fa
Feedback
ገድለ ቅዱሳን ዘእለታት

ገድለ ቅዱሳን ዘእለታት

رفتن به کانال در Telegram

ከኢ/ኦ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ የተገኙ የእለቱ የቅዱሳን(የጻድቃን) አባቶቻችን እና የቅዱሳን(የጻድቃን) እናቶቻችን ጽድቅ እና ገድላት ይነገርበታል። በመሀልም ጠቃሚና አስተማሪ ነው የምንላቸውን ታሪኮች ወደእናንተ የምናቀርብ ይሆናል። https://telegram.me/gedlekdusan

نمایش بیشتر
1 164
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
+930 روز

در حال بارگیری داده...

ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
ژوئیه '26
ژوئیه '26
+27
در 2 کانال‌ها
ژوئن '26
+54
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '26
+202
در 1 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '26
+66
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '26
+64
در 1 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '26
+39
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '26
+59
در 2 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '25
+54
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '25
+45
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '25
+39
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '25
+18
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '25
+28
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '25
+23
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '25
+44
در 1 کانال‌ها
Get PRO
مه '25
+22
در 1 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '25
+11
در 1 کانال‌ها
Get PRO
مارس '25
+22
در 2 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '25
+11
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '25
+36
در 1 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '24
+33
در 1 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '24
+65
در 1 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '24
+55
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '24
+45
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '24
+41
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '24
+16
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '24
+10
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '24
+9
در 1 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '24
+13
در 1 کانال‌ها
Get PRO
مارس '24
+27
در 1 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '24
+39
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '24
+28
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '23
+41
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '23
+11
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '23
