ግጥም ብቻ 📘
✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን። ✔ @getem @serenity13 ✔ @wegoch @Words19 ✔ @seiloch ✔ @zefenbicha @leul_mekonnen1
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel ግጥም ብቻ 📘
Channel ግጥም ብቻ 📘 (@getem) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 63 188 subscribers, ranking 782 in the Religion & Spirituality category and 525 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 63 188 subscribers.
According to the latest data from 01 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -264 over the last 30 days and by -3 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 13.77%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 4.36% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 8 699 views. Within the first day, a publication typically gains 2 758 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 61.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።
✔ @getem @serenity13
✔ @wegoch @Words19
✔ @seiloch
✔ @zefenbicha
@leul_mekonnen1”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 02 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 02 September | 0 | |||
| 01 September | +7 |
| 2 | @mypoems396
@getem
@getem
@getem | 3 570 |
| 3 | «ናፈቅሽኝ አቦ !» ብዬ የፃፍኩት
ኩራት ሲሰማኝ - ቀድጄ ጣልኩት ።
«ናፈቅከኝ በጣም» ብለሽ የፃፍሽው
ልምምጥ መስሎሽ
ወርውረሽ ጣልሽው ።
የፍቅር ብርሃን እንዳልተሰማን
ቅር እንዳላለን እንዳልናፈቅን
በአዲስ ወረቀት - ፀብ ተላላክን ።
እንበልና ...
እኒያ ወረቀቶች ...
ቀደን የጣልናቸው
የክረምት ጎርፍ አገናኛቸው ።
እስኪ አስቢያቸው ...
ደራሽ ተሳፍረው
ሆነው ጎን ለጎን
እርስ በርሳቸው ተያይተው ቢሆን ?
ምን ይሉ ይሆን ?
By Habtamu Hadera
@getem
@getem
@paappii | 4 698 |
| 4 | ๘
ቃና አልባ ህይወቴ
የፈሰሰ ሀሞቴ
ጣዕም ፣
መልኩ ጠፍቶ ፡ የጠቆረ ወተቴ
ያ ‛መት ሙት አመቴ 𓏸 𓏸 𓏸
ተሰርዮልኛል ! !
....ተሰርዞልኛል...
እናትነት ፍቅርሽ ፡ ያለፍኩትን አይቶ
፤ አዝኖ ራርቶልኛል
ከአዘቅት እመቃት ፡ከባርያነት ግዞት
ለይቶ አንስቶኛል ⨳
ఎ
ማህፀንሽ ሳለሁ ኪዳን ገብተሽልኝ
ያንቺን መልከ ስጋ ˔ ከእግዜር ገዝተሽልኝ
. . . አገልግለሽኛል
ተርበሽ ተጠምተሽ አሳድገሽኛል ꨄ
𓏲 አፈር ግፈሽ ቅመሽ
ርኩስ ፍጡር ወንድን በስራሽ አስንቀሽ
‟ቅድሚያ ላንተ” ብለሽ
ከሰው እኩል አርገሽ
አሁን ያለሁትን ፣
ነገ ምሆነውን . . . ሰውነቴን ሰራሽ !
{ አበጀሽ ! አበጀሽ ! }
𓏲 እናት ሴት እናቴ
ኅቡዕ ቃለ~ጥበብ ˔ የፀሎት ቅናቴ
ከፈራረስኩበት ፣
ከወለገድኩበት ፣
ደርሰሽ አንከብክበሽ ፥ በፍቅርሽ መቅናቴ ⨳
𖥔
[ ምን ትባል ፅዕዱቴ ?
. . . በምን ስም ትጠራ
ምድራዊ የሆነች የሰማያት ጣራ ]
𓏲 ስላንቺ ማንሳቱን ˔ ላልፈፅም ሰደርኩት
ላላከትም ካደምኩት
ቢሆንም
ቢሆንም እንኳንም ጀመርኩት...
