es
Feedback
Ethio - ዜና 🇪🇹

Ethio - ዜና 🇪🇹

Ir al canal en Telegram

የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot

Mostrar mĂĄs

📈 Análisis del canal de Telegram Ethio - ዜና 🇪🇹

El canal Ethio - ዜና 🇪🇹 (@ethio_zena23) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 105 164 suscriptores, ocupando la posición 72 en la categoría Fotos y el puesto 277 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 105 164 suscriptores.

SegĂşn los Ăşltimos datos del 22 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los Ăşltimos 30 dĂ­as la variaciĂłn de miembros fue de -2 760, y en las Ăşltimas 24 horas de -76, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificaciĂłn: No verificado
  • Tasa de interacciĂłn (ER): El promedio de interacciĂłn de la audiencia es 3.26%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 2.23% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicaciĂłn recibe en promedio 3 429 visualizaciones. En el primer dĂ­a suele acumular 2 346 visualizaciones.
  • Reacciones e interacciĂłn: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicaciĂłn es 25.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot”

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (Ăşltimos datos recibidos el 23 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analĂ­tica demuestra que la audiencia interactĂşa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categorĂ­a Fotos.

105 164
Suscriptores
-7624 horas
-6407 dĂ­as
-2 76030 dĂ­as

Carga de datos en curso...

Nube de Etiquetas
Sin datos
ÂżAlgĂşn problema? Por favor, actualice la pĂĄgina o contacte a nuestro gerente de soporte.
Menciones Entrantes y Salientes
---
---
---
---
---
---
Atraer Suscriptores
julio '26
julio '260
en 4 canales
junio '26
+64
en 9 canales
Get PRO
mayo '26
+129
en 11 canales
Get PRO
abril '26
+74
en 12 canales
Get PRO
marzo '26
+2 127
en 10 canales
Get PRO
febrero '26
+8
en 4 canales
Get PRO
enero '26
+2 108
en 54 canales
Get PRO
diciembre '25
+2 159
en 81 canales
Get PRO
noviembre '25
+4 183
en 51 canales
Get PRO
octubre '25
+4 892
en 3 canales
Get PRO
septiembre '25
+7 709
en 3 canales
Get PRO
agosto '25
+5 654
en 1 canales
Get PRO
julio '25
+6 591
en 2 canales
Get PRO
junio '25
+6 975
en 0 canales
Get PRO
mayo '25
+7 406
en 1 canales
Get PRO
abril '25
+7 575
en 1 canales
Get PRO
marzo '25
+8 127
en 1 canales
Get PRO
febrero '25
+7 065
en 3 canales
Get PRO
enero '25
+7 127
en 1 canales
Get PRO
diciembre '24
+9 050
en 4 canales
Get PRO
noviembre '24
+11 169
en 2 canales
Get PRO
octubre '24
+14 487
en 4 canales
Get PRO
septiembre '24
+12 613
en 0 canales
Get PRO
agosto '24
+11 528
en 5 canales
Get PRO
julio '24
+4 340
en 29 canales
Get PRO
junio '24
+871
en 5 canales
Get PRO
mayo '24
+1 669
en 5 canales
Get PRO
abril '24
+1 824
en 7 canales
Get PRO
marzo '24
+3 958
en 6 canales
Get PRO
febrero '24
+1 530
en 2 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
23 julio0
22 julio0
21 julio0
20 julio0
19 julio0
18 julio0
17 julio0
16 julio0
15 julio0
14 julio0
13 julio0
12 julio0
11 julio0
10 julio0
09 julio0
08 julio0
07 julio0
06 julio0
05 julio0
04 julio0
03 julio0
02 julio0
01 julio0
Publicaciones del Canal
ኢትዮ ቴሌኮም በ2018 ዓመት 215.8 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ 👉 በቴሌብር 4.9 ትሪሊዮን ብር የገንዘብ ዝውውር ተደርጓል የኢትዮ ቴሌኮም በተጠናቀቀዉ የ2018 በበጀት ዓመት 215.8
ኢትዮ ቴሌኮም በ2018 ዓመት 215.8 á‰˘áˆŠá‹¨áŠ• ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ      👉 በቴሌብር 4.9 ትሪሊዮን ብር የገንዘብ ዝውውር ተደርጓል   የኢትዮ ቴሌኮም በተጠናቀቀዉ የ2018 በበጀት ዓመት 215.8ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘት ችሏል። ይህዉ ገቢዉ ካለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ33.2 በመቶ áŒ­áˆ›áˆŹ አሳይቷል። በዚህም 99.2 በመቶ እቅዱን ማሳካት ችሏል።   የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሼል አስፈጻሚ ወይዘሮ ፍሬህይወት ታምሩ እንደገለጹት ከተገኘው ጠቅላላ ገቢ ውስጥ የኢንተርኔት አገልግሎት 31.1 በመቶ፣ ድምጽ 23.5 በመቶ፣ ቴሌብር 3.6 በመቶ እና ዲቫይስ 4 በመቶ ድርሻ ይዘዋል።የኢትዮ ቴሌኮም ዲጂታል ፋይናንስ መድረክ የሆነው ቴሌብር በ2018 በጀት ዓመት 60.5 ሚሊዮን ደንበኞች ቁጥር የደረሰ ሲሆን  ይህ የዲጂታል ክፍያና የፋይናንስ አገልግሎት ተደራሽነት እየጨመረ መሆኑ እንደሚያሳይ መናገራቸዉን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል፡፡   በበጀት ዓመቱ በቴሌብር 4.9 ትሪሊዮን ብር የገንዘብ ዝውውር መከናወኑን የገለጹት ዋና ሼል አስፈጻሚዋ አገልግሎቱ በ410 ሺህ ኤጀንቶች እና ከ31 ባንኮች ጋር በትብብር እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህም የቴሌብር አገልግሎት በመላ ሀገሪቱ በስፋት መዳረሱንና ከባንክ ሥርዓቱ ጋር በተቀናጀ መልኩ እየሰራ መሆኑን ያመላክታል።  