+19
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '23
+15
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '23
+72
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '23
+11
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '23
+12
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '23
+15
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '23
+4
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '23
+9
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '23
+14
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '23
+20
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '22
+30
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '22
+18
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '22
+18
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '22
+84
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '22
+140
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '22
+22
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '22
+14
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '22
+17
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '22
+20
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '22
+27
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '22
+12
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '22
+6
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '21
+18
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '21
+7
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '21
+17
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '21
+18
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '21
+243
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
19 ژوئیه+2
18 ژوئیه+1
17 ژوئیه+2
16 ژوئیه0
15 ژوئیه+1
14 ژوئیه+1
13 ژوئیه0
12 ژوئیه+2
11 ژوئیه0
10 ژوئیه0
09 ژوئیه+1
08 ژوئیه0
07 ژوئیه+2
06 ژوئیه+2
05 ژوئیه+1
04 ژوئیه+7
03 ژوئیه+1
02 ژوئیه+1
01 ژوئیه+3
پست‌های کانال
2
✝††† እንኳን ለአባታችን ቅዱስ ብስንድዮስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። ✝ ✝††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!✝ ††† ††† ቅዱስ ብስንድዮስ ጻድቅ ††† => ቅዱስ ብስንድዮስ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ድንቅ ሥራ ከሠሩት እንደ አንዱ ሆኖ ይዘከራል:: ቅዱሱ ግብጻዊ ሲሆን በልጅነቱ ወደ ትምሕርት ቤት ገብቶ ቅዱሳት መጻሕፍትን ተምሯል:: የሚገርመው የብሉይም ሆነ የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትን በሙሉ ያጠናቸው በቃሉ ነበር:: በእርግጥ ይሕንን ማድረግ የቻሉ በርካታ የሃገራችን ሊቃውንት ዘንድሮም አሉ:: ልዩነቱ ግን ወዲህ ነው:: ቅዱስ ብስንድዮስ መጻሕፍቱን ያጠናቸው ለሕይወት እንጂ ለእውቀት