FastMereja.com
📈 Análisis del canal de Telegram FastMereja.com
El canal FastMereja.com (@fastmereja) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 49 053 suscriptores, ocupando la posición 3 552 en la categoría Educación y el puesto 654 en la región Etiopía.
📊 Métricas de audiencia y dinámica
Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 49 053 suscriptores.
Según los últimos datos del 07 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -545, y en las últimas 24 horas de -11, conservando un alto alcance.
- Estado de verificación: No verificado
- Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 12.53%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 7.78% de reacciones respecto al total de suscriptores.
- Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 6 148 visualizaciones. En el primer día suele acumular 3 819 visualizaciones.
- Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 30.
📝 Descripción y política de contenido
No se ha proporcionado la descripción del canal.
Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 08 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Educación.
Carga de datos en curso...
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 08 julio | 0 | |||
| 07 julio | 0 | |||
| 06 julio | 0 | |||
| 05 julio | 0 | |||
| 04 julio | +2 | |||
| 03 julio | +5 | |||
| 02 julio | 0 | |||
| 01 julio | 0 |
| 2 | 5 የነዳጅ ማደያዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ
ቀን፦ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም.
#FastMereja I በአዲስ አበባ ከተማ በተደረገ ድንገተኛ ቁጥጥርና ክትትል ህገ-ወጥ አሰራር ሲተገብሩ የተገኙ አምስት የነዳጅ ማደያዎች ላይ እንደ ጥፋት ደረጃቸው የዕገዳ እና የመጨረሻ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ እርምጃ ተወሰደባቸው።
በተደረገው የክትትል ስምሪት መሠረት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ጋርመንት አካባቢ የሚገኘው ኖክ ነዳጅ ማደያ እና በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የሚገኘው አልፋ ነዳጅ ማደያ ህገ-ወጥ አሰራር በማከናወናቸው ከነዳጅ አቅርቦት እንዲታገዱ ተደርጓል። በተመሳሳይ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የሚገኘው ተባረክ ነዳጅ ማደያ ከተፈጸመው ጥሰት አሳሳቢነት አንጻር ከነዳጅ አቅርቦት ለአንድ ወር ሙሉ እንዲታገድ ውሳኔ ተላልፎበታል።
በሌላ በኩል በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቱሉ ዲምቱ የሚገኘው የተባበሩት ነዳጅ ማደያ እና በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በካዛንቺስ ሱፐር ማርኬት አካባቢ የሚገኘው ኦላ ነዳጅ ማደያ ከዚህ ድርጊታቸው ተቆጥበው ወደ ትክክለኛ አሰራር እንዲመለሱ የመጨረሻ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የከተማው አስተዳደር በነዳጅ ስርጭት ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችን እና መደበኛ አሰራርን የሚያስተጓጉሉ አሰራሮችን ለመግታት የሚደረገው ቁጥጥር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ታውቋል። | 4 243 |
| 3 | በአዲስ አበባ የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆነ
ቀን፦ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም.
#FastMereja I በአዲስ አበባ ከተማ ለ2019 በጀት ዓመት የሚተገበረው የግል መኖሪያ ቤቶች ኪራይ ዓመታዊ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ መጽደቁንና የአከራይ-ተከራይ አዲስ የውል እድሳት ምዝገባ ከዛሬ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም ክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ፅ/ቤቶች በይፋ መጀመሩን የከተማዋ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።
ይህ የዋጋ ማስተካከያ ውሳኔ በከተማዋ ሰፊ ሳይንሳዊ ጥናት ተካሂዶ የነዋሪውን እውነተኛ የመክፈል አቅም ባገናዘበ መልኩ የተዘጋጀ ሲሆን፣ በኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን በዘላቂነት ለመግታትና የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ ታስቦ የተወሰነ መሆኑ ተገልጿል።
አዲሱ አሰራር በአንድ በኩል አከራዮች ወቅቱንና የኢኮኖሚ ሁኔታውን ያገናዘበ ፍትሐዊ ገቢ እንዲያገኙ የሚያረጋግጥ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ ተከራዮች ከገቢያቸው ጋር የተመጣጠነ ኪራይ በመክፈል ከተደጋጋሚ መፈናቀልና ከስነ-ልቦና ስጋት ድነው የተረጋጋ ሕይወት እንዲመሩ ያደርጋል። ይህ እርምጃ በከተማዋ ያለውን የኑሮ ውድነት ጫና በከፍተኛ ደረጃ በመቀነስ ረገድ የጎላ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና መልካም አስተዳደር ፋይዳዎች እንዳሉት ቢሮው አረጋግጧል።
#ማህበራዊ | 3 967 |
| 4 | አርጀንቲናን 2 ለ 0 ስትመራ የነበረው ግብጽ በድራማ በተሞላው ምሽት አርጀንቲና 3 ጎሎች በማስቆጠር 3 ለ 2 በማሸነፍ፣ አርጀንቲና ስታልፍ ግብጽ ወድቃለች። | 4 904 |
| 5 | የሰኔ ወር የቅን ልቦች የማህበራዊ ሚዲያ ተፅኖ ፈጣሪዎች ታወቁ፤ ኮሜዲያን ያሲኖ ሽልማቱን በአካል ተቀበለ
#FastMereja I የሰኔ ወር 2018 ዓ.ም የቅን ልቦች የማህበራዊ ሚዲያ ተፅኖ ፈጣሪ ውድድር አሸናፊዎች ይፋ የተደረጉ ሲሆን፣ ከቲክቶክ ኮሜዲያን ያሲኖ እና ዩቲናስ ሽልማቱን ማሸነፋቸው ተነግሯል። ኮሜዲያን ያሲኖ በአካል ተገኝቶ የአሸናፊነት ዋንጫውን እና ሜዳሊያውን በደስታ ተረክቧል።
ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ ተግባር እና ለህዝብ ግንኙነት በበጎ መልኩ ለተጠቀሙ አካላት እውቅና በሚሰጠው በዚህ መርሃ-ግብር ላይ የኮሜዲያን ያሲኖ እና የዩቲናስ ተሳትፎ በከፍተኛ ድምፅ ተደግፎ ለአሸናፊነት አብቅቷቸዋል። | 4 863 |
| 6 | የኦሮሞ ኢንፍሉዌንሰር አዋርድስ በይፋ ተጀመረ!
