FastMereja.com
📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу FastMereja.com
Канал FastMereja.com (@fastmereja) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 49 456 підписників, посідаючи 3 570 місце в категорії Освіта та 644 місце у регіоні Ефіопія.
📊 Показники аудиторії та динаміка
З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 49 456 підписників.
За останніми даними від 13 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -750, а за останні 24 години на -29, загальне охоплення залишається високим.
- Статус верифікації: Не верифікований
- Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 13.68%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 8.58% реакцій від загальної кількості підписників.
- Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 6 769 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 4 243 переглядів.
- Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 32.
📝 Опис та контентна політика
Опис каналу не надано.
Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 14 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Освіта.
Триває завантаження даних...
| Дата | Залучення підписників | Згадування | Канали | |
| 14 червня | 0 | |||
| 13 червня | 0 | |||
| 12 червня | 0 | |||
| 11 червня | 0 | |||
| 10 червня | 0 | |||
| 09 червня | 0 | |||
| 08 червня | 0 | |||
| 07 червня | 0 | |||
| 06 червня | 0 | |||
| 05 червня | 0 | |||
| 04 червня | 0 | |||
| 03 червня | 0 | |||
| 02 червня | 0 | |||
| 01 червня | +1 |
| 2 | ኢትዮጵያዊው የቴክኖሎጂ ስራ ፈጣሪ በሰፊቃድ ጌታቸው በአፍሪካ ምርጥ 100 የንግድ ጀግኖች ዝርዝር ውስጥ ተካተቱ
#FastMereja | የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኩባንያ የሆነው “ኢግል ላይን ሲስተም ቴክኖሎጂ” መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ በሰፊቃድ ጌታቸው፣ በ2026ቱ “አፍሪካ ቢዝነስ ሄሮውስ” (ABH) ውድድር ከመላው አፍሪካ ከተውጣጡ ከ24 ሺህ በላይ ተወዳዳሪዎች መካከል በማለፍ፣ በምርጥ 100 የንግድ ጀግኖች ዝርዝር ውስጥ መካተታቸው ተገለጸ።
በሰፊቃድ ጌታቸው የሚመራው “ኢግል ላይን ሲስተም ቴክኖሎጂ” በተለይም በፋይናንስ፣ በግብርና፣ በዲጂታል ክፍያ እና በቱሪዝም ዘርፎች ከሁለት ደርዘን በላይ የቴክኖሎጂ መፍትሄዎችን በማዘጋጀት ይታወቃል። በዘርፉ ካበረከቷቸው ፈጠራዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ከአንድ ሚሊየን ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የግብርና ግብዓት ግዥን ያቀለለው የ”ጌትፊ ኢንተርፕራይዝ” (GetFee Enterprise) የክፍያ ስብስብ መድረክ እና የዳሽን ባንክ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ዋነኞቹ ናቸው።
በተጨማሪም እንደ “ካሽ ጎ” (CashGo)፣ “ኢትዮ-ዳይሬክት ኮኔክት” (Ethio-Direct Connect) እና የ”ዱቤ አለ” (DubeAle) የክፍያ መድረክ የመሳሰሉ ፈጠራዎች በኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስ ስነ-ምህዳር ውስጥ ያላቸውን ተፅእኖ አሳይተዋል። ከእነዚህም ባሻገር ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ ማሰባሰቢያ የሆነውን “ItsMyDam.com” መድረክ በማልማትም ይታወቃሉ።
የአፍሪካ ቢዝነስ ሄሮውስ (ABH) ተነሳሽነት በ2018 ዓ.ም. በአሊባባ መስራች ጃክ ማ የተጀመረ ሲሆን፣ ዓላማውም በየአመቱ በአህጉሪቱ አስር ምርጥ ስራ ፈጣሪዎችን በመለየት የገንዘብ ድጋፍ፣ ስልጠና እና የአማካሪነት አገልግሎት መስጠት ነው። ለዘንድሮው የውድድር ዘመን በአጠቃላይ 1.5 ሚሊዮን ዶላር የሽልማት በጀት ተይዞለታል።
የሰፊቃድ ጌታቸው በምርጥ 100 ዝርዝር ውስጥ መካተት፣ ኢትዮጵያውያን ስራ ፈጣሪዎች በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላቸውን አቅም በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማሳየትና አህጉራዊ ተወዳዳሪነትን ለመቀዳጀት እንደ ትልቅ ምዕራፍ ተወስዷል። ቀደም ሲል ከነበሩት ዓመታት አንጻር፣ በውድድሩ የኢትዮጵያውያን ተሳትፎ እየጨመረ መምጣቱን መረጃዎች ይጠቁማሉ። | 1 750 |
| 3 | ጀግናዋ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የረዳት ኮሚሽነርነት ማዕረግ አገኘች
#FastMereja I የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የስፖርት ክለብ እንዲሁም የሙዚቃና ቴአትር ቡድን የተመሠረተበት 40ኛ ዓመት ክብረ በዓል በአድዋ ድል መታሰቢያ በድምቀት ተከብሯል።
በዚሁ መድረክ ላይ በኦሎምፒክና በዓለም ሻምፒዮና ውድድሮች በርካታ ሜዳሊያዎችን በማምጣት የሀገርን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ ላደረገችው ጀግናዋ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የተቋሙ ከፍተኛ የዕድገት እርከን የሆነው የረዳት ኮሚሽነርነት ማዕረግ ተሰጥቷታል።
በዕለቱም ለረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ፣ ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን፣ ለኮማንደር ፋጡማ ሮባ፣ ለኮማንደር አትሌት ሰለሞን ባረጋ እና ለምክትል ኮማንደር ሰንበሬ ተፈሪ የዕውቅናና ሽልማት ፕሮግራም ተካሂዷል።
በተጨማሪም በአሰልጣኝነት ከ30 ዓመታት በላይ በማገልገል የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱት ረዳት ኮሚሽነር ሁሴን ሸቦ የኒሻን ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን፤ በኪነ-ጥበቡ ዘርፍ ለሀገር ትልቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የሙዚቃና ቴአትር ቡድኑ አባላትም ዕውቅና ተሰጥቷል።
በክብረ በዓሉ ላይ የተገኙት የፍትሕ ሚኒስትር ሐና አርዓያሥላሴ የኮሚሽኑ የስፖርት ክለብ ባለፉት 40 ዓመታት እውቅ ጀግኖችን በማፍራት በኩል የላቀ ሚና መጫወቱን ጠቅሰው፤ ተቋሙ ይህንኑ አበረታች ሥራውን ይበልጥ ዘመናዊ በማድረግ አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል። | 2 496 |
| 4 | ከሽያጭ በኋላ የጥገና አገልግሎት የያዘው «ቴክ ኢዚ» ማዕከል ስራ ጀመረ!
