es
Feedback
ገድለ ቅዱሳን

ገድለ ቅዱሳን

Ir al canal en Telegram

@Gedelat ለተለያዩ አስተያየት እና ጥቆማ ማድረስ ከፈለጉ በአድራሻችን ቢያደርሱን ይደርሰናል፡፡ በአድራሻችን ✍ @Mnfesawi_bot

Mostrar más
6 490
Suscriptores
Sin datos24 horas
+87 días
+630 días

Carga de datos en curso...

Atraer Suscriptores
junio '26
junio '26
+56
en 1 canales
mayo '26
+63
en 2 canales
Get PRO
abril '26
+77
en 2 canales
Get PRO
marzo '26
+58
en 1 canales
Get PRO
febrero '26
+44
en 1 canales
Get PRO
enero '26
+59
en 1 canales
Get PRO
diciembre '25
+98
en 2 canales
Get PRO
noviembre '25
+91
en 1 canales
Get PRO
octubre '25
+77
en 1 canales
Get PRO
septiembre '25
+56
en 1 canales
Get PRO
agosto '25
+103
en 1 canales
Get PRO
julio '25
+85
en 1 canales
Get PRO
junio '25
+99
en 1 canales
Get PRO
mayo '25
+96
en 1 canales
Get PRO
abril '25
+96
en 2 canales
Get PRO
marzo '25
+140
en 1 canales
Get PRO
febrero '25
+107
en 1 canales
Get PRO
enero '25
+190
en 1 canales
Get PRO
diciembre '24
+198
en 2 canales
Get PRO
noviembre '24
+66
en 1 canales
Get PRO
octubre '24
+109
en 3 canales
Get PRO
septiembre '24
+60
en 1 canales
Get PRO
agosto '24
+89
en 1 canales
Get PRO
julio '24
+129
en 2 canales
Get PRO
junio '24
+107
en 2 canales
Get PRO
mayo '24
+109
en 1 canales
Get PRO
abril '24
+120
en 2 canales
Get PRO
marzo '24
+94
en 2 canales
Get PRO
febrero '24
+74
en 2 canales
Get PRO
enero '24
+102
en 2 canales
Get PRO
diciembre '23
+116
en 3 canales
Get PRO
noviembre '23
+81
en 1 canales
Get PRO
octubre '23
+98
en 7 canales
Get PRO
septiembre '23
+79
en 0 canales
Get PRO
agosto '23
+73
en 0 canales
Get PRO
julio '23
+94
en 0 canales
Get PRO
junio '23
+64
en 0 canales
Get PRO
mayo '23
+75
en 0 canales
Get PRO
abril '23
+78
en 0 canales
Get PRO
marzo '23
+84
en 0 canales
Get PRO
febrero '23
+54
en 0 canales
Get PRO
enero '23
+83
en 0 canales
Get PRO
diciembre '22
+62
en 0 canales
Get PRO
noviembre '22
+70
en 0 canales
Get PRO
octubre '22
+54
en 0 canales
Get PRO
septiembre '22
+61
en 0 canales
Get PRO
agosto '22
+48
en 0 canales
Get PRO
julio '22
+73
en 0 canales
Get PRO
junio '22
+47
en 0 canales