2
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ስለ ህወሃት‼️👇 ህወሓት አዲስ ነገር ለመስማት እና ለማየት ፍላጎት የለውም'-ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር)‼️ ህወሃት ወደ መሬት መውረድ በማይችል ያረጀ አስተሳሰብና ሀሳብ የታጠረ ድርጅት ነው። ይህ ብቻ ሳይሆን ራሱን ወደ አደጋ የሚከቱ እርምጃዎችን ሲወስድ ቆይቷል፣አሁንም እየወሰደ ይገኛል። ይህ ደግሞ ጤና ያለው ድርጅት ባህሪ አይደለም። አዲስ ነገር ለመስማት ጆሮ የለውም፣አዲስ ነገር ለማየት አይን የለውም፣ፍላጎትም የለውም። አዲስ ነገር ለመስማት ዝግጁ ያልሆነ ድርጅት ለህዝቡ ጥሩ ስራ ይሰራል ተብሎ አይጠበቅም። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትናንት ሐምሌ 15 ስለህወሓት በትግርኛ ከተናገሩት ተተርጉሞ የተወሰደ
575
3
የጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች ሥራ ሊያቆሙ መሆኑን አሣውቀዋል። የኢትዮጵያ የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች ማህበር የታሪፍ ማሻሻያ ጥያቄን ምላሽ ባለማግኘቱ አባላቱ ከገበያ ሊወጡ እንደሚችሉ ተናግረዋ
የጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች ሥራ ሊያቆሙ መሆኑን አሣውቀዋል። የኢትዮጵያ የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች ማህበር የታሪፍ ማሻሻያ ጥያቄን ምላሽ ባለማግኘቱ አባላቱ ከገበያ ሊወጡ እንደሚችሉ ተናግረዋል። ​ማህበሩ ከትራንስፖርት፣ ንግድና ነዳጅ ቁጥጥር መስሪያ ቤቶች ጋር ጥናት አቅርቦ ምላሽ ማጣቱንም ገልጿል። አሁን ባለው የነዳጅ ፍላጎት መጨመር፣ የመለዋወጫ እቃዎች ዋጋ መናር እና ድርብ ጫናዎች ምክንያት ሥራውን መቀጠል አስቸጋሪ ሆኗልም ተብሏል። ​በተጨማሪም ባለንብረቶች እውቅናቸው ውጪ በሹፌሮች በሚፈጸም የኮንትሮባንድ ወንጀል ምክንያት ተሽከርካሪና ነዳጅ እየተወረሰባቸው እንደሚገኝም ተናግረዋል።
706
4
መረጃ‼️ 59 በመቶው የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንድ ክፍል ቤት ውስጥ እንደሚኖር የፌደራል ስታትስቲክስ አገልግሎት ከአውሮፓዊያኑ 2024 እስከ 2025 ያካሄደው ጥናት አመለከተ። የመኖሪያ ቤቶች መጨናነቅ በተለይ በከተሞች አካባቢ እንዲባባስ ካደረጉት ምክንያቶች አንዱ፣ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገው ያልተቋረጠ ፍልሠት መኾኑን ዋዜማ ከጥናቱ ላይ ተመልክታለች። በተጠቀሠው ጊዜ ውስጥ በጥናቱ 31 በመቶ የሴቶች እና 24 በመቶ የወንዶች ፍልሠት ተመዝግቧል። የተሻለ የሥራ ዕድል፣ ትምህርትና የመሠረተ ልማት አቅርቦትን ፍለጋ የሚደረገው ፍልሠት፣ በከተሞች ላይ የመኖሪያ ቤት አቅርቦት ላይ ከፍተኛ ጫና በመፍጠሩ በባለ ሁለት ክፍል ቤቶች የሚኖሩ ዜጎች ድርሻ 31 በመቶ መድረሱን ሪፖርቱ ያትቷል። @Seledadotio @Seledadotio
713
5
#የውቅያኖስ ወለል ምስጢር፦ የዓለምን ኢንተርኔት የሚያንቀሳቅሱት የባህር ስር መስመሮች❗❗ ብዙዎቻችን በየቀኑ በስልካችን የምንጠቀመው ኢንተርኔት፣ ማህበራዊ ሚዲያ እና ዓለም አቀፍ የመረጃ ፍሰት በሳተ+4
