ገድለ ቅዱሳን
Открыть в Telegram
@Gedelat ለተለያዩ አስተያየት እና ጥቆማ ማድረስ ከፈለጉ በአድራሻችን ቢያደርሱን ይደርሰናል፡፡ በአድራሻችን ✍ @Mnfesawi_bot
Больше6 496
Подписчики
+224 часа
+37 дней
-230 день
Загрузка данных...
Похожие каналы
Облако тегов
Нет данных
Возникли проблемы? Пожалуйста, обновите страницу или обратитесь к нашему support-менеджеру .
Входящие и исходящие упоминания
---
---
---
---
---
---
Привлечение подписчиков
июнь '26
июнь '26
+94
в 1 каналах
май '26
+63
в 2 каналах
Get PRO
апрель '26
+77
в 2 каналах
Get PRO
март '26
+58
в 1 каналах
Get PRO
февраль '26
+44
в 1 каналах
Get PRO
январь '26
+59
в 1 каналах
Get PRO
декабрь '25
+98
в 2 каналах
Get PRO
ноябрь '25
+91
в 1 каналах
Get PRO
октябрь '25
+77
в 1 каналах
Get PRO
сентябрь '25
+56
в 1 каналах
Get PRO
август '25
+103
в 1 каналах
Get PRO
июль '25
+85
в 1 каналах
Get PRO
июнь '25
+99
в 1 каналах
Get PRO
май '25
+96
в 1 каналах
Get PRO
апрель '25
+96
в 2 каналах
Get PRO
март '25
+140
в 1 каналах
Get PRO
февраль '25
+107
в 1 каналах
Get PRO
январь '25
+190
в 1 каналах
Get PRO
декабрь '24
+198
в 2 каналах
Get PRO
ноябрь '24
+66
в 1 каналах
Get PRO
октябрь '24
+109
в 3 каналах
Get PRO
сентябрь '24
+60
в 1 каналах
Get PRO
август '24
+89
в 1 каналах
Get PRO
июль '24
+129
в 2 каналах
Get PRO
июнь '24
+107
в 2 каналах
Get PRO
май '24
+109
в 1 каналах
Get PRO
апрель '24
+120
в 2 каналах
Get PRO
март '24
+94
в 2 каналах
Get PRO
февраль '24
+74
в 2 каналах
Get PRO
январь '24
+102
в 2 каналах
Get PRO
декабрь '23
+116
в 3 каналах
Get PRO
ноябрь '23
+81
в 1 каналах
Get PRO
октябрь '23
+98
в 7 каналах
Get PRO
сентябрь '23
+79
в 0 каналах
Get PRO
август '23
+73
в 0 каналах
Get PRO
июль '23
+94
в 0 каналах
Get PRO
июнь '23
+64
в 0 каналах
Get PRO
май '23
+75
в 0 каналах
Get PRO
апрель '23
+78
в 0 каналах
Get PRO
март '23
+84
в 0 каналах
Get PRO
февраль '23
+54
в 0 каналах
Get PRO
январь '23
+83
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '22
+62
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '22
+70
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '22
+54
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '22
+61
в 0 каналах
Get PRO
август '22
+48
в 0 каналах
Get PRO
июль '22
+73
в 0 каналах
Get PRO
июнь '22
+47
в 0 каналах
Get PRO
май '22
+61
в 0 каналах
Get PRO
апрель '22
+75
в 0 каналах
Get PRO
март '22
+91
в 0 каналах
Get PRO
февраль '22
+57
в 0 каналах
Get PRO
январь '22
+99
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '21
+55
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '21
+64
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '21
+141
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '21
+174
в 0 каналах
Get PRO
август '21
+223
в 0 каналах
Get PRO
июль '21
+245
в 0 каналах
Get PRO
июнь '21
+205
в 0 каналах
Get PRO
май '21
+161
в 0 каналах
Get PRO
апрель '21
+520
в 0 каналах
Get PRO
март '21
+395
в 0 каналах
Get PRO
февраль '21
+333
в 0 каналах
Get PRO
январь '21
+517
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '20
+9 090
в 0 каналах
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 29 июня | +5 | |||
| 28 июня | +3 | |||
| 27 июня | +3 | |||
| 26 июня | +3 | |||
| 25 июня | +7 | |||
| 24 июня | +1 | |||
| 23 июня | +1 | |||
| 22 июня | +2 | |||
| 21 июня | +7 | |||