#Fastmereja I በኢትዮጵያ የኤሌክትሮኒክስ ገበያ ውስጥ ሸማቶች የተለያዩ ብራንዶችን በአንድ ቦታ እንዲያገኙ ለማስቻል «ቴክ ኢዚ» (TekEasy) የተሰኘው የኤሌክትሮኒክስ መሸጫ ማዕከል የመጀመሪያውን ቅርንጫፍ በይፋ አስመርቋል።
ማዕከሉ እንደ ቴክኖ፣ አፕል፣ ሚዲያ እና ኢንፊኒክስ ያሉ ታዋቂ ዓለም አቀፍና የሀገር ውስጥ የኤሌክትሮኒክስ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንደሚያቀርብ ተገልጿል።
ኩባንያው በአዲስ አበባ የጀመረውን ይህንን የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንት በቀጣይ ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ዋና ዋና ከተሞች የማስፋፋት ዕቅድ እንዳለው አስታውቋል።
ይህ ማዕከል ከተለመደው የሽያጭ አሰራር በተለየ መልኩ ከሽያጭ በኋላ በሚሰጥ አገልግሎት የያዘ ሲሆን ዕቃዎችን ደንበኞች እስከሚፈልጉበት ቦታ ድረስ የሚያደርስ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሁም የቴክኒክ ብልሽቶች በሚያጋጥሙበት ወቅትም ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ የጥገና ማዕከልና የባለሙያ ቡድን የተደራጀ ስለመሆኑም ነዉ የተገለፀዉ።
ይህ አዲስ ማዕከል በኢትዮጵያ በፍጥነት እያደገ የመጣውን የዲጂታል ኑሮ ዘይቤ በማገዝና ለሸማቾች አስተማማኝ አማራጭ በመሆን ረገድ የራሱን አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወት ይጠበቃል። | 3 919 |
| 5 | የአሜሪካዋ ግዛት ምክር ቤት ለአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን ሰየመ
#FastMereja I በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ ‘መጋቢት 2’ በግዛቱ የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን እንዲሆን የቀረበን የውሳኔ ሐሳብ በከፍተኛ ድምጽ አፀደቀ።
ይህ ‘ኤችአር 441’ የተሰኘው የውሳኔ ሐሳብ የፀደቀው ባለፈው ሳምንት በግዛቲቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተደረገ የድምጽ አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት ነው።
በአሜሪካ የግዛቶች ምክር ቤት አሠራር መሠረት፣ ይህ ውሳኔ በግዛቲቱ የሕግ መዝገብ ላይ የአድዋ ድል በይፋ ዕውቅና ያገኘበት ታሪካዊ ሰነድ ሆኖ በቋሚነት ይቀመጣል።
ይህ የውሳኔ ሐሳብ ረቂቅ፣ የአውሮፓውያኑ ‘ማርች 2 ቀን 2026’ የ130ኛ ‘የአድዋ ድል ቀን’ ሆኖ በፔንሲልቬኒያ ግዛት ዕውቅና እንዲሰጠው የሚደነግግ ነው።
ውሳኔው በሪፐብሊካን እና በዲሞክራቲክ ፓርቲ እንደራሴዎች በተሰጠ 195 ከፍተኛ የድጋፍ ድምጽ እና በ6 ተቃውሞ ብቻ ነው የፀደቀው።
ረቂቁ የቀረበው ከወራት በፊት ቢሆንም የምክር ቤቱን የውስጥ አሠራሮችን አልፎ፣ ውይይቶች ተደርገውበት ከቆየ በኋላ የውሳኔ ድምጽ የተሰጠበት ግን ባለፈው ሳምንት ነው።
”ኤችአር 441” ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረቡት የሰሜን ፊላደልፊያ ሜንገመሪ ካውንቲ፣ የሕዝብ ተወካይ የሆኑት ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ ናቸው።
ቢቢሲ የፀደቀውን የውሳኔ ሐሳብ አስመልክቶ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጡት ሴናተሩን በኢሜይል ጥያቄ አቅርቦላቸው የነበረ ሲሆን፣ ይህ ዘገባ እስኪጠናቀር ድረስ ምላሽ አልሰጡም።
ሆኖም እርሳቸው ረቂቁን ባቀረቡት ዕለት በምክር ቤቱ ባደረጉት ንግግር፣ አድዋ ለአፍሪካ አሜሪካዊያን ያለውን ታላቅ ትርጉም አውስተዋል።
የምክር ቤቱ አባል ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ በዕለቱ በንባብ ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር በዘመናዊ የዓለም ታሪክ ውስጥ አድዋ የማይናቅ ቦታ እንዳለው ካወሱ በኋላ “ኢትዮጵያዊው ንጉሥ ዳግማዊ ምንሊክ እና ባለቤታቸው ጣይቱ ብጡል በአመራር ሰጪነት አገራቸውን ከቅኝ ገዥ ተቀራማቾች” ማስጣላቸውን አብራርተዋል።
ይህም ለአፍሪካ አሜሪካዊያን፣ በአገረ ግዛቱ ውስጥ ለሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ታላቅ ኩራት ነው ብለዋል።
የፔንሲልቬኒያ ግዛት የተወካዮች ምክር ቤት በበኩሉ በድረ ገጹ ባሰፈረው ጽሑፍ አውሮፓውያን የአፍሪካ አገራትን ቅኝ ግዛት በያዙበት እና መቼም ነፃ የሚወጡ በማይመስልበት በዚያን ወቅት ኢትዮጵያ ነፃነቷን በማስከበር የአደዋ ድልን አድንቋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ቅኝ ያልተገዛች ብቸኛዋ አፍሪካዊት አገር በመሆን በ19ኛው እና በ20ኛው ክፍለ ዘመን በነበሩ የዓለም ኃያላን ዕውቅና ማግኘቷን ገልጿል።
በመሆኑም የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 በፔንሲልቬኒያ ግዛት “የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን” እንዲሆን ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቋል።