#Fastmereja I የኦሮሞን ባህል፣ ቋንቋ፣ ወግ እና የቱሪስት መዳረሻዎችን በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የሚያስተዋውቁ ይዘት ፈጣሪዎችን (ኢንፍሉዌንሰሮችን) እውቅና ለመስጠትና ለማበረታታት ያለመ “የኦሮሞ ኢንፍሉዌንሰር አዋርድስ” የተሰኘ አዲስ የሽልማት መርሃ ግብር ይፋ ሆነ።
በጎዶ ኢቨንት ፕሮሞሽን እና በኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን ትብብር የተዘጋጀዉ ይህ መርሀ-ግብር ዋና ዓላማውም የኦሮሞ ሕዝብ ቁጥር ከፍተኛ ቢሆንም በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ያለው የዲጂታል ተደራሽነትና ተፅዕኖ አሁንም ከቁጥሩ ጋር የማይመጥን በመሆኑ ይዘት ፈጣሪዎች ጠንካራ የዲጂታል አሻራ እንዲያሳርፉ በማነቃቃት ይህንን ክፍተት መሙላት እንደሆነ አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
በዚህ የመጀመሪያ ዙር የሽልማት መርሃ ግብር ላይ ከ200 በላይ የሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች የሚሳተፉ ሲሆን፣ ውድድሩ በቲክቶክ9፣ በፌስቡክ 3እና በዩቲዩብ 3 መድረኮች ላይ የተመሰረቱ 15 የተለያዩ የሽልማት ዘርፎችን ያካተተ ነው።
ከእነዚህም በተጨማሪ ሁሉንም ፕላትፎርሞች የሚያጠቃልል “የዓመቱ ምርጥ የኦሮሞ ኢንፍሉዌንሰር” እና የቱሪዝም መዳረሻዎችን የሚያስተዋውቁ ባለሙያዎች የሚሸለሙበት ልዩ የ”Best of Visit Oromia” ዘርፎች ተካተዋል። በውድድሩ በአንደኝነት ለሚያሸንፈው ተወዳዳሪ ታላቅ የመኪና ሽልማት የተዘጋጀ ሲሆን፣ ታዋቂ የሆኑ ሕፃናት የሚበረታቱበት የገንዘብና የቁስ ሽልማትም መመቻቸቱ ነዉ የተገለፀዉ።
የዕጩዎች ምርጫ የኦሮሞን ቋንቋ በንቃት መጠቀም፣ ባህልና አዎንታዊ ማኅበራዊ እሴቶችን ማስተዋወቅ እንዲሁም ለማኅበረሰቡ ዕድገት ገንቢ ተፅዕኖ መፍጠር በሚሉ ሦስት ዋና ዋና መስፈርቶች ላይ የተመሰረተ ነው።
የአሸናፊዎች አወሳሰን ሥርዓት 80 በመቶ በሕዝብ በቀጥታ ድምፅ የሚወሰን ሲሆን፣ ቀሪው 20 በመቶ ደግሞ ባህል፣ ታሪክና እሴት ሳይበረዝ በጥንቃቄ እንዲገመገም በታዋቂ ዳኞች የሚወሰን ተገልጿል።
ለአዋርዱ ከተለያዩ ዘርፎች የተመረጡት እጩዎች oiiaward.com ይፋዊ ድረ-ገጽ ላይ ቀርቧል። | 4 784 |
| 7 | ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል ገዳም ለጀመረው የልማት ፕሮጀክት ከ63 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማግኘቱን አስታወቀ!