አልነበረምና ሁሌም ነግቶ እስከ ሚመሽ እያንዳንዱን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል እያጣጣመ ይጸልይ ነበር:: ይሕንን ሲያደርግ ደግሞ ባጭር ታጥቆ ጫማውን አውልቆ: በባዶ ሆዱ ቁሞ ነው:: ታዲያ እያንዳንዱን የመጽሐፍ ክፍል ሲጸልይ ነቢይ ቢሆን ሐዋርያ ወደ እርሱ ይወርድለት ነበር:: ለምሳሌ ዘፍጥረትን ሲጸልይ ሊቀ ነቢያት ሙሴ ይመጣና ከፊቱ ተቀምጦ ይሰማዋል:: ትንቢተ ኢሳይያስ ላይ ሲደርስ ኢሳይያስ: ወንጌለ ማቴዎስ ላይ ሲደርስ ቅዱስ ማቴዎስ ይመጡና ደስ እያላቸው ያደምጡት ነበር:: አንዱ ነቢይ: ወይ ሐዋርያ ሲወጣ ቅዱስ ብስንድዮስን ባርኮ ሌላኛውን ተክቶ ነው:: በዚህ ምክንያት የቅዱሱ ሕይወት በምድር እያለ ሰማያዊ ሆነ: ሰማንያ አንዱን አሥራው መጻሕፍት የጻፉ ቅዱሳንን ለማየት በቃ: በእጆቻቸውም ተባረከ:: የቅዱስ ብስንድዮስ ቀጣይ የሕይወቱ ተግባር ብሕትውና ሆነ:: ዓለምንና ግሳንግሷን ትቶም ወደ በርሃ መነነ:: በአጽንዖ በዓት: በጾምና በጸሎት: በትሕርምትም ተጋደለ:: በየደረሰበት ቦታ ሁሉ እግዚአብሔር በእጆቹ ድንቅ ተአምር ይሠራ ነበር:: ብዙ ድውያንን ፈወሰ: አጋንንትንም ከአካባቢው አሳደደ:: በእነዚህ ሁሉ ጊዜያት ግን ስዕለት ስላለበት ሴቶችን ላለማየት ይጠነቀቅ ነበር:: በሆድ ሕመም ትሰቃይ የነበረችና ጥሪቷን በመድኃኒት የጨረሰች አንዲት ሴት ስለ ቅዱሱ ዝና ትሰማለች:: ችግሩ ግን እርሱ ከውዳሴ ከንቱና ከሴት የሚርቅ ነውና እንዴት ብላ ታግኘው? አንድ ቀን ከበዓቱ አካባቢ ተደብቃ ውላ ሲመጣ የልብሶቹን ዘርፍ ለመንካት በእምነት አሰበች:: ልክ ከበዓቱ ሲዘልቅ ስሉጥ(ፈጣን) ነበርና ገና እንዳያት ሩጦ አመለጣት:: እንዳትከተለው ድውይ ናትና አልቻለችም:: አዝና ዝቅ ስትል ግን የረገጠውን ኮቲ ተመለከተች:: በፍጹም ልቧ: በእምነት "የጻድቁ አምላክ ማረኝ" ብላ ከአፈሩ ቆንጥራ በላች:: ደቂቃ አልቆየችም:: ፈጥና ከደዌዋ ዳነች:: እንደ እንቦሳ እየዘለለች ወደ ከተማ ሔዳ ተአምሩን ተናገረች:: ከእነዚህ ዘመናት በኋላ በእግዚአብሔር ፈቃድ ቅፍጥ(Qift) በምትባል ሃገር ጵጵስናን (እረኝነትን) ተሹሟል:: ወደ ከተማ ሲገባ የቀደመ ተጋድሎውን ቸል አላለም:: ይልቁኑ ይተጋ ነበር እንጂ:: ከብቃት መዓርግ ደርሷልና ሲቀድስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በገሃድ ያየው: ሠራዊተ መላእክትም ይከቡት ነበር:: ሕዝቡ ሊቆርቡ ሲመጡ የእያንዳንዱ ኃጢአት በግንባራቸው ተጽፎ ይታየው ነበር:: የበቁትን እያቀበለ: ያልበቁትን እየመከረና ንስሐ እየሰጠ ይመልሳቸዋል:: እንዲሕ በጽድቅ: በሐዋርያዊ አገልግሎትና በንጽሕና ተመላልሶ ቅዱስ ብስንድዮስ በዚህች ቀን ዐርፏል:: ቅዱስ ብስንድዮስ ካረፈ በኋላ ደቀ መዝሙሩ ከመግነዙ ጥቂት ቆርጦ አስቀርቶ ብዙ ድውያንን ፈውሶበታል:: ††† ቸር አምላክ ለአባቶቻችን የሰጠውን ጸጋ ለእኛ ለባሮቹም አይንሳን:: ከቅዱሱ በረከትም ያድለን:: ††† ሐምሌ 13 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ቅዱስ ብስንድዮስ ሊቅ ወጻድቅ 2.ቅዱስ አሞን ሰማዕት (ዘሃገረ ጡህ) ††† ወርኀዊ በዓላት 1.እግዚአብሔር አብ 2.ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላእክት 3.ዘጠና ዘጠኙ ነገደ መላእክት 4.ቅዱስ አስከናፍር 5.አሥራ ሦስቱ ግኁሳን አባቶች 6.ቅዱስ አርሳንዮስ ጠቢብ ገዳማዊ 7.አቡነ ዘርዐ ቡሩክ ††† "አንተ ግን በተማርህበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር:: ከማን እንደተማርኸው ታውቃለህና:: ከሕፃንነትህም ጀምረህ ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን ቅዱሳት መጻሕፍትን አውቀሃል:: የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጐ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምሕርትና ለተግሣጽ: ልብንም ለማቅናት: በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል::" ††† (፪ጢሞ. ፫፥፲፬) ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር ††† ከኢ/ኦ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ የተገኙ የእለቱ የቅዱሳን(የጻድቃን) አባቶቻችን እና የቅዱሳን(የጻድቃን) እናቶቻችን ጽድቅ እና ገድላት ይነገርበታል። በመሀልም ጠቃሚና አስተማሪ ነው የምንላቸውን ታሪኮች ወደእናንተ የምናቀርብ ይሆናል። https://telegram.me/gedlekdusan