“የአድዋ ድል ቀንን በማክበር የአሜሪካን ታሪክንም እናከብራለን” ብሏል።
ምክር ቤቱ ያሳለፈውን ውሳኔ በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ ግንኙነት ላይ የሚሠራው ‘አሜሪካን ኢትዮጵያን ፐብሊክ አፌርስ ኮሚቴ’ አወድሶታል።
“የፔንሲልቬኒያ ምክር ቤት በውሳኔው ከአድዋ የተቀሰመው ትምህርት ዛሬም ድረስ ወሳኝ መሆኑን የሚያሳይ ትልቅ መልዕክት አስተላልፏል። በዓለም ሚሊዮኖችን ለሚያነሳሳ እና ለሚያኮራ ለዚህ ታሪካዊ ቀን ዕውቅና በመስጠቱ እናመሰግናለን” ብሏል።
ኮሚቴው ኤችአር 441 ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ ምክር ቤት ላቀረቡት የሕዝብ ተወካይ ቤንጃሚን ሳንቼዝም ምስጋናውን አቅርቧል።
በኮሎራዶ ግዛት የአውሮራ ከተማ ምክር ቤት እንደራሴ እና የሪፐብሊካን ፓርቲ አባል የሆኑት ትውልደ ኢትዮጵያዊው አቶ አምሳሉ ፀጋዬ ኤችአር 441′ የተባለው ውሳኔ በምክር ቤቱ ባሉ ሁለቱም ፓርቲዎች [ ዲሞክራት እና ሪፐብሊካን] በከፍተኛ ድምጽ የጸደቀ መሆኑን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ውሳኔው የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 የኢትዮጵያ አርበኞች በ1896 በአድዋ ተራሮች የጣሊያንን ዘመናዊ ጦር ድል ያደረጉበትን ዕለት ለማስታወስ የተላለፈ መሆኑንም አክለዋል።
13 ሚሊዮን ሕዝብ በሚኖርባት ፔንሲልቬኒያ ግዛት በርካታ ትውልደ ኢትዮጵያን ፊላዴልፊያን ጨምሮ በሌሎች የግዛቲቱ ትልልቅ ከተሞች ውስጥ ይኖራሉ።
“የኢትዮጵያ ታሪክ በኢትዮጵያውያን ብቻ ተወስኖ የሚቀር አይደለም” ያሉት አቶ አምሳሉ፣ “ያ ታሪክ የአፍሪካውያን እና የጥቁር አሜሪካውያን ታሪክም ጭምር ነው” በማለት፣ የድል ቀኑ በፔንሲልቬኒያ ግዛት እንዲታሰብ መደረጉ ወርቃማ ዕድልን የሚፈጥር እንደሆነም ገልጸዋል።
የአድዋ ድል በተመሳሳይ እርሳቸው በተወከሉበት ኮሎራዶ ግዛት፣ አውሮራ ከተማ ምክር ቤትም ዕውቅና ተሰጥቶት ‘የጥቁሮች ታሪክ ከሚዘከርበት ወር’ ጋር ተጣምሮ የሚከበር በዓል እንደሆነም አስታውሰዋል።
ጉዳዩ ወደ ምክር ቤቱ ከመምጣቱ በፊት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ሲደረግበት እንደነበር ያወሱት አቶ አምሳሉ “ይህ ታሪካዊ ድል ለኢትዮጵያውያን፣ ለአሜሪካውያን፣ ለጥቁሮች በሙሉ ትልቅ ዕድል ነው” ብለዋል።
በግዛቲቱ ‘መጋቢት 2፣ 2026 ‘ለ130ኛው የዓድዋ በዓል’ መታሰቢያ እንዲሆን ተወሰነ ሲባል ትርጉሙ ምንድነው? ለምንስ ውሳኔው ረዥም ጊዜን ሊወስድ ቻለ በሚል የተጠየቁት አቶ አምሳሉ፣ በምክር ቤት አሠራር የውሳኔ ሐሳቦች (ሪዞሉሽንስ) ብዙ ማለፍ ያለባቸው ሂደት ስላለ ነው ብለዋል።
‘መጋቢት 2’ የአድዋ ቀን መባሉ ደግሞ ለአንድ ጊዜና ለአንድ ዓመት ብቻ ሳይሆን ቋሚና ቀጣይ እንደሆነ አብራርተዋል።
ዕለቱ ለአድዋ ድል መሰየሙ በተግባር ምን ማለት እንደሆነ ተጠይቀው በግዛቲቱ ቀን መቁጠሪያ (ካላንደር) ውስጥ ‘የአድዋ ቀን’ ተብሎ ተካትቶ ታስቦ ይውላል። ይህም ትልቅ ትርጉም ያለው ተዕምርታዊ (ሲምቦሊክ) ነው’ ብለዋል።
ሆኖም ውሳኔው በዚያው ግዛት ተፈፃሚ የሚሆን እንጂ ወደ ፌደራል የሚያመራ እንዳልሆነም አክለዋል።
ይሁንና አድዋ በበርካታ ግዛቶች ዕውቅና እያገኘ ከመጣ፣ ወደፊት ኢትዮ- አሜሪካውያን፣ ጥቁር አሜሪካውያን እና የተለያዩ አደረጃጀቶች ጉዳዩን በጊዜ ሂደት ወደ ፌደራል ይዘውት እንዲሄዱ አንዳች ዕድል ሊፈጥረ እንደሚችል ያላቸውን ተስፋ ተናግረዋል።
አድዋ ኢትዮጵያ በአፄ ምንሊክ እና ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ አመራር ሰጪነት የጣሊያን ወራሪዎችን ድል በመምታት ሉዓላዊነቷን አስከብራ የቆየችበት እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የጥቁር ሕዝቦች ነፃነት እና ፀረ-ቅኝ ግዛት ትግል ምልክት የሆነ ታሪካዊ ድል ነው።
ከአድዋ ድል በኋላ በርካታ አገራት የፀረ-ቅኝ ግዛት ተጋድሏቸውን በማጠናከር ለዓመታት በዘለቀ ትግል ነፃነታቸውን መቀዳጀት ችለዋል።
በአፍሪካ ሁለት አገራት ቅኝ አለመገዛታቸውን ታሪክ የሚያስረዳ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ራሷን ያስከበረችው አርበኞቿ ባደረጉ ትግል ነው።
በአድዋ ጦርነት በሺዎች የሚቆጠሩ የጣሊያን ሠራዊት አባላት ሲገደሉ ሌሎች ሺህዎች ደግሞ ተማርከዋል። መድፎችን ጨምሮ ከፍተኛ መጠን ያለው የጦር መሳሪያዎችም መማረካቸውን ታሪክ ያስረዳል።
በተጨማሪም የጣሊያንን ሠራዊት ከመሩት መኮንኖች መካከል ጄነራል አልቤርቶኒ ሲማረክ ዋና አዛዥ ጄነራል ባራቴሪ ሸሽቶ አምልጧል።
ኢትዮጵያ ይህንን ታሪካዊ ድል የተጎናፀፈችበትን የካቲት 23 ቀንን በየዓመቱ በደማቅ ታሪካዊ ሁነቶች ታከብራለች።
ባለፈው የካቲት ወርም 130ኛው የአድዋ ድል በዓል ተከብሯል። ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው | 4 601 |
| 6 | ያለ ሐኪም ትዕዛዝ አንቲባዮቲክስ መውሰድ ጀርሞችን በሰውነታችን ውስጥ ማሳደግ መሆኑን ያውቃሉ?
