይወት አለው"። ይህችንም ምሥጢርንና ዕውቀትን የተመላች መልእክት ለአንጾኪያ ሊቀ ጵጵስና ወደ ተሾመ ወደዚያ መናፍቅ በደረሰች ጊዜ ትርጓሜዋን ያውቅ ዘንድ የልቡ ድንቁርና የአእምሮው ጉድለት አለቀቀውም። ነገር ግን በክህደቱ ጸና። አባ ድምያኖስም ከዚህ መናፍቅ አንድነት ተለየ ማኅበሩንም በቅዳሴና በጸሎት ጊዜ ይህ ከሀዲ እስኪሞት ድረስ ለሃያ ዓመት ስሙን እንዳይጠሩት አዘዛቸው። ❤ ይህም አባት ድምያኖስ በተግሣጾቹና በመልክቶቹ መንጋውን እየጠበቀ አርባ ሦስት ዓመታት ያህል ከኖረና ወደ በጎ እርጅና ከደረሰ እግዚአብሔርንም ከአገለገለ በኋላ ሰኔ 18 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ድምያኖስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሰኔ 18 ስንክሳር።                           ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ሠርከ ወነግሀ ወመዓልተ እነግር። አየድዕ ወኢሰምዑኒ ቃልየ። አድኅና በሰላም ለነፍስየ እምእለ ይትቃረኑኒ"። መዝ 54፥17-18። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ጢሞ 2፥1-ፍ.ም፣ 2ኛ ጴጥ 2፥9-14 እና የሐዋ ሥራ 17፥5-13። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 18፥15-19። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የጾም ጊዜና በዓል ለሁላችን ይሁንልን።                        @Teamihokidusan
306
19
Нет текста...
396
20
❤ አባ ጰላሞንም እየጸለየ ቃሉ ወዳመለከተው ወደ አባ ለትጹን በዓት ደረሰ፡፡ አባ ጰላሞንም ባየው ጊዜ በደስታ ተቀብሎ ሰላምታ ሰጠው፡፡ ወደ ተራራውም ወጥተው ከጸለዩ በኋላ ተቀምጡ፡፡ አባ ጰላሞንም የመረረ ልቅሶን እያለቀሰ ሰይጣን በፈተናው እንደጣለው ለአባ ለትጹን ይነግረው ጀመረ፡፡ እንዲህም አለው፡- "በአንዲት ዕለት የእጅ ሥራዬን ለመሸጥ በግብፅ ገበያ መንገድ ስጓዝ ሰይጣን መጥቶ ልቤን አዘነጋት፤ መድኃኒት የሚሆነኝን የጌታዬ የኢየሱስ ክርስቶስን ስም እጠራ ዘንድ አልተወኝም፡፡ ዳግመኛም እንደ ንጉሥ ከተማ የታነፀች ውኃዎችና ተክሎች መልካም ዛፎችም ያሏት ከተማን አሳየኝ፡፡ የእጅ ሥራዬንም ልሸጥ ሳስብ ባሏ ብዙ ገንዘብ ትቶላት ሙቶ በምታዝን ሴት አምሳል ታየኝ፡፡ "የእጅ ሥራህን እኔ እገዛሃለሁ" ብለኝ ወደ አዳራሽ አስገባችኝ፡፡ እንቅቦቹንም ከላዬ አውርዳ አኖረች፣ እግሮቼንም አጠበች፣ አሽከሮቿንም ምግብ ያቀርቡ ዘንድ አዘዘቻቸው፡፡ ከእርሷ ጋርም እበላ ዘንድ ብዙ ማለደችኝ፣ በልተን ጠጥተን ሰከርን፡፡ ስንጨዋወትም አሽከሮቿ ሁሉም ወጡና ሁለታችን ብቻችንን ቀረን፡፡ ያንጊዜም ልቤ በዝሙት እሳት ተቃጠለ፡፡ እግዚአብሔርንም መላእክቶቹንም ቢሆን አላሰብኩም በእርግጥ ከእርሷ ጋር እንደሚተኛ ሆንኩ፡፡ ❤ ከዚህ በኋላ በነቃሁ ጊዜ ብመለከት ምንም ነገር አላገኘሁም፡፡ ሴትም ቤትም ማዕድም አትክልትም ቢሆን አላገኘሁም፡፡ ነገር ግን ራሴን ከተራራው በታች አገኘሁት፡፡ ምንም እንዳልበላና እንዳልጠጣም ሰው ሆንኩ፡፡ እጅግም