ገድለ ቅዱሳን
Відкрити в Telegram
@Gedelat ለተለያዩ አስተያየት እና ጥቆማ ማድረስ ከፈለጉ በአድራሻችን ቢያደርሱን ይደርሰናል፡፡ በአድራሻችን ✍ @Mnfesawi_bot
Показати більше6 491
Підписники
-324 години
-37 днів
Немає даних30 день
Триває завантаження даних...
Схожі канали
Хмара тегів
Немає даних
Виникли проблеми? Будь ласка, оновіть сторінку або зверніться до нашого support-менеджера.
Вхідні та вихідні згадування
---
---
---
---
---
---
Залучення підписників
червень '26
червень '26
+70
в 1 каналах
травень '26
+63
в 2 каналах
Get PRO
квітень '26
+77
в 2 каналах
Get PRO
березень '26
+58
в 1 каналах
Get PRO
лютий '26
+44
в 1 каналах
Get PRO
січень '26
+59
в 1 каналах
Get PRO
грудень '25
+98
в 2 каналах
Get PRO
листопад '25
+91
в 1 каналах
Get PRO
жовтень '25
+77
в 1 каналах
Get PRO
вересень '25
+56
в 1 каналах
Get PRO
серпень '25
+103
в 1 каналах
Get PRO
липень '25
+85
в 1 каналах
Get PRO
червень '25
+99
в 1 каналах
Get PRO
травень '25
+96
в 1 каналах
Get PRO
квітень '25
+96
в 2 каналах
Get PRO
березень '25
+140
в 1 каналах
Get PRO
лютий '25
+107
в 1 каналах
Get PRO
січень '25
+190
в 1 каналах
Get PRO
грудень '24
+198
в 2 каналах
Get PRO
листопад '24
+66
в 1 каналах
Get PRO
жовтень '24
+109
в 3 каналах
Get PRO
вересень '24
+60
в 1 каналах
Get PRO
серпень '24
+89
в 1 каналах
Get PRO
липень '24
+129
в 2 каналах
Get PRO
червень '24
+107
в 2 каналах
Get PRO
травень '24
+109
в 1 каналах
Get PRO
квітень '24
+120
в 2 каналах
Get PRO
березень '24
+94
в 2 каналах
Get PRO
лютий '24
+74
в 2 каналах
Get PRO
січень '24
+102
в 2 каналах
Get PRO
грудень '23
+116
в 3 каналах
Get PRO
листопад '23
+81
в 1 каналах
Get PRO
жовтень '23
+98
в 7 каналах
Get PRO
вересень '23
+79
в 0 каналах
Get PRO
серпень '23
+73
в 0 каналах
Get PRO
липень '23
+94
в 0 каналах
Get PRO
червень '23
+64
в 0 каналах
Get PRO
травень '23
+75
в 0 каналах
Get PRO
квітень '23
+78
в 0 каналах
Get PRO
березень '23
+84
в 0 каналах
Get PRO
лютий '23
+54
в 0 каналах
Get PRO
січень '23
+83
в 0 каналах
Get PRO
грудень '22
+62
в 0 каналах
Get PRO
листопад '22
+70
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '22
+54
в 0 каналах
Get PRO
вересень '22
+61
в 0 каналах
Get PRO
серпень '22
+48
в 0 каналах
Get PRO
липень '22
+73
в 0 каналах
Get PRO