46
3
ናዛዚትነ እም ኀዘን ወኃይለ ዉርዙትነ እም ርሳን በማኅጸንኪ ተጸዉረ ብሉየ መዋዕል ሕፃንኦ ማርያም ተስፋ ለቅቡጻን በጊዜ ጸሎት ወእጣን ወበ ጊዜ ቅዱስ ቁርባን ለናዝዞትነ ንዒኀበ ዝ መካን
  ናዛዚትነ እም ኀዘን ወኃይለ ዉርዙትነ እም ርሳን በማኅጸንኪ ተጸዉረ ብሉየ መዋዕል ሕፃንኦ ማርያም ተስፋ ለቅቡጻን በጊዜ ጸሎት ወእጣን ወበ ጊዜ ቅዱስ ቁርባን ለናዝዞትነ ንዒኀበ ዝ መካን        
85
4
✨🤍 12 ቅድስት ሚካኤል + ሰንበት(የጌታ ቀን) 🤲መልካም እለተ ሰንበት 🤲
99
5
sticker.webp
96
6
sticker.webp
83
7
+2
#ኦ_ሚካኤል ኦ ሚካኤል መላዕከ ሃይል/2/ ስንጠራህ ድረስልን ኦ ሚካኤል መላዕከ ሃይል ዘንዶው ጠላታችን ከፊታችን ቆሟል ከባህር ሊጥለን አድፍጦ ያደባል የመላዕክት አለቃ እርዳን በፀሎትህ ጥበቃህ አይራቀን በቀን በሌሊት/2/ ክርስትና ኑሮ እጅጉን ከብዶናል የጌታን ውለታ ፍቅሩን ዘንግተናል አፅናኙ መልዐክ ከፊታችን ቅደም በመንገድህ ምራን እንድንሆን ሰላም/2/ የጌታ ባለሟል የህዝብ እረኛ ባህሩን አሻግረን ቅረበን ወደ እኛ ከጌታህ አማልደን መልዐከ ራማ የልጆችህን ቃል ድምፃችንን ስማ በሚያስፈራው ዘመን ሰላም በሌለበት ባስጨናቂው ጊዜ ፍቅር በጠፋበት የፍቅርን ወንጌል ቃሉንም ስበከን ሚካኤል ተራዳን ድረስም አፅናናን ዘ/ዲ ሱራፌል ስዩም
116
8
+2
بدون متن...
79
9
✞✞✞✝️ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ✝️ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞ ❖ ✝️ሐምሌ ፲፪✝️ ❖ ✞✞✞ እንኩዋን ለቅዱስ "ሚካኤል ሊቀ መላእክት" የተአምር በዓልና ለሰማዕቱ "አባ ሖር" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞ +*" ተአምረ ቅዱስ ሚካኤል "*+ =>ቅዱስ መጽሐፍ እንደ ነገረን በዚህች ዕለት የመላእክት ሁሉ አለቃቸው: የቅዱሳንም ረዳታቸው የሆነው ደጉ መልአክ #ቅዱስ_ሚካኤል ንጉሡን ሕዝቅያስን ግሩም በሆነ ተአምር ከከተማው #ኢየሩሳሌም ጋር ታድጐታል:: ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ:- +ከመድኃኒታችን #ክርስቶስ ልደት 700 ዓመታት በፊት #ሕዝቅያስ የሚባል ንጉሥ በይሁዳ ላይ ነግሦ ነበር:: ደጋጉ #ዳዊትና #ሰሎሞን ካረፉ በሁዋላ የሕዝቅያስን ያክል ቅን እና የእግዚአብሔር ሰው በእሥራኤል ላይ አልነገሰም:: ንጉሡ ጣዖት አምልኮን ነቃቅሎ አጥፍቶ ሕዝቡ እግዚአብሔርን ብቻ እንዲያመልክ አድርጐም ነበር:: +ነገር ግን ቅዱስ ሕዝቅያስ በነገሠ በ14ኛው ዓመት የአሕዛብ (የአሦር) ንጉሥ ሰናክሬም በጠላትነት ተነሳበት:: ወደ አካባቢውም መጥቶ: ከቦ አስጨነቀው:: ሰናክሬም በጦር እጅግ ኃይለኛ ነበር:: በዚያውም ላይ ጦር የሚመዙ ከ185,000 በላይ ብርቱ ተዋጊዎች ነበሩትና ሕዝቅያስ እንደማይችለው ተረድቶ መልእክተኛ ላከበት:: +"እገብርልሃለሁ:: የፈለግከውንም እሰጥሃለሁ:: ሃገሬን ግን አታጥፋ:: ኢየሩሳሌምን አታቃጥል:: ሕዝቤንም አትግደል" በሚል ለመነው:: እጅ መንሻ ግብሩንም ከከተማዋ የተገኘውን ወርቅና ብር ሁሉ ጭኖ ላከለት:: +ሰናክሬም ግን ሰይጣን ያደረበት ነውና የሕዝቅያስን ልመና ወደ ጐን ብሎ የእሥራኤልን አምላክ : ቅዱስ ስሙንም ተገዳደረ:: ለሕዝቅያስም "ከእኔ እጅ የሚያድንህ ማነው? ሕዝቡንም #እግዚአብሔር ያድናል ብለህ አታታልላቸው" ሲል ላከበት:: ቅዱስ ሕዝቅያስ በዚህ ጊዜ የፈጣሪው ስም ሲቃለል ሰምቷልና ፈጽሞ አዘነ:: +መልእክተኞችን ወደ ነቢዩ #ቅዱስ_ኢሳይያስ ልኮ እርሱ ወደ ቤተ መቅደስ ገባ:: በእግዚአብሔር ፊት ልብሱን ቀድዶ ማቅ ለበሰ:: ስለ ኢየሩሳሌምና ሕዝቡም ፈጽሞ አለቀሰ:: በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር የሰናክሬምን መገዳደርና የሕዝቅያስን ልመና ሰምቷልና በኢሳይያስ አንደበት እንዲሕ አለ:- "ስለ ባሪያየ ስለ #ዳዊት ከተማዋን