uk
Feedback
ገድለ ቅዱሳን

ገድለ ቅዱሳን

Відкрити в Telegram

@Gedelat ለተለያዩ አስተያየት እና ጥቆማ ማድረስ ከፈለጉ በአድራሻችን ቢያደርሱን ይደርሰናል፡፡ በአድራሻችን ✍ @Mnfesawi_bot

Показати більше
6 488
Підписники
+624 години
Немає даних7 днів
+630 день

Триває завантаження даних...

Хмара тегів
Немає даних
Виникли проблеми? Будь ласка, оновіть сторінку або зверніться до нашого support-менеджера.
Вхідні та вихідні згадування
---
---
---
---
---
---
Залучення підписників
червень '26
червень '26
+71
в 1 каналах
травень '26
+63
в 2 каналах
Get PRO
квітень '26
+77
в 2 каналах
Get PRO
березень '26
+58
в 1 каналах
Get PRO
лютий '26
+44
в 1 каналах
Get PRO
січень '26
+59
в 1 каналах
Get PRO
грудень '25
+98
в 2 каналах
Get PRO
листопад '25
+91
в 1 каналах
Get PRO
жовтень '25
+77
в 1 каналах
Get PRO
вересень '25
+56
в 1 каналах
Get PRO
серпень '25
+103
в 1 каналах
Get PRO
липень '25
+85
в 1 каналах
Get PRO
червень '25
+99
в 1 каналах
Get PRO
травень '25
+96
в 1 каналах
Get PRO
квітень '25
+96
в 2 каналах
Get PRO
березень '25
+140
в 1 каналах
Get PRO
лютий '25
+107
в 1 каналах
Get PRO
січень '25
+190
в 1 каналах
Get PRO
грудень '24
+198
в 2 каналах
Get PRO
листопад '24
+66
в 1 каналах
Get PRO
жовтень '24
+109
в 3 каналах
Get PRO
вересень '24
+60
в 1 каналах
Get PRO
серпень '24
+89
в 1 каналах
Get PRO
липень '24
+129
в 2 каналах
Get PRO
червень '24
+107
в 2 каналах
Get PRO
травень '24
+109
в 1 каналах
Get PRO
квітень '24
+120
в 2 каналах
Get PRO
березень '24
+94
в 2 каналах
Get PRO
лютий '24
+74
в 2 каналах
Get PRO
січень '24
+102
в 2 каналах
Get PRO
грудень '23
+116
в 3 каналах
Get PRO
листопад '23
+81
в 1 каналах
Get PRO
жовтень '23
+98
в 7 каналах
Get PRO
вересень '23
+79
в 0 каналах
Get PRO
серпень '23
+73
в 0 каналах
Get PRO
липень '23
+94
в 0 каналах
Get PRO
червень '23
+64
в 0 каналах
Get PRO
травень '23
+75
в 0 каналах
Get PRO
квітень '23
+78
в 0 каналах
Get PRO
березень '23
+84
в 0 каналах
Get PRO
лютий '23
+54
в 0 каналах
Get PRO
січень '23
+83
в 0 каналах
Get PRO
грудень '22
+62
в 0 каналах
Get PRO
листопад '22
+70
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '22
+54
в 0 каналах
Get PRO
вересень '22
+61
в 0 каналах
Get PRO
серпень '22
+48
в 0 каналах
Get PRO
липень '22
+73
в 0 каналах
Get PRO
червень '22
+47
в 0 каналах
Get PRO
травень '22
+61
в 0 каналах
Get PRO
квітень '22
+75
в 0 каналах
Get PRO
березень '22
+91
в 0 каналах
Get PRO
лютий '22
+57
в 0 каналах
Get PRO
січень '22
+99
в 0 каналах
Get PRO
грудень '21
+55
в 0 каналах
Get PRO
листопад '21
+64