червень '22
+47
в 0 каналах
Get PRO
травень '22
+61
в 0 каналах
Get PRO
квітень '22
+75
в 0 каналах
Get PRO
березень '22
+91
в 0 каналах
Get PRO
лютий '22
+57
в 0 каналах
Get PRO
січень '22
+99
в 0 каналах
Get PRO
грудень '21
+55
в 0 каналах
Get PRO
листопад '21
+64
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '21
+141
в 0 каналах
Get PRO
вересень '21
+174
в 0 каналах
Get PRO
серпень '21
+223
в 0 каналах
Get PRO
липень '21
+245
в 0 каналах
Get PRO
червень '21
+205
в 0 каналах
Get PRO
травень '21
+161
в 0 каналах
Get PRO
квітень '21
+520
в 0 каналах
Get PRO
березень '21
+395
в 0 каналах
Get PRO
лютий '21
+333
в 0 каналах
Get PRO
січень '21
+517
в 0 каналах
Get PRO
грудень '20
+9 090
в 0 каналах
| Дата | Залучення підписників | Згадування | Канали | |
| 22 червня | +1 | |||
| 21 червня | +7 | |||
| 20 червня | +2 | |||
| 19 червня | +3 | |||
| 18 червня | +1 | |||
| 17 червня | +4 | |||
| 16 червня | +3 | |||
| 15 червня | +3 | |||
| 14 червня | +5 | |||
| 13 червня | +7 | |||
| 12 червня | +2 | |||
| 11 червня | +4 | |||
| 10 червня | +5 | |||
| 09 червня | +2 | |||
| 08 червня | +1 | |||
| 07 червня | +7 | |||
| 06 червня | +1 | |||
| 05 червня | +1 | |||
| 04 червня | +3 | |||
| 03 червня | +7 | |||
| 02 червня | 0 | |||
| 01 червня | +1 |
Дописи каналу
| 2 | ❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ሰኔ_፲፭ (15) ቀን።
❤ እንኳን #ለታላቁ_ሰማዕት_ለሰማይ_ጭፍራ ለተባለ #ለቅዱስ_ሚናስ_ቤተ_ ክርስቲያን_መርዩጥ በተባለ አገር #ለከበረችበት_ለቅዳሴ_ቤቱ_በዐል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የቅዱስ_ሚናስ_ቤተ_ክርስቲያን_ቅዳሴ_ቤት፦ ከዚህ አስቀድሞ የቅዱስ ሚናስ ሥጋ ተሠውሮ ይኖር ነበር ጌታችንም ሊገልጠው በወደደ ጊዜ ምክንያት አደረገ ይኸውም እንዲህ ነው ቅዱስ ሚናስ ሥጋው ተደፍኖ በሚኖርበት ኮረብታ አቅራቢያ በጎችን የሚያረባ አንድ ሰው በጎቹን እየጠበሸ ይኖር ነበር። ከዚያ እረኛ በጎች ውስጥ ደዌ ያለበት አንዱ በግ በዚያ በኮረብታው አጠገብ ባለ የጒድጓድ ውኃ ተጠምቆ ወዲያውኑ ከደዌው ዳነ እረኛውም አይቶ አደነቀ ሌሎችንም ደዌ ያለባቸውን አመጣ በዚያ ውኃም በታጠቡ ጊዜ ሁሉም ዳኑ።
❤ ከዚህም በኋላ ይህ በቦታው ሁሉ ታወቀ ደዌ ያለባቸውም ሁሉ እየመጡ አፈሩን ከውኃው ጋራ አንድ አድርገው ለውሰው በመቀባት ወዲያውኑ ይድኑ ነበሩ ምክንያቱን ግን አላወቁም። በዚያ ውኃና በአፈሩ በሽተኞችን እንደሚያድን የዚያ በግ ጠባቂ ወሬው በሮሙ ንጉሥ ዘንድ ተሰማ ለንሡም የቊስል ደዌ የታመመች ልጅ ነበረችው ወደ በግ ጠባቂውም ላካት እርሱም በጎቹን እንደ አዳናቸው አዳናት። እርሷም በተፈወሰች ጊዜ ከዚያ ቦታ ፈውስ የሚደረግበትን ምክንያት ታውቅ ዘንድ ወደደች።
