ገድለ ቅዱሳን
Открыть в Telegram
@Gedelat ለተለያዩ አስተያየት እና ጥቆማ ማድረስ ከፈለጉ በአድራሻችን ቢያደርሱን ይደርሰናል፡፡ በአድራሻችን ✍ @Mnfesawi_bot
Больше6 486
Подписчики
-124 часа
-37 дней
+330 день
Загрузка данных...
Похожие каналы
Облако тегов
Нет данных
Возникли проблемы? Пожалуйста, обновите страницу или обратитесь к нашему support-менеджеру .
Входящие и исходящие упоминания
---
---
---
---
---
---
Привлечение подписчиков
июнь '26
июнь '26
+72
в 1 каналах
май '26
+63
в 2 каналах
Get PRO
апрель '26
+77
в 2 каналах
Get PRO
март '26
+58
в 1 каналах
Get PRO
февраль '26
+44
в 1 каналах
Get PRO
январь '26
+59
в 1 каналах
Get PRO
декабрь '25
+98
в 2 каналах
Get PRO
ноябрь '25
+91
в 1 каналах
Get PRO
октябрь '25
+77
в 1 каналах
Get PRO
сентябрь '25
+56
в 1 каналах
Get PRO
август '25
+103
в 1 каналах
Get PRO
июль '25
+85
в 1 каналах
Get PRO
июнь '25
+99
в 1 каналах
Get PRO
май '25
+96
в 1 каналах
Get PRO
апрель '25
+96
в 2 каналах
Get PRO
март '25
+140
в 1 каналах
Get PRO
февраль '25
+107
в 1 каналах
Get PRO
январь '25
+190
в 1 каналах
Get PRO
декабрь '24
+198
в 2 каналах
Get PRO
ноябрь '24
+66
в 1 каналах
Get PRO
октябрь '24
+109
в 3 каналах
Get PRO
сентябрь '24
+60
в 1 каналах
Get PRO
август '24
+89
в 1 каналах
Get PRO
июль '24
+129
в 2 каналах
Get PRO
июнь '24
+107
в 2 каналах
Get PRO
май '24
+109
в 1 каналах
Get PRO
апрель '24
+120
в 2 каналах
Get PRO
март '24
+94
в 2 каналах
Get PRO
февраль '24
+74
в 2 каналах
Get PRO
январь '24
+102
в 2 каналах
Get PRO
декабрь '23
+116
в 3 каналах
Get PRO
ноябрь '23
+81
в 1 каналах
Get PRO
октябрь '23
+98
в 7 каналах
Get PRO
сентябрь '23
+79
в 0 каналах
Get PRO
август '23
+73
в 0 каналах
Get PRO
июль '23
+94
в 0 каналах
Get PRO
июнь '23
+64
в 0 каналах
Get PRO
май '23
+75
в 0 каналах
Get PRO
апрель '23
+78
в 0 каналах
Get PRO
март '23
+84
в 0 каналах
Get PRO
февраль '23
+54
в 0 каналах
Get PRO
январь '23
+83
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '22
+62
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '22
+70
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '22
+54
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '22
+61
в 0 каналах
Get PRO
август '22
+48
в 0 каналах
Get PRO
июль '22
+73
в 0 каналах
Get PRO
июнь '22
+47
в 0 каналах
Get PRO
май '22
+61
в 0 каналах
Get PRO
апрель '22
+75
в 0 каналах
Get PRO
март '22
+91
в 0 каналах
Get PRO
февраль '22
+57
в 0 каналах
Get PRO
январь '22
+99
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '21
+55
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '21
+64
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '21
+141
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '21
+174
в 0 каналах
Get PRO
август '21
+223
в 0 каналах
Get PRO
июль '21
+245
в 0 каналах
Get PRO
июнь '21
+205