< ግዴም ሆኖ ቢገኝ አበጀሁ >
እሺ by ሰምረ የሽዋስ
@getem
@getem
@getem | 4 363 |
| 5 | ታግሼ እንዳላልፈው ፥
ክህደት ስላጠቃኝ
አበባ እሰጥ ብዬ ፥
እሾህ ስለወጋኝ
ሁሉንም ለመተው ፥
ትንሽ ነው ሚበቃኝ
By ሲራክ ወንድሙ
@getem
@getem
@paappii | 5 719 |
| 6 | 🔔 ውድ የቻናላችን አባላት፣ አዲስ የምስራች አለን!
የተመረጡ ግጥሞችን እና ሀሳቦችን, ወጎችን የምናጋራበትን ጉዞአችንን የበለጠ ለማሳደግ እና ጽሁፎቻችንን ባማረ ሁኔታ ለማቅረብ አዲስ Substack ገጽ ከፍተናል!
📌 ግጥሞች ለማንበብ እና አዳዲስ ጽሁፎቻችን በኢሜይል እንዲደርሷችሁ ከታች ያለውን ሊንክ ተጭነው Substack ገጻችንን Subscribe ያድርጉ፡
https://substack.com/@getembicha
@getem | 7 241 |
| 7 | ትናንትን በዛሬ_!
ያቺ ትናንቴ ሀ--ሁ-- ዬ የነበረች፣
የሆነ ቀን ዛሬ ነበረች።
እንድያው ሳላስብ ዘንግቻት፣
ይሄው ዛሬ አስታወስኳት።
ቁጭ ብዬ በዛሬ ፊት ስታዘባት፣
የኳተነች ጎስቋላ ፊት የነበራት፣
በደስታ እና በፈተና የረሳዃት፣
ይሄው አሁን በዛሬ ፊት አነሳዃት።
ከፊቴ ፊት ቁጭ ብላ ስትስቅብኝ፣
ስጠብቃት ብን ብላ እንዳጠፋኝ።
ባትሆን ኖሮ የኔ ትናንት፣
ይችን ዛሬ-- አሁን ባልል ታምኜባት።
መምህሬ የኔ ትናንት፣
መቆሚያዬ የዛሬ እናት፣
የጉዞዬ እርሾ የነገዬ ርስት፣
የጉልበቴ ሰደፍ የዘመኔ ሽበት።
በ መ/ር ሰይድ: ነሐሴ 6, 2018
@getem
@getem
@getem | 6 765 |
| 8 | ውደቅ እስቲ ላንዴ
እንደ ጥልያን ጦር፣
ገላህ ይሸለታል
በጦር በጎራዴ።
፡
አንተ ባለ ክብር !
ላንዴ እስቲ አቀርቅር
መታሸት ያወዛው …
ጀርባህ ይነረታል ፣
በዱላ ና በትር።
:
ተገልጠህ ብታየው
ትከ’ሻህ ተከፍቶ
አናትህ አይተርፍም
በኮናኝ ተሞልቶ።
.
ፅጌረዳ የሰጠህ
በዘመንህ ወራት
እሾሁን ያስቀራል
ቅጠሏን አራግፏት።
:
ከፊት ስትቀርብ አይደል?
(እንደ ለቅሶ ንፍሮ)
ተዘግነህ ‘ምታልቀው
ልኬትህ ተሽሮ ?
:
ተሞልቷል ከተማው
በድንጋይ ፣ በምሳር
ዘንበል ያልህ ጊዜ
ተቋጥሮ ያመሻል
የፈካልህ ግንባር ።
:
ብቻ!