❤ ከዚህም በኋላ ቅዱስ ሚናስ በሕልም ተገለጸላትና ሥጋዬ በዚህ ቦታ ተደፍኖ ስለሚኖር እነሆ አስቆፍረሽ ታወጪው ዘንድ እግዚአብሔር አዞሻል" አላት። ከእንቅልፍም በነቃች ጊዜ ቅዱስ ሚናስ እንዳዘዛት አደረገች የከበረ ሥጋውንም አወጣች በዚያም ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያን ሠራችለት ንጉሡም በዚያ ቦታ ከተማ እንዲሠሩ መኳንንቱንና ሹሞቹን አዘዛቸው ታላቅ ከተማም ተሠራች ስሟም መርዩጥ ተባለች።
❤ እግዚአብሔር ከቅዱስ ሚናስ ሥጋ ቊጥር የሌላቸው ድንቆችንና ተአምራትን ገለጠ። ሊቀ ጳጳሳቱም ከኤጲስቆጶሳቱ መጥቶ ቤተ ክርስቲያኒቱን በዛሬዋ ሰኔ 15 ዕለት አከበራት በዚያቺም ቦታ የሚሠሩ የድንቆችና የተአምሮች ወሬ በቦታው ሁሉ ተሰማ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ሚናስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሰኔ15 ስንክሳር።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ውእተ አሚረ ተናገርኮሙ በራእይ ለደቂቅከ። ወትቤ እሬሲ ረድኤተ በላዕለ ኃይል። ወአልዐልኩ ኅሩይየ እምሕዝብየ"። መዝ 88፥19። የሚነበቡት መልዕክታት ኤፌ 7፥10-ፍ.ም፣ 1ኛ ዮሐ 4፥16-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 25፥1-13። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 13፥44-51። የሚቀደሰው ቅዳሴ የወልደ ነጎድጓድ የቅዱስ ዮሐንስ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ሚናስ የቅዳሴ ቤት በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
@Teamihokidusan | 141 |
| 3 | Немає тексту... | 119 |
| 4 | [ ስንክሳር ሰኔ - ፲፭ - ] .mp3 | 110 |
| 5 | 🕊
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ †
🕊 እንኳን አደረሳችሁ 🕊
[ † እንኩዋን ለሰማዕቱ ቅዱስ ሚናስ ዓመታዊ
የቅዳሴ ቤት በዓል በሰላም አደረሳችሁ † ]
🕊 † ቅዱስ ሚናስ ምዕመን ሰማዕት † 🕊
ቅዱስ ሚናስ [ ማር_ሚና ] በምድረ ግብጽ ተወዳጅ ከሆኑ ሰማዕታት ዋነኛው ነው:: ልክ በሃገራችን ቅዱስ ጊዮርጊስ ልዩ ቦታ እንዳለው ሁሉ ግብፃውያን ማር ሚናስን ጠርተው አይጠግቡትም::
ምክንያቱም ከታላላቅ ሰማዕታት አንዱ በመሆኑና ዛሬም ድረስ ለጆሮና ለዐይን ድንቅ የሆኑ ተአምራትን ስለሚሠራ ነው:: በተለይ ለታመመ: ለደከመና ለተጨነቀ ፈጥኖ ደራሽ: ባለ በጐ መድኃኒት ፈዋሽና አማላጅ ነው::
ግብጽ ውስጥ ቅዱሱን የማያውቅ ሰው ካገኛችሁ እርሱ ኦርቶዶክሳዊ አይደለም ማለት ነው ሲባልም ሰምተናል:: በነገራችን ላይ ለቅዱሳን ተገቢውን ክብር በመስጠት: ታሪካቸውን በመጻፍ: በማጥናት: በመጽሔት: በፊልምና በመሳሰሉት ለሕዝብ በማስተዋወቅ ግብጻውያኑ ከእኛ ብዙ ርቀት ሒደዋል:: ዛሬ እንኩዋ የምንጠቀምበትን ስንክሳር ፹ [80] ከመቶ እጁን ያዘጋጁት እነርሱ ናቸው::
አባቶቻችንና እናቶቻችን ኢትዮዽያውያን ቅዱሳን ግን አብዛኞቹ ተረስተው ቀርተዋል:: መጽሐፈ ገድላቸውንም ብል በልቶታል:: ዛሬም የቤት ሥራው የእኛ ብቻ ነው::
ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ቅዱስ ሚናስ [ትርጉሙ ታማኝና ቡሩክ ማለት ነው] :-
- በ፫ [3] ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበረ የደጋግ ክርስቲያኖች ልጅ
- በልጅነቱ የቅድስና ሕይወትን ያጣጣመ
- በዘመኑ ሰው እጅግ ተወዳጅ የነበረ
- ሃብትን: ክብርን: ሥልጣንን ንቆ በጾምና በጸሎት የተወሰነ
- በመጨረሻም በክርስቶስ ስላመነ አላውያን የገደሉት ሰማዕት ነው::
እርሱ ሰማዕት ከሆነ ከበርካታ ዘመናት በሁዋላ ምዕመናን ክቡር አካሉን ፈልገው ያጡታል::