в 0 каналах
Get PRO
май '21
+161
в 0 каналах
Get PRO
апрель '21
+520
в 0 каналах
Get PRO
март '21
+395
в 0 каналах
Get PRO
февраль '21
+333
в 0 каналах
Get PRO
январь '21
+517
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '20
+9 090
в 0 каналах
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 24 июня | 0 | |||
| 23 июня | +1 | |||
| 22 июня | +2 | |||
| 21 июня | +7 | |||
| 20 июня | +2 | |||
| 19 июня | +3 | |||
| 18 июня | +1 | |||
| 17 июня | +4 | |||
| 16 июня | +3 | |||
| 15 июня | +3 | |||
| 14 июня | +5 | |||
| 13 июня | +7 | |||
| 12 июня | +2 | |||
| 11 июня | +4 | |||
| 10 июня | +5 | |||
| 09 июня | +2 | |||
| 08 июня | +1 | |||
| 07 июня | +7 | |||
| 06 июня | +1 | |||
| 05 июня | +1 | |||
| 04 июня | +3 | |||
| 03 июня | +7 | |||
| 02 июня | 0 | |||
| 01 июня | +1 |
Посты канала
| 2 | ❤ አባ ጰላሞንም እየጸለየ ቃሉ ወዳመለከተው ወደ አባ ለትጹን በዓት ደረሰ፡፡ አባ ጰላሞንም ባየው ጊዜ በደስታ ተቀብሎ ሰላምታ ሰጠው፡፡ ወደ ተራራውም ወጥተው ከጸለዩ በኋላ ተቀምጡ፡፡ አባ ጰላሞንም የመረረ ልቅሶን እያለቀሰ ሰይጣን በፈተናው እንደጣለው ለአባ ለትጹን ይነግረው ጀመረ፡፡ እንዲህም አለው፡- "በአንዲት ዕለት የእጅ ሥራዬን ለመሸጥ በግብፅ ገበያ መንገድ ስጓዝ ሰይጣን መጥቶ ልቤን አዘነጋት፤ መድኃኒት የሚሆነኝን የጌታዬ የኢየሱስ ክርስቶስን ስም እጠራ ዘንድ አልተወኝም፡፡ ዳግመኛም እንደ ንጉሥ ከተማ የታነፀች ውኃዎችና ተክሎች መልካም ዛፎችም ያሏት ከተማን አሳየኝ፡፡ የእጅ ሥራዬንም ልሸጥ ሳስብ ባሏ ብዙ ገንዘብ ትቶላት ሙቶ በምታዝን ሴት አምሳል ታየኝ፡፡ "የእጅ ሥራህን እኔ እገዛሃለሁ" ብለኝ ወደ አዳራሽ አስገባችኝ፡፡ እንቅቦቹንም ከላዬ አውርዳ አኖረች፣ እግሮቼንም አጠበች፣ አሽከሮቿንም ምግብ ያቀርቡ ዘንድ አዘዘቻቸው፡፡ ከእርሷ ጋርም እበላ ዘንድ ብዙ ማለደችኝ፣ በልተን ጠጥተን ሰከርን፡፡ ስንጨዋወትም አሽከሮቿ ሁሉም ወጡና ሁለታችን ብቻችንን ቀረን፡፡ ያንጊዜም ልቤ በዝሙት እሳት ተቃጠለ፡፡ እግዚአብሔርንም መላእክቶቹንም ቢሆን አላሰብኩም በእርግጥ ከእርሷ ጋር እንደሚተኛ ሆንኩ፡፡
❤ ከዚህ በኋላ በነቃሁ ጊዜ ብመለከት ምንም ነገር አላገኘሁም፡፡ ሴትም ቤትም ማዕድም አትክልትም ቢሆን አላገኘሁም፡፡ ነገር ግን ራሴን ከተራራው በታች አገኘሁት፡፡ ምንም እንዳልበላና እንዳልጠጣም ሰው ሆንኩ፡፡ እጅግም አለቀስኩ፡፡ ሰይጣንም በሩቁ ቆሞ "መጻተኛ ጰላሞን ሆይ ወዮልህ እንደወፍ ላጠምድህ በአንተ ላይ በርትቻለሁና…" እያለ ሲዘብትብኝ አየሁት፡፡ ነገሩንም ሰምቼ በመስቀል ምልክት በላዩ አማተብኩ፣ ከእኔም ሸሸ፡፡ "አሁንም አባቴ ለትጹን ሆይ በደሌን ይቅር ይለኝ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር እንድትለምንልኝ በቅድስናህ ተማፅኛለሁ" አለው፡፡ ቅዱስ አባ ጰላሞንም "አይዞህ እግዚአብሔር ኃጢአትህን ይቅር እንደሚልህ አምናሁ" ብሎ አጽናናው፡፡ ከዚህም በኋላ ተነሥቶ ሦስት መዓልትና ሦስት ሌሊት ጸለየ፡፡ ወደ እነርሱም እንዲህ የሚል ቃል መጣ፡- "የታመናችሁ አገልጋዮቼ አትፍሩ ከእንግዲህ ወዲህ ጠላት በእናንተ ላይ አይበረታታም፡፡ ጰላሞንም የሠራውን ኃጢአት በራሱ በሰይጣን ላይ አደረግሁ፣ የጰላሞንን ኃጢአት ብቻ አይደለም ነገር ግን የሚፈትናቸውን ሰዎች ሁሉ ኃጢአታቸውን በሰይጣን በራሱ ላይ እመልሳለሁ"፡፡
❤ ከዚህም በኋላ አባ ጰላሞን ከአባ ለትጹን በረከትን ተቀብሎ እግዚአብሔርን እያመሰገነ ወደ በዓቱ ሄደ፡፡ ተጋድሎውንም ፈጽሞ በዚህች ዕለት በሰላም ዐረፈ፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ሁሉ ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፡- የሰኔ 17 ስንክሳር።
✝️ ✝️ ✝️