#Fastmereja:- የጸረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች በጀርሞች መላመድን (AMR) ለመከላከል አስቸኳይና የተቀናጀ እርምጃ የማይወሰድ ከሆነ፣ እ.ኤ.አ በ2050 በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ወደ 10 ሚሊዮን ሊያሽቆለቁል እንደሚችል የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን አስታወቀ።
ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ይህንን ያስታወቀው፤ «የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች በጀርሞች መለመድን ለመከላከል የተቀናጀ እርምጃ፡ የአንድ ጤናን በግንዛቤ እና በትምህርት ማሳደግ» በሚል መሪ ቃል፣ በአገር አቀፍ ደረጃ ለ14ኛ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚከበረውን የግንዛቤ ማስጨበጫ ቀንን አስመልክቶ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው።
የጀርሞች መድኃኒት መላመድ (AMR) ማለት በሰውም ሆነ በእንስሳት ላይ ለሚከሰቱ ተላላፊ በሽታዎች ማከሚያ የምንወስዳቸው የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች (ለምሳሌ፦ አንቲባዮቲክስ፣ የቲቢ፣ የኤች.አይ.ቪ ወይም የወባ መድኃኒቶች) በሽታ አምጪ ጀርሞችን መግደል ወይም መቆጣጠር ሳይችሉ ሲቀሩ ሲሆን ጀርሞቹ መድኃኒቱን የመቋቋም አቅም ስለሚያገኟቸው በሰውነት ውስጥ ተከማችተው በመኖርና በመራባት ሕመሙ በቀላሉ እንዳይድን እንደሚያደርጉት አስታውቋል።
ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ በሰጠው መግለጫ፤ ችግሩ በአሁኑ ወቅት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱንና በሰው፣ በእንስሳትና በአካባቢ ጤና እንዲሁም በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ቀውስ እያስከተለ እንደሚገኝ ጠቅሷል።
በአሁኑ ወቅት በየዓመቱ ከ750,000 በላይ ሰዎች በዚህ ምክንያት ህይወታቸውን እንደሚያጡና ወደፊት ሊደርስ የሚችለውን የሰው ህይወት መጥፋት ከመከላከል ባሻገር፣ በዓለም ኢኮኖሚ ላይ ሊደርስ የሚችለውን የ10 ትሪሊዮን ዶላር ከፍተኛ ኪሳራ (ከ2-3% የኢኮኖሚ ቅናሽ) ለመታደግ አስቸኳይ እርምጃ እንደሚያስፈልግ ግምቶች ማሳየታቸውን ባለሥልጣኑ ገልጿል።
በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ በቂ የሕክምና ተቋማት፣ የንጹህ ውሃ አቅርቦት እጥረት ባለባቸውና ውስን ሀብት ባላቸው ታዳጊ አገራት ላይ የችግሩ አሳሳቢነት ይበልጥ ጎልቶ እንደሚታይም ተመልክቷል።
ይህንን ድምፅ አልባ ወረርሽኝ ለመከላከል ህብረተሰቡ መድኃኒቶችን በባለሙያ ትዕዛዝ ብቻ መውሰድና የግል ንጽህናውን መጠበቅ እንዳለበት ያሳሰበው ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ፤ ችግሩን መከላከል ለአንድ አካል ብቻ የሚተው ባለመሆኑ መላው ህብረተሰብ፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ የጤና ባለሙያዎችና መገናኛ ብዙኃን በጋራ ሊረባረቡ እንደሚገባ ጥሪ አቅርቧል።
ዕለቱም በመጪው ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም (June 15, 2026) በልዩ ልዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅቶች በአገር አቀፍ ደረጃ እንደሚከበር ታውቋል። | 4 654 |
| 7 | ፌስቡክ ተቋረጠ | 6 903 |
| 8 | አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ በዶፒንግ ምርመራ የአራት ወር እገዳ ተጣለባት
#FastMereja | የዓለም 5,000 እና 10,000 ሜትር የቀድሞ ሻምፒዮን አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ፣ በዶፒንግ ምርመራ ወቅት በሰውነቷ ውስጥ “ሌትሮዞል” የተባለ ንጥረ ነገር በመገኘቱ የአራት ወር እገዳ ተላልፎባታል።
እንደ አትሌቲክስ ዊክሊ ዘገባ በአትሌቷ የተገኘው ንጥረ ነገር የታዘዘላትን የህክምና ችግር ለመቆጣጠር ትጠቀምበት የነበረ መሆኑን በማስረጃ ማቅረቧን ተከትሎ፣ የዓለም አትሌቲክስ ጥብቅና ክፍል (AIU) ከረዥም ጊዜ ቅጣት ይልቅ የአራት ወር እገዳን እንዲወስን ስምምነት ላይ ተደርሷል።
የ29 ዓመቷ አትሌት ጉዳፍ፣ ይህን ተከትሎ የ2026 የውድድር ዓመትን የትራክ ውድድሮች በሙሉ እንደማትሳተፍ ተገልጿል።
የአትሌቲክስ ጥብቅና ክፍሉ ባወጣው መግለጫ፣ ጉዳፍ ምርመራው መገኘቱን አምና Case Resolution Agreement እንደፈረመች አስታውቋል። | 6 911 |
| 9 | ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነኢየሱስ ከሐዋርያዊ ኃላፊነታቸው በጡረታ አስረከቡ
#FastMereja | የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳስ እና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የነበሩት ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነኢየሱስ ሱራፌል በጡረታ ምክንያት ከኃላፊነታቸው ተሰናብተዋል። ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሌዎ 14ኛ፣ ካርዲናሉ ቀደም ብለው ያቀረቡትን የጡረታ ጥያቄ በዛሬው ዕለት ተቀብለዋል።
የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ቀኖናዊ አሰራርን ተከትሎ የቀረበው ይህ ጥያቄ በቅድስት መንበር በኩል ተቀባይነት አግኝቷል። ውሳኔው በቅድስት መንበር ልዩ መልዕክተኛ ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ በኩል ይፋ የተደረገ ሲሆን፣ የካርዲናሉ የረጅም ዘመን አገልግሎት በቤተክርስቲያኗ ታሪክ ውስጥ ጉልህ ስፍራ የሚሰጠው ነው።
በብፁዕ ካርዲናል ብርሃነኢየሱስ ቦታ ላይ፣ ቀደም ሲል የአዲስ አበባ ረዳት ጳጳስ በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ተስፋስላሴ ተተኪ ሊቀጳጳስ ሆነው መሾማቸው ታውቋል። | 6 235 |
| 10 | የኢትዮጵያ ምስጋና ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን የ3 ሳምንታት ታላቅ የምስጋና እና የጸሎት መርሃ-ግብር አዘጋጀች!