| 20 июня | +2 | |||
| 19 июня | +3 | |||
| 18 июня | +1 | |||
| 17 июня | +4 | |||
| 16 июня | +3 | |||
| 15 июня | +3 | |||
| 14 июня | +5 | |||
| 13 июня | +7 | |||
| 12 июня | +2 | |||
| 11 июня | +4 | |||
| 10 июня | +5 | |||
| 09 июня | +2 | |||
| 08 июня | +1 | |||
| 07 июня | +7 | |||
| 06 июня | +1 | |||
| 05 июня | +1 | |||
| 04 июня | +3 | |||
| 03 июня | +7 | |||
| 02 июня | 0 | |||
| 01 июня | +1 |
Посты канала
| 2 | ❤ #ታላቅ_የኦንላይ_ገቢ_ማሰባሰቢያ ለገበዘ ኢትዮጵያ #ለቅዱስ_ጊዮርጊስ (#ለአራዳ) ቤተ ክርስቲያን። #ሼር_ሼር_ሼር በማድረግ ለሌሎች እናዳርስ።
❤ "#ታሪክን_ለትውልድ_የማሻገር_ተራው_የኔ_ነው"
#ከሰኔ_26-28 ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ
ዓለም አቀፍ ገቢ ማሰባሰብያ ቀጥታ ሥርጭት ላይ ሁላችንም በሀገር ውስጥም በባሕር ማዶ ያላን ኢትዮጵያዊ ሕዝብ በሙሉ ለገበዘ ኢትዮጵያና ባለ ውለታ ለፍጡነ ረትኤት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን እንረብና የህንፃ እድሳቱን ለፍጻሜ እናድርሰው።
"መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን (#አራዳ_ቅዱስ_ጊዮርጊስ)።
✝️ ለመርዳት ከበረከቱ ለመሳተፍ፦ #በሁሉም_ባንኮች_አጭን_የአካውንት_ቁጥር_1423_ይጠቀሙ። | 62 |
| 3 | Нет текста... | 45 |
| 4 | ነበር። ወደ ንጉሡ ከተማም በደረሱ ጊዜ ወደ ንጉሡ ከመግባታቸው በፊት በውኃ ያጥቧቸውና አዳዲስ ልብሶችን ያለብሷቸው ጀመሩ እንዲሁም ለሁሉ አደረጉ ቅዱስ አባ ኖብ ግን አልታጠበም ልብሱንም አልለወጠም።
❤ ወደ ንጉሡም በገቡ ጊዜ ከእነርሱ ቡራኬ ተቀበለ ቁስላቸውንም ሳመ እጅግም አከበራቸው ብዙ ገንዘብም ሰጣቸው እነርሱ ግን ለቤተ ክርስቲያን ከሚሆን ንዋየ ቅዱሳት በቀር ምንም ምን አልተቀበሉም ከዚህም በኋላ ሰላምታ ሰጥቶ ወደየአገራቸው በሰላም አሰናበታቸው። አባ ኖብም ወደ ቦታው ተመልሶ ዐረፈና ወደ ወደደው ክርስቶስ ሔደ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ኖብ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሰኔ 23 ስንክሳር።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "እግዚኦ ኵነኔከ ሀቦ ለንጉሥ። ወጽድቀከኒ ለወልደ ንጉሥ። ከመ ይኰንኖሙ ለሕዝብከ በጽድቅ"። መዝ 71፥1-2። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 12፥38-42።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "በጽሑ መላእክት ወቦሙ መዘምራን። ማዕከለ ደናግል ዘባጥያተ ከበሮ። በማኅበር ባርክዎ ለእግዚአብሔር"። መዝ 67፥25-26። የሚነበበው መልዕክታት ሮሜ 13፥1-11፣ 1ኛ ጴጥ 2፥13-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 7፥44-54። የሚነበበው ወንጌል ማቴ11፥12-30 ወይም ማቴ12፥38-43። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታች ማርያም ወይም የወልደ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቅዳሴ ነው። መልካም የጾም ጊዜና በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።
@Teamihokidusan | 42 |
| 5 | አጠባ ዘንድ በጧት በነቃሁ ጊዜም ያንን የሞተ ልጅ አገኘሁ በነጋም ጊዜ አየሁት እነሆ የወለድሁት ልጄ አይደለም አለች። ያቺ ሁለተኛዋ ሴትም አይደለም ይህ ደኅነኛው የኔ ልጅ ነው እንጂ ያንቺ ልጅ አይደለም ያንቺስ የሞተው ነው አለች። በንጉሡም ፊት እንዲህ ተባባሉ።
❤ ንጉሡም "ሰይፍን አምጡ ደኅነኛውንም ልጅ ከሁለት ቆርጣችሁ እኵሌታውን ለዚች እኵሌታውን ለዚያች ስጡ" አለ። ስለ ልጅዋ ማሕፀኗ ታውኳልና ልጅዋ ደኅና የሆነ ያቺ ሴት መልሳ "ንጉሡን ጌታዬ አይደለም መግደልስ አትግደሉት ደኅነኛውን ልጅ ለሷ ስጧት" አለችው ያቺ ሴት ግን "አካፍሉን እንጂ ለእኔም ለእሷም አይሁን" አለች። ንጉሡም "መግደልስ አትግደሉት እሱን ለእሷ ስጧት ላለችው ለዚች ሴት ደኅነኛውን ሕፃን ስጧት እርስዋ እናቱ ናትና" አለ። እስራኤልም ሁሉ ንጉሡ የፈረደውን ይህን ፍርድ ሰምተው ቅን ፍርድን ይፈርድ ዘንድ የእግዚአብሔር ጥበቡ በሱ ላይ እንዳለ አይተዋልና በንጉሡ ፊት ፈሩ።
❤ ከዚህም በኋላ የእስራኤል ልጆች ከግብጽ ከወጡ አራት መቶ ሰማንያ አራት ዘመን በሆነ ጊዜ ሰሎሞን በእስራኤል ላይ በነገሠ በአራተኛው ዓመት በሁለተኛው ወር የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ሊያንፅ ጀመረ። በዐሥራ አንደኛውም ዘመነ መንግሥቱ ወሩ ባዕድ በሚባል በስምንተኛው ወር ቤቱንና ሥርዓቱን ሁሉ ፈጸመ በሰባት ዓመትም ውስጥ ሠራው የራሱንም ቤት በዐሥራ ሦስት ዓመት ሠርቶ ጨረሰ። ከዚህ በኋላ ሰሎሞን የእግዚአብሔርን ቤትና የራሱን ቤት በሃያ ዘመን ሠርቶ በጨረሰ ጊዜ የእግዚአብሔርን ታቦተ ሕግ ከዳዊት ከተማ ከጽዮን ያመጣት ዘንድ ያን ጊዜ የእስራኤልን ሽማግሌዎችና የነገድ አለቆች የአባቶቻቸውንም ቤት አለቆች ሁሉ በኢየሩሳሌም ሰበሰባቸው።
