ግጥም ብቻ 📘
✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን። ✔ @getem @serenity13 ✔ @wegoch @Words19 ✔ @seiloch ✔ @zefenbicha @leul_mekonnen1
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ግጥም ብቻ 📘
کانال ግጥም ብቻ 📘 (@getem) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 63 109 مشترک است و جایگاه 784 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 522 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 63 109 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 16 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -241 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -17 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 14.16% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 3.95% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 8 939 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 2 492 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 76 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።
✔ @getem @serenity13
✔ @wegoch @Words19
✔ @seiloch
✔ @zefenbicha
@leul_mekonnen1”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 17 سپتامبر, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 16 سپتامبر | +2 | |||
| 15 سپتامبر | 0 | |||
| 14 سپتامبر | +4 | |||
| 13 سپتامبر | +5 | |||
| 12 سپتامبر | +1 | |||
| 11 سپتامبر | +8 | |||
| 10 سپتامبر | +2 | |||
| 09 سپتامبر | +8 | |||
| 08 سپتامبر | +1 | |||
| 07 سپتامبر | +5 | |||
| 06 سپتامبر | 0 | |||
| 05 سپتامبر | +2 | |||
| 04 سپتامبر | 0 | |||
| 03 سپتامبر | +7 | |||
| 02 سپتامبر | +4 | |||
| 01 سپتامبر | +7 |
| 2 | ሳይፀልዩ ማደር
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የተራበ ነብር ከሩቅ ተመልክታ
ሚዳቆ ፀለየች "አውጣኝ አውጣኝ" አለች ለፈጠራት ጌታ
ነብሩም ተርቦ
ወደ አምላኩ ቀርቦ
አንጀቱ ከሆዱ እንደተጣበቀ
ፈቅዶ እንዲሰጠው አምላኩን ጠየቀ
የሁላችን ሰሪ
ፀሎታቸውንም ሰማቸው ፈጣሪ
አምላክም በድምጹ ሚዳቆዋን አላት
"እሩጠሽ አምልጪ ከበረታው ጠላት።"
ነብሩንም አለው "እሩጥ ተከተላት
ምግብ አድርገህም ብላት"
ሚዳቆዋ ስትሮጥ
ከነብር ለማምለጥ
ነብሩም ሲከተላት
ሆዱን ሊሞላባት
ቋጥኙን ስትዘል እግሯ ተስፈንጥሮ
ሆዱን ብትረግጠው የተኛ ከርከሮ
ከእንቅልፉ ሲነቃ ልክ ሲደነብር
ጉሮሮውን ያዘው የፀለየው ነብር
አውጣኝ ያለው ወጥቶ አብላኝ ያለው በላ
ሳይፀልይ ያደረው ከርከሮ ተበላ።
By በረከት በላይነህ
@getem
@getem
@paappii | 3 388 |
| 3 | ደርሷል ትዕዛዛችን ፣ እንብላ ከእህሉ
አዘን አዘን የተቀመጥን ፣ ዳስዳስ ያለን ሁሉ
እንደአበሻ ገበሬ ፣ አርሶ እንዳጨደ
ነዶን ከምረን ፣ እጃችን ሰብል ያዘ
የመብቃትን ማዕረግ ፣ የመድረስን ከፍታ
እጃችን ጨብጦ ፣ ክንዳችን ባይገታ
ግና
ግና ሆዳችን ፣ አልጠገበም ሞልቶ
ሰው ሰው ተርቧል ፣ ወዳጁን አጥቶ
የእራሱ ራስ ከዳ ፣ የሆዱን ሆድ ፈጀ
ፍቅር እየዘራ ፣ አሜከላ አጨደ
ሰውን ሰው ራበው ፣ ሰውን ሰው ተጠማ
አበሻ በታሪኩ ፣ ዛሬ ብቸኝነት ደማ።
By ናትናኤል_አበበ
@getem
@getem
@getem | 6 131 |
| 4 | ብንሥቅም ፡ ባንሥቅም
አደይ ቀርታ አታውቅም።
by Seifu Worku
መልካም አዲስ አመት
@getem
@getem
@paappii | 6 737 |
| 5 | ትዝ ይልሻል?
የዛሬው ዋዜማ በጳጉሜ 5 አምና
ከበርሽ ነበርኩኝ
የሀሳቤን ልኖር ደጅሽን ስጠና
አይገርምም?