❤ "#ሰላም_ለአባ_ለትጹን_እስከ_ፍጻሜ_ዘክህለ። ከመ ያውጽእ እምደይን ብእሴ ህጉለ። ለለ መዋዕል ሰዱስ እንዘ ይበልዕ ቈጽለ። በትርሕምት ዐቢይ እምብዝኀ ተጋደለ ገድለ። በአምሳለ ዖፍ ኮነ ሥጋሁ ቀሊለ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሰኔ_17።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ኀይልየኒ ወዝክርየኒ እግዚአብሔር። ወውእቱ ኮነኒ መድኃንየ። ቃለ ትፍሥሕት ውስተ አብያቲሆሙ ለጻድቃን"። መዝ 117፥14። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 17፥5-11።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "አኮ ከመዝ ኃጥአንሰ አኮ ከመዝ። ዳዕሙ ከመ መሬት ዘይግሕፎ ነፋስ እምገጸ ምድር። ወበእንተዝ ኢይትነሥኡ ረሲዓን እምደይን"። መዝ 1፥4-5። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ጢሞ 1፥1-10፣ ያዕ 5፥14-17 እና የሐዋ ሥራ 13፥44-49። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 6፥20-24። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም የአባ ገሪማ ከሞት የተሰወሩበት በዓል፣ ለአባ ለትጹን፣ የአባ ጰላሞን የዕረፍት በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
@Teamihokidusan | 139 |
| 3 | ❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ሰኔ ፲፯ (17) ቀን።
❤ እንኳን ለታላቁ አባት እናቱን በዝሙት አስረግዞ ፅንሱንም መርዝ አጠጥቶ በማኅፀኗ የገደለውን ርጉም ሰው ከዘላለማዊው ሥቃይና ኩነኔ ለታደጉት #ለአባ_ለትጹንና ፍፁም መናኒ ለሆነ ለመጻተኛ ከሰው ጋር ተነጋግሮ ለማያውቀውና በተራራ ላይ ብቻውን በገድል ተጠምዶ ሲኖር የጌታችንን መከራ እያሰበ ቀንና ሌሊት ያለቅስ ለነበረው ለባሕታዊ #አባ_ጰላሞን ለዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከሰማዕታት #ከነአኮራን፣ #ከበርተሎሜዎስ፣ #ከእለስክንድርያ፣ #ከእለስክንድሮስ፣ #ከዮሴፍና_ከጻድቂቱ_አርሴማ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝️ ✝️ ✝️
❤#አባ_ለትጹን፦ ይህም አባት ከብህንሳ አገር ነበር ጎልማሳ በነበረ ጊዜም "ነፍሱን ስለ እኔ የጣላትም ያገኛታል ለዘላለም ሕይወትንም ይጠብቃታል" የሚለውን በቅዱስ ወንጌል ውስጥ የተጻፈውን የሕያው ንጉሥን ቃል ሰማ ወዲያውኑ ልቡ ስለ እግዚአብሔር ፍቅርና ስለ ዘላለማዊ ተድላ እንደ እሳት ነደደ። ቅዱስ ቁርባንንም ተቀብሎ እስዋሕት ወደ ሚባል ገዳም ሔደ በጾም በጸሎትና በስግደት ታላቅ ተጋድሎን ያለ ማቋረጥ ይጋደል ጀመር ሰባት ሰባት ቀንም ይጾም ነበር።
❤ የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጸለትና የምንኲስና ልብስን ዘንድ ወደ አባ ኤስድሮስ እንዲሔድ አዘዘው እርሱም መልአኩ እንዳዘዘው ሔደ አባ ኤስድሮስም በልብሱና በአስኬማው ላይ አርባ ቀኖች ጸለየ ከዚያም በኋላ ልብሱንና አስኬማውን አለበሰው በገድል መጠመድን ጨመረ።
❤ ከዚያም መምህሩንም አስፈቅዶ ወጥቶ ብቻውን መጋደል ጀመረ፡፡ በአቅራቢያውም አንድ ገዳም ነበረና አንድ ቀን አበ ምኔቱ ታሞ ለሞት ደርሶ አገኘው፡፡ መነኰሳትም ዙሪያውን ከበውት ሲያለቅሱት አገኛቸው፡፡ እንዲሁም የሰይጣን ሠራዊትም አበ ምኔቱን ከበውት ደስ ሲሰኙ አያቸውና ደንግጦ "አባት ሆይ በአንተ ላይ የሆነው ምንድነው?" ብሎ አበ ምኔቱን ጠየቀው፡፡ እርሱም መነኰሳቱን ከእርሱ እንዲርቁ ካደረገ በኋላ የሠራውን በደሉን እንዲህ ብሎ ነገረው "እኔ ካሁን በፊት ማንም ያልሠራውን ኃጢአት ሠርቻለሁና አባቴ ሆይ በጸሎትህ አትርሳኝ፡፡ እኔ ቅስና ልሾም ፈልጌ ባልሾሙኝ ጊዜ ወደ ሌላ ሀገር ሄድኩ፡፡ "ኤጲስቆጶሱም ቅስና ሹሞኛል" ብዬ በድፍረት በቁርባን ላይ የምቀድስ ሆንኩ፡፡ ለጠላሁትም በቁርባኑ መሥዋዕት ውስጥ መርዝ አድርጌ እሰጠዋለሁ እርሱም ይሞታል፡፡ ከእናቴም ጋራ ዓሥር ጊዜ ተኝቻለሁ፣ ከእኔም ፀንሳ ለመውለድ በደረሰች ጊዜ ሥራይ አጠጥቼ ሕፃኑን በሆዷ ውስጥ ገደልኩት፡፡ ኃጢአቴ ብዙ ነውና ተነግሮ አያልቅም፡፡ ከበጎ ሥራም ምንም ምን የሠራሁት የለም፡፡ ነገር ግን በጸሎትህ አትርሳኝ ከዚህ ከኃላፊው ዓለም መውጫዬ ደርሷልና" ብሎ ለአባ ለትጹን ነገረው፡፡ ወዲያውም በክፉ አሟሟት ሞተ፤ ነፍሱንም አጋንንት ሲቀበሏትና በየራሱ በሆነ ሥቃይ ሲያሠቃዩዋት አባ ለትጹን ተመለከታት፡፡
❤ በዚህም አባ ለትጹን የመረረ ልቅሶን አለቀሰ፡፡
ከዚህም በኋላ አባ ለትጹን "ስለ ወዳጆቹ ነፍሱን አሳልፎ የሚሰጥ ያለ ከሆነ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር የለም" የሚለውን የቅዱስ ወንጌልን ቃል አስቦ ስለዚያ ኃጥእ ሰው ነፍስ ወደ ጌታችን እየለመነ አምስት ጊዜ እስከሚሞት ሰውነቱን ሊያሠቃያት ጀመረ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል መትቶ አስነሣውና እንዲህ አለው "ስለዚያ ኃጢአተኛ ነፍስ ነፍስህን አትግደል ምሕረት አይገባውምና፡፡ እግዚአብሔር እውነት ፈራጅ ስለሆነ በደሉ አይሠረይለትም"፡፡