አድናታለሁ::" +በዚያች ሌሊትም ድንቅ መልአክ #ቅዱስ_ሚካኤል ከሰማያት በግርማ ወረደ:: ወደ ሰናክሬም የጦር ሠፈር ደርሶ አንድ ጊዜ የእሳት ሰይፉን መዝዞ ቢያሳያቸው ከአሕዛብ ሠራዊት 185 ሺ ኃያላን እንደ ቅጠል ረገፉ:: በለኪሶ የነበረው ሰናክሬም በጧት ቢነሳ ሠራዊቱ ሁሉ ወደ አስከሬን ክምር ተቀይሯል:: +በድንጋጤ ወደ #ነነዌ ሒዶ ወደ ጣዖት ቤቱ ሲገባ የራሱ ልጆች (አድራማሌክና ሳራሳር) ገደሉት:: ትዕቢተኛው ሰናክሬም ለአሕዛብ ሁሉ መዘባበቻ ሆነ:: ቅዱስ ሕዝቅያስ ግን በፈጣሪው ታምኗልና ቅዱስ ሚካኤል ሞገስ ሆኖ የዓለም ነገሥታት ሁሉ ፈሩት:: (መጽሀፈ ነገሥት ካልዕ. 18:13, 19:1) +*" ቅዱስ አባ ሖር ሰማዕት "*+ =>ዳግመኛ በዚህ ቀን #አባ_ሖር ሰማዕቱ ይታሠባል:: +ቅዱሱ:- ¤ስርያቆስ በምትባል የግብጽ አውራጃ ተወልዶ ያደገ: ¤ገና በልጅነቱ መንኖ እግዚአብሔርን ያገለገለ: ¤ዘመነ ሰማዕታት በመጣ ጊዜም በመኮንኑ ፊት ቀርቦ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ያመነ: ¤ከመኮንኑም ብዙ ስቃይ የደረሰበት: ¤ብዙ ተአምራትን በመስራቱ ያሰቃየው የነበረውን መኮንን ወደ ክርስትና መልሶ ለሰማዕትነት ያበቃ አባት ነው:: +እርሱም የሰማዕትነትን ክብር በእጅጉ ሽቷታልና ወደ ሌላ ሃገር ሒዶ በዚህች ቀን አንገቱን ተሰይፎ የክብርን አክሊል ተቀዳጅቷል:: በሐዋርያዊ አገልግሎቱ ያሳመናቸው 127 ወንዶችና 20 ሴቶችም አብረውት ተሰይፈዋል:: =>እግዚአብሔር በሊቀ መላእክት ክንፍ ሃገራችንን ከአሕዛብ ስውር ጦር ይጠብቅልን:: ከሰማዕቱም በረከት ያሳትፈን:: =>ሐምሌ 12 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት= 1.ቅዱስ ሕዝቅያስ ንጉሥ 2.ቅዱስ ኢሳይያስ ልዑለ ቃል 3.ቅዱስ አባ ሖር ሰማዕት 4."147" ሰማዕታት (የአባ ሖር ማሕበር) =>ወርሐዊ በዓላት 1.ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት 2.ቅዱስ ላሊበላ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ) 3.ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ 4.ቅዱስ ድሜጥሮስ 5.ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ 6.ቅዱስ ቴዎድሮስ ምሥራቃዊ (ሰማዕት) 7.ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ 8.አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ =>+"+ እግዚአብሔር ይላል:- ስለ እኔም ስለ ባሪያየም #ስለ_ዳዊት ይህችን ከተማ አድናት ዘንድ እጋርዳታለሁ:: በዚያችም ሌሊት የእግዚአብሔር መልአክ ወጣ:: ከአሦራውያንም ሠፈር መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ ገደለ:: ማለዳም በተነሱ ጊዜ እነሆ ሁሉ በድኖች ነበሩ:: +"+ (መጽሀፈ ነገሥት ካልዕ. 19:34) <<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>> ከኢ/ኦ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ የተገኙ የእለቱ የቅዱሳን(የጻድቃን) አባቶቻችን እና የቅዱሳን(የጻድቃን) እናቶቻችን ጽድቅ እና ገድላት ይነገርበታል። በመሀልም ጠቃሚና አስተማሪ ነው የምንላቸውን ታሪኮች ወደእናንተ የምናቀርብ ይሆናል። https://telegram.me/gedlekdusan
92
10
ዲያብሎስ በእውቀት፣ በጥበብ፣ በድንግልና እና በትሕትና ይቀናል፡፡ ስለዚህም አላዋቂነትን፣ ዝሙትንና ትዕቢትን በያዘው ክፉ አስተሳሰብ በዓለም ውስጥ ያስፋፋል፡፡ ሰሎሞንን ከጠቢብነቱ መልሶ በኃጢአት ጥ
ዲያብሎስ በእውቀት፣ በጥበብ፣ በድንግልና እና በትሕትና ይቀናል፡፡ ስለዚህም አላዋቂነትን፣ ዝሙትንና ትዕቢትን በያዘው ክፉ አስተሳሰብ በዓለም ውስጥ ያስፋፋል፡፡ ሰሎሞንን ከጠቢብነቱ መልሶ በኃጢአት ጥሎታል፡፡ ወደፊትም የተሳሳተ እውቀት መዝራቱን ይቀጥላል፡፡ «ሰነፍ በልቡ እግዚአብሔር የለም ይላል፡፡» መዝ 13:1፡፡ ዝሙትም ዓለሙን ሁሉ የሚዋጋበት አደገኛ መሣሪያው ነው፡፡ ትዕቢትም ሌሎች ኃጢአቶችን ሁሉ ያሸነፉትን ሰዎች የሚጠምድበት ጠንካራ የኃጢአት መረብ ስለሆነ ብዙዎችን በዚህ ጥሏል፡፡
151
11
