ገድለ ቅዱሳን
@Gedelat ለተለያዩ አስተያየት እና ጥቆማ ማድረስ ከፈለጉ በአድራሻችን ቢያደርሱን ይደርሰናል፡፡ በአድራሻችን ✍ @Mnfesawi_bot
Mostrar más6 669
Suscriptores
-224 horas
-37 días
-830 días
- Suscriptores
- Cobertura postal
- ER - ratio de compromiso
Carga de datos en curso...
Tasa de crecimiento de suscriptores
Carga de datos en curso...
00:46
Video unavailableShow in Telegram
†
[ የምታሰድዳት ከሆነ ... ግድ የለም ! ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
❝ ዘንዶውም ወደ ምድር እንደ ተጣለ ባየ ጊዜ ወንድ ልጅ የወለደችውን ሴት አሳደዳት።
ከእባቡም ፊት ርቃ አንድ ዘመን ፥ ዘመናትም ፥ የዘመንም እኵሌታ ወደ ምትመገብበት ወደ ስፍራዋ ወደ በረሀ እንድትበር ለሴቲቱ ሁለት የታላቁ ንሥር ክንፎች ተሰጣት። ❞ [ ራእ.፲፪፥፲፫ ]
❝ ህፃኑንና እናቱንም ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ ❞ [ ማቴ . ፪ ፥ ፲፫ ]
† † †
💖 🕊 💖
1.99 MB
❤ 1
Photo unavailableShow in Telegram
🕊 💖 ▬▬ † ▬▬ 💖 🕊
[ ያ ለ እ ም ነ ት ! ]
[ ክፍል - ፲ - ]
💖 ድንቅ ትምህርት 💖
🕊 በመምህራችን በቀሲስ ኅብረት የሺጥላ 🕊
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
❝ ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም ፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንዲሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋልና። ❞
[ ዕብ . ፲፩ ፥ ፮ ]
ሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ሊሰማው የሚገባው እጅግ ድንቅ ተከታታይ ትምህርት ! 💞
† † †
💖 🕊 💖
👇
Photo unavailableShow in Telegram
†
🕊 💖 ሰ ላ ም ታ 💖 🕊
❝ ክርስቶስ ተንስአ እሙታን
▸ በዐቢይ ኃይል ወስልጣን ፤
አሠሮ ለሰጣን
▸ አግዐዞ ለአዳም ፤
ሰላም
▸ እምይእዜሰ ፤
ኮነ
▸ ፍስሐ ወሰላም ❞
🕊
❝ ክርስቶስ በታላቅ ኃይልና ስልጣን ከሙታን ተነሳ ፤ ሰይጣንን አሰረው ፤ አዳምንም ነጻ አወጣው ፤ ስለዚህም ከእንግዲህ ወዲህ ፍፁም ሰላም እና ደስታ ሆነ።
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ 🕊 እነሆ ሁሉም አዲስ ሆነ ! 🕊 ]
† † †
💖 🕊 💖
❝ ብርሃን ዘመጽአ ውስተ ዓለም ዘያበርህ ላዕለ ጻድቃን መርአዊሃ ለቤተ ክርስቲያን ይርዳዕ ዘተኃጕለ ያስተጋብእ ዝርዋነ መጽአ ኀቤነ ፤ ❞
ትርጉም ፦ [ ወደ ዓለም የመጣው ብርሃን በጻድቃን ላይ የሚያበራ ነው ፣ የቤተ ክርስቲያን ሙሽራዋ ነው ፣ የጠፋው ይረዳ ዘንድ የተበተኑትን ይሰበስብ ዘንድ ወደ እኛ መጣ [ ሰው ሆነ ] ]
[ ድጓ ዘአስተምህሮ ]
† † †
💖 🕊 💖
🕊
[ † እንኳን ለኢትዮዽያዊው ጻድቅ አቡነ ተጠምቀ መድኅን እና ለእናታችን ቅድስት ማርታ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †
🕊 † አቡነ ተጠምቀ መድኅን † 🕊
† ጻድቁ የተወለዱት በአፄ ሱስንዮስ ዘመን በ፲፮፻፲ [1610] ዓ/ም ሲሆን ወላጆቻቸው ወልደ-ክርስቶስና ወለተ-ማርያም ይባላሉ:: ታሕሳስ ፪ [2] ቀን እንደ መወለዳቸው ክርስትና የተነሱት ጥር ፲፩ [11] ቀን ነበርና ካህኑ "ተጠምቀ መድኅን" አላቸው:: በምድረ ጐጃም ከበቀሉ ታላላቅ ቅዱሳን አንዱ የሆኑት አባ ተጠምቀ መድኅን ገና ከሕጻንነታቸው ጀምሮ ጸጋ-እግዚአብሔር የጠራቸው ነበሩ::
ሕጻን እያሉ ቃለ-እግዚአብሔር መማር ቢፈልጉም አባታቸው በግድ እረኛ አደረጋቸው:: እርሳቸው ግን በሕጻን ልባቸውም ቢሆን ቤተሰብን ማሳዘን አልፈለጉም::
