ግጥም ብቻ 📘
✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን። ✔ @getem @serenity13 ✔ @wegoch @Words19 ✔ @seiloch ✔ @zefenbicha @leul_mekonnen1
Ko'proq ko'rsatish📈 Telegram kanali ግጥም ብቻ 📘 analitikasi
ግጥም ብቻ 📘 (@getem) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 63 210 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 777-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 520-o'rinni egallagan.
📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika
невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 63 210 obunachiga ega bo‘ldi.
29 Avgust, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -317 ga, so‘nggi 24 soatda esa 4 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.
- Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
- Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 13.51% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 4.27% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
- Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 8 541 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 700 ta ko‘rish yig‘iladi.
- Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 56 ta reaksiya keladi.
📝 Tavsif va kontent siyosati
Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።
✔ @getem @serenity13
✔ @wegoch @Words19
✔ @seiloch
✔ @zefenbicha
@leul_mekonnen1”
Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 30 Avgust, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.
Ma'lumot yuklanmoqda...
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 30 Avgust | 0 | |||
| 29 Avgust | +13 | |||
| 28 Avgust | +2 | |||
| 27 Avgust | +2 | |||
| 26 Avgust | 0 | |||
| 25 Avgust | 0 | |||
| 24 Avgust | +4 | |||
| 23 Avgust | +6 | |||
| 22 Avgust | +5 | |||
| 21 Avgust | +1 | |||
| 20 Avgust | +1 | |||
| 19 Avgust | 0 | |||
| 18 Avgust | 0 | |||
| 17 Avgust | 0 | |||
| 16 Avgust | +19 | |||
| 15 Avgust | 0 | |||
| 14 Avgust | 0 | |||
| 13 Avgust | 0 | |||
| 12 Avgust | +11 | |||
| 11 Avgust | +22 | |||
| 10 Avgust | +2 | |||
| 09 Avgust | 0 | |||
| 08 Avgust | +2 | |||
| 07 Avgust | +2 | |||
| 06 Avgust | +3 | |||
| 05 Avgust | +8 | |||
| 04 Avgust | 0 | |||
| 03 Avgust | +2 | |||
| 02 Avgust | 0 | |||
| 01 Avgust | 0 |
| 2 | ๘
ቃና አልባ ህይወቴ
የፈሰሰ ሀሞቴ
ጣዕም ፣
መልኩ ጠፍቶ ፡ የጠቆረ ወተቴ
ያ ‛መት ሙት አመቴ 𓏸 𓏸 𓏸
ተሰርዮልኛል ! !
....ተሰርዞልኛል...
እናትነት ፍቅርሽ ፡ ያለፍኩትን አይቶ
፤ አዝኖ ራርቶልኛል
ከአዘቅት እመቃት ፡ከባርያነት ግዞት
ለይቶ አንስቶኛል ⨳
ఎ
ማህፀንሽ ሳለሁ ኪዳን ገብተሽልኝ
ያንቺን መልከ ስጋ ˔ ከእግዜር ገዝተሽልኝ
. . . አገልግለሽኛል
ተርበሽ ተጠምተሽ አሳድገሽኛል ꨄ
𓏲 አፈር ግፈሽ ቅመሽ
ርኩስ ፍጡር ወንድን በስራሽ አስንቀሽ
‟ቅድሚያ ላንተ” ብለሽ
ከሰው እኩል አርገሽ
አሁን ያለሁትን ፣
ነገ ምሆነውን . . . ሰውነቴን ሰራሽ !
{ አበጀሽ ! አበጀሽ ! }
𓏲 እናት ሴት እናቴ
ኅቡዕ ቃለ~ጥበብ ˔ የፀሎት ቅናቴ
ከፈራረስኩበት ፣
ከወለገድኩበት ፣
ደርሰሽ አንከብክበሽ ፥ በፍቅርሽ መቅናቴ ⨳
𖥔
[ ምን ትባል ፅዕዱቴ ?
. . . በምን ስም ትጠራ
ምድራዊ የሆነች የሰማያት ጣራ ]
𓏲 ስላንቺ ማንሳቱን ˔ ላልፈፅም ሰደርኩት
ላላከትም ካደምኩት
ቢሆንም
ቢሆንም እንኳንም ጀመርኩት...