❤ አባ ለትጹን ግን መሐሪ ይቅር ባይ ወደሆነ እግዚአብሔር ስለዚያ ኃጢአተኛ እየለመነ ራሱን ማሠቃየት አልተወም፡፡ ከዚህም በኋላ ራሱን በባሕር አስጥሞ ሞተ፡፡ ያን ጊዜም ጌታችን መጥቶ በባሕሩ ዳር ተቀመጠና ከባሕሩ ውስጥ አውጥቶ ከሞት ያድነው ዘንድ ሚካኤልን አዘዘው፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም አባ ለትጹንን ከባሕሩ አውጥቶ ከሞት አድኖ ቤታችን ፊት አቆመው፡፡ ክብር ይግባውና ጌታችንም "የመጥኩህ ለትጹን ሆይ ኃጢአቱ እጅግ ብዙ ስለሆነ በደሉም ከኃጢአተኞች ሁሉ በደል ስለሚከፋ ምሕረት ስለማይገባው ስለዚያ ኃጢአተኛ ሰው ብዙ ጊዜ ነፍስህን ለምን ትገድላለህ?" አለው፡፡ አባ ለትጹንም "መሐሪና ይቅር ባይ ጌታዬ ፈጣሪዬ ሆይ ያን ኃጢአተኛ ትምረው ዘንድ እለምንሃለሁ ያለዚያ ግን የእኔንም ነፍሴን ከእርሱ ጋራ ወደ ሥቃይ ውሰዳት" ብሎ ጌታችንን ለመነው፡፡
❤ ከዚህም በኋላ ጌታችን የዚያን ኃጥእ ነፍስ ያመጣት ዘንድ ቅዱስ ሚካኤልን አዘዘውና አመጣት፡፡ ጌታችንም በከበሩ እጆቹ ዳሰሳትና እንዳልተፈጠረች አደረጋት፡፡ ወዲያውም "ይህቺ ነፍስ አፈር ትሁን እንጂ ለሥቃይ ወይም ለሕይወት አትሁን" አለ፡፡ አባ ለትጹንም ስለይቅርታውና ስለቸርነቱ ገናናነት መድኃኒታችንን ፈጽሞ አመሰገነው፡፡
❤ ከዚህም በኋላ ጌታችን አባ ለትጹንን "የመጥኩህ ለትጹን ሆይ በእውነት እነግርሃለሁ መታሰቢያህን ለሚያደርግ ሁሉ በስምህ መባ ለሚያስገባ ወይም የተራበ ለሚያበላ የተጠማ ለሚያጠጣ የተራቆተ ለሚያለብስ ገድልህን ለሚጽፍ እኔ የሁሉንም ኃጢአታቸውን ይቅር እላለሁ፣ ስማቸውንም በሕይወት መጽሐፍ እጽፋለሁ፣ በጎ ዋጋቸውንም እሰጣቸዋለሁ" የሚል ቃልኪዳን ሰጥቶት ወደ ሰማያት ዐረገ፡፡ አባ ለትጹንም እጅግ ደስ ብሎት ወደ በዓቱ በመመለስ ብዙ ከተጋደለ በኋላ ገድሉን ፈጽሞ ሰኔ 17 ቀን በሰላም ዐረፈ፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ለትጹን ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትጉር ለዘላለሙ አሜን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #ባሕታዊ_አባ_ጰላሞን፦ ከተጋድሎው የተነሣ ሰይጣን እስከ ደከመ ድረስ በተራራ ላይ እግዚአብሔርን እያገለገለ በገድል ተጠምዶ ሲኖር ቀንና ሌሊት ያለቅስ ነበር፡፡ ከሰው ጋር ሳይነጋገር ብዙ ዘመን ከኖረ በኋላ ሰይጣን የሚያስቅ ነገርንና ጨዋታን እያመጣበት ይፈትነው ነበር፡፡ ነገር ግን አባ ጰላሞን የጌታችንን መከራ እያሰበ ይተክዝ ያለቅስ ነበር፡፡ ሰይጣንም በዚህ ተቆጥቶ አንበሳ ሚዳቋን እንደሚያድን አባ ጰላሞንን ያድነው ነበር፡፡ በአንዲት ቀንም አባ ጰላሞን የእጅ ሥራውን ሊሸጥ ተነሠቶ ወደ ገበያ ሲጓዝ ሰይጣን ጎዳናውን አሳተው፣ ልቡንም መሰጠው እንጂ የሚያደርገውን ያውቅ ዘንድ አልተወውም፡፡
❤ ከሰባት ቀኖች በኋላ አባ ጰላሞን ከረኀብና ከውኃ ጥም የተነሣ ከመሬት ላይ ወደቀ፤ ለሞትም የደረሰ ሆነ፡፡ ሰውን ወዳድ የሆነ ጌታችንም እንዲጠፋ አልተወውምና ሰይጣንን ከእርሱ አርቆ አሳደደው፡፡ አባ ጰላሞን በእርሱ ላይ የሆነውን ባወቀ ጊዜ ወደ ጌታን ጮኸ፡፡ ወዲያውም "ጰላሞን ሆይ አትፍራ ከእንግዲህ ወዲህ ጠላት በአንተ ላይ ክፉ ሊሠራ አይልችም፡፡ ነገር ግን ተነሥተህ ወደ ደቡብ ጥቂት ተጓዝ በዚያም በተራራው አጠገብ የሚኖር ስሙ ለትጹን የሚባል ሽማግሌ ጻድቅ ሰው ታገኛለህ፣ እርሱ ስለ ስሜ ብዙ መከራ የተቀበለ ነው፡፡ ያደረከውንም ሁሉ ሰይጣንም እንዴት እንዳሳተህ ንገረው፣ እርሱ ኃጢአትህ እስኪሠረይ ስለ አንተ ይጸልያልና" የሚል ቃልን ሰማ፡፡ | 95 |
| 4 | Нет текста... | 64 |
| 5 | ❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ሰኔ ፲፯ (17) ቀን።
❤ እንኳን #ከዘጠኙ_ቅዱሳን_አንዱ_ለሆኑት ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ይስሐቅ ባደረጉት ተአምር ስማቸው
#አባ_ገሪማ_ለተባሉት ከዚህ ዓለም #ከሞት_ለተሰወሩበት_ዓመታዊ_መታሰቢያ_በዐል እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #አቡነ_ይስሐቅ_አባ_ገሪማ፦ የዚህም ቅዱስ አባቱ የሮም ንጉሥ ነበር ስሙም መስፍንያኖስ ይባላል። የንግሥት እናቱ ስምም ሰፍንግያ ነው እርሷም መካን ስለሆነች በእናቱ በቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም ከማላጅነት በመማፀን ወደ እግዚአብሔር እየለመነች ኖረች። ከዚህ በኋላ ይህን የተባረከ ልጅ ተቀበለች ስሙንም ይስሐቅ ብላ ጠራችው። ጥቂት በከደገ ጊዜም የቤተ ክርስቲያን ትምህርት አስተምረው ዲቁና አሾሙት።
