fa
Feedback
ግጥም ብቻ 📘

ግጥም ብቻ 📘

رفتن به کانال در Telegram

✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን። ✔ @getem @serenity13@wegoch @Words19@seiloch@zefenbicha @leul_mekonnen1

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ግጥም ብቻ 📘

کانال ግጥም ብቻ 📘 (@getem) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 63 241 مشترک است و جایگاه 783 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 518 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 63 241 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 26 اوت, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -347 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -21 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 13.28% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 4.24% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 8 398 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 684 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 69 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን። ✔ @getem @serenity13 ✔ @wegoch @Words19 ✔ @seiloch ✔ @zefenbicha @leul_mekonnen1

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 27 اوت, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

63 241
مشترکین
-2124 ساعت
-637 روز
-34730 روز
آرشیو پست ها
ትናንትን በዛሬ_! ያቺ ትናንቴ ሀ--ሁ-- ዬ  የነበረች፣ የሆነ ቀን ዛሬ ነበረች።              እንድያው ሳላስብ ዘንግቻት፣              ይሄው ዛሬ አስታወስኳት። ቁጭ ብዬ በዛሬ ፊት ስታዘባት፣ የኳተነች ጎስቋላ ፊት የነበራት፣              በደስታ እና በፈተና የረሳዃት፣               ይሄው አሁን በዛሬ ፊት አነሳዃት። ከፊቴ ፊት ቁጭ ብላ ስትስቅብኝ፣ ስጠብቃት ብን ብላ እንዳጠፋኝ።                ባትሆን ኖሮ የኔ ትናንት፣                 ይችን ዛሬ-- አሁን ባልል ታምኜባት። መምህሬ የኔ ትናንት፣ መቆሚያዬ የዛሬ እናት፣           የጉዞዬ እርሾ የነገዬ ርስት፣           የጉልበቴ ሰደፍ የዘመኔ ሽበት።                                                 በ መ/ር ሰይድ: ነሐሴ 6, 2018 @getem @getem @getem

ውደቅ እስቲ ላንዴ እንደ ጥልያን ጦር፣ ገላህ ይሸለታል በጦር በጎራዴ። ፡ አንተ ባለ ክብር ! ላንዴ እስቲ አቀርቅር መታሸት ያወዛው … ጀርባህ ይነረታል ፣ በዱላ ና በትር። : ተገልጠህ ብታየው         ትከ’ሻህ ተከፍቶ አናትህ አይተርፍም         በኮናኝ ተሞልቶ። . ፅጌረዳ የሰጠህ በዘመንህ ወራት እሾሁን ያስቀራል ቅጠሏን አራግፏት። : ከፊት ስትቀርብ አይደል? (እንደ ለቅሶ ንፍሮ) ተዘግነህ ‘ምታልቀው ልኬትህ ተሽሮ ? : ተሞልቷል ከተማው በድንጋይ ፣ በምሳር ዘንበል ያልህ ጊዜ ተቋጥሮ ያመሻል የፈካልህ ግንባር ። : ብቻ! ወንዝ እንደወረደች የገጠር ኮረዳ ፣ ላስቲክ ጫማዋ ስር አዳልጧት በነበር ረጢብ  እንግጫ ፣ - ሚዛን ስተህ ውደቅ በቋጥኝ ፣ በጭንጫ ፤ ፡ ያጨበጨቡ እጆች ጉያህ ይሰርጋሉ፣ ደግሞ ለቁንጥጫ ። (ሚካኤል አ) @getem @getem @paappii

ተኳረፍኩኝ ካገሬ ጋር ተሳቅቄ ሆኜ ከዳር ጀርባየን አላምነውም ጠላቴንም አላውቀውም ማውቀውንም አላውቀውም ባውቀውም አልንቀውም መተንፈሻ አጣ አገሩ ኩፍ በዛ በየዳሩ ሰቀቀን በርዞታል አይጥምም አየሩ ዘር በዛ ባገሩ አዲስ ጠፋች በአበባ ሚሰቴ አሏት ባለቤቴን ቀለበቴን አይቶ አገባ አገሯ ዳር ናት ሰውም ወድቋል ጥጉጥጉ ሬሳው ሳይነሳ ዘሩን ዘሩን እየፈለጉ አዲስ አመት ባክህ ና አታብቅል አበባ ኢትዬጵያን ሚሏት ሀገር ባይሆን ይዘህ ግባ . . ግዕዝ ሙላት @geez_mulat @getem @getem @getem