የሚገለጥበት ጊዜ ሲደርስ ግን እርሱ የተቀበረበት ምድረ በዳ የበጐችና የእረኞች መዋያ ነበርና ተአምራትን አደረገ:: አንድ እረኛ በጐቹ ድውያን ሆኑበት:: በዚያ ሰሞን ከቅዱሱ መቃብር ላይ ጸበል ፈልቆ ነበርና እረኛው ተርታ ውሃ ነው ብሎ በጎቹን ሲያጠጣቸው አንዱ ድውይ በግ ወደ ጸበሉ በመዘፈቁ ዳነ::
በዚህ የተገረመው እረኛ ሁሉንም የታመሙ በጐቹን አምጥቶ ነከራቸው:: እነርሱም ተፈወሱ:: ይህ ዜና በምድረ ግብፅ ሲሰማ ድውያን ሁሉ እየመጡ ይፈወሱ ገቡ:: ግን እነሱም ሆነ እረኛው ምክንያቱን ማወቅ አልቻሉም::
ነገሩ በሮም ንጉሥ ዘንድ ሲሰማ ሴት ልጁን ከሠራዊቱ ጋር ላካት:: ምክንያቱም እርሷ ከብዙ ዘመን ጀምራ መጻጉዕ ነበረችና ፈውስን አጥታ ነበር:: መጥታ ተጠመቀች: ፈጥናም ተፈወሰች:: እርሷ ግን እንደ ሌሎች ያዳናትን ማንነት ሳታውቅ መሔድ አልፈለገችምና ሱባዔ ገባች::
ቅዱስ ሚናስ በሌሊት ራዕይ መጥቶ ሥጋው እንዳለ ነገራት:: እርሷም መሬቱን አስቆፍራ የቅዱሱን አካል በክብር አስወጣች:: ከዚያም በንጉሡ ትዕዛዝ ምድረ በዳው ከተማ እንዲሆን ተቀየረ:: ስሙም " መርዩጥ " ተባለ:: ጸበሉ የነበረበት ቦታም ላይ የማር ሚናስ ቤተ_ክርስቲያን ታንጾበት በዚህች ዕለት ቅዳሴ ቤቱ ተከብሯል::
አምላካችን ከቅዱሱ ሰማዕት በረከትን ይክፈለን::
🕊
[ † ሰኔ ፲፭ [ 15 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ሚናስ [ማር ሚና] ሰማዕት [ቅዳሴ ቤቱ]
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ
፪. ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ [አፈ በረከት]
፫. ቅድስት እንባ መሪና
፬. ቅድስት ክርስጢና
" ፈጥኜ ወደ አንተ እንድመጣ ተስፋ አድርጌ ይሕን እጽፍልሃለሁ:: ብዘገይ ግን በእግዚአብሔር ማደሪያ ቤት መኖር እንዴት እንደሚገባ ታውቅ ዘንድ እጽፍልሃለሁ:: ቤቱም የእውነት ዓምድና መሠረት የሕያው እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ነው:: እግዚአብሔርንም የመምሠል ምሥጢር ያለ ጥርጥር ታላቅ ነው:: " [፩ጢሞ.፫፥፲፬] (3:14)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖 | 126 |
| 6 | Немає тексту... | 168 |
| 7 | 🕊 💖 🕊
🕊 [ ጽ ዮ ን እ ና ታ ች ን ] 🕊
🌺 🕊 🌺
የእመቤታችን ምሳሌዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ፦
፯. [ ዕፀ ገነት [ የገነት ዛፍ ] Tree of Heaven ]
የሕይወት ፍሬ ክርስቶስን በድንግልና የወለደች ቅድስት ድንግል ማርያም በገነት ውስጥ ባሉት ዕፀዋት ኹሉ እንደምትመሰል በርካቶች ሊቃውንት በየድርሳናቸው ገልጸዋል፡፡ እነዚኽም በገነት ያሉ አዝርዕት ፣ አትክልት ፣ ዕፀዋት በዚኽ ዓለም ካሉት የተለዩ ናቸው ፤ ቅጠላቸው ሰፋፊ ነው። ዐሥራ ኹለት ክንድ ይኾናል ፧ መዐዛቸው የመንፈቅ መንገድ ኼዶ ይሸታል ፤ ፍሬያቸው የጋን መክደኛ ያኽላል ፤ ጣዕማቸው ነፍስን ከሥጋ ይለያል ፤ አላምጠው እስኪውጧቸው ድረስ ፍሬ ይተካሉ ፤ ጥራታቸው እንደ መስታዮት ፊትን ያሳያል። [ሕዝ ፵፯፥፲፪-፲፫፤ ራእይ ፳፪፥፪-፫]፡፡
የገነት ዛፍ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ስትኾን ፤ የማይጠወልገው ቅጠሏ ለዘላለም የማይለወጠው የድንግልናዋ ፤ የዛፏ ፍሬ የልጇ የፍሬ ሕይወት የክርስቶስ ምሳሌ ነው ፤ ያ ፍሬ ሲቈርጡት እየተካ እንደማያልቅ ኹሉ ለቤዛ ብዙኀን የተሰጠ የጌታ ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ ዕለት ዕለት እየተሠዋ ሲሰጥ የመኖሩ ምሳሌ ነውና ፤ ይኽነን ልዩ ምስጢር የተረዱ ሊቃውንት ይቺ ነቢዩ ሔኖክ ያያት በሱራፊ መልአክ የምትጠበቅ የገነት ዛፍ የድንግል ማርያም ምሳሌ መኾኗን መስክረዋል። ኢትዮጵያዊው ሊቅ አባ ጊዮርጊስም በእንዚራ ስብሐት መጽሐፉ ላይ ፦ [ እመቤቴ ማርያም ሆይ በሔኖክ መጽሐፍ ውስጥ ትእዛዟ የተጻፈ ፤ የመዐዛ ዕፀዋት የሚከቧት የትንቢት ተራራ ነሽ ] በማለት በእውነት ምሳሌዋ መኾኑን ሲያስተምር ፤ የማሕሌተ ጽጌ ደራሲያን ሊቃውንት አባ ገብረ ማርያም ዘደብረ ሓንታና አባጽጌ ድንግል በማሕሌተ ጽጌ መጽሐፋቸው ፦