#Fastmereja I የሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የገጠመውን መጠለያ የማጣት ችግር ለመቅረፍና ራሱን ለማስቻል በጀመረው የልማት ፕሮጀክት ገዳሙ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከስድስት ወራት ውስጥ ባከናወናቸው የገቢ ማሰባሰብ ሥራዎች፣ ከ63 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብና የዓይነት ድጋፍ ማግኘት መቻሉን በዛሬዉ እለት የአስተዳደሩ ተወካዮች ገልጸዋል።
በመግለጫው ላይ የካናዳ ሐገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብጹዕ አቡነ መርቆሪዮስ፣ የቤተክርስቲያን ሊቃውንትና ጥሪ የተደረገላቸው የሚዲያ ተቋማት ተገኝተዋል።
የገዳሙ አስተዳደር እንዳመለከተው፣ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዶክመንተሪዎችና በማኅበራዊ ሚዲያ አማካኝነት በተደረገው ሰፊ የገቢ ማሰባሰብ ጥረት፦52 ሚሊዮን 640 ሺህ ብር በጥሬ ገንዘብ፣11 ሚሊዮን 320 ሺህ ብር የሚገመት የዓይነት (የቁሳቁስ) ድጋፍ መሰብሰቡ ነዉ የተገለፀዉ።
ይህ የተገኘው ድጋፍ የልማት ፕሮጀክቱን የመጀመሪያና ሁለተኛ ምዕራፎች ከ65 በመቶ በላይ ለማሳካት ያስቻለ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የእናቶች በዓት (የመኖሪያ ክፍል) እና የእንግዳ ማረፊያ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ እናቶች አገልግሎት ማግኘት መጀመራቸው ተጠቅሷል።
ከ160 በላይ ገዳማውያን የሚገኙበት ይህ አንድነት ገዳም፣ ከተፈጥሮአዊና ሰው ሠራሽ ችግሮች ጋር ተያይዞ ገዳማውያኑ ከብርድና ከዝናብ የሚከላከል መጠለያ አጥተው በከፍተኛ ችግር ውስጥ ይገኙ እንደነበር በመግለጫው ላይ ተስቷል።
ይህንን የህልውና ፈተና በዘላቂነት ለመቅረፍ የተቀረጸው ይህ ፕሮጀክት፤ በጠቅላይ ቤተ-ክህነት ዕውቅና፣ በሐገረ ስብከቱ ፈቃድ እንዲሁም በሊቃነ ጳጳሳት የቅርብ ክትትልና ቡራኬ ከወረዳ ቤተ-ክህነት ጀምሮ በቅንጅት እየተመራ ይገኛል።
የገዳሙ አስተዳደር “ጾም የነፍስ ምግብ ነው፤ ለፈተናም መቋቋሚያ ጥንካሬን ይሰጣል” የሚለውን የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅን ኃይለ ቃል በመጥቀስ፣ በአሁኑ ወቅት ምዕመናን የሚገኙበት የሐዋርያት ጾም (የሰኔ ጾም) የበረከት ወቅት በመሆኑ፣ የተጀመረው የልማት ሥራ ሙሉ በሙሉ ፍጻሜ እንዲያገኝ ሕዝበ ክርስቲያኑ የጀመረውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል። | 4 083 |
| 8 | “ኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ሥራ ቢኖርም ሰራተኛ ማግኘት በጣም ከባድ ሆኗል” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
#FastMereja I ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ሥራ ቢኖርም ሰራተኛ ማግኘት በጣም ከባድ ሆኗል አሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፥ ወላጆች ከከተማ ውጪ የሚሰሩ ሥራዎችን ወጣቶች እንዲሞክሯቸው ማበረታታት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡
ለአብነትም በግንባታ ላይ በሚገኘው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በቂ የሰው ኃይል ማግኘት አዳጋች መሆኑን ነው ያስረዱት፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ የቤት ሰራተኝነት ሥራን የሚሰሩ ሰዎች ቁጥር እጅግ ጥቂት መሆኑን ጠቁመው፥ ለተመሳሳይ ሥራ ከሀገር የሚወጡ ዜጎች ቁጥር ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡
ከሀገር የወጡ ወጣቶች በቀን ለ16 ሰዓታት ያህል ሰርተው ራሳቸውን ሲለውጡ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ወጣቶች ግን ጊዜን በአግባቡ የመጠቀም ክፍተት እንዳለባቸው ነው የገለጹት፡፡
በሁለት እና ሶስት የሥራ ፈረቃዎች በመስራት አቅምን ማሳደግና መተጋገዝ ካልተቻለ የኑሮ ውድነት ከዚህ በላይ ሊሆን አንደሚችል አመልክተዋል፡፡
#ፖለቲካ | 4 231 |
| 9 | አዋሽ ኢንሹራንስ የ6.1 ቢሊዮን ብር አረቦን በመሰብሰብ የገበያ መሪነቱን አጠናከረ
#FastMereja I አዋሽ ኢንሹራንስ በ2018 በጀት ዓመት ከ6.1 ቢሊዮን ብር በላይ አጠቃላይ የአረቦን ገቢ (GWP) በመሰብሰብ የ35 በመቶ ከፍተኛ ዕድገት ማስመዝገቡንና በግሉ የመድን ዘርፍ የገበያ መሪነቱን በይፋ ማስቀጠሉን አስታወቀ። ኩባንያው በሁሉም ዋና ዋና የሥራ ዘርፎቹ ዓመታዊ ግቡን የተሻገረ ጠንካራ አፈጻጸም ያሳየ ሲሆን፣ በተለይም በሕይወትና ጤና እንዲሁም በተካፉል ኢንሹራንስ ዘርፎች በአገር አቀፍ ደረጃ ያለውን ቀዳሚ ሥፍራ አጠናክሮ መጓዙ ተገልጿል።