Get PRO
mayo '22
+61
en 0 canales
Get PRO
abril '22
+75
en 0 canales
Get PRO
marzo '22
+91
en 0 canales
Get PRO
febrero '22
+57
en 0 canales
Get PRO
enero '22
+99
en 0 canales
Get PRO
diciembre '21
+55
en 0 canales
Get PRO
noviembre '21
+64
en 0 canales
Get PRO
octubre '21
+141
en 0 canales
Get PRO
septiembre '21
+174
en 0 canales
Get PRO
agosto '21
+223
en 0 canales
Get PRO
julio '21
+245
en 0 canales
Get PRO
junio '21
+205
en 0 canales
Get PRO
mayo '21
+161
en 0 canales
Get PRO
abril '21
+520
en 0 canales
Get PRO
marzo '21
+395
en 0 canales
Get PRO
febrero '21
+333
en 0 canales
Get PRO
enero '21
+517
en 0 canales
Get PRO
diciembre '20
+9 090
en 0 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
18 junio0
17 junio+4
16 junio+3
15 junio+3
14 junio+5
13 junio+7
12 junio+2
11 junio+4
10 junio+5
09 junio+2
08 junio+1
07 junio+7
06 junio+1
05 junio+1
04 junio+3
03 junio+7
02 junio0
01 junio+1
Publicaciones del Canal
photo content

2
[ ስንክሳር ሰኔ - ፲፩ - ] .mp3
152
3
🕊 [ † እንኳን ለታላቁ ሰማዕት ማር ገላውዴዎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን። † ] † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! † 🕊  †  ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት  †   🕊 † ቅዱስ ገላውዴዎስ የተወለደው በ3ኛው መቶ ክ/ዘ በድሮው የሮም ግዛት በአንጾኪያ [አሁን ሶርያ ውስጥ] ነው:: አባቱ አብጥልዎስ የሮም ቄሣር የኑማርያኖስ ወንድም ነበር:: በዚህ ምክንያት ቅዱሱ ያደገው በቤተ መንግሥት ውስጥ ነው:: ወቅቱ መልካምም ክፉም ነገሮች ነበሩት:: መልካሙ ነገር በቤተ መንግሥት አካባቢ ይኖሩ የነበሩት ልዑላኑ አብዛኞቹ በፍቅረ ክርስቶስ የታሠሩ ነበሩ:: ከእነዚህ መካካከል "ቅዱስ ፋሲለደስ: ቅዱሳኑ :- ፊቅጦር: ቴዎድሮስ: አባዲር: አውሳብዮስ: ዮስጦስ: አቦሊ: እስጢፋኖስ . . ." ነበሩ:: ቅዱሳቱ "ማርታ: ታውክልያ: ኢራኢ: ሶፍያ. . ." ነበሩ:: አስቸጋሪው ነገር ደግሞ ነጋ መሸ ኑሯቸው ጦርነት ነበር:: የዘመኑ የፋርስና የቁዝ መሪዎች ጦረኞች ነበሩና ዕለት ዕለት ፍልሚያ ነበር:: በዚህ ምክንያት ቅዱስ ገላውዴዎስ የተመሠከረለት አርበኛና የተባረከ ንጹሕ ክርስቲያን ሆኖ አድጓል:: ከልጅነቱ ጀምሮ ቅዱሳት መጻሕፍትን በማጥናቱ ሕይወቱ በመንፈስ ቅዱስ ጨውነት ታሽቷል:: እርሱ የነገሥታቱ ቤተሰብ ነው:: ማዕዱ በየዓይነቱ ሞልቶ ካልመሸ እህል አይቀምስም:: ጸሎቱ ስሙር: ስግደቱ ከምድር: አኗኗሩ በፍቅር ሆነ:: በዚያውም ላይ በድንግልናው የጸና ኃያል ነበር:: በጊዜው የቅዱስ ገላውዴዎስን ያህል መልኩ ያማረ [ደመ ግቡ] በአካባቢው አልነበረም:: ይህ ግን ሊያታልለው አልቻለም:: ሁሉ በእጁ ቢሆንም ለእርሱ ግን ብቸኛ ምርጫው ሃይማኖተ ክርስቶስ ነበር:: ቅዱስ ገላውዴዎስ ለጦርነት ወጥቶ ሲመለስ ንጉሡ ዲዮቅልጢያኖስ ሃይማኖቱን