ገድለ ቅዱሳን
Ir al canal en Telegram
@Gedelat ለተለያዩ አስተያየት እና ጥቆማ ማድረስ ከፈለጉ በአድራሻችን ቢያደርሱን ይደርሰናል፡፡ በአድራሻችን ✍ @Mnfesawi_bot
Mostrar más6 488
Suscriptores
-124 horas
+67 días
+530 días
Carga de datos en curso...
Canales Similares
Nube de Etiquetas
Sin datos
¿Algún problema? Por favor, actualice la página o contacte a nuestro gerente de soporte.
Menciones Entrantes y Salientes
---
---
---
---
---
---
Atraer Suscriptores
junio '26
junio '26
+58
en 1 canales
mayo '26
+63
en 2 canales
Get PRO
abril '26
+77
en 2 canales
Get PRO
marzo '26
+58
en 1 canales
Get PRO
febrero '26
+44
en 1 canales
Get PRO
enero '26
+59
en 1 canales
Get PRO
diciembre '25
+98
en 2 canales
Get PRO
noviembre '25
+91
en 1 canales
Get PRO
octubre '25
+77
en 1 canales
Get PRO
septiembre '25
+56
en 1 canales
Get PRO
agosto '25
+103
en 1 canales
Get PRO
julio '25
+85
en 1 canales
Get PRO
junio '25
+99
en 1 canales
Get PRO
mayo '25
+96
en 1 canales
Get PRO
abril '25
+96
en 2 canales
Get PRO
marzo '25
+140
en 1 canales
Get PRO
febrero '25
+107
en 1 canales
Get PRO
enero '25
+190
en 1 canales
Get PRO
diciembre '24
+198
en 2 canales
Get PRO
noviembre '24
+66
en 1 canales
Get PRO
octubre '24
+109
en 3 canales
Get PRO
septiembre '24
+60
en 1 canales
Get PRO
agosto '24
+89
en 1 canales
Get PRO
julio '24
+129
en 2 canales
Get PRO
junio '24
+107
en 2 canales
Get PRO
mayo '24
+109
en 1 canales
Get PRO
abril '24
+120
en 2 canales
Get PRO
marzo '24
+94
en 2 canales
Get PRO
febrero '24
+74
en 2 canales
Get PRO
enero '24
+102
en 2 canales
Get PRO
diciembre '23
+116
en 3 canales
Get PRO
noviembre '23
+81
en 1 canales
Get PRO
octubre '23
+98
en 7 canales
Get PRO
septiembre '23
+79
en 0 canales
Get PRO
agosto '23
+73
en 0 canales
Get PRO
julio '23
+94
en 0 canales
Get PRO
junio '23
+64
en 0 canales
Get PRO
mayo '23
+75
en 0 canales
Get PRO
abril '23
+78
en 0 canales
Get PRO
marzo '23
+84
en 0 canales
Get PRO
febrero '23
+54
en 0 canales
Get PRO
enero '23
+83
en 0 canales
Get PRO
diciembre '22
+62
en 0 canales
Get PRO
noviembre '22
+70
en 0 canales
Get PRO
octubre '22
+54
en 0 canales
Get PRO
septiembre '22
+61
en 0 canales
Get PRO
agosto '22
+48
en 0 canales
Get PRO
julio '22
+73
en 0 canales
Get PRO
junio '22
+47
en 0 canales
Get PRO
mayo '22
+61
en 0 canales
Get PRO
abril '22
+75
en 0 canales
Get PRO
marzo '22
+91
en 0 canales