#Fastmereja I የኢትዮጵያ ምስጋና ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን በአዲስ አበባ ከተማ ለቡ አካባቢ ከመንግስት የተሰጣትንና ላለፉት ስምንት ዓመታት በፍርድ ቤት ክርክር ውስጥ የነበረውን 10 ሺህ ካሬ ሜትር ስፋት ያለው መሬት በሕጋዊ መንገድ በይፋ መረከቧን አስታወቀች።
ቤተ ክርስቲያኒቱ በዚህ አዲስ ይዞታ ላይ በአገር አቀፍ ደረጃ 78ዐኛውን፣ በአዲስ አበባ ደግሞ 7ኛውን አዲስ አጥቢያ በይፋ እንደምትጀምር በዛሬዉ እለት በሰጠችው ጋዜጣዊ መግለጫ ገልጻለች።
የኢትዮጵያ ምስጋና ወንጌላዊት ቤተክርስትያን ፕሬዝዳንት መጋቢ ዶ/ር ጌታሁን ነሲቡ በለቡ አጥቢያ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳመለከቱት፤ አዲሱ ይዞታ (ለቡ 01 ሆፕ ዩኒቨርሲቲ አጠገብ) በ2010 ዓ.ም ከመንግስት የተሰጠ ቢሆንም፣ ባለፉት ስምንት ዓመታት ባጋጠሙ የተለያዩ ይዞታ ነክ ተግዳሮቶችና ክርክሮች ምክንያት ጉዳዩ በፍርድ ቤት ሲታይ መቆየቱን ገልፀዉ በአሁኑ ወቅት ግን ተቋሙ ሁሉንም ፈተናዎች በሕጋዊ መንገድ በማለፍ መሬቱን በይፋ ለመረከብ መቻሉን አስታውቀዋል።
በይፋ በተረከቡት አዲሱ ስፍራ ላይ በቀጣይ ታላላቅ የልማት ዕቅዶች እንደሚከናወኑ የተገለፀ ሲሆን ከታቀዱት ዋና ዋና ፕሮጀክቶች መካከል የዘመናዊ አምልኮ እና የቢሮ ሕንጻ ግንባታ፣ ለስነ-መለኮት ኮሌጅ አገልግሎት የሚውሉ ዘመናዊ የተማሪዎችና የአገልጋዮች ማደሪያ ክፍሎች (Dormitories) ግንባታ፣ እና ከአካባቢው ወንዝ ተያያዥነት ያለው የ10 ሺህ ካሬ የወንዝ ዳርቻ ልማትና የአረንጓዴ ስፍራ ጥበቃ እንደሚገኙበት ጠቁመዋል።
ቤተ ክርስቲያኒቱ እነዚህን ታላላቅ የልማትና የህንጻ ግንባታ ዕቅዶች ከመጀመሯ በፊት፣ ባለፉት 8 ዓመታት የነበሩትን ፈታኝ የፍርድ ቤት ጉዞዎች በድል እንድትወጣ የረዳትን አምላክ ማመስገን ቀዳሚ ተግባሯ መሆኑን ገልጻ የሦስት ሳምንት ተከታታይ መርሃ-ግብር ማዉጣቷን አስታዉቃለች።
የፊታችን እሁድ ሰኔ 07 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያሉ የቤተ እምነቱ አጥቢያዎች በሙሉ በጋራ በመሆን ሙሉ ቀን የሚቆይ ታላቅ ታሪካዊ የጸሎት እና የአምልኮ ፕሮግራም ያካሂዳሉ።
እሁድ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ደግሞ የቤተ እምነት መሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ልዩ የምስጋና ፕሮግራም ይደረጋል።
ከእሁድ ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በየሳምንቱ እሁድ ከሰዓት በኋላ በዚህ በአዲሱ 7ኛ ለቡ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን መደበኛ የአምልኮ አገልግሎት በይፋ እንደሚቀጥል ታውቋል።
የኢትዮጵያ ምስጋና ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን ላለፉት 45 ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ ውስጥ በወንጌል አገልግሎት እንዲሁም በልማትና ማኅበራዊ አገልግሎቶች ላይ በስፋት ስትሳተፍ የቆየች ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ሁሉም ክልሎች ላይ ከ780 በላይ አጥቢያዎች እንዳሏት ከመግለጫው ለመረዳት ተችሏል።
ዶ/ር ጌታሁን ነሲቡ ለዚህ ታሪካዊ ስኬት መሳካት አምላካቸውን እያመሰገኑ፣ ክርስቲያኒቱ ጎን ለቆሙ አካላት በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። | 4 740 |
| 11 | የወልድያ ከተማ ለዶ/ር አረጋ ይርዳው የክብር ሐውልት አቆመ
#FastMereja I የወልድያ ከተማ አስተዳደር ለከተማዋ እድገት ላበረከቱት የላቀ አስተዋጽኦ ዶ/ር አረጋ ይርዳውን የክብር እውቅና ሰጥቷል። የዚሁ እውቅና አካል የሆነውና በከተማዋ አዳጎ አደባባይ የተገነባው የክብር ሐውልት ተመርቆ ለህዝብ እይታ በቅቷል።
የከተማ አስተዳደሩ ይህንን የክብር ሐውልት ያቆመው ዶ/ር አረጋ ይርዳው በትምህርት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በኢኮኖሚ ግንባታ ዘርፎች ላሳዩት አርአያነት ያለው አመራርና ለወልድያ ከተማ የልማት አሻራ ምልክት እንዲሆን ታስቦ መሆኑን ገልጿል። | 4 323 |
| 12 | 🏢 የሰመር ሪል እስቴት ልዩ የቤት ባለቤት የመሆን እድል!
