FastMereja.com
📈 تحلیل کانال تلگرام FastMereja.com
کانال FastMereja.com (@fastmereja) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 49 545 مشترک است و جایگاه 3 565 را در دسته آموزش و رتبه 643 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 49 545 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 09 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -732 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -18 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 12.82% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.43% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 6 351 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 4 675 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 28 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
توضیحی برای کانال ارائه نشده است.
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 10 ژوئن, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 10 ژوئن | 0 | |||
| 09 ژوئن | 0 | |||
| 08 ژوئن | 0 | |||
| 07 ژوئن | 0 | |||
| 06 ژوئن | 0 | |||
| 05 ژوئن | 0 | |||
| 04 ژوئن | 0 | |||
| 03 ژوئن | 0 | |||
| 02 ژوئن | 0 | |||
| 01 ژوئن | +1 |
| 2 | "እርሻችን አሁንም ስራ ላይ ነው!! በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ሱቆቻችን ሽንኩርት 95-110 በደረጃ እየሸጥን ነው። አየሩን ጨምሮ ብዙ አስቸጋሪ ጊዜ ብናሳልፍም ከዚህም በታች እንዲቀንስ ሰራተኞቻችን እንቅልፍ አጥተው እየሰሩ ነው።" በረከት ገበሬዋ ከአየርላንድ | 2 900 |
| 3 | 🏢 የሰመር ሪል እስቴት ልዩ የቤት ባለቤት የመሆን እድል!
በከተማችን እምብርት ቡልጋሪያ አደባባይ አካባቢ የሚገኙትን እጅግ ዘመናዊ፣ ሰፊ እና ምቹ የመኖሪያ አፓርታማዎችን በፈለጉት የካሬ አማራጭ ለሽያጭ አቅርበናል።
📐 የምርጫዎትን የካሬ እና የመኝታ አማራጮች ይምረጡ፦
🛏️ ባለ 1 መኝታ – 81 ካሬ
🛏️ ባለ 2 መኝታ – 111 እና 134 ካሬ
🛏️ ባለ 3 መኝታ – ከ168 ካሬ ጀምሮ
💰 እጅግ አስገራሚ ዋጋ እና ልዩ የክፍያ አማራጭ፦
💵 ዋጋ፦ በካሬ 89,000 ብር ብቻ!
📉 ቅድመ ክፍያ፦ 10% ብቻ በመክፈል ውል ያሰሩ!
🏦 የባንክ ብድር፦ 50% የባንክ ብድር የተመቻቸለት።
⏳ ጊዜ አይውሰዱ!
ይህ ታላቅ የዋጋ ቅናሽ የሚቆየው ለውስን ጊዜ ብቻ ስለሆነ፣ ቀድመው በመምጣት የዕድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ።
📍 ቦታ፦ ቡልጋሪያ አደባባይ አካባቢ
📞 ለበለጠ መረጃ አሁኑኑ ይደውሉልን፦0912355631
የህልምዎን ቤት ዛሬውኑ በእጅዎ ያስገቡ!
#Summer #AddisAbabaBusiness #apartmentforrentplantation #shopforsale #apartmentforrent #amibaraproperties #realestate #የንግድቦታ #Temerrealestate #teklehaymanotmall | 3 435 |
| 4 | ለ17 ዓመታት ያለ ትክክለኛ ፈቃድ አውሮፕላን ሲያበር የነበረው ኤር ካናዳ ፓይለት በቁጥጥር ስር ዋለ
#FastMereja I የቀድሞ የኤር ካናዳ ፓይለት ትክክለኛ የካፒቴንነት ፈቃድ ሳይኖረው ለ17 ዓመታት ያህል በሺዎች የሚቆጠሩ መንገደኞችን በንግድ በረራዎች ሲያጓጉዝ በመቆየቱ በቁጥጥር ስር መዋሉን የካናዳ ፖሊስ አስታወቀ። ጄፍሪ ዎል የተባለው የ59 ዓመት ፓይለት እ.ኤ.አ ከ2009 ጀምሮ በሀሰተኛ ሰነድ ሲያበር እንደነበር የተደረሰበት ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከማጭበርበር ጋር የተያያዙ ሰባት የወንጀል ክሶች ተመስርተውበታል።
ፖሊስ እንዳለው ተከሳሹ ከ1998 ጀምሮ በድርጅቱ ውስጥ በፓይለትነት ሲሰራ የቆየ ቢሆንም፣ በ2009 ወደ ዋና አብራሪነት (ካፒቴን) ካደገበት ጊዜ ጀምሮ ለቦይንግ አውሮፕላኖች የሚፈለገውን ከፍተኛ የበረራ ፈቃድ ሳይኖረው በሀሰተኛ ሰነድ 900 ያህል የአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ በረራዎችን አድርጓል። ድርጊቱ ባለፈው ዓመት በተደረገ መደበኛ ግምገማ የሰነድ አለመጣጣም በመታየቱ በምርመራ የተደረሰበት ሲሆን፣ ኤር ካናዳ ግለሰቡን ወዲያውኑ ከስራ ማገዱን ገልጿል።