ክዶ: ሕዝቡን ለጣዖት ሲያሰግድ: ክርስቲያኖችን ሲገድል ደረሰ:: †  ቅዱሱ ኃያል የጦር ሰው ነውና ንጉሡን መግደል ሲችል ተወው:: በዚያ ሰሞንም ለገላውዴዎስ ሁለት ምርጫዎች ቀረቡለት :- ፩. ክርስቶስን ክዶ የንጉሡ ተከታይ መሆን: ፪. በክርስትናው ደሙን ማፍሰስ:: የቅዱሳኑ ምርጫቸው የታወቀ ነውና ታስሮ ወደ ግብጽ ተጋዘ:: በዚያ ከመኮንኑ ጋር ስለ ሃይማኖት ተከራክረው መኮንኑ ስለተበሳጨ ቅዱሱን በረዥም ጦር ጐኑን ወጋው:: ዘለፍ ብሎ ነፍሱን ሰጠ:: ሕዝበ ክርስቲያኑ በድብቅ መጥተው የቅዱሱን ሥጋ ሽቱ ቀብተው: ከዝማሬ ጋር ገነዙት:: የጓደኛው እናት ቅድስት ሶፍያ መጥታ ወደ ሶርያ ወስዳዋለች:: † ተወዳጅ: ኃያል: ቡሩክና መልካም ሰው ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት በሆነባት በዚሕች ዕለት በመላው ኦርቶዶክሳውያን ይከበራል:: † አምላካችን የቅዱሱን መንኖ ጥሪት: ትዕግስት: ጸጋና በረከት ያሳድርብን:: አሜን:: 🕊 [ † ሰኔ ፲፩ [ 11 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ] ፩. ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት [ሕይወቱ መላእክትን የመሰለ] ፪. አንድ ሺ ሰማንያ ስምንት ሰማዕታት [የቅዱስ ገላውዴዎስ ማኅበር] ፫. አባ ክርዳኑ ሊቀ ጳጳሳት ፬. እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ክብራ ኢትዮጵያዊት [የአቡነ በጸሎተ ሚካኤል እህት] ፭. የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዳሴ ቤቱ [ግብጽ] [ †  ወርኀዊ በዓላት ] ፩. ቅዱስ ያሬድ ካህን ፪. ቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት ፫. ብፁዐን ኢያቄም እና ሐና ፬. አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ † " የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ:: ደስ አያሰኙም የምትላቸውም ዓመታት ሳይደርሱ: ፀሐይ: ጨረቃና ከዋክብትም ሳይጨልሙ . . . አፈርም ወደ ነበረበት ምድር ሳይመለስ: ነፍስም ወደ ሰጠው ወደ እግዚአብሔር ሳይመለስ ፈጣሪህን አስብ:: ሰባኪው :- "ከንቱ: ከንቱ: ሁሉ ከንቱ ነው" ይላል:: " † [መክ. ፲፪፥፩-፱] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
136
4
+8
Sin texto...
138
5
+9
Sin texto...
145
6
❤ ውድ የቴሌግራሜ ቻናል ተከታታዮች ተወዳጅ ቤተሰቦቼ  እንዴት ሰነበታችሁ ቸር አላችሁ በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በግሼ ራቤል ወረዳ ቤተ ክህነት ስር ለሚገኘው #ለአጋዘን_በር_ደብረ_ምሕረት_ቅዱስ_ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ለዓመቱ ክብረ በዓል እረዳታ የጠየኳችሁ፣ አንድ ወንድሜ ከአሜሪካ ሀገር፣ ከቤሩት ሊባኖስ የሚኖሩ እኅቶች አስተባብረው፣ በተለያዩ ባሕር ማዶ ሀገር የሚኖሩ ወንድሟች እና እኅቶች በላኩት ገንዘብ እናተንም በማስተባበር የተገዙት የሶላርና ድምጽ ማጉያ ሙሉ ሲስተም፣ የተለያዩ ንዋየ ቅድሳት  #ማክሰኞ_ማለትም_ሰኔ_9 ቀን ማታ በጭነት መኪና ልኬ አባቶች #ዛሬ_ሰኔ_10 ቀን ተቀብለዋል። ለዚህ ያደረሰን አምላከ ቅዱስ ሚካኤል ይክበር ይመስገን።                 @Teamihokidusan
101
7
Sin texto...
88
8
❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #ሰኔ ፲፩ (11) ቀን። ❤ እንኳን በጦርነት ድል አድራጊው ከቤተ መንግሥት ወገን ለሆነ #በንጽሕናው_የመላእክት_አርያ_ላለው #ለከበረ_ሰማዕት_ለቅዱስ_ገላውዴዎስ ለተጋድሎው ፍጻሜ #ለዕረፍቱ_በዐል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡት፦ #በመድኃኒታችን_በኢየሱስ_ክርስቶስ ስም በእስክንድርያ ከተማ ከሠራችበት #ከአርባ_ሰማዕታት #ከቅዳሴ_ቤተ_ክርስቲያንና #ከእስክንድርያ_ሊቀ_ጳጳሳት #ከቅዱስ_ክርዳኑ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                        ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #ሰማዕቱ_ቅዱስ_ገላውዴዎስ፦ ይህ ቅዱስ ምድራዊ መንግሥትንና የዚህን ዓለም ክብር የናቀ ነበረ መልካም ገድልንም ተጋደለ። የማይጠፋ ሰማያዊ መንግሥትንና የማያልቅ ክብርንም ወረሰ። ❤ የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም አብጥልዎስ ነው እርሱም ለሮሜ ንጉሥ ለኑማርያኖስ ወንድሙ ነው መልኩም እንደ እስራኤል ያዕቆብ ልጅ እንደ ዮሴፍ ውብ ነበር። እርሱም በጦርነት ላይ የበረታ ነበር። የአንጾኪያ ተወላጆችም ይመኩበት ነበር። ስለ ደም ግባቱና ጽናቱ በሁሉ ዘንድ የተወደደ ነበር። እርሱንም ከመውደዳቸው ብዛት የተነሣ ጠላቶችን ድል እንዳረጋቸው እነርሱም ድል ሁነው በውርደት በብዙ ድንጋጤ ከፊቱ እንደሸሹ አድርገው ሥዕሉን ሥለው በከተማው መግብያ በር ላይ ያኖሩት ነበር። ❤ ቅዱስ ገላውዴዎስ የቤተ ክርስቲያን ቅዱሳት መጻሕፍትን ዘወትር ያነብ ነበር። የሮሜ ንጉሥም ዜናውን ሰምቶ ሊያየው ወደደ ልጁ ገላውዴዎስንም ይልክለት ዘንድ ወደ አባቱ ላከ እርሱም ላከለት። በደረሰም ጊዜ በደስታ ሊቀበለው ንጉሡ ከሠራዊቱ ጋራ ወጣ በአየውም ጊዜ ደስ ተሰኘበት የሮሜ ከተማ ሰዎች ሁሉም ደስ አላቸው። ከእነዚያ ወራቶችም በኋላ ከቊዝ አገር ሰዎችና ከአርማንያ ታላቅ ጸብ ተነሣ ይህም ቅዱስ ገላውዴዎስ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ታምኖ ወደ እነርሱ ወጣ ድልም አደረጋቸው ንጉሣቸውንም ያዘው ጣዖታቶቻቸውንም ሰበራቸው። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ አንጾኪያ ተመለሰ ዲዮስቆሮስም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ክዶ አምልኮ ጣዖትን በአጸና ጊዜ እጅግ አዘነ ፊቅጦር የሚባል የኅርማኖስ ልጅ ወዳጅ ነበረው ሁልጊዜም የመጻሕፍትን ቃል ይሰሙ ነበር ስለ ነፍሳቸውም ድኅነት ያነቡ ነበር። ❤ ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደማቸውን ያፈሱ ዘንድ ተስማሙ። በዚያ ጊዜም ሰይጣን በሽማግሌ አምሳል ታያቸው ያዘነላቸውም መስሎ እንዲህ አላቸው "ልጆቼ ሆይ መልካምች ጐልማሶች ናችሁ የነገሥታት ልጆችም ናችሁ። ስለ እናንተ እፈራለሁ አዝንላችኋለሁም እኔም ከንጉሡ ጋር ትስማሙ ዘንድ ለአማልክትም ታጥኑ ዘንድ እመክራችኋለሁ ሲአዝዛችሁም ትእዛዙን አትተላለፉ እናንተም ክርስቶስን በቤታችሁ አምልኩት ይህ ንጉሥ ኃይለኛ ርኅራኄም የሌለው ጫካኝ ነውና" አላቸው። ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእነርሱ ጋር የሚነጋገራቸው ሰይጣን እንደሆነ አስገነዘባቸው "ክፋትን ሁሉ የተመላህ የሐሰት አባት ሆይ ከእኛ ራቅ አንተ ሁል ጊዜ እግዚአብሔርን ሕግ ትቃረናለህና" አሉት። ያን ጊዜም መልኩን ለውጦ እንደ ጥቁር ባሪያ ሆነ እንዲህም አላቸው "እነሆ ከንጉሥ አጣልቼ ደማችሁን እንዲአፈስስ አደርገዋለሁ" ሰይጣኑም ይህንን ብሎ ወደ ዲዮቅልጥያኖስ ሔዶ "ፊቅጦርና ገላውዴዎስን ካልገደልካቸው በአንተ ላይ ይነሣሉ አንተንም ገድለው መንግሥትህን ይወስዳሉ እነርሱም የመንግሥት ልጆች ናቸውና" አለው። ❤ ስለዚህም ንጉሡ ወደ ቅዱስ ገላውዴዎስ ልኮ ወደርሱ አስመጣው ለጣዖታቱም እንዲሠዋ ለመነው የአባቱንም ሹመት ይሾመው ዘንድ ቃል ገባለት ሰምቶም አልታዘዘለትም። ንጉሡም ክፉ ቃልን ሊናገረው አልደፈረም ቅዱስ ገላውዴዎስ ግን በድፍረት ይናገረው ነበር ያለ መፍራትም ንጉሡንና የረከሱ አማልክቶቹን ሰደበ። ኅርማኖስም ቅዱስ ገላውዴዎስን ወደ ግብጽ እንዲልከውና በዚያ እንዲገድሉት ንጉሡን መከረው እርሱ እንደ ልጄ እንደ ፊቅጦር ዐመፀኛ ነውና። ❤ ንጉሡም ወደ እንዴናው ገዥ እንዲህ ብሎ ጻፈ "ገላውዴዎስ ትእዛዛችንን አልተቀበለም ቃላችንንም አልሰማም አንተም ወደ ትዕዛዛችን ይመለስ እንደሆነ በብዙ ድካም ሸንግለው ይህ ካልሆነ ራሱን በሰይፍ ቁረጥ"። ቅዱስ ገላውዴዎስ ወደ እስክንድርያ ይወስዱት ዘንድ ንጉሡ እንደ አዘዘ በአወቀ ጊዜ የእኅቱ ባል የሆነ ሲድራማኮስን ጠርቶ ክብር ይግባውና ጌታችንን በማመን እንዲጸና ወገኖቹንም እንዲያጸናቸው አደራ አለውና በሰላምታ ተሰናበተው። ❤ ወደ እንዴናው ገዥ ወደ አርያኖስም በደረሰ ጊዜ አርያኖስ አይቶ ደነገጠ ተነሥቶም እጁን ሳመው እንዲህም ብሎ ለመነው "ጌታዬ ገላውዴዎስ ሆይ ይህን ሥራ አትሥራ የንጉሥንም ትዕዛዝ አትተላለፍ። ቅዱስ ገላውዴዎስም እንዲህ ሲል መለሰለት "ንጉሥ ያዘዘህን ልትፈጽም እንጂ በነገርህ ልታስተኝ አልተላክሁም" አለው። መኰንኑም እስከሚቆጣ ድረስ እንዲህ እርስበርሳቸው ይነጋገሩ ነበር በመኰንኑም እጅ ጦር ነበር ቅዱስ ገላውዴዎስ ወጋው ነፍሱንም ክብር ይግባውና በጌታችን እጅ ሰኔ 11 ቀን ሰጠ በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ። ምዕመናንም መጥተው የቅዱስ ገላውዴዎስን ሥጋ ወሰዱ በመልካም አገናነዝም ገነዙት ከቅዱስ ፊቅጦር ሥጋ ጋርም በሣጥን ውስጥ አኖሩት። የስደቱም ዘመን እስኪሚፈጸም ጠበቁት። ❤ ከዚህም በኋላም የቅዱስ ፊቅጦር እናት ቅድስት ሶፍያ ወደ እንዴናው አገር መጣች የቅዱሳን ገላውዴዎስንና የፊቅጦርን ሥጋቸውንም ወስዳ ወደ አንጾኪያ አደረሰች። የቅዱስ ገላውዴዎስ ሥጋ አስዩጥ በሚባል አገር ይኖራል የሚልም አለ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ መስተጋድል በቅዱስ ገላውዴዎስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላሀሙ አሜን። ምንጭ፦ የሰኔ 11 ስንክሳር።                          ✝️ ✝️ ✝️ ❤ "#ሰላም_ለቅዳሴ_ቤትከ_ኢየሱስ_ክርስቶስ_መድኃኒነ። በእስክንድርያ ዘኮነ። ኀቤከ እግዚኦ አንቃዕዶና አዕይንተነ። ከመ ተሀበነ እምቅኔ ኃጢአት ግዕዛነ። ንጸንሐከ ንሕነ እምዘመን ዘመነ። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሰኔ_11።                         ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወኢትፈርህ እምግርማ ሌሊት። እምሐፅ ዘይሠርር በመዓልት። እምግብር ዘየሐውር በጽልመት"። መዝ 90፥5-6። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ቆሮ 5፥1-11፣ 1ኛ ጴጥ 5፥7-12 እና የሐዋ ሥራ 16፥35-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 10፥16-32። የሚቀደሰው ቅዳሴ ቅዳሴ እግዚእነ ነው። መልካም አቡነ ገብረ ኢየሱስ፣ አቡነ መዝሙረ ድንግልና የቅዱስ ገላውዴዎስ የዕረፍት በዓልና የጾም ጊዜ። በሁላችንም ይሁንልን።                  @Teamihokidusan
77
9
Sin texto...