Get PRO
febrero '22
+57
en 0 canales
Get PRO
enero '22
+99
en 0 canales
Get PRO
diciembre '21
+55
en 0 canales
Get PRO
noviembre '21
+64
en 0 canales
Get PRO
octubre '21
+141
en 0 canales
Get PRO
septiembre '21
+174
en 0 canales
Get PRO
agosto '21
+223
en 0 canales
Get PRO
julio '21
+245
en 0 canales
Get PRO
junio '21
+205
en 0 canales
Get PRO
mayo '21
+161
en 0 canales
Get PRO
abril '21
+520
en 0 canales
Get PRO
marzo '21
+395
en 0 canales
Get PRO
febrero '21
+333
en 0 canales
Get PRO
enero '21
+517
en 0 canales
Get PRO
diciembre '20
+9 090
en 0 canales
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 19 junio | +1 | |||
| 18 junio | +1 | |||
| 17 junio | +4 | |||
| 16 junio | +3 | |||
| 15 junio | +3 | |||
| 14 junio | +5 | |||
| 13 junio | +7 | |||
| 12 junio | +2 | |||
| 11 junio | +4 | |||
| 10 junio | +5 | |||
| 09 junio | +2 | |||
| 08 junio | +1 | |||
| 07 junio | +7 | |||
| 06 junio | +1 | |||
| 05 junio | +1 | |||
| 04 junio | +3 | |||
| 03 junio | +7 | |||
| 02 junio | 0 | |||
| 01 junio | +1 |
Publicaciones del Canal
| 2 | ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ይትሌቃሕ ኃጥእ ወኢይፈዲ። ወጻድቅሰ ይምሕር ወይሁብ። እስመ እለ ይበርክዎ ይወርስዋ ለምድር"። መዝ 36፥21-22። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 6፥7-20፣ 1ኛ ጴጥ 1፥13-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 8፥20-26። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 18፥18-23። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ወይም የቅዱስ ኤጲፋንዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ገብርኤል መታሰቢያ በዓል፣ አቡነ ማትያስ የዕረፍት በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
@Teamihokidusan | 1 |
| 3 | ❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ❤
❤ #ሰኔ ፲፫ (13) ቀን።
❤ እንኳን #ለከበረ_መልአክ_ለሐዲስ_የምሥራች ነጋሪ ለሆነ #ለመላእክት_አለቃ_ቅዱስ_ገብርኤል (በዓልን ያደርጉለት ዘንድ መምህራን በግብጽ አገር ለክርስቲያን ወገኖች ሥርዓት ሠሩላቸው)፣ ለኄኖስ ልጅ #ለቅዱስ_ቃይናን_ለዕረፍቱ_መታሰቢያ_በዐልና #ለኢየሩሳሌም_ኤጲስቆጶስ_ለአባ_ዮሐንስ ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡት፦ ከሰማዕቱ #ከቅዱስ_አቡላግ፣ #ከሁለት_መቶ_ሰማዕታትና ስለ እውነት ከሰደደ ከአባታችን #ከቅዱስ_ማትያንም ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝️ ✝️ ✝️
❤#በዚችም_ዕለት_ለከበረ_መልአክ_አዲስ_የምሥራች_ነጋሪ_ለሆነ_የመላእክት_አለቃ_ለቅዱስ_ገብርኤል_በዓልን ያደርጉለት ዘንድ መምህራን በግብጽ አገር ለክርስቲያን ወገኖች ሥርዓት ሠሩላቸው።
❤ ይህ የከበረ መልአክ የእራኤል ልጆች ከሰይጣን እጅ ስለመዳናቸውና ከምርኮም ስለ መመለሳቸው ነቢዩ ዳንኤል ወደ እግዚአብሔር በሚጸልይና በሚማልድ ጊዜ አስቀድሞ የተገለጠለትና ስለ ድኅነታቸውና ስለ ቤተ መቅደስም መታነፅ የነገረው ነውና። ዳግመኛም ክብር ይግባውና ስለ ክርስቶስ መምጣትና መገደል ስለ ቤተ መቅደስም መፍረስ ከዚያም በኋላ ስለ ሐሳዊ መሲሕ መምጣት ነገረው።