❤ የእስራኤልም ሰዎች ሁሉ ወደ ንጉሡ ወደ ሰሎሞን በሰባተኛው ወር በጥቅምት ተሰበሰቡ። የእስራኤልም ሽማግሌዎች ሁሉ መጡ ካህናቱም ታቦትዋንና የምስክሩን ድንኳን በምስክሩ ድንኳን ውስጥ ያለ ንዋየ ቅድሳቱንም ሁሉ ተሸከሙ። ንጉሡና እስራኤል ሁሉ በታቦትዋ ፊት ሥፍር ቍጥር የሌላቸው በጎችና ላሞችን ይሠዉ ነበር። ካህናቱም ታቦቷን ከኪሩቤል ክንፎች በታች በቤቱ ውስጥ ወዳለው ወደ ቅድስተ ቅዱሳን ቦታዋ አገቧት። ኪሩቤል በታቦትዋ ቦታ ላይ ክንፋቸውን ጋርደዋልና ኪሩቤልም በስተላይ በኩል በቅድስተ ቅዱሳን ላይ ታቦትዋን ጋርደዋት ነበር። ከቅድስተ ቅዱሳንም ጋራ የተያያዙ ነበሩ። ቅዱሳን ኪሩቤል ከፍ ብለው ከቅድስተ ቅዱሳኑ አንጻር ላይ ሁነው ያያሉ በውጭ ግን አይታይም ነበር። ከግብጽ አገር በወጡ ጊዜ እግዚአብሔር ከእስራኤል ልጆች ጋራ ቃል ኪዳን ከገባባቸው ሙሴም በዚያ በኮሬብ ከአኖራቸው ከሁለቱ ጽላቶች በቀር በታቦቱ ውስጥ ሌላ አልነበረም።
❤ ከዚህ በኋላ ካህናቱ ከቤተ መቅደስ በወጡ ጊዜ ቤተ መቅደሱን ሁሉ ብርሃን መላው። የእግዚአብሔር ብርሃን በማደሪያው ቤተ መቅደስ መልቷልና ከብርሃኑ መገለጥ የተነሣ ካህናቱ ሥራቸውን መሥራትና ከፊቱ መቆም ተሳናቸው። ያን ጊዜ ሰሎሞን "እግዚአብሔር በደመና ውስጥ እኖራለሁ" ብሏል። "እኔም ለዘላለም የምትኖርበት ማደሪያህ ቤተ መቅደስን በእውነት ሠራሁልህ" አለ። ንጉሡም ፊቱን መልሶ የእስራኤልን ጉባኤ ሁሉ መረቃቸው ወደ እግዚአብሔርም ረዥም ጸሎትን ጸለየ። ሰሎሞንም ይህን ሁሉ ልመና ወደ እግዚአብሔር ለምኖ በጨረሰ ጊዜ በጉልበቱ ተንበርክኮ ከሰገደበት እጆቹንም ከዘረጋበት ከመሠዊያው ፊት ተነሣ። ቆሞም የእስራኤልን ማኅበር "እንደተናገረው ሁሉ ለወገኖቹ ለእስራኤል ዕረፍትን የሰጣቸው እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን" ብሎ በታላቅ ቃል መረቃቸው። ከዚህ በኋላ ንጉሡና የእስራኤል ልጆች ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት መሥዋዕትን ሠዉ።
❤ ንጉሡ ሰሎሞንም ለእግዚአብሔር ስለ ሰላም መሥዋዕት የሠዋቸው ሃያ ሁለት ሽህ ላሞችና አንድ መቶ ሃያ ሽህ በጎች ናቸው ንጉሡ ሰሎሞንና የእስራኤል ልጆች ሁሉ ያንጊዜ ለእግዚአብሔር ማደሪያ ለቤተ መቅደስ ቅዳሴ ቤት አደረጉ። ቀድሞ በገባዖን እንደታየው ዳግመኛ እግዚአብሔር ለሰሎሞን ታየው "በፊቴ የለመንኸኝ ልመናህንና ጸሎትህን ሰማሁ። እንደ ልመናህም ሁሉ አደረግሁልህ ስሜ በዚያ ለዘላለሙ ጸንቶ ይኖር ዘንድ የሠራኸውንም ቤተ መቅደስ አከበርሁት ልቡናዬም ዐይኖቼም በዘመኑ ሁሉ በዚያ ጸንተው ይኖራሉ" አለው። ሰሎሞንም አርባ ዘመን ነገሠ ከመንገሡም በፊት ዐሥራ ሁለት ዓመት ኖረ መላ ዕድሜውም ሃምሳ ሁለት ዓመት ነበር በሰላም አረፈ።
ይህም ጥበብ የተሰጠው ንጉሥ ሰሎሞን ጥቅም ያላቸው ብዙዎች መጻሕፍትን ደርሶአል። እሊህም ትንቢትና ትምህርት ያለባቸው ምሳሌዎችና መኃልዮች ናቸው።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #ቅዱስ_አባ_ኖብ፦ ይህም ቅዱስ መነኰስ በላይኛው ግብጽ ከሚገኙ ገዳማት በአንዱ ገዳም ውስጥ የሚጋደል ጽሙድ ነበር። ዲዮቅልጥያኖስም ብዙዎች ሰማዕታትን ሊአሠቃይና ደማቸውን ሊያፈስስ በጀመረ ጊዜ በአንዲት ቀን ሰማንያ ሰማዕታትን አቅርቦ ደማቸውን አፈሰሰ። በዚያን ጊዜ አባ ኖብን አስታወሱት የእንዴናው ገዥ ወደሆነው ወደ አርያኖስ አቀረቡት። እርሱም "ለአማልክት ዕጠን ሠዋ ይህንንም የምንኵስና ልብስ ከላይህ አውጥተህ ጣል" አለው። አባ ኖብም "ይህ ሥራ ከቶ ከእኔ ዘንድ አይደረግም የክብር ባለቤት ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስንም አልተውም የረከሱ ጣዖታትንም አላመልክም" አለ። መኰንኑም በየራሱ በሆነ ሥቃይ እጅግ አሠቃየው ያም አባ ኖብ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ኃይል ታግሦ ተቀበለ።
❤ ከዚህም በኋላ ወደ አምስቱ አህጉር ሰደደው በዚያም በጉድጓድ ውስጥ ጣሉት በውስጡም ጌታችን ከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስን አጥፍቶ ደግ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስን እስከሾመው ድረስ ሰባት ዓመት ኖረ። ቈስጠንጢኖስም በነገሠ ጊዜ ክብር ይግባውና ስለ ክርስቶስ የታሠሩትን ሁሉ ፈትተው ወደርሱ እንዲአቀርቧቸውና ከእርሳቸው እንዲባረክ ወደ አገሮች ሁሉ ደብዳቤዎችን ላከ። ለመልእክተኞችም እንዲህ አላቸው "ሁሉንም ወደ እኔ ማድረስ ካልተቻላችሁ እጆቻቸውን በራሴ ላይ ጭነው ይባርኩኝ ዘንድ ክብር ያላቸውን ታላላቆችንና መምህራኑን አምጡአቸው"።
ከእነርሱም ውስጥ የታወቁ አህናህ ከተባለ አገር አባ ዘካርያስ ከፍዩም መክሲሞስ ከሀገረ ድኂን አጋብዮስ ከሀገረ በላኦስ አባ ኖብ ናቸው የንጉሥ መልእክተኞችም በየአገሮች ሁሉ እየዞሩ የታሠሩ ቅዱሳንን ከእሥር ያወጡአቸው ነበር እነርሱም ደስ ይላቸው ነበር የተመሰገነ እግዚአብሔርንም ያመሰግኑት ነበር ይዘምሩለትም ነበር።
❤ የንጉሥ መልእክተኛም አባ ኖብን ከአምስቱ አገሮች ፈልጎ የአገሩ አንጻር ወደ ሆነች ወደ ሀገረ በሰላ ወሰደው። በዚያም የብረት ልብስ ለብሶ ተቀምጦ ነበር የንጉሡ መልእከተኛም አገኘውና ከእርሱ ጋራ ወሰደው ወደ እንዴናውም እስከ ደረሱ በመርከብ ተሳፈሩ ክርስቲያኖችም ተሰበሰቡ ከውስጣቸውም አራት ኤጲስቆጶሳት ነበሩ አባ ኖብንም ያለ ውዴታው ቅስና ሾሙትና የቊርባን ቅዳሴን ቀደሰ።
❤ በቅዳሴውም ፍጻሜ ቅድሳት ለቅዱሳን ብሎ ጮኸ ይህም ማለት ንጹሕና ቅዱስ የሆነ ከሥጋው ከደሙ ይቀበል ማለት ነው በዚያን ጊዜም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በመሠዊያው ላይ ተቀምጦ ንስሐ የገቡትን ኃጢአታቸውን ይቅር ሲላቸው አየው ሥጋውንና ደሙንም ከአቀበላቸው በኋላ ወደ ንጉሡ ለመሔድ ተዘጋጁ ቍጥራቸውም ሰባ ሁለት ነበር ሠላሳ ሰባት ሠረገላም አዘጋጅተውላቸው እየአንዳንዳቸው በሠረገላው ተቀመጡ። በአለፉም ጊዜ የደናግል ገዳማት ካሉበት ደረሱ ደናግሎም ወጥተው ተቀበሏቸው ቊጥራቸው ሰባት መቶ ነበር ከእነርሱ ጋራም እስከሚሰበሰቡ በቅዱሳን ፊት ይዘምሩ | 27 |