ድርጅቱ በሰጠው መግለጫ ፓይለቱ መደበኛ የንግድ በረራ ፈቃድ የነበረው በመሆኑ የመንገደኞች ደህንነት ለአደጋ ተጋልጦ እንደማያውቅና ሁሉም አብራሪዎች በየስድስት ወሩ የብቃት ማረጋገጫ ስልጠና እንደሚወስዱ አስታውቋል። እንዲሁም በሌሎች አብራሪዎች ላይ በተደረገ ድንገተኛ ኦዲት ምንም አይነት ተመሳሳይ ችግር እንዳልተገኘ ድርጅቱ ጨምሮ ገልጿል። | 3 482 |
| 5 | ሚድሮክ የ80 ሚሊዮን ዶላር ታሪካዊ ስምምነት ተፈራረመ
#FastMereja I ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ እና ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) በኬንያ ናይሮቢ ከተማ የ80 ሚሊዮን አሜሪካን ዶላር የረጅም ጊዜ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱን የሚድሮክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል አሕመድ እና የIFC የአፍሪካ ቀጠና ምክትል ፕሬዚዳንት ኢትዮጲስ ተፈራ የፈረሙት ሲሆን፣ የተገኘው የገንዘብ ድጋፍ በዋናነት ታዋቂውን ሸራተን አዲስ ሌግዠሪ ኮሌክሽን ሆቴልን በዘመናዊ መልኩ ለማደስ እና በሸራተን ደረጃ አዲስ ተጨማሪ ሆቴል ለመገንባት ይውላል።
ይህ ከፍተኛ የፋይናንስ አጋርነት የሀገሪቱን የሆስፒታሊቲ እና ቱሪዝም ዘርፍ ከማዘመን ባለፈ፣ ከ9,400 በላይ ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆኑ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን በተለይም ለወጣቶችና ለሴቶች እንደሚፈጥር ተገልጿል። አቶ ጀማል አሕመድ አጋርነቱ ቀጣይነት ላለው የሀገር ውስጥ ሥራ ዕድል ፈጠራ ያለውን ሚና ሲያጎሉ፣ የIFC ምክትል ፕሬዚዳንት በበኩላቸው ስምምነቱ የሚድሮክን የአገልግሎት ጥራት ለማሳደግ ታስቦ የተደረገ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP32) ለማስተናገድ መመረጧን ተከትሎ ሚድሮክ ግዙፍ የሆቴል ማስፋፊያና የእድሳት ስራዎችን በከፍተኛ ፍጥነት እያከናወነ ይገኛል። ከእነዚህም መካከል በሚሊኒየም አዳራሽ ቅጥር ግቢ የ”Moxy by Marriott”፣ በመሀመድያ የመኖሪያ መንደር የ”Four Points by Sheraton” እና በአፍሪካ ህብረት አጠገብ የ”Westin Addis” ሆቴሎች ግንባታ በስፋት እየተካሄደ ይገኛል።
በተጨማሪም በቅርቡ ግሩፑን የተቀላቀለው ዋቢ ሸበሌ ሆቴል ታሪካዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ ወደ “Autograph Collection by Marriott” ደረጃ የማደስ ስራው የተጀመረ ሲሆን፣ በባህርዳር፣ ጅማ፣ ሃዋሳ እና በላንጋኖ ሳቫና ሪዞርት ተመሳሳይ ዓለም አቀፍ የሆቴል ፕሮጀክቶች በመገንባት ላይ ናቸው። በአሁኑ ወቅት ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በማኑፋክቸሪንግ፣ ግብርና፣ ማዕድን፣ ንግድና ሆስፒታሊቲ ዘርፎች ላይ በመሰማራት ከ80 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩ ይታወቃል። | 3 884 |
| 6 | የትግራይ ወጣቶች ክልሉን ለቀዉ እየወጡ ነዉ
#FastMereja I በትግራይ ክልል ያለውን የጦርነት ሥጋት በመሸሽ በርካታ ወጣቶች ክልሉን ለቀው በመውጣት ላይ መሆናቸው እየተነገረ ነው፡፡አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ የሰጡ የክልሉ ወጣቶች እና በክልሉ ያለውን ፖለቲካዊ ሁናቴ በቅርበት የሚከታተሉት ወገኖች እንደሚሉት ማህበረሰቡ ተደጋግሞ በሚመጣው ጦርነት መሰላቸቱን ይናገራሉ።
በትግራይ እየተካሄደ ባለው የጦርነት ዝግጅት ምክንያት አጠቃላይ ማህበረሰቡም ሆነ ወጣቱ እጅግ አስቸጋሪ ጊዜን እያሳለፈ ይገኛል ሲል አስተያየቱን ለዶይቼ ቬለ ያጋራው አንድ የመቐለ ነዋሪ ወጣት፤ “በተለይም ሺራሮ አከባቢ ከሰሞኑ የተወሰደው የድሮን ጥቃት እርምጃ ድንጋጤን ፈጥሯል” የሚለው ወጣቱ ከዚሁ የተነሳ አሁን ላይ በርካታ ወጣት ወደ አዲስ አበባ እና ሌሎችም መሃል አገር አከባቢ በመሸሽ በተጨማሪ ጦርነት ላለመሳተፍ ጥረት እያደረገ ይገኛል ነው ያለው፡፡ “በክልሉ በተለይም ከመቀሌ ውጪ ባሉ አከባቢዎች ላይ ወጣቱ ወደ አስገዳጅ የጦርነት ምልመላ እየገባ ነው” የሚለው ወጣቱ ከዚሁ የተነሳ የተቻለው ወጣት በሙሉ ትግራይ ለቆ ለመውጣት የተቻለውን ሁሉ እያደረገ ነው ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል፡፡
ሌላው የመቀሌ ከተማ ነዋሪ የሆነው ወጣትም ባከለው ተመሳሳይ አስተያየቱ፤ “ወጣቱ አሁን መማር መስራት እንጂ ወደ ጦርነት መግባት አይፈልግም” በማለት እሱ ራሱን ጨምሮ በርካታ ወጣት “የማይከፈለው ዋጋ እየከፈለ ከክልሉ እየሸሸ እየወጣ” መሆኑን ገልጿል፡፡ ወጣቱ እራሱም ከክልሉ ለመውጣት የአውሮፕላን ቲኬት ቆርጦ እየተጠባበቀ መሆኑን ነው የገለጸው፡፡
በትግራይ ክልል እንደ ከዚህ ቀደሙ ደም አፋሳሹ ጦርነት ወጣቶች ወደ ግጭት ከመግባት ይልቅ የጦርነት ሃሳቡን የማይገዙት ለምን ይሆን ተብለው የተጠየቁት ወጣቶቹ፤ “በቂ ምክንያት የለንም” ይላሉ፡፡ “ትናንት ከደፈረን ሃይል ጋር መስራት አልፈልግም” ሲል አስተያየቱን ሰጠው አንደኛው ወጣት፤ ወጣቱ በዚህ የሚቀየር የለም የሚለውን ሃሳብ በመያዝ ከጦርነቱ መሸሽን ምርጫው ማድረጉን ነው ያመለከተው፡፡ ሌላኛውም አስተያየቱን ያከለው የመቀሌ ከተማ ነዋሪው ወጣት፤ “ወጣቱ ካለፈው ጦርነት በመማር አሁን ሰላም ወዳለበት ሄዶ ሰርቶ መለወጥ ነው ፍላጎቱ” ሲል ሃሳቡን አጋርቷል፡፡
