ግጥም ብቻ 📘
✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን። ✔ @getem @serenity13 ✔ @wegoch @Words19 ✔ @seiloch @shiyach_bicha ✔ @zefenbicha @leul_mekonnen1
显示更多📈 Telegram 频道 ግጥም ብቻ 📘 的分析概览
频道 ግጥም ብቻ 📘 (@getem) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 63 813 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 794,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 494 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 63 813 名订阅者。
根据 30 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -398,过去 24 小时变化为 4,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 15.55%。内容发布后 24 小时内通常能获得 4.21% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 9 925 次浏览,首日通常累积 2 684 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 103。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።
✔ @getem @serenity13
✔ @wegoch @Words19
✔ @seiloch @shiyach_bicha
✔ @zefenbicha
@leul_mekonnen1”
凭借高频更新(最新数据采集于 01 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
数据加载中...
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 01 七月 | +6 |
| 2 | ሀሜት የት ነበረ??
በፊት....
የጎረቤቴ በር በቀን አይዘጋም
እኛም ለመፋቀር መሽቶልን አይነጋም
'አቡሽ' ቡና ጥራ...ሲሉን ደስ እያለን
አዋቂው ሲታደም ጓዳ ግባ ሁላ መቼ እናውቃለን??
ልክ እንደ ቡና ቁርስ መሀል ቁልጭ ቁልጭ
ሲያዝኑ እያዘንን ሲስቁም መብለጭለጭ
ውሉን ባንረዳው የጨዋታቸውን
እናውቅ ግን ነበር አንጀት ሆዳቸውን፤
እንከን በየዘመን፣ጥልም በየጊዜው ነበረ አይካድም፣
ግን በኛ ልጅነት እዛው እርቅ ይወርዳል ወዴትም አይሄድም፤
አሁን...
ባህል የለሽ ወጉ እኛን አርቆናል
በዘመን መዘመን ስራ አቀለለ እንጂ እኛን አቅልሎናል፤
ንግግር በግጥም ወዝ ቸፍ ቢልበት
ለአንዳንዱ ይከብደዋል ለአንዳንዱ ቀሎበት
ከእውነታው አልርቅም መቅረቡ ይጥመኛል
ከማስመሰል በላይ መምሰሉ ከብዶኛል፤
በቀን ሰው ፈርተናል የጨለመው ጥሞን
ውሸት ሰፍቶብናል ቀናው መንገድ ጠቦን!
እሺ....
ይሄ መፈራራት ፣ይሄ መተማማት ኢትዮጵያን ካስቀረ፣
ያኔ ልጅ እያለን 'ሀሜት' የት ነበረ????
@Weyblann ያቡ
@getem
@getem | 3 259 |
| 3 | ለምን አይባልም
-------------------
አንዱ
ዘመኑን በሙሉ ፤
ያለምንም እረፍት ተግቶ ያስቀድሳል
ሌላው....
"ባንድ ቀን ንሰሀ ፤
ከፃድቁ እኩል፥ ገነትን ይወርሳል ።
ይህንን እያየ ...
ልባችን አስካክቶ ጥያቄ ቢጥልም እግዜር አዋቂ ነው ለምን? አይባልም።
By kirubel
@getem
@getem
@paappii | 3 644 |
| 4 | የውድቀቴን መንገድ
ሸርሽራ በመውደድ
ያቀናችኝ ንግስት ... የሰጠችኝ ክብር
አቤት አቤት ሲያምር
{ልክ እንዳንቺ ማርያም}
መኖር እንድጠላ መንፈሴን አድክሞ
ማጣት አንቆኝ ሲዞር ክንዱን አፈርጥሞ
የምሆነው ጠፍቶኝ
ተንበርክኬ ሳዝን ሳትለኝ ደካማ
ቀና አረገችኝ ቀንበሬን ተሸክማ!