የኩባንያው የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ታደሰ ገመዳ ባስተላለፉት መልዕክት፣ የተመዘገበው አስደናቂ ውጤት ተቋሙ የተከተለው ጠንካራ ስትራቴጂ፣ በሳል አመራርና የሰው ኃይል ቁርጠኝነት ውጤት መሆኑን ገልጸዋል። ኩባንያው ያቀዳቸውን ግቦች በላቀ ሁኔታ ማሳካቱ ዓላማውን ወደ ተጨባጭ ውጤት የመቀየር አቅሙን እንደሚያሳይ የጠቆሙት ሰብሳቢው፣ ለዚህ ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱ ደንበኞችና ባለአክሲዮኖች ምስጋና አቅርበዋል።
የአዋሽ ኢንሹራንስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጅባት አለምነህ ፋጂ በበኩላቸው፣ ስኬቱ ከሠራተኞች፣ ደንበኞች፣ ባለአክሲዮኖች፣ የሽያጭ ወኪሎችና ብሮከሮች ጋር የተደረገ የጠንካራ ትብብር ፍሬ መሆኑን አብራርተዋል። በአዲሱ የሥራ ዓመት የገበያ መሪነቱን ይበልጥ ለማጠናከር በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የላቀ የደንበኛ አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት እንደሚሠራ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገልጸው፣ ኩባንያው ወደፊትም ተደራሽ የኢንሹራንስ አገልግሎቶችን በማቅረብ ለኢትዮጵያ የመድን ዘርፍ ዕድገት የበኩሉን አስተዋጽኦ ማበርከቱን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
#ቢዝነስ ዘገባ | 4 747 |
| 10 | የሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ሊጀመር ነው፡ ኮሚሽኑ የ4 ሺህ ተወካዮችን ዝግጅት አጠናቀቀ
#FastMereja I የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለቀጣዮች አራት ሳምንታት በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል። በጉባዔው ላይ ከወረዳ፣ ከክልል፣ ከፌዴራልና ከስደት ዓለም የተወጣጡ 4,000 ተወካዮች የሚሳተፉ ሲሆን፣ ለዚህም ይረዳ ዘንድ የመስተንግዶ፣ የትራንስፖርትና የጸጥታ ቅድመ ዝግጅቶች ሙሉ በሙሉ መጠናቀቃቸውን ኮሚሽኑ አረጋግጧል።
ይህ ግዙፍና ታሪካዊ ጉባዔ በዋናነት በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል የሚካሄድ ሲሆን፣ ማዕከሉ ለተሳታፊዎች ምቹና ደህንነቱ የተጠበቀ እንዲሆን ተደርጎ ተዘጋጅቷል። በተለይም እናቶችና ሴት ተሳታፊዎችን ከግምት ውስጥ በማስገባት የሕፃናት ማቆያ ስፍራዎች በባለሙያ የተደራጁ ሲሆን፣ ለአካል ጉዳተኞችና ልዩ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖችም ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል። ተሳታፊዎች ቆይታቸውን በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ እና በፌደራል ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ግቢዎች ውስጥ እንደሚያደርጉ የተገለጸ ሲሆን፣ ባህልንና ማህበራዊ ደረጃን ያገናዘበ የምግብ፣ የንጽህናና የሕክምና አገልግሎት በጊዜያዊ ክሊኒኮች ጭምር እንደሚቀርብ ተገልጿል።
የትራንስፖርትና የጸጥታ ጉዳይን በተመለከተም ኮሚሽኑ ከፌደራልና ከክልል የጸጥታ አካላት እንዲሁም ከትራንስፖርት ሚኒስቴር ጋር የተቀናጀ ዝግጅት ማድረጉን አስታውቋል። ተሳታፊዎች ከየአካባቢያቸው ወደ አዲስ አበባ የሚገቡበት የአየርና የየብስ አማራጮች የተመቻቹ ሲሆን፣ በከተማው ውስጥም የትራንስፖርትና የቋንቋ እገዛ የሚያደርጉ በጎ ፈቃደኞች ተሰማርተዋል።
ኮሚሽኑ ተሳታፊዎች እስከ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ አዲስ አበባ በመግባት ሪፖርት እንዲያደርጉ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን፣ በአንዳንድ የግልና የመንግሥት ተቋማት ውስጥ ያሉ ተወካዮች የፈቃድ ችግር እየገጠማቸው መሆኑን ጠቁሟል።
በማቋቋሚያ አዋጁ ቁጥር 1265/2014 አንቀጽ 41 መሠረት ማንኛውም ተቋም ለኮሚሽኑ ሥራ ትብብር የማድረግ ግዴታ እንዳለበት በማሳሰብ፣ ተሳታፊዎች ያለምንም እንግልት በጉባዔው ላይ እንዲገኙ አስፈላጊው ትብብር እንዲደረግላቸው በጥብቅ አሳስቧል። ኮሚሽኑ እስካሁን ከ1300 በላይ ወረዳዎችን በማሻገር ከመቶ በላይ የማህበረሰብ ክፍሎችን ያካተቱ በርካታ አጀንዳዎችን መሰብሰቡን ገልጾ፣ ጉባዔው ስኬታማ እንዲሆን መላው ሕዝብ በጸሎትና በንቃት እንዲከታተል ጠይቋል። | 4 377 |
| 11 | የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የሀብት ማሰባሰቢያ ንቅናቄ በይፋ ጀመረ!