67
10
❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #ሰኔ ፲፩ (11) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያውያኑ_ጻድቃን ነገረ ማርያምን ወደ ግእዝ ቋንቋና አራቱ ወንጌልን ወደ ተለያየ ቋንቋ ለተረጎሙት #ለአቡነ_መዝሙረ_ድንግል ለዕረፍታቸው በዐልና #በግብጽ_ቤተ_ክርስቲያ_ጨምር_ቅድስና ለተሰጣቸው #ለአብረ_ገብረ_ኢየሱስ_ለዕረፍታቸው በዐል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                         ✝️ ✝️ ✝️ ❤#አቡነ_መዝሙረ_ድንግል፦ የተባሉት ጻድቅ አገራቸው ጎጃም ነው፤ ታላቅ የቤተ ክርስቲያናችን ባለ ውለታ ናቸው። ጻድቁ በአምስት ሊቃውንት እየተመሩ በአራት ዓመት ጊዜ ውስጥ አራቱን ወንጌላት ወደ ተለያዩ ቋንቋዎች በመተርጎም በግእዝ፣ በአረማይክ፣ በዕብራይስጥና በዐረብኛ ጽፈው በአራት ዓምት ያዘጋጁ ታላቅ አባት ናቸው። ዛሬም በሞጊና ገዳም ይገኛል። ❤ ከዚህም ሌላ ነገረ ማርያምንም በግእዝና በዕብራይስጥ አዘጋጅተው ጽፈውታል። ሌሎችንም በርካታ መጻሕፍት ወደ ተለያዩ ቋንቋዎች እየተረጎሙ ጽፈው ያስቀመጡ ነበር። በጣም ጸሎተኛ፣ ደራሲ፣ ባሕታዊ፣ ጻድቅና መናኝ የሆኑት አቡነ መዝሙረ ድንግል ዐርፈው የተቀበሩት ጣና ክብራን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ነው። ከአቡነ መዝሙረ ድንግል እግዚአብሔር አምላክዐ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!።                         ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #አቡነ_ገብረ_ኢየሱስ፦ የተባሉት ኢትዮጵያዊ ጻድቅ በአገራችን ብዙ ተአምራትን በማድረግ ወንጌል ሲሰብኩ ከኖሩ በኋላ የግብጽ ገዳማትን ለመሳለም ወደ ግብጽ ወርደው አባ መቃርስ ገዳም ገቡ። ከዚያም ወጥተው በአባ ዮሐንስ ሐፂር ገዳም ገብተው በዚያ ብዙ ጊዜ ተቀመጡ። አቡነ ገብረ ኢየሱስ ታላቅ የሆነ ሀብተ ትንቢት የተሰጣቸው አባት ስለሆኑ በዚህም ግብጻውያን ይቀኑባቸው ነበር። ❤ ስልሳ ስድስተኛው የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳቱ አባ ገብረ ክርስቶስ ባረፉ ጊዜ ኤጲስቆጶሳቱ ተሰብስበው ወደ አባ መቃርስ ገዳም ወደ አስቄጥስ መጥተው ለከበረች ሹመት የሚገባውን እየመረመሩ ሁለት ወር ተቀመጡ። በዚህም ጊዜ በአባ ዮሐንስ ሐፂር ገዳም ለሚኖሩት ለጻድቁ አቡነ ገብረ ኢየሱስ የታዘዘ መልአክ ተገልጦላቸው "ለኤጲስ ቆጶሳቱ ለዚህች ለከበረች ሹመት የሚገባው ስሙ ገአርጊ የሚባል በመካከላችሁ አለና እርሱን ሹሙት አትዘኑ" በላቸው ብሎ ነገራቸው። አቡነ ገብረ ኢየሱስም "ከመካከላችሁ ስሙ ገአርጊ የሚባል ጻድቅ አለና እርሱን ሹሙት" ብለው መልአኩ የነገራቸውን መልእክት ነግረዋቸው አባ ገአርጊን ስልሳ ሰባተኛው የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አድርገው ሾመዋቸዋል። ❤ አባ ገአርጊም ስማቸው አባ ቄርሎስ ተብሎ ከተሾሙ በኋላ ቤተ ክርስቲያንን በሚገባ አገልግለዋል። በወቅቱ የነበረው የግብጻውያኑ ንጉሥ በጣም ብዙ ሚስቶች የነበሩት ቢሆንም አቡነ ገብረ ኢየሱስ ሄደው በድፍረት አስተምረውትና ገሥጸውት በአንድ ሚስት ብቻ እንዲጸና አድርገውታል። የጻድቁ አባታችን ገዳላቸው በጣና ይገኛል። ሰኔ11 ቀን ዐርፈው የተቀበሩት ግን በዛው በግብጽ በቊስቋም ገዳም ነው። ግብጻውያን የቅድስና ማዕረግ ሰጥተዋቸው ታቦት ቀርጸውላቸው በዓላቸውን በሚገባ ያከብሩላቸዋል። ከአቡነ ገብረ ኢየሱስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳንና ቅዱሳት በዓላት።                    @Teamihokidusan
97
11
🕊 💖 🕊 ❝ እኔ ብቻዬንና ችግረኛ ነኝና ፊትህን ወደ እኔ አድርግ ማረኝም። የልቤ ችግር ብዙ ነው ፤ ከጭንቀቴ አውጣኝ። ድካሜንና መከራዬን እይ ፥ ኃጢአቴንም ሁሉ ይቅር በለኝ። ❞ [ መዝ.፳፭፥
🕊                        💖                        🕊 ❝ እኔ ብቻዬንና ችግረኛ ነኝና ፊትህን ወደ እኔ አድርግ ማረኝም። የልቤ ችግር ብዙ ነው ፤ ከጭንቀቴ አውጣኝ። ድካሜንና መከራዬን እይ ፥ ኃጢአቴንም ሁሉ ይቅር በለኝ። ❞ [ መዝ.፳፭፥፲፮ ] ════════════════                            †††                ✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟ 🕊                         💖                        🕊
153
12
Sin texto...