❤ አባቱ በሞተ ጊዜ የሮም ሰዎች በአባቱ ዙፋን ላይ አነገሡት እየፈረደና በቅን እየገዛ ሰባት ዓመት ኖረ። በዋሻ የሚኖረው አባ ጰንጠሌዎንም በሰማ ጊዜ እንዲህ ብሎ ወደርሱ ላከ "ልጄ ይስሐቅ ሆይ ሙታኖቻቸውን ይቀብሩ ዘንድ ሙታኖችን ተዋቸው አንተ ግን ክብር ይግባውና የክርስቶስን የማያልፍ መንግሥት ትሻ ዘንድ ወደ እኔ ና" አባ ገሪማም መልእክቱ ደርሶት በሰማ ጊዜ መንግሥቱን ትቶ በሌሊት ወጥቶ ሔደ ያንጊዜም ጌታ የላከው የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ተገለጠለት ብርሃናውያን በሆኑ ክንፎቹም ተሸክሞ የዐሥር ወር የሚሆነውን መንገድ በሦስት ሰዓት አደረሰው በአባ ጰንጠሌዎንም ደጅ አቆመው ይህም በኢትዮጵያ ንጉሥ በእልአሚድ ዘመን ነበር።
❤ አባ ጰንጠሌዎንም ቅዱስ ይስሐቅን በአየው ጊዜ ደስ ብሎት አቅፎ ሳመው ወደ በዓቱም አስገብቶ የምንኲስና ልብስን አለበሰው። ይስሐቅም በጾም በጸሎትና በስግደት ተጠምዶ ቆዳው ከዐፅሙ እስከሚጣበቅ ሲጋደል ኖረ።
❤ ከዚህም በኋላ መደራ ወደተባለ ቦታ ሔደ በዚያም ድንቅና ተአምር እየአደረገ በሽተኞችን በመፈወስና አጋንንትን በማስወጣት ብዙ ዘመን ኖረ። በአንዲት ዕለትም በጥዋት ሥንዴ ዘራ በሠርክም መሥዋትን አሳረገ። በማግሥቱም በግራር ዛፍ ላይ በሮችን አውጥቶ የሥንዴውን ነዶ አበራየ ሰባ ሰባት የእንቅብ መስፈሪያም ሆነ። ሁለተኛም የወይን አረግ በአለት ላይ ተከለ ወዲያውም በቀለች አበበችና አፈራች በእርሷም መሥዋዕትን አሳረገ። አንዲት ቀንም ሲጽፍ መሸና ፀሐይ ሊጠልቅ ተቃረበ በቦታውም እንዲቆም አዘዘው ጽሕፈቱንም እስቲጨርስ ቆመ። ምራቁንም ትፍ ባለበት ዘንድ ጠበል ፈልቆ እስከ ዛሬ ለበሽተኞች ፈውስ ሆኖ ይኖራል።
❤ በአንዲት ዕለትም ሰዎች ወደ አባ ጰንጠሌዎን መጥተው "ቀሲስ ይስሐቅ እኮ ከበላ በኋላ የቁርባን ቅዳሴ ቀደሰ" ብለው ነገሩት አባ ጰንጠሌዎንም ወደርሱ ሒዶ "ልጄ ይስሐቅ ሆይ ምሥጢር ስለ አለኝ ከአጠገባችን ሰዎችን አስገልል" አለው ይስሐቅም "ሰዎችን ተውና ዕንጨቶችና ድንጋዮችም ይገለሉ" አለ። ወዲያውኑም ዕንጨቶችና ድንጋዮች አንድ ምራፍ ያህል ሸሹ። አባ ጰንጠሌዎንም "ልጄ ይስሐቅ ገረምከኝ" አለ ስለዚህም ከዚያች ጊዜ ጀምሮ ገሪማ ተባለ።
❤ መልካም ተጋድሎንና የቀና አካሔዱን በፈፀመ ጊዜ ክብር ይግባውና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጠለት "ስሙን ለሚጠራና መታሰቢያው ለሚያደርግ፣ ገድሉንም ለሚጽፍና ለሚያጽፍ፣ ለሚያነበውና ለሚተረጉመው ስማቸውን በሕይወት መጽሐፍ እንደሚጽፍ ቃል ኪዳን ሰጠው ዳግመኛም "የተራበውን ላበላ፣ የተጠማውንም ላጠጣ እኔ የሕይወት እንጀራን እመግበዋለሁ የድኅነት ጽዋንም አጠጣዋለሁ" አለው። በቤተ ክርስቲያንህም በማኅሌት ያመሰገነውንና የፀለየውን እኔ የመላእክትን ምስጋና አሰማዋለሁ የተራቆተውንም ለሚያለብስ የብልህ እጅ ያልሠራው የብርሃን ግምጃን አለብሰዋለሁ ነፍሱም ከሥጋው በምትለይ ጊዜ የጨለማ መላእክት አይቀርቡትም። የብርሃን መላእክትም በዙሪያው አቆማቸዋለሁ። በስምህም ቤተ ክርስቲያን ለሠራ በሰማያት አርባ ሰባት የብርሃን ቦታዎችን እኔ እሰጠዋለ፣ ለቤተ ክርስቲያንህ መባ የሚሰጠውንም እኔ በመንግሥቴ እቀበለዋለሁ፣ ቦታህን የሚያከብረውንም እኔ በመንግሥቴ አከብረዋለሁ፣ ጠላቶች አጋንንትን ረግጦ የሚገዛበትንም እሰጠዋለሁ"።
❤ አባ ገሪማም "ይህን ታላቅ ሀብት በቸርነትህ ብዛት የሰጠኸኝ አቤቱ ስምህ ይክበር ይመስገን ግን ጌታዬ ሆይ መታሰቢያዬን ላደረገ፣ ገድሎንም ለጻፈ እስከ ስንት ትውልድ ትምርልኛለህ" አለ። መድኃኒታችንም "እስከ ዐሥራ ሁለት ትውልድ እምርዋለሁ" አለው አባ ገሪማም መድኃኒታችንን "ልጆች ባይኖሩትስ ምን ታደርግለታለህ" አለው። መድኃኒታችንም "ዐሥራ ሁለት ዕጽፍ ክብር እሰጠዋለሁ" ብሎ መለሰለት።
❤ ዳግመኛም "የሞት ጥላ እንደማያገኝህ ታላቅ የምሥራች እነግርሃለሁ" አለው ይህንንም ተናግሮ ሰላምታ ሰጥቶት በታላቅ ክብር ወደ ሰማያት ዐረገ። ቅዱስ አባ ገሪማም በልቡ ደስ ተሰኘ ወዲያውኑም ሰኔ 17 ቀን በብርሃን ሠረገላ ተነጥቆ ብሔረ ሕያዋን ገባ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም አባ ገሪማ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሰኔ 17 ስንክሳር።
@Teamihokidusan | 73 |
| 6 | Нет текста... | 67 |
| 7 | [ ስንክሳር ሰኔ - ፲፯ - ] .mp3 | 67 |
| 8 | 🕊
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡
❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖
ሰኔ ፲፯ [ 17 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
[ 🕊 ✞ አባ ገሪማ [ ይስሐቅ ] መደራ ✞ 🕊 ]
አቡነ ገሪማ የተወለዱት በ፭ [5] ኛው መቶ ክ/ዘመን ሮም ውስጥ ነው:: ወላጆቻቸው መስፍንያኖስና ሰፍንግያ እግዚአብሔርን የሚወዱ የሮም ከተማ ንጉሥና ንግሥት ነበሩ:: ልጅ በማጣታቸው እመቤታችንን ለመኑ፡፡
እመ ብርሃንም ደግ ፍሬ ሰጠቻቸው:: ስሙን ይስሐቅ ብለው አሳደጉት:: ገና በልጅነቱ አባቱ ድንገት በመሞቱ ይስሐቅ በዙፋኑ ተተክቶ ነገሠ:: ለ፯ [7] ዓመታት ሕዝቡን በፍትሕ እያስተዳደረ: መጻሕፍትንም እያጠና ኑሯል::