እግዚአብሄ የወደቁትን ያነሳል
እግዚአብሄ የወደቁትን ያነሳል
122
12
بدون متن...
97
13
እግዚአብሄ የወደቁትን ያነሳል+1
እግዚአብሄ የወደቁትን ያነሳል
1
14
✝ †††እንኳን ለጻድቅና ሰማዕት ቅዱስ ዮሐንስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። ✝ ††† ✝ †††በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ✝ ††† ✝ †††ቅዱስ ዮሐንስ ጻድቅ ወሰማዕት✝ ††† ††† ቅዱስ ዮሐንስ በቀደመው ዘመን ከነበሩ ታላላቅ አበው አንዱ ሲሆን ሃገረ ሙላዱ መርባስ ትባላለች:: ወላጆቹ እግዚአብሔርን የሚወዱ: ምጽዋትን የሚያዘወትሩና በበጐው ጐዳና የሚኖሩ ነበሩ:: ነገር ግን ልጅ በማጣታቸው ምክንያት ፈጽመው ያዝኑ: ይጸልዩም ነበር:: በተለይ ለመጥምቁ ዮሐንስ ልዩ ፍቅር ስለ ነበራቸው ዝክሩን ይዘክሩ: በስሙም ይማጸኑ ነበርና መጥምቁ ሰማቸው:: ወደ ፈጣሪውም ልመናቸውን በማድረሱ መልክ ከደም ግባት የተባበረለት ደግ ልጅን ወለዱ:: እጅጉን ደስ ስላላቸው በአካባቢያቸው የመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስን ቤተ ክርስቲያን በገንዘባቸው አነጹ:: ሕፃኑንም በመጥምቁ ስም "ዮሐንስ" አሉት:: ጻድቁ ቅዱስ ዮሐንስ ገና ከልጅነቱ ጀምሮ ጸጋ እግዚአብሔር አድሮበታልና ሕይወቱ ግሩም ነበር:: በሕፃን ገላው ይጾምና ይሰግድ: በልጅ አንደበቱም ተግቶ ይጸልይ ነበር:: ወላጆቹ ወደ እረኝነት ባሰማሩት ጊዜም መፍቀሬ ነዳያን ነውና ቁርስና ምሳውን ለነዳያን እያበላ እርሱ ጾሙን ይውል ነበር:: አባቱ የሚያደርገውን ሰምቶ ለማረጋገጥ ተከተለው:: እንዳሉትም እናቱ ጋግራ የሰጠችውን ትኩስ ዳቦ ለነዳያን ሲሰጥ አየው:: ሊቆጣው ፈልጐ "ዳቦህ የታለ?" ቢለው ሕፃኑ ቅዱስ ዮሐንስ "በአገልግሉ ውስጥ አለ" ሲል መለሰለት:: አባት ለመቆጣት እንዲመቸው አገልግሉን ሲከፍተው ግን ያየውን ማመን አልቻለም:: በእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ ዳቦዎቹ ትኩስ እንደሆኑ ተገኙ:: አባትም ወደ ቤቱ ወስዶ "ልጄ! አንተ የእግዚአብሔር ሰው ስለሆንክ እኛን ሳይሆን እርሱን አገልግል" ብሎ ወደ ቤተ ክርስቲያን ላከው:: በዚህ ምክንያት ቅዱስ ዮሐንስ በአሥራ ሁለት ዓመቱ ወደ ትምህርት ገባ:: በስድስት ዓመታትም ብሉይ ከሐዲስ ጠነቀቀ:: አሥራ ስምንት ዓመት ሲሞላው ደግነቱን ወደዋልና በግድ ቅስና ሾሙት:: እርሱ ግን ለተወሰነ ጊዜ አስተምሮ ዘመዱ የሆነውንና ዲያቆኑን ቅዱስ ስምዖንን አስከትሎ መነነ:: በዚያም በፍጹም ገድል ሲኖር ብዙ ተአምራትን ሰርቷል:: ¤አንድ ወታደር (አንድ ዐይና ነው) ሊባረክ ብሎ ሲጐነበስ የታወረች ዐይኑን የቅዱስ ዮሐንስ ልብስ ቢነካት በርታለታለች:: ከዚህ አልፎም ቅዱሱ ብዙ ድውያንን ፈውሷል: ለምጻሞችን አድኗል: አጋንንትን ከማደሪያቸው (ከሰው ላይ) አሳድዷል:: ታዲያ አንድ ቀን የወቅቱ የአንጾኪያ ንጉሥ የቅዱስ ዮሐንስን ዜና ይሰማል:: የእርሱ ልጅ ደግሞ አጋንንት አድረውባት ስቃይ ላይ ነበረችና የሚያድናት አልተገኘም:: ንጉሡ "ጻድቁን አምጡልኝ" ብሎ መልዕክተኛ ሲልክ ቅዱስ ዮሐንስ ደመና ጠቅሶ: በዚያውም ላይ ተጭኖ ከተፍ አለ:: ንጉሡ አይቶት ደነገጠ:: አባ ዮሐንስ ግን "እኔ ኃጢአተኛ የሆንኩ ሰው ለምን እንዲህ ትፈልገኛለህ?" ብሎ ታማሚዋን አስጠራ:: ጻድቁ እጆቹን አንስቶ ወደ ፈጣሪው ሲጸልይ በወጣቷ ላይ ያደረው ሰይጣን ሕዝቡ እያዩት ከሆዷ በዘንዶ አምሳል ወጥቶ ሔደ:: ንጉሡ ስለተደረገለት ውለታ ለቅዱስ ዮሐንስ ወርቅና ብር ብዙ ሽልማትም አቀረበ:: አባቶቻችን እንዲህ ዓይነት ነገር አይወዱምና ቅዱሱ "እንቢ አልወስድም" አለ:: ቅዱስ ዮሐንስ "ልሒድ" ብሎ ሲነሳ ንጉሡ "አባቴ ወድጄሃለሁና አትሒድ" ብሎ የልብሱን ዘርፍ (ጫፍ) ያዘው:: በቅጽበት ግን ደመና መጥታ ነጥቃ ወሰደችው:: የቀሚሱ ቁራጭም በንጉሡ እጅ ላይ ቀረች:: እርሱም ቤተ ክርስቲያን አሳንጾ ያችን የተባረከች ጨርቅ በክብር አኑሯታል:: ቅዱስ ዮሐንስና ቅዱስ ስምዖን (ደቀ መዝሙሩ) ግን ከብዙ የተጋድሎ ዓመታት በኋላ ሌላ ክብር መጣላቸው:: "ክርስቶስን ካዱ: ለጣዖት ስገዱ" የሚል ንጉሥ በመነሳቱም ሒደው በጌታችን ስም መሰከሩ:: በገድል በተቀጠቀጠ ገላቸው ላይ ግርፋትን: እሳትን ታገሱ:: በዚህች ቀንም አንገታቸውን ተቆርጠው በሰማዕትነት ዐርፈዋል:: ††† ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምልጃቸው ይማረን:: ከበረከታችቸውም ያድለን:: <<<ሐምሌ 11 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት>>> 1.