#Fastmereja:- የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና የሥራ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ ተቋማዊ አቅማቸውን ለማሳደግና ዘላቂ የልማት ፕሮጀክቶችን ለመተግበር ያለመ ታሪካዊ የሀብት ማሰባሰቢያ ንቅናቄ በይፋ መጀመራቸውን አስታወቁ።
ንቅናቄው ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ኤሊያና ሆቴል በተካሄደ ደማቅ መርሐ ግብር የተበሰረ ሲሆን፣ በሥነ ሥርዓቱ ላይ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የገዳሙ ፍሬዎች፣ የሃይማኖት ማኅበራት ተወካዮች፣ ምዕመናንና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ይህ አገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ንቅናቄ በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ የገዳሙን ተማሪዎች፣ ወዳጆችና በጎ ፈቃደኞችን በአንድ ራዕይ በማሰባሰብ የገዳሙን የትምህርትና የማኅበራዊ አገልግሎት ሥራዎች ለማስፋፋት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
በዚህ ንቅናቄ አማካኝነት ተግባራዊ የሚደረጉ ዋና ዋና ፕሮጀክቶች ይፋ የተደረጉ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በዲፕሎማ ደረጃ ትምህርት እየሰጠ የሚገኘውን የመንፈሳዊ ሥራ አመራር ኮሌጅ ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ ማሳደግ ዋነኛው መሆኑ ተጠቅሷል።
ከዚህ በተጨማሪም የካህናትና የሰባኪያን ሥልጠናን በኦሮምኛ፣ በሌሎች የአገር ውስጥ ቋንቋዎችና በእንግሊዝኛ መስጠት፣ ወላጅ ያጡ ሕፃናትን የመቀበል አቅምን ማሳደግ፣ እንዲሁም የአገልግሎትና የፋይናንስ ተቋሙን በዘላቂነት ለመደገፍ በአዲስ አበባ ከተማ ቋሚ የገቢ ምንጭ የሚሆን ዘመናዊ ሁለገብ ሕንፃ (Mixed-Use Building) መገንባት የሚሉት ይገኙበታል።
የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ ባስቆጠረው አገልግሎቱ፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ውስጥ መንፈሳዊ ብቃትና አመራርን ያጣመሩ መሪዎችን በማፍራት የሚታወቅ አንጋፋ ማዕከል ነው።
ከተቋሙ የፈሩ ከ17 በላይ ሊቃነ ጳጳሳት፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ከፍተኛ ኃላፊዎችና የወንጌል አገልግሎት መሪዎች በአሁኑ ወቅት በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት በብቃት በማገልገል ላይ እንደሚገኙ ተመላክቷል።
የገዳሙ ታሪክ እንደሚያስረዳው፣ ተቋሙ በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ መሪነት የተማረው ትውልድና የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ወደ ቤተክርስቲያን እንዲመጡ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ሚና የተጫወተ ሲሆን፣ ይህ እንቅስቃሴ በቀጣይ ለማኅበረ ቅዱሳን መመሥረት መሠረት የጣለ እንደሆነም የተገለፀዉ።
ገዳሙ ይህንን ትውልድ ተሻጋሪና ዘላቂ በጎ ቅርስ ለማንጽ የተጀመረውን የልማት ፕሮጀክት በገንዘብ፣ በእውቀትና በሙያ ይደግፉ ዘንድ ለሁሉም የገዳሙ ፍሬዎች፣ ምዕመናን፣ ባለሀብቶችና የልማት አጋሮች የከበረ ጥሪ የተላለፈ ሲሆን ይህ በተለያዩ መርሐ ግብሮች የተዋቀረው የሀብት ማሰባሰቢያ ንቅናቄ እስከ መጪው ታኅሣሥ 19 ቀን 2019 ዓ.ም. ድረስ በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥል ተገልጿል። | 4 629 |
| 12 | የትግራይ ትምህርት ቢሮ የራሱን ፈተና አዘጋጅቶ ተማሪዎችን ሊፈትን መሆኑን አስታወቀ
#FastMereja I ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም.
የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ በትምህርት ሚኒስቴር ውሳኔ ባለመስማማት በራሱ አሠራር በአጭር ጊዜ ውስጥ ፈተና አውጥቶ ተማሪዎችን ሊፈትን መሆኑን የቢሮው ኃላፊ ዶክተር ኪሮስ ጉዕሽ ገለጹ።
ዶክተር ኪሮስ ጉዕሽ ይህንን የገለጹት የ2018 ዓ.ም. የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መውጫ ፈተና አሰጣጥን አስመልክቶ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ነው። እንደ ኃላፊው ማብራሪያ፣ በክልሉ በወረቀት ፈተና ለመውሰድ ተመዝግበው ዝግጅት ሲያደርጉ የቆዩ 15 ሺህ 349 ተፈታኝ ተማሪዎች ከሐምሌ 1 ቀን ጀምሮ ፈተናቸውን እንዲወስዱ ዕቅድ ተይዞ የነበረ ቢሆንም፣ የፌደራል ትምህርት ሚኒስቴር ግን እስካሁን ድረስ የፈተና ወረቀቶችን ወደ ክልሉ አላከም። ፈተናው በአውሮፕላን ተጓጉዞ በፌደራል ፖሊስ ጥበቃ የሚደረግለት በመሆኑ፣ በአሁኑ ወቅት የፈተና ወረቀቱን ወደ ትግራይ ክልል ላለመላክ ምንም ዓይነት አሳማኝ ምክንያት የለም ሲሉ ኃላፊው ወቅሰዋል።
የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ካቢኔ ለችግሩ እልባት እንዲሰጥበት ለትምህርት ሚኒስቴር ደብዳቤ ቢልክም እስካሁን ይፋዊ ምላሽ አላገኘም። ሐምሌ 1 ቀን ለሚጀምረው ፈተና ተማሪዎች በሰኔ 29 ቀን ወደየዩኒቨርሲቲዎቹ መግባት የነበረባቸው ቢሆንም፣ በትምህርት ሚኒስቴር ምክንያት በመቅረቱ ተማሪዎች ጉዟቸውን እንዲያቋርጡ ተደርጓል። በትምህርት ሚኒስቴር የተላለፈው ይህ ውሳኔ የፖለቲካ ውሳኔና የጦርነቱ ቀጣይ አካል በመሆኑ ተቀባይነት የለውም ያሉት ዶክተር ኪሮስ፣ በትግራይ ክልል በኦንላይን (በኢንተርኔት) እና በወረቀት ሳይፈተኑ የቀሩ በአጠቃላይ 29 ሺህ 755 ተማሪዎችን ክልሉ የራሱን ፈተና በአጭር ጊዜ ውስጥ አዘጋጅቶ እንደሚፈትን አስታውቀዋል።
በመጨረሻም የትግራይ ክልላዊ መንግሥት የራሱን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ወስኖ ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንደሚያስገባ የገለጹት ኃላፊው፣ ፈተናው የሚሰጥበት ትክክለኛ ጊዜ ወደፊት ይፋ እንደሚደረግና ተማሪዎች ይህንን አውቀው ዝግጅታቸውን እንዲቀጥሉ አሳስበዋል። | 4 855 |
| 13 | መርጌታ ነን በማለት 827 ሺህ ብር ያጭበረበሩት ወንድማማቾች በቁጥጥር ሥር ዋሉ
#FastMereja I ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም.