[ ሱራፊ መልአክ የእሳት ጦርን ይዞ የሚጠብቅሽ ፤ መዐዛሽንም ጸሐፊ ሔኖክ ያሸተተልሽ የማትረግፊ የማትጠፊ የገነት ዛፍ ማርያም ] በማለት ሔኖክ ያያቸው የገነት ዛፎች በእውነት የድንግል ማርያም ምሳሌ መኾናቸውን ተናግረዋል፡፡ ዳግመኛም እነዚኹ ሊቃውንት የቅድስት ድንግልን የመዐዛ ንጽሕናዋን፣ የመዐዛ ቅድስናዋን ፣ የመዐዛ ምግባሯን ድንቅነት በገነት ውስት ባሉት ልዩ ሽታን በሚሸቱ በገነት ዛፎች ሲመስሉ ፦
[ ለአፍንጫ መዐዛን የምትሰጪ የገነት ዛፍ ማርያም ሆይ ፤ ልጅሽ በክንዱ ዐቅፎ በአፉ እየሳመ በቀኙ ሊያሳርፍሽ ባሳረገሽ ጊዜ ፤ አንቺን ለመቀበል ክንፍ ለክንፍ እየተጋጩ እልፍ አእላፋት መላእክት ወረዱ ] በማለት የመዐዛዋን ታላቅነት መስክረውላታል፡፡
ኢትዮጵያዊዉ ቄርሎስ የተባለው ሊቁ አባ ጊዮርጊስም ቅድስት ድንግል ማርያም አማናዊት ዕፀ ገነት መኾኗን በአርጋኖን መጽሐፉ ❝ዕፀ ገገት ዘበጽጌሃ ንትሜዐዝ ወእምፍሬሃ ንሴሰይ ወታሕት አዕጹቂሃ ናጸልል… ኦ ድንግል ዖመ ገነት ዘተከላ የማነ እግዚአብሔር ወአጽገያ ኀይለ መንፈስ ወአፍረያ ጽላሎተ አብ ❞ [ በአበባዋ የምንሻተትባት ፤ ከፍሬዋም የምንመገባት ፤ በሥሯም [ በቅርንጫፎቿም ] የምንጠለልባት የገነት ዕንጨት ናት… ድንግል ሆይ የእግዚአብሔር ቀኝ የተከላት የመንፈስ ቅዱስ ኀይል እንድታብብ ያደረጋት ፣ የአብ ጥላ እንድታፈራ ያደረጋት የገነት ዛፍ ነሽ ] በማለት በሥልጣነ እግዚአብሔር ተጠብቃ በሃይማኖት ፣ በምግባር ፣ በንጽሕና ፣ በቅድስና ጸንታ በግብረ መንፈስ ቅዱስ አምላክን አፍርታ የተገኘች አማናዊት ዕፀ ገነት የመኾኗን ምስጢር አጕልቶ አሳይቷል [ሉቃ ፩፥፴፫-፵፪]፡፡
🩵 † 🩵
❝ ሰው እናታችን ጽዮን ይላል ፥ በውስጥዋም ሰው ተወለደ ፤ እርሱ ራሱም ልዑል መሠረታት። ❞ [ መዝ.፹፯፥፭ ]
════════════════
†††
✟ 𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y ✟
🕊 💖 🕊 | 168 |
| 8 | Немає тексту... | 152 |
| 9 | 💖 🕊 💖
[ ቤተ ክርስቲያንን እንወቅ ]
[ ክፍል አሥራ ስድስት ]
💖 🕊 💖
[ መቅደስ የእግዚአብሔር መገለጫ ! ]
🕊
ቤተ መቅደስ የእግዚአብሔር መገለጫ ፣ የሰማይና የምድር የጋራ ዛቢያ ነው ወይንም ምድር [ መሠረት ] ሰማይን ጣሪያ ዓምዱ ቤተ መቅደስ ነው:: ያለ ዓምድ ቤት እንዳይቆም ያለ ቤተ መቅደስም ሰማይና ምድር አንድነት የላቸውምና እንደ ቤተ መቅደስ በምድር ላይ የሚያስፈራ ክብር ያለውም ቦታ የለም።
" ይህ ሥፍራ እንዴት ያስፈራ ... ! "
ቤተ ክርስቲያን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደሙ ዋጅቶ የመሠረታት ፣ በክርስቶስ ክርስቲያን ለተባልን በሙሉ መሰብሰቢያችን የተቀደሰች ቤታችን ናት፡፡ ቤተ ክርስቲያን ስንልም ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ፣ የክርስቲያን ወገን ፣ የምእመናን አንድነት ወይንም ማኅበረ ምእመናን እንዲሁም እያንዳንዱ ምእመናን ማለታችን ነው፡፡
[ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ]
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አምልኮተ እግዚአብሔር የምንፈጽምባት የእግዚአብሔር ማደሪያ ናት ፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ቅዱሳን መላእክት ፈጣሪያቸውን የሚያገለግሉባት የክብሩ መገለጫ የሰማያዊት ኢየሩሳሌም ምሳሌ በመሆኗ አባቶቻችን በአሠራሯ ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያደርጉ ሲሆን የሕንፃዋ ቤተ ክርስቲያን አሠራርም በሦስት ዓይነት ቅርጽ ሊሆን ይችላል፡፡
