FastMereja.com
📈 Аналитический обзор Telegram-канала FastMereja.com
Канал FastMereja.com (@fastmereja) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 49 437 подписчиков, занимая 3 574 место в категории Образование и 644 место в регионе Эфиопия.
📊 Показатели аудитории и динамика
С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 49 437 подписчиков.
Согласно последним данным от 14 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -739, а за последние 24 часа — -19, при этом общий охват остаётся высоким.
- Статус верификации: Не верифицирован
- Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 13.98%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 8.78% реакций от общего числа подписчиков.
- Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 6 914 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 4 343 просмотров.
- Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 34.
📝 Описание и контентная политика
Описание канала не предоставлено.
Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 15 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Образование.
Загрузка данных...
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 15 июня | 0 | |||
| 14 июня | 0 | |||
| 13 июня | 0 | |||
| 12 июня | 0 | |||
| 11 июня | 0 | |||
| 10 июня | 0 | |||
| 09 июня | 0 | |||
| 08 июня | 0 | |||
| 07 июня | 0 | |||
| 06 июня | 0 | |||
| 05 июня | 0 | |||
| 04 июня | 0 | |||
| 03 июня | 0 | |||
| 02 июня | 0 | |||
| 01 июня | +1 |
| 2 | ኢትዮጵያ የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ አስጀመረች
#FastMereja I ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ዛሬ በይፋ አስጀምረዋል። መንግስት በዘንድሮው የክረምት ወራት 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል እቅድ መያዙን ይፋ አድርጓል።
ይህ መርሃ-ግብር፣ ኢትዮጵያ በአምስት ዓመታት ውስጥ ለመትከል ካቀደችው 65 ቢሊዮን ችግኞች ግብ አንፃር የሚደረግ ወሳኝ አካል መሆኑ ተመላክቷል። አገሪቱ ባለፉት ዓመታት በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሚደርሰውን ተጽዕኖ ለመቀነስ እና የተፈጥሮ ሀብቷን ለመጠበቅ ዘመቻውን በስፋት እየተገበረች ትገኛለች።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባስተላለፉት መልእክት፣ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በሀገር አቀፍ ደረጃ በመሳተፍ ለቀጣዩ ትውልድ አረንጓዴ ዐሻራውን እንዲያኖር ጥሪ አቅርበዋል። መርሃ-ግብሩ የአካባቢ ጥበቃን ከማሻሻል ባሻገር፣ የኢኮኖሚ እና የብዝሃ-ህይወት ፋይዳ እንዳለው በመንግስት በኩል በተደጋጋሚ ሲገለጽ ቆይቷል። | 813 |
| 3 | 12 ዓመታት የፈጀው የድምፃዊት ፅላት ገዝሙ አልበም ሊወጣ ነው።
#FastMereja I ድምፃዊት ፅላት ገዝሙ ረጅም ዓመታትን የፈጀውን እና 10 ሙዚቃዎችን የያዘውን “ስኬት” የተሰኘ አዲስ አልበሟን ሰኔ 12/2018 ዓ.ም ለህዝብ ይፋ እንደምታደርግ አስታወቀች።
አልበሙ በዕለቱ በራሷ የዩቲዩብ ቻናል እና በዞጃክ ዎርልድ ዋይድ (Zojak Worldwide) አማካኝነት በመላው ዓለም በአንድነት ይለቀቃል።
አርቲስቷ ለአልበሙ መውጣት ከ12 ዓመታት በላይ ዝግጅት ስታደርግ የቆየች ሲሆን፣ በውስጡም የተካተቱት 10 ስራዎች የጥበብ አስተዋጽኦዋን ወደ ሌላ ከፍታ የሚያሳድጉ እንደሆኑ ተገልጿል።
በተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ቋንቋዎች በመዝፈን ተወዳጅነትን ያተረፈችው ፅላት፣ የ2018 ዓ.ም የኦዳ አዋርድ አሸናፊ መሆኗ ይታወቃል። | 2 246 |
| 4 | 14ኛው ሀገራዊ እና የመጀመሪያው የምስራቅ አፍሪካ የአንቲማይክሮቢያል ግንዛቤ ቀን ተከበረ!
#Fastmereja: የፀረ-ተህዋስያን መድኃኒቶች መላመድ ወይም መቋቋም (AMR) እያደረሰ ያለው ዘርፈ-ብዙ ጉዳት በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍም ሆነ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሰው፣ በእንስሳትና በአካባቢ ጤና እንዲሁም በኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ስጋት መደቀኑ ተገለፀ።
ይህ የተገለጸው በአገር አቀፍ ደረጃ ለ14ኛ ጊዜ፣ በምስራቅ አፍሪካ ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ የተከበረውን ብሔራዊ የአንቲማይክሮቢያል ግንዛቤ ቀንን አስመልክቶ በተዘጋጀው ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ መድረክ ላይ ነው።
የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሪት ሄራን ገርባ እንደገለፁት በአሁኑ ወቅት በዓለም ላይ በየዓመቱ ከ750 ሺህ በላይ ሰዎች በዚህ ችግር ሳቢያ ሕይወታቸውን እንደሚያጡ የተገለፀ ሲሆን አፋጣኝ እርምጃ ካልተወሰደ ግን እ.ኤ.አ በ2050 የሟቾች ቁጥር ወደ 10 ሚሊዮን ሊጠጋ እንደሚችልና በዓለም ኢኮኖሚ ላይም እስከ 10 ትሪሊዮን ዶላር (ከ2% እስከ 3%) ኪሳራ ሊያደርስ እንደሚችል እና ይህ የኢኮኖሚ ኪሳራ በተለይ በታዳጊ አገራት ላይ ከ5% በላይ ሊበልጥ እንደሚችል ተነግሯል።
በኢትዮጵያ አሁንም ተላላፊ በሽታዎች ከፍተኛውን ቁጥር ይዘው እንደሚገኙ የተገለፀ ሲሆን፣ ጀርሞች መድኃኒቶችን የመቋቋም አቅም እንዲያዳብሩ የሚያደርጉ ዋና ዋና መንስኤዎች የታዘዘን መድኃኒት ሳይጨርሱ ማቋረጥ፣የመውሰጃ ሰዓትን ማዛባት፣ያለሀኪም ትዕዛዝ መድኃኒት ገዝቶ መውሰድ፣እና የሌላ ሰውን መድኃኒት “ያድናል” በሚል እሳቤ መውሰድ ዋነኞቹ መሆናቸው ተጠቅሷል።
ይህ አሠራር በበሽታዎች የመዳን ዕድልን ከመቀነሱም በላይ የሆስፒታል ቆይታንና የሕክምና ወጪን በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረው እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ይህንን ችግር ለመከላከል ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመሆን ባለፉት ሁለት ዓመታት “ሀገር አቀፍ የማህበረሰብ ፋርማሲ አስገዳጅ ደረጃ መመሪያ” ያወጣ ሲሆን፣ የአምስት ዓመት ስትራቴጂካዊ ዕቅዱን ባለፈው ግንቦት 2026 ዓ.ም ከወጣው የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) የ10 ዓመት የAMR መከላከያ ዕቅድ ጋር የማስማማት ሥራ መሠራቱ ተረጋግጧል።
የኢትዮጵያ ፋርማሲስቶች ማኅበር (EPA) ከዩኬ የጤና ደኅንነት ኤጀንሲ (UKHSA)፣ ከዓለም አቀፍ የፋርማሲዩቲካል ፌዴሬሽን (FIP)፣ ከአፍሪካ ፋርማሲዩቲካል ፎረምና ከዩኒዶ (UNIDO) ጋር በመሆን የ”አንድ ጤና” (One Health) አካሄድን ለማጠናከር እየሠራ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ችግሩን ለመከላከል መላው ማኅበረሰብ፣ የጤና ባለሙያዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎችና በተለይም ሕዝብ ዘንድ የመድረስ ከፍተኛ አቅም ያላቸው መገናኛ ብዙኃን (ሚዲያዎች) የተቀናጀ ግንዛቤ በመፍጠር ረገድ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል። | 2 073 |
| 5 | ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዘገበ። | 3 876 |
| 6 | የጃፓን እግር ኳስ አፍቃሪዎች በዘንድሮው የአለም ዋንጫም በስነ-ምግባራቸው አለምን አስደመሙ
#FastMereja | በ2026 የአለም ዋንጫ ጨዋታዎች እየታደሙ የሚገኙት የጃፓን ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎች፣ ጨዋታው ከተጠናቀቀ በኋላ በስታዲየም ውስጥ የሚገኙትን መጣያዎችን በማንሳትና አካባቢውን በማጽዳት ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታላቅ አርአያነትን እያሳዩ ይገኛሉ።
የጃፓን ደጋፊዎች ይህንን ተግባር በየጨዋታው በቋሚነት ማከናወናቸው፣ የሀገራቸውን ባህል እና ከፍተኛ ዲሲፕሊን የሚያንፀባርቅ ሆኖ ተገኝቷል። በስታዲየም ውስጥ የሚገኙ ሌሎች ሀገራት ደጋፊዎች እና ታዛቢዎች ይህንን የጃፓናውያንን ድርጊት በአድናቆት እየተመለከቱት ሲሆን፣ በስፖርታዊ ጨዋነት ጎን ለጎን የሚታይ የላቀ ማህበራዊ ስነ-ምግባር መሆኑን እየገለጹ ይገኛል።
ባለፈው የአለም ዋንጫ ውድድሮችም ተመሳሳይ ተግባር ሲፈጽሙ የነበሩት የጃፓን ደጋፊዎች፣ በዘንድሮው የውድድር ዘመን ድርጊቱን በይበልጥ በማጠናከር በሁሉም ስታዲየሞች ውስጥ የጽዳት ስራቸውን በመቀጠል ላይ ናቸው። ይህ ድርጊታቸው በሶሻል ሚዲያ መድረኮች ላይ ሰፊ አድናቆትን እያተረፈ ሲሆን፣ ለሌሎች ደጋፊዎችም የንጽህና አጠባበቅን መሰረት ያደረገ ትልቅ መልእክት አስተላልፏል። | 3 938 |
| 7 | የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) በሀገሬ ቲቪ ላይ ያቀረበውን የእግድ አቤቱታ ውድቅ አ
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) በሀገሬ ቲቪ ላይ ያቀረበውን የእግድ አቤቱታ ውድቅ አደረገ
#FastMereja | የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የንግድና ኢንቨስትመንት ችሎት፣ የ2026 የአለም ዋንጫ የእግር ኳስ ጨዋታዎችን በተመለከተ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) በሀገሬ ቲቪ ላይ አቅርቦት የነበረውን የእግድ ጥያቄ ውድቅ ማድረጉን ኢትዮጲካሊንክ ዘግበዋል።
ኢቢሲ ባለፈው ግንቦት 5 ቀን ባቀረበው የክስ ማመልከቻ፣ ተከሳሾች የቅጂ መብት በመጣስ እና ያልተገባ የንግድ ውድድር በመፈጸም የኮርፖሬሽኑን አጋር ድርጅቶች እንዳሳሳቱ ገልጾ ነበር። በዚህም የደረሰውን ጉዳት ለማካካስ ተከሳሾች 105 ሚሊዮን ብር እንዲከፍሉ ጠይቆ ነበር።
በግንቦት 25 ቀን በገባው ተጨማሪ አቤቱታ ደግሞ፣ የኢቢሲ ስፖርት መዝናኛ ቻናል ኃላፊ የነበሩት አቶ ንዋይ ይመር፣ የድርጅቱን ሚስጥር አሳልፈው በመስጠታቸው ሀገሬ ቲቪ የአለም ዋንጫውን ለማስተላለፍ መብት እንዳገኘ ክስ ቀርቦ ነበር። በዚሁ መነሻነት፣ ሀገሬ ቲቪ ጨዋታውን እንዳያስተላልፍ ከፍተኛው ፍርድ ቤት እግድ እንዲጥል ኢቢሲ ተማጽኖ ነበር።