| 6 | ❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ❤
❤ #ሰኔ ፳፫ (23) ቀን።
❤ እንኳን #ለንጉሥ_ለቅዱስ_ዳዊት_ልጅ ለጥበበኛው ንጉሥ #ለቅዱስ_ሰሎሞን_ለዕረፍቱ መታሰቢያ ቀን በዓል፣ በክብር ባለቤት #በኢየሱስ_ክርስቶስ ለታመነ #ለአባ_ኖብ ለዕረፍት መታሰቢያ በዓልና ለሊቀ ሰማዕታት ለቅዱስ ጊዮርጊስ ለወራዊ በዓል መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከቅዱሳን ሰማዕታት #ከመርቆሬዎስ_ከቶማስና_ፊልጶስ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከት ያሳትፈን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የልበ_አምላክ_የቅዱስ_ዳዊት_ልጅ_ንጉሥ_ሰሎሞን፦ የዚህ የሰሎሞንም እናት ስም ቤርሳቤህ ነው ዳዊትም ሕግ ተላልፎ ከእርሷ ጋራ ስለ መበደሉ ባሏንም ስለ ማስገደሉ ጌታ በገሠጸው ጊዜ ንስሓ ገብቶ መሪር ልቅሶን አለቀሰ ጌታም ንጹሕ ስለሆነ ንስሓው ይቅር አለው። ከዚህም በኋላ በእግዚአብሔር ፈቃድ እርሷን አገባትና ሰሎሞንን ወለደው ንጉሥ ዳዊትም ከእርሱ በኋላ ልጅዋ ሰሎሞን እንዲነግሥና በዙፋኑ ላይ እንዲቀመጥ ቃል ገባለት።
❤ እንዲህም ሆነ ሰሎሞን ዐሥራ ሁለት ዓመት በሆነው ጊዜ አዶንያስ እነግሣለሁ ብሎ ተነሣ ምክሩም ሁሉ ከሶርህያ ልጅ ከኢዮአብና ከካህኑ አብያታር ጋር ሆነ። እርሱም አዶንያስን ተከትለው ሰደዱት። አዶንያስም በሮጌል ምድር ምንጭ አጠገብ ባለ በኤልቲ ዘዘኤልቲ ላይ ፍየሎችን በጎችንና ላሞችን አርዶ የንጉሥ አሽከሮች የሆኑ የይሁዳ አርበኞችን ሁሉና የንጉሡን ልጆች ወንድሞቹን ሁሉ ጠራ።
❤ ከዚህም በኋላ አዶንያስ ይህን እንዳደረገ ለቤርሳቤህ በነገሩዋት ጊዜ ወደ ንጉሥ አዳራሽ ውስጥ ገብታ ለንጉሡ ሰገደች ንጉሥ ዳዊትም "ምን ሆነሽ" አላት። "ጌታዬ ንጉሥ ሆይ ልጅሽ ሰሎሞን ከእኔ በኋላ ይነግሣል በዙፋኔም ላይ ይቀመጣል ብለህ ለእኔ ለባርያህ በፈጣሪህ በእግዚአብሔር ስም አንተ ማልክልኝ እነሆ ዛሬ አዶንያስ ነገሠ ጌታዬ ንጉሥ ሆይ አንተ ግን አላወቅህም" አለችው። ከንጉሥም ጋራ ገና ስትነጋገር ነቢዩ ናታን መጣ ለንጉሡም "ናታን መጣ" ብለው ነገሩት። ወደ ንጉሡም ገባ በምድር ላይም በግምባሩ ተደፍቶ ሰገደ። ነቢዩ ናታንም "ከእኔ ቀጥሎ አዶንያስ ይንገሥ በዙፋኔም ላይ ይቀመጥ ያልክ አንተ ነህን? ዛሬ ወርዶ በጎችንና ብዙ ፍየሎችን አርዶ የሠራዊቱ አለቆችንና የንጉሥ አሽከሮችን ሁሉ ካህኑ አብያታርንም ጠርቷልና በፊቱም ይበላሉ ይጠጣሉ አንዶንያስ ሽህ ዓመት ያንግሥህ ይሉታል" አለው።
❤ ዳዊትም መልሶ "ቤርሳቤህን ጥርዋት" አለና ጠሩዋት ገብታም በንጉሡ ፊት ቆመች። "በእግዚአብሔር ፊት እንደማልኩልሽ አሁንም በዚች ቀን እንደዚሁ እንዳደርግ ሰውነቴን ከመከራዬ ሁሉ ያዳናት የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ሕያው ነው" ብሎ ማለ። በቤርሳቤህም አንገቷን ደፍታ በግምባርዋ በመሬት ወድቃ ለንጉሡ ሰገደች "ጌታዬ ንጉሥ ዳዊት ለዘላለም ኑር" አለች።
❤ ንጉሥ ዳዊትም "የዮዳሄ ልጅ ብንያስና ካህኑ ሳዶቅን ነቢዩ ናታንንም ግራዝማቹንና ቀኝ አዝማቹን ጥሩልኝ" አለ። ንጉሡም ከእናንተ ጋራ የጌታችሁ አሽከሮችን ይዛችሁ ልጄ ሰሎሞንን በበቅሎዬ ላይ አስቀምጣችሁ ወደ ግዮን አውርዱት"። በዚያም ነቢዩ ናታንና ካህኑ ሳዶቅ "ቀብታችሁ በእስራኤል ላይ አንግሡት" አላቸው። ቀንደ መለከት ንፉ "ሰሎሞን ሺህ ዓመት ያንግሥህ በሉ። ተከትላችሁም ውጡ ገብቶም በዙፋኔ ላይ ይቀመጥ እርሱም ስለ እኔ ፈንታ ይንገሥ በሁሉቱ ነገድና በዐሥሩ ነገድ ይነግሥ ዘንድ እኔ አዝዣለሁ"።
❤ ካህኑ ሳዶቅም ከድንኳን ቀርነ ቅብዑን ወስዶ ሰሎሞንን ቀባው ቀንደ መለከትንም ነፉ ሕዝቡም ሁሉ ተከትለውት ወጡ ከበሮም መቱ ታላቅ ደስታም አደረጉ ከድምፃቸውም የተነሣ ምድሪቱ ተናወጸች።
❤ ሰሎሞንም በመንግሥት ዙፋኑ ተቀመጠ። የንጉሡም አሽከሮች ጌታቸው ንጉሡ ዳዊትን ሊአመሰግኑ ገቡ። "እግዚአብሔር የሰሎሞንን ስም ከስምህ ይልቅ መልካም ያደርገው ዙፋኑንም ከዙፋንህ ይልቅ የበለጠ ያድርገው" አሉት። ንጉሡም በዐልጋው ሁኖ ሰገደ። እንዲህም አለ "ዐይኖቼ ሲያዩ በዙፋኔ ላይ የሚቀመጥ ልጅን ለኔ ለባሪያው ዛሬ የሰጠ የእስራኤል ፈጣሪ እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን" አለ።
❤ ዳዊትም የሚሞትበት ወራት በደረሰ ጊዜ ልጁ ሰሎሞንን እንዲህ ሲል አዘዘው። "እኔ ሰው ሁሉ በሚሔድበት በሞት ጎዳና እሔዳለሁ አንተ ግን ጽና ብልህ ሰውም ሁን። በሕጉ ጸንተህ ትኖር ዘንድ የፈጣሪህ የእግዚአብሔርን ትዕዛዝን ጠብቅ እኔ እንዳዘዝሁህ እንዴት እንደምታደርግ ታውቅ ዘንድ በመሴ ሕግ የተጻፈውን ትእዛዙንና ሕጉን ፍርዱንም ጠብቅ ልጆችህ ሕጌን ቢጠብቁ በፊቴም በፍጹም ልቡናቸው በፍጹም ሰውነታቸው በዕውነት ጸንተው ቢኖሩ ከእስራኤል ዙፋን ላይ ሰው አይጠፋብህም ብሎ እግዚአብሔር ለእኔ የነገረኝ ቃሉን ያጸና ዘንድ ጠብቅ" ብሎ አዘዘው። ዳግመኛም ከኢዮአብና በሳሚ ወልደ ጌራ ላይ በቀል እንዲአደርግ አዘዘው እነርሱ እጅግ የከፋና ብዙ ክፋት የሠሩ ነበሩና።
❤ ከዳዊት ዕረፍትም በኋላ ሰሎሞን ከዚያ መሥዋዕትን ይሠዋ ዘንድ ተነሥቶ ወደ ገባዖን ሔደ ገባዖን ፈጽማ ትሰፋ ነበርና ሰሎሞንም በገባዖን በዚያው መሠዊያ ውስጥ ሽህ መሥዋዕትን ሠዋ።