፩. [ ክብ ]
በፊልጵስዩስ የተሠራችው የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን ክብ ቅርጽ ነበራት፡፡ የሙሉ ክብነቷ ትርጓሜም የፍጹምነቷ ምልክት ነው ፤ በዚህም መሠረት በአብዛኛው ቤተ ክርስቲያናት በክብ ቅርጽ ይታነጻሉ ፤ የዚህ ዓይነት ሕንጻ ቤተ ክርስቲያንም ዙሪያው ክብ ሆኖ ውስጡ በሦስት የተከፈለ ሰሆን ሦስት በሮችም አሉት ፤ ቤተ ንጉሥ ቅርጽም ይባላል ፤ አንድ ጉልላት ሲኖረው ከጉልላቱም ላይ መስቀል ይኖራል፡፡ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚሣሉት ቅዱሳንም ዓይንና ፊታቸው ክብ ሆኖ የሚሣለው ሃይማኖትን ከምግባር አዋሕደው የተገኙና ከሕግ በላይ የሆኑ ፍጹማን መሆናቸውን ለመግለጽ ነው፡፡
፪. [ ሰቀላማ ወይም ሞላላ ቅርጽ ማዕዘን
ቅርጽ ]
የዚህ ዓይነት የቤተ ክርስቲያን ሕንጻ አሠራር ጠቢቡ ሰሎሞን ያሠራውን ቤተ-መቅደስ መሠረት ያደረገ ነው ፤ ለዚህ ምሳሌ በሀገራችን የአክሱም ጽዮን ፣ የጎንደሩ ደብረ ብርሃን ሥላሴ እና ደብረ ዳሞ ፣ ዐፄ ዮሐንስ በደብረ ሊባኖስ ገዳም ያሠሩት የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ዐሥራ ስምነት ጉልላት ያላቸውን ሰቀላማ ቅርጽ ያላቸውን አብያተ ቤተ ክርስቲያናትን መጥቀስ ይቻላል ፤ በሞላላ ቅርጽ የታነፁ አብያተ ቤተ ክርስቲያናት መሠረታቸው የመስቀል ቅርጽ ያለው በመሆኑ በዚህ ቅርጽ የመታነፃቸው ምሥጢር ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ሰው ልጆች ኃጢአት በመስቀል ላይ የፈጸመውን የድኅነት ሥራ እንድናስብበት ነው፡፡ ለሰው ልጆች ሲል መከራ ተቀብሎ ፣ ተሰቅሎና ሞትን ድል አድርጎ ማረጉን ያመለክታል፡፡ ከላይ የጠቀስናቸው ሰቀላማ ቅርጽ አብያተ ክርስቲያናት በተጨማሪ መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያንና ምስካየ ኀዙናን መድኃኔዓለም ገዳማት ለሰቀላማ ቅርጽ አብያተ ክርስቲያናት በምሳሌነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
፫. [ ዋሻ ቅርጽ ]
የዚህ ዓይነት ሕንፃ ቤተ ክርስቶያናት ሰማዕታት ከዓላማውያን ነገሥታት ሸሽተው በዋሻ ሲሸሸጉ የጀመሩት አሠራር ዓይነት ነው፡፡ አንድ በርም አለው ፤ በአብዛኛውም ጊዜ በውስጡ ያሉትን ክፍሎች በመጋረጃ ይከፈላል፡፡ ሆኖም ግን ጉልላት የለውም ፤ ተራራ በመፈልፈል በዋሻ ውስጥ ሲሆን ለብቻው የቆመ ድንጋይን [አለትን] በመፈልፈል ሊሠራ ይችላል ምሳሌ ፦ አቡነ ሀብተ ማርያም ገዳም ፣ አዳዲ ማርያም ፣ የቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ምሳሌዎች ናቸው፡፡
" ይህ ሥፍራ እንዴት ያስፈራ ፤ ይህ ሥፍራ የእግዚአብሔር ቤት ነው እንጂ ሌላ አይደለም ይህም የሰማይ ደጅ ነው::" [ ዘፍ.፳፰፥፲፮ ]
[ ይቆየን ]
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፥ ወለወላዲቱ ድንግል ፥ ወለመስቀሉ ክቡር፡፡ [ ይቆየን ]
════════════════
†††
✟ 𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y ✟
🕊 💖 🕊 | 169 |
| 10 | Немає тексту... | 218 |
| 11 | በቅድስና .mp3 | 201 |
| 12 | እግዚአብሔር እረኛዬ_ነው .mp3 | 205 |
| 13 | 🩵 † 🩵
🕊 💖 ክብርት ሰንበት ! 💖 🕊
❝ እግዚአብሔር እረኛዬ ነው ፥ የሚያሳጣኝም የለም። በለመለመ መስክ ያሳድረኛል ፤ በዕረፍት ውኃ ዘንድ ይመራኛል። ነፍሴን መለሳት ፥ ስለ ስሙም በጽድቅ መንገድ መራኝ። በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም ፤ በትርህና ምርኵዝህ እነርሱ ያጸናኑኛል።