በከተማችን እምብርት ቡልጋሪያ አደባባይ አካባቢ የሚገኙትን እጅግ ዘመናዊ፣ ሰፊ እና ምቹ የመኖሪያ አፓርታማዎችን በፈለጉት የካሬ አማራጭ ለሽያጭ አቅርበናል።
📐 የምርጫዎትን የካሬ እና የመኝታ አማራጮች ይምረጡ፦
🛏️ ባለ 1 መኝታ – 81 ካሬ
🛏️ ባለ 2 መኝታ – 111 እና 134 ካሬ
🛏️ ባለ 3 መኝታ – ከ168 ካሬ ጀምሮ
💰 እጅግ አስገራሚ ዋጋ እና ልዩ የክፍያ አማራጭ፦
💵 ዋጋ፦ በካሬ 89,000 ብር ብቻ!
📉 ቅድመ ክፍያ፦ 10% ብቻ በመክፈል ውል ያሰሩ!
🏦 የባንክ ብድር፦ 50% የባንክ ብድር የተመቻቸለት።
⏳ ጊዜ አይውሰዱ!
ይህ ታላቅ የዋጋ ቅናሽ የሚቆየው ለውስን ጊዜ ብቻ ስለሆነ፣ ቀድመው በመምጣት የዕድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ።
📍 ቦታ፦ ቡልጋሪያ አደባባይ አካባቢ
📞 ለበለጠ መረጃ አሁኑኑ ይደውሉልን፦0912355631
የህልምዎን ቤት ዛሬውኑ በእጅዎ ያስገቡ!
#Summer #AddisAbabaBusiness #apartmentforrentplantation #shopforsale #apartmentforrent #amibaraproperties #realestate #የንግድቦታ #Temerrealestate #teklehaymanotmall | 4 450 |
| 13 | አፍሪካ በደቡብ አፍሪካ ጮቤ ረገጠች
#FastMereja I ትናንት ምሽት በሜክሲኮ በተጀመረው የዓለም ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታ፣ ሜክሲኮ ደቡብ አፍሪካን በመግጠም ውድድሩን በድል ጀምራለች። ጨዋታው በሜዳ ላይ ከነበረው ፉክክር ባሻገር፣ በሶሻል ሚዲያ መድረኮች ላይ ከፍተኛ ትኩረት የሳበ ክስተት ሆኗል።
የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን መሸነፉን ተከትሎ፣ በርካታ አፍሪካዊያን በሶሻል ሚዲያ መድረኮች ደስታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ። ይህ ስሜት የመነጨው በደቡብ አፍሪካ ውስጥ በሚኖሩ ሌሎች አፍሪካዊያን ስደተኞች ላይ በቅርቡ በተፈጠረው “ከሀገራችን ውጡልን” ጥሪ እና ተያያዥ ፀረ-ስደተኞች እንቅስቃሴ ሳቢያ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ።
በሶሻል ሚዲያ አስተያየት ሰጪዎች እንደገለጹት፣ የደቡብ አፍሪካ ቡድን መሸነፍ በወቅቱ በሀገሪቱ እየታየ ካለው የመገፋፋት ስሜት ጋር በተያያዘ፣ በሌሎች አፍሪካዊያን ዘንድ እንደ አንድ የምሬት መግለጫ እየታየ ነው። | 5 103 |
| 14 | በዓለ ኀምሳን በአንድነት ለማክበር የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ጥሪ አቀረቡ!
#Fastmereja I የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ከአርሞኒየም ተሀድሶ ቤተክርስቲያን ጋር በመተባበር “ምስጋና ለመንፈስ ቅዱስ” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀውን የዘንድሮውን የበዓለ ኀምሳ ቀን ሰኔ 7 እንደሚከበር በዛሬዉ እለት በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ተገልጿል።
ይህ ታሪካዊ የበዓለ ኀምሳ ቀን በዓል የፊታችን እሁድ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ጀምሮ በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም አዳራሽ በታላቅ ድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል።
የያሬድ መንገድ ተሀድሶ ቤተክርስቲያን መጋቢ የሆኑት ፓስተር ሄኖክ መንግስቱ በሰጡት ማብራሪያ፣ በዓሉ አማኞች በጋራ ሆነው መንፈስ ቅዱስን የሚያመሰግኑበትና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ግንዛቤያቸውን የሚያሳድጉበት መሆኑን ገልጸዋል።
ፓስተር ሄኖክ አክለውም ቀደም ሲል በየግል ቤተክርስቲያኑ ይከበር የነበረው ይህ በዓል ዘንድሮ ግን በጋራና በአንድነት እንዲከበር መታቀዱን አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ተወካይ ፓስተር አሸብር ከተማ በበኩላቸው ይህ በዓል የአንድ ጊዜ ክስተት ወይም ስነ-ስርዓት (ceremony) ብቻ ሳይሆን፣ ዓመቱን ሙሉ ሊታሰብና ሊከበር የሚገባው ታላቅ በዓል ነው” ብለዋል።
የጥንቷ ቤተክርስቲያን በ24 ዓመታት ውስጥ መላውን ዓለም በወንጌል መድረስ የቻለችው በመንፈስ ቅዱስ መውረድ ምክንያት ባገኘችው መለኮታዊ ጉልበት መሆኑን የጠቀሱት ፓስተር አሸብር፣ በዓለ ሃምሳ የዶክትሪን ጉዳይ ሳይሆን አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ቅድስናን እያወጁ የእግዚአብሔርን መንግስት ለማስፋትና ወንጌልን በጋራ ለመስራት የሚተጉበት መሆኑን አስገንዝበዋል።
እሁድ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም በአድዋ ሙዚየም አዳራሽ በሚከበረው በዚህ ታላቅ መንፈሳዊ መርሃ ግብር ላይ የእግዚአብሔር ቃል ስብከት፣ ልዩ የዝማሬና የአምልኮ ጊዜ እንዲሁም ስለ በዓለ ሃምሳ ትርጉምና አስፈላጊነት የሚያተኩር የውይይት መድረክ እንደሚኖር አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
እንዲሁም ካውንስሉ መላው የወንጌል አማኞች ልዩነቶቻቸውን ወደ ጎን በመተው በዓሉን በአንድነት እንዲያከብሩ ጥሪ አቅርቧል። | 5 581 |
| 15 | በቀጣይ አመት ለክልሎች የሚሰራጨው የበጀት ድጎማ
ምንጭ፦ ኢትዮጵያን ኢንሳይደር | 5 793 |
| 16 | "እርሻችን አሁንም ስራ ላይ ነው!! በመላው ኢትዮጵያ ባሉ ሱቆቻችን ሽንኩርት 95-110 በደረጃ እየሸጥን ነው። አየሩን ጨምሮ ብዙ አስቸጋሪ ጊዜ ብናሳልፍም ከዚህም በታች እንዲቀንስ ሰራተኞቻችን እንቅልፍ አጥተው እየሰሩ ነው።" በረከት ገበሬዋ ከአየርላንድ | 5 908 |
| 17 | 🏢 የሰመር ሪል እስቴት ልዩ የቤት ባለቤት የመሆን እድል!