በትግራይ የጦርነት አይቀሬነት አሁን አሁን ጎልቶ እየመጣ መሆኑን በማስረዳት አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ የሰጡ የክልሉን ፖለቲካዊ ሁናቴዎች በቅርበት የሚከታተሉት ፖለቲከኛ መስፍን ደሳለኝ እንደሚሉት አሁን አሁን አጠቃላይ እንደማህበረሰብም ሆነ ወጣቱ ክፍል በትግራይ ባለው የፖለቲካዊ ሁኔታዎች ላይ ተስፋ እየቆረጠ መጥቷል ነው የሚሉት፡፡ “በተለይም ከፕሪቶሪያው የቅጭት ማቆም ስምምነቱ በኋላ የትግራይ ፖለቲካ ተከፋፍሎ ታይቷል” ያሉን ፖለቲከኛው፤ በተለይም ወጣቱ ሃይል ተጨማሪ ዋጋ የመክፈል ፍላጎትን ፈጽሞ እያሳየም አይደለም ነው ያሉት፡፡ በመሆኑ አቅም ያላቸው ወጣቶችም ሆኑ ሌሎችም እየተጋገዙ ከክልሉ በመውጣት ሌሎች አከባቢዎች ላይ ሄደው ስራ ፈጥረው ህይወታቸውን የመምራት አዝማሚያዎችን እያሳዩ ስለመምጣታቸውም በሰፊው እየተስተዋለ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡
ዘገባው የዶይቼ ቬለ ነው! | 4 771 |
| 7 | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት የ24 ምርጫ ክልል ውጤቶችን ይፋ አድርጓል።
#FastMereja I ዛሬ ይፋ በተደረጉት ውጤቶች ብልጽግና ፓርቲ በኦሮሚያ ክልል እና በጋምቤላ ክልል፥ ለህዝብ ተወካዮችና ለክልል ምክር ቤት ያቀረባቸው ሁሉም እጩዎች ወንበሩን አግኝተዋል።
በአማራ ክልል በጎንደር ዙሪያ 4 ምርጫ ክልል የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ እጩ የሆኑት አቶ ጣሂር ሙሐመድ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፓርቲያቸውን ወክለው ወንበር ሲያገኙ፤ በቀሪዎቹ ለህዝብ ተወካዮች እና ለክልል ምክር ቤት ብልጽግና ፓርቲ ያቀረባቸው እጩዎች ወንበሩን አግኝተዋል።
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፤ የጉሙዝ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ወክለው ለክልል ምክር ቤት የተወዳደሩት ሀሲል አርባብ ሀሚስ አንድ መቀመጫ ሲያገኙ፥ ብልጽግና ፓርቲ በምርጫ ክልሉ ለክልል ምክር ቤት ያቀረባቸው 8 እጩዎች መቀመጫ አግኝተዋል።
የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ዛሬ ውጤታቸው ይፋ የተደረጉ የምርጫ ክልሎች አንድ ፓርቲ ብቻ የተወዳደረባቸው እና በድምጽ ቆጠራው አሸናፊ በሆኑትና ከታች ባሉት መካከል ያለው የድምጽ ልዩነት “በሺዎች” ልዩነት ያላቸው መሆኑን አስረድተዋል።
በሌላ በኩል ሰብሳቢዋ ምርጫ ከተካሄደባቸው 1,138 የምርጫ ክልሎች ውስጥ 816 የሚሆኑት የማዳመር ሥራቸውን አጠናቀው ወደ ማዕከል ውጤታቸውን መላካቸውን አስታውቀዋል።
ቦርዱ ይፋ የተደረጉ ውጤቶችን በዌብሳይቱ ላይ እንደሚለጥፍ ገልጿል።
ማስታወሻ ፦ ከላይ የቀረቡት ውጤቶች ቦርዱ በዛሬው ዕለት ይፋ ያደረጋቸውን ብቻ የሚመለከት ነው።
ዘገባው የቲክቫህ ኢትዮጵያ | 4 836 |
| 8 | በቲክቶክ ጸያፍ ንግግር ሲያሰራጩ የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
#FastMereja I በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባምባሲ ወረዳ በማህበራዊ ሚዲያ (በተለይም በቲክቶክ) ላይ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችን የሚያንቋሽሹ፣ የሚሳደቡ እና የማህበረሰቡን ወግና ልማድ የሚፃረሩ ጸያፍ ቃላትን ሲነዙ የነበሩ ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የባምባሲ ወረዳ ፖሊስ ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
የባምባሲ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አዛዥ ኮማንደር ሀሩን ሄረላ እንደገለጹት፣ ተጠርጣሪዎቹ የዲጂታል መድረኮችን በመጠቀም የህዝብን ሞራልና የአካባቢውን ሰላም የሚነኩ ተግባራትን ሲፈጽሙ ቆይተዋል። በአሁኑ ወቅት በግለሰቦቹ ላይ ጥብቅ የምርመራ ሂደት እየተከናወነ ሲሆን፣ የምርመራው ውጤት ተጠናቆ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለህብረተሰቡ ይፋ እንደሚደረግ ፖሊስ ተናግሯል። | 5 425 |
| 9 | 🏢 የሰመር ሪል እስቴት ልዩ የቤት ባለቤት የመሆን እድል!
በከተማችን እምብርት ቡልጋሪያ አደባባይ አካባቢ የሚገኙትን እጅግ ዘመናዊ፣ ሰፊ እና ምቹ የመኖሪያ አፓርታማዎችን በፈለጉት የካሬ አማራጭ ለሽያጭ አቅርበናል።
📐 የምርጫዎትን የካሬ እና የመኝታ አማራጮች ይምረጡ፦
🛏️ ባለ 1 መኝታ – 81 ካሬ
🛏️ ባለ 2 መኝታ – 111 እና 134 ካሬ
🛏️ ባለ 3 መኝታ – ከ168 ካሬ ጀምሮ
💰 እጅግ አስገራሚ ዋጋ እና ልዩ የክፍያ አማራጭ፦
💵 ዋጋ፦ በካሬ 89,000 ብር ብቻ!