❤ ለመድኅን መምጣትም በሱባዔ የወሰናቸው ዘመናት በተፈጸሙ ጊዜ ይህ የከበረ መልአክ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተልኮ ወደ ቅድስት ድንግል ወደ እመቤታችን ማርያም መጣ ዓለምን ስለ ማዳን የእግዚአብሔር ልጅ ከርሷ ሰው ስለመሆኑ ነገራት።
❤ ስለዚህም የበዓላቶቹን መታሰቢያ እንድናደርግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አባቶቻችን አዘዙን። እኛም ከጠላታችን ሰይጣን እጅ ያድነን ዘንድ ለመንግሥቱም የተዘጋጀን ያደርገን ዘንድ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ፊት ስለ እኛ እንለምነው። ልዕልና ችሎታም ገንዘቡ ለሆነ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን የዚህም የከበረ መልአክ የቅዱስ ገብርኤል ረድኤቱ ከእኛ ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #ቅዱስ_ቃይናን፦ ቃይናንም መቶ ሰብዓ ዓመት ኖረ መላልዔልንም ወለደው መላልዔልንም ከወለደው በኋላ ሰባት መቶ አርባ ዓመት ኖረ ሴቶች ልጆችና ወንዶችም ወለደ። ቅዱስ ቃይናን መላ ዘመኑ ሁሉ ዘጠኝ መቶ ዐሥር ነው ከዚያም በኋላ ዐረፈ። የቅዱስ ቃይናን በረከቱ ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #አባ_ዮሐንስ፦ ይህም ቅዱስ አባ ኢላርዮንና በታላቁ አባ ኤስድሮስ ገዳም በታናሽነቱ መነኰሰ ከአባ ኤጲፋንዮስ ጋራም በገድል በመጠመድ ታላቅ ተጋድሎ ተጋደለ የደግነቱ የተጋድሎውና የትሩፋቱ ዜናም በቦታው ሁሉ ተሰማ። ከዚህም በኋላ ኤጲፋንዮስ በቆጵሮስ አገር ኤጲቆጶስነት ከተሾመ በኋላ እርሱን መርጠው በኢየሩሳሌም ኤጲስቆስነት ሾሙት።
❤ ይህ አባት በሹመት በነበረ ጊዜ ሰይጣን በገንዘብ ፍቅርና በዚህ ዓለም ክብር አሳተው ብዙ ገንዘብ ሰብስቦ ለማዕዱ የሚመገብበት የወርቅና የብር ሣህን አሠርቶ ነበርና ለድኆችና ለምስኪኖችም መራራትን ተወ፤ ምንም የእንጀራ ቁራሽ አይሰጣቸውም ነበር። ቅዱስ ኤጲፋንዮስ በሰማ ጊዜ የቀድሞውን ተጋድሎውንና የዓለም መናኒነቱን ፍቅሩንም አስታውሶ እጅግ አዘነ ከቀድሞ ጀምሮ በመንፈስ ወንድሙና ወዳጁ ነበርና።
❤ ስለዚህም ብፁዕ ኤጲፋንዮስ ከቆጵሮሰሰ ተነሥቶ ወደ ኢየሩሳሌም ወደ አባ ዮሐንስ መጣ አባ ዮሐንስን በጥበብ ከስሕተት ያድነው ዘንድም ክብር ይግባውና የጌታችን መቃብር ባለበት ቤተ መቅደስ ለመስገድ እንደመጣ አገኘው። በተገናኙም ጊዜ አባ ዮሐንስ አባ ኤጲፋንዮስን ወደ ቤቱ አስገብቶ ማዕድ አዘጋጀለት በማዕድም ላይ ከብርና ከወርቅ የተሠራ ሣህኖችን አኖረ አባ ኤጲፋንዮስም በልቡ አዘነ ለድኆችና ለምስኪኖች ርኄራኄ እንደሌለውም አየ።
❤ ከዚህም በኋላ ከእርሱ ዘንድ ወጥቶ በኢየሩሳሌም ካሉ ገዳማት በአንዱ አደረ። ምክንያትም አዘጋጀ ይህም እንዲህ ነው ወደ አባ ዮሐንስ እንዲህ ብሎ መልእክተኞችን ላከ "ወንድሜ ሆይ ከቆጵሮስ አገር ሽማግሎችና የሕዝቡ መምህራን ወደ እኔ መጥተዋልና በእነርሱ ፊት ታከብረኝ ዘንድ ከወርቅና ከብር የተሠሩ የማዕድ ዕቃዎችን ይመገቡባቸው ዘንድ እንድትልክልኝ እሻለሁ" እርሱም ላከለት። ያን ጊዜም አባ ኤጲፋንዮስ ዕቃዎቹን ወስዶ ሸጣቸው ዋጋቸውንም ለድኆችና ለምስኪኖች መጸወታቸው።
❤ ከዚህም በኋላ በተገናኙ ጊዜ አባ ዮሐንስ አባ ኤጲፋንዮስን "የላክሁልህን የማዕድ ዕቃዎቼን መልስ" አለው እርሱም "እሺ" አለው እንዲሁም ሁለተኛና ሦስተኛ ጊዜ ነገረው አባ አረጲፋንዮስም "እሺ" አለው። በአንዲት ዕለትም ክብር ይግባውና የጌታችን መቃብር ካለበት ቤተ መቅደስ ሲወጣ አገኘው ያን ጊዜም ያዘውና "ገንዘቤን እስምትሰጠኝ አልለቅህም" አለው አባ ኤጲፋንዮስም ክብር ይግባውና ወደ ጌታችን ጸለየ በዚያን ጊዜም የአባ ዮሐንስ ዐይኖቹ ታወሩ። ያን ጊዜም ይቅር ብሎት ዐይኖቹን ይገልጥለት ዘንድ እያለቀሰ ወደ አባ ኤጲፋንዮስ ማለደ እርሱም መጸጸቱን አይቶ አንዲቱን ዐይኑን ገለጠለት እንዲህም አለው "ነፍስህን ታስብ ዘንድ አንዲቷ ዐይንህ ዕውርት እንደሆነች ትቶልሃል"። ገሠጸውም እንሆ "ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የቀድሞ ድካምህን ብርታትህንና ተጋድሎህን አስቦ ራራልህ ከስሕተትም አዳነህ" አለው።