በአንጻሩ ሀገሬ ቲቪ ሰኔ 1 ቀን ለፍርድ ቤቱ በሰጠው ምላሽ፣ የኢቢሲ ክስ ከባለቤትነት መብት ጋር እንደማይገናኝ በመጥቀስ ክሱ ውድቅ እንዲደረግ ጠይቋል። ሀገሬ ቲቪ ጨዋታውን ለማስተላለፍ የቻለው በራሱ ዝግጅት፣ የጋዜጠኞች ስልጠና እና መሰረታዊ የልማት ድጋፎችን በማከናወን መሆኑን በማስረዳት፣ እግዱ እንዲነሳ መከራከሪያውን አቅርቦ ነበር።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሁለቱንም ወገኖች የክርክር ነጥቦች በመመልከት፣ ሰኔ 3 ቀን ኢቢሲ ያቀረበውን የእግድ አቤቱታ በሙሉ ድምፅ ውድቅ አድርጎታል። | 3 624 |
| 8 | ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት አለፈ።
አደጋው የደረሰው ከደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች መካከል በሚገኘው የሐረጎ መንገድ ላይ ነው።
ዛሬ ሰኔ 08/10/18ዓ.ም ማለዳ ከደሴ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ የሕዝብ አውቶቡስ በተለምዶ ሐረጎ እየተባለ በሚጠራው መንገድ ላይ በደረሠበት አደጋ እስካሁን የ28 ሰው ሕይወት ሲያልፍ በርካቶች ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሶባተቸዋል።
የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪው በግምት 100 ሜትር ጥልቀት ወዳለው ገደል ገብቶ ነው አደጋው የደረሠው። በሕይወት የተረፉትን ወደ ሕክምና ቦታ ለማድረስ አሁንም ርብርብ እየተደረገ መኾኑን የገለጸው ፓሊስ የአደጋውን ምክንያት በመጣራት ላይ ነው ብሏል። | 3 439 |
| 9 | ሲናፕስ ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን አገር አቀፍ የኒውሮፋይናንስ ጉባኤ ሊያካሂድ ነው
#FastMereja I ሲናፕስ ኢትዮጵያ (Synapse Ethiopia) የሀገሪቱን የፋይናንስ ዘርፍ በዕውቀትና በቴክኖሎጂ ለማዘመን ያለመ “የ2026 አገር አቀፍ የኒውሮፋይናንስ ጉባኤ” (National NeuroFinance Summit Ethiopia 2026) ሰኔ 9 ቀን በአዲስ አበባ እንደሚያካሂድ አስታወቀ።
ይህ ታሪካዊ ጉባኤ በባንክ፣ በኢንሹራንስ፣ በካፒታል ገበያ እና በመንግስት አካላት ላይ የሚገኙ ከፍተኛ የሥራ መሪዎችንና ውሳኔ ሰጪዎችን በአንድ መድረክ ያገናኛል።
በዚህም የውሳኔ አሰጣጥ ጥራትን ለማሻሻል፣ የስጋት አስተዳደርን (risk management) ለማጠናከር እና የባህሪ ሳይንስን፣ የአዕምሮ ሳይንስን (Neuroscience) እንዲሁም አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን (AI) ከፋይናንስ ጋር የሚያገናኘውን “ኒውሮፋይናንስ” እውቀት በሀገሪቱ ማስተዋወቅ ያለመም ነው።
መድረኩን በኒውሮሳይንስ እና በAI ዘርፍ ዓለም አቀፍና አገር በቀል ልምድ ያላቸው ባለሙያዎች ይመሩታል ተብሏል።
የፋይናንስ ተቋማት መሪዎች የኒውሮፋይናንስን ምንነትና ፋይዳ ተረድተው በስራዎቻቸው ላይ እንዲተገብሩትም በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ጥሪ ቀርቧል።
በጉባኤውም የሚጠበቁ ጉዳዮችንም ;- የብሔራዊ ኒውሮፋይናንስ አስፈጻሚ ግንዛቤ ሪፖርት (NeuroFinance Executive Insights Report) ይዘጋጃል።
በዲጂታል እምነት፣ በባህሪ ተኮር ስጋት አስተዳደር እና በፋይናንስ ፈጠራ ላይ የፖሊሲና የኢንዱስትሪ ምክረ ሃሳቦች ይቀርባሉ።
በባንኮች፣ ኢንሹራንሶች፣ ተቆጣጣሪ አካላት እና ባለሀብቶች መካከል ጠንካራ የመሪዎች ትስስር ይፈጠራል።
በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የኒውሮፋይናንስ ማህበረሰብ (National NeuroFinance Community) ይመሰረታል።
ሲናፕስ ኢትዮጵያ በኒውሮሳይንስ፣ በባህሪ ሳይንስ፣ በስትራቴጂክ አማካሪነት እና በመሪነት ልማት ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰራ ድርጅት ሲሆን፣ ይህ ጉባኤ በኢትዮጵያ የፋይናንስ ሥርዓት ላይ አዲስ የዕድገት ምዕራፍ ለመክፈት የተዘጋጀ ነው። | 4 208 |
| 10 | በአማራጭ የህፃናት እንክብካቤ ላደጉ ወጣቶች የተዘጋጀዉ የመጀመሪያው የስፖርት ፌስቲቫል ተጠናቀቀ!
#Fastmereja I በአማራጭ የህፃናት እንክብካቤና ማሳደጊያ ተቋማት ውስጥ አድገው ለወጡ ወጣቶች የተዘጋጀው እና ላለፉት ሁለት ሳምንታት ሲካሄድ የቆየው የመጀመሪያው የስፖርት ፌስቲቫል የፍፃሜ ውድድር በዛሬዉ እለት በአዲስ አበባ በድምቀት ተጠናቋል።
ይህ የስፖርት ፌስቲቫል የተዘጋጀው ወጣቶቹ ከነበሩባቸው የማሳደጊያ ተቋማት ከወጡ በኋላ የሚገጥሟቸውን ዘርፈ-ብዙ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተግዳሮቶች በጋራ ለመጋፈጥ ባቋቋሙት ብሔራዊ ጥምረት አማካኝነት ሲሆን፣ መርሃ-ግብሩም በዴንማርክ መንግስት የሚደገፈዉ የ”Leave No Youth Behind” (ማንንም ወጣት ወደኋላ አንተዉም) ፕሮጀክት አካል መሆኑ ታዉቋል።
የብሔራዊ አማራጭ የህፃናት እንክብካቤ አድገው የወጡ ወጣቶች ማህበር ጥምረት የሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ሀላፊ አቶ ምስክር ታደሰ እንደገለጹት፤ የዚህ ስፖርታዊ ውድድር ዋና ዓላማ ወጣቶቹ እርስ በርስ እንዲገናኙ፣ ጤናቸውን እንዲጠብቁ እና ትስስራቸውን ይበልጥ እንዲያጠናክሩ ለማድረግ መሆኑን ገልፀዋል።
በተጨማሪም ወጣቶች ከማሳደጊያ ተቋማት ከወጡ በኋላ የሚያጋጥሟቸውን እንደ ስራ አጥነት እና የመኖሪያ ቤት ችግር ያሉ ፈተናዎችን በጋራ ለመፍታት እንዲሁም ወጣቶቹ እርስ በርስ ጠንካራ ትስስር(Network) እንዲፈጥሩ እና ወደፊት በጋራ ለሚቆሙላቸው መብቶች፣ የፖሊሲ ተፅዕኖ ማሳደርን ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ለመምከር ትልቅ መድረክ መፍጠሩን አቶ ምስክር አክለው አብራርተዋል።