159
13
[ + ከኃጢዓት ስለመውጣት + ] .mp3
145
14
🕊 💖 🕊 🩵 [ ምክረ ቅዱሳን ] 🩵 ════════════════ ▷ " ከሐጢዓት ስለመውጣት ! " [ 💖 በብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ 💖 ] ▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬ ❝ በነፍሳችሁ ዝላችሁ እ
🕊                        💖                        🕊     🩵       [   ምክረ ቅዱሳን   ]        🩵 ════════════════ ▷      "  ከሐጢዓት ስለመውጣት !  "  [  💖  በብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ  💖  ]  ▬▬▬▬▬▬   ♱    ▬▬▬▬▬▬ ❝ በነፍሳችሁ ዝላችሁ እንዳትደክሙ ፥ ከኃጢአተኞች በደረሰበት እንዲህ ባለ መቃወም የጸናውን አስቡ። ከኃጢአት ጋር እየተጋደላችሁ ገና ደምን እስከ ማፍሰስ ድረስ አልተቃወማችሁም ፤ ❞ [ ዕብ.፮፥፲፪-፫ ] ════════════════                            †††                ✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟ 🕊                         💖                        🕊
191
15
Sin texto...
174
16
[ ቤተ ክርስቲያን ቅድስት ] .mp3
158
17
🕊 💖 🕊 † 🕊 እናታችን ቤተ ክርስቲያን 🕊 † 💛 💛 ❝ እንደ ቀጋ የምትሸቺ ቤተ ክርስቲያን እናቴ ሰላምታ ለአንቺ ይገባል ፤ ከእናቴ ማሕፀን ዠምሮ በአንቺ ጸናሁ ፤ የራሴ አክሊል የምትኾ
🕊                        💖                       🕊  †   🕊   እናታችን ቤተ ክርስቲያን   🕊   † 💛                                                      💛 ❝  እንደ ቀጋ የምትሸቺ ቤተ ክርስቲያን እናቴ ሰላምታ ለአንቺ ይገባል ፤ ከእናቴ ማሕፀን ዠምሮ በአንቺ ጸናሁ ፤ የራሴ አክሊል የምትኾኚ ቤተ ክርስቲያን ሰላምታ ለአንቺ ይገባሻል። ... ሰላምታ የተገባሽ እናታችን ቤተ ክርስቲያን ሰላም ሰላም እንልሻለን ፤ በመኻከላችን ሰላምን አድርጊ ፤ ከፍጹም ጠላት እኛን ጠብቂ ፤ ልመናሽም ከእኛ ጋር ይሁን። ... አቤቱ ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንኽ ብለኽ በምሕረትኽ ዐስበኝ ፤ በኹለተኛው ልደት በጥምቀት በርሷም ውስጥ ስለተወለዱ በጡቶቿም ስላደጉ ስለ ወንዶች በጎች [ ምእመናን ] ስለ ሴቶች በጎች [ ምእመናት ] ብለኽ ዐስበኝ። ❞ .... [ ተአምኆ ቅዱሳን ] ▬▬▬▬▬▬   ♱     ▬▬▬▬▬▬ ❝ ብዘገይ ግን ፥ በእግዚአብሔር ማደሪያ ቤት መኖር እንዴት እንደሚገባ ታውቅ ዘንድ እጽፍልሃለሁ ፤ ቤቱም የእውነት ዓምድና መሠረት ፥ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ነው። ❞ [   ፩ጢሞ.፫፥፲፭   ] † በዚሕች ቀን ለ፵ [ 40 ] ዓመታት በመላው ዓለም የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናት የተከፈቱበት ቀን ይታሠባል:: ════════════════                            †††                ✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟ 🕊                         💖                        🕊
190
18
Sin texto...