❤ "የማዕድ ዕቃዎችንም እኔ እንደሸጥኳቸውና ስለ አንተ ለድኆችና ለምክኪኖች እንደ መጸወትኳቸው ዕወቅ አንተ በገንዘብ ፍቅር መጠመድህንና የቀድሞውን መልካም ሥራህን መተውህን ብሰማ ነው እንጂ ከቆጵሮስ ወደ ኢየሩሳሌም አልመጣም ነበር"። ከዚያችም ሰዓት ጀምሮ ቅዱስ ዮሐንስ ከእንቅልፍ እንደነቃ ሆነ በርኅራኀረም መንገድ ሔደ ያለውንም ጥሪቱን ሁሉ ሰጠ ምንም አላስቀረም ልብሶቹንም ለተራቆቱ ሰጠ በሞተ ጊዜ አንድ አላድ ከዚያም በታች ከእርሱ ዘንድ እስከ አልተገኘ ድረስ ሰጠ።
❤ ጌታችንም የመፈውስ ሀብትን ሰጠው ብዙዎች ድንቆችንና ተአምራቶችን አደረገ ከተቀደሰ ዘይት እየቀባ ፊታቸውንም አዳኝ በሆነ መስቀል ምልክት እያማተበ ደዌ ያለባቸውን ሁሉ አዳናቸው። መልካም ተጋድሎውን ፈጽሞ ክብር ይግባውና ጌታችንን አገልግሎ ሰኔ 13 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ አባ ዮሐንስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሰኔ 13 ስንክሳር።
✝️ ✝️ ✝️
❤ "#ሰላም_ለገብርኤል_በእደዊሁ_ዘተአሥሩ። መላእክተ ሰማይ ጌጋየ በትውልደ ሰብእ ዘገብሩ። ለዝንቱ መልአክ በእንተ ዕበዩ ወክብሩ። በብሔረ ግብጽ መምህራን ሥርዓት አንበሩ። በዛቲ ዕለት ይትገበር ተዝካሩ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሰኔ_13።
✝️ ✝️ ✝️ | 1 |
| 4 | Sin texto... | 1 |
| 5 | ለትልልቆች ነው የሚገባው፣ ትዕግሥት አድርግ…" ሲሉት እርሱም "…ለእኔ የሚሻለኝን ዐውቃለሁ" ብሎ መለሰ። እነርሱም በመልሱ ተገርመው አመነኰሱትና ማትያስ የሚል ስም ሰጡት።
❤ ከዚህም በኋላ አቡነ ማትያስ ቅዱሳት መጻሕፍትን ተምረው በጾም በጸሎት ተወስነው ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን እየተቀበሉ ማገልገል ጀመሩ። በዚኸም ጊዜ ሰይጣን በሥጋቸው ፈተናቸው። እርሳቸውም ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔደው "ኦ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ነፍሴን ተቀበላት፣ ግደለኝ፤ እንዴት ከተወለድኹ ጀምሮ እስከዛሬ ፍጹም የማላውቀው መጥፎ ሀሳብ ከሚመጣብኝ ሞት ይሻለኛል፣ ግደለኝ.. እያሉ ሲጸልዩ የክብር ባለቤት ጌታችን በአካል ተገልጦላቸው በመለኮታዊ እጆቹ ዳስሶ ፈጽሞ አዳናቸው።
❤ ከዕለታት በአንደኛው ቀን አቡነ ማትያስ ከአንድ መነኵሴ ጋር ለገዳሙ ማኅበር ምግብ ለማዘጋጀት ወደ በረሓ እንደደረሱ የሚጠጡት ውኃ ሲያጡ አባታችን ማትያስ ጸሎት ካደረሱ በኋላ በበትራቸው መሬትን ባርከው እንደ ሊቀ ነቢያትሙሴ ውኃ አፈለቁ። እነርሱም የማኅበሩን ምግብ ይዘው ሲመለሱ በመንገድ ላይ ሽፍቶች አግኝተዋቸው ምግቡን ወሰዱባቸው፤ አባታችንም ጸሎት ቢያደርጉ ወዲያው እነዚያ ሽፍቶች ታመው ወደቁ። ከዚያም ሽፍቶቹ "እናንት የአምላክ ሰዎች ሆይ! እባካችሁ ይቅር በሉን፣ የወሰድንባችሁንም እንኩ ውሰዱ፣ እኛንም እርዱን…" እያሉ ለመኗቸው። አባታችንም ምራቃቸውን እንትፍ ብለው በትእምርተ መስቀል አማትበው በእርሱ ዳበሷቸውና ሽፍቶቹ ዳኑ።
❤ ዳግመኛም በአንደኛው ቀን መነኰሳቱ ሁሉም ሥራ ጨርሰው ተኝተው ሳለ አቡነ ማትያስ ግን ደከመኝ ሳይሉ መቶ ሃምሳውንም መዝሙረ ዳዊት ሲደግሙ አደሩ እግዚአብሔርም መላእክቱን ልኮ አንድ ፈረስ ሰጣቸው። አባታችንም በዚህ ተደስተው ለኹለተኛ ጊዜ መቶ ሃምሳውን መዝሙረ ዳዊት ሲደግሞ አሁንም ለኹለተኛ ጊዜ ፈረስ ተላከላቸው። ከእርሳቸውም ጋር የነበሩት መነኰሳት ምን እንደተፈጠረ ሳያውቁ ተኝተው አደሩ።
አቡነ ማትያስን መላእክት ወደ ሰማያት አውጥተዋቸው በገነት ተድላ ያሉ ጻድቃንን አሳይተው ዳግመኛም የኀጥአንን ፍዳና መከራ አሳዩዋቸው። አባታችንም የኀጥአንን መከራ አይተው አዝነው ደንግጠው አለቀሱ። በዚህም ጊዜ "የተመረጥህ ማትያስ ሆይ! አትፍራ፣ እነዚህ ሕጌን የማያከብሩ ትእዛዜን ያፈረሱ ናቸው፣ በተድላ ገነት ያየኻቸውም ጻድቃን ናቸው" የሚል ቃል አጽናናቸው።