ይልቁኑ ወደ በርሃ ይወርዱና አንበሳውን: ነብሩን: ተኩላውን ሰብስበው:- "በሉ እኔ ልማር ልሔድ ስለ ሆነ እስከ ማታ ድረስ ጠብቁልኝ" ብለው ለአራዊቱ አደራ ይሰጣሉ:: አራዊቱ ከበጉ: ከፍየሉ: ከላሙ ጋር ሲቦርቁ ይውላሉ:: ተጠምቀ መድኅን ደግሞ ዳዊቱን: ወንጌሉን ሲማሩና ሲጸልዩ ውለው ማታ ይገባሉ::
ተጠምቀ መድኅን በሕጻንነታቸው ቁርስና ምሳቸውን ለነዳያን በመስጠት በቀን አንድ ማዕድ ብቻ ይቀምሱ ነበር:: ፳፫ [23] ዓመት ሲሞላቸው ወደ መርጡለ_ማርያም ሔደው መንኩሰዋል:: ከዚሕ ጊዜ በሁዋላ ለ፴፯ [37] ዓመታት:-
፩. በፍጹም ተጋድሎ ኑረዋል
፪. ራሳቸውን ዝቅ አድርገው አገልግለዋል
፫. ከጐጃም እስከ ሱዳን ድረስ ወንጌልን ሰብከው በርካቶችን አሳምነው አጥምቀዋል [ካህን ናቸውና]
፬. ፯ "7" ገዳማትንና ፲፪ "12" አብያተ ክርስቲያናትን አንጸዋል::
† ጻድቁ በተሰጣቸው መክሊት አትርፈው በ፷ [60] ዓመታቸው በ፲፮፻፸ [1670] ዓ/ም [በአፄ ዮሐንስ_ጻድቁ ዘመን] ዐርፈዋል:: እግዚአብሔር የምሕረት ቃል ኪዳን የገባላቸው ሲሆን አጽማቸው ዛሬ በጋሾላ ቅዱስ ጊዮርጊስ የእናቶች ገዳም ውስጥ ይገኛል::
🕊 † ቅድስት ማርታ † 🕊
† እናታችን ቅድስት ማርታ በቀደመ ሕይወቷ እጅግ ኃጢአቷ የበዛ ሴት ነበረች:: እጅግ ቆንጆ መሆኗን ሰይጣን ለኃጢአት እንድትጠቀምበት አባበላት:: እርሷም ተቀበለችው:: በወጣትነት ዘመኗ በመልኩዋና በገላዋ በርካቶችን ወደ ኃጢአት ሳበች::
መጽሐፍ እንደሚል ለሁሉም ሰው የመዳን ቀን ጥሪ አለውና አንድ ቀን [በበዓለ ልደት] ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔደች:: ዘበኛው ግን ሲያያት ተጸይፏልና አትገቢም አላት:: ተከራከረችው: ለመነችው:: ግን አልተሳካላትም:: ሰዓቱ የቅዳሴ ቢሆንም እርሷ እሪ አለች:: ለቅዳሴ የቆሙ ሁሉ በመታወካቸው ዻዻሱ ወጥቶ ገሰጻት::
ያን ጊዜ ነበር ወደ ልቧ የተመለሰችው:: በጉልበቷ ተንበርክካ መራራ ለቅሶን አለቀሰች:: ዻዻሱንም ተማጸነችው:- "እጠፋ ዘንድ አትተወኝ:: ወደ ጌታየ አድርሰኝ" አለችው:: ወዲያውም ወደ ቤቷ ሔዳ የዝሙት እቃዋን አቃጠለች:: ጸጉሯን ተላጨች:: ንብረቷን ሁሉ ለነዳያን አካፈለች:: ዻዻሱም ንስሃ ሰጥቶ ወደ ገዳም አሰናበታት::
ወደ ገዳም ገብታ: በዓት ተቀብላ: ጾምና ጸሎትን ከእንባ ጋር አዘወተረች:: ለ፳፭ [25] ዓመታት በፍጹም ተጋድሎ ከበዓቷ ሳትወጣ: አንድም ሰው ሳታይ ኖረች:: ከማረፏ በፊትም ብዙ ተአምራትን አድርጋለች::
† የቅዱሳን አምላክ ለእኛም እድሜ ለንስሃ: ዘመን ለፍስሐ አይንሳን:: ከበረከታቸውም ያድለን:: †
🕊
[ † ሰኔ ፫ [ 3 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅድስት ማርታ ተሐራሚት
፪. አቡነ ተጠምቀ መድኅን ጻድቅ [ኢትዮዽያዊ]
፫. ቅዱስ ኢላርዮን ሰማዕት
፬. ቅዱስ ኮርዮን ሰማዕት
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. በዓታ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ
፪. ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
፫. ቅዱሳን ሊቃነ ካህናት አበው [ዘካርያስና ስምዖን]
፬. አባ ሊባኖስ ዘመጣዕ
፭. አቡነ ዜና ማርቆስ
፮. አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ዘደብረ በንኮል
† " አልሞትም : በሕይወት እኖራለሁ እንጂ:: የእግዚአብሔርንም ሥራ እናገራለሁ:: መገሠጽስ እግዚአብሔር ገሠጸኝ:: ለሞት ግን አልሠጠኝም:: የጽድቅን ደጆች ክፈቱልኝ:: ወደ እነርሱ ገብቼ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ:: ይህች የእግዚአብሔር ደጅ ናት:: ጻድቃን ወደ እርስዋ ይገባሉ:: ሰምተኸኛልና: መድኃኒትም ሆነኸኛልና አመሰግንሃለሁ:: " † [መዝ.፻፲፯፥፲፯-፳፪] (117:17-22)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