ወንዝ እንደወረደች
የገጠር ኮረዳ ፣
ላስቲክ ጫማዋ ስር
አዳልጧት በነበር
ረጢብ እንግጫ ፣
-
ሚዛን ስተህ ውደቅ
በቋጥኝ ፣ በጭንጫ ፤
፡
ያጨበጨቡ እጆች
ጉያህ ይሰርጋሉ፣
ደግሞ ለቁንጥጫ ።
(ሚካኤል አ)
@getem
@getem
@paappii | 8 210 |
| 9 | ተኳረፍኩኝ ካገሬ ጋር
ተሳቅቄ ሆኜ ከዳር
ጀርባየን አላምነውም
ጠላቴንም አላውቀውም
ማውቀውንም አላውቀውም
ባውቀውም አልንቀውም
መተንፈሻ አጣ አገሩ
ኩፍ በዛ በየዳሩ
ሰቀቀን በርዞታል
አይጥምም አየሩ
ዘር በዛ ባገሩ
አዲስ ጠፋች በአበባ
ሚሰቴ አሏት ባለቤቴን
ቀለበቴን አይቶ አገባ
አገሯ ዳር ናት
ሰውም ወድቋል ጥጉጥጉ
ሬሳው ሳይነሳ
ዘሩን ዘሩን እየፈለጉ
አዲስ አመት ባክህ ና
አታብቅል አበባ
ኢትዬጵያን ሚሏት ሀገር
ባይሆን ይዘህ ግባ
.
.
ግዕዝ ሙላት
@geez_mulat
@getem
@getem
@getem | 7 654 |
| 10 | °.
ልቤን አታናጋው ፣
እንደቆየ ተስፋ
ሳልፈልግህ መጥተህ ፣
ስወድህ አትጥፋ።
By መክሊት
@getem
@getem
@paappii | 7 248 |
| 11 | በቃኝ
-----------------------
እሳት ሆኘ ስነድ፥
አንች ቆፈን ወርሶሽ
ሎሚ ብወረውር፥
እንቧይ ሆኖ ደርሶሽ
ዝምድና ሳያንሰን፥
እየቆየሽ ባዳ መላመድ
ሳይጎድለን፥ እያደርሽ እንግዳ፤
እንግዲህ ደህና ሁኝ!
ምኞቴም በረደ፥ ቁጣየም አለፈ
ከእድሉ ጋር ታግሎ፥ ማነው-ያሸነፈ።
By Bewuketu Siyum
@getem
@getem
@paappii | 9 780 |
| 12 | //<ውሸታም> መባል..አሁን ስድብ ነው?//
@mypoems396
@getem
@getem
@getem | 9 933 |
| 13 | ጊዜው በረረ አይድል
የሮቤል አልበምን
በቅጡ ሳንሰማ
ያን ሌት ያደርነውን
ሰፈር ሳንታማ
አመቱ ሄደ አድል
ክንፍ አበጀ አይድል
ዝም ብሎ ይበራል
አሞራ የሌለው
የዚህ ትውልድ እድል
ነይ እንሂድን ዜማ
ሌሊት ስንሳሳም
በቅጡ ሳንሰማ..
ፍፁም ሳንረጋ
ጊዜው ሄደ አይድል
ሄደን ተመለስን
ሳንመለስ ከጥል
ወድቀን ከራስ ትግል
ደግሞ ሳንዋጋ
ከፍለን የደም ዋጋ
አልጋው ፀጥ ያለበት ትግላችን
በቃ ሳንረጋ
ጊዜ በረረ አድል
ፈርቶ ዝምታችን ..
ነይ እንሂድ
ነይ አንሂድ
ሄደን ለማይቆም ጊዜ
እግራችን አይልፋ
እንኳን የሰማነው
የተሳሳምነው
ከአልጋችን እየጠፋ
አንሂድ አንሂድ
አይሰክንም አየሩ
ብዙ ነው አገሩ
ልታይ ልታይ ይላል
መስታዎት ለእውሩ
ጊዜው በረረ አድል
በእኒያ ሌሊት ከፈን
በሮቤል ዘፈን
በሀይል ተቃቅፈን
የተሻሸንበት..
የተሟሸንበት
ምናለ እንኳ
ሙዚቃ እስኪያበቃ
እግዜሩ ዘመኑን
ክንፍ ቢነሳበት
መናፈቄ እንኳ
አለመናፈቄ እንኳ
ማወላወሌ እንኳ
ሳልወስን ሳላውቀው
በረረብኝ አይድል
ትዝታ ሲነፍገኝ
የዚህ ትውልድ እድል
እንጃ ተነጫነጭኩ
ናፍቀሽኝስ አይድል??
.