< ግዴም ሆኖ ቢገኝ አበጀሁ >
እሺ by ሰምረ የሽዋስ
@getem
@getem
@getem | 1 518 |
| 3 | ታግሼ እንዳላልፈው ፥
ክህደት ስላጠቃኝ
አበባ እሰጥ ብዬ ፥
እሾህ ስለወጋኝ
ሁሉንም ለመተው ፥
ትንሽ ነው ሚበቃኝ
By ሲራክ ወንድሙ
@getem
@getem
@paappii | 3 194 |
| 4 | 🔔 ውድ የቻናላችን አባላት፣ አዲስ የምስራች አለን!
የተመረጡ ግጥሞችን እና ሀሳቦችን, ወጎችን የምናጋራበትን ጉዞአችንን የበለጠ ለማሳደግ እና ጽሁፎቻችንን ባማረ ሁኔታ ለማቅረብ አዲስ Substack ገጽ ከፍተናል!
📌 ግጥሞች ለማንበብ እና አዳዲስ ጽሁፎቻችን በኢሜይል እንዲደርሷችሁ ከታች ያለውን ሊንክ ተጭነው Substack ገጻችንን Subscribe ያድርጉ፡
https://substack.com/@getembicha
@getem | 5 141 |
| 5 | ትናንትን በዛሬ_!
ያቺ ትናንቴ ሀ--ሁ-- ዬ የነበረች፣
የሆነ ቀን ዛሬ ነበረች።
እንድያው ሳላስብ ዘንግቻት፣
ይሄው ዛሬ አስታወስኳት።
ቁጭ ብዬ በዛሬ ፊት ስታዘባት፣
የኳተነች ጎስቋላ ፊት የነበራት፣
በደስታ እና በፈተና የረሳዃት፣
ይሄው አሁን በዛሬ ፊት አነሳዃት።
ከፊቴ ፊት ቁጭ ብላ ስትስቅብኝ፣
ስጠብቃት ብን ብላ እንዳጠፋኝ።
ባትሆን ኖሮ የኔ ትናንት፣
ይችን ዛሬ-- አሁን ባልል ታምኜባት።
መምህሬ የኔ ትናንት፣
መቆሚያዬ የዛሬ እናት፣
የጉዞዬ እርሾ የነገዬ ርስት፣
የጉልበቴ ሰደፍ የዘመኔ ሽበት።
በ መ/ር ሰይድ: ነሐሴ 6, 2018
@getem
@getem
@getem | 5 133 |
| 6 | ውደቅ እስቲ ላንዴ
እንደ ጥልያን ጦር፣
ገላህ ይሸለታል
በጦር በጎራዴ።
፡
አንተ ባለ ክብር !
ላንዴ እስቲ አቀርቅር
መታሸት ያወዛው …
ጀርባህ ይነረታል ፣
በዱላ ና በትር።
:
ተገልጠህ ብታየው
ትከ’ሻህ ተከፍቶ
አናትህ አይተርፍም
በኮናኝ ተሞልቶ።
.
ፅጌረዳ የሰጠህ
በዘመንህ ወራት
እሾሁን ያስቀራል
ቅጠሏን አራግፏት።
:
ከፊት ስትቀርብ አይደል?
(እንደ ለቅሶ ንፍሮ)
ተዘግነህ ‘ምታልቀው
ልኬትህ ተሽሮ ?
:
ተሞልቷል ከተማው
በድንጋይ ፣ በምሳር
ዘንበል ያልህ ጊዜ
ተቋጥሮ ያመሻል
የፈካልህ ግንባር ።
:
ብቻ!
ወንዝ እንደወረደች
የገጠር ኮረዳ ፣
ላስቲክ ጫማዋ ስር
አዳልጧት በነበር
ረጢብ እንግጫ ፣
-
ሚዛን ስተህ ውደቅ
በቋጥኝ ፣ በጭንጫ ፤
፡
ያጨበጨቡ እጆች
ጉያህ ይሰርጋሉ፣
ደግሞ ለቁንጥጫ ።
(ሚካኤል አ)
@getem
@getem
@paappii | 6 253 |
| 7 | ተኳረፍኩኝ ካገሬ ጋር
ተሳቅቄ ሆኜ ከዳር
ጀርባየን አላምነውም
ጠላቴንም አላውቀውም
ማውቀውንም አላውቀውም
ባውቀውም አልንቀውም
መተንፈሻ አጣ አገሩ
ኩፍ በዛ በየዳሩ
ሰቀቀን በርዞታል
አይጥምም አየሩ
ዘር በዛ ባገሩ
አዲስ ጠፋች በአበባ
ሚሰቴ አሏት ባለቤቴን
ቀለበቴን አይቶ አገባ
አገሯ ዳር ናት
ሰውም ወድቋል ጥጉጥጉ
ሬሳው ሳይነሳ
ዘሩን ዘሩን እየፈለጉ
አዲስ አመት ባክህ ና
አታብቅል አበባ
ኢትዬጵያን ሚሏት ሀገር
ባይሆን ይዘህ ግባ
.