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '21
+141
в 0 каналах
Get PRO
вересень '21
+174
в 0 каналах
Get PRO
серпень '21
+223
в 0 каналах
Get PRO
липень '21
+245
в 0 каналах
Get PRO
червень '21
+205
в 0 каналах
Get PRO
травень '21
+161
в 0 каналах
Get PRO
квітень '21
+520
в 0 каналах
Get PRO
березень '21
+395
в 0 каналах
Get PRO
лютий '21
+333
в 0 каналах
Get PRO
січень '21
+517
в 0 каналах
Get PRO
грудень '20
+9 090
в 0 каналах
Дата
Залучення підписників
Згадування
Канали
22 червня+2
21 червня+7
20 червня+2
19 червня+3
18 червня+1
17 червня+4
16 червня+3
15 червня+3
14 червня+5
13 червня+7
12 червня+2
11 червня+4
10 червня+5
09 червня+2
08 червня+1
07 червня+7
06 червня+1
05 червня+1
04 червня+3
03 червня+7
02 червня0
01 червня+1
Дописи каналу
photo content

2
[ ስንክሳር ሰኔ - ፲፮ - ] .mp3
25
3
🕊 † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ † ❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖ ❖ ሰኔ ፲፮ [ 16 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 🕊  † ቅዱስ አቡናፍር ገዳማዊ  †  🕊 ጻድቁ ተወልዶ ያደገው በ፭ [5] ኛው መቶ ክ/ዘመን በምድረ ግብፅ ነው:: ወቅቱ ሥርዓተ መነኮሳት የሚጠበቅበት:አበው ባሕታውያን እንደ ሰማይ ከዋክብት በዝተው የደመቁበት ነበር:: ታላቁ አቡናፍርም ከክርስቲያን ወላጆቹ ተወልዶ: በሥርዓት አድጎ: መጻሕፍትንም ተምሮ ገና በወጣትነቱ መንኗል:: ሥርዓተ መነኮሳትን ከአባ ኤስድሮስ ታላቁ አጥንቶ ገዳሙንና መምሕሩን እየረዳ ለብዙ ዓመታት በጾምና በጸሎት ኑሯል:: መነኮሳቱ ስለ ትሕትናውና ስለ ታዛዥነቱ ፈጽመው ያከብሩት ነበር:: ከዕለታት በአንዱ ቀን አረጋውያን መነኮሳት ጭው ባለ በርሃ ስለሚኖሩ ባሕታውያን ሲጨዋወቱ: ሲያደንቁዋቸውም ሰማ:: እርሱ በዛ ወቅት ባሕታውያን በበርሃ መኖራቸውን አያውቅም ነበርና ሒዶ መምሕሩን አባ ኤስድሮስን ጠየቃቸው:: እርሳቸውም "አዎ ልጄ! ከዚሕ በጣም ርቅው: ንጽሕናቸውን ጠብቀው: ከሰውና ከኃጢአት ተይለው የሚኖሩ ገዳማውያን አሉ" አሉት:: ቅዱስ አቡናፍር "በዚሕ ካሉት መነኮሳትና በበርሃ ካሉት ማን ይበልጣል?" ቢላቸው "እነርሱ በጣም ይበልጣሉ:: ዓለም እንኩዋ ከነ ክብሯ የእግራቸውን ሰኮና አታህልም" አሉት:: ይሕንን የሰማው ቅዱስ አባ አቡናፍር ጊዜ አላጠፋም:: ከመምሕሩ ቡራኬ ተቀብሎ ወደ በርሃ ሔደ:: ለብዙ ቀናት ከተጉዋዘ በኋላ አንድ ባሕታዊ አግኝቶ አብሯቸው ተቀመጠ:: ከእርሳቸው ዘንድም ሥርዓተ ባሕታውያንን ተምሮ እንደገና ወደ ዋናው በርሃ ጉዞውን ቀጠለ:: ከብዙ ቀናት መንገድ በኋላም አንድ ሠፊ ሜዳ ላይ ደረሰ:: አካባቢው የውሃ ጠብታ የማይገኝበት: ይቅርና መጠለያ ዛፍ የሣር ዘር እንኩዋ የሌለበት ወይም በልሳነ አበው "ዋዕየ ፀሐይ የጸናበት: ልምላሜ ሣዕር የሌለበት: ነቅዐ ማይ የማይገኝበት" ቦታ ነበር:: በዚህ ቦታ ይቅርና የሰው ልጅ አራዊትም አይኖሩበትም:: ለአባ አቡናፍር ግን ተመራጭ ቦታ ነበር:: ቅዱሳኑን ይሕ አያሳስባቸውም:: ምክንያቱም ለእነርሱ ምግባቸውም: ልብሳቸውም ፍቅረ ክርስቶስ ነውና:: አባ አቡናፍር ወደ ፈጣሪ ጸለዩ:: በእግዚአብሔር ቸርነት ከጎናቸው አንዲት ዘንባባ [በቀልት] በቀለች:: ከእግራቸው ሥርም ጽሩይ ማይ [ንጹሕ ምንጭ] ፈለቀች:: ጻድቁ ተጋድሏቸውን ቀጠሉ:: ዓመታት አለፉ:: ልብሳቸውን ፀሐይና ብርድ ጨርሶት ቅጠል ለበሱ:: በዚያ ቦታም የሰው ዘርን ሳያዩ ለ፷ [60] ዓመታት በተጋድሎ ኖሩ:: የሚያርፉበት ጊዜ ሲደርስ እግዚአብሔር አባ በፍኑትዮስን [የባሕታውያንን ዜና የጻፈ አባት ነው] ላከላቸው:: ቃለ እግዚአብሔርን እየተጨዋወቱ ሳለ የአባ አቡናፍር አካሉ ተለወጠ:: እንደ እሳትም ነደደ:: አባ በፍኑትዮስም ደነገጠ:: ታላቁ ገዳማዊ ግን እጆቻቸውን ዘርግተው ጸለዩ: ሰገዱና