ድሮ ልንል በቃን እኒያ ቀናት አልፈው
ትዝብት ሊሆኑን በፊደል ተጽፈው
ይሄውልሽ አለሜ ይሄንን እወቂ
፡
እንዳለፈው ዘመን
ለእኔ ኑሪ እያለ
ደጅ ይጠናል ብለሽ እንዳትጠብቂ።
፡
ባይሆን
እኔ የምፈልገው
ይሄን አዲስ ዘመን ንጹህ እንቁ'ጣ'ጣሽ
ለሚመጣው ዓመት
:
ከሀሳቤ አሻግሮ
:
ከስኬቴ ጀርባ አምላክ አንችን ያምጣሽ።
ጳጉሜ ፭ ፳፻፲፰ እኩለ ሌሊት
By ይክበር ፀጋዬ
@getem
@getem
@paappii | 6 255 |
| 6 | አዲስ አመት
.
.
ያ...ጠቢብ ሰለሞን..........
ያማረ ቀለበት ከእጅሽ ያጠለቀዉ፤
ምን ያክል ዉበትሽ ልቡን ቢገዛዉ ነው?
ከአደይቷ ይልቅ ደምቀሽ ብትታይዉ፤
ሽንፈት የማያዉቀዉ ፍቅርሽ አሸነፈው።
ትዋቢበት ዘንዳ ዉብ እንቁን ለጣትሽ፤
ችግር ሲያገኝሽ ማለፊያ ለጣጣሽ፤
አንድም ለልብሽ ነዉ ማሰሪያ ለቃልሽ፤
ለቅድስቷ ምድር አንድም ለሀገርሽ።
የካም እድል ፈንታ እንቁ ዕጣ ለወጣች፤
ጸሎቷን ለማድረስ እጇን ለዘረጋች፤
ህመምሽ ለሆነች ፈዋሽሽም እሷዉ፤
ለቅድስቷ ምድር አንድም ለሀገርሽ ነው።
ዛሬም ለሀገሬ........
መከራ እንደ ሀምሌ ፀንቶ ላጨገጋት፤
ዉሽንፍር መባርቅት አብሮ ለሚንጣት፤
ቀለበትሽን አዉሻትና........
መከራዋ ያብቃ ነጭ ልብስ ትልበስ፤
ተስፋዋ ይለምልም በፍቅር ትታደስ፤
እንባዋ ታብሶ ብርሃን ይታያት፤
በዚ በአዲስ አመት ደግ ቀን ይዉጣላት።
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
✍✍ዔደን
@topazionnn
@getem
@getem | 5 579 |
| 7 | "እኔ
ባዲስ ቀን አላምንም
ቀን ከቀን አልለይም
አሮጌ መሆን ነው የቀረኝ አንድ አቅም!"
የሚል ድባቴያም ሰምተህ ግን አታውቅም?!
ካደፈ ልብሱ አልፎ ከርሞ ልቡናውን እያስተባበረ
መስኮት ግድግዳውን እያሰማመረ
ድባብ የሚጨምር ደርሶ ባያየውም
እንዲህ ያለውንስ አላስተዋልኸውም?!
ግን
ከዚ ሁሉ ረቅቀን መጠቅ ነጠቅ ብለን፣
ከአይደለም እና አዎ መሃል ወጥተን፣
ካዲስነት ጀርባ ምን ታምር ታይቶሃል?፣
እውነትም ብርሃን ያለው ይመስልሃል?!
...
መልስ ያበጀህ እንደው ያጣህም እንደሆን
ወዴት ትሸሻለህ ተቀባይ ከመሆን?!
ሰው ፍጡር ነውና የለም የሚዘልለው፣
ከሚሆነው መሃል እንዳይሆን ሚነቅለው!
መቼም አለመቻል አስካቆረመደው
ሰውነት አንድ እርሙ መቀበል ብቻ ነው!
እናም..
ከመፈለግና ከመመኘት በስቲያ
እንደፈቃዳችን ከመናፈቅ ወዲያ
አዲስ ቀን ያው ቀን ነው መምጣቱን አይተውም፧
ተአምር ቢያመጣልን ወይ
አንዳች ባይፈጥርም፣
ከመኖር አይበልጥም።
አደይ ታብባለች ጠሃይ ትወጣለች
ህይወትም አትቀልልም፣
...
(ወደሚቀጥለው ብናልፍ አይሻልም?)
ለምኑም ለምኑም:(
@mypoems396
@getem
@getem
@getem | 6 103 |
| 8 | ድልድይ ናት ጳጉሜ ከዝያ ወደዚኛው፣
ከመጨረሽኛው~ወደ~መጀመሪያው
ሲታደል አይደል ወይ ቋጭቶም ለመደምደም፣
የዓመት ቆይታን በ5 ቀን መገምገም!