.
Based on idea
ሮቤል ሚደቅሳ (ነይ እንሂድ Music )
ግዕዝ ሙላት
@geez_mulat
@getem
@getem
@getem | 10 171 |
| 14 | የተፈጥሮ ልዕልት
ልብን ካስደሰተች ቆንጆ ሴት በሳቋ
ሀሴት ትርቃለች ቀጥ ሲል ማፍቀሯ
የጨከነች ለት መሸሽ ስታበዛ
ሀዘን ይመለሳል ስትቀር ቀዝቅዛ
ፀሃይቱም ብትሆን የጠዋቷ ብስራት
የንጋቷ ኮከብ የአስራ ሁለት ሰዓት
ዓለምን ብትከብ ፀዳሏን አርብባ
ከቀን መብራት ጋር እሷም ተደርባ
እንደለመደባት ባትወጣም ጨክና
ፅልመት አትፈጥርም አይደለችም ዋና
ፋኖስም ተተኪ አምፖል ተሰባሪ
አልቃሻውም ሻማ ሲለኩሱት ቀሪ
ያቺ ጨረቃ ግን ተስፋ ግራ ሲዘም
ሞት ጥላ ሲያጠላ ስትጠበብ ዓለም
ልቦና ሲሰለብ ሰዎች ሲያንቀላፉ
መናፍስተ እርኩሳን ሲያንሰፈስፉ
ምድር ስታረምም ሸፍኗት ጨለማ
ተፈጥሮ ሲነጥቃት የድምቀቷን ግርማ
የብርሃን ልዕልት አለቃ ምስለኔ
የእስትንፋስ ያህል ጨረቃ ናት ለኔ !
ዳዊት ጥዑማይ
17/11/18
ዳ ሰኒያ ዓዲ _አሕፈሮም
@getem
@getem
@getem | 7 956 |
| 15 | በር እና ስንቀር
--------------------------------
የፍላጎት ቤቱ፤ የምኞት ማደሪያው
እያደር ሲለጠጥ' ግድግዳና ጣሪያው
ኗሪው ገላው ሰፋ፤ ጎጆውም ገዘፈ
ለበር የታሰበው፤ ሽንቁር ኾኖ ዐረፈ።
By bewuketu siyum
@getem
@getem
@paappii | 8 059 |
| 16 | አንተና እኔ
የአሁን እድሜ ላይ ኗሪዎች
ዛሬን አጥተን አሁን ነጥተን ለነገ አሳ አስጋሪዎች
በደጉ ቀን ሳሉ
ለክፉ ቀን ብሎ ስንቅን መለቃቀም
ፍቅርን መጠርቀም።
ደሞ……….
ተፈቃቅረን
ተፈላልገን
ተብሰልስለን
………ደሞ ተፈራርተን
ምናባቱን ፍርሀት ከሞት መቼ ይበልጣል
አሁን ላይ ተዋዶ አሁን እንደሚ’ኖር
እራሱስ መች ያዉቃል
እዚሁ ላይ ተፋቅረን
…………. አሁን እንደሚሞት
ለነገ ሳናስቀር
……………ትእቢታችን ሰብረን
ና እንታረቅና
ነገ በኛ ይቅና
@getem
@Tizita21 | 8 579 |
| 17 | #አምላኬ_ሆይ
.
.
.