.
ግዕዝ ሙላት
@geez_mulat
@getem
@getem
@getem | 6 265 |
| 8 | °.
ልቤን አታናጋው ፣
እንደቆየ ተስፋ
ሳልፈልግህ መጥተህ ፣
ስወድህ አትጥፋ።
By መክሊት
@getem
@getem
@paappii | 6 271 |
| 9 | በቃኝ
-----------------------
እሳት ሆኘ ስነድ፥
አንች ቆፈን ወርሶሽ
ሎሚ ብወረውር፥
እንቧይ ሆኖ ደርሶሽ
ዝምድና ሳያንሰን፥
እየቆየሽ ባዳ መላመድ
ሳይጎድለን፥ እያደርሽ እንግዳ፤
እንግዲህ ደህና ሁኝ!
ምኞቴም በረደ፥ ቁጣየም አለፈ
ከእድሉ ጋር ታግሎ፥ ማነው-ያሸነፈ።
By Bewuketu Siyum
@getem
@getem
@paappii | 8 641 |
| 10 | //<ውሸታም> መባል..አሁን ስድብ ነው?//
@mypoems396
@getem
@getem
@getem | 8 929 |
| 11 | ጊዜው በረረ አይድል
የሮቤል አልበምን
በቅጡ ሳንሰማ
ያን ሌት ያደርነውን
ሰፈር ሳንታማ
አመቱ ሄደ አድል
ክንፍ አበጀ አይድል
ዝም ብሎ ይበራል
አሞራ የሌለው
የዚህ ትውልድ እድል
ነይ እንሂድን ዜማ
ሌሊት ስንሳሳም
በቅጡ ሳንሰማ..
ፍፁም ሳንረጋ
ጊዜው ሄደ አይድል
ሄደን ተመለስን
ሳንመለስ ከጥል
ወድቀን ከራስ ትግል
ደግሞ ሳንዋጋ
ከፍለን የደም ዋጋ
አልጋው ፀጥ ያለበት ትግላችን
በቃ ሳንረጋ
ጊዜ በረረ አድል
ፈርቶ ዝምታችን ..
ነይ እንሂድ
ነይ አንሂድ
ሄደን ለማይቆም ጊዜ
እግራችን አይልፋ
እንኳን የሰማነው
የተሳሳምነው
ከአልጋችን እየጠፋ
አንሂድ አንሂድ
አይሰክንም አየሩ
ብዙ ነው አገሩ
ልታይ ልታይ ይላል
መስታዎት ለእውሩ
ጊዜው በረረ አድል
በእኒያ ሌሊት ከፈን
በሮቤል ዘፈን
በሀይል ተቃቅፈን
የተሻሸንበት..
የተሟሸንበት
ምናለ እንኳ
ሙዚቃ እስኪያበቃ
እግዜሩ ዘመኑን
ክንፍ ቢነሳበት
መናፈቄ እንኳ
አለመናፈቄ እንኳ
ማወላወሌ እንኳ
ሳልወስን ሳላውቀው
በረረብኝ አይድል
ትዝታ ሲነፍገኝ
የዚህ ትውልድ እድል
እንጃ ተነጫነጭኩ
ናፍቀሽኝስ አይድል??
.
.