እምቅ የእንባ ጠል
ጉንጬን ሲንጠለጠል
ኅዘን በደቆሰው ልስልስ ስስ አንጀቷ
ዕንባዬን ያበሰው
አቤት ሲያምር ጣቷ
{ልክ እንዳንቺ ማርያም}
እኔነት እስካጣ ፍቅር ሸሽቶኝ በሮ
ብቸኝነት ሚስማር ሲያደማኝ ቸንክሮ
የማረገው ጠፍቶኝ
ሞቴን እየናፈቅኩ ሳዘጋጅ መስቀሌን
ትንፋሽ ለገሰችኝ ዳብሳ ሰንበር ቁስሌን
የጅራፍ ሹል ትርትራት
የልቤ ስውር ስብራት
አድቅቆ ሲጥለኝ ... እንዲሆን ለነፍሷ
ስሞ ሳቅ ያሳየኝ
አቤት ሲያምር ጥርሷ
{ልክ እንዳንቺ ማርያም}
ስትችልበት ማዘን
ስታውቅበት ማቀፍ
ብሶት አስዘርግፎ
በሰላም ማሳረፍ
{ልክ እንዳንቺ ማርያም}
ስትችልበት ጸሎት
ስታውቅበት ማውራት
ጨለማን ገርስሶ
በፈገግታ ማብራት
{ልክ እንዳንቺ ማርያም}
ስትችልበት ማከም
ስታውቅበት ማዳን
ፍቅር በልብ ሰጥቶ
መለገስ ማር ኪዳን
#ኤልዳን
@eldan29
@getem
@getem
@paappii | 4 655 |
| 5 | የራስ ገድል!
^^ ^^ ^^ ^^ ^^ ^^ ^^ ^^ ^^
ደፈጣ ነው ውጊያ ብቻ፥
መገዳደር ያለ መርቻ፣
ላለመርገፍ ተቀርጥፎ፥
ላለመውደቅ ተዝለፍልፎ!
የማልጣል ተንጠልጥዬ፥
የማልወድቀው ተፈንቅዬ፥
ይሄው ምርኮ ከ'ግሬ በታች፣
በረሃዬን በእምባ ሸማች።!
ቀራንዮ በኮረብታ፣
የብቻዬን ጎለጎታ፣ ... ... ..
ችንካር አለው ደግሞ ስቅል፣...
የራስ ምርኮ የራስ ገድል።፨!
@alem3_b [ዓለም]
@getem
@getem
@getem | 4 479 |
| 6 | ¹
አለሽ የሆነ ነገር......
አለሽ የሆነ መስህብ ....
አለሽ የሆነ ግርማ.......
(እንዲያ ባይሆንማ.....)
ወደ ላይ.... ወደ ላይ......
(ወደ ጥጥ ደመና) ሽቅብ መንጠራራት (መኩራራት) ሳያንሰው ፣
ዝቅ ሊል ወዳንቺ —···
ዋርካን እንደ ሐረግ ምን አልፈሰፈሰው?
ያልለመደበትን (ያ'ላፈጣጠሩ) ስለምን ይቸገር?
አለሽ የሆነ ነገር....!
²
(እኔማ በእኔ ቤት......)
ከሆዱ በልጦበት....
ገበሬ ለውበት —···· እርሻውን አይለቅም ፣
ወፍ ያለ አይመስለኝም....
ዝማሬ የማያውቅ —··· ስንጥር የማይለቅም ፣
ሰው ገላ ላይ ሆኖም —···መንደፍ የጠፋበት — ንብ አይቼ አላውቅም ።
እንዲህ ያለ ጥበብ — እንዲህ ያለ መላ ፣
ባንቺ አየሁ ፡ ባንቺ አየሁ — የታለ በሌላ?!
³
አለሽ የሆነ ነገር....
አለሽ....!
ከጥንት መንፈስ የተዋረሰሽ ....
እንደ ደሊላ — የጀግናውን ልብ ያስበረገገ
(ሳምሶንን ድኩም ያረገ ) ።
እሷስ በአንዲት መቀስ — በፀጉር መላጫ ፤
ይበልጣል ያንቺ ሳቅ — የጥሜ መቁረጫ ።
⁴
አለሽ የሆነ ነገር.....
ያቺ “ሔለን” ሚሏት የግሪክ ሀገር ውብ
የትሮይ ምርኮኛ ፤
የጠፋች እንደሆን እሷን ለማስመለስ......
በሺህ መርከብ ፈረስ — ዘምቶ አየን ጦረኛ ።
ሰውማ አመሉ ነው ይዋጋል ይሞታል ፤
አይበቃም ላንቺ ግን ባህሩም ይዘምታል።
⁵
አለሽ የሆነ ነገር.....