በከተማችን እምብርት ቡልጋሪያ አደባባይ አካባቢ የሚገኙትን እጅግ ዘመናዊ፣ ሰፊ እና ምቹ የመኖሪያ አፓርታማዎችን በፈለጉት የካሬ አማራጭ ለሽያጭ አቅርበናል።
📐 የምርጫዎትን የካሬ እና የመኝታ አማራጮች ይምረጡ፦
🛏️ ባለ 1 መኝታ – 81 ካሬ
🛏️ ባለ 2 መኝታ – 111 እና 134 ካሬ
🛏️ ባለ 3 መኝታ – ከ168 ካሬ ጀምሮ
💰 እጅግ አስገራሚ ዋጋ እና ልዩ የክፍያ አማራጭ፦
💵 ዋጋ፦ በካሬ 89,000 ብር ብቻ!
📉 ቅድመ ክፍያ፦ 10% ብቻ በመክፈል ውል ያሰሩ!
🏦 የባንክ ብድር፦ 50% የባንክ ብድር የተመቻቸለት።
⏳ ጊዜ አይውሰዱ!
ይህ ታላቅ የዋጋ ቅናሽ የሚቆየው ለውስን ጊዜ ብቻ ስለሆነ፣ ቀድመው በመምጣት የዕድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ።
📍 ቦታ፦ ቡልጋሪያ አደባባይ አካባቢ
📞 ለበለጠ መረጃ አሁኑኑ ይደውሉልን፦0912355631
የህልምዎን ቤት ዛሬውኑ በእጅዎ ያስገቡ!
#Summer #AddisAbabaBusiness #apartmentforrentplantation #shopforsale #apartmentforrent #amibaraproperties #realestate #የንግድቦታ #Temerrealestate #teklehaymanotmall | 5 887 |
| 18 | ለ17 ዓመታት ያለ ትክክለኛ ፈቃድ አውሮፕላን ሲያበር የነበረው ኤር ካናዳ ፓይለት በቁጥጥር ስር ዋለ
#FastMereja I የቀድሞ የኤር ካናዳ ፓይለት ትክክለኛ የካፒቴንነት ፈቃድ ሳይኖረው ለ17 ዓመታት ያህል በሺዎች የሚቆጠሩ መንገደኞችን በንግድ በረራዎች ሲያጓጉዝ በመቆየቱ በቁጥጥር ስር መዋሉን የካናዳ ፖሊስ አስታወቀ። ጄፍሪ ዎል የተባለው የ59 ዓመት ፓይለት እ.ኤ.አ ከ2009 ጀምሮ በሀሰተኛ ሰነድ ሲያበር እንደነበር የተደረሰበት ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከማጭበርበር ጋር የተያያዙ ሰባት የወንጀል ክሶች ተመስርተውበታል።
ፖሊስ እንዳለው ተከሳሹ ከ1998 ጀምሮ በድርጅቱ ውስጥ በፓይለትነት ሲሰራ የቆየ ቢሆንም፣ በ2009 ወደ ዋና አብራሪነት (ካፒቴን) ካደገበት ጊዜ ጀምሮ ለቦይንግ አውሮፕላኖች የሚፈለገውን ከፍተኛ የበረራ ፈቃድ ሳይኖረው በሀሰተኛ ሰነድ 900 ያህል የአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ በረራዎችን አድርጓል። ድርጊቱ ባለፈው ዓመት በተደረገ መደበኛ ግምገማ የሰነድ አለመጣጣም በመታየቱ በምርመራ የተደረሰበት ሲሆን፣ ኤር ካናዳ ግለሰቡን ወዲያውኑ ከስራ ማገዱን ገልጿል።
ድርጅቱ በሰጠው መግለጫ ፓይለቱ መደበኛ የንግድ በረራ ፈቃድ የነበረው በመሆኑ የመንገደኞች ደህንነት ለአደጋ ተጋልጦ እንደማያውቅና ሁሉም አብራሪዎች በየስድስት ወሩ የብቃት ማረጋገጫ ስልጠና እንደሚወስዱ አስታውቋል። እንዲሁም በሌሎች አብራሪዎች ላይ በተደረገ ድንገተኛ ኦዲት ምንም አይነት ተመሳሳይ ችግር እንዳልተገኘ ድርጅቱ ጨምሮ ገልጿል። | 5 414 |
| 19 | ሚድሮክ የ80 ሚሊዮን ዶላር ታሪካዊ ስምምነት ተፈራረመ
#FastMereja I ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ እና ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) በኬንያ ናይሮቢ ከተማ የ80 ሚሊዮን አሜሪካን ዶላር የረጅም ጊዜ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱን የሚድሮክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል አሕመድ እና የIFC የአፍሪካ ቀጠና ምክትል ፕሬዚዳንት ኢትዮጲስ ተፈራ የፈረሙት ሲሆን፣ የተገኘው የገንዘብ ድጋፍ በዋናነት ታዋቂውን ሸራተን አዲስ ሌግዠሪ ኮሌክሽን ሆቴልን በዘመናዊ መልኩ ለማደስ እና በሸራተን ደረጃ አዲስ ተጨማሪ ሆቴል ለመገንባት ይውላል።
ይህ ከፍተኛ የፋይናንስ አጋርነት የሀገሪቱን የሆስፒታሊቲ እና ቱሪዝም ዘርፍ ከማዘመን ባለፈ፣ ከ9,400 በላይ ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆኑ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን በተለይም ለወጣቶችና ለሴቶች እንደሚፈጥር ተገልጿል። አቶ ጀማል አሕመድ አጋርነቱ ቀጣይነት ላለው የሀገር ውስጥ ሥራ ዕድል ፈጠራ ያለውን ሚና ሲያጎሉ፣ የIFC ምክትል ፕሬዚዳንት በበኩላቸው ስምምነቱ የሚድሮክን የአገልግሎት ጥራት ለማሳደግ ታስቦ የተደረገ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP32) ለማስተናገድ መመረጧን ተከትሎ ሚድሮክ ግዙፍ የሆቴል ማስፋፊያና የእድሳት ስራዎችን በከፍተኛ ፍጥነት እያከናወነ ይገኛል። ከእነዚህም መካከል በሚሊኒየም አዳራሽ ቅጥር ግቢ የ”Moxy by Marriott”፣ በመሀመድያ የመኖሪያ መንደር የ”Four Points by Sheraton” እና በአፍሪካ ህብረት አጠገብ የ”Westin Addis” ሆቴሎች ግንባታ በስፋት እየተካሄደ ይገኛል።