በወንዶች የእግር ኳስ እና በሴቶች የመረብ ኳስ (ቮሊቦል) ውድድሮች በተካሄዱበት በዚህ ፌስቲቫል ላይ በርካታ የወጣቶች ማህበራት የተሳተፉ ሲሆን፤ የዓለም አካባቢ ጥበቃ ቀንን በማስመልከትም በዕለቱ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ተከናውኗል።
በፌስቲቫሉ ላይ የኤስ ኦ ኤስ (SOS) ህፃናት መንደር ወጣቶችን ያቀፈው “አልሙናይ ዩዝ አሶሴሽን’፣ የሰላም የህፃናት መንደር ወጣቶች ማህበር(ሰላም ፍሩትስ)፣ እንዲሁም እንደ ኮልፌ፣ ክበበ ፀሀይ እና ቀጨኔ ካሉ የመንግስት ማሳደጊያ ተቋማት የወጡ ወጣቶች የመሰረቱት “ፎር ኬ ኬር ሊቨርስ ቻሪቲ አሶሴሽን’ የተሳተፉ ሲሆን፤ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ደግሞ በክብር ተጋባዥነት ተገኝቷል።
በኢትዮጵያ የኤስ ኦ ኤስ (SOS) ህጻናት መንደሮች የአዲስ አበባ እና ዙሪያዋ ፕሮግራሞች ዳይሬክተር አቶ አለም ጌታቸው በበኩላቸው፤ ተቋማቸው ለዚህ የወጣቶች ጥምረት መመስረትና ለፌስቲቫሉ መሳካት የፋይናንስ እንዲሁም የቴክኒክ ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል።
ድጋፉ በዴንማርክ መንግስት የገንዘብ እገዛ በሚተገበረው ሊቭ ኖ ዩዝ ቢሀይንድ(Leave No Youth Behind) ፕሮጀክት አማካኝነት የተደረገ ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም ወጣቶቹ ተነቃቅተው ለራሳቸው መብት እንዲቆሙና የፖሊሲ ተፅዕኖ መፍጠር እንዲችሉ ማገዝ እንደሆነ አስረድተዋል።
በመሆኑም ይህንን መሰል የስፖርት መርሃ-ግብሮችን በየወሩ እንዲያካሂዱ፣ በፌስቲቫል ደረጃ ደግሞ በየስድስት ወሩ ወይም ባልተቻለ ሁኔታ በዓመት አንድ ጊዜ በቋሚነት እንዲያዘጋጁ ተቋማቸው ሁለንተናዊ እገዛ ማድረጉን እንደሚቀጥልበት አረጋግጠዋል። | 3 892 |
| 11 | በቆጂ ከተማ የ2018 ኢትዮ ቴሌኮም ታላቁ ሩጫን በስኬት አጠናቀቀች
#FastMereja I ለአምስተኛ ጊዜ የተካሄደውን 12 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን የ2018 ኢትዮ ቴሌኮም ታላቁ የቦቆጂ ሩጫ በስኬት ተጠናቀቀ።
በቦቆጂ ስታድየም መነሻና መድረሻውን ባደረገው የዛሬው ውድድር በወንዶች የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን አትሌት የሆነው ማሞ ሐጫሉ ቀዳሚ ሲሆን፣ አማን ቃዲ እና አልዬ ቃሲም 2ኛ እና 3ኛ ደረጃን ይዘዋል። በሴቶች ደግሞ የአሰላ አትሌቲክስ ክለብ ተወዳዳሪዋ ማህሌት ካሳሁን ስታሸንፍ፣ ኪያ ፍስሃ እና ድርቤ ኢርኮ ተከታትለው በመግባት የ2ኛ እና 3ኛ ደረጃን ተቆጣጥረዋል።
የ’ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ’ ተከታታይ ውድድር አካል በሆነው በዚህ መርሃ ግብር ላይ የ15 ዓመት በታች የታዳጊዎች ሻምፕዮናም የተካሄደ ሲሆን፣ በተጨማሪም የ11 ዓመት በታች እና የህጻናት ውድድሮች ተካሂደዋል።
ከ2500 በላይ የአካባቢው ነዋሪዎች እና ከአዲስ አበባ የተጓዙ ከ70 በላይ ሯጮች የተሳተፉበት ይህ ውድድር በአርሲ አባቶች ምርቃት እና በብሔራዊ መዝሙር ተጀምሯል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ አቶ መኪዩ ሙሐመድ፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) እና የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሮዛ ቢያ፣ የአርሲ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሂም ከድር እና የቦቆጂ ከተማ ከንቲባን ብርሃነ ነገሰ ጨምሮ በርካታ የመንግስት ከፍተኛ ኃላፊዎች በቦታው ተገኝተዋል። | 3 947 |
| 12 | ኢትዮጵያዊው የቴክኖሎጂ ስራ ፈጣሪ በሰፊቃድ ጌታቸው በአፍሪካ ምርጥ 100 የንግድ ጀግኖች ዝርዝር ውስጥ ተካተቱ
#FastMereja | የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኩባንያ የሆነው “ኢግል ላይን ሲስተም ቴክኖሎጂ” መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ በሰፊቃድ ጌታቸው፣ በ2026ቱ “አፍሪካ ቢዝነስ ሄሮውስ” (ABH) ውድድር ከመላው አፍሪካ ከተውጣጡ ከ24 ሺህ በላይ ተወዳዳሪዎች መካከል በማለፍ፣ በምርጥ 100 የንግድ ጀግኖች ዝርዝር ውስጥ መካተታቸው ተገለጸ።
በሰፊቃድ ጌታቸው የሚመራው “ኢግል ላይን ሲስተም ቴክኖሎጂ” በተለይም በፋይናንስ፣ በግብርና፣ በዲጂታል ክፍያ እና በቱሪዝም ዘርፎች ከሁለት ደርዘን በላይ የቴክኖሎጂ መፍትሄዎችን በማዘጋጀት ይታወቃል። በዘርፉ ካበረከቷቸው ፈጠራዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ከአንድ ሚሊየን ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የግብርና ግብዓት ግዥን ያቀለለው የ”ጌትፊ ኢንተርፕራይዝ” (GetFee Enterprise) የክፍያ ስብስብ መድረክ እና የዳሽን ባንክ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ዋነኞቹ ናቸው።
በተጨማሪም እንደ “ካሽ ጎ” (CashGo)፣ “ኢትዮ-ዳይሬክት ኮኔክት” (Ethio-Direct Connect) እና የ”ዱቤ አለ” (DubeAle) የክፍያ መድረክ የመሳሰሉ ፈጠራዎች በኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስ ስነ-ምህዳር ውስጥ ያላቸውን ተፅእኖ አሳይተዋል። ከእነዚህም ባሻገር ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ ማሰባሰቢያ የሆነውን “ItsMyDam.com” መድረክ በማልማትም ይታወቃሉ።
የአፍሪካ ቢዝነስ ሄሮውስ (ABH) ተነሳሽነት በ2018 ዓ.ም. በአሊባባ መስራች ጃክ ማ የተጀመረ ሲሆን፣ ዓላማውም በየአመቱ በአህጉሪቱ አስር ምርጥ ስራ ፈጣሪዎችን በመለየት የገንዘብ ድጋፍ፣ ስልጠና እና የአማካሪነት አገልግሎት መስጠት ነው። ለዘንድሮው የውድድር ዘመን በአጠቃላይ 1.5 ሚሊዮን ዶላር የሽልማት በጀት ተይዞለታል።