°. ልቤን አታናጋው ፣ እንደቆየ ተስፋ ሳልፈልግህ መጥተህ ፣ ስወድህ አትጥፋ። By መክሊት @getem @getem @paappii

በቃኝ ----------------------- እሳት ሆኘ ስነድ፥ አንች ቆፈን ወርሶሽ ሎሚ ብወረውር፥ እንቧይ ሆኖ ደርሶሽ ዝምድና ሳያንሰን፥ እየቆየሽ ባዳ መላመድ ሳይጎድለን፥ እያደርሽ እንግዳ፤ እንግዲህ ደህና ሁኝ! ምኞቴም በረደ፥ ቁጣየም አለፈ ከእድሉ ጋር ታግሎ፥ ማነው-ያሸነፈ። By Bewuketu Siyum @getem @getem @paappii

//<ውሸታም> መባል..አሁን ስድብ ነው?// @mypoems396 @getem @getem @getem
//<ውሸታም> መባል..አሁን ስድብ ነው?// @mypoems396 @getem @getem @getem

ጊዜው በረረ አይድል የሮቤል አልበምን በቅጡ ሳንሰማ ያን ሌት ያደርነውን ሰፈር ሳንታማ አመቱ ሄደ አድል ክንፍ አበጀ አይድል ዝም ብሎ ይበራል አሞራ የሌለው የዚህ ትውልድ እድል ነይ እንሂድን ዜማ ሌሊት ስንሳሳም በቅጡ ሳንሰማ.. ፍፁም ሳንረጋ ጊዜው ሄደ አይድል ሄደን ተመለስን ሳንመለስ ከጥል ወድቀን ከራስ ትግል ደግሞ ሳንዋጋ ከፍለን የደም ዋጋ አልጋው ፀጥ ያለበት ትግላችን በቃ ሳንረጋ ጊዜ በረረ አድል ፈርቶ ዝምታችን .. ነይ እንሂድ ነይ አንሂድ ሄደን ለማይቆም ጊዜ እግራችን አይልፋ እንኳን የሰማነው የተሳሳምነው ከአልጋችን እየጠፋ አንሂድ አንሂድ አይሰክንም አየሩ ብዙ ነው አገሩ ልታይ ልታይ ይላል መስታዎት ለእውሩ ጊዜው በረረ አድል በእኒያ ሌሊት ከፈን በሮቤል ዘፈን በሀይል ተቃቅፈን የተሻሸንበት.. የተሟሸንበት ምናለ እንኳ ሙዚቃ እስኪያበቃ እግዜሩ ዘመኑን ክንፍ ቢነሳበት መናፈቄ እንኳ አለመናፈቄ እንኳ ማወላወሌ እንኳ ሳልወስን ሳላውቀው በረረብኝ አይድል ትዝታ ሲነፍገኝ የዚህ ትውልድ እድል እንጃ ተነጫነጭኩ ናፍቀሽኝስ አይድል?? . . Based on idea ሮቤል ሚደቅሳ (ነይ እንሂድ Music ) ግዕዝ ሙላት @geez_mulat @getem @getem @getem

የተፈጥሮ ልዕልት      ልብን ካስደሰተች ቆንጆ ሴት በሳቋ ሀሴት ትርቃለች ቀጥ ሲል ማፍቀሯ የጨከነች ለት መሸሽ ስታበዛ ሀዘን ይመለሳል ስትቀር ቀዝቅዛ ፀሃይቱም ብትሆን የጠዋቷ ብስራት የንጋቷ ኮከብ የአስራ ሁለት ሰዓት ዓለምን ብትከብ ፀዳሏን አርብባ ከቀን መብራት ጋር እሷም ተደርባ እንደለመደባት ባትወጣም ጨክና ፅልመት አትፈጥርም   አይደለችም ዋና ፋኖስም ተተኪ አምፖል ተሰባሪ አልቃሻውም ሻማ ሲለኩሱት ቀሪ ያቺ ጨረቃ ግን ተስፋ ግራ ሲዘም ሞት ጥላ ሲያጠላ ስትጠበብ ዓለም ልቦና ሲሰለብ ሰዎች ሲያንቀላፉ መናፍስተ እርኩሳን ሲያንሰፈስፉ ምድር ስታረምም ሸፍኗት ጨለማ ተፈጥሮ ሲነጥቃት የድምቀቷን ግርማ የብርሃን ልዕልት አለቃ ምስለኔ የእስትንፋስ ያህል ጨረቃ ናት ለኔ ! ዳዊት ጥዑማይ 17/11/18 ዳ ሰኒያ ዓዲ _አሕፈሮም @getem @getem @getem

በር እና ስንቀር -------------------------------- የፍላጎት ቤቱ፤ የምኞት ማደሪያው እያደር ሲለጠጥ' ግድግዳና ጣሪያው ኗሪው ገላው ሰፋ፤ ጎጆውም ገዘፈ ለበር የታሰበው፤ ሽንቁር ኾኖ ዐረፈ። By bewuketu siyum @getem @getem @paappii