በፊቴ ገበታን አዘጋጀህልኝ በጠላቶቼ ፊት ለፊት ራሴን በዘይት ቀባህ ፥ ጽዋዬም የተረፈ ነው። ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል ፥ በእግዚአሔርም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ። ❞ [ መዝ.፳፫፥፩-፮ ]
🕊 💛 🕊
❝ እኔስ ክርስቲያን እንድባል ክርስቲያን ሁኜም እንድኖር እወዳለሁ:: እንደ አባቶቼ ሐዋርያት ትምህርት በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ክርስቲያን ሁኜ እንድውል ክርስቲያንም ሁኜ እንዳድር እወዳለሁ:: እንደ አባቶቼ ሐዋርያት ክርስቲያን ሁኜ በመቃብር ውስጥ እንዳንቀላፋ እወዳለሁ:: በትንሣኤዬም ከአባቶቼ ሐዋርያት ጋር ክርስቲያን ሁኜ እንድነቃ እወዳለሁ:: በጽዮን ተራራም በአባቶቼ ሐዋርያት እቅፍ ውስጥ እንዳርፍ እወዳለሁ፡፡ ❞ [ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ]
† 🕊 ክብርት ሰንበት 🕊 †
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊 | 226 |
| 14 | Немає тексту... | 260 |
| 15 | [ ስንክሳር ሰኔ - ፲፬ - ] .mp3 | 253 |
| 16 | 🕊
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ †
[ † እንኩዋን ለአራቱ ቅዱሳን አበው ሰማዕታት
ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ † ]
🕊 † አራቱ ቅዱሳን አበው ሰማዕታት † 🕊
፬ [4] ቱ ቅዱሳን አበው የዘመነ ሰማዕታት ፍሬዎች ሲሆኑ ስማቸው አባ አክራ አባ ዮሐንስ : አባ አብጥልማ እና አባ ፊልዾስ ይባላሉ:: ከመከራ ዘመን በፊት [ማለትም በቀደመ ሕይወታቸው] ካህናትና ሃብታሞች ነበሩ:: ሀብቱ ግን በሥራ ብቻ የተገኘ ነው::
ታዲያ ቅዱሳኑ በያሉበት ሆነው በሀብታቸው እንግዳ እየተቀበሉ : ድሆችን እያበሉ: በክህነታቸው ደግሞ እያስተማሩና እየናዘዙ ትጉሃን ስለ ነበሩ በሰውም ሆነ በእግዚአብሔር ዘንድ ሞገስ ነበራቸው:: በእንዲህ ያለ ግብር ሳሉ ዘመነ ሰማዕታት አሐዱ አለ:: "ክርስቶስን ካዱ: ለጣዖት ስገዱ" እያሉ መኩዋንንቱና ነገሥታቱ ሕዝበ ክርስቲያኑን ያሰቃዩ ገቡ::
በዚህ ጊዜ ፬ [ 4 ] ቱ ቅዱሳን አንድ ነገር መከሩ:: በየእሥር ቤቱ የተጣሉ ክርስቲያኖችን ለማገልገል ቆረጡ:: እግረ መንገዳቸውን እያስተማሩ እሥረኞችን ያጽናኑ ገቡ:: የራበውን ያበላሉ: የተሰበረውን ይጠግናሉ: በቁስሉም ላይ መድኃኒትን ያደርጉ ነበር:: የመከራው ዘመን ግን እየረዘመ: ግፉም ከልክ እያለፈ መጣ::
በዚህ ጊዜ ፬ [ 4 ] ቱ ቅዱሳን ትልቁንና የመጨረሻውን ውሳኔ አስተላለፉ:: ከሰማዕታት ወገን ይቆጠሩ ዘንድ መርጠዋልና: ክርስቶስን በሞቱ ይመስሉት ዘንድ ሽተዋልና: የሩጫቸው መጨረሻ ሰማዕትነት እንዲሆን መረጡ::
አራቱም ያላቸውን ንብረት ሁሉ ሰብስበው ለነዳያን
አካፈሉ:: በትከሻቸው ካለች አጽፍ በቀር ስባሪ ገንዘብ ከሃብታቸው አላስቀሩም:: ከዚያ ጉዞ ወደ ምስክርነት አደባባይ [ዐውደ ስምዕ] አደረጉ::
በዙፋኑ የተቀመጠው የመኮንኑ ግርማ: መሬት ላይ የፈሰሰው የወገኖቻቸው ደም: የሠራዊቱ ድንፋታ ቅዱሳኑን አላስፈራቸውም:: በይፋ "ክርስቲያን ነን" ሲሉ ተናገሩ:: በዘመኑ እንዲሕ ብሎ መናገር አንገት የሚያስቆርጥ ትልቅ ድፍረት ነበር::
መኮንኑም ከበጐ ሃይማኖታቸው ይለያቸው ዘንድ በእሳት አቃጠላቸው:: እግዚአብሔር አዳናቸው:: በቀስትም: በስለትም: በብረትም ለቀናት አሰቃያቸው:: ቅዱሳኑ ግን አምላካቸውን አምነው ሁሉን በአኮቴት ተቀበሉ:: በመጨረሻ ግን በዚሕች ዕለት የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው ተገድለዋል:: ስለ ምጽዋታቸው: በጎ አገልግሎታቸውና ሰማዕትነታቸው ጻድቅ: ፈራጅ ከሆነ ፈጣሪ አክሊልን ተቀብለዋል::
የበረከት አምላክ ከወዳጆቹ ጸጋ ክብርን ያድለን::
🕊
[ † ሰኔ ፲፬ [ 14 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱሳን አበው ሰማዕታት [አባ አክራ: አባ ዮሐንስ: አባ አብጥልማ: አባ ፊልዾስ]