📉 ቅድመ ክፍያ፦ 10% ብቻ በመክፈል ውል ያሰሩ!
🏦 የባንክ ብድር፦ 50% የባንክ ብድር የተመቻቸለት።
⏳ ጊዜ አይውሰዱ!
ይህ ታላቅ የዋጋ ቅናሽ የሚቆየው ለውስን ጊዜ ብቻ ስለሆነ፣ ቀድመው በመምጣት የዕድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ።
📍 ቦታ፦ ቡልጋሪያ አደባባይ አካባቢ
📞 ለበለጠ መረጃ አሁኑኑ ይደውሉልን፦0912355631
የህልምዎን ቤት ዛሬውኑ በእጅዎ ያስገቡ!
#Summer #AddisAbabaBusiness #apartmentforrentplantation #shopforsale #apartmentforrent #amibaraproperties #realestate #የንግድቦታ #Temerrealestate #teklehaymanotmall | 5 245 |
| 10 | የሿሿ ወንጀል የፈጸሙ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ
#FastMereja I ተጠርጣሪዎቹ የወንጀል ድርጊቱን የፈጸሙት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ልዩ ቦታው ሳሪስ አቦ የትራፊክ መብራት አካባቢ ነው።
ተጠርጣሪዎቹ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3 A 02122 ኦሮ በሆነ ሚኒባስ ተሽከርካሪ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪና ተጠቃሚ በመምሰል አዲሱ መኮንንና ኢሳያስ ደገፋ የተባሉ የግል ተበዳዮችን በመጫን ጥቂት እንደተጓዙ ኪሳቸው ውስጥ የነበረውን የሞባይል ስልክ እና ገንዘብ ለመውሰድ ሲሞክሩ የግል ተበዳዮች ወንጀሉን ለመከላከል በሚሞክሩበት ወቅት ገፍትረዋቸው በፍጥነት በመጓዝ ላይ ሳሉ ከሌላ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨት ቆመዋል።
በወቅቱ ድርጊቱን በተመለከተው የአካባቢው ህብረተሰብና በትራፊክ ፖሊስ አማካኝነት በተሽከርካሪው ውስጥ የነበሩ ትዕግስት ጌታቸው፣ ገነት ደሳለኝ፣ ሜላት ጌታቸው፣ እየሩሳሌም ጌታነህና መአዛ ማሞ የተባሉ ተጠርጣሪዎችን ከ6 የተለያዩ ስማርት ሞባይል ስልኮችና 11 ሚሞሪ ካርዶች ጋር ሊያዙ መቻላቸውን በወንጀል ምርመራ ም/ዋና ጠቅላይ መምሪያ የልዩ ልዩ እና የተደራጁ ወንጀሎች ምርመራ መምሪያ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በተያዙ ተጠርጣሪዎች ላይ ተገቢው ምርመራ የማስፋት ተግባር እየተከናወነ ሲሆን ሌሎች ያልተያዙ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋልም ከፍተኛ ክትትል እየተደረገ መሆኑን ፖሊስ ገልጿል።
ተጠርጣሪዎቹ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች እየተንቀሳቀሱ ወንጀሉን የሚፈፅሙ በመሆናቸው በእነዚህ ተጠርጣሪዎች ወንጀል የተፈጸመባቸው አዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በመቅረብ ስልኮቻቸውን መረከብ እንደሚችሉ ተገልጿል። | 4 951 |
| 11 | የቲክቶክ ተፅዕኖ ፈጣሪው ባርኮት (ክሊንተን) የ“ቅን ልቦች” ሽልማትን አሸነፈ
#FastMereja I በቲክቶክ ማህበራዊ ሚዲያ የሚታወቀው ባርኮት (በመታወቂያ ስሙ ክሊንተን) የወርሃ ግንቦት የ“ቅን ልቦች” ተሸላሚ ሆኗል።
ይህ የወርሃዊ ሽልማት መርሃ-ግብር በማህበረሰቡ ውስጥ አዎንታዊ ተፅዕኖ ለሚያሳድሩ ግለሰቦች እውቅና ለመስጠት የሚዘጋጅ ሲሆን፣ ወጣቱ የቲክቶክ ተፅዕኖ ፈጣሪ ባርኮት በግንቦት ወር ባከናወናቸው ተግባራት አሸናፊ መሆን ችሏል። ሽልማቱን ከተቀበለ በኋላ ባደረገው ንግግር፣ የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች ለበጎ ተግባር መዋል እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥቷል። በተለይም በዲጂታሉ ዓለም ውስጥ ያሉ ወጣቶች የሀገር ባለውለታዎችንና ታላላቆችን በማክበር ረገድ ግንባር ቀደም መሆን እንደሚገባቸው አሳስቧል። | 4 970 |
| 12 | በጋምቤላ ከተማ ተከስቶ የነበረው የተኩስ ልውውጥ
#FastMereja I ዛሬ ማምሻውን በጋምቤላ ከተማ በአንድ የፌዴራል ፖሊስ አባል አማካኝነት ተከስቶ የነበረው ያልተጠበቀ የተኩስ ክስተት በቁጥጥር ሥር መዋሉንና በአሁኑ ሰዓት በአካባቢው ሙሉ መረጋጋት መስፈኑን የክልሉ መንግሥት በሰጠው ወቅታዊ መግለጫ አስታውቋል።