አንተና እኔ
የአሁን እድሜ ላይ ኗሪዎች ዛሬን አጥተን አሁን ነጥተን ለነገ አሳ አስጋሪዎች በደጉ ቀን ሳሉ ለክፉ ቀን ብሎ ስንቅን መለቃቀም ፍቅርን መጠርቀም። ደሞ………. ተፈቃቅረን ተፈላልገን ተብሰልስለን ………ደሞ ተፈራርተን ምናባቱን ፍርሀት ከሞት መቼ ይበልጣል አሁን ላይ ተዋዶ አሁን እንደሚ’ኖር እራሱስ መች ያዉቃል እዚሁ ላይ ተፋቅረን …………. አሁን እንደሚሞት ለነገ ሳናስቀር ……………ትእቢታችን ሰብረን ና እንታረቅና ነገ በኛ  ይቅና @getem @Tizita21

#አምላኬ_ሆይ . . . ለጎረምሳ ገላ፣ ከቆንጆ ሴት ሌላ። ላንበሳ ምንጋጋ ፣ የድኩላ ስጋ ። ለልባም እመቤት፣ የጣልያን ድርብ ድስት። ላራሽ ለገበሬ፣ ሁለት ጥንድ በሬ ። የምትሰጥ ፈጣሪ፣ የህዝበ አዳም መሪ። ለጠገበ ማጣት፣ ለሰነፍ ሰው ቅጣት። ለተዋጊ ጦሩን፣ ለሚወጣ በሩን። ለሂያጅ ሰፊ መንገድ፣ ለሚጠይቅ ዘመድ። ላዘነ ሰው መርሻ፣ ለተራበው ጉርሻ፣ ለጠማው ማርከሻ፣ የምትሆን መጠጊያ፣ የምትችል ትከሻ። ላም ለገዛ በረት፣ ለበደለ ምህረት፣ ላገባ በረከት። ለእስራኤል መና፣ ለዝናብ ደመና። ለጌቶ ብርንዶ፣ ለእንቦሳ ሰርዶ። ለጴጥሮስ መረብ፣ ለላሜህ ልጅ መርከብ። ለዳዊት መንግስቱን፣ ለእዮብ ትዕግስቱን። የቸርካቸው አባት፣ የሌለህ ደም ግባት። ጎዶሎን የምትሞላ፣ ጥብቁን የምታላላ። እደጅህ ካረፈው፣ ሞልቶ ከተረፈው። ለኔም ሰው አታጣም፣ ይልቅ ስጠኝና፤ ላመስግንህ በጣም 🙏🙏🙏 ✍️ ዓቢይ ( @abiye12 ) @getem @getem @getem

የመፅሐፉ ርዕስ :- የርሷ ስም ገጣሚው / ፀሐፊው :- ዳዊት ጥዑማይ በገበያ ላይ ውሏል መፅሐፋን ማግኘት ለምትሹ አዲስ አበባ ለምትገኙ 👉 + 2519 47 15 39 95 ወይንም 👉 +2519 45
የመፅሐፉ ርዕስ :- የርሷ ስም ገጣሚው / ፀሐፊው :- ዳዊት ጥዑማይ በገበያ ላይ ውሏል መፅሐፋን ማግኘት ለምትሹ አዲስ አበባ ለምትገኙ 👉 + 2519 47 15 39 95 ወይንም 👉 +2519 45 52 52 49 ሐዋሳ ለምትገኙ ....... +251949002056 👉 +2519 47 15 39 95 ወይንም 👉 + 2519 49 00 20 56 @faberfortunae በመደወል ማዘዝ ትችላላችሁ ። ( መልካም ንባብ )

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ እኔ ያንቺን ውበት በቋሚነት ማደንቅ፣ ብዙ ሰው አየሁኝ እውነትን ሲደብቅ፡፡ እኔስ አያስችለኝ፧ መኳል ነው ማስሸብረቅ ባለቀው ማማርሽ፣ አይቶ ዝም ሲል ግን ስንቱን ታዘብኩልሽ?! ይቺ ጠባብ ቤቱ ትዕቢቱ ከልክላው እንጂ የማይስልሽ፧ ዝምታ ሲያበዛ መልስ ያጣ እንዳይመስልሽ፨ //ክብሬን ክሬን ሲል ነው የማያወድስሽ// (ወትሮም በዚ አገር           አብሰልሳይ ይቀድማል፧                                     ከሚያቆላጵስሽ!) @mypoems396 @getem @getem @getem