አንድ ቀን ግን ከግብፅ በርሃ የተላከ ደብዳቤ ደረሰው:: ላኪው አባ ዸንጠሌዎን ሲሆኑ መልዕክቱ "ምድራዊ ንግሥና ምን ያደርግልሃል? ይልቁኑስ በሰማይ ለዘለዓለም እንድትነግሥ ወደ በርሃ ና" የሚል ነበር::
ንጉሥ ይስሐቅ አላመነታም ሌሊት ተነስቶ ወደ ፈጣሪው ጸልዮ በለበሳት ልብስ ብቻ ዙፋኑን ጥሎ መነነ:: ድንገት ግን ቅዱስ ገብርኤል ደርሶ በቀኝ ክንፉ ነጥቆ ግብፅ አባ ዸንጠሌዎን በዓት ላይ አኖረው::
እርሳቸውም ተቀብለው ፍኖተ አበውን አስተምረው አመነኮሱትና ዘጠኝ ሁነው ወደ ኢትዮዽያ መጡ:: ተስዓቱ ቅዱሳን በሃገራችን ብዙ ሲሰሩ አንዱና ታላቁ አባ ይስሐቅ [ገሪማ] ናቸው:: ሰውነታቸውን በገድል ቀጥቅጠውት ቆዳና አጥንታቸው ተጣብቆ ነበር::
አንድ ቀን አባ ይስሐቅ በልቶ ቀደሰ ብለው ነግረዋቸው አባ ዸንጠሌዎን አዘኑ:: ልምከር ብለው "ልጄ ይስሐቅ የሰማውብህ ነገር አለና ሰዎችን አርቅልኝ" አሉ:: አባ ይስሐቅ ግን "ሰዎች ብቻ አይደሉም: ዛፉም እንጨቱም ገለል ይበል" ቢሉ የቤተ ክርስቲያኑ አጸድ አንድ ምዕራፍ ፰ መቶ ሜትር [800 ሜትር] ተጠራርጎ ሸሸ::
ይሕንን የተመለከቱት አባ ዸንጠሌዎን "ወልድየ ይስሐቅ ገረምከኒ [ልጄ ይስሐቅ ገረምከኝ] አሏቸው:: ከዚያ ጊዜ ጀምሮም "አቡነ_ገሪማ" ተብለው ቀሩ፡፡
አቡነ ገሪማ ወደ መደራ ሲሔዱ እነዚያ የሸሹ ዛፍና ድንጋዮች "ገሪማ ለእኛም ግሩም ነህ" እያሉ በዝማሬ ተከትለዋቸዋል::
ጻድቁ ወንጌልን: ገዳማትን ከማስፋፋት ባለፈ ብዙ ተአምራትን ሰርተዋል :-
፩. ስንዴ ጠዋት ዘርተውት በ9 ሰዓት ያፈራ ነበር "በጽባሕ
ይዘርዕ: ወበሠርክ የአርር" እንዲል::
፪. ጧት የተከሉት ወይን በ9 ሰዓት ያፈራ ነበር::
፫. አንድ ቀን ምራቃቸው ቢወድቅ ጸበል ሆኖ ዛሬም አለ::
፬. ብዕራቸው ወድቃ አብባ አፍርታለች::
፭. አንድ ቀን ድርሳን እየደረሱ ሊመሽ በመሆኑ ፀሐይን
አቁመዋታል::
ከእነዚህ ሁሉ ዘመናት በኋላ ጌታችን ተገልጦ በማይዋሽ ንጹሕ አንደበቱ ቃል ኪዳን ሰጣቸው:: "ስምሕን የጠራ: መታሰቢያህን ያደረገ: እስከ ፲፪ [12] ትውልድ እምርልሃለሁ:: አንተ ግን ሞትን አትቀምስም" ብሏቸው ተሰወረ:: ያን ጊዜ መላእክቱ በሠረገላ ጭነው እየዘመሩ ብሔረ ሕያዋን አድርሰዋቸዋል፡፡
[ 🕊 ✞ አባ ለትጹን የዋህ ✞ 🕊 ]
ስመ ጥሩ ጻድቅ አባ ለትጹን በ፬ [4] ኛው መቶ ክ/ዘመን በግብጽ የተወለዱ:
- በፍጹም ተግሣጽ ያደጉ:
- ከልጅነታቸው ጀምሮ ራሳቸውን በሕገ ወንጌል የመሩ:
- አንድ ቀን በሰሟት የወንጌል ቃል የመነኑ:
- ገዳም ገብተው በትሕትና ለዘመናት ያገለገሉ:
- በመጨረሻም ወደ ትልቅ ተራራ ወጥተው ተጋድሏቸውን
የፈጸሙ ታላቅ አባት ናቸው::
ከየዋሕነታቸው የተነሳ ኃጢአተኛ ሰው ሲያገኙ ራሳቸው ንስሃ ይገቡ ነበር:: አንዴ ግን እናቱን ፲ [10] ጊዜ በዝሙት ያረከሰ: ስትጸንስም መርዝ አጠጥቶ ጽንሱን በማሕጸኗ የገደለና በሥጋ ወደሙ ላይ የተዘባበተ ሰው ሊሞት ሲል ደረሱ::
አጋንንት ሲዖል ታች ሲጥሉትም ተመለከቱ:: ኃጢአቱ ጭንቅ ቢሆንም የእርሱን ንስሃ ሊቀበሉ ጀመሩ: ከንስሃቸው ጽናት የተነሳ ሞቱ:: ጌታችን ከሞት አስነስቶ "አትለምነኝ: አልምረውም" አላቸው::
ጻድቁ ተስፋ አልቆረጡምና ቀጠሉ:: ለ፪ [2] ኛ ጊዜ ሞቱ:: አሁንም ቀጠሉ: ፫ [3] ኛ: ፬ [4] ኛ: ፭ [5] ኛ ጊዜም ሞቱ:: በ፮ [6] ኛው ግን መፍትሔ መጣ:: ጌታችን አእላፍ መላእክትን አስከትሎ: ያችንም ኃጥእ ነፍስ ይዞ መጣ:: "ፍርዴ አይታጠፍምና ወደ ገነት አላስገባትም:: ስለ አንተ ጽድቅና የዋሕነት ደግሞ ሲዖል አልጥላትም:: ስለዚሕም እንዳልተፈጠረች ትሁን" ብሎ እፍ አለባት:: ፈጥና ወደ ትቢያነት ተቀየረች::
ጻድቁም የፈጣሪያቸውን ቸርነት አድንቀው ሰገዱ:: ከብዙ ዘመናት ተጋድሎ በኋላም በዚህች ቀን ዐረፉ::
[ 🕊 ✞ አባ ዸላሞን ፈላሲ ✞ 🕊 ]
ቤተ ክርስቲያን ካፈራቻቸው ታላላቅ ገዳማውያን አንዱ አባ ዸላሞን የአባ ለትጹን ወዳጅ ነበር:: ይሕ ቅዱስ ከአጋንንት ጋር በገጠመው ጦርነት ምክንያት ለየት ይላል:: ከ፷ [60] ዓመታት በላይ እንኳን ሳቅና ደስታ ቀና ብሎም ሰው አላየም::
በነዚሁ ዘመናት ሁሉ ቅንድቡ እስኪላጥ አልቅሷል:: በዓለም ያሉ አጋንንት ሁሉ ተሰብስበው አሰቃይተውታል:: እርሱ ግን በእግዚአብሔር ቸርነት: በወዳጁ በአባ ለትጹን ጸሎትና በትጋት አሸንፏቸው ዛሬ ዐርፏል::
ቸሩ አምላካችን ከታላላቁ ቅዱሳን ጸጋ በረከት ይክፈለን:: በምልጃቸውም ይቅር ይበለን::
🕊
[ † ሰኔ ፲፯ [ 17 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ብጹዕ አባ ገሪማ [ይስሐቅ] ዘመደራ
፪. አባ ለትጹን ዐቢይ ወየዋሕ
፫. አባ ዸላሞን ፈላሲ
፬. ቅድስት አርሴማ ጻድቅት
፭. ሰማዕታት እለ አኮራን
፮. ፯፼ ፹፻ ሰማዕታት ማኅበረ ቅዱስ ተክለሃ ይማኖት
[ † ወርኃዊ በዓላት ]