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. አቡነ አረጋዊ [ ዘሚካኤል ]
፪. ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ መርዓዊ
፫. ቅዱስ ፊልዾስ ሐዋርያ
፬. ቅዱስ ሙሴ [ የእግዚአብሔር ሰው ]
፭. አባ ስምዖን ገዳማዊ
፮. አባ ዮሐንስ ጻድቅ
፯. እናታችን ቅድስት ነሣሒት
" እግዚአብሔር ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ: እስከ አሁንም ስለምታገለግሏቸው ያደረጋችሁትን ሥራ: ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመጸኛ አይደለምና:: በእምነትና በትእግስትም የተስፋውን ቃል የሚወርሱትን እንድትመስሉ እንጂ ዳተኞች እንዳትሆኑ ተስፋ እስኪሞላ ድረስ እያንዳንዳችሁ ያን ትጋት እስከ መጨረሻ እንድታሳዩ እንመኛለን። " [ዕብ.፮፥፲-፲፫] (6:10-13)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖 | 262 |
| 17 | Немає тексту... | 247 |
| 18 | ❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ❤
❤ #ሰኔ ፲፬ (14) ቀን።
❤ እንኳን #ለቅዱሳን_አባ_አክራና_ለዮሐንስ፣ #ለአብጥልማና_ለፊልጶስ_ሰማዕትነት_ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። ከእነዚህ ቅዱሳን እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #ቅዱሳን_አባ አክራ_ዮሐንስ_አብጥለሰማና ፊልጶስ፦ ይህም ቅዱስ አክራ ከግብጽ ደቡብ ይምንሑር ከሚባል አገር ሰዎች ወገን ነው ስሙ ፊልጶስ የሚባል ወንድም ነበረው እነርሱም ባለጸጎች ነበሩ ስማቸው ዮሐንስና አብጥልማ ከሚባል ሁለት ቀሳውስት ጋራ ሰማዕታት ይሆኑ ዘንድ ተስማሙ አራቱም ቀርጥስ ወደሚባል አገር ሔዱ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በመኰንኑ ፊት ታመኑ። መኰንኑም በቀስቶች እንዲነድፏቸው አዘዘ ግን ቀስቶች አልነኳቸውም። ሁለተኛም እሳትን አንድደው በሚነድ የእሳት ምድጃ ውስጥ ይጨምሩአቸው ዘንድ አዘዘ እንዲሁም አደረጉባቸው ጌታም መልአኩን ልኮ አዳናቸው።
❤ ከዚህም በኋላ በፈረስ ጅራት ላይ አሥረው ከቀርጥስ ከተማ እስከ ይምንሑር አገር ድረስ ይጐትቷቸው ዘንድ አዘዘና ይህንንም አደረጉባቸው ግን ምንም ምን ጉዳት አልደረሰባቸውም። ከዚህም በኋላ ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጧቸው አዘዘ ከይምንሑር ከተማም አውጥተው ራሶቻቸውን ሰኔ 14 ቀን ቆረጡአቸው።
❤ ፃ ከሚባል አገር ሰዎች መጥተው የቅዱስ አባ አክራን ሥጋውን ወሰዱ ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያንም ሠርተው ሥጋውን በውስጧ አኖሩ ከእርሱም ታላላቅ ድንቆችና ተአምራት በብዛት ተገለጠ።
❤ እንዲሁም የእነዚያን የሦስቱን ቅዱሳን የፊልጶስን፣ የአብጥልማንና የዮሐንስን ሥጋቸውን ከይምንሑር ከተማ ሰዎች መጥተው ወሰዱ በመልካም ልብሶችም ገንዙአቸው ጥሩ ቤተ ክርስቲያንም ሠርተው ሥጋቸውን በውስጧ አኖሩ ከእነርሳቸውም ቊጥር የሌለው ድንቅ ተአምር ተገለጠ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእሊህ በቅዱሳን ሰማዕታት በአባ አክራና ዮሐንስ፣ አብጥልማና ፊልጶስ በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸው ከእኛ ጋራ ለዘላለም ይኑር አሜን። ምንጭ፦ የሰኔ14 ስንክሳር።
@Teamihokidusan | 255 |
| 19 | Немає тексту... | 209 |
| 20 | [ የእግዚአብሔር ሕግ - ፳፬ - ] .mp3 | 209 |
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