በምስራቅ ጎጃም ዞን ሉማሜ ከተማ “መርጌታ ስመኘው የባህል መድኃኒት” በሚል የሐሰት ስም በመጠቀም፣ ከአንድ የአርባ ምንጭ ከተማ ነዋሪ ላይ 827 ሺህ ብር ያጭበረበሩ ስመኝ አባትነህ እና ያዛቸው አባትነህ የተባሉ ወንድማማቾች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የከተማዋ ፖሊስ አስታወቀ።
የሉማሜ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት አዛዥ ኢንስፔክተር በድሉ መልሰው እንደገለጹት፣ አካሉ መለሰ የተባለው ተበዳይ በቡና ንግድ ሥራ ላይ የተሰማራ ሲሆን፣ ቡና ያስረከበው ደንበኛ ገንዘቡን ሊመልስለት ባለመቻሉ ለችግር ተዳርጎ ነበር። ተጠርጣሪዎቹ ወንድማማቾች ይህንን አጋጣሚ በመጠቀምና የሐሰት ሰነድ በማዘጋጀት “መርጌታ ነን፤ ያልተመለሰልህን ገንዘብ በባህል መድኃኒትና በጸሎት እናስመልሳለን” በሚል ማታለል የጠቀሱትን ከፍተኛ ገንዘብ ተቀብለዋል።
ፖሊስ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ባደረገው ተከታታይ ክትትል በቁጥጥር ሥር ያዋላቸው ሲሆን፣ የተጭበረበረው 827 ሺህ ብር በከተማ አስተዳደሩ ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ጽህፈት ቤት በጊዜያዊነት በኤግዚቢትነት እንዲቀመጥ ተደርጓል። በአሁኑ ወቅት በአጭበርባሪዎቹ ላይ ሕጋዊና ተገቢው ቅጣት እንዲያገኙ የምርመራ መዝገብ ተደራጅቶ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል።
በሉማሜ ከተማ ተመሳሳይ የማጭበርበር ወንጀሎች እየተደጋገሙ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም 625 ሺህ ብር በሐሰት ያጭበረበረ ሌላ ግለሰብ በ2 ዓመት ከ9 ወር ፅኑ እስራት መቀጣቱ ይታወሳል። ማኅበረሰቡ በተለይም በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የሚለጠፉ መሰል የተጋነኑና የሐሰት ማስታወቂያዎችን በመለየት ራሱን ከትልቅ የገንዘብ ኪሳራና ማጭበርበር እንዲጠብቅ ፖሊስና የፋስት መረጃ ዝግጅት ክፍል መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
#ችሎት | 4 796 |
| 14 | “ስለ እናት” የበጎ አድራጎት ድርጅት ለ1,500 ህጻናት የትምህርት ቁሳቁስ ማሰባሰብ ጀመረ!
#Fastmereja I የዘንድሮው የአለም የአፍሪካ ህጻናት ቀን “በአፍሪካ ለሚገኙ ደህንነቱና ንፅህናው የተጠበቀ አካባቢ ለሁሉም ህፃናት” በሚል አህጉራዊ መሪ ቃል በአዲስ አበባ በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል።
“ስለ እናት” የበጎ አድራጎት ድርጅት (SECO) በዓሉን ምክንያት በማድረግ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ አቅመ-ደካማ ወላጆችን ለመደገፍና ህጻናትን ከትምህርት ማቋረጥ ለመታደግ ያለመ የ1,500 ህጻናት የክረምት የትምህርት ቁሳቁስ ማሰባሰብ ንቅናቄ በይፋ መጀመሩን አስታውቋል።
የድርጅቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ያሬድ አብዱ እንደገለፁት፣ ንጹህ የመጠጥ ውሃ ማግኘት፣ ጤናማና ንጹህ አካባቢ መፍጠር እንዲሁም መሰረታዊ የንጽህና ቁሳቁሶችን ማቅረብ ችሮታ ሳይሆን የማንኛውም ህጻን መሰረታዊ ሰብአዊ መብት መሆኑን አብራርተዋል።
አሁንም በአህጉሪቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ህጻናት በውሃ ወለድ በሽታዎች እየተጠቁና ሴት ህጻናት ደግሞ በቂ የንፅህና መጠበቂያ ባለመኖሩ ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው እየቀሩ መሆናቸውን የጠቀሱት ዋና ስራ አስኪያጁ፣ ማህበረሰቡ፣ መንግስታዊ አካላትና አለምአቀፍ አጋሮች ለWASH (የንጹህ ውሃ እና ንፅህና) ተደራሽነት መስፋፋት በጋራ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።
ድርጅቱ አሁን ላይ በአገሪቱ ካለው የኑሮ ውድነት አንጻር በርካታ አቅመ-ደካማ ወላጆች ለልጆቻቸው መሰረታዊ የትምህርት ቁሳቁሶችን ማሟላት ብርቱ ፈተና እንደሆነባቸው ገልጿል።