በተጨማሪም በቅርቡ ግሩፑን የተቀላቀለው ዋቢ ሸበሌ ሆቴል ታሪካዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ ወደ “Autograph Collection by Marriott” ደረጃ የማደስ ስራው የተጀመረ ሲሆን፣ በባህርዳር፣ ጅማ፣ ሃዋሳ እና በላንጋኖ ሳቫና ሪዞርት ተመሳሳይ ዓለም አቀፍ የሆቴል ፕሮጀክቶች በመገንባት ላይ ናቸው። በአሁኑ ወቅት ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በማኑፋክቸሪንግ፣ ግብርና፣ ማዕድን፣ ንግድና ሆስፒታሊቲ ዘርፎች ላይ በመሰማራት ከ80 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩ ይታወቃል። | 5 298 |
| 20 | የትግራይ ወጣቶች ክልሉን ለቀዉ እየወጡ ነዉ
#FastMereja I በትግራይ ክልል ያለውን የጦርነት ሥጋት በመሸሽ በርካታ ወጣቶች ክልሉን ለቀው በመውጣት ላይ መሆናቸው እየተነገረ ነው፡፡አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ የሰጡ የክልሉ ወጣቶች እና በክልሉ ያለውን ፖለቲካዊ ሁናቴ በቅርበት የሚከታተሉት ወገኖች እንደሚሉት ማህበረሰቡ ተደጋግሞ በሚመጣው ጦርነት መሰላቸቱን ይናገራሉ።
በትግራይ እየተካሄደ ባለው የጦርነት ዝግጅት ምክንያት አጠቃላይ ማህበረሰቡም ሆነ ወጣቱ እጅግ አስቸጋሪ ጊዜን እያሳለፈ ይገኛል ሲል አስተያየቱን ለዶይቼ ቬለ ያጋራው አንድ የመቐለ ነዋሪ ወጣት፤ “በተለይም ሺራሮ አከባቢ ከሰሞኑ የተወሰደው የድሮን ጥቃት እርምጃ ድንጋጤን ፈጥሯል” የሚለው ወጣቱ ከዚሁ የተነሳ አሁን ላይ በርካታ ወጣት ወደ አዲስ አበባ እና ሌሎችም መሃል አገር አከባቢ በመሸሽ በተጨማሪ ጦርነት ላለመሳተፍ ጥረት እያደረገ ይገኛል ነው ያለው፡፡ “በክልሉ በተለይም ከመቀሌ ውጪ ባሉ አከባቢዎች ላይ ወጣቱ ወደ አስገዳጅ የጦርነት ምልመላ እየገባ ነው” የሚለው ወጣቱ ከዚሁ የተነሳ የተቻለው ወጣት በሙሉ ትግራይ ለቆ ለመውጣት የተቻለውን ሁሉ እያደረገ ነው ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል፡፡
ሌላው የመቀሌ ከተማ ነዋሪ የሆነው ወጣትም ባከለው ተመሳሳይ አስተያየቱ፤ “ወጣቱ አሁን መማር መስራት እንጂ ወደ ጦርነት መግባት አይፈልግም” በማለት እሱ ራሱን ጨምሮ በርካታ ወጣት “የማይከፈለው ዋጋ እየከፈለ ከክልሉ እየሸሸ እየወጣ” መሆኑን ገልጿል፡፡ ወጣቱ እራሱም ከክልሉ ለመውጣት የአውሮፕላን ቲኬት ቆርጦ እየተጠባበቀ መሆኑን ነው የገለጸው፡፡
በትግራይ ክልል እንደ ከዚህ ቀደሙ ደም አፋሳሹ ጦርነት ወጣቶች ወደ ግጭት ከመግባት ይልቅ የጦርነት ሃሳቡን የማይገዙት ለምን ይሆን ተብለው የተጠየቁት ወጣቶቹ፤ “በቂ ምክንያት የለንም” ይላሉ፡፡ “ትናንት ከደፈረን ሃይል ጋር መስራት አልፈልግም” ሲል አስተያየቱን ሰጠው አንደኛው ወጣት፤ ወጣቱ በዚህ የሚቀየር የለም የሚለውን ሃሳብ በመያዝ ከጦርነቱ መሸሽን ምርጫው ማድረጉን ነው ያመለከተው፡፡ ሌላኛውም አስተያየቱን ያከለው የመቀሌ ከተማ ነዋሪው ወጣት፤ “ወጣቱ ካለፈው ጦርነት በመማር አሁን ሰላም ወዳለበት ሄዶ ሰርቶ መለወጥ ነው ፍላጎቱ” ሲል ሃሳቡን አጋርቷል፡፡
በትግራይ የጦርነት አይቀሬነት አሁን አሁን ጎልቶ እየመጣ መሆኑን በማስረዳት አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ የሰጡ የክልሉን ፖለቲካዊ ሁናቴዎች በቅርበት የሚከታተሉት ፖለቲከኛ መስፍን ደሳለኝ እንደሚሉት አሁን አሁን አጠቃላይ እንደማህበረሰብም ሆነ ወጣቱ ክፍል በትግራይ ባለው የፖለቲካዊ ሁኔታዎች ላይ ተስፋ እየቆረጠ መጥቷል ነው የሚሉት፡፡ “በተለይም ከፕሪቶሪያው የቅጭት ማቆም ስምምነቱ በኋላ የትግራይ ፖለቲካ ተከፋፍሎ ታይቷል” ያሉን ፖለቲከኛው፤ በተለይም ወጣቱ ሃይል ተጨማሪ ዋጋ የመክፈል ፍላጎትን ፈጽሞ እያሳየም አይደለም ነው ያሉት፡፡ በመሆኑ አቅም ያላቸው ወጣቶችም ሆኑ ሌሎችም እየተጋገዙ ከክልሉ በመውጣት ሌሎች አከባቢዎች ላይ ሄደው ስራ ፈጥረው ህይወታቸውን የመምራት አዝማሚያዎችን እያሳዩ ስለመምጣታቸውም በሰፊው እየተስተዋለ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡
ዘገባው የዶይቼ ቬለ ነው! | 5 963 |
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