የሰፊቃድ ጌታቸው በምርጥ 100 ዝርዝር ውስጥ መካተት፣ ኢትዮጵያውያን ስራ ፈጣሪዎች በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላቸውን አቅም በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማሳየትና አህጉራዊ ተወዳዳሪነትን ለመቀዳጀት እንደ ትልቅ ምዕራፍ ተወስዷል። ቀደም ሲል ከነበሩት ዓመታት አንጻር፣ በውድድሩ የኢትዮጵያውያን ተሳትፎ እየጨመረ መምጣቱን መረጃዎች ይጠቁማሉ። | 4 204 |
| 13 | ጀግናዋ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የረዳት ኮሚሽነርነት ማዕረግ አገኘች
#FastMereja I የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የስፖርት ክለብ እንዲሁም የሙዚቃና ቴአትር ቡድን የተመሠረተበት 40ኛ ዓመት ክብረ በዓል በአድዋ ድል መታሰቢያ በድምቀት ተከብሯል።
በዚሁ መድረክ ላይ በኦሎምፒክና በዓለም ሻምፒዮና ውድድሮች በርካታ ሜዳሊያዎችን በማምጣት የሀገርን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ ላደረገችው ጀግናዋ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የተቋሙ ከፍተኛ የዕድገት እርከን የሆነው የረዳት ኮሚሽነርነት ማዕረግ ተሰጥቷታል።
በዕለቱም ለረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ፣ ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን፣ ለኮማንደር ፋጡማ ሮባ፣ ለኮማንደር አትሌት ሰለሞን ባረጋ እና ለምክትል ኮማንደር ሰንበሬ ተፈሪ የዕውቅናና ሽልማት ፕሮግራም ተካሂዷል።
በተጨማሪም በአሰልጣኝነት ከ30 ዓመታት በላይ በማገልገል የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱት ረዳት ኮሚሽነር ሁሴን ሸቦ የኒሻን ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን፤ በኪነ-ጥበቡ ዘርፍ ለሀገር ትልቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የሙዚቃና ቴአትር ቡድኑ አባላትም ዕውቅና ተሰጥቷል።
በክብረ በዓሉ ላይ የተገኙት የፍትሕ ሚኒስትር ሐና አርዓያሥላሴ የኮሚሽኑ የስፖርት ክለብ ባለፉት 40 ዓመታት እውቅ ጀግኖችን በማፍራት በኩል የላቀ ሚና መጫወቱን ጠቅሰው፤ ተቋሙ ይህንኑ አበረታች ሥራውን ይበልጥ ዘመናዊ በማድረግ አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል። | 4 171 |
| 14 | ከሽያጭ በኋላ የጥገና አገልግሎት የያዘው «ቴክ ኢዚ» ማዕከል ስራ ጀመረ!
#Fastmereja I በኢትዮጵያ የኤሌክትሮኒክስ ገበያ ውስጥ ሸማቶች የተለያዩ ብራንዶችን በአንድ ቦታ እንዲያገኙ ለማስቻል «ቴክ ኢዚ» (TekEasy) የተሰኘው የኤሌክትሮኒክስ መሸጫ ማዕከል የመጀመሪያውን ቅርንጫፍ በይፋ አስመርቋል።
ማዕከሉ እንደ ቴክኖ፣ አፕል፣ ሚዲያ እና ኢንፊኒክስ ያሉ ታዋቂ ዓለም አቀፍና የሀገር ውስጥ የኤሌክትሮኒክስ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንደሚያቀርብ ተገልጿል።
ኩባንያው በአዲስ አበባ የጀመረውን ይህንን የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንት በቀጣይ ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ዋና ዋና ከተሞች የማስፋፋት ዕቅድ እንዳለው አስታውቋል።
ይህ ማዕከል ከተለመደው የሽያጭ አሰራር በተለየ መልኩ ከሽያጭ በኋላ በሚሰጥ አገልግሎት የያዘ ሲሆን ዕቃዎችን ደንበኞች እስከሚፈልጉበት ቦታ ድረስ የሚያደርስ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሁም የቴክኒክ ብልሽቶች በሚያጋጥሙበት ወቅትም ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ የጥገና ማዕከልና የባለሙያ ቡድን የተደራጀ ስለመሆኑም ነዉ የተገለፀዉ።
ይህ አዲስ ማዕከል በኢትዮጵያ በፍጥነት እያደገ የመጣውን የዲጂታል ኑሮ ዘይቤ በማገዝና ለሸማቾች አስተማማኝ አማራጭ በመሆን ረገድ የራሱን አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወት ይጠበቃል። | 4 910 |
| 15 | የአሜሪካዋ ግዛት ምክር ቤት ለአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን ሰየመ
#FastMereja I በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ ‘መጋቢት 2’ በግዛቱ የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን እንዲሆን የቀረበን የውሳኔ ሐሳብ በከፍተኛ ድምጽ አፀደቀ።
ይህ ‘ኤችአር 441’ የተሰኘው የውሳኔ ሐሳብ የፀደቀው ባለፈው ሳምንት በግዛቲቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተደረገ የድምጽ አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት ነው።
በአሜሪካ የግዛቶች ምክር ቤት አሠራር መሠረት፣ ይህ ውሳኔ በግዛቲቱ የሕግ መዝገብ ላይ የአድዋ ድል በይፋ ዕውቅና ያገኘበት ታሪካዊ ሰነድ ሆኖ በቋሚነት ይቀመጣል።
ይህ የውሳኔ ሐሳብ ረቂቅ፣ የአውሮፓውያኑ ‘ማርች 2 ቀን 2026’ የ130ኛ ‘የአድዋ ድል ቀን’ ሆኖ በፔንሲልቬኒያ ግዛት ዕውቅና እንዲሰጠው የሚደነግግ ነው።
ውሳኔው በሪፐብሊካን እና በዲሞክራቲክ ፓርቲ እንደራሴዎች በተሰጠ 195 ከፍተኛ የድጋፍ ድምጽ እና በ6 ተቃውሞ ብቻ ነው የፀደቀው።
ረቂቁ የቀረበው ከወራት በፊት ቢሆንም የምክር ቤቱን የውስጥ አሠራሮችን አልፎ፣ ውይይቶች ተደርገውበት ከቆየ በኋላ የውሳኔ ድምጽ የተሰጠበት ግን ባለፈው ሳምንት ነው።