የክልሉ መንግሥት ዛሬ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ ክስተቱ ከተቀሰቀሰ በኋላ የክልሉና የፌዴራል ፀጥታ አካላት በቅንጅት ባደረጉት ፈጣን እንቅስቃሴ ሁኔታው ወደ ከፋ ደረጃ እንዳይሸጋገር ማድረግ ተችሏል። በማረጋጋት ሂደቱ ወቅት የተኩስ ልውውጥ እንደነበረ የተገለጸ ሲሆን፣ በአሁኑ ሰዓት ግን ውጥረቱ ሙሉ በሙሉ ረግቦ አካባቢው ወደ መደበኛ እንቅስቃሴው ተመልሷል።
የክልሉ መንግሥት ከጉዳዩ ጋር ተያይዘው ያሉ ዝርዝር ምክንያቶች በሕግና በሥርዓት ተጣርተው ተገቢው እርምጃ እንደሚወሰድ ያረጋገጠ ሲሆን፣ የፀጥታ አካላትም አስፈላጊውን የጥበቃና የክትትል ሥራ በቀጣይነት እንደሚያከናውኑ አስታውቋል። | 5 578 |
| 13 | ለትግራይ ጦርነት መነሻ ወደኋላ ተመልሶ የሚተገበርና ጋዜጠኞችን እስከ 25 ዓመት ሊያስቀጣ የሚችል አዲስ ረቂቅ ሕግ መዘጋጀቱ ተ
ለትግራይ ጦርነት መነሻ ወደኋላ ተመልሶ የሚተገበርና ጋዜጠኞችን እስከ 25 ዓመት ሊያስቀጣ የሚችል አዲስ ረቂቅ ሕግ መዘጋጀቱ ተገለጠ
#FastMereja I ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በትግራይ ክልል ውስጥ ወታደራዊ ንቅናቄን የሚቃወሙ፣ በትጥቅ ትግሉ ላይ ትችት የሚያቀርቡ ወይም መከላከያ ጥረቱን ያደናቅፋሉ የተባሉ ግለሰቦችና የሚዲያ ተቋማት ላይ እስከ 25 ዓመት የሚደርስ ፅኑ እስራትን የሚጥል አዲስ ረቂቅ አዋጅ ማዘጋጀቱ ታወቀ። ይህ ረቂቅ ሕግ ከትግራይ ክልል ወሰን ውጭ ባሉ የዲያስፖራ አባላትና ተሟጋቾች ላይ ጭምር ተፈጻሚነት እንዲኖረው የተደረገ ሲሆን፣ ይበልጥ አጋዥና አከራካሪ ያደረገው ደግሞ ሕጉ ጸድቆ ሥራ ላይ ከሚውልበት ቀን ይልቅ ወደኋላ ተመልሶ ጦርነቱ ወደተቀሰቀሰበት ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ተፈጻሚ እንዲሆን መደንገጉ ነው።
ይህ “የመከላከያ ጥረትን ማደናቀፍ” በሚል ርዕስ በረቂቅ አዋጁ አንቀጽ 17 ስር የሰፈረው ድንጋጌ፤ በማንኛውም የመገናኛ ብዙኃን ዘዴ ወይም ሌላ አማራጭ ሰዎችን በወታደራዊ ክተት ውስጥ እንዳይሳተፉ ቅስቀሳ ያደረገ፣ ያበረታታ፣ የገንዘብ ድጋፍ ያሰባሰበ ወይም የተቃወመ ሰው ከ5 እስከ 15 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት እንደሚቀጣ ይደነግጋል። ድርጊቱ በከባድ ሁኔታ ከተፈጸመ ደግሞ ቅጣቱ ከ15 እስከ 25 ዓመት ሊደርስ እንደሚችል ተመልክቷል። በተጨማሪም አንቀጽ 17(5) ማንኛውም የጋዜጣ፣ የቴሌቪዥን፣ የድረ-ገጽ ወይም የማኅበራዊ ሚዲያ ተቋም በዚህ ወንጀል ውስጥ እጁ እንዳለበት ከተረጋገጠ የገንዘብ መቀጮ፣ የሥራ እገዳ፣ የፈቃድ ስረዛና የንብረት መወረስ ቅጣቶች እንደሚጠብቁት ያሳያል።
በሌላ በኩል ረቂቁ ሕግ በትግራይ ታጋዮች፣ በጦርነቱ መስዋዕትነት በከፈሉ ወገኖች፣ በታጋይ ቤተሰቦች እንዲሁም በትግራይ እናቶች ላይ የሚሰነዘሩ ትችቶችንና ንቀቶችን ወንጀል አድርጎታል። ይህንን የጣሰ ግለሰብ ከ5 እስከ 10 ዓመት፤ ድርጊቱ በተደራጀ ቡድን ወይም በሚዲያ አማካኝነት ከተፈጸመ ደግሞ ከ10 እስከ 15 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራትና በከፍተኛ የገንዘብ መቀጮ እንደሚቀጣ በረቂቁ አንቀጽ 18 ላይ ሰፍሯል። የክልሉን ሰንደቅ ዓላማ፣ ብሔራዊ መዝሙርና ታሪካዊ ትግሎችን ያንኳሰሰም እስከ 5 ዓመት ሊታሰር እንደሚችል ተደንግጓል።
የሕግ ባለሙያዎችና ተቺዎች ረቂቅ ሕጉ በክልሉ ያለውን የመናገር፣ የመጻፍና የፕሬስ ነፃነት ሙሉ በሙሉ ሊያሳጣና የፖለቲካ ልዩነትን ሊያጠፋ ይችላል የሚል ከፍተኛ ሥጋት ገልጸዋል። በተለይም ሕጉ ወደኋላ ተመልሶ ባለፉት ስድስት ዓመታት በተከናወኑ ድርጊቶች ላይ ጭምር ክስ ለመመስረት የሚያስችል መሆኑና ከክልሉ ውጭ ባሉ ማኅበረሰቦች ላይ ተፈጻሚ እንዲሆን መደረጉ ዓለም አቀፍ የሕግ መርሆችን የጣሰ ነው በማለት ተቃውመዋል። በአንጻሩ የሕጉ ደጋፊዎች ድንጋጌው የትግራይን ደኅንነት ለመጠበቅ፣ ወታደራዊ ዝግጁነትን ለማረጋገጥና ለሕዝቡ ሲሉ መስዋዕት የሆኑ ወገኖችን ክብር ለማስጠበቅ አስፈላጊ ነው የሚል መከራከሪያ ያቀርባሉ። | 5 206 |
| 14 | ህወሓት በክልሉ ያሉ ህዝቦች በረሃብ እና በሽታ እየተሰቃዩ ነው አለ!