#የውቅያኖስ ወለል ምስጢር፦ የዓለምን ኢንተርኔት የሚያንቀሳቅሱት የባህር ስር መስመሮች❗❗ ብዙዎቻችን በየቀኑ በስልካችን የምንጠቀመው ኢንተርኔት፣ ማህበራዊ ሚዲያ እና ዓለም አቀፍ የመረጃ ፍሰት በሳተላይት በኩል በአየር ላይ የሚጓዝ ቢመስለንም፣ እውነታው ግን ከዚህ እጅግ የራቀ ነው። የዓለማችን 99 በመቶ የሚያህለው የኢንተርኔት ዳታ የሚጓዘው በጨለማውና በጥቁሩ የውቅያኖሶች ወለል ላይ በተዘረጉ የፋይበር ኦፕቲክስ መስመሮች በኩል ነው። በዓለም ዙሪያ በውቅያኖሶች ስር የተዘረጉት እነዚህ ከ550 በላይ ንቁ ካብሎች ከ1.4 ሚሊዮን ኪሎሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ሲሆን፣ በሴኮንድ በመቶ ቴራባይት የሚቆጥር ዳታ የሚያስተላልፉት እነዚህ መስመሮች እንደተጠበቀው ትልቅ ሳይሆኑ የመጠጥ ውሃ ማስተላለፊያ ወይም የጓሮ ቧንቧ ያህል ውፍረት ብቻ ያላቸው ናቸው። በኬብሉ መሃል የሚገኙት የመረጃ ማስተላለፊያ የብርጭቆ ጫፎች ወይም ቀጫጭን የብርጭቆ ገመዶች የሰው ፀጉር ያህል ቀጫጭን ሲሆኑ፣ መረጃን በብርሃን ፍጥነት ያጓጉዛሉ።እነዚህ መስመሮች ለአደጋ ተጋላጭነታቸው ከፍተኛ በመሆኑ በየዓመቱ በአማካይ ከ100 በላይ የመቆረጥ አደጋዎች ያጋጥሟቸዋል ተብሏል። የመርከብ መልሕቆች መሬት ሲቧጥጡ፣ የባህር ስር የመሬት መንቀጥቀጥ ሲከሰት ወይም አልፎ አልፎ የሻርክ አሳዎች ሲነክሷቸው መስመሮቹ የሚበጠሱ ሲሆን፣ አንድ የባህር ስር ኬብል ከተቋረጠ የሙሉ ሀገር ወይም ቀጠና ኢንተርኔት ሙሉ በሙሉ ሊቋረጥ ወይም ሊዘገይ ይችላል ነው የተባለው። በአሁኑ ወቅት እንደ Google፣ Meta፣ Microsoft እና Amazon ያሉ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የራሳቸውን የባህር ስር ኬብሎች በመዘርጋት የዓለምን የመረጃ መረብ በባለቤትነት እየተቆጣጠሩት ይገኛሉ። @Addis_Reporter @Addis_Reporter
1 388
6
የዝናብ ሁኔታ‼️ በቀጣዮቹ አስር ቀናት የተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ። በቀጣዮቹ አስር ቀናት የተለያዩ የሀገሪቷ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለጸ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ መሰረት፣ ከሐምሌ 14 እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት አስር ቀናት ውስጥ የዝናብ ሁኔታን የሚፈጥሩ ሁኔታዎች የበለጠ እየተጠናከሩ እንደሚሄዱ አሰታወቋል። በዚህም መሰረት በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን፣ መካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ እና ምስራቅ የሀገሪቷ ክፍሎች የተሻለ የዝናብ ሥርጭት መጠን  ይኖራቸዋል። በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብና ሰሜን የሀገራችን አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ገልጿል። በተጨማሪም በመካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ፣ ምስራቅ እና ደቡብ የሀገሪቷ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያመለክታሉ ብሏል። በሚቀጥሉት