ቅዱስ አባ ዮሐንስ (ሰማዕት ወጻድቅ) 2.ቅዱስ ስምዖን (ደቀ መዝሙሩ) 3.አባ ኢሳይያስ ዘገዳመ አስቄጥስ 4.አባ ገብርኤል ሊቀ ጳጳሳት <<< ወርኀዊ በዓላት>>> 1.ቅዱስ ያሬድ ካህን 2.ቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት 3.ብፁዐን ኢያቄም እና ሐና 4.አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ 5.ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት ††† "ሒዳችሁም መንግስተ ሰማያት ቀርባለች ብላችሁ ስበኩ:: ድውዮችን ፈውሱ: ሙታንን አንሱ: ለምጻሞችን አንጹ: አጋንንትን አውጡ:: በከንቱ ተቀብላችሁ በከንቱ ስጡ:: ወርቅ: ወይም ብር: ወይም ናስ በመቀነታችሁ: ወይም ለመንገድ ከረጢት: ወይም ሁለት እጀ ጠባብ: ወይም ጫማ: ወይም በትር: አታግኙ:: ለሠራተኛ ምግቡ ይገባዋልና::" ††† (ማቴ. ፲፥፯) ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር ††† ከኢ/ኦ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ የተገኙ የእለቱ የቅዱሳን(የጻድቃን) አባቶቻችን እና የቅዱሳን(የጻድቃን) እናቶቻችን ጽድቅ እና ገድላት ይነገርበታል። በመሀልም ጠቃሚና አስተማሪ ነው የምንላቸውን ታሪኮች ወደእናንተ የምናቀርብ ይሆናል። https://telegram.me/gedlekdusan
113
15
ወንድሞች ሆይ በማንኛቸውም ጊዜ ቢሆን ዝም በሉ ታገሱ የትዕግስት ጌጡ ዝምታ ነውና! በመጨረሻ ልትናገሩ ብትፈልጉ ነገር አሳጥሩ የመናገር ጌጡ ማሳጠር ነውና። ✍️ ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ    🌿 @gedlekdusan🌿      ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥                            ⌲                                       ˢʰᵃʳᵉ
125
16
ሀጢአት ሳልሰራ አውለኝ ብላችሁ ጸልያችሁ ታውቃላችሁ?..
ሀጢአት ሳልሰራ አውለኝ ብላችሁ ጸልያችሁ ታውቃላችሁ?..
138
17
بدون متن...
132
18
የብጹዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ ወርቃማ ብሒላዊ ንግግር ❝ ሊቅ በሊቅነቱ ቢያስተምርህ ሊቅ ትሆናለህ ሊቅ በህይወቱ ቢያስተምርህ ግን ክርስቲያን ትሆናለህ። ❝ 💚@gedlekdusan💚 💛@gedlekdusan💛 ❤️@gedlekdusan❤️
117
19
†††✝ እንኳን ለሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤል ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። ††† ††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ††† ††† ✝ቅዱስ ናትናኤል✝ ††† ††† በቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት ከቅዱሳን ሐዋርያት መካከል ዘግይቶ ሰማዕትነትን የተቀበለ ይህ ቅዱስ ሐዋርያ ነው:: ቅዱሱ ሐዋርያ የተወለደው ከእሥራኤላውያን ወላጆቹ ጌታችን በተወለደበት ዘመን አካባቢ ነው:: ይህ በምን ይታወቃል ቢሉ እርሱ ሕፃን እያለ ሔሮድስ 144,000 ሕፃናትን ሲፈጅ እርሱ ግን በእግዚአብሔር ጥበብ ተርፏል:: እናቱ በቅርጫት ውስጥ አድርጋ የበለስ ዛፍ ላይ አስቀምጣው ተደብቃ ታጠባው ነበር:: ለሐዋርያው ወላጆቹ ያወጡለት ስም ስምዖን ሲሆን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ ናትናኤል ብሎታል:: በባልንጀሮቹ ሐዋርያት ደግሞ የቃናው ስምዖን (ገሊላ ቃና አካባቢ ስላደገ) አንዳንዴም ቀናተኛው ስምዖን ይሉት ነበር:: ምሑረ ኦሪት ነበርና ዘወትር ለሕግ ይቀና ነበር:: በገሊላ ቃና ሰርግ የደገሰው ዶኪማስ የቅዱስ ናትናኤል የአጎት ልጅ ነው:: ጌታና ደቀ መዛሙርቱን ዶኪማስ የጠራበት አንዱ ምክንያትም ይሔው