አማተቡ:: ነፍሳቸውም ከሥጋቸው በፍቅር ተለየች:: ቅዱሳን መላዕክትም በዝማሬና በማኅሌት አሳረጉዋት:: የሚገርመው ደግሞ አባ በፍኑትዮስ ይሕን ሲያይ ቆይቶ ዘወር ቢል ዛፏ ወድቃለች: ቅርንጯም ደርቃለች:: ዳግመኛ ይህች ዕለት የቅዱሳን አበው ባሕታውያን መታሠቢያ ናት:: ከሰው [ ከዓለም ] ርቀው: ንጽሕ ጠብቀው: ዕጸበ ገዳሙን: ግርማ አራዊቱን: ጸብዐ አጋንንትን ታግሠው የኖሩ: ስማቸውን የምናውቀውንም ሆነ የማናውቃቸውን እንድናከብራቸው ቤተ-ክርስቲያን ሥርዓትና በዓል ሠርታለች:: አምላካችን ከአበው ባሕታውያን ጸጋ በረከት ይክፈለን:: 🕊 [ † ሰኔ ፲፮ [ 16 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ] ፩. አባ አቡናፍር ገዳማዊ [ስም አጠራሩ የከበረ: ሽምግልናው ያማረ አባት] ፪. አበው ቅዱሳን ባሕታውያን [ ዛሬ የሁሉም ቅዱሳን ባሕታውያን [በተለይም የስውራኑ] ዓመታዊ በዓል ነው:: - ከሰው: ከዓለምና ከኃጢአት ርቀው - ንጽሕ ጠብቀው - ዕጸበ ገዳሙን - ድምጸ አራዊቱን - ግርማ ሌሊቱን - የሌሊቱን ቁር - የመዓልቱን ሐሩር - ረሐቡን: ጽሙን: መራቆቱን . . . ሁሉ ስለ ፍቅረ-ክርስቶስ ሲሉ ታግሠውታልና:: "ዛሬም በየበርሃው የወደቁ: ስለ ዓለም ምሕረትን የሚማጸኑ አሉ::" አምላካቸው በረከታቸውን ያድለን። ፫. የእግዚአብሔር መልአክ ለዮሴፍ በሕልም ከግብጽ እንዲመለስ የነገረበት [ተዝካረ ሚጠታ ለእግዝእትነ ማርያም] ፬. አፄ ይኩኖ አምላክ [ንጉሠ ኢትዮዽያ] [ †  ወርኃዊ በዓላት ] ፩፡ ኪዳነ ምሕረት ማርያም ፪፡ ቅድስት ኤልሳቤጥ ፫፡ አባ ዳንኤል ገዳማዊ ፬፡ ቅዱስ አኖሬዎስ ንጉሠ ሮሜ ፭፡ አባ ዮሐንስ ወንጌሉ ዘወርቅ ፮፡ ቅዱስ ሐርቤ ንጉሠ ኢትዮጵያ " . . . ሌሎችም መዘበቻ በመሆንና በመገረፍ: ከዚሕም በላይ በእሥራትና በወኅኒ ተፈተኑ . . . ሁሉን እያጡ መከራን እየተቀበሉ: እየተጨነቁ: የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ:: ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ: በዋሻና በምድር ጉድጉዋድ ተቅበዘበዙ:: ዕብ.፲፩፥፴፮] (11:36) " † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
21
4
Немає тексту...
124
5
[ + ማር ሚና + ] .mp3
115
6
🩵 † 🩵 [ 🕊 ማር ሚና 🕊 ] 🕊 💛 🕊 🕊 † ቅዱስ ሚናስ ምዕመን ሰማዕት † 🕊 ❝ የክርስቶስ ምርጥ ጭፍራ ከገንዘብ ይልቅ ጽድቅን የመረጠ ፤ እንደ ምሳሌው እንደ ጨረቃ ለደመቀና እን
🩵                          †                          🩵        [    🕊    ማር ሚና      🕊    ]   🕊                         💛                      🕊 🕊  † ቅዱስ ሚናስ ምዕመን ሰማዕት † 🕊 ❝ የክርስቶስ ምርጥ ጭፍራ ከገንዘብ ይልቅ ጽድቅን የመረጠ ፤ እንደ ምሳሌው እንደ ጨረቃ ለደመቀና እንደ ፀሐይም ብሩህ ለኾ ለሚናስ ሰላምታ ይገባል። መካን ሳለች ጸሎትን እየጸለየች ሳለች ከእመቤታችን ማርያም ሥዕል አሜን የሚል ቃልን ሰምታ የተሸከመችኽ ማሕፀን ሚናስ ብላ የሰየመችኽ የመድኅን ክርስቶስ ምስክር ፤ የጦር መኮንን ለኾንኽ ላንተ ሰላምታ ይገባል። የምድር የኾነ ክብርን ንቀኽ የሰማይ ክብርን የመረጥኽ የክርስቶስ ጭፍራው የኾንኽ ሚናስ አንተ ንኡድ ክቡር ነኽ ፣ በሰማይ አዳራሽ የተመረጠው ሚናስ ፤ ፊቱም እንደ ፀሓይ ብሩህ ነው ፤ ብዙ በኾነ ሰላም እግዚአብሔር ከፍ ከፍ አደረገው። ❞ [ ተአምኆ ቅዱሳን ] 🕊 ❝ ጻድቃን ስለአንተ ታመሙ [ መከራን ተቀበሉ ] መከራቸውም ደስታ ሆነላቸው ፣ ክብር ይገባቸዋል ፣ በተጋድሎአቸው ሰማዕታት ፣ በትዕግስታቸውም መንግሥተ ሰማያትን ወረሱ። ❞ [  ቅዱስ ያሬድ   ] 💛 ማር ቅዱስ ሚናስ በዚኽች ዕለት ኅዳር ፲፭ [15] ቀን ዓመታዊ የዕረፍት በዓሉ ሲሆን ሰኔ ፲፭ [15] ደግሞ ታላላቅ ተአምራት ያደረገበትና ቅዳሴ ቤቱ የተከበረበት ዓመታዊ በዓሉ ነው፡፡ የቅዱስ ሚናስ ምልጃና ጸሎቱ ከዘለዓለም እሳት ያድነን:: ጸጋ በረከቱ ይክፈለን:: ════════════════                            †††               ✟ 𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y ✟ 🕊                       💖                      🕊
116
7
Немає тексту...