#FastMereja I ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ባወጣው ሳምንታዊ መግለጫ፣ የፌደራል መንግሥት ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ሌሊት በትግራይ ሠራዊት አባላት ላይ የድሮን ጥቃት መፈጸሙን ገለጸ። ድርጅቱ በትግራይና በፌደራል መንግሥት መካከል ያለው ውጥረት አሁንም በከፍተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አመልክቷል።
በመግለጫው መሠረት፣ የትግራይ ክልል 40 በመቶ መሬት አሁንም በሌሎች ኃይሎች እጅ እንደሚገኝና ከተፈናቀሉበት መሬት ውጭ ያሉ ወገኖች በረሃብና በበሽታ እየተሰቃዩ መሆኑ ተገልጿል።
የፌደራል መንግሥት የትግራይን ሰላም ለማናጋት በዓፋርና በጸለምቲ በኩል አዲስ የደም ማፋሰስ ጦርነት ለመክፈትም ከጫፍ እስከ ጫፍ መሣሪያና ሠራዊት እያስገባ መሆኑን ህወሓት በመግለጫው አስፍሯል።
ህወሓት በአሁኑ ወቅት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ ድርጅቱ ራሱን ፈትሾ ያደረገው መዋቅራዊ ጥንካሬ እና የትግራይ ሠራዊት (TDF) ክልሉን ለመከላከል በጥሩ ቁመና ላይ እንደሚገኙ ገልጾ፤ በትግራይ ውስጥና ከክልሉ ውጭ የሚኖሩ ተጋሩ ሙሉ አቅማቸውን አስተባብረው ለህልውና እና ለሉዓላዊነት እንዲታገሉ ጥሪ አቅርቧል።
በዚህ ዙሪያ ከፌደራል መንግሥት በኩል የተሰጠ ምላሽ የለም። | 4 457 |
| 15 | ኬብሮን አማኑኤል በ“ጣፋጭ ሕይወት” ልዩ ተመስጋኝ ሆናለች
#FastMereja I በጎ ተግባርን ማዕከል በማድረግ ለ6ኛ ዙር በተካሄደው የ“ጣፋጭ ሕይወት” የምስጋና መርሃ ግብር ላይ፣ “ልጄ ሆይ” በተሰኘው የበጎ አድራጎት እንቅስቃሴዋ የምትታወቀው ኬብሮን አማኑኤል የዘንድሮው የ“ልዩ ተመስጋኝ” ተሸላሚ ሆና ተመርጣለች።
ባለፉት ዓመታት በልጆች፣ በወላጆችና በችግረኛ ማህበረሰብ ክፍሎች ላይ ትኩረት አድርጋ ስትሠራ የቆየችው ኬብሮን አማኑኤል፣ ማኅበረሰቡን ማገልገል ግዴታዋ እንደሆነ ብታምንም ድርጅቱ ለታናናሾች ተምሳሌት እንድትሆንና ለወደፊቱ ይበልጥ እንድትተጋ ይህንን ዕውቅና እንደሰጣት ተገልጿል። ተሸላሚዋ ባለፉት አራት ዓመታት ውስጥ ብቻ 38 ሕፃናትን በትምህርት፣ በቁሳቁስና በነፃ ሕክምና ከመርዳቷም በላይ በሚኪሊላንድ መንግሥት ትምህርት ቤት የእናት አምባሳደር በመሆን አገልግላለች። በተጨማሪም በሆለታ፣ በፋኖስ እና በጅማ ለሚገኙ ከ3,000 በላይ ሴት ተማሪዎች የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ድጋፍ ያደረገች ሲሆን፣ በአረጋውያን፣ በተጣሉ ሕፃናት እና በካንሰር ታማሚዎች ዘንድ በመገኘት ማህበራዊ ድጋፍ ስትሰጥ መቆየቷ ተመልክቷል።
በዓመት ሦስት ጊዜ የደም ልገሳ ፕሮግራም በማዘጋጀትና ብቻቸውን ልጆቻቸውን የሚያሳድጉ እናቶችን እንዲሁም ከሱስ ለማገገም የሚጥሩ ሴቶችን በመደገፍ የምትታወቀው ኬብሮን፣ ሽልማቱን ከተቀበለች በኋላ ባስተላለፈችው መልዕክት “ውስጥ ካለኝ ሳይሆን ከሌለኝ ያካፈልኩት የኖርኩት ኑሮዬ ነው” በማለት ምስጋናዋን አቅርባለች። ወደፊትም በ“ልጄ ሆይ” ተግባሯ የተጣለባትን አደራ ለመወጣት ቃል የገባች ሲሆን፣ በገንዘብና በሃሳብ ከጎኗ ለቆሙት የ“200 ብር ቻሌንጅ” ተሳታፊዎችና የቅርብ ደጋፊዎቿ ምስጋናዋን አቅርባለች።
በርቺ ብለናል 🤝 | 3 936 |
| 16 | 6ኛው “ጣፋጭ ሕይወት” የምስጋና ፕሮግራም በደመቀ ሁኔታ ተከናወነ
#FastMereja I ዜጎች በሕይወታቸው መልካም የዋሉላቸውን ባለውለታዎች የሚያመሰግኑበትና ዘንድሮ ለ6ኛ ጊዜ የተዘጋጀው “ጣፋጭ ሕይወት የምስጋና ፕሮግራም” በአዲስ አበባ፣ በሐዋሳ እና በሐረር ከተሞች ሙሉ ቀን የቆዩ ልዩ ልዩ የክብር መርሃ ግብሮችን በማካተት በደመቀ ሁኔታ ተከናወነ።
የዘንድሮው የምስጋና ቀን መርሃ ግብር ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ በሦስቱም ከተሞች ለአካባቢ ጥበቃና ውበት ከፍተኛ አስተዋፅኦ የሚያበረክቱ የፅዳት ባለሙያዎችን በማህበረሰቡ ዘንድ ታላቅ ምስጋና እና ክብር በመስጠት ተጀምሯል። በመቀጠልም ከረፋዱ 2:00 ሰዓት ላይ መምህራን ከተማሪዎቻቸው ደማቅ የእውቅና ስነ-ስርዓት የተበረከተላቸው ሲሆን፣ በምሳ ሰዓት ደግሞ በየሆስፒታሎቹና በሕክምና ተቋማቱ የሚገኙ ታካሚዎች የሕክምና ባለሙያዎችን በአካል በመገኘት አመስግነዋል።