”ኤችአር 441” ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረቡት የሰሜን ፊላደልፊያ ሜንገመሪ ካውንቲ፣ የሕዝብ ተወካይ የሆኑት ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ ናቸው።
ቢቢሲ የፀደቀውን የውሳኔ ሐሳብ አስመልክቶ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጡት ሴናተሩን በኢሜይል ጥያቄ አቅርቦላቸው የነበረ ሲሆን፣ ይህ ዘገባ እስኪጠናቀር ድረስ ምላሽ አልሰጡም።
ሆኖም እርሳቸው ረቂቁን ባቀረቡት ዕለት በምክር ቤቱ ባደረጉት ንግግር፣ አድዋ ለአፍሪካ አሜሪካዊያን ያለውን ታላቅ ትርጉም አውስተዋል።
የምክር ቤቱ አባል ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ በዕለቱ በንባብ ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር በዘመናዊ የዓለም ታሪክ ውስጥ አድዋ የማይናቅ ቦታ እንዳለው ካወሱ በኋላ “ኢትዮጵያዊው ንጉሥ ዳግማዊ ምንሊክ እና ባለቤታቸው ጣይቱ ብጡል በአመራር ሰጪነት አገራቸውን ከቅኝ ገዥ ተቀራማቾች” ማስጣላቸውን አብራርተዋል።
ይህም ለአፍሪካ አሜሪካዊያን፣ በአገረ ግዛቱ ውስጥ ለሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ታላቅ ኩራት ነው ብለዋል።
የፔንሲልቬኒያ ግዛት የተወካዮች ምክር ቤት በበኩሉ በድረ ገጹ ባሰፈረው ጽሑፍ አውሮፓውያን የአፍሪካ አገራትን ቅኝ ግዛት በያዙበት እና መቼም ነፃ የሚወጡ በማይመስልበት በዚያን ወቅት ኢትዮጵያ ነፃነቷን በማስከበር የአደዋ ድልን አድንቋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ቅኝ ያልተገዛች ብቸኛዋ አፍሪካዊት አገር በመሆን በ19ኛው እና በ20ኛው ክፍለ ዘመን በነበሩ የዓለም ኃያላን ዕውቅና ማግኘቷን ገልጿል።
በመሆኑም የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 በፔንሲልቬኒያ ግዛት “የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን” እንዲሆን ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቋል።
“የአድዋ ድል ቀንን በማክበር የአሜሪካን ታሪክንም እናከብራለን” ብሏል።
ምክር ቤቱ ያሳለፈውን ውሳኔ በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ ግንኙነት ላይ የሚሠራው ‘አሜሪካን ኢትዮጵያን ፐብሊክ አፌርስ ኮሚቴ’ አወድሶታል።
“የፔንሲልቬኒያ ምክር ቤት በውሳኔው ከአድዋ የተቀሰመው ትምህርት ዛሬም ድረስ ወሳኝ መሆኑን የሚያሳይ ትልቅ መልዕክት አስተላልፏል። በዓለም ሚሊዮኖችን ለሚያነሳሳ እና ለሚያኮራ ለዚህ ታሪካዊ ቀን ዕውቅና በመስጠቱ እናመሰግናለን” ብሏል።
ኮሚቴው ኤችአር 441 ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ ምክር ቤት ላቀረቡት የሕዝብ ተወካይ ቤንጃሚን ሳንቼዝም ምስጋናውን አቅርቧል።
በኮሎራዶ ግዛት የአውሮራ ከተማ ምክር ቤት እንደራሴ እና የሪፐብሊካን ፓርቲ አባል የሆኑት ትውልደ ኢትዮጵያዊው አቶ አምሳሉ ፀጋዬ ኤችአር 441′ የተባለው ውሳኔ በምክር ቤቱ ባሉ ሁለቱም ፓርቲዎች [ ዲሞክራት እና ሪፐብሊካን] በከፍተኛ ድምጽ የጸደቀ መሆኑን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ውሳኔው የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 የኢትዮጵያ አርበኞች በ1896 በአድዋ ተራሮች የጣሊያንን ዘመናዊ ጦር ድል ያደረጉበትን ዕለት ለማስታወስ የተላለፈ መሆኑንም አክለዋል።
13 ሚሊዮን ሕዝብ በሚኖርባት ፔንሲልቬኒያ ግዛት በርካታ ትውልደ ኢትዮጵያን ፊላዴልፊያን ጨምሮ በሌሎች የግዛቲቱ ትልልቅ ከተሞች ውስጥ ይኖራሉ።
“የኢትዮጵያ ታሪክ በኢትዮጵያውያን ብቻ ተወስኖ የሚቀር አይደለም” ያሉት አቶ አምሳሉ፣ “ያ ታሪክ የአፍሪካውያን እና የጥቁር አሜሪካውያን ታሪክም ጭምር ነው” በማለት፣ የድል ቀኑ በፔንሲልቬኒያ ግዛት እንዲታሰብ መደረጉ ወርቃማ ዕድልን የሚፈጥር እንደሆነም ገልጸዋል።
የአድዋ ድል በተመሳሳይ እርሳቸው በተወከሉበት ኮሎራዶ ግዛት፣ አውሮራ ከተማ ምክር ቤትም ዕውቅና ተሰጥቶት ‘የጥቁሮች ታሪክ ከሚዘከርበት ወር’ ጋር ተጣምሮ የሚከበር በዓል እንደሆነም አስታውሰዋል።
ጉዳዩ ወደ ምክር ቤቱ ከመምጣቱ በፊት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ሲደረግበት እንደነበር ያወሱት አቶ አምሳሉ “ይህ ታሪካዊ ድል ለኢትዮጵያውያን፣ ለአሜሪካውያን፣ ለጥቁሮች በሙሉ ትልቅ ዕድል ነው” ብለዋል።
በግዛቲቱ ‘መጋቢት 2፣ 2026 ‘ለ130ኛው የዓድዋ በዓል’ መታሰቢያ እንዲሆን ተወሰነ ሲባል ትርጉሙ ምንድነው? ለምንስ ውሳኔው ረዥም ጊዜን ሊወስድ ቻለ በሚል የተጠየቁት አቶ አምሳሉ፣ በምክር ቤት አሠራር የውሳኔ ሐሳቦች (ሪዞሉሽንስ) ብዙ ማለፍ ያለባቸው ሂደት ስላለ ነው ብለዋል።
‘መጋቢት 2’ የአድዋ ቀን መባሉ ደግሞ ለአንድ ጊዜና ለአንድ ዓመት ብቻ ሳይሆን ቋሚና ቀጣይ እንደሆነ አብራርተዋል።
ዕለቱ ለአድዋ ድል መሰየሙ በተግባር ምን ማለት እንደሆነ ተጠይቀው በግዛቲቱ ቀን መቁጠሪያ (ካላንደር) ውስጥ ‘የአድዋ ቀን’ ተብሎ ተካትቶ ታስቦ ይውላል። ይህም ትልቅ ትርጉም ያለው ተዕምርታዊ (ሲምቦሊክ) ነው’ ብለዋል።
ሆኖም ውሳኔው በዚያው ግዛት ተፈፃሚ የሚሆን እንጂ ወደ ፌደራል የሚያመራ እንዳልሆነም አክለዋል።
ይሁንና አድዋ በበርካታ ግዛቶች ዕውቅና እያገኘ ከመጣ፣ ወደፊት ኢትዮ- አሜሪካውያን፣ ጥቁር አሜሪካውያን እና የተለያዩ አደረጃጀቶች ጉዳዩን በጊዜ ሂደት ወደ ፌደራል ይዘውት እንዲሄዱ አንዳች ዕድል ሊፈጥረ እንደሚችል ያላቸውን ተስፋ ተናግረዋል።