@mypoems
@getem
@getem
@getem | 7 338 |
| 9 | @mypoems396
@getem
@getem
@getem | 9 841 |
| 10 | @mypoems396
@getem
@getem
@getem | 10 230 |
| 11 | «ናፈቅሽኝ አቦ !» ብዬ የፃፍኩት
ኩራት ሲሰማኝ - ቀድጄ ጣልኩት ።
«ናፈቅከኝ በጣም» ብለሽ የፃፍሽው
ልምምጥ መስሎሽ
ወርውረሽ ጣልሽው ።
የፍቅር ብርሃን እንዳልተሰማን
ቅር እንዳላለን እንዳልናፈቅን
በአዲስ ወረቀት - ፀብ ተላላክን ።
እንበልና ...
እኒያ ወረቀቶች ...
ቀደን የጣልናቸው
የክረምት ጎርፍ አገናኛቸው ።
እስኪ አስቢያቸው ...
ደራሽ ተሳፍረው
ሆነው ጎን ለጎን
እርስ በርሳቸው ተያይተው ቢሆን ?
ምን ይሉ ይሆን ?
By Habtamu Hadera
@getem
@getem
@paappii | 9 951 |
| 12 | ๘
ቃና አልባ ህይወቴ
የፈሰሰ ሀሞቴ
ጣዕም ፣
መልኩ ጠፍቶ ፡ የጠቆረ ወተቴ
ያ ‛መት ሙት አመቴ 𓏸 𓏸 𓏸
ተሰርዮልኛል ! !
....ተሰርዞልኛል...
እናትነት ፍቅርሽ ፡ ያለፍኩትን አይቶ
፤ አዝኖ ራርቶልኛል
ከአዘቅት እመቃት ፡ከባርያነት ግዞት
ለይቶ አንስቶኛል ⨳
ఎ
ማህፀንሽ ሳለሁ ኪዳን ገብተሽልኝ
ያንቺን መልከ ስጋ ˔ ከእግዜር ገዝተሽልኝ
. . . አገልግለሽኛል
ተርበሽ ተጠምተሽ አሳድገሽኛል ꨄ
𓏲 አፈር ግፈሽ ቅመሽ
ርኩስ ፍጡር ወንድን በስራሽ አስንቀሽ
‟ቅድሚያ ላንተ” ብለሽ
ከሰው እኩል አርገሽ
አሁን ያለሁትን ፣
ነገ ምሆነውን . . . ሰውነቴን ሰራሽ !
{ አበጀሽ ! አበጀሽ ! }
𓏲 እናት ሴት እናቴ
ኅቡዕ ቃለ~ጥበብ ˔ የፀሎት ቅናቴ
ከፈራረስኩበት ፣
ከወለገድኩበት ፣
ደርሰሽ አንከብክበሽ ፥ በፍቅርሽ መቅናቴ ⨳
𖥔
[ ምን ትባል ፅዕዱቴ ?
. . . በምን ስም ትጠራ
ምድራዊ የሆነች የሰማያት ጣራ ]
𓏲 ስላንቺ ማንሳቱን ˔ ላልፈፅም ሰደርኩት
ላላከትም ካደምኩት
ቢሆንም
ቢሆንም እንኳንም ጀመርኩት...
< ግዴም ሆኖ ቢገኝ አበጀሁ >
እሺ by ሰምረ የሽዋስ
@getem
@getem
@getem | 8 806 |
| 13 | ታግሼ እንዳላልፈው ፥
ክህደት ስላጠቃኝ
አበባ እሰጥ ብዬ ፥
እሾህ ስለወጋኝ
ሁሉንም ለመተው ፥
ትንሽ ነው ሚበቃኝ
By ሲራክ ወንድሙ
@getem
@getem
@paappii | 7 764 |
| 14 | 🔔 ውድ የቻናላችን አባላት፣ አዲስ የምስራች አለን!
የተመረጡ ግጥሞችን እና ሀሳቦችን, ወጎችን የምናጋራበትን ጉዞአችንን የበለጠ ለማሳደግ እና ጽሁፎቻችንን ባማረ ሁኔታ ለማቅረብ አዲስ Substack ገጽ ከፍተናል!
📌 ግጥሞች ለማንበብ እና አዳዲስ ጽሁፎቻችን በኢሜይል እንዲደርሷችሁ ከታች ያለውን ሊንክ ተጭነው Substack ገጻችንን Subscribe ያድርጉ፡
https://substack.com/@getembicha
@getem | 9 911 |
| 15 | ትናንትን በዛሬ_!