92
8
[ + መንፈሳዊ ጥንካሬ + ] .mp3
91
9
🕊 💖 🕊 🩵 [ ምክረ ቅዱሳን ] 🩵 ════════════════ ▷ " የጥንካሬ ዓይነቶች ! " [ 💖 በብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ 💖 ] ▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬ ❝ ከደስታም ጋር በሁሉ ለ
🕊                        💖                        🕊     🩵       [   ምክረ ቅዱሳን   ]        🩵 ════════════════ ▷      "  የጥንካሬ ዓይነቶች !  "  [  💖  በብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ  💖  ]  ▬▬▬▬▬▬   ♱    ▬▬▬▬▬▬ ❝ ከደስታም ጋር በሁሉ ለመጽናትና ለመታገሥ እንደ ክብሩ ጉልበት መጠን በኃይል ሁሉ እየበረታችሁ ፥ በቅዱሳንም ርስት በብርሃን እንድንካፈል ያበቃንን አብን እያመሰገናችሁ ፥ በነገር ሁሉ ደስ ልታሰኙ ለጌታ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እንለምናለን። ❞ [ ቆላ.፩፥፲፪ ] ════════════════                            †††                ✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟ 🕊                         💖                        🕊
114
10
+1
Немає тексту...
329
11
❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤               ❤ #ሰኔ_፲፭ (15) ቀን። ❤ እንኳን #ለታላቁ_ሰማዕት_ለሰማይ_ጭፍራ ለተባለ #ለቅዱስ_ሚናስ_ቤተ_ ክርስቲያን_መርዩጥ በተባለ አገር #ለከበረችበት_ለቅዳሴ_ቤቱ_በዐል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                         ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የቅዱስ_ሚናስ_ቤተ_ክርስቲያን_ቅዳሴ_ቤት፦ ከዚህ አስቀድሞ የቅዱስ ሚናስ ሥጋ ተሠውሮ ይኖር ነበር ጌታችንም ሊገልጠው በወደደ ጊዜ ምክንያት አደረገ ይኸውም እንዲህ ነው ቅዱስ ሚናስ ሥጋው ተደፍኖ በሚኖርበት ኮረብታ አቅራቢያ በጎችን የሚያረባ አንድ ሰው በጎቹን እየጠበሸ ይኖር ነበር። ከዚያ እረኛ በጎች ውስጥ ደዌ ያለበት አንዱ በግ በዚያ በኮረብታው አጠገብ ባለ የጒድጓድ ውኃ ተጠምቆ ወዲያውኑ ከደዌው ዳነ እረኛውም አይቶ አደነቀ ሌሎችንም ደዌ ያለባቸውን አመጣ በዚያ ውኃም በታጠቡ ጊዜ ሁሉም ዳኑ። ❤ ከዚህም በኋላ ይህ በቦታው ሁሉ ታወቀ ደዌ ያለባቸውም ሁሉ እየመጡ አፈሩን ከውኃው ጋራ አንድ አድርገው ለውሰው በመቀባት ወዲያውኑ ይድኑ ነበሩ ምክንያቱን ግን አላወቁም። በዚያ ውኃና በአፈሩ በሽተኞችን እንደሚያድን የዚያ በግ ጠባቂ ወሬው በሮሙ ንጉሥ ዘንድ ተሰማ ለንሡም የቊስል ደዌ የታመመች ልጅ ነበረችው ወደ በግ ጠባቂውም ላካት እርሱም በጎቹን እንደ አዳናቸው አዳናት። እርሷም በተፈወሰች ጊዜ ከዚያ ቦታ ፈውስ የሚደረግበትን ምክንያት ታውቅ ዘንድ ወደደች። ❤ ከዚህም በኋላ ቅዱስ ሚናስ በሕልም ተገለጸላትና ሥጋዬ በዚህ ቦታ ተደፍኖ ስለሚኖር እነሆ አስቆፍረሽ ታወጪው ዘንድ እግዚአብሔር አዞሻል" አላት። ከእንቅልፍም በነቃች ጊዜ ቅዱስ ሚናስ እንዳዘዛት አደረገች የከበረ ሥጋውንም አወጣች በዚያም ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያን ሠራችለት ንጉሡም በዚያ ቦታ ከተማ እንዲሠሩ መኳንንቱንና ሹሞቹን አዘዛቸው ታላቅ ከተማም ተሠራች ስሟም መርዩጥ ተባለች። ❤ እግዚአብሔር ከቅዱስ ሚናስ ሥጋ ቊጥር የሌላቸው ድንቆችንና ተአምራትን ገለጠ። ሊቀ ጳጳሳቱም ከኤጲስቆጶሳቱ መጥቶ ቤተ ክርስቲያኒቱን በዛሬዋ ሰኔ 15 ዕለት አከበራት በዚያቺም ቦታ የሚሠሩ የድንቆችና የተአምሮች ወሬ በቦታው ሁሉ ተሰማ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ሚናስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሰኔ15 ስንክሳር።                                                   ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ውእተ አሚረ ተናገርኮሙ በራእይ ለደቂቅከ። ወትቤ እሬሲ ረድኤተ በላዕለ ኃይል። ወአልዐልኩ ኅሩይየ እምሕዝብየ"። መዝ 88፥19። የሚነበቡት መልዕክታት ኤፌ 7፥10-ፍ.ም፣ 1ኛ ዮሐ 4፥16-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 25፥1-13። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 13፥44-51። የሚቀደሰው ቅዳሴ የወልደ ነጎድጓድ የቅዱስ ዮሐንስ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ሚናስ የቅዳሴ ቤት በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።                     @Teamihokidusan
311
12
Немає тексту...