❤ እግዚአብሔርም ለሰሎሞን በሌሊት በሕልም ተገለጠለት "ለአንተ እሰጥህ ዘንድ በልብህ ያሰበውን ልመናን ለምን" አለው። ሰሎሞንም "በቅንነትና በእውነት በንጹሕ ልቡናም ከአንተ ጋራ በፊትህ ጸንቶ እንደኖረ ከአባቴ ከዳዊት ጋራ ታላቅ ቸርነትን አድርገሃል በዚችም ቀን ልጁን በዙፋኑ ላይ ታስቀምጠው ዘንድ ይህን ታላቁን ቸርነት አጽንተህለታል" አለው። "አሁንም አቤቱ አንተ ፈጣሪዬ ስለ አባቴ ስለ ዳዊት ፈንታ እኔን ባሪያህን አነገሥኸኝ እኔም መግቢያዬንና መውጫዬን የማላውቅ ታናሽ ብላቴና ነኝ። እኔ ባሪያህ ግን የማይቈጠር ብዙ ሕዝብ በሆነ በመረጥከው ወገንህ መፍረድ የሚችል የለምና ሰምቶ ለወገኖችህ በእውነት ፍርድን ይፈርድ ዘንድ ከክፉ ነገርም ለይቶ በጎውን ነገር ያውቅ ዘንድ ለባሪያህ ዕውቀትን ስጠው"። ሰሎሞን ይህንን ነገር ለምኖታልና ይህ ነገር እግዚአብሔርን በፊቱ ደስ አሰኘው።
❤ እግዚአብሔርም "ይህንን ነገር ከእኔ ለምነሃልና ለአንተም ብዙ ዘመንንና ባለጸግነትን አለመንህምና ጠላቶችህንም አጥፋልኝ ብለህ አልለመንህምና ነገር ግን ፍርድ መስማትን ታውቅ ዘንድ ለምነሃልና እነሆ እንዳልህ አደረግሁልህ። እነሆ ከአንተ አስቀድሞ እንዳልነበረ ከአንተም በኋላ እንዳንተ ያለ እንዳይነሣ አድርጌ ብልህና አስዋይ ልቡናን ሰጠሁህ። ሰው በመንግሥቱ እንዳንተ እንዳልሆነ አድርጌ ያልለመንኽኝን ባለጠግነትንና ክብርንም በዘመንህ ሁሉ እሰጥሃለሁ" አለው። ሰሎሞንም ከእንቅልፋ በነቃ ጊዜ እውነተኛ ሕልም እንደ ሆነ ዐወቀ ተነሥቶም ወደ ኢየሩሳሌም ሔደ በጽዮንም በእግዚአብሔር ታቦት ሕግ አንጻር ባለ በመሠዊያው ፊት ቆሞ የሰላም መሥዋዕትን አቀበረ ለሰዎቹና ለሱም ታላቅ ግብዣ አደረገ።
❤ በዚያን ጊዜም ሁለት አመንዝራ ሴቶች ወደ ንጉሡ መጥተው በፊቱ ቆሙ አንዲቱም ሴት "ጌታዬ ስማኝ እኔና ይህች ሴት በአንድ ቤት እንኖራለን በአንድ ቦታም ወለድን እኔ በወለድሁ በሦስተኛው ቀን ይህች ሴት ወለደች በአንድነትም እንኖራለን በዚያም ቤት ከሁለታችን በቀር ከኛ ጋራ ማንም አልነበረም። በላዩ ላይ ተጭናዋለችና የዚያች ሴት ልጅ በሌሊት ሞተ። በሌሊት እኩሌታም ተነሥታ ተኝቼ ሳለሁ ልጄን ከአጠገቤ ወስዳ በብብቷ አስተኛችው። የሞተውን ልጅዋንም በአጠገቤ አስተኛችው። ልጄን | 26 |
| 7 | Нет текста... | 29 |
| 8 | ❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ❤
❤ #ሰኔ ፳፫ (23) ቀን።
❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ አራዊትና እንስሳት እንደሰው በድምፅ ያነጋግሯቸውና ይታዘዙላቸው ለነበረው፤ ይጠብቋቸው የነበሩትን በጐችና ፍየሎችን በነብርና በተኩላ ያስጠብቁ ለነበሩት ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ተጠምቀ_መድኅን_ለዕረፍታቸው_በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #አቡነ_ተጠምቀ_መድኀን፦ በጐጃም ከሚታወቁ ታላላቅ ቅዱሳን ውስጥ እንዱና ዋነኛው ናቸው። እርሳቸውም እንደነ አቡነ አብራንዮስ ላሉ ቅዱሳን ገዳማቸውን እንዲመሠርቱ ያደረጉ ታላቅ አባት ናቸው" አቡነ አብራንዮስ በነፋስ ሠረገላ እየሔዱ ሲታዩ እንዲሁም ሌሎች ተኣምራትን ሲያደርጉ ይኽንንም ድንቅ ሥራቸውን ሰዎች ቢያውቁባቸው ውዳሴ ከንቱን ንቀው ወደ አቡነ ተጠምቀ መድኅን ዘንድ ሔደው በዚያ በታላቅ ተጋድሎ ከኖሩ በኋላ አቡነ ተጠምቀ መድኀን "በአንተ ምክንያት ብዙ ነፍሳት ይድናሉ ክፍልህ በዚያ ነው" በማለት ዛሬ ላይ ኤርትራ ውስጥ ወደሚገኘው ደብረ ጥሉል ልከዋቸዋል። እርሳቸውም ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል እየመሯቸው መጥተው አስደናቂውን እንዳ ኣቦና ደብረ ጥሉል ገዳምን መሥርተዋል።
❤ አቡነ ተጠምቀ መድኅን በጻድቁ ዮሐንስ ዘመነ መንግሥት የነበሩ ሲሆን የታላቁ የጉሐንቻ አንድነት ገዳም መሥራች ናቸው። በ17ኛው መ/ክ/ዘ የነበሩት አቡነ ተጠምቀ መድኅን በርካታ ገዳማትን መሥርተዋል። ከእነዚኸም ውስጥ፡- አውሽካን ኢየሱስ ገዳም፣ ካጋና ኤዎስጣቴዎስ ገዳም፣ ወገዳ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም እና ሌሎችንም በርካታ ገዳማትን ጻድቁ እንዳቋቋሙ ከጎሐንቻ ቅድስት ማርያም ገዳም የተገኘ ጽሑፍ ይገልጻል። እነዚኸም ገዳማት አሁን ላይ የት እንዳሉ ማወቅ አልተቻለም፣ ምናልባትም በእነ ግራኝ አህመድ የጠፉ ይሆናሉ።
❤ ሌላኛዋ በአቡነ ተጠምቀ መድኅን የተመሠረተችው ሐረጽ ማርያም ገዳም ናት። ይኸችም ገዳም የምትገኘው በአዊ ዞን ሀገረ ስብከት መተከል ውስጥ በጓንጓ ወረዳ ውስጥ ነው። ሌላው የጻድቁ ገዳም ቻግኒ የሚገኘው የስጋዲ ቅዱስ ሚካኤል አቡነ ተጠምቀ መድኅን አንድነት ገዳም ነው። ይኸም የጻድቁ ገዳም በርካታ መነኰሳት የሚገኙበት ታላቅ የአንድነት ገዳም ሲሆን በተለያዩ የልማት ሥራዎች ይታወቃል። አቡነ ተጠምቀ መድኀን አባታቸው ወልደ ክርስቶስ እናታቸው ወለተ ማርያም የተባሉ ደጋግ ክርስቲያኖች ሲሆኑ ጻድቁ የተወለዱት ታኅሣሥ 2 ቀን ነው። በጥምቀት ሀብተ ውልድና የተቀበሉት ደግሞ ጌታችን በተጠመቀበት ዕለት ጥር 11 ቀን ስለሆነ "ተጠምቀ መድኅን" ተብለው መጠራታቸውም ከዚህ ከክርስትና ቀናቸው በመነሣት ነው።
❤ አቡነ ተጠምቀ መድኅን አስተዳደጋቸው እንደማንኛውም የገጠር ልጅ እረኛ ሆነው ያደጉት። እርሳቸው ግን ከልጅነታቸው ጀምረው መንፈሳዊ ትምህርት ለመማር ካላቸው ጽኑ ፍላጎት የተነሣ ያግዷቸው (ይጠብቋቸው) የነበሩትን በጐችና ፍየሎችን በነብርና በተኩላ አስጠብቀውና አደራ ሰጥተው ወደ አባቶች ዘንድ በመሔድ ከመነኰሳት እግር ሥር ተቀምጠው ዳዊት ደግመው ወንጌል ተምረው ማታ ይመለሳሉ። ተምረው ጨርሰው ሲመለሱም በጐቹና ፍየሎች ከነብርና ከተኩላ ከአራዊት ጋር ሲቦርቁ ያገኟቸዋል።