Based on idea
ሮቤል ሚደቅሳ (ነይ እንሂድ Music )
ግዕዝ ሙላት
@geez_mulat
@getem
@getem
@getem | 9 473 |
| 12 | የተፈጥሮ ልዕልት
ልብን ካስደሰተች ቆንጆ ሴት በሳቋ
ሀሴት ትርቃለች ቀጥ ሲል ማፍቀሯ
የጨከነች ለት መሸሽ ስታበዛ
ሀዘን ይመለሳል ስትቀር ቀዝቅዛ
ፀሃይቱም ብትሆን የጠዋቷ ብስራት
የንጋቷ ኮከብ የአስራ ሁለት ሰዓት
ዓለምን ብትከብ ፀዳሏን አርብባ
ከቀን መብራት ጋር እሷም ተደርባ
እንደለመደባት ባትወጣም ጨክና
ፅልመት አትፈጥርም አይደለችም ዋና
ፋኖስም ተተኪ አምፖል ተሰባሪ
አልቃሻውም ሻማ ሲለኩሱት ቀሪ
ያቺ ጨረቃ ግን ተስፋ ግራ ሲዘም
ሞት ጥላ ሲያጠላ ስትጠበብ ዓለም
ልቦና ሲሰለብ ሰዎች ሲያንቀላፉ
መናፍስተ እርኩሳን ሲያንሰፈስፉ
ምድር ስታረምም ሸፍኗት ጨለማ
ተፈጥሮ ሲነጥቃት የድምቀቷን ግርማ
የብርሃን ልዕልት አለቃ ምስለኔ
የእስትንፋስ ያህል ጨረቃ ናት ለኔ !
ዳዊት ጥዑማይ
17/11/18
ዳ ሰኒያ ዓዲ _አሕፈሮም
@getem
@getem
@getem | 7 322 |
| 13 | በር እና ስንቀር
--------------------------------
የፍላጎት ቤቱ፤ የምኞት ማደሪያው
እያደር ሲለጠጥ' ግድግዳና ጣሪያው
ኗሪው ገላው ሰፋ፤ ጎጆውም ገዘፈ
ለበር የታሰበው፤ ሽንቁር ኾኖ ዐረፈ።
By bewuketu siyum
@getem
@getem
@paappii | 7 816 |
| 14 | አንተና እኔ
የአሁን እድሜ ላይ ኗሪዎች
ዛሬን አጥተን አሁን ነጥተን ለነገ አሳ አስጋሪዎች
በደጉ ቀን ሳሉ
ለክፉ ቀን ብሎ ስንቅን መለቃቀም
ፍቅርን መጠርቀም።
ደሞ……….
ተፈቃቅረን
ተፈላልገን
ተብሰልስለን
………ደሞ ተፈራርተን
ምናባቱን ፍርሀት ከሞት መቼ ይበልጣል
አሁን ላይ ተዋዶ አሁን እንደሚ’ኖር
እራሱስ መች ያዉቃል
እዚሁ ላይ ተፋቅረን
…………. አሁን እንደሚሞት
ለነገ ሳናስቀር
……………ትእቢታችን ሰብረን
ና እንታረቅና
ነገ በኛ ይቅና
@getem
@Tizita21 | 8 173 |
| 15 | #አምላኬ_ሆይ
.
.
.
ለጎረምሳ ገላ፣
ከቆንጆ ሴት ሌላ።
ላንበሳ ምንጋጋ ፣
የድኩላ ስጋ ።
ለልባም እመቤት፣
የጣልያን ድርብ ድስት።
ላራሽ ለገበሬ፣
ሁለት ጥንድ በሬ ።
የምትሰጥ ፈጣሪ፣
የህዝበ አዳም መሪ።
ለጠገበ ማጣት፣
ለሰነፍ ሰው ቅጣት።
ለተዋጊ ጦሩን፣
ለሚወጣ በሩን።
ለሂያጅ ሰፊ መንገድ፣
ለሚጠይቅ ዘመድ።
ላዘነ ሰው መርሻ፣
ለተራበው ጉርሻ፣
ለጠማው ማርከሻ፣
የምትሆን መጠጊያ፣
የምትችል ትከሻ።
ላም ለገዛ በረት፣
ለበደለ ምህረት፣
ላገባ በረከት።
ለእስራኤል መና፣
ለዝናብ ደመና።
ለጌቶ ብርንዶ፣
ለእንቦሳ ሰርዶ።
ለጴጥሮስ መረብ፣
ለላሜህ ልጅ መርከብ።
ለዳዊት መንግስቱን፣
ለእዮብ ትዕግስቱን።
የቸርካቸው አባት፣
የሌለህ ደም ግባት።
ጎዶሎን የምትሞላ፣
ጥብቁን የምታላላ።