ረሳኋት (ሚካኤል አ) ጤዛ እኮ ነው ገጽዋ በማለዳ ረጥቦ ፣ ቀትር የሚሰዋ። ጉም ነው የሷ መውደድ ጋርዳዋለች ሲሉ ፣ እኔ አለው ስራመድ። ጣሟን ዘነጋሁት ፣ እንደ በዓል ዶሮ ዛሬ እንኳ ብቀምሳት ፣ እኩል ነች ከሽሮ። ጠረኗ ጠፍቶኛል ፣ አዲስ ነኝ ለራሴ እሰይ ከስማ ቀረች ፣ ያቺ የሰው ከሴ ! ጆሮዬን አልሰጥም ስሟን እየጠሩ ፣ ተቀምጠው ጎኔ እዛው ጨፈርኩበት ፣ በአምና ድንኳኔ። ፡ እያየኋት ከሳች ፡ እያየኋት ጠፋች ፡ እንደ አየር ጢያራ፣ ደመናማው ሰማይ ይብላኝ ለሷ ፣ ጠራ። : እያልኩኝ ደንፍቼ ላገኘሁት ሁሉ ፣ ጉራዬን ስነፋ “ረሳኋት “ በሚል አንድ ከንቱ ግጥም ፣ ብቅ አለች ተጽፋ። ኡፋ 🥹 @getem @getem @paappii

የምጓጓለትን ባውቅስ እንዴት ልሻው? መውደቅ ሆኖ ቀርቷል፤ ምኞት መጨረሻው። By Red-8 @getem @getem @paappii

ያላሉትን ነገር አዳምጥ የማይሉትን ነገር ስማ. ተብዬ ነው ያደኩት ፤ . ዕንባሽ እርግማን ሲመራ .እንዴት ነው ያላወኩት ? . አየሽ ሳትከብጂበትም በፊት እንዲሁ ሰው ፤ ' ሰው መሆኑ' አድክሞታል መንቃት ነውር ሆኖበታል ። አየሽ ሰሞኑን በባሰው የሚኮረሸም ጨለማ . የሚያጨራምት ዝምታ ውስጤን ወሮታል . አየሽ ዕንባሽ ድንቃር ሆኖ ፤ ውስጤ እረፍት ነውር ሆኖበታል ። (አንዱ ጌታቸው) @getem @getem

𝙞𝙣𝙨𝙥𝙞𝙧𝙚𝙙 𝙗𝙮 አያሙሌ'𝙨 𝙥𝙤𝙚𝙢 @mypoems396 @getem @getem @getem
𝙞𝙣𝙨𝙥𝙞𝙧𝙚𝙙 𝙗𝙮 አያሙሌ'𝙨 𝙥𝙤𝙚𝙢 @mypoems396 @getem @getem @getem

ነገን ኑረን ፥ ዛሬን ሞትን ትላንትናን እየለፋን ፥ በቀደም 'ለት ተቀበርን መሞቻና መሰንበቻው ፥ ሳይታወቅ የውል ፍቺው ቀን ልንጨብጥ በቀናችን ፥ ቀን አስጣለን መኖራችን። By ፍቅረ-ማርያም ተሾመ @getem @getem @paappii

ትንሣኤሽን ልየዉ ውዳሴሽን አንብቤ ቅዳሴሽን ሰምቼ፣ በዝግ ባዕት በሱባኤ ሰንብቼ። ትንሳኤሽን ልየዉ ከመቅደሱ ቆሜ፣ ከመሳጭ አንድምታ እዉቀትን ቀስሜ። ስብሐተ ነግህ ን አድርሼ፣ ድርሳን ስንክሳሩን ከልሼ። ቅዳሴን ላስቀድስ ከበራፉ ታዛ፣ አለሙን አስትቶ ለነፍስ የሚያስገዛ። ትንሣኤሽን ልየዉ ከመቅደሱ ቆሜ፣ ከመሳጭ አንድምታ እዉቀትን ቀስሜ። እንደ ሐዋርያዉ ትንሣኤሽ ይታየኝ፣ ከነጩ ሰበናት በረከቱ ይድረሰኝ። ዕርገትሽን እንዳይ ፍቀጂ እናቴ፣ በጸሎት በምልጃሽ ይሞላልኝ ቤቴ። እንኳን አደረሳችሁ🙏 ✍ዔደን ታደሰ @topazionnn @getem @getem

ተኳረፉ ብሎ ፡ ሊያስማማ ሊዳኘን ህይወት ስንት መንገድ ፡ ፈጥሮ ሲያገናኘን የልጅ ነገር ብለን፡ ጥሪውን ንቀናል ከእንግዲህ በኋላ... ሽማግሌ ሆኖ፡ ሞት ያስታርቀናል። by red-8 @getem @getem @paappii