❤ አባታቸውም ሳያውቁባቸው ከእረኝነታቸው እንደተመለሱ ሆነው ማታ ወደቤታቸው ይመለሳሉ። ከዕለታትም በአንደኛው ቀን አንድ ባሕታዊ አባታቸውን ወልደ ክርስቶስን አግኝቶ "ልጅህን ስጠኝ ላስተምረው" ሲላቸው አባታቸውም "በጎቹንና ፍየሎቹን ማን ይጠብቃቸዋል?" በማለት እምቢ አሉ። አባታቸውም ተጠምቀ መድኅንን ዳዊት አንግበው ስላዩዋቸው ይኸንን ሁኔታ ለማረጋገጥ ልጃቸው እያገዱ በእረኝነት ከሚውሉበት ቦታ ቢሔዱ በሚያስገርም ሁኔታ በጎቹና ፍየሎቹ ከነብርና ከተኩላ ጋር ሲጫወቱ ሲቦርቁ ተመለከቱ። ሲመሽም አውራዎቹ እንስሶቹን ሲሸኟቸው አዩ" ማታም ልጃቸውን ተጠምቀ መድኅንን "ልጄ የት ዋልህ?" ብለው ሲጠቋቸው "ከብት ሳግድ ዋልሁ" ሲሉ አባታቸውም "ልጄ ሆይ! ነገሩን ተረድቼዋለሁ፣ ከዛሬ ጀምሮ እረኛ አትሆንም፣ ከባሕታውያን ዘንድ ሔደህ ተማር" ብለው ወደ ገዳም ላኳቸው።
❤ ከዚህም በኋላ አቡነ ተጠምቀ መድኅን መንፈሳዊ ትምህርት እየተማሩ የአባቶችን መንገድ እየተከተሉ በተጋድሎ መኖር ጀመሩ። ገና ከሕፃንነታቸው ጀምረው ቁርስና ምሳቸውን ለነዳያን በመስጠት እርሳቸው ግን ሲጾሙ ውለው በቀን እንድ ጊዜ ብቻ ይቀምሱ ነበር። ተጋድሏቸውንም ለማጽናት ወደ ታላቋ መርጡል ማርያም በመሔድ በ23 ዓመታቸው አባ ዝክረ ማርያም በሚባለ አባት እጅ መነኰሱ። ከመነኰሱም በኋላ ከሚለብሱት የፍየል ቆዳ ሥር ሰውነታቸውን በሰንሰለት አሥረው ከመኖራቸውም በላይ ቅዳሜና እሑድ ከሚቀምሱት ዳቤ በቀር እህል አይቀምሱም ነበር። ስግደታቸውም በቀን አንድ ሺህ እንደነበር ገድላቸው ይናገራል።
❤ ጻድቁ ከተሰጣቸው ጸጋ የተነሣ አራዊትና እንስሳት እንደሰው በድምፅ ያነጋግሯቸውና ይታዘዙላቸው ነበር። እንደ ረድእ ሆኖ የሚታዘዛቸው ጸዋሬ መስቀል የሚባል አንድ አህያ ነበራቸው፤ እርሱም መልእክት በማድረስና በመቀበል አባታችንን ያገለግላቸው ነበር፣ አምጣ ያሉትን ያመጣል፣ ውሰድ ያሉትን ይወስዳል። እርሳቸውም ከጐጃም እስከ ሱዳን ጠረፍ ድረስ ወንጌልን ሰብከው በርካታ ከሃዲያንን አስተምረው በማጥመቅ ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን ከፈጸሙ በኋላ ከጌታችን ቃልኪዳን ተቀብለው በጻድቁ ዮሐንስ ዘመን በ1670 ዓም በክብር ዐርፈዋል።
❤ አቡነ ተጠምቀ መድኀን ያረፉት ሰኔ 23 ሲሆን በዓለ ዕረፍታቸው ዐፅማቸው በክብር ተቀምጦ ባለበት በጋሾላ ቅዱስ ጊዮርጊስ አንድነት ገዳም ውስጥ በታላቅ ድምቀት ይከበራል። ያረፉትም ለአገልግሎት ወደ ጋሾላ ቅዱስ ጊዮርጊስ የእናቶች ገዳም በሔዱበት ወቅት ስለነበር ዛሬም የከበረ ዐፅማቸውም በዚያው ይገኛል። ከአቡነ ተጠምቀ መድኅን እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን፣ በጸሎታቸው ይማረን። ምንጭ፦ በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን መጽሐፍ።
@Teamihokidusan | 39 |
| 9 | Нет текста... | 80 |
| 10 | [ ስንክሳር ሰኔ - ፳፫ - ] .mp3 | 72 |
| 11 | 🕊
✞ የሰኔ ፳፫ [ 23 ] ✞
✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞
❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖
❖ ሰኔ ፳፫ [ 23 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
🕊 † ቅዱስ ሰሎሞን ንጉሠ እሥራኤል † 🕊
መፍቀሬ ጥበብ :
¤ ጠቢበ ጠቢባን:
¤ ንጉሠ እሥራኤል:
¤ ነቢየ ጽድቅ:
¤ መስተሣልም [ ሰላማዊ ] . . . እየተባለ የሚጠራው ቅዱስ ሰሎሞን የታላቁ ነቢይና ንጉሥ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊትና የቅድስት ቤርሳቤህ [ቤትስባ] ልጅ ነው:: ከ ፫ [3] ሺ ዓመታት በፊት የተወለደው ቅዱስ ሰሎሞን እስከ ፲፪ [12] ዓመቱ ድረስ በቤተ መንግሥት ከአባቱ ጋር አድጉዋል::
ቅዱስ ዳዊት ፸ [70] ዘመን በሞላው ጊዜ የአካሉን መድከም አይቶ አዶንያስ በጉልበት እነግሣለሁ ቢልም አልተሳካለትም:: እግዚአብሔር ሰሎሞንን መርጧልና ገና በ፲፪ [12] ዓመቱ ነገሠ:: ልበ አምላክ አባቱ ዳዊት ነፍሱ ከሥጋው ከመለየቷ በፊት መከረው::
"ልጄ ሆይ ! ልብህን ስጠኝ:: ፈጣሪህንም አምልክ" አለው::
ቅዱስ ሰሎሞን እንደ ነገሠ በገባዖን ለእግዚአብሔር መስዋዕትን አቀረበ:: ጌታም ተገልጾ "ምን ትፈልጋለህ?" አለው:: ሰሎሞንም ልክ እንደ አባቱ ማስተዋልን: ልቡናን ለመነ:: በዚህም ጌታ ደስ ስለተሰኘ "አልቦ እምቅድሜከ: ወአልቦ እምድኅሬከ - ከአንተም በፊት: ከአንተም በኋላ እንዳንተ ያለ ጠቢብና ባለጠጋ ሰው የለም: አይኖርም" ብሎት ተሠወረ:: ቅዱስ ሰሎሞን ለ፵ [40] ዓመታት በእሥራኤል ላይ ነገሠ::
ግሩም በሆነ ፍትሑ: በልዩ ጥበቡ ዓለም ተገዛለት:: እግዚአብሔር የመረጣት የእኛዋ ንግስተ ሳባ /አዜብ/ማክዳም ትፈትነው ዘንድ ሒዳ ምኒልክን [እብነ መለክን] ጸነሰች:: በኋላም ታቦተ ጽዮንና ሥርዓተ ኦሪት መጣልን:: ነቢየ ጽድቅ ቅዱስ ሰሎሞን ድንግል ማርያም ከእነሱ ዘር እንደምትወለድ ነግሮት ነበርና ያበጀሁ መስሎት ሴቶችን አብዝቶ ነበር::
ነገር ግን :-
¤ አንደኛ ሰው [ሥጋ ለባሽ] ነውና:
¤ ሁለተኛ ደግሞ ከብዙ ሴቶች መካከል ከአንዷ እመ ብርሃን ትገኛለች መስሎት ነበር:: ነገሩ መንገድ ስቶበት ከአሕዛብ
[ከፈርዖን ልጅ] ጋር በመወዳጀቱ ለጣዖት አሰገደችው:: እግዚአብሔር እጅግ አዘነ::
በራዕይ ተገልጦ "ስለ ወዳጄ ስለ ዳዊት ስል በአንተ ላይ ክፉን አላደርግም" አለው:: ታላቁ ነቢይ ሰሎሞን ይህንን ሲሰማ ወደ ልቡ ተመለሰ:: ማቅ ለብሶ: አመድ ነስንሶ በፍጹም ልቡ አለቀሰ:: ንስሃ ገባ:: መፍቀሬ ንስሃ ጌታችንም ንስሃውን ተቀበለው::
የይቅርታው መገለጫም ተወዳዳሪ የሌላቸውን ፭ [5] መጻሕፍት ገለጠለት:: ተናገራቸው:: ጻፋቸው:: እሊሕም :-
፩. መጽሐፈ ጥበብ
፪. መጽሐፈ ተግሣጽ
፫. መጽሐፈ መክብብ
፬. መጽሐፈ ምሳሌ
፭. መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን ናቸው::