ይህንን ክፍተት ለመሙላትም በመጪው አዲስ የትምህርት ዘመን የኢኮኖሚ አቅም ማነስ የትምህርት እክል ሊሆንባቸው የሚችሉ 1,500 እና ከዚያ በላይ የሚሆኑ ህጻናትን በደብተር፣ በቦርሳና በሌሎች የትምህርት ቁሳቁሶች ለመደገፍ ዘመቻ መጀመሩን አስታውቆ፣ በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ በጎ አድራጊዎች በቁሳቁስም ሆነ በገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቋል።
በሌላ በኩል ድርጅቱ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ላለፉት ሩብ ክፍለ ዘመን (25 ዓመታት) በህጻናት ጥበቃ፣ በቤተሰብ መልሶ ማቋቋም እንዲሁም በሴት የቤት መሪዎች ኢኮኖሚያዊ አቅም ማጎልበት ረገድ በርካታ ስኬቶችን ማስመዝገቡን ገልጿል።
በመጪው ነሐሴ ወር የሚከበረውን የ25ኛ ዓመት የብር ኢዮቤልዩ በዓልን አስመልክቶ የድርጅቱን የህጻናት መቀበል አቅም በብዙ እጥፍ የሚያሳድግ የአዲስ ህንጻ ግንባታ የማስጀመሪያ መርሃ ግብርም አብሮ እንደሚከናወን ተገልጿል።
#ማህበራዊ | 4 346 |
| 15 | አራት ሽልማት የወሰደችው ተማሪ የምስራች ምትኩ በዲላ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ አዲስ ታሪክ ጻፈች
#FastMereja I በዲላ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የዘንድሮ የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ፣አንድ ስም ከመድረኩ ጎልቶ አስተጋባ—የምስራች ምትኩ በባችለር ዲግሪ መርሃ-ግብር ትምህርቷን የተከታተለችው ይህች ብርቱ ተማሪ፣ማንም ያልጠበቀውን እና በኮሌጁ ታሪክ እጅግ አነጋጋሪ የሆነ ደማቅ ድል አስመዝግባለች።
የምስራች ያስመዘገበችው ስኬት ተራ አልነበረም የአሸናፊዎች አሸናፊ የሚያሰኛትን አራት ታላላቅ የክብር ሽልማቶች በአንድ መድረክ ጠራርጋ ወስዳለች።
በዕለቱ የክብር ሞገስ የሆነችው የምስራች ከክፍሏ 1ኛ በመውጣት የመጀመሪያዋን የወርቅ ሜዳሊያ ተሸልማለች፣ከዲፓርትመንቷ 1ኛ በመሆን ልህቀቷን አጠናክራ ሁለተኛዋን የወርቅ ሜዳሊያ በአንገቷ ላይ አጥልቃለች፣ከአጠቃላይ የዲግሪ መርሃ-ግብሩ 1ኛ በመሆን ከሁሉም ተማሪዎች ልቃ በመገኘት የክብር ዋንጫን ወደ ላይ ከፍ አድርጋለች።
በመጨረሻ ከአጠቃላይ ሴት ተማሪዎች 1ኛ በመውጣት የሴቶችን አቅምና ጥንካሬ በተግባር በማስመስከር ሁለተኛዋን የክብር ዋንጫ በድል አነሳች።
ሁለት የወርቅ ሜዳሊያዎችን እና ሁለት የክብር ዋንጫዎችን በአንድ ጊዜ የወሰደችው የምስራች ለሌሎች ተማሪዎች በተለይም ለሴት እህቶቿ ትልቅ የብርታት ምንጭ እና ህያው አርአያ ሆና አልፋለች።ይህ አይነቱ የተደራረበ ስኬት በትምህርት ጥራትና በግል ጥረት የሚመጣ እንጂ በአጋጣሚ የሚገኝ አለመሆኑን የዕለቱ ታዳሚዎች በሞቀ ጭብጨባ መስክረውላታል።
ዘገባው፦ የዳራሮ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን ነው #ማህበራዊ | 4 894 |
| 16 | ከኢትዮጵያዊያን ወላጆች የተገኘው የካናዳ 20 ቁጥር ተጨዋች አሊ አህመድ
#FastMereja I በትውልድ ኢትዮጵያዊ ከሆኑት ቤተሰብ የተገኘው በአሁኑ ወቅት በካናዳ ፕሮፌሽናል እግር ኳስ ሊግ ውስጥ አስደናቂ ብቃቱን እያሳየ የሚገኘው ወጣቱ አማካይ አሊ አህመድ። ሁለቱም ወላጆቹ ከኢትዮጵያ ምሥራቃዊ ክፍል ሐረርጌ በዴሳ የተገኙት አሊ፣ በሰሜን አሜሪካ እግር ኳስ መድረክ ተስፋ ሰጪ ተጫዋች መሆኑን እያስመሰከረ ይገኛል።
በእግር ኳስ ስፖርት ታላቅ ተስፋ የተጣለበትና በአሁኑ ወቅት በሜዳ ላይ በሚያሳየው ቀልጣፋ እንቅስቃሴ ስሙ እየገነነ የመጣው አሊ አህመድ፣ የእግር ኳስ ህይወቱን የጀመረው ገና በስድስት ዓመት ዕድሜው በሰሜን ቶሮንቶ የስፖርት ክለብ (North Toronto SC) እንደነበር መረጃዎች ያመላክታሉ። ከወላጆቹ ከአቶ አፈንዲ እና ከወይዘሮ ሙና የተወለደው አሊ፣ እንግሊዝኛ እና አፋን ኦሮሞ ቋንቋዎችን አቀናጅቶ መናገር የሚችል ሲሆን፣ ከእግር ኳስ በተጨማሪ የቅርጫት ኳስ ጨዋታ ከፍተኛ ፍላጎት አለው።