❤ ከዚህም በኋላ አባታችን ወደ ምድር ተመልሰው በመጡ ጊዜ አበ ምኔቱ አባ ተወልደ ምድኅን ዐርፈው በእርሳቸው መንበር አባ ፊቅጦር ተተኩ፤ ከአባ ፊቅጦርም በኋላ አስቀድሞ በተነገረው ትንቢት መሠረት አቡነ ማትያስን መርጠው ለመሾም ተስማሙ ነገር ግን አባታችን ማትያስ ሹመቱን እምቢ ሲሉ እጅና እግራቸውን አሥረው በግድ አበ ምኔት አድርገው ሾሟቸው።
❤ አቡነ ማትያስም ወደ ሰማያት ወጥተው የጻድቃንን ደስታና የኀጥአንን ፍዳ መከራ ከተመለከቱና ወደምድር ተመልሰው ከመጡ በኋላ መነኰሳቱን ሁሉ ሰብስበው ሕግንና ሥርዓትን ተግብረው ይኖሩ ዘንድ ስለነገሯቸው ከእነርሱ ውስጥ አንዳንድ ክፉዎች ወደ ንጉሡ ዘንድ ሔደው በብዙ ነገር በሐሰት ከሰሷቸው።
ንጉሡም የተነገረው ሁሉ እውነት መስሎት አባታችንን ከሥልጣን አወረዳቸውና አሳደዳቸው። አቡነ ማትያስም ከገዳሙ ወጥተው ሲሔዱ "ከአንተ ከአባታችን አንለይም ብለው 230 መነኰሳት አብረዋቸው ሔዱ። ከዚህም በኋላ "ትኹል ጎዳዕ፣ ጨዓት፣ ቃቕብዳ፣ ኣቄታብ፣ ወኪ፣ ምድረ ባሕር" ወደተባሉ የተለያዩ | ቦታዎች ሔደው በተጋድሎ ኖሩ። በየበረሓውም ሲጓዙ ልጆቻቸው ውኃ ሲጠማቸው አባታችን መሬትን ባርከው ውኃ አፍልቀው አጠጧቸው። አባታችንም በምድረ ባሕር ሣሉ እህል ሳይቀምሱ በአንዲት ዋሻ ለኹለት ሳምንት ከቆዩ በኋላ በዚኸች ቦታ ላይ በሞት ማረፍ ፈለጉ፣ ነገር ግን እግዚአብሔር መልአኩን ልኮ "ለአንተ የምትሆን ምድር አዘጋጅቼልሃለሁና ወደልጆችህ ተመለስ" አላቸው።
❤ አባታችን ዳግመኛም ከልጆቻቸው ጋር ሆነው ወደ ዓንደቕ ከዚያም ወደ ዒላ ሔደው ለ66 ቀናት ከቆዩ በኋላ ደብረ ብርሃን ደረሱ። አባታችንም ይኸችን ቦታ "እግዚአብሔር የሰጠን ገዳማችን ናት" አሉ። ቦታዋንም ደብረ በረከት ብለው ሰየሟት።
❤ የዕረፍታቸውም ጊዜ ሲደርስ ልጆቻቸውን ሰብስበው በቃለ እግዚአብሔር አጽናንተው "በሥጋ ብለያችሁም በመንፈስ ግን ከመካከላችሁ አልለያችሁምና አትፍሩ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝ፣ የአቡነ ኤዎስጣቴዎስንና የአቡነ አብሳዲን ሥርዓት ጠብቁ…" ብለው ከመከሯቸው በኋላ በእርሳቸው ቦታ ዮሐንስን ሾመውላቸው ከጌታችን ታላቅ የምሕረት ቃልኪዳን ከተቀበሉ በኋላ ሰኔ 13 ቀን በሰላም ዐረፉ።
❤ አቡነ ማትያስም ካረፉ በኋላ ለልጆቻቸው በአካለ ነፍስ እየተገለጡ አጽናንተዋቸዋል ። ከማረፋቸውም በፊት "አስቀድመው .....ከእናንተ ውስጥ የሚማረኩ አሉ፣ ነገር ግን እኔ አድናችኋለሁ" ብለዋቸው ስለነበር ትንቢታቸው ደርሶ ኹለቱ መነኰሳት ተማረኩ ነገር ግን በአባታችን ጸሎት ወደ ገዳማቸው ተመለሱ። ዳግመኛም ከመነኰሳቱ ውስጥ ሰባቱን ዐረማውያን ማረኳቸው፣ ንብረታቸውንም ወስደው ኹለቱን ገድለው፣ አምስቱን በባሕር ውስጥ ጣሏቸው፤ በዚኸም ጊዜ አባታችን ማትያስ በአካለ ነፍስ መጥተው "ልጆቼ አይዟችሁ፣ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝና አወጣችኋለሁ፣ ባሕሩንም በእሳት አቃጥለዋለሁ" ብለው ካወጧቸው በኋላ ባሕሩን በእሳት አቃጥለውታል። ከአቡነ ማትያስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ በእንተ ቅዱሳን ኅሩያን መጽሐፍ።
@Teamihokidusan | 1 |
| 6 | ❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ❤
❤ #ሰኔ_፲፫ (13) ቀን።
❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ በበትራቸው መሬትን ባርከው እንደ ሊቀ ነቢያት ሙሴ ውኃ ላፈለቁት ዳግመኛም በባሕር የተጣሉ ልጆቻቸውን ባሕሩን በተአምራት አቃጥለው ልጆቻቸውን ላዳኑት በኤርትራ አገር የሚገኘውን "ደብረ ብርሃን ወደብረ በረከት ወደብረ ሰማዕት" ገዳም ለመሰረቱት #ለአቡነ_ማትያስ_ዘምራራ ለዕረፍታቸው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #አቡነ_ማትያስ (#ማይታን)፦ አባታቸው በዚህ ዓለም ሀብትና ንብረት ያፈራ ቢሆኑም በመጀመሪያ የክርስትና እምነትን ግን አልተቀበለም ነበር። ሀብቱንም የሚያወርሰው ልጅ ስላልነበረው በዚህ ይጨነቅ ነበር። የአቡነ ማትያስም እናት "…ክርስቲያን ሴቶች እኮ ወደ እግዚአብሔር ለምነው ልጅ ያገኛሉ፣ እኛም ወደ እግዚአብሔር እንለምንና ልጅ ካገኘን ለእግዚአብሔር ይሆናል" በማለት ለባሏ ነገረችው። እነርሱም ከተመካከሩ በኋላ "ልጅ ካገኘን እኛም ክርስቲያን እንሆናለን" ብለው ስዕለት ተሳሉ። ለቤተ ክርስቲያንም ዕጣን ሰጥተው ካህኑን "እግዚአብሔር ልጅ እንዲሰጠን ጸልይልን" አሉት።
❤ እመቤታችንንም በጸሎት ሲማጸኗት ቆይተው እግዚአብሔር ስዕለታቸውንና ጸሎታቸውን ተቀብሎ ልጅ ሰጣቸውና እጅግ ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርንና እመቤታችንን አመሰገኑ። ከዚህም በኋላ ወላጆቻቸው አምነው ተጠመቁና ስማቸው አብርሃም እና ኂሩተ ማርያም ሲባሉ የሕፃኑም ስም ድኁነ እግዚእ ተባለ። አብርሃምና ኂሩተ ማርያምም ፍጹም ክርስቲያኖች ከሆኑ በኋላ እግዚአብሔር በበረከት ጎበኛቸውና ሌሎች ፈቃደ እግዚእ፣ ባርያ እግዚእ፣ ንዋየ እግዚእ፣ ደጋፊነ እግዚእ እና ጥሪተ እግዚእ የሚባሉ አምስት ልጆችን ወለዱ። ስለዚህም አቡነ ማትያስ በ14 መ/ክ/ዘ ጽልማ ታኺታ በሚባል ቦታ ተወለዱ። እርሳቸውም በመጀመሪያ ስማቸው ጥሪተ እግዚእ ተብለው እንደ ቅዱስ ዳዊት የመጨረሻ ልጅ ሆነው በእረኝነት ወላጆቻቸውን ያገለግሉ ነበር።
❤ ጥሪተ እግዚእ ከዕለታት በአንደኛው ቀን ከእርሱ ጋር በግ የሚጠብቁ ጓደኞቹ ከሰው ማሳ እሽት ሰርቀው አምጥተው "ና ከእኛ ጋር ብላ" አሉት። እርሱ ግን የሌላን ሰው እህል አልበላም ብሎ እምቢ አለ፤ ለእናቱም ሲነገራት እናቱ ተደስታ አቅፋ ሳመችው። ጓደኞቹም በሌላ ጊዜ እንዲሁ የተሰረቀ እያመጡ ይበላ ዘንድ ቢፈታተኑትም እርሱ ግን እሺ አይላቸውም ነበር።
በዚኸም ነገር ይህ ታናሽ ብላቴና ጥሪተ እግዚእ ኢትዮጵያዊውን ታላቅ ጻድቅ አቡነ ሀብተ ማርያምን መሰላቸው። ከዕለታትም በአንደኛው ዕለት አባታቸን ሀብተ ማርያም በጐችን ሲጠብቁ ሌሎች እረኞች በአመጻ ከሰው ሰርቀው ቆርጠው ያመጡትን እሸት "ና እንብላ" አሏቸው። አባታችን ግን "ከየት እንዳመጣቸሁት ምንም ስለማላውቅ አልበላም" አሏቸው። እረኞቹም ሀብተ ማርምን በቁጣ ዐይን እያዩአቸው ተቀምጠው ሲበሉ አባታችን "የማንችለው ዝናብ መጥቷልና ተነሡ በፍጥነት ወደቤታችን እንሂድ" አሏቸው። እረኞቹም "ሠማዩ ብራ ነው ምንም ደመና የለውም፤ ነፋስም አይነፍስም። እኛ የማናየው አንተ ብቻ የምታየው ምን ነገር አለ?" እያሉ በአባታችን ላይ ተዘባበቱባቸው። አባታችን ግን በጎቻቸውን እያስሮጡ በፍጥነት ወደ ቤታቸው ሔዱ፤ ወዲያውም በጣም ኃይለኛ ዝናብ ዘነበ፤ የጥፋት ውኃው በላያቸው እስኪፈጸምባቸው ድረስ እነዚያን እረኞች ከቦታቸው አልተነቃነቁም ነበርና በጥፋቱ ውኃ አለቁ። በዚያችም ሌሊት አቡነ ሀብተ ማርያን ከሰማይ ሦስት ጊዜ "ሀብተ ማርያም ሀብተ ማርያም" የሚል ድምፅ ጠራቸው። አባታችንም እንደ ሳሙኤል "ጌታዬ ባሪያህ ይሰማሃል ተናገር" ሲሉ ጌታችን አናገራቸው።
❤ ከዚህ በኋላ "ለሚሰሙ ለመረጥኳቸው ቃሌን ትነግራቸው ዘንድ ከእኔም ጋር በምሥጢር በባለሟልነት ትነጋገር ዘንድ መርጨሃለሁ" አላቸው። ከጥቂት ቀንም በኋላ አባታችን ዳግመኛ በጐችን እየጠበቁ ሳሉ አንድ አመጸኛ መጣና በትራቸውን በኃይል ነጥቆ ወሰደባቸው። አቡነ ሀብተ ማርያምም "በሕያው እግዚአብሔር አምልሃለሁ እቋቋምህ ዘንድ ኃይል የለኝምና በትሬን መልስልኝ" ቢሉት የትዕቢትን ቃል ተናገራቸው። አባታችንም "እምቢ ካልክስ እሺ የእግዚአብሔርን ኃይል ታያለህ" አሉት። ወዲያም ያ አመጸኛ ላዩ ታች ታቹ ላይ፣ ግራው ቀኝ ቀኙ ግራ ሆኖ በአየር ላይ ተሰቅሎ ዋለና እየጮኸ አባታችንን ለመናቸው። አባታችንም "የቀጣህ እግዚአብሔር ይቅር ይበልህ ባሉት ጊዜ ከተሰቀለበት ወርዶ በእግሩ ቆመ። በዚያ የነበሩና ይህንን ተአምር ያዩ እረኞችም እጅግ ፈርተው ሔደው ለወላጆቻቸው ያዩትን ተናገሩ። የሀገሩ ሰዎችም "ቀድሞ እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ እያለ ሲጸልይ ሲሰግድ አይተነዋል፣ አሁንም ጠላቱን በነፋስ የሚቀጣ ይህ ልጅ ወደፊት ምን ይሆን!" እያሉ አደነቁ። ወላጆቻቸውም ይህን በሰሙ ጊዜ በግ ጠባቂነቱን አስተዋቸውና ሃየማኖትን ይማሩ ዘንድ ወስደው ለመምህር ሰጧቸው።