አዳም የጥንቱ — ቀልብ የሳተበት
ሕግ የሻረበት (የሔዋን ፍቅር)
የተቀጣበት ።
(የእሱን አየን....)
ገነት ሲቀር (ሞት ሲመጣ)
በአንዲት ፍሬ — ትንሽ በለስ ፣
እኔስ ባንቺ የገባሁት —···
ሃጢያቴ በምን ይመለስ?
አለሽ የሆነ ነገር....
__
By Bekalu shumye
Inspired by Cole Porter's: “You've got that thing ”
@getem
@getem
@paappii | 4 886 |
| 7 | ይቅናት
.
.
ልጂት ተላላ አይኗም ቀልቃላ
በሺ ሰው ትኩረት ልቧ ማይሞላ
ሁሉንም መያዝ ሁሉንም ማግኘት
ሰላሳ ነገር ባንዴ መመኘት
የማያደክማት እረፍት የማታውቅ
ገና ጅምር ናት ተፈጥራ ማታልቅ
ደሞ ታምራለች እግዚኦ መልኳ
አይደርስባትም ሉሲፈርንኳ
አይኗም እንደ ልጅ አንጀት ያባባል
ጉድፍ ገብቶበት ውበት ያነባል
ልኬት የላትም ማነፃፀሪያ
ንጉስ ቢጠጋት ይመስላል ባሪያ
ኧረ'ዲያ....!
እኔ ግን ልቤን ልኬን ስለማውቅ
ቅዠት ህልሜ ላይ ከምደባልቅ
ምንም ብወዳት ምንም ብታምርም
መ'ላክ ጠልፌ ከቤቴ አላስርም
የራሴን ቀብር በጄ አልቆፍርም
ትሂድ ትንሳፈፍ ክንፏን ታማታ
እድል የቀናው የማታ ማታ
ላባዋ ሲረግፍ ዳዴ ስትጀምር
ያግኛትና መንገዷን ያስምር...
እያልኩ ለሰው ቸር እመኛለሁ
አልችላትማ... ምን አደርጋለሁ?
By Tadios Alemayehu
@getem
@getem
@paappii | 6 004 |
| 8 | @topazionnn
@getem
@getem | 7 258 |
| 9 | ላ'ባቴ
ሰው ብቻ አይደለህም፣
ካፈር ወጥተህ ላፈር
መላክ ነህ ሉሲፈር...
ክብርህ ማንነትህ፣ ባመፅ የሚታፈር
የማትንበረከክ የማትርመጠመጥ፣
ከባለጌ ዙፋን በርጩማ የምትመርጥ።
ያለ ባህር ሰርጓጅ ያለ ሙሴ በትር፣
በመታገስ ብቻ ባህር የምትመትር።
ካዘልከኝ ጀምሮ በእንኮኮ ጫንቃህ ላይ፣
ከፍታውን እንጂ፣ ዝቅታውን ሳላይ።
እንደ ንሥር መጠቅሁ፣ እንደ ኮከብ በራሁ፣
የገዛ ክንፎቼን እንደ ዳንቴል ሰራሁ።
በርግጥ ደሀ ነበርክ...
ከሰላምታ በቀር የማታበረክት፣
ነጠላህ መናኛ፣ ሰውነትህ የክት።
በርግጥ ደሀ ነበርክ፣ የነጣህ የጠራህ፣
ከጦር ሜዳ ይልቅ፣ ገበያ ሚያስፈራህ።
ቤሳ ባታወርሰኝ፣ አወረስከኝ ትግል፣
የትም እንዳይጥለኝ ህይወት እንደ ፈንግል።
አባዬ ብርሃን አባ የምስራቅ በር፣
ገመና ሸሻጊ እንደ ካባ ገበር፣
አባቴ ባትሆን፣ ምን ይውጠኝ ነበር።
By ብዕውቀቱ ስዩም
@getem
@getem
@paappii | 9 129 |
| 10 | እንዳትረሺኝ ብዬሽ፤
አትርሳኝ ብለሽኝ ፤
በቃል ክር አስሬሽ፤
በቃል ክር አስረሽኝ፤
በደልሽኝ በደልኩሽ፤
በደልኩሽ በደልሽኝ ፤
ቃልሽን አከበርሽ
ቃሌን አከበርኩኝ ፤
ይሄ በደላችን...