አሊ አህመድ በታዋቂዎቹ የእግር ኳስ ኮከቦች ሊዮኔል ሜሲ እና ኤደን ሀዛርድ እንዲሁም በእንግሊዙ ቼልሲ ክለብ አጫዋች ዘይቤ ተጽዕኖ አድሮበታል። በቅርጫት ኳስ በኩል ደግሞ እንደ ኮቢ ብራያንት፣ ዴማር ዴሮዛን እና ስቴፍ ካሪ ያሉ የኤንቢኤ (NBA) ታላላቅ ተጫዋቾችን በአርአያነት እንደሚከተል ይነገራል። ይህ የተለያየ የስፖርት ፍቅርና ክህሎት በሜዳ ላይ ላለው የአስተሳሰብ ብስለትና የአካል ብቃት ጥንካሬ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳበረከተለት የስፖርት ተንታኞች ይገልጻሉ።
#ስፖርት ዘገባ | 5 388 |
| 17 | በጅማ ከተማ በከተማዋ በጀት የተገነቡ 300 የቁጠባ ቤቶች ለምረቃ ዝግጁ ሆነዋል። | 7 134 |
| 18 | ተሸንፋ የዓለምን ልብ ያሸነፈችው ኬፕ ቨርዴ 🇨🇻🌍🏆
የዓለም ዋንጫ በትልልቅ ሀገራት ስም ብቻ የሚደመቅ ሳይሆን፣ እንደ ኬፕ ቨርዴ ባሉ በትናንሽ ደሴቶች ስብስብ ግን ደግሞ ግዙፍ የአሸናፊነት መንፈስ ባላቸው ሀገራት ጭምር የሚዋብ ታላቅ መድረክ ነው።
በሕዝብ ቁጥር አነስተኛ የሆነችው ኬፕ ቨርዴ፣ በዓለም ዋንጫ ማጣሪያዎችና ውድድሮች ላይ ስሟን በደማቁ መጻፍ ችላለች። በትልልቅ ከዋክብት ለተሞሉ ብሔራዊ ቡድኖች ፈታኝ እና አስፈሪ ተጋጣሚ መሆኗን አስመስክራለች።
ሜዳ ላይ እስከ መጨረሻዋ ሰከንድ ድረስ የሚዋደቁት "ሰማያዊዎቹ ሻርኮች"፣ እግር ኳስ በገንዘብና በታሪክ ብቻ ሳይሆን በማይበገር ስሜት ጭምር እንደሚጫወቱ ለዓለም አሳይተዋል።
ምንም እንኳ በአርጀንቲና ተሸንፋ ውጤት ባይቀናትም ያሳየችው አስደናቂ ታክቲክና ፍፁም ስፖርታዊ ጨዋነት የዓለምን ስፖርት አፍቃሪ ቀልብ ለመግዛት አልከለከላትም። | 5 912 |
| 19 | ቴክኖ ኢትዮጵያ የሀገሪቱን ቱሪዝም በሞባይል ፎቶግራፍ ለማስተዋወቅ የ10 ቀናት የፎቶግራፍ ኤግዚቢሽን ከፈተ
#FastMereja I ቴክኖ ኢትዮጵያ የሀገሪቱን የቱሪዝም መስህቦች በሞባይል ፎቶግራፍ ጥበብ ለማስተዋወቅ ያለመ የ10 ቀናት የፎቶግራፍ ኤግዚቢሽን እና የማስተዋወቂያ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ በይፋ መጀመሩን አስታውቋል። ኩባንያው ከተለያዩ የመንግስት እና የግል ተቋማት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ይህ ኤግዚቢሽን፣ የሀገሪቱን የተፈጥሮ ውበት፣ ታሪካዊ ቅርሶች እና ባህላዊ እሴቶች የሚያሳዩ ከ100 በላይ በሞባይል ስልክ የተነሱ ድንቅ ፎቶግራፎችን ለዕይታ አብቅቷል።
በአዲስ አበባ ከተማ በተከናወነው የዚሁ ኤግዚቢሽን የመክፈቻ ስነ-ስርዓት ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ቴክኖ ኢትዮጵያ ይህንን ዝግጅት ያዘጋጀው ከአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን፣ ከቦርድ ሴልፎን አዲስ አበባ እንዲሁም ከህፃናትና ወጣቶች ቲያትርና ሲኒማ አዳራሽ ጋር በመተባበር መሆኑ ተገልጿል።
በኤግዚቢሽኑ ላይ የቀረቡት ምስሎች በሙሉ በኩባንያው የቅርብ ጊዜ ምርት በሆነው “TECNO CAMON 50 Pro” ስማርት ስልክ ብቻ የተነሱ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን፣ ይህም የሞባይል ስልኩን የፎቶግራፍ ጥራትና የቴክኖሎጂ ደረጃ ለማሳየት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተመልክቷል። ስልኩ 50 ሜጋ ፒክስል (50MP) የካሜራ ሲስተም እና AI ቴክኖሎጂዎችን ያካተተ እንደሆነም ተጠቁሟል።
የዚህ መርሃ ግብር ዋነኛ አካል የሆነው በቴክኖ ኢትዮጵያ፣ በአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን፣ በቪዚት አዲስ አበባ እና በህፃናትና ወጣቶች ቲያትርና ሲኒማ መካከል በጋራ ለመስራት ተስማምቷል። ይህ ስምምነት የቴክኖሎጂ፣ የፎቶግራፍ እና የፈጠራ ስራዎችን በመጠቀም የኢትዮጵያን የቱሪዝም መዳረሻዎች በአገር ውስጥና በአለም አቀፍ ደረጃ በጋራ ለማስተዋወቅ ያለመ እንደሆነ ስምምነቱን የፈረሙት አካላት አስታውቀዋል።
#ሳይ_ቴክ | 5 369 |
| 20 | በአርባ ምንጭ በ52 ሺህ ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው የኩሪፍቱ ሪዞርት እና ስፓ ተመረቀ
#FastMereja I በአርባ ምንጭ ከተማ በ52,000 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የተገነባው ዘመናዊው የኩሪፍቱ ሪዞርት እና ስፓ ዛሬ በይፋ ተመርቋል። ፕሮጀክቱ 53 ቅንጡ ቪላዎችን ያካተተ ነው። | 5 011 |