አለቀስኩ፡፡ ሰይጣንም በሩቁ ቆሞ "መጻተኛ ጰላሞን ሆይ ወዮልህ እንደወፍ ላጠምድህ በአንተ ላይ በርትቻለሁና…" እያለ ሲዘብትብኝ አየሁት፡፡ ነገሩንም ሰምቼ በመስቀል ምልክት በላዩ አማተብኩ፣ ከእኔም ሸሸ፡፡ "አሁንም አባቴ ለትጹን ሆይ በደሌን ይቅር ይለኝ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር እንድትለምንልኝ በቅድስናህ ተማፅኛለሁ" አለው፡፡ ቅዱስ አባ ጰላሞንም "አይዞህ እግዚአብሔር ኃጢአትህን ይቅር እንደሚልህ አምናሁ" ብሎ አጽናናው፡፡ ከዚህም በኋላ ተነሥቶ ሦስት መዓልትና ሦስት ሌሊት ጸለየ፡፡ ወደ እነርሱም እንዲህ የሚል ቃል መጣ፡- "የታመናችሁ አገልጋዮቼ አትፍሩ ከእንግዲህ ወዲህ ጠላት በእናንተ ላይ አይበረታታም፡፡ ጰላሞንም የሠራውን ኃጢአት በራሱ በሰይጣን ላይ አደረግሁ፣ የጰላሞንን ኃጢአት ብቻ አይደለም ነገር ግን የሚፈትናቸውን ሰዎች ሁሉ ኃጢአታቸውን በሰይጣን በራሱ ላይ እመልሳለሁ"፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ አባ ጰላሞን ከአባ ለትጹን በረከትን ተቀብሎ እግዚአብሔርን እያመሰገነ ወደ በዓቱ ሄደ፡፡ ተጋድሎውንም ፈጽሞ በዚህች ዕለት በሰላም ዐረፈ፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ሁሉ ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፡- የሰኔ 17 ስንክሳር።                            ✝️ ✝️ ✝️ ❤ "#ሰላም_ለአባ_ለትጹን_እስከ_ፍጻሜ_ዘክህለ። ከመ ያውጽእ እምደይን ብእሴ ህጉለ። ለለ መዋዕል ሰዱስ እንዘ ይበልዕ ቈጽለ። በትርሕምት ዐቢይ እምብዝኀ ተጋደለ ገድለ። በአምሳለ ዖፍ ኮነ ሥጋሁ ቀሊለ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሰኔ_17።                           ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ኀይልየኒ ወዝክርየኒ እግዚአብሔር። ወውእቱ ኮነኒ መድኃንየ። ቃለ ትፍሥሕት ውስተ አብያቲሆሙ ለጻድቃን"። መዝ 117፥14። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 17፥5-11።                            ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "አኮ ከመዝ ኃጥአንሰ አኮ ከመዝ። ዳዕሙ ከመ መሬት ዘይግሕፎ ነፋስ እምገጸ ምድር። ወበእንተዝ ኢይትነሥኡ ረሲዓን እምደይን"። መዝ 1፥4-5። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ጢሞ 1፥1-10፣ ያዕ 5፥14-17 እና የሐዋ ሥራ 13፥44-49። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 6፥20-24። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም የአባ ገሪማ ከሞት የተሰወሩበት በዓል፣ ለአባ ለትጹን፣ የአባ ጰላሞን የዕረፍት በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።                   @Teamihokidusan
353