209
13
[ ስንክሳር ሰኔ - ፲፭ - ] .mp3
188
14
🕊 †  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡  † 🕊 እንኳን አደረሳችሁ 🕊 [ †  እንኩዋን ለሰማዕቱ ቅዱስ ሚናስ ዓመታዊ የቅዳሴ ቤት በዓል በሰላም አደረሳችሁ † ] 🕊 † ቅዱስ ሚናስ ምዕመን ሰማዕት † 🕊 ቅዱስ ሚናስ [ ማር_ሚና ] በምድረ ግብጽ ተወዳጅ ከሆኑ ሰማዕታት ዋነኛው ነው:: ልክ በሃገራችን ቅዱስ ጊዮርጊስ ልዩ ቦታ እንዳለው ሁሉ ግብፃውያን ማር ሚናስን ጠርተው አይጠግቡትም:: ምክንያቱም ከታላላቅ ሰማዕታት አንዱ በመሆኑና ዛሬም ድረስ ለጆሮና ለዐይን ድንቅ የሆኑ ተአምራትን ስለሚሠራ ነው:: በተለይ ለታመመ: ለደከመና ለተጨነቀ ፈጥኖ ደራሽ: ባለ በጐ መድኃኒት ፈዋሽና አማላጅ ነው:: ግብጽ ውስጥ ቅዱሱን የማያውቅ ሰው ካገኛችሁ እርሱ ኦርቶዶክሳዊ አይደለም ማለት ነው ሲባልም ሰምተናል:: በነገራችን ላይ ለቅዱሳን ተገቢውን ክብር በመስጠት: ታሪካቸውን በመጻፍ: በማጥናት: በመጽሔት: በፊልምና በመሳሰሉት ለሕዝብ በማስተዋወቅ ግብጻውያኑ ከእኛ ብዙ ርቀት ሒደዋል:: ዛሬ እንኩዋ የምንጠቀምበትን ስንክሳር ፹ [80] ከመቶ እጁን ያዘጋጁት እነርሱ ናቸው:: አባቶቻችንና እናቶቻችን ኢትዮዽያውያን ቅዱሳን ግን አብዛኞቹ ተረስተው ቀርተዋል:: መጽሐፈ ገድላቸውንም ብል በልቶታል:: ዛሬም የቤት ሥራው የእኛ ብቻ ነው:: ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ቅዱስ ሚናስ [ትርጉሙ ታማኝና ቡሩክ ማለት ነው] :- - በ፫ [3] ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበረ የደጋግ ክርስቲያኖች ልጅ - በልጅነቱ የቅድስና ሕይወትን ያጣጣመ - በዘመኑ ሰው እጅግ ተወዳጅ የነበረ - ሃብትን: ክብርን: ሥልጣንን ንቆ በጾምና በጸሎት የተወሰነ - በመጨረሻም በክርስቶስ ስላመነ አላውያን የገደሉት ሰማዕት ነው:: እርሱ ሰማዕት ከሆነ ከበርካታ ዘመናት በሁዋላ ምዕመናን ክቡር አካሉን ፈልገው ያጡታል:: የሚገለጥበት ጊዜ ሲደርስ ግን እርሱ የተቀበረበት ምድረ በዳ የበጐችና የእረኞች መዋያ ነበርና ተአምራትን አደረገ:: አንድ እረኛ በጐቹ ድውያን ሆኑበት:: በዚያ ሰሞን ከቅዱሱ መቃብር ላይ ጸበል ፈልቆ ነበርና እረኛው ተርታ ውሃ ነው ብሎ በጎቹን ሲያጠጣቸው አንዱ ድውይ በግ ወደ ጸበሉ በመዘፈቁ ዳነ:: በዚህ የተገረመው እረኛ ሁሉንም የታመሙ በጐቹን አምጥቶ ነከራቸው:: እነርሱም ተፈወሱ:: ይህ ዜና በምድረ ግብፅ ሲሰማ ድውያን ሁሉ እየመጡ ይፈወሱ ገቡ:: ግን እነሱም ሆነ እረኛው ምክንያቱን ማወቅ አልቻሉም:: ነገሩ በሮም ንጉሥ ዘንድ ሲሰማ ሴት ልጁን ከሠራዊቱ ጋር ላካት:: ምክንያቱም እርሷ ከብዙ ዘመን ጀምራ መጻጉዕ ነበረችና ፈውስን አጥታ ነበር:: መጥታ ተጠመቀች: ፈጥናም ተፈወሰች:: እርሷ ግን እንደ ሌሎች ያዳናትን ማንነት ሳታውቅ መሔድ አልፈለገችምና ሱባዔ ገባች:: ቅዱስ ሚናስ በሌሊት ራዕይ መጥቶ ሥጋው እንዳለ ነገራት:: እርሷም መሬቱን አስቆፍራ የቅዱሱን አካል በክብር አስወጣች:: ከዚያም በንጉሡ ትዕዛዝ ምድረ በዳው ከተማ እንዲሆን ተቀየረ:: ስሙም " መርዩጥ " ተባለ:: ጸበሉ የነበረበት ቦታም ላይ የማር ሚናስ ቤተ_ክርስቲያን ታንጾበት በዚህች ዕለት ቅዳሴ ቤቱ ተከብሯል:: አምላካችን ከቅዱሱ ሰማዕት በረከትን ይክፈለን:: 🕊 [ †  ሰኔ ፲፭ [ 15 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ] ፩. ቅዱስ ሚናስ [ማር ሚና] ሰማዕት [ቅዳሴ ቤቱ] [ † ወርሐዊ በዓላት ] ፩. ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ ፪. ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ [አፈ በረከት] ፫. ቅድስት እንባ መሪና ፬. ቅድስት ክርስጢና " ፈጥኜ ወደ አንተ እንድመጣ ተስፋ አድርጌ ይሕን እጽፍልሃለሁ:: ብዘገይ ግን በእግዚአብሔር ማደሪያ ቤት መኖር እንዴት እንደሚገባ ታውቅ ዘንድ እጽፍልሃለሁ:: ቤቱም የእውነት ዓምድና መሠረት የሕያው እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ነው:: እግዚአብሔርንም የመምሠል ምሥጢር ያለ ጥርጥር ታላቅ ነው:: " [፩ጢሞ.፫፥፲፬] (3:14) † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
217
15
Немає тексту...
245
16
🕊                        💖                        🕊 🕊   [       ጽ ዮ ን    እ ና ታ ች ን     ]    🕊 🌺                       🕊                        🌺 የእመቤታችን ምሳሌዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ፦ ፯. [ ዕፀ ገነት [ የገነት ዛፍ ] Tree of Heaven  ] የሕይወት ፍሬ ክርስቶስን በድንግልና የወለደች ቅድስት ድንግል ማርያም በገነት ውስጥ ባሉት ዕፀዋት ኹሉ እንደምትመሰል በርካቶች ሊቃውንት በየድርሳናቸው ገልጸዋል፡፡ እነዚኽም በገነት ያሉ አዝርዕት ፣ አትክልት ፣ ዕፀዋት በዚኽ ዓለም ካሉት የተለዩ ናቸው ፤ ቅጠላቸው ሰፋፊ ነው። ዐሥራ ኹለት ክንድ ይኾናል ፧ መዐዛቸው የመንፈቅ መንገድ ኼዶ ይሸታል ፤ ፍሬያቸው የጋን መክደኛ ያኽላል ፤ ጣዕማቸው ነፍስን ከሥጋ ይለያል ፤ አላምጠው እስኪውጧቸው ድረስ ፍሬ ይተካሉ ፤ ጥራታቸው እንደ መስታዮት ፊትን ያሳያል። [ሕዝ ፵፯፥፲፪-፲፫፤ ራእይ ፳፪፥፪-፫]፡፡ የገነት ዛፍ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ስትኾን ፤ የማይጠወልገው ቅጠሏ ለዘላለም የማይለወጠው የድንግልናዋ ፤ የዛፏ ፍሬ የልጇ የፍሬ ሕይወት የክርስቶስ ምሳሌ ነው ፤ ያ ፍሬ ሲቈርጡት እየተካ እንደማያልቅ ኹሉ ለቤዛ ብዙኀን የተሰጠ የጌታ ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ ዕለት ዕለት እየተሠዋ ሲሰጥ የመኖሩ ምሳሌ ነውና ፤ ይኽነን ልዩ ምስጢር የተረዱ ሊቃውንት ይቺ ነቢዩ ሔኖክ ያያት በሱራፊ መልአክ የምትጠበቅ የገነት ዛፍ የድንግል ማርያም ምሳሌ መኾኗን መስክረዋል። ኢትዮጵያዊው ሊቅ አባ ጊዮርጊስም በእንዚራ ስብሐት መጽሐፉ ላይ ፦ [ እመቤቴ ማርያም ሆይ በሔኖክ መጽሐፍ ውስጥ ትእዛዟ የተጻፈ ፤ የመዐዛ ዕፀዋት የሚከቧት የትንቢት ተራራ ነሽ ] በማለት በእውነት ምሳሌዋ መኾኑን ሲያስተምር ፤ የማሕሌተ ጽጌ ደራሲያን ሊቃውንት አባ ገብረ ማርያም ዘደብረ ሓንታና አባጽጌ ድንግል በማሕሌተ ጽጌ መጽሐፋቸው ፦ [ ሱራፊ መልአክ የእሳት ጦርን ይዞ የሚጠብቅሽ ፤ መዐዛሽንም ጸሐፊ ሔኖክ ያሸተተልሽ የማትረግፊ የማትጠፊ የገነት ዛፍ ማርያም ] በማለት ሔኖክ ያያቸው የገነት ዛፎች በእውነት የድንግል ማርያም ምሳሌ መኾናቸውን ተናግረዋል፡፡ ዳግመኛም እነዚኹ ሊቃውንት የቅድስት ድንግልን የመዐዛ ንጽሕናዋን፣ የመዐዛ ቅድስናዋን ፣ የመዐዛ ምግባሯን ድንቅነት በገነት ውስት ባሉት ልዩ ሽታን በሚሸቱ በገነት ዛፎች ሲመስሉ ፦ [ ለአፍንጫ መዐዛን የምትሰጪ የገነት ዛፍ ማርያም ሆይ ፤ ልጅሽ በክንዱ ዐቅፎ በአፉ እየሳመ በቀኙ ሊያሳርፍሽ ባሳረገሽ ጊዜ ፤ አንቺን ለመቀበል ክንፍ ለክንፍ እየተጋጩ እልፍ አእላፋት መላእክት ወረዱ ] በማለት የመዐዛዋን ታላቅነት መስክረውላታል፡፡ ኢትዮጵያዊዉ ቄርሎስ የተባለው ሊቁ አባ ጊዮርጊስም ቅድስት ድንግል ማርያም አማናዊት ዕፀ ገነት መኾኗን በአርጋኖን መጽሐፉ ❝ዕፀ ገገት ዘበጽጌሃ ንትሜዐዝ ወእምፍሬሃ ንሴሰይ ወታሕት አዕጹቂሃ ናጸልል… ኦ ድንግል ዖመ ገነት ዘተከላ የማነ እግዚአብሔር ወአጽገያ ኀይለ መንፈስ ወአፍረያ ጽላሎተ አብ ❞ [ በአበባዋ የምንሻተትባት ፤ ከፍሬዋም የምንመገባት ፤ በሥሯም [ በቅርንጫፎቿም ] የምንጠለልባት የገነት ዕንጨት ናት… ድንግል ሆይ የእግዚአብሔር ቀኝ የተከላት የመንፈስ ቅዱስ ኀይል እንድታብብ ያደረጋት ፣ የአብ ጥላ እንድታፈራ ያደረጋት የገነት ዛፍ ነሽ ] በማለት በሥልጣነ እግዚአብሔር ተጠብቃ በሃይማኖት ፣ በምግባር ፣ በንጽሕና ፣ በቅድስና ጸንታ በግብረ መንፈስ ቅዱስ አምላክን አፍርታ የተገኘች አማናዊት ዕፀ ገነት የመኾኗን ምስጢር አጕልቶ አሳይቷል [ሉቃ ፩፥፴፫-፵፪]፡፡ 🩵                          †                          🩵 ❝ ሰው እናታችን ጽዮን ይላል ፥ በውስጥዋም ሰው ተወለደ ፤ እርሱ ራሱም ልዑል መሠረታት።  ❞ [ መዝ.፹፯፥፭ ] ════════════════                            †††               ✟ 𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y ✟ 🕊                       💖                      🕊
268
17
Немає тексту...