ከምሽቱ 10:00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ በተካሄደው ማጠቃለያ ፕሮግራም ላይ ከአምስት መቶ በላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም ታዋቂና በጎ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች በታደሙበት ስድስተኛው ጣፋጭ ሕይወት ምስጋና መርሃ ግብር በአምስት ዘርፍ የሚመሰገኑ አካላት እውቅና አግኝተዋል ።
ከ15 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን ጋር ይደርሳል ተብሎ የታቀደው የዚህ መርሃ ግብር አዘጋጆች ቲኤች ሚድያ ግሩፕ እና ስዊት ላይፍ ፎር ኦል ሲሆኑ፣ ዋና ዓላማቸውም በሚቀጥሉት አሥር ዓመታት ውስጥ ግንቦት 30 ቀን በኢትዮጵያ ብሔራዊ “የምስጋና ቀን“ ሆኖ እንዲሰየም ማድረግ እንደሆነ አስታውቀዋል። | 4 021 |
| 17 | የግብፅ እና የኤርትራ መሪዎች በካይሮ ተገናኙ፤ የአፍሪካ ቀንድ እና የቀይ ባህር ጉዳይ ዋነኛ አጀንዳ ሆኗል
#FastMereja I የግብፁ ፕሬዚዳንት አብደል ፈታህ ኤል-ሲሲ የኤርትራውን ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂን ዛሬ ሰኞ በካይሮ በይፋዊ የስራ ጉብኝት ተቀብለው አነጋግረዋል። መሪዎቹ በሁለትዮሽ ግንኙነት፣ በአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ሁኔታዎች እና በቀይ ባህር ፀጥታ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ማድረጋቸውን የግብፅ ፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤት አስታውቋል።
ለሶስት ቀናት በሚቆየው በዚህ ጉብኝት፣ ፕሬዚዳንት ኤል-ሲሲ ግብፅ ለኤርትራ ሉዓላዊነት እና ግዛታዊ አንድነት የምታደርገውን ድጋፍ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ በበኩላቸው ከግብፅ ጋር ያለውን የምጣኔ ሀብት እና የንግድ ትብብር ይበልጥ ለማስፋት ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል። በሁለቱ መሪዎች መካከል የተደረገው ይህ ከፍተኛ ውይይት፣ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ካለው ዲፕሎማሲያዊ እና ጂኦፖለቲካዊ ውጥረት አንጻር ቀጠናዊ ትኩረትን ስቧል። | 4 083 |
| 18 | 🏢 የሰመር ሪል እስቴት ልዩ የቤት ባለቤት የመሆን እድል!
በከተማችን እምብርት ቡልጋሪያ አደባባይ አካባቢ የሚገኙትን እጅግ ዘመናዊ፣ ሰፊ እና ምቹ የመኖሪያ አፓርታማዎችን በፈለጉት የካሬ አማራጭ ለሽያጭ አቅርበናል።
📐 የምርጫዎትን የካሬ እና የመኝታ አማራጮች ይምረጡ፦
🛏️ ባለ 1 መኝታ – 81 ካሬ
🛏️ ባለ 2 መኝታ – 111 እና 134 ካሬ
🛏️ ባለ 3 መኝታ – ከ168 ካሬ ጀምሮ
💰 እጅግ አስገራሚ ዋጋ እና ልዩ የክፍያ አማራጭ፦
💵 ዋጋ፦ በካሬ 89,000 ብር ብቻ!
📉 ቅድመ ክፍያ፦ 10% ብቻ በመክፈል ውል ያሰሩ!
🏦 የባንክ ብድር፦ 50% የባንክ ብድር የተመቻቸለት።
⏳ ጊዜ አይውሰዱ!
ይህ ታላቅ የዋጋ ቅናሽ የሚቆየው ለውስን ጊዜ ብቻ ስለሆነ፣ ቀድመው በመምጣት የዕድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ።
📍 ቦታ፦ ቡልጋሪያ አደባባይ አካባቢ
📞 ለበለጠ መረጃ አሁኑኑ ይደውሉልን፦0912355631
የህልምዎን ቤት ዛሬውኑ በእጅዎ ያስገቡ!
#Summer #AddisAbabaBusiness #apartmentforrentplantation #shopforsale #apartmentforrent #amibaraproperties #realestate #የንግድቦታ #Temerrealestate #teklehaymanotmall | 4 235 |
| 19 | በምግብ ወለድ በሽታዎች በዓለም ላይ በየዓመቱ እስከ 1.5 ሚሊዮን ሕዝብ ይሞታል ተባለ!