ቅዱስ ሰሎሞን ልዩ የሆነውን ቤተ መቅደስ በመስራቱም ይደነቃል:: ደጉ ንጉሥ: ጠቢብና ነቢይ ሰሎሞን በዚህች ዕለት በ፶፪ [52] ዓመቱ ዐርፎ ወደ ፈጣሪው ሔዷል::
🕊 † አባ ኖብ † 🕊
ዳግመኛ በዚህ ቀን ታላቁ ሰማዕት አባ ኖብ አርፏል:: በዚሕ ስም የሚጠሩ ብዙ ቅዱሳን ቢኖሩም ዋናው ይኼው ቅዱስ ነው::
አባ ኖብ እንደ ገዳማውያን በበርሃ የተጋደለ: እንደ ሊቃውንት መጻሕፍትን ያመሰጠረ: በተለይ ደግሞ በዘመነ ሰማዕታት ጭንቅ ጭንቅ መከራዎችን የተቀበለ አባት ነው:: ስለ ገድሉ ብዛት "ኃያል ሰማዕት": አንገቱን ስላልተቆረጠም "ሰማዕት ዘእንበለ ደም" ይባላል:: ዘመነ ሰማዕታትን ካለፉ ፸፪ [72] ቱ ከዋክብትም አንዱ ነው::
ከመፍቀሬ ጥበብ ቅዱስ ሰሎሞን: ከኃያሉ ሰማዕት አባ ኖብ በረከትን አምላካችን ይክፈለን::
🕊
[ † ሰኔ ፳፫ [ 23 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ነቢየ ጽድቅ ቅዱስ ሰሎሞን [ንጉሠ እሥራኤል]
፪. ቅዱስ አባ ኖብ [ሰማዕት ወጻድቅ]
፫. ቅዱሳን መርቆሬዎስ: ፊልዾስና ቶማስ [ሰማዕታት]
[ † ወርኃዊ በዓላት ]
፩ ፡ ቅዱስ ዳዊት ልበ አምላክ
፪ ፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት
፫ ፡ ቅዱስ ጢሞቴዎስ ገዳማዊ
፬ ፡ አባ ሳሙኤል
፭ ፡ አባ ስምዖን
፮ ፡ አባ ገብርኤል
፯ ፡ ቅዱስ ዳንኤል ነቢይ
" የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ:: ደስ አያሰኙም የምትላቸውም ዓመታት ሳይደርሱ: ፀሐይ: ጨረቃና ከዋክብትም ሳይጨልሙ . . . አፈርም ወደ ነበረበት ምድር ሳይመለስ: ነፍስም ወደ ሰጠው ወደ እግዚአብሔር ሳይመለስ ፈጣሪህን አስብ:: ሰባኪው :- "ከንቱ: ከንቱ: ሁሉ ከንቱ ነው" ይላል::" [መክ.፲፪፥፩-፱] (12:1-9)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖 | 90 |
| 12 | Нет текста... | 249 |
| 13 | 🕊 † 🕊
[ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ]
🩵 🩵
[ በእኛም ባሕርይ ተገለጠ ! ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
❝ ቅዱሳን አባቶቻችን ስለ ጌታችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እርሱ ከአብ ባሕርይ የተገኘ አንድ ወልድ ቃል እንደሆነ ተናገሩ ፤ ከባሕርይ አምላክ [ ከዘለዓለም ] የተገኘ የባሕርይ አምላክ ፤ ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ፤ ሁሉ የተፈጠረበት እርሱ ነፍስን ሥጋን ነሥቶ ሰው ሆነ።
ከድንግልም በሥጋ ይወለድ ዘንድ ወደደ። በእኛም ባሕርይ ተገለጠ ፤ ሰው የሆነበት ባሕርይ ይህ ነው። አብ አንድ ነው ፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አንድ ነው ፤ ይኸውም ከአብ የተገኘ አንድ ቃል ነው ፤ ሰው ሆነ። ገንዘቡ ከሚሆን ከልዑል ጌትነቱም አልተለየም ሰውም ቢሆን በአምላክነቱ ጸንቶ ይኖራል። ገዢ እርሱ በተገዢ ባሕርይ ተገለጠ ፤ ንዴት በሚስማማው በእኛ ባሕርይ ሳለ ፍጹም መለኮት ገንዘቡ ነው።
በድካመ ሥጋ ተገልጦ ሳለ የኀያላን መላእክት ጌታ ነው ፤ በሰው መጠን በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ሳለ ከፍጥረት ሁሉ በላይ ነው ፤ ከኃጢአት ብቻ በቀር በሰውነቱ የሰውነት ሥራ ሁሉ ገንዘቡ ነው። አንድ የእግዚአብሔር ልጅ ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ፤ ሕይወት ፣ ኀይል የሚሆን እርሱ እግዚአብሔር ባሕርዩ ያልነበረ ሥጋን ተዋሐደ ፤ ሰው ስለሆነም በሥጋ ተገለጠ ፤ በማይመረመር ረቂቅ ተዋሕዶ ከእርሱ ጋር አንድ የሆነ ሥጋን ስለተዋሐደ የሰውነትን ሥራ ሁሉ ገንዘብ አደረገ ፤ ሥጋም ገንዘቡ ነው የሌላ አይደለም። ❞
[ 🕊 ቅዱስ ቄርሎስ 🕊 ]
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊 | 247 |
| 14 | Нет текста... | 280 |
| 15 | [ ስንክሳር ሰኔ - ፳፪ - ] .mp3 | 254 |
| 16 | 🕊
[ † እንኳን ለቅዱሱ አባታችን የዋህ ዻውሊ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
🕊 † ቅዱስ ዻውሎስ የዋህ † 🕊
† በ፬ [ 4 ] ኛው መቶ ክ/ዘመን መጀመሪያ አካባቢ ግብፅ ውስጥ ተወልዶ ያደገው ቅዱሱ ስሙ ዻውሎስ ቢሆንም ብዙ ጊዜ የሚጠራው "የዋህ ዻውሊ" በሚል ነው:: ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ :-
የዋህ ዻውሊ ከሕጻንነቱ ጀምሮ መጻሕፍትን የተማረ: ግን ደግሞ ትዕቢት: ቁጣና ቂምን የማያውቅ ገራገር ሰው ነው:: እድሜው ለአካለ መጠን ሲደርስ ቤተሰቦቹ ሚስት አግባ አሉት:: እርሱ ባያስብበትም ወገኖቹን ላለማሳዘን አገባ:: እንዳለመታደል ሆኖ ግን ያገባት ሴት በጣም ቆንጆ በዚያም ላይ ክፉ ነበረች:: የዋህ ዻውሊ ክፋቷን ሁሉ ታግሶ ለበርካታ ዓመታት አብሮ ኖረ:: ልጆችንም አፈሩ::
አሁንም ግን እርሷ ከክፋቷ ልትታገስ አልቻለችም:: ይባስ ብሎ ዻውሊ በሌለበት ከሌሎች ወንዶች ጋር ትዘሙት ያዘች:: የዋሁ ሰው ይሕንኑ ያውቃል ግን የእግዚአብሔርን ሥራ ዝም ብሎ በተስፋ ይጠብቅ ነበር:: ለነገሩስ እሱ ያርሳል: ይቆፍራል: ነዳያንን ያበላል: እንግዳ ይቀበላል እንጂ ክፋትን ለማሰብ ጊዜ አልነበረውም::
አንድ ቀን ግን ለሥራ ወደ በርሃ ወጥቶ አንድ ግሩም ዜና ሰማ:: "አባ እንጦንስ ምንኩስና የሚባል ሕይወተ መላእክትን ጀምሯል: ደቀ መዛሙርትንም ይቀበላል" አሉት:: ግን ሚስትና ልጆች አሉትና ምን ያደርጋል?