ለጎረምሳ ገላ፣
ከቆንጆ ሴት ሌላ።
ላንበሳ ምንጋጋ ፣
የድኩላ ስጋ ።
ለልባም እመቤት፣
የጣልያን ድርብ ድስት።
ላራሽ ለገበሬ፣
ሁለት ጥንድ በሬ ።
የምትሰጥ ፈጣሪ፣
የህዝበ አዳም መሪ።
ለጠገበ ማጣት፣
ለሰነፍ ሰው ቅጣት።
ለተዋጊ ጦሩን፣
ለሚወጣ በሩን።
ለሂያጅ ሰፊ መንገድ፣
ለሚጠይቅ ዘመድ።
ላዘነ ሰው መርሻ፣
ለተራበው ጉርሻ፣
ለጠማው ማርከሻ፣
የምትሆን መጠጊያ፣
የምትችል ትከሻ።
ላም ለገዛ በረት፣
ለበደለ ምህረት፣
ላገባ በረከት።
ለእስራኤል መና፣
ለዝናብ ደመና።
ለጌቶ ብርንዶ፣
ለእንቦሳ ሰርዶ።
ለጴጥሮስ መረብ፣
ለላሜህ ልጅ መርከብ።
ለዳዊት መንግስቱን፣
ለእዮብ ትዕግስቱን።
የቸርካቸው አባት፣
የሌለህ ደም ግባት።
ጎዶሎን የምትሞላ፣
ጥብቁን የምታላላ።
እደጅህ ካረፈው፣
ሞልቶ ከተረፈው።
ለኔም ሰው አታጣም፣
ይልቅ ስጠኝና፤
ላመስግንህ በጣም 🙏🙏🙏
✍️ ዓቢይ ( @abiye12 )
@getem
@getem
@getem | 8 410 |
| 18 | የመፅሐፉ ርዕስ :- የርሷ ስም
ገጣሚው / ፀሐፊው :- ዳዊት ጥዑማይ
በገበያ ላይ ውሏል
መፅሐፋን ማግኘት ለምትሹ
አዲስ አበባ ለምትገኙ
👉 + 2519 47 15 39 95
ወይንም
👉 +2519 45 52 52 49
ሐዋሳ ለምትገኙ
....... +251949002056
👉 +2519 47 15 39 95
ወይንም
👉 + 2519 49 00 20 56
@faberfortunae
በመደወል ማዘዝ ትችላላችሁ ።
( መልካም ንባብ ) | 9 585 |
| 19 | ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
እኔ ያንቺን ውበት በቋሚነት ማደንቅ፣
ብዙ ሰው አየሁኝ እውነትን ሲደብቅ፡፡
እኔስ አያስችለኝ፧
መኳል ነው ማስሸብረቅ ባለቀው ማማርሽ፣
አይቶ ዝም ሲል ግን ስንቱን ታዘብኩልሽ?!
ይቺ ጠባብ ቤቱ ትዕቢቱ ከልክላው
እንጂ የማይስልሽ፧
ዝምታ ሲያበዛ መልስ ያጣ እንዳይመስልሽ፨
//ክብሬን ክሬን ሲል ነው የማያወድስሽ//
(ወትሮም በዚ አገር
አብሰልሳይ ይቀድማል፧
ከሚያቆላጵስሽ!)
@mypoems396
@getem
@getem
@getem | 9 188 |
| 20 | ረሳኋት
(ሚካኤል አ)
ጤዛ እኮ ነው ገጽዋ
በማለዳ ረጥቦ ፣ ቀትር የሚሰዋ።
ጉም ነው የሷ መውደድ
ጋርዳዋለች ሲሉ ፣ እኔ አለው ስራመድ።
ጣሟን ዘነጋሁት ፣ እንደ በዓል ዶሮ
ዛሬ እንኳ ብቀምሳት ፣ እኩል ነች ከሽሮ።
ጠረኗ ጠፍቶኛል ፣
አዲስ ነኝ ለራሴ
እሰይ ከስማ ቀረች ፣
ያቺ የሰው ከሴ !
ጆሮዬን አልሰጥም
ስሟን እየጠሩ ፣ ተቀምጠው ጎኔ
እዛው ጨፈርኩበት ፣ በአምና ድንኳኔ።
፡
እያየኋት ከሳች
፡
እያየኋት ጠፋች
፡
እንደ አየር ጢያራ፣
ደመናማው ሰማይ
ይብላኝ ለሷ ፣ ጠራ።
:
እያልኩኝ ደንፍቼ
ላገኘሁት ሁሉ ፣ ጉራዬን ስነፋ
“ረሳኋት “ በሚል
አንድ ከንቱ ግጥም ፣ ብቅ አለች ተጽፋ።
ኡፋ 🥹
@getem
@getem
@paappii | 9 287 |