፩ ፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ ቀዳሜ ሰማዕት
፪ ፡ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ ዘቆጵሮስ
፫ ፡ ቅዱሳን መክሲሞስ ወደማቴዎስ
፬ ፡ ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ
" እግዚአብሔር ፍርድን ይወድዳልና::ቅዱሳኑንም አይጥላቸውምና:: ለዘለዓለምም ይጠብቃቸዋል. . . ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ:: በእርስዋም ለዘላለም ይኖራሉ::የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል:: አንደበቱም ፍርድን ይናገራል::የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው:: በእርምጃውም አይሰናከልም:: " [መዝ. ፴፮፥፳፰-፴፩] (36:28-31)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖 | 85 |
| 9 | 🩵 † 🩵
❝ ሳ ይ ገ ባ ው ይ ወ ጣ ል ! ❞
💛 💛
❝ ሕይወት የሚገኝበትን ትምህርት የማይታገሡበት ዘመን ይመጣልና ፤ ነገር ግን ጆሮቻቸውን የሚያሳክክ ስለ ሆነ ፥ እንደ ገዛ ምኞታቸው ለራሳቸው አስተማሪዎችን ያከማቻሉ። ❞ [ ፪ጢሞቲ.፬፥፫ ]
[ ረዳት ፕሮፌሰር መ/ር ግርማ ባቱ ]
🕊
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊 | 128 |
| 10 | Нет текста... | 135 |
| 11 | [ በእግዚአብሔር ላይ ታመን ] .mp3 | 122 |
| 12 | 🕊 💖 🕊
🩵 [ ምክረ ቅዱሳን ] 🩵
════════════════
▷ " በእግዚአብሔር ላይ መታመን ! "
[ 💖 በሊቀ ዲያቆናት ሀቢብ ጊዮርጊስ 💖 ]
▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬
❝ በእግዚአብሔር ታመንሁ ፤ ነፍሴን። እንደ ወፍ ወደ ተራሮች ተቅበዝበዢ እንዴት ትሉአታላችሁ? ❞ [ መዝ.፲፩፥፩ ]
❝ በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን ፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ ፤ በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ ፥ እርሱም ጎዳናህን ያቀናልሃል። ❞ [ ምሳ.፫፥፭ ]
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊 | 153 |
| 13 | Нет текста... | 343 |
| 14 | [ ስንክሳር ሰኔ - ፲፮ - ] .mp3 | 328 |
| 15 | 🕊
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ †
❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖
❖ ሰኔ ፲፮ [ 16 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
🕊 † ቅዱስ አቡናፍር ገዳማዊ † 🕊
ጻድቁ ተወልዶ ያደገው በ፭ [5] ኛው መቶ ክ/ዘመን በምድረ ግብፅ ነው:: ወቅቱ ሥርዓተ መነኮሳት የሚጠበቅበት:አበው ባሕታውያን እንደ ሰማይ ከዋክብት በዝተው የደመቁበት ነበር:: ታላቁ አቡናፍርም ከክርስቲያን ወላጆቹ ተወልዶ: በሥርዓት አድጎ: መጻሕፍትንም ተምሮ ገና በወጣትነቱ መንኗል::
ሥርዓተ መነኮሳትን ከአባ ኤስድሮስ ታላቁ አጥንቶ ገዳሙንና መምሕሩን እየረዳ ለብዙ ዓመታት በጾምና በጸሎት ኑሯል:: መነኮሳቱ ስለ ትሕትናውና ስለ ታዛዥነቱ ፈጽመው ያከብሩት ነበር::
ከዕለታት በአንዱ ቀን አረጋውያን መነኮሳት ጭው ባለ በርሃ ስለሚኖሩ ባሕታውያን ሲጨዋወቱ: ሲያደንቁዋቸውም ሰማ:: እርሱ በዛ ወቅት ባሕታውያን በበርሃ መኖራቸውን አያውቅም ነበርና ሒዶ መምሕሩን አባ ኤስድሮስን ጠየቃቸው:: እርሳቸውም "አዎ ልጄ! ከዚሕ በጣም ርቅው: ንጽሕናቸውን ጠብቀው: ከሰውና ከኃጢአት ተይለው የሚኖሩ ገዳማውያን አሉ" አሉት::
ቅዱስ አቡናፍር "በዚሕ ካሉት መነኮሳትና በበርሃ ካሉት ማን ይበልጣል?" ቢላቸው "እነርሱ በጣም ይበልጣሉ:: ዓለም እንኩዋ ከነ ክብሯ የእግራቸውን ሰኮና አታህልም" አሉት:: ይሕንን የሰማው ቅዱስ አባ አቡናፍር ጊዜ አላጠፋም::
ከመምሕሩ ቡራኬ ተቀብሎ ወደ በርሃ ሔደ:: ለብዙ ቀናት ከተጉዋዘ በኋላ አንድ ባሕታዊ አግኝቶ አብሯቸው ተቀመጠ:: ከእርሳቸው ዘንድም ሥርዓተ ባሕታውያንን ተምሮ እንደገና ወደ ዋናው በርሃ ጉዞውን ቀጠለ::
ከብዙ ቀናት መንገድ በኋላም አንድ ሠፊ ሜዳ ላይ ደረሰ:: አካባቢው የውሃ ጠብታ የማይገኝበት: ይቅርና መጠለያ ዛፍ የሣር ዘር እንኩዋ የሌለበት ወይም በልሳነ አበው "ዋዕየ ፀሐይ የጸናበት: ልምላሜ ሣዕር የሌለበት: ነቅዐ ማይ የማይገኝበት" ቦታ ነበር:: በዚህ ቦታ ይቅርና የሰው ልጅ አራዊትም አይኖሩበትም::