አድዋ ኢትዮጵያ በአፄ ምንሊክ እና ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ አመራር ሰጪነት የጣሊያን ወራሪዎችን ድል በመምታት ሉዓላዊነቷን አስከብራ የቆየችበት እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የጥቁር ሕዝቦች ነፃነት እና ፀረ-ቅኝ ግዛት ትግል ምልክት የሆነ ታሪካዊ ድል ነው።
ከአድዋ ድል በኋላ በርካታ አገራት የፀረ-ቅኝ ግዛት ተጋድሏቸውን በማጠናከር ለዓመታት በዘለቀ ትግል ነፃነታቸውን መቀዳጀት ችለዋል።
በአፍሪካ ሁለት አገራት ቅኝ አለመገዛታቸውን ታሪክ የሚያስረዳ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ራሷን ያስከበረችው አርበኞቿ ባደረጉ ትግል ነው።
በአድዋ ጦርነት በሺዎች የሚቆጠሩ የጣሊያን ሠራዊት አባላት ሲገደሉ ሌሎች ሺህዎች ደግሞ ተማርከዋል። መድፎችን ጨምሮ ከፍተኛ መጠን ያለው የጦር መሳሪያዎችም መማረካቸውን ታሪክ ያስረዳል።
በተጨማሪም የጣሊያንን ሠራዊት ከመሩት መኮንኖች መካከል ጄነራል አልቤርቶኒ ሲማረክ ዋና አዛዥ ጄነራል ባራቴሪ ሸሽቶ አምልጧል።
ኢትዮጵያ ይህንን ታሪካዊ ድል የተጎናፀፈችበትን የካቲት 23 ቀንን በየዓመቱ በደማቅ ታሪካዊ ሁነቶች ታከብራለች።
ባለፈው የካቲት ወርም 130ኛው የአድዋ ድል በዓል ተከብሯል። ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው | 5 318 |
| 16 | ያለ ሐኪም ትዕዛዝ አንቲባዮቲክስ መውሰድ ጀርሞችን በሰውነታችን ውስጥ ማሳደግ መሆኑን ያውቃሉ?
#Fastmereja:- የጸረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች በጀርሞች መላመድን (AMR) ለመከላከል አስቸኳይና የተቀናጀ እርምጃ የማይወሰድ ከሆነ፣ እ.ኤ.አ በ2050 በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ወደ 10 ሚሊዮን ሊያሽቆለቁል እንደሚችል የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን አስታወቀ።
ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ይህንን ያስታወቀው፤ «የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች በጀርሞች መለመድን ለመከላከል የተቀናጀ እርምጃ፡ የአንድ ጤናን በግንዛቤ እና በትምህርት ማሳደግ» በሚል መሪ ቃል፣ በአገር አቀፍ ደረጃ ለ14ኛ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚከበረውን የግንዛቤ ማስጨበጫ ቀንን አስመልክቶ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው።
የጀርሞች መድኃኒት መላመድ (AMR) ማለት በሰውም ሆነ በእንስሳት ላይ ለሚከሰቱ ተላላፊ በሽታዎች ማከሚያ የምንወስዳቸው የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች (ለምሳሌ፦ አንቲባዮቲክስ፣ የቲቢ፣ የኤች.አይ.ቪ ወይም የወባ መድኃኒቶች) በሽታ አምጪ ጀርሞችን መግደል ወይም መቆጣጠር ሳይችሉ ሲቀሩ ሲሆን ጀርሞቹ መድኃኒቱን የመቋቋም አቅም ስለሚያገኟቸው በሰውነት ውስጥ ተከማችተው በመኖርና በመራባት ሕመሙ በቀላሉ እንዳይድን እንደሚያደርጉት አስታውቋል።
ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ በሰጠው መግለጫ፤ ችግሩ በአሁኑ ወቅት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱንና በሰው፣ በእንስሳትና በአካባቢ ጤና እንዲሁም በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ቀውስ እያስከተለ እንደሚገኝ ጠቅሷል።
በአሁኑ ወቅት በየዓመቱ ከ750,000 በላይ ሰዎች በዚህ ምክንያት ህይወታቸውን እንደሚያጡና ወደፊት ሊደርስ የሚችለውን የሰው ህይወት መጥፋት ከመከላከል ባሻገር፣ በዓለም ኢኮኖሚ ላይ ሊደርስ የሚችለውን የ10 ትሪሊዮን ዶላር ከፍተኛ ኪሳራ (ከ2-3% የኢኮኖሚ ቅናሽ) ለመታደግ አስቸኳይ እርምጃ እንደሚያስፈልግ ግምቶች ማሳየታቸውን ባለሥልጣኑ ገልጿል።
በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ በቂ የሕክምና ተቋማት፣ የንጹህ ውሃ አቅርቦት እጥረት ባለባቸውና ውስን ሀብት ባላቸው ታዳጊ አገራት ላይ የችግሩ አሳሳቢነት ይበልጥ ጎልቶ እንደሚታይም ተመልክቷል።
ይህንን ድምፅ አልባ ወረርሽኝ ለመከላከል ህብረተሰቡ መድኃኒቶችን በባለሙያ ትዕዛዝ ብቻ መውሰድና የግል ንጽህናውን መጠበቅ እንዳለበት ያሳሰበው ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ፤ ችግሩን መከላከል ለአንድ አካል ብቻ የሚተው ባለመሆኑ መላው ህብረተሰብ፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ የጤና ባለሙያዎችና መገናኛ ብዙኃን በጋራ ሊረባረቡ እንደሚገባ ጥሪ አቅርቧል።
ዕለቱም በመጪው ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም (June 15, 2026) በልዩ ልዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅቶች በአገር አቀፍ ደረጃ እንደሚከበር ታውቋል። | 5 551 |
| 17 | ፌስቡክ ተቋረጠ | 7 373 |
| 18 | አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ በዶፒንግ ምርመራ የአራት ወር እገዳ ተጣለባት
#FastMereja | የዓለም 5,000 እና 10,000 ሜትር የቀድሞ ሻምፒዮን አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ፣ በዶፒንግ ምርመራ ወቅት በሰውነቷ ውስጥ “ሌትሮዞል” የተባለ ንጥረ ነገር በመገኘቱ የአራት ወር እገዳ ተላልፎባታል።
እንደ አትሌቲክስ ዊክሊ ዘገባ በአትሌቷ የተገኘው ንጥረ ነገር የታዘዘላትን የህክምና ችግር ለመቆጣጠር ትጠቀምበት የነበረ መሆኑን በማስረጃ ማቅረቧን ተከትሎ፣ የዓለም አትሌቲክስ ጥብቅና ክፍል (AIU) ከረዥም ጊዜ ቅጣት ይልቅ የአራት ወር እገዳን እንዲወስን ስምምነት ላይ ተደርሷል።