እደጅህ ካረፈው፣
ሞልቶ ከተረፈው።
ለኔም ሰው አታጣም፣
ይልቅ ስጠኝና፤
ላመስግንህ በጣም 🙏🙏🙏
✍️ ዓቢይ ( @abiye12 )
@getem
@getem
@getem | 8 036 |
| 16 | የመፅሐፉ ርዕስ :- የርሷ ስም
ገጣሚው / ፀሐፊው :- ዳዊት ጥዑማይ
በገበያ ላይ ውሏል
መፅሐፋን ማግኘት ለምትሹ
አዲስ አበባ ለምትገኙ
👉 + 2519 47 15 39 95
ወይንም
👉 +2519 45 52 52 49
ሐዋሳ ለምትገኙ
....... +251949002056
👉 +2519 47 15 39 95
ወይንም
👉 + 2519 49 00 20 56
@faberfortunae
በመደወል ማዘዝ ትችላላችሁ ።
( መልካም ንባብ ) | 9 585 |
| 17 | ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
እኔ ያንቺን ውበት በቋሚነት ማደንቅ፣
ብዙ ሰው አየሁኝ እውነትን ሲደብቅ፡፡
እኔስ አያስችለኝ፧
መኳል ነው ማስሸብረቅ ባለቀው ማማርሽ፣
አይቶ ዝም ሲል ግን ስንቱን ታዘብኩልሽ?!
ይቺ ጠባብ ቤቱ ትዕቢቱ ከልክላው
እንጂ የማይስልሽ፧
ዝምታ ሲያበዛ መልስ ያጣ እንዳይመስልሽ፨
//ክብሬን ክሬን ሲል ነው የማያወድስሽ//
(ወትሮም በዚ አገር
አብሰልሳይ ይቀድማል፧
ከሚያቆላጵስሽ!)
@mypoems396
@getem
@getem
@getem | 9 188 |
| 18 | ረሳኋት
(ሚካኤል አ)
ጤዛ እኮ ነው ገጽዋ
በማለዳ ረጥቦ ፣ ቀትር የሚሰዋ።
ጉም ነው የሷ መውደድ
ጋርዳዋለች ሲሉ ፣ እኔ አለው ስራመድ።
ጣሟን ዘነጋሁት ፣ እንደ በዓል ዶሮ
ዛሬ እንኳ ብቀምሳት ፣ እኩል ነች ከሽሮ።
ጠረኗ ጠፍቶኛል ፣
አዲስ ነኝ ለራሴ
እሰይ ከስማ ቀረች ፣
ያቺ የሰው ከሴ !
ጆሮዬን አልሰጥም
ስሟን እየጠሩ ፣ ተቀምጠው ጎኔ
እዛው ጨፈርኩበት ፣ በአምና ድንኳኔ።
፡
እያየኋት ከሳች
፡
እያየኋት ጠፋች
፡
እንደ አየር ጢያራ፣
ደመናማው ሰማይ
ይብላኝ ለሷ ፣ ጠራ።
:
እያልኩኝ ደንፍቼ
ላገኘሁት ሁሉ ፣ ጉራዬን ስነፋ
“ረሳኋት “ በሚል
አንድ ከንቱ ግጥም ፣ ብቅ አለች ተጽፋ።
ኡፋ 🥹
@getem
@getem
@paappii | 9 287 |
| 19 | የምጓጓለትን ባውቅስ
እንዴት ልሻው?
መውደቅ ሆኖ ቀርቷል፤
ምኞት መጨረሻው።
By Red-8
@getem
@getem
@paappii | 9 480 |
| 20 | ያላሉትን ነገር አዳምጥ
የማይሉትን ነገር ስማ.
ተብዬ ነው ያደኩት ፤
.
ዕንባሽ እርግማን ሲመራ
.እንዴት ነው ያላወኩት ?
.
አየሽ
ሳትከብጂበትም በፊት
እንዲሁ ሰው ፤ ' ሰው መሆኑ' አድክሞታል
መንቃት ነውር ሆኖበታል ።
አየሽ
ሰሞኑን በባሰው
የሚኮረሸም ጨለማ
.
የሚያጨራምት ዝምታ ውስጤን ወሮታል
.
አየሽ
ዕንባሽ ድንቃር ሆኖ ፤
ውስጤ
እረፍት ነውር ሆኖበታል ።
(አንዱ ጌታቸው)
@getem
@getem | 9 130 |