ለአባ አቡናፍር ግን ተመራጭ ቦታ ነበር:: ቅዱሳኑን ይሕ አያሳስባቸውም:: ምክንያቱም ለእነርሱ ምግባቸውም: ልብሳቸውም ፍቅረ ክርስቶስ ነውና:: አባ አቡናፍር ወደ ፈጣሪ ጸለዩ:: በእግዚአብሔር ቸርነት ከጎናቸው አንዲት ዘንባባ [በቀልት] በቀለች:: ከእግራቸው ሥርም ጽሩይ ማይ [ንጹሕ ምንጭ] ፈለቀች::
ጻድቁ ተጋድሏቸውን ቀጠሉ:: ዓመታት አለፉ:: ልብሳቸውን ፀሐይና ብርድ ጨርሶት ቅጠል ለበሱ:: በዚያ ቦታም የሰው ዘርን ሳያዩ ለ፷ [60] ዓመታት በተጋድሎ ኖሩ:: የሚያርፉበት ጊዜ ሲደርስ እግዚአብሔር አባ በፍኑትዮስን [የባሕታውያንን ዜና የጻፈ አባት ነው] ላከላቸው::
ቃለ እግዚአብሔርን እየተጨዋወቱ ሳለ የአባ አቡናፍር አካሉ ተለወጠ:: እንደ እሳትም ነደደ:: አባ በፍኑትዮስም ደነገጠ:: ታላቁ ገዳማዊ ግን እጆቻቸውን ዘርግተው ጸለዩ: ሰገዱና አማተቡ:: ነፍሳቸውም ከሥጋቸው በፍቅር ተለየች:: ቅዱሳን መላዕክትም በዝማሬና በማኅሌት አሳረጉዋት:: የሚገርመው ደግሞ አባ በፍኑትዮስ ይሕን ሲያይ ቆይቶ ዘወር ቢል ዛፏ ወድቃለች: ቅርንጯም ደርቃለች::
ዳግመኛ ይህች ዕለት የቅዱሳን አበው ባሕታውያን መታሠቢያ ናት::
ከሰው [ ከዓለም ] ርቀው: ንጽሕ ጠብቀው: ዕጸበ ገዳሙን: ግርማ አራዊቱን: ጸብዐ አጋንንትን ታግሠው የኖሩ: ስማቸውን የምናውቀውንም ሆነ የማናውቃቸውን እንድናከብራቸው ቤተ-ክርስቲያን ሥርዓትና በዓል ሠርታለች::
አምላካችን ከአበው ባሕታውያን ጸጋ በረከት ይክፈለን::
🕊
[ † ሰኔ ፲፮ [ 16 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. አባ አቡናፍር ገዳማዊ [ስም አጠራሩ የከበረ:
ሽምግልናው ያማረ አባት]
፪. አበው ቅዱሳን ባሕታውያን [ ዛሬ የሁሉም ቅዱሳን ባሕታውያን [በተለይም የስውራኑ] ዓመታዊ በዓል ነው::
- ከሰው: ከዓለምና ከኃጢአት ርቀው
- ንጽሕ ጠብቀው
- ዕጸበ ገዳሙን
- ድምጸ አራዊቱን
- ግርማ ሌሊቱን
- የሌሊቱን ቁር
- የመዓልቱን ሐሩር
- ረሐቡን: ጽሙን: መራቆቱን . . . ሁሉ
ስለ ፍቅረ-ክርስቶስ ሲሉ ታግሠውታልና::
"ዛሬም በየበርሃው የወደቁ: ስለ ዓለም ምሕረትን
የሚማጸኑ አሉ::"
አምላካቸው በረከታቸውን ያድለን።
፫. የእግዚአብሔር መልአክ ለዮሴፍ በሕልም ከግብጽ እንዲመለስ የነገረበት [ተዝካረ ሚጠታ ለእግዝእትነ ማርያም]
፬. አፄ ይኩኖ አምላክ [ንጉሠ ኢትዮዽያ]
[ † ወርኃዊ በዓላት ]
፩፡ ኪዳነ ምሕረት ማርያም
፪፡ ቅድስት ኤልሳቤጥ
፫፡ አባ ዳንኤል ገዳማዊ
፬፡ ቅዱስ አኖሬዎስ ንጉሠ ሮሜ
፭፡ አባ ዮሐንስ ወንጌሉ ዘወርቅ
፮፡ ቅዱስ ሐርቤ ንጉሠ ኢትዮጵያ
" . . . ሌሎችም መዘበቻ በመሆንና በመገረፍ: ከዚሕም በላይ በእሥራትና በወኅኒ ተፈተኑ . . . ሁሉን እያጡ መከራን እየተቀበሉ: እየተጨነቁ: የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ:: ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ: በዋሻና በምድር ጉድጉዋድ ተቅበዘበዙ:: ዕብ.፲፩፥፴፮] (11:36) "
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖 | 303 |
| 16 | Нет текста... | 250 |
| 17 | [ + ማር ሚና + ] .mp3 | 226 |
| 18 | 🩵 † 🩵
[ 🕊 ማር ሚና 🕊 ]
🕊 💛 🕊
🕊 † ቅዱስ ሚናስ ምዕመን ሰማዕት † 🕊
❝ የክርስቶስ ምርጥ ጭፍራ ከገንዘብ ይልቅ ጽድቅን የመረጠ ፤ እንደ ምሳሌው እንደ ጨረቃ ለደመቀና እንደ ፀሐይም ብሩህ ለኾ ለሚናስ ሰላምታ ይገባል።
መካን ሳለች ጸሎትን እየጸለየች ሳለች ከእመቤታችን ማርያም ሥዕል አሜን የሚል ቃልን ሰምታ የተሸከመችኽ ማሕፀን ሚናስ ብላ የሰየመችኽ የመድኅን ክርስቶስ ምስክር ፤ የጦር መኮንን ለኾንኽ ላንተ ሰላምታ ይገባል።
የምድር የኾነ ክብርን ንቀኽ የሰማይ ክብርን የመረጥኽ የክርስቶስ ጭፍራው የኾንኽ ሚናስ አንተ ንኡድ ክቡር ነኽ ፣ በሰማይ አዳራሽ የተመረጠው ሚናስ ፤ ፊቱም እንደ ፀሓይ ብሩህ ነው ፤ ብዙ በኾነ ሰላም እግዚአብሔር ከፍ ከፍ አደረገው። ❞ [ ተአምኆ ቅዱሳን ]
🕊
❝ ጻድቃን ስለአንተ ታመሙ [ መከራን ተቀበሉ ] መከራቸውም ደስታ ሆነላቸው ፣ ክብር ይገባቸዋል ፣ በተጋድሎአቸው ሰማዕታት ፣ በትዕግስታቸውም መንግሥተ ሰማያትን ወረሱ። ❞ [ ቅዱስ ያሬድ ]
💛
ማር ቅዱስ ሚናስ በዚኽች ዕለት ኅዳር ፲፭ [15] ቀን ዓመታዊ የዕረፍት በዓሉ ሲሆን ሰኔ ፲፭ [15] ደግሞ ታላላቅ ተአምራት ያደረገበትና ቅዳሴ ቤቱ የተከበረበት ዓመታዊ በዓሉ ነው፡፡
የቅዱስ ሚናስ ምልጃና ጸሎቱ ከዘለዓለም እሳት ያድነን:: ጸጋ በረከቱ ይክፈለን::
════════════════
†††
✟ 𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y ✟
🕊 💖 🕊 | 236 |
| 19 | Нет текста... | 209 |
| 20 | [ + መንፈሳዊ ጥንካሬ + ] .mp3 | 218 |
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