❤ ወደ ጥሪተ እግዚእ ዜና ገድል እንመለስና እርሱም ከአመጸኞች ጋር ባለመተባበር ፈሪሃ እግዚአብሔርን ገንዘብ አደረገ። መንፈስ ቅዱስ በእናቱ ማሕፀን ሳለ እንደነቢዩ ኤርምያስ መርጦታልና በዋዛ ፈዛዛም ከእነርሱ ጋር አይተባበርም ነበር። ፊደልን እንኳን ሳይማር መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት መጻሕፍትን ዐወቀ፣ ትእዛዛትንም ሁሉ ጠበቀ። አባቱ አብርሃምም ዳግመኛ በጎችን መጠበቅ ትቶ ከብቶችን እንዲጠብቅ ስላዘዘው ሕፃኑም በኅብረት የማንንም ከብት ሳይለይ ይጠብቅ ነበር።
❤ በዚህም ወቅት ፈቃደ እግዚእ የተባለው ወንድማቸው ዓለምን ንቆ ገዳም ገብቶ ስለመነኰሰ ወንድሞቹ ሔደው ለአባታቸው ነገሩት፤ አባታቸውም "የእኛ ፈቃድ ሳይሆን የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን" አላቸው። እርሱም ከነልጆቹ እንደሚመነኵስ ራእይ አይቶ ልጆቹን ጠርቶ "ልጆቼ ሆይ! እኛም እንደ ፈቃደ እግዚእ እንመነኵስ ዘንድ አለን" ሲላቸው ልጆቹም "የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን፣ ስሙ በእኛ በባሪያዎቹ ይክበር ይመስገን" አሉ።
❤ ከዚህም በኋላ አራቱ የአብርሃም ልጆች ታኺታ የምትባለውን ቦታ ትተው ወንድማቸው ወደመነኰሰበት ገዳም ለማየት ሲሔዱ ታናሹ ጥሪተ እግዚእም አብሮ ለመሔድ ተነሣ። እነርሱም "መንገዱ ሩቅ ነው አንተ ትንሽ ልጅ ነህ ከዚሁ ቆይ" ብለው ትተውት ቢሔዱም እርሱ ግን ከኋላ ከኋላቸው እየተከተላቸው ሲሔድ እንዲመለስ ያባርሩት ነበር። ከዚያም ሕርሻ የሚባል ቦታ ላይ ሲደርሱ ጥሪተ እግዚእን "ንብረትና ስንቅ እየጠበቅህ ከዚህ ቆየን እኛ ማሳችንን አይተን እንመለሳለን",ብለው ትተውት ሔዱ። እርሱም በዚህ ጊዜ በደብረ ማርያም ያሉ መነኰሳትን ተመለከተና የሚጠብቀውን ንብረትና ስንቅ ትቶ መነኰሳቱን ተከትሎ ወደ ገዳም ሲገባ ወንድሙን ፈቃደ እግዚእን በዚሁ ገዳም ውስጥ አገኘው። ፈቃደ እግዚእ እና መነኰሳቱም ከየት እንደመጣ እየጠየቁት አቅፈው ሳሙት። ጥሪተ እግዚእም አመጣጡን ነገራቸው።
❤ ወንድሞቹም ከሔዱበት ሲመለሱ ጥሪተ እግዚእን ስላጡት እያዘኑ ሳለ የገዳሙ አንድ መነኵሴ ሕፃኑ ወደ ገዳም እንደገባና ከታላቅ ወንድሙ ጋር እንደተገናኘ ነገሯቸው። ወንድሞቹም ወደ ገዳሙ ገብተው አበ ምኔቱን አባ ተወልደ መድኅንን አግኝተው ተባረኩ። አበ ምኔቱም ከወንድሞቻቸው ጋር አገናኛቸውና እያለቀሱ ተሳሳሙ። ከዚያም ወንድሞቹ ወጥተው ወደ ማሳቸው ሲሔዱ ሕፃኑ ጥሪተ እግዚእ ግን በገዳም ቀረ። በዚያም መመንኰስ እንደሚፈልግ ሲናገር መነኰሳቱ "ልጄ ሆይ! ይህ ለአንተ ይከብድሃል ምንኵስና | 1 |
| 7 | Sin texto... | 59 |
| 8 | [ የቅዱሳን መላእክት አማላጅነት ] .mp3 | 66 |
| 9 | 🕊 💖 🕊
[ 💛 የቅዱሳን መላእክት አማላጅነት 💛 ]
🕊 በቀሲስ ኅብረት የሺጥላ 🕊
🩵 † 🩵
❝ የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል ፥ ያድናቸውማል። ❞ [መዝ.፴፬፥፯]
❝ ከክፉ ነገር ሁሉ ያዳነኝ መልአክ ❞ [ዘፍ.፵፰፥፲፮]
† ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በክንፈ ረድኤቱ ከክፉ ሁሉ ይጠብቀን::
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊 | 57 |
| 10 | A a yafomiya eredat neh.mp3 | 136 |
| 11 | 🕊 💖 🕊
🕊 † ቅድስት አፎምያ † 🕊
ከቅዱስ አስተራኒቆስ ጋር በተቀደሰ ትዳር የኖረች
- ምጽዋትን ያዘወተረች
- በፍቅረ ቅዱሳን የጸናች
- ንጽሕናዋን ጠብቃ ሰይጣንን ያሳፈረች ደግ እናት ናት::
ዛሬ የቅዱስ ሚካኤልን ስዕል ታቅፋ : በትእምርተ መስቀልም አማትባ አርፋለች : ቅዱሱ መልአክም ወደ ገነት አሳርጓታል::
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊 | 135 |
| 12 | A MIKAEL.mp3 | 88 |
| 13 | 🕊 💖 🕊
🕊 † ቅዱስ ባሕራን ቀሲስ † 🕊
የደጋግ ክርስቲያኖች የምስኪን የድሆች ልጅ::
- በሕጻንነቱ በግፍ ወደ ባሕር የተጣለ::