ያቺ ትናንቴ ሀ--ሁ-- ዬ የነበረች፣
የሆነ ቀን ዛሬ ነበረች።
እንድያው ሳላስብ ዘንግቻት፣
ይሄው ዛሬ አስታወስኳት።
ቁጭ ብዬ በዛሬ ፊት ስታዘባት፣
የኳተነች ጎስቋላ ፊት የነበራት፣
በደስታ እና በፈተና የረሳዃት፣
ይሄው አሁን በዛሬ ፊት አነሳዃት።
ከፊቴ ፊት ቁጭ ብላ ስትስቅብኝ፣
ስጠብቃት ብን ብላ እንዳጠፋኝ።
ባትሆን ኖሮ የኔ ትናንት፣
ይችን ዛሬ-- አሁን ባልል ታምኜባት።
መምህሬ የኔ ትናንት፣
መቆሚያዬ የዛሬ እናት፣
የጉዞዬ እርሾ የነገዬ ርስት፣
የጉልበቴ ሰደፍ የዘመኔ ሽበት።
በ መ/ር ሰይድ: ነሐሴ 6, 2018
@getem
@getem
@getem | 8 732 |
| 16 | ውደቅ እስቲ ላንዴ
እንደ ጥልያን ጦር፣
ገላህ ይሸለታል
በጦር በጎራዴ።
፡
አንተ ባለ ክብር !
ላንዴ እስቲ አቀርቅር
መታሸት ያወዛው …
ጀርባህ ይነረታል ፣
በዱላ ና በትር።
:
ተገልጠህ ብታየው
ትከ’ሻህ ተከፍቶ
አናትህ አይተርፍም
በኮናኝ ተሞልቶ።
.
ፅጌረዳ የሰጠህ
በዘመንህ ወራት
እሾሁን ያስቀራል
ቅጠሏን አራግፏት።
:
ከፊት ስትቀርብ አይደል?
(እንደ ለቅሶ ንፍሮ)
ተዘግነህ ‘ምታልቀው
ልኬትህ ተሽሮ ?
:
ተሞልቷል ከተማው
በድንጋይ ፣ በምሳር
ዘንበል ያልህ ጊዜ
ተቋጥሮ ያመሻል
የፈካልህ ግንባር ።
:
ብቻ!
ወንዝ እንደወረደች
የገጠር ኮረዳ ፣
ላስቲክ ጫማዋ ስር
አዳልጧት በነበር
ረጢብ እንግጫ ፣
-
ሚዛን ስተህ ውደቅ
በቋጥኝ ፣ በጭንጫ ፤
፡
ያጨበጨቡ እጆች
ጉያህ ይሰርጋሉ፣
ደግሞ ለቁንጥጫ ።
(ሚካኤል አ)
@getem
@getem
@paappii | 9 107 |
| 17 | ተኳረፍኩኝ ካገሬ ጋር
ተሳቅቄ ሆኜ ከዳር
ጀርባየን አላምነውም
ጠላቴንም አላውቀውም
ማውቀውንም አላውቀውም
ባውቀውም አልንቀውም
መተንፈሻ አጣ አገሩ
ኩፍ በዛ በየዳሩ
ሰቀቀን በርዞታል
አይጥምም አየሩ
ዘር በዛ ባገሩ
አዲስ ጠፋች በአበባ
ሚሰቴ አሏት ባለቤቴን
ቀለበቴን አይቶ አገባ
አገሯ ዳር ናት
ሰውም ወድቋል ጥጉጥጉ
ሬሳው ሳይነሳ
ዘሩን ዘሩን እየፈለጉ
አዲስ አመት ባክህ ና
አታብቅል አበባ
ኢትዬጵያን ሚሏት ሀገር
ባይሆን ይዘህ ግባ
.
.
ግዕዝ ሙላት
@geez_mulat
@getem
@getem
@getem | 8 538 |
| 18 | °.
ልቤን አታናጋው ፣
እንደቆየ ተስፋ
ሳልፈልግህ መጥተህ ፣
ስወድህ አትጥፋ።
By መክሊት
@getem
@getem
@paappii | 7 767 |
| 19 | በቃኝ
-----------------------
እሳት ሆኘ ስነድ፥
አንች ቆፈን ወርሶሽ
ሎሚ ብወረውር፥
እንቧይ ሆኖ ደርሶሽ
ዝምድና ሳያንሰን፥
እየቆየሽ ባዳ መላመድ
ሳይጎድለን፥ እያደርሽ እንግዳ፤
እንግዲህ ደህና ሁኝ!
ምኞቴም በረደ፥ ቁጣየም አለፈ
ከእድሉ ጋር ታግሎ፥ ማነው-ያሸነፈ።
By Bewuketu Siyum
@getem
@getem
@paappii | 10 214 |
| 20 | //<ውሸታም> መባል..አሁን ስድብ ነው?//
@mypoems396
@getem
@getem
@getem | 10 105 |