እንኳን በ'ዚህ ሕይወት
በመቃብርም ውስጥ ችሎ አያረሳሳም፤
ደግሞ እንደምታውቂው
የወዳጅ ፍቅሩ እንጅ በደሉ አይረሳም ።
By Tewodros kassa
@getem
@getem
@paappii | 10 368 |
| 11 | 📢 የሰላም ድምፆች | Voices for Peace
የግጥም ስብስብ (Anthology) — የሕትመት ጥሪ
ዓለም አቀፉ የፀሐፊያን ማኅበር PEN International አባል የሆነው PEN Eritrea፣ ‘የሰላም ድምፆች’ በሚል ርዕስ ለኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ገጣሚያን የሚሆን ድንቅ የጋራ መድብል የሕትመት ዕድል አዘጋጅቷል።
📌 መሥፈርቶች
✍️ ከዚህ ቀደም ያልታተሙ እስከ 3 ግጥሞች (በአጠቃላይ ከ5 ገጽ ያልበለጠ)
🕊️ ጭብጥ፦ ሰላም፣ ግጭት፣ ተስፋ፣ ስደት፣ መትረፍ (Survival) ወይም ተያያዥ ማኅበራዊ ጉዳዮች
🌍 በየትኛውም ቋንቋ የተጻፉ ግጥሞችን ማቅረብ ይቻላል
🎁 የተመረጡ ግጥሞች፦
📖 በጋራ መድበል ተሰብስበው ይታተማሉ
✍️ ከገጣሚያኑ ጋር በመመካከርና ባለቤትነታቸው ተጠብቆ ወደ እንግሊዘኛ ቋንቋ ይተረጎማሉ
👉🏾 የተመረጡ ገጣሚያን የ $200 ዶላር (ሁለት መቶ ዶላር) ክፍያ ያገኛሉ።
📅 ማብቂያ ቀን፦ ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ.ም. (June 29, 2026)
🔗 ዝርዝር መረጃና ማመልከቻ ሊንክ፦
አማርኛ፦ https://peneritrea.com/blog/%e1%8b%a8%e1%88%b0%e1%88%8b%e1%88%9d-%e1%8b%b5%e1%88%9d%e1%8d%86%e1%89%bd-voices-for-peace-%e1%8b%a8%e1%8c%8d%e1%8c%a5%e1%88%9d-%e1%88%b5%e1%89%a5%e1%88%b5%e1%89%a5
English: https://peneritrea.com/blog/%e1%8b%a8%e1%88%b0%e1%88%8b%e1%88%9d | 9 822 |
| 12 | ሰራተኛ እያፈላለኩ በደላላ አንዲት ልጅ አገኘው
አንገቷን እንደደፋች "ጋሽዬ እኔ የስራ ሆነ የሙያ ችግር የለብኝም ብቻ ስራ እንዳልቆይ ተደግሞብኛል ፤ ሰርቼ እንዳልለወጥ አሰርተውብኛል" ምናምን ብላ ዘበዘበች
"ብሎ ነገር የለም እኔ ተረት ተረት አልወድም ድግምት ምናምን የለም " ብዬ ካለችው አምስት መቶ ብር ጨምሬ ቀጠርኳት
21 ቀን እንደሰራች
አንዴ
ጠረጴዛዬ ላይ አንገቴን ደፍቼ እየፃፍኩ አንድ ሶስቴ ስጠራኝ አልሰማ ብያታለሁ መሰለኝ
"ምን አባህ ይዘጋሃል ብላ"
ይዛው በነበረው ፔርሙዝ አናቴን አለቺኝ
ተጮኸ። I think እኔ ነኝ የጮህኩት
ጎረቤት ተሰበሰበ መቼ ፣ ማን እንደመታኝ በደንብ ያወቅኩት ከሁለት ቀን በኋላ ነው
መንፈስ ፣ ድግምት ፣ ተተብትቦብኛል የሚለኝ ሰው ሲገጥመኝ የጀመረውን አረፍተነገር ሳይጨረሰው ነው የማመልጠው
የሻሼን ፍንክት የቀመሰ ሰው በዚህ ነገር አይፈላሰፍም 😁
By Adhanom Mitiku
@wegoch
@wegoch
@paappii | 1 |
| 13 | እስኪ ንገሪኝ
የኔ ቀረርቶ ፥ የኔማ ዛቻ
መቁረጥ አያውቅም
፥ መገዝገዝ ብቻ፡፡
የኔም ስንብት ፥ የመለየቴ ጫፍ
ቢቆይ እስከ ምሽት ፥ ቢርቅ እስከ ደጃፍ!
"ቻው" ስልሽ ሰምቶ
ከጭፍሮቹ ጋር ፥ መንገዴን ዘግቶ
ናፍቆትሽ በሌት ፥ ይጠብቀኛል ፥
"አይኗስ?" ፥ ይለኛል
"ሳቋስ?" ፥ ይለኛል
"ጥርሷስ?" ፥ ይለኛል
የማልችለውን ይጠይቀኛል፡፡
እስኪ ንገሪኝ …
ስንቴ 'ቻው' ብልሽ ፥ ይቆርጥልኛል?
By Habtamu Hadera
@getem
@getem
@paappii | 8 887 |
| 14 | ......
ቀንም ለኛ ሲፈርድ
ነገር ሲደላደል
ክፋት ደግ ይሆናል
ልክነት ነው በደል፤
አሻጋሪን ጊዜ ምኞት ቢያስጠብቀን
ያለ ፈራጁ ግን ብዙ ነው ሚርቀን
ብንፈጥን አንደርስም ብንዘገይም እዛው
አምላኩን ለማያውቅ እድል ነው ሚገዛው፤
'ስማኝ ጃል!'
ጊዜን መጠበቁ ያለ ዳኛ አይሆንም
'ራሱም ባበጀው' ፈጣሪ አይኮነንም!!!
ጊዜን ሳይሆን እግዜርን ነው መጠበቅ!
ያቡ✍️ @Weyblann
@getem
@getem
@getem | 10 810 |
| 15 | የዘውትር ፀሎት
አቤቱ...
በሰው ጉልበቴ የምችላት ሴት
አይኗ ሁሉንም የማያሳስት
ልቧ በተንኮል ያልተነካካ
እራሷን ከሰው ሳታለካካ
በቁመቴ ልክ በጎጆው መጠን
የማይቸግራት እግሯን መመጠን
ለኔና ቤቴ እሷኑ ስጠን
አቤቱ...
ምጥ ላስተምርሽ የማልላትን
ዋጋዋ ቀልሎ የማልደፍራትን
ጠንካራ ጊደር ቀንዷ ማይከብዳት
ቅናት መንገዷን የማይጋርዳት
አቅጣጫ ብስት ሳትስት አብራኝ
እንዳልቀላውጥ ድምጿ ሚገራኝ
እሷን ጀባበል ወደሷ ምራኝ
አቤቱ...
የዘመን ግርዶሽ አይኗን ያልያዘው
እልኳን ፍቅር ያደበዘዘው
የሰው ምርቃት የሰው በረካ
አንተው አድለኝ አንተው በል እንካ
ላልበላው ነገር ሁሉን አልንካ
By Tadios Alemayehu
@getem
@getem
@paappii | 10 778 |
| 16 | @topazionnn
@getem
@getem | 9 670 |
| 17 | ( ሞክሼ ... )
========
ያ ሁሉ እግዚኦ
ያ ሁሉ ቢስሚላ
ያ ሁሉ ጾም ጸሎት
ያ ሁሉ ምህላ ...
የት ነው የሚሄደው
ስሚኝ እስቲ ሀገሬ
ሞክሼ አለሽ ወይ ሌላ ??
By Kiyorna
@getem
@getem
@paappii | 9 820 |
| 18 | ችዬ እንዳይመስልህ!
ደክርቼ ሳለሁ ዐለት የመሰልኩ፣
በሃያላን ፊት ደክሜ ያልሰለልኩ፣
ወና ብሆንም ከሌለኝ ያጣው፣
እንደ ምንዱባን ደጅ የማልጠናው ፣
ችዬ እንዳይመስልህ አስችሎኝ ነው።
...አስችሎን አይደል?!...
by[ዓለም] @alem3_b
@getem
@getem
@getem | 9 387 |
| 19 | #ዕጣ_ፋንታ
አላውቃትም እና
የመኖርን ትርጉም ህይወትን አየኋት
ተጣልተን ተዋደን...ሳፈቅራት አጣኋት
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem | 10 341 |
| 20 | 没有文字... | 9 839 |
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