የዋህ ዻውሊ ሙሉ ቀን ሢሠራ ውሎ ወደ ቤቱ ሲመለስ ግን የጠበቀው ሌላ ነው:: ሚስቱ በራሱ መኝታ ላይ ከአገልጋይ እረኛው ጋር ራቁታቸውን አገኛቸው:: ልብ በሉልኝ በትክሻው ሞፈርና ምሳር: መጥረቢያም ይዟል:: እርሱ ግን ክፉን አላሰበም:: ጥሩ ልብስ አንስቶ ሁለቱንም አለበሳቸው:: እንዲሕም አላቸው:- "ከዚሕ በሁዋላ እኔ አልመለስም:: ሀብት ንብረቴን ውረሱ: በደስታም ኑሩ:: የልጆቼን ነገር ግን አደራ" ብሏቸው ተነሳ::
በእጁ ምንም አልያዘም:: በትከሻው ያለችውን ብጣሽ ጨርቅ ይዞ ወደ በርሀ ተጉዋዘ:: አባ እንጦንስም ተቀብለው አስተምረው አመነኮሱት:: ከዚያች ቀን ጀምሮ ራስን ዝቅ በማድረግ: በመታዘዝ አገለገለ:: ጾም: ጸሎትና ስግደቱንማ ማን ቆጥሮት::
እያለ እያለ ከብቅዐት ማዕርግ ደረሰ:: ምዕመናንም ሆነ መነኮሳት ሊጠይቁት ሲመጡ የእያንዳንዱ ኃጢአት በግንባራቸው ተጽፎ ይመለከት ነበርና ስለነሱ ሲያለቅስ ቅንድቡ ተላጠ:: ሰውነቱም አለቀ:: አንድ ቀን ጋኔን የያዘውን ሰው ፈውስ ብለው አመጡለት:: እርሱ ግን በአጋንንት ላይ ሥልጣን እያለው በትሕትና ተጠግቶ ጋኔኑን "አባ እንጦንስን ከምጠራብህ ቀስ ብለህ ውጣ" አለው:: ጋኔኑ ግን የፈራው መስሎት በትዕቢት "እንጦንስ ማነው?" አለው::
ያን ጊዜ የዋህ ዻውሊ እንደ እሳት ከጋለ ድንጋይ ላይ ቁሞ "ሕያው እግዚአብሔር ምስክሬ ነው:: ይሕ ጋኔን ካልወጣ አልወርድም" አለ:: ወዲያው በዘንዶ አምሳል ከሴትዮዋ ወጥቶ እየጮኸ ወደ ቀይ ባሕር ገባ:: ቅዱስ ዻውሊ የዋሕም እንዲሕ በቅድስና ተመላልሶ በዚሕች ቀን በመልካም ሽምግልና ዐርፏል::
" የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር: ደስታ: ሰላም: ትእግስት: ቸርነት: በጐነት: እምነት: የውሃት: ራስን መግዛት ነው:: እንደዚህ ያሉትን የሚከለክል ሕግ የለም:: የክርስቶስ ኢየሱስም የሆኑቱ ሥጋን ከክፉ መሻቱና ከምኞቱ ጋር ሰቀሉ::" [ገላ.፭፥፳፪] (5:22)
🕊
[ † ሰኔ ፳፪ [ 22 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ አባ ዻውሊ የዋሕ
፪. ቅዱሳን ወክቡራን ቆዝሞስና ድምያኖስ [ ሰማዕታት ]
፫. ቅድስት ቴዎዳዳ ሰማዕት [ እናታቸው ]
፬. አንቲቆስ: ዮንዲኖስና አብራንዮስ [ ሰማዕታት ]
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላእክት
፪. ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ
፫. ቅዱስ ደቅስዮስ [ የእመቤታችን ወዳጅ ]
፬. አባ እንጦንዮስ [ አበ መነኮሳት ]
[ † አምላካችን ከቅዱስ ዻውሊ የውሃትን: ትእግስትን : በጐነትን : ጸጋ በረከትን ይክፈለን:: አሜን:: † ]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖 | 252 |
| 17 | Нет текста... | 226 |
| 18 | ❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን" ❤
❤ #ሰኔ_፳፪ 22 ቀን።
❤ እንኳን #ለመነኰሳት_መጀመሪያቸው_ለሆነ ለከበረ #አባ_እንጦንስ_ረድእ ለነበረው ለየዋህ #ለቅዱስ_ጳውሎስ ለዕረፍት በዐል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከከበሩ_ቅዱሳን_ከቆዝሞስና #ከድምያኖስ_ከእናታቸውና_ከወንድሞቻቸው ከበዐላቸው መታሰቢያና ቤተ ክርስቲያናቸውም ከከበረችበት ተአምራታቸውም ከተገለጠበት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የአባ_እንጦስ_ረድእ_የዋህ_ቅዱስ_ጳውሎስ፦ ይህም ጳውሎስ በረኸኛና እጅግ የዋህ ነበር ደም ግቧቷ ውብ ሥራዋ ግን ክፉ የሆነ ሚስት አገባ ከእርሱም ልጆችን ወለደች። በአንዲትም ቀን ከእርሻው በተመለሰ ጊዜ ከሎሌው ጋራ ስታመነዝር አገኛት በአያቸውም ጊዜ ሣቀ ያንን ሎሌውንም እንዲህ አለው "ከልጆቿ ከቤቷና ከንብረቷ ጋራ ውሰዳት እኔ ምንም አላዝንም እግዚአብሔርም ወደ ፈቀደልኝ እሔዳለሁ" አለው።
❤ ከዚህም በኋላ ወጥቶ ወደ አባ እንጦንስ ሒዶ የምንኵስና ልብስ ለበሰ የአባ እንጦንስንም ሥራ ተከተለ። በደዌያትና በሰይጣናት ላይ ጸጋና ኃይል እስከተሰጠው ድረስ በጾምና በጸሎት ተጋደለ።
❤ በአንዲት ዕለትም ጋኔን የያዘውን ሰው ያድነው ዘንድ ወደ አባ እንጦንስ አመጡ። አባ እንጦንስም ይፈውሰው ዘንድ ረድኡ ጳውሊን አዘዘው ጳውሊም ጋኔናሙን ሰው ወስዶ "አባቴ እንጦንስ ውጣ ይልሃል" አለው ሰይጣኑ ግን መውጣትን እምቢ አለ። እርሱንም እንጦንስንም ተሳደበ። ጳውሊም "ካልወጣህስ ለእንጦስ እነግረዋለሁ እንደሚቀጣህም ታያለህ" አለ። ይህንንም ብሎ በቀትር ጊዜ ወጥቶ ፀሐይ በአጋለው ደንጊያ ላይ ቁሞ "ይህ ጋኔን ያደረበት ሰው እስኪድን ድረስ ከዚህ አለት እንዳልወርድ እንዳልበላና እንዳልጠጣ ሕያው እግዚአብሔር" አለ። በዚያንም ጊዜ ጋኔኑ ጮኸ በታላቅ ዘንዶ አምሳልም ከሰውዬው ላይ ወጥቶ በኤርትራ ባሕር ውስጥ ገባ።
❤ ይህም የዋህ ጳውሊ የሰዎችን ሥራ ሁሉ እያየ ስለ ኃጥአን ያለቅስ ነበር ስለ እነርሱም ይማልድ ነበር። በመልካም እርጅናም ሰኔ 22 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ የዋህ በቅዱስ ጳውሎስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሰኔ 22 ስንክሳር።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወኢትቅናእ ላዕለ ዘይዴሎ በሕይወቱ። ወላዕለ ሰብእ ዘይገብር ዐመፃ። ኅድጋ ለመዓት ወግድፋ ለቊጥዓ"። መዝ 36፥7-8። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 5፥6-ፍ.ም፣ ያዕ 5፥14-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 13፥44-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 5፥39-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ወይም የሐዋርያት ቅዳሴ ነው። መልካም የጾም ጊዜና በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።
@Teamihokidusan | 222 |
| 19 | Нет текста... | 237 |
| 20 | [ የእግዚአብሔር ሕግ - ፳፮ - ] .mp3 | 233 |
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