#Fastmereja I በዓለም ላይ በየዓመቱ ወደ 866 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች በምግብ ወለድ በሽታዎች (Foodborne illnesses) የሚጠቁ ሲሆን፣ ከእነዚህም ውስጥ እስከ 1.5 ሚሊዮን የሚሆኑት ሕይወታቸውን እንደሚያጡ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) አዲስ ያወጣው መረጃ አመለከተ።
ይህ አስደንጋጭ የወረርሽኝ ጫና በተለይ ዕድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትን እና በማደግ ያሉ አገራትን በከፍተኛ ሁኔታ እያጠቃ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA) ከዓለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) ጋር በመተባበር “ከምግብ ደህንነት ችግሮች ወደ መፍትሔዎች በሁሉም ቦታ ደህንነቱ የተጠበቀ ምግብ” በሚል መሪ ቃል በዛሬዉ እለት በስካይላይት ሆቴል ባዘጋጁት የዉይይት መድረክ ላይ ነው።
መድረኩ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ8ኛ ጊዜ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ7ኛ ጊዜ የተከበረውን የዓለም የምግብ ደህንነት ቀንን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ ሲሆን፣ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት በኢትዮጵያ የደብሊውኤፍፒ (WFP) የሰፕላይ ቼይን ኃላፊ የሆኑት ክላራ ሲልቫ እንደገለፁት ፣ እነዚህ ቁጥሮች ዝም ብለው ቁጥር ብቻ ሳይሆኑ አስቸኳይ የድርጊት ጥሪዎች መሆናቸውን ገልጸዋል።
ድርጅታቸው በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ለ3 ሚሊዮን ተጋላጭ ወገኖች ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፣ ከ2026 እስከ 2030 ባለው ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ምግብን ከውጭ ከማስገባት ይልቅ ወደ ሀገር ውስጥ ምርት ግዢ (Local Sourcing) ለማሸጋገር እየተሠራ መሆኑን አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን በበኩሉ የምግብ ቁጥጥር ሥርዓቱን “ከቅድመ-ገበያ እስከ ድኅረ‐ገበያ” ለማዘመን በርካታ ስኬቶችን ማስመዝገቡን ይፋ ያደረገ ሲሆን በተጨማሪም በኬላዎች ላይ ያለውን ቁጥጥር የሚያጠናክር ግዙፍና ዘመናዊ የላቦራቶሪ ኮምፕሌክስ ግንባታ ወደ ማጠናቀቂያው መድረሱ ተገልጿል።
እንዲሁም ማንኛውም ያልታወቀ ወይም ያልተረጋገጠ የምግብ ምርት ወደ አገር ውስጥ እንዳይገባ፣ ይዘቱና የአመራረት ሂደቱ በጥልቀት የሚገመገምበት ዘመናዊ የሰነድ ምዝገባ ሥርዓት ወደ ሥራ መግባቱን አስታዉቋል።
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሄራን ገርባ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደተናገሩት፣ ይህንን የጥራት ማረጋገጫና የቁጥጥር ሥርዓት ወደ ክልሎች፣ በተለይም የተቀናጁ የግብርና ማቀነባበሪያና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደሚገኙባቸው አካባቢዎች የማውረድ ሥራ መጀመሩን ገልፀዋል።
ዋና ዳይሬክተሯ አክለዉም ክልሎች የችርቻሮ ንግዱንና የአቅርቦት መስመሩን የሚቆጣጠሩ በመሆናቸው፣ በታችኛው መዋቅር ላይ የጥራት ማረጋገጫ ሥርዓት መዘርጋት “የመደራደሪያ ጉዳይ አይደለም” ሲሉ ገልፀዋል።
ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍም የክትትል ሥርዓትን ማጠናከር፣ በሳይንስ ላይ የተመሰረቱ ውሳኔዎችን መውሰድ፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን (AI) ጨምሮ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ያለውን ትብብር ማሳደግ እንደሚገባ በመድረኩ ላይ አቅጣጫ ተቀምጧል።
እንዲሁም በመርሀ-ግብሩ ላይ ባለድርሻ አካላት በጉዳዩ ዙሪያ የተለያዩ ገለፃዎችን ያቀረቡ ሲሆንየ2026 (እ.ኤ.አ) የዓለም የምግብ ደህንነት ቀን ዋና መሪ ቃል የሆነውን “ከችግር ወደ መፍትሄ – አስተማማኝ ምግብ በየትኛውም ቦታ” (From Burden to Solutions – Safe Food Everywhere) የሚለውን ሀሳብ መሰረት ያደረገ የፓናል ዉይይትም ተካሂዷል። | 4 225 |
| 20 | በከባድ ሙስና የተከሰሱትን ወ/ሮ በረከት ወርቁን ጨምሮ 4 ተከሳሾችን፤ ፖሊስ ፍርድ ቤት ማቅረብ ሳይችል ቀረ፡፡
በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው በፖሊስ የ'ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ የወጣባቸው ወ/ሮ በረከት ወርቁን ጨምሮ አራት ተከሳሾን ፖሊስ በዛሬ ፍርድ ቤት እንዲያቀርብ ታዞ ነበር።
ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ በጋዜጣ ጥሪ ተደርጎላቸው እንዲቀርቡ በማዘዝ ለሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት፤ "በገበያ ላይ የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት አድርገዋል" የተባሉ የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርን እና የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ በ13 ግለሰቦች ላይ የተመሰረተውን የከባድ ሙስና ወንጀል ክስ፣ የክስ መቃወሚያ እና የአቃቤ ህግን ምላሽ ዛሬ መርምሯል።
የፌደራል አቃቤ ህግ ተከሳሾቹን በዋና ወንጀል አድራጊነት እና በልዩ ተካፋይነት፤ ስልጣንን ያለአግባብ በመገልገልና የመንግስትን ስራ በማይመች አኳኋን በመምራት ወንጀል ከሷቸዋል።
ችሎቱ የተከሳሾችን የክስ መቃወሚያ እና የአቃቤ ህግን ምላሽ ለመስማት ለዛሬ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጠሮ ይዞ የነበረ ቢሆንም፣ በክስ መዝገቡ ከ6ኛ እስከ 10ኛ ተራ ቁጥር ላይ የተጠቀሱት ተከሳሾች ሳይገኙ ቀርተዋል።
ችሎት ያልተገኙት ተጠርጣሪዎች በከባድ የሙስና ወንጀል ተፈልገው ማግኘት ባለመቻሉ፣ ፖሊስ ቀደም ሲል የ"ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ አውጥቶባቸው እንደነበር ይታወሳል።
ዛሬ በዋለው ችሎት የቀረበውን የክስ መቃወሚያ እና የአቃቤ ህግን ምላሽ የመረመረው ፍርድ ቤቱ፤ አቃቤ ህግ ክሱን ለይቶ (አሻሽሎ) እንዲያቀርብም አዝዟል።
በተጨማሪም በችሎቱ ያልተገኙት ተከሳሾች በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግላቸው ትዕዛዝ አስተላልፏል።
በመዝገቡ 7ኛ ተከሳሽ የሆኑት ወ/ሮ በረከት ወርቁ ከሀገር መውጣታቸው በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች በሚያደርጉት ንግግር በመረጋገጡ፣ አቃቤ ህግ ለእሳቸው ጥሪው በአዲስ ዘመን እና በኢትዮጵያን ሄራልድ ጋዜጦች ጭምር እንዲያወጣ ባቀረበው ማሳሰቢያ መሰረት ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
ችሎቱ የተሻሻለውን ክስ ለመመልከት እና የጥሪውን ሂደት ለመከታተል ለሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ዘገባው የሸገር ሬዲዮ ነው። | 4 321 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