- በእግዚአብሔር ጥበብ አድጎ የግፈኛውን ንብረት የወረሰ::
- በመልካም ትዳር በቅስና ያገለገለ::
- ምጽዋትን ያዘወተረ::
- አብያተ ክርስቲያናትን ያሳነጸ ደግ ክርስቲያን ነው::
¤ አርፎ ቅዱስ ሚካኤል ወዳጁ በዕረፍተ ገነት አኑሮታል::
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊 | 85 |
| 14 | Sin texto... | 94 |
| 15 | [ + ነዋ ሚካኤል + ] .mp3 | 89 |
| 16 | 🕊 💖 🕊
💛 🕊 ቅዱስ ሚካኤል 🕊 💛
🕊 🕯🕯🕯 💖 🕯🕯🕯 🕊
❝ ክብረ ሚካኤል ናሁ ተዐውቀ በትሕትናሁ ዐብየ ወልሕቀ ዲበ አእላፍ ዘተሰምየ ሊቀ ዘይትዐፀፍ መብረቀ ይተነብል ጽድቀ። ❞
ትርጉም ፦
[ የቅዱስ ሚካኤል ክብር እነሆ አኹን ታወቀ ፤ በትሕትናውም ፈጽሞ ላቀ ከፍ ከፍ አለ ፤ በአእላፍ ነገደ መላእክት ላይ አለቃን የተባለ መብረቅን የሚጎናፀፍ ርሱ ጽድቅን ይለምናል። ] [ ቅዱስ ያሬድ ]
🕊 🕯🕯🕯 💖 🕯🕯🕯 🕊
❝ የተጨነቀውን የተጨቆነውን ነፃ የምታወጣው ሚካኤል ሆይ ፦ ሰላም ላንተ ይሁን ፡ ሠራተኛው ሠርቶ እንዲበላ ውሎ እንዲገባ የምትጠብቀው ሚካኤል ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን፡፡
ችግረኛውን ለመርዳት ከልዑል ዘንድ የምትላክ ሚካኤል ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን። አዳኝነትህን በማመን የለመነህን በክንፈ ረድኤትህ የምትሠውረው ሚካኤል ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን፡፡
በኀዘን በትካዜ ላይ ወድቆ የሚፍገመገመውን የሚንፈራገጠውን ፈጥነህ ደርሰህ ደግፈህ የምታጽናናው ሚካኤል ሆይ ፤ አንገትህን ዘንበል ቀለስ አድርገህ በፈጣሪ ፊት ሰግደህ እኛ ባሮቹን በቸርነቱ ይጎበኘን ዘንድ የማናዊት እጁን ዘርግቶ ይባርከን ዘንድ ለምን አማልድ ለዘላለሙ አሜን፡፡ ❞ [ መልክአ ሚካኤል ]
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊 | 100 |
| 17 | Sin texto... | 182 |
| 18 | [ + ዓይኑ ዘርግብ + ] .mp3 | 175 |
| 19 | 🕊
[ ርኅሩኁና የይቅርታ መልአክ ]
የርኅራኄ መዝገብ፣ ትሑት፣ ታዛዥና ለዘለዓለም ፈጣሪውን አመስጋኝ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ጌታ በሚያደርገው ቸርነት ላይ ለሰው አንድ ወገን የሚሆን መልአክ ነው፡፡ [ሄኖ.፮፥፭ ፣ ፲፪፥፭ ፣ ፲፥፲፪]
⇨ Michael, one of the Holy Angels, namely the one put in charge of the best part of humankind, in charge of the nation. [ሔኖ ፮፥፭]
⇨ This first is Michael, the merciful and long-suffering without an urge to harm. [ሔኖ ፲፥፲፪]
አምላካችን እግዚአብሔርን የሚፈሩትን እንደ አጥር ሆኖ የሚጠብቃቸው፣ የመልእክት አለቃቸው፣ ምሕረት ማድረግን የተሰጠው፣ የክብር አክሊልን የተቀዳጀ፣ በግርማው የተፈራ፣ የቅዱሳን ወዳጅ፣ የኃጥአን የምሕረት አማላጅ፣ በብርሃን መጎናጸፍያ የሚጎናጽፍ፣ ከክብሩ ብርሃን የተነሣ ምድርን በብርሃን የሚሞላት፣ የቅዱሳንን ጸሎት ከዕጣኑ ጢስ ጋር ወደ እግዚአብሔር የሚያሳርግ፣ በትንሣኤ ዘጉባኤ የመለከት ድምጽ የሚያሰማ፣ በሰማይ ካሉ ሁሉ በላይ በማዕረግ የከበረ፣ ድንቅ ተአምራትን የሚያደርግ ቅዱስ ሚካኤል በዚህ ቀን ያደረገውን ነገር እወቁ !
፩. በመላእክት ሁሉ ላይ አለቃ ሆኖ መሾሙን
፪. ቅድስት አፎምያን መርዳቱን
፫. ቅዳሴ ቤቱን [ግብፅ ውስጥ]
፬. ቅዱስ ባሕራንን መጎብኘቱን
፭. ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ማሳረጉን
፮. ለፍጥረታት ሁሉ ምሕረት የሚጠይቅበት ዕለት ነውና
† ሊቀ መላእክት በክንፈ ረድኤቱ ከክፉ ሁሉ ይጠብቀን::
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊 | 187 |
| 20 | Sin texto... | 291 |
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