186
18
💖                     🕊                      💖       [    ቤተ ክርስቲያንን እንወቅ   ]            [  ክፍል አሥራ ስድስት  ]                   💖                     🕊                      💖                               [   መቅደስ የእግዚአብሔር መገለጫ !   ] 🕊 ቤተ መቅደስ የእግዚአብሔር መገለጫ ፣ የሰማይና የምድር የጋራ ዛቢያ ነው ወይንም ምድር [ መሠረት ] ሰማይን ጣሪያ ዓምዱ ቤተ መቅደስ ነው:: ያለ ዓምድ ቤት እንዳይቆም ያለ ቤተ መቅደስም ሰማይና ምድር አንድነት የላቸውምና እንደ ቤተ መቅደስ በምድር ላይ የሚያስፈራ ክብር ያለውም ቦታ የለም። " ይህ ሥፍራ እንዴት ያስፈራ ... ! " ቤተ ክርስቲያን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደሙ ዋጅቶ የመሠረታት ፣ በክርስቶስ ክርስቲያን ለተባልን በሙሉ መሰብሰቢያችን የተቀደሰች ቤታችን ናት፡፡ ቤተ ክርስቲያን ስንልም ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ፣ የክርስቲያን ወገን ፣ የምእመናን አንድነት ወይንም ማኅበረ ምእመናን እንዲሁም እያንዳንዱ ምእመናን ማለታችን ነው፡፡ [   ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን    ] ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አምልኮተ እግዚአብሔር የምንፈጽምባት የእግዚአብሔር ማደሪያ ናት ፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ቅዱሳን መላእክት ፈጣሪያቸውን የሚያገለግሉባት የክብሩ መገለጫ የሰማያዊት ኢየሩሳሌም ምሳሌ በመሆኗ አባቶቻችን በአሠራሯ ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያደርጉ ሲሆን የሕንፃዋ ቤተ ክርስቲያን አሠራርም በሦስት ዓይነት ቅርጽ ሊሆን ይችላል፡፡ ፩. [  ክብ   ] በፊልጵስዩስ የተሠራችው የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን ክብ ቅርጽ ነበራት፡፡ የሙሉ ክብነቷ ትርጓሜም የፍጹምነቷ ምልክት ነው ፤ በዚህም መሠረት በአብዛኛው ቤተ ክርስቲያናት በክብ ቅርጽ ይታነጻሉ ፤ የዚህ ዓይነት ሕንጻ ቤተ ክርስቲያንም ዙሪያው ክብ ሆኖ ውስጡ በሦስት የተከፈለ ሰሆን ሦስት በሮችም አሉት ፤ ቤተ ንጉሥ ቅርጽም ይባላል ፤ አንድ ጉልላት ሲኖረው ከጉልላቱም ላይ መስቀል ይኖራል፡፡ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚሣሉት ቅዱሳንም ዓይንና ፊታቸው ክብ ሆኖ የሚሣለው ሃይማኖትን ከምግባር አዋሕደው የተገኙና ከሕግ በላይ የሆኑ ፍጹማን መሆናቸውን ለመግለጽ ነው፡፡ ፪. [ ሰቀላማ ወይም ሞላላ ቅርጽ  ማዕዘን  ቅርጽ ] የዚህ ዓይነት የቤተ ክርስቲያን ሕንጻ አሠራር ጠቢቡ ሰሎሞን ያሠራውን ቤተ-መቅደስ መሠረት ያደረገ ነው ፤ ለዚህ ምሳሌ በሀገራችን የአክሱም ጽዮን ፣ የጎንደሩ ደብረ ብርሃን ሥላሴ እና ደብረ ዳሞ ፣ ዐፄ ዮሐንስ በደብረ ሊባኖስ ገዳም ያሠሩት የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ዐሥራ ስምነት ጉልላት ያላቸውን ሰቀላማ ቅርጽ ያላቸውን አብያተ ቤተ ክርስቲያናትን መጥቀስ ይቻላል ፤ በሞላላ ቅርጽ የታነፁ አብያተ ቤተ ክርስቲያናት መሠረታቸው የመስቀል ቅርጽ ያለው በመሆኑ በዚህ ቅርጽ የመታነፃቸው ምሥጢር ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ሰው ልጆች ኃጢአት በመስቀል ላይ የፈጸመውን የድኅነት ሥራ እንድናስብበት ነው፡፡ ለሰው ልጆች ሲል መከራ ተቀብሎ ፣ ተሰቅሎና ሞትን ድል አድርጎ ማረጉን ያመለክታል፡፡ ከላይ የጠቀስናቸው ሰቀላማ ቅርጽ አብያተ ክርስቲያናት በተጨማሪ መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያንና ምስካየ ኀዙናን መድኃኔዓለም ገዳማት ለሰቀላማ ቅርጽ አብያተ ክርስቲያናት በምሳሌነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ ፫.   [   ዋሻ ቅርጽ   ] የዚህ ዓይነት ሕንፃ ቤተ ክርስቶያናት ሰማዕታት ከዓላማውያን ነገሥታት ሸሽተው በዋሻ ሲሸሸጉ የጀመሩት አሠራር ዓይነት ነው፡፡ አንድ በርም አለው ፤ በአብዛኛውም ጊዜ በውስጡ ያሉትን ክፍሎች በመጋረጃ ይከፈላል፡፡ ሆኖም ግን ጉልላት የለውም ፤ ተራራ በመፈልፈል በዋሻ ውስጥ ሲሆን ለብቻው የቆመ ድንጋይን [አለትን] በመፈልፈል ሊሠራ ይችላል ምሳሌ ፦ አቡነ ሀብተ ማርያም ገዳም ፣ አዳዲ ማርያም ፣ የቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ምሳሌዎች ናቸው፡፡ " ይህ ሥፍራ እንዴት ያስፈራ ፤ ይህ ሥፍራ የእግዚአብሔር ቤት ነው እንጂ ሌላ አይደለም ይህም የሰማይ ደጅ ነው::" [ ዘፍ.፳፰፥፲፮ ] [ ይቆየን ] ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፥ ወለወላዲቱ ድንግል ፥ ወለመስቀሉ ክቡር፡፡ [ ይቆየን ] ════════════════                            †††               ✟ 𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y ✟ 🕊                       💖                      🕊
218
19
Немає тексту...
245
20
በቅድስና .mp3
233