146
19
🕊                       †                         🕊   [ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ] 🩵                                                  🩵 [    በቦታው ሁሉ ምሉ ነውና  !   ] ▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬ ❝ ነፍሱን በሲኦል አልተወም ፥ ሥጋውም ሙስና መቃብርን አላየም። መለኮት ከሁለቱ [ ከነፍስ ከሥጋ ] አልተለየም ፤ ሁለንተናው ከነፍስ ጋር በሲኦል ነበረ። በሲኦልም ለጻድቃን የምሥራችን አበሠረ። ሁለንተናውም ከሥጋ ጋር በመቃብር ነበረ እንጂ። በቦታው ሁሉ ምሉ ነውና መለኮት በሕማም ድል አይነሣም ለሕማም አይገኝም። [ መዝ.፲፮ [፲፭]፥፲ ፤ ፹፰ [፹፯]፥፫-፮ ። ግብ ሐዋ.፪፥፳፯ ። ፩ጴጥ.፫፥፲፱ ና ፳ ] ሌሎችም ባለማወቃቸው ቃል ሰው ስለመሆኑ ሲናገሩ 'ነፍስን ሥጋን አልነሣም እግዚአብሔር ቃል እንደ ዕሩቅ ብእሲ መርጦ አደረበት እንጂ' ይላሉ። ዳግመኛም ቃል በባሕርዩ እንደ ታመመ እንደ ሞተ  አብም እንደ አስነሣው ይናገራሉ ፥ ይህንን የሚናገሩ ሦስቱ ሞቱ እንዲያሰኝባቸው አያውቁም። እግዚአብሔር ቃል በባሕርዩ ከሞተስ እነሆ አብም ዳግመኛ ሞተ እርሱ ራሱ [ ወልድ ] እኔ በአብ ህልው ነኝ አብም በእኔ ህልው ነው እኛ አንድ ነን ብሏልና። ዳግመኛ እኔን ያየ አባቴን አየ ብሏልና ፤ ይህም እኔ የነገርኳችሁ ቃል እኔ ከራሴ አንቅቼ የነገርኳችሁ አይደለም ፤ በእኔ ህልውና ያለ አብ እርሱ ሥራውን ይሠራል እንጂ ብሏልና። እኛ ግን ፦ ከእኛ ባሕርይ በነሣው ሥጋ እንደ ታመመ እንደ ሞተ እናምናለን። እርሱ እግዚአብሔር ቃልም የተዋሐደውን ሥጋ ከሙታን ለይቶ እንዳስነሣው ፤ ያስነሣውም ሌላ እንዳይደለ እናምናለን ፤ ቅዱሳን አባቶቻችን ያስተማሩትን ትምህርት ትተው ክርስቶስ ፈጽሞ እንዳልታመመ እንዳልሞተ እንዳልተነሣ የሚናገሩ አሉ ፤ ይህንንም በመናገራቸው መለኮት ያጻፋቸውን መጻሕፍት ሁሉ ይለውጣሉ ፤ ሐሰትም ያደርጓቸዋል። [ ፪ጴጥ.፪፥፫-፲፮ ] ለእኛ ግን ፦ እግዚአብሔር ያጻፋቸው ቅዱሳት መጻሕፍት ትምህርታችን ናቸው። መንፈስ ቅዱስም ክርስቶስ የማይታመም ፍጹም አምላክ ፤ የሚታመም ፍጹም ሰው ያለመለየትም አንድ አካል አንድ ባሕርይ ነው ብሎ በሐዋርያት አድሮ ተናገረ ፤ በሊቃውንት አድሮ አስተማረ ፤ ካልታመመ ካልሞተ ፤ ካልተነሣ ሌሎችን እንደምን ያስነሣል ? [ ፩ቆሮ.፲፪፥፫ ፤ ፩ጴጥ.፩፥፲፩ ] አልሞተም አልተነሣም የሚሉ ግን መለኮት ያጻፋቸው መጻሕፍትን ሐሰተኞች ያደርጓቸዋል ፤ ባለማወቃቸውም አምላክ የለም ፤ ትንሣኤም ቢሆን ፤ መንግሥተ ሰማያትም ቢሆን ወቀሳም ቢሆን ፍርድም ሲሆን የለም ይላሉ እርሱ ግን እንደ ከሀሊነቱ የወደደውን ሁሉ ያደርጋል። ❞ [    🕊   ቅዱስ ቄርሎስ   🕊     ] ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን። ════════════════                            †††                ✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟ 🕊                        💖                       🕊
179
20
Sin texto...
251