የ29 ዓመቷ አትሌት ጉዳፍ፣ ይህን ተከትሎ የ2026 የውድድር ዓመትን የትራክ ውድድሮች በሙሉ እንደማትሳተፍ ተገልጿል።
የአትሌቲክስ ጥብቅና ክፍሉ ባወጣው መግለጫ፣ ጉዳፍ ምርመራው መገኘቱን አምና Case Resolution Agreement እንደፈረመች አስታውቋል። | 7 275 |
| 19 | ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነኢየሱስ ከሐዋርያዊ ኃላፊነታቸው በጡረታ አስረከቡ
#FastMereja | የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳስ እና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የነበሩት ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነኢየሱስ ሱራፌል በጡረታ ምክንያት ከኃላፊነታቸው ተሰናብተዋል። ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሌዎ 14ኛ፣ ካርዲናሉ ቀደም ብለው ያቀረቡትን የጡረታ ጥያቄ በዛሬው ዕለት ተቀብለዋል።
የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ቀኖናዊ አሰራርን ተከትሎ የቀረበው ይህ ጥያቄ በቅድስት መንበር በኩል ተቀባይነት አግኝቷል። ውሳኔው በቅድስት መንበር ልዩ መልዕክተኛ ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ በኩል ይፋ የተደረገ ሲሆን፣ የካርዲናሉ የረጅም ዘመን አገልግሎት በቤተክርስቲያኗ ታሪክ ውስጥ ጉልህ ስፍራ የሚሰጠው ነው።
በብፁዕ ካርዲናል ብርሃነኢየሱስ ቦታ ላይ፣ ቀደም ሲል የአዲስ አበባ ረዳት ጳጳስ በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ተስፋስላሴ ተተኪ ሊቀጳጳስ ሆነው መሾማቸው ታውቋል። | 6 549 |
| 20 | የኢትዮጵያ ምስጋና ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን የ3 ሳምንታት ታላቅ የምስጋና እና የጸሎት መርሃ-ግብር አዘጋጀች!
#Fastmereja I የኢትዮጵያ ምስጋና ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን በአዲስ አበባ ከተማ ለቡ አካባቢ ከመንግስት የተሰጣትንና ላለፉት ስምንት ዓመታት በፍርድ ቤት ክርክር ውስጥ የነበረውን 10 ሺህ ካሬ ሜትር ስፋት ያለው መሬት በሕጋዊ መንገድ በይፋ መረከቧን አስታወቀች።
ቤተ ክርስቲያኒቱ በዚህ አዲስ ይዞታ ላይ በአገር አቀፍ ደረጃ 78ዐኛውን፣ በአዲስ አበባ ደግሞ 7ኛውን አዲስ አጥቢያ በይፋ እንደምትጀምር በዛሬዉ እለት በሰጠችው ጋዜጣዊ መግለጫ ገልጻለች።
የኢትዮጵያ ምስጋና ወንጌላዊት ቤተክርስትያን ፕሬዝዳንት መጋቢ ዶ/ር ጌታሁን ነሲቡ በለቡ አጥቢያ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳመለከቱት፤ አዲሱ ይዞታ (ለቡ 01 ሆፕ ዩኒቨርሲቲ አጠገብ) በ2010 ዓ.ም ከመንግስት የተሰጠ ቢሆንም፣ ባለፉት ስምንት ዓመታት ባጋጠሙ የተለያዩ ይዞታ ነክ ተግዳሮቶችና ክርክሮች ምክንያት ጉዳዩ በፍርድ ቤት ሲታይ መቆየቱን ገልፀዉ በአሁኑ ወቅት ግን ተቋሙ ሁሉንም ፈተናዎች በሕጋዊ መንገድ በማለፍ መሬቱን በይፋ ለመረከብ መቻሉን አስታውቀዋል።
በይፋ በተረከቡት አዲሱ ስፍራ ላይ በቀጣይ ታላላቅ የልማት ዕቅዶች እንደሚከናወኑ የተገለፀ ሲሆን ከታቀዱት ዋና ዋና ፕሮጀክቶች መካከል የዘመናዊ አምልኮ እና የቢሮ ሕንጻ ግንባታ፣ ለስነ-መለኮት ኮሌጅ አገልግሎት የሚውሉ ዘመናዊ የተማሪዎችና የአገልጋዮች ማደሪያ ክፍሎች (Dormitories) ግንባታ፣ እና ከአካባቢው ወንዝ ተያያዥነት ያለው የ10 ሺህ ካሬ የወንዝ ዳርቻ ልማትና የአረንጓዴ ስፍራ ጥበቃ እንደሚገኙበት ጠቁመዋል።
ቤተ ክርስቲያኒቱ እነዚህን ታላላቅ የልማትና የህንጻ ግንባታ ዕቅዶች ከመጀመሯ በፊት፣ ባለፉት 8 ዓመታት የነበሩትን ፈታኝ የፍርድ ቤት ጉዞዎች በድል እንድትወጣ የረዳትን አምላክ ማመስገን ቀዳሚ ተግባሯ መሆኑን ገልጻ የሦስት ሳምንት ተከታታይ መርሃ-ግብር ማዉጣቷን አስታዉቃለች።
የፊታችን እሁድ ሰኔ 07 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያሉ የቤተ እምነቱ አጥቢያዎች በሙሉ በጋራ በመሆን ሙሉ ቀን የሚቆይ ታላቅ ታሪካዊ የጸሎት እና የአምልኮ ፕሮግራም ያካሂዳሉ።
እሁድ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ደግሞ የቤተ እምነት መሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ልዩ የምስጋና ፕሮግራም ይደረጋል።
ከእሁድ ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በየሳምንቱ እሁድ ከሰዓት በኋላ በዚህ በአዲሱ 7ኛ ለቡ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን መደበኛ የአምልኮ አገልግሎት በይፋ እንደሚቀጥል ታውቋል።
የኢትዮጵያ ምስጋና ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን ላለፉት 45 ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ ውስጥ በወንጌል አገልግሎት እንዲሁም በልማትና ማኅበራዊ አገልግሎቶች ላይ በስፋት ስትሳተፍ የቆየች ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ሁሉም ክልሎች ላይ ከ780 በላይ አጥቢያዎች እንዳሏት ከመግለጫው ለመረዳት ተችሏል።
ዶ/ር ጌታሁን ነሲቡ ለዚህ ታሪካዊ ስኬት መሳካት አምላካቸውን እያመሰገኑ፣ ክርስቲያኒቱ ጎን ለቆሙ አካላት በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። | 5 212 |
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