ነው:: ቅዱስ ናትናኤል ኦሪትን ከገማልያል ተምሮ: ከበለስ ቁጭ ብሎ ይተክዝ ነበር:: "መሲሕ ምነው ቀረህ?" እያለም ይተክዝ ነበር:: ማዕምረ ኅቡዓት አምላካችን ክርስቶስ ይህንን አውቆ በፊልጶስ አማካኝነት ጠርቶታል:: ናትናኤል ለጊዜው ተከራክሮ ነበር:: በኋላ ግን የጌታችንን ማንነት በደቂቃዎች ተረድቶ አምኗል:: ጌታችንም "ክዳት ሽንገላ በልቡ ውስጥ የሌለበት ንጹሕ እሥራኤላዊ" ሲል አመስግኖታል:: ሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤል ከጌታችን እግር ሥር ምሥጢረ መንግስተ ሰማያትን ተምሮ: በጸጋ መንፈስ ቅዱስም ሰክሮ: ብዙ አሕዛብን ከጨለማ (ጣኦት አምልኮ) ወደ ብርሃን (አሚነ ክርስቶስ) መልሷል:: እጅግ ብዙ መከራንም ተቀብሏል:: የጌታችን ወንድም የተባለ ቅዱስ ያዕቆብ በአይሁድ ከተገደለ በኋላም ቅዱስ ናትናኤል የኢየሩሳሌም ሁለተኛ ኤጲስ ቆጶስ ሆኖ አገልግሏል:: ከአይሁድም ዘንድ ብዙ መከራ ደርሶበታል:: በመጨረሻም በዚህች ዕለት በሰማዕትነት አልፏል:: በገድለ ሐዋርያት ላይ እንደተጠቀሰው ቅዱሱ ሰማዕት የሆነው በመቶ ሃምሳ ዓመቱ ነው:: ያ ማለት ደግሞ ከሐዋርያት አባቶች በመጨረሻ ያረፈው እርሱ ነው ያሰኛል:: †††✝ አባ ብስንዳ ✝††† ††† ዳግመኛ በዚህ ቀን ታላቁ አባ ብስንዳ ይታሠባል:: አባ ብስንዳ በዘመነ ጻድቃን ምድረ ግብጽ ውስጥ ከነበሩ ታላላቅ አበው አንዱ ነው:: ቅዱሱን ከገድሉ ጽናት የተነሳ መላእክት በእጅጉ ይወዱት ነበር:: "እኔ ልሸከምህ - እኔ ልሸከምህ" እያሉ ይሻሙበት: በተራ በተራም ተሸክመውት ይውሉ ነበር:: እርሱም ለበርካታ ዓመታት ውኃ የሞላበት ጉድጓድ ውስጥ ገብቶ ይጸልይ ነበር:: እንደ እሳት በሚባላው በረዶ ውስጥ ገብቶ መጸለዩ የፈጣሪውን ሕማማት ለመሳተፍ እና ለኃጥአን ምሕረትን ይለምን ዘንድ ነው:: ሁሌም በዘጠኝ ሰዓት መላእክት ተሠብስበው ይመጡና በብርሃን ሠረገላ ይሸከሙታል:: ከመሬትም ዘጠኝ ክንድ ከፍ ያደርጉት ነበር:: ከብዙ ዓመታት ተጋድሎ በኋላም በዚህች ቀን ዐርፎ ወደ ፈጣሪው ሒዷል:: ††† እግዚአብሔር በቅዱስ ናትናኤል ምልጃ ሃገራችንን ከጥፋት: ሕዝቦቿንም ከመቅሰፍት ይሰውርልን:: ከሐዋርያው እና ከጻድቁ አባ ብስንዳ በረከትም አይለየን:: ††† ሐምሌ 10 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ (ቀናተኛው ስምዖን) 2.ታላቁ አባ ብስንዳ ጻድቅ 3.አባ ከላድያኖስ ሊቀ ጳጳሳት ††† ወርኀዊ በዓላት 1.ታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ 2.ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሃገረ ሜራ 3.አቡነ መልክዐ ክርስቶስ 4.ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ (ወልደ እልፍዮስ) 5.ቅድስት ዕሌኒ ንግስት 6.ቅዱስ ዕፀ መስቀል ††† "ጌታ ኢየሱስ ናትናኤልን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ ስለ እርሱ 'ተንኰል የሌለበት በእውነት የእሥራኤል ሰው እነሆ' አለ:: ናትናኤልም 'ከወዴት ታውቀኛለህ?' አለው:: ጌታ ኢየሱስም መልሶ 'ፊልጶስ ሳይጠራህ ከበለስ በታች ሳለህ አየሁህ' አለው:: ናትናኤልም መልሶ 'መምሕር ሆይ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ:: አንተ የእሥራኤል ንጉሥ ነህ' አለው::" ††† (ዮሐ. ፩፥፵፰-፶፩) ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር ††† ከኢ/ኦ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ የተገኙ የእለቱ የቅዱሳን(የጻድቃን) አባቶቻችን እና የቅዱሳን(የጻድቃን) እናቶቻችን ጽድቅ እና ገድላት ይነገርበታል። በመሀልም ጠቃሚና አስተማሪ ነው የምንላቸውን ታሪኮች ወደእናንተ የምናቀርብ ይሆናል። https://telegram.me/gedlekdusan
496
20
የብጹዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ ወርቃማ ብሒላዊ ንግግር ❝ በእግዚአብሔር ፊት መቆምህንና እርሱም እንደሚመለከትህ አስታውስ፦ ያኔ ኃጢአት አትሰራም እግዚአብሔርን ታየዋለህና። ❝ 💚@gedlekdusan💚 💛@gedlekdusan💛 ❤️@gedlekdusan❤️
120