አስር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አብዛኛዎቹ አካባቢዎች  ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም ነው ኢንስቲትዩቱ የጠቆመው። በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን እና በመካከለኛው የሀገሪቷ አካባቢዎች ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ገልጿል። በተጨማሪም በኤሊ ዳር፣ ዱብቲ፣ ሰመራ፣ ቡሬ፣ አሳይታ፣ ሁንዱፎ፣ ገዋኔ፣ ሚሌ፣ ዳሊፋጊ፣ አይሻ፣ ጉሊና፣ አዋሽ አርባ፣ ባቲ፣ ዶሎ አዶ፣ ዳዋ፣ አሶሶ፣ ጎዴ፣ ቋራ፣ አዋሽ ፈንታሌ፣ ጭፍራ፣ ላሬ፣ መተሀራ እና፣ ላሬ፣ ፉኙዶ አካባቢዎች  ከሚኖረው የቀን ከፍተኛ የፀሀይ ሀይል ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ሙቀት ይኖራቸዋል። ኢንስቲትዩቱ በቀጣይ ቀናት የሚኖረውን መልካም አጋጣሚዎችን ለመጠቀም እና የሚጠበቁ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ለመከላከል የግብርና ሚቲዎሮሎጂ ምክር ሀሳብን ከወዲሁ መተግበር እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።
1 522
7
የዝናብ ሁኔታ‼️ በቀጣዮቹ አስር ቀናት የተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ። በቀጣዮቹ አስር ቀናት የተለያዩ የሀገሪቷ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለጸ። ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ መሰረት፣ ከሐምሌ 14 እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት አስር ቀናት ውስጥ የዝናብ ሁኔታን የሚፈጥሩ ሁኔታዎች የበለጠ እየተጠናከሩ እንደሚሄዱ አሰታወቋል። በዚህም መሰረት በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን፣ መካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ እና ምስራቅ የሀገሪቷ ክፍሎች የተሻለ የዝናብ ሥርጭት መጠን  ይኖራቸዋል። በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብና ሰሜን የሀገራችን አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ገልጿል። በተጨማሪም በመካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ፣ ምስራቅ እና ደቡብ የሀገሪቷ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያመለክታሉ ብሏል። በሚቀጥሉት አስር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አብዛኛዎቹ አካባቢዎች  ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም ነው ኢንስቲትዩቱ የጠቆመው። በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን እና በመካከለኛው የሀገሪቷ አካባቢዎች ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ገልጿል። በተጨማሪም በኤሊ ዳር፣ ዱብቲ፣ ሰመራ፣ ቡሬ፣ አሳይታ፣ ሁንዱፎ፣ ገዋኔ፣ ሚሌ፣ ዳሊፋጊ፣ አይሻ፣ ጉሊና፣ አዋሽ አርባ፣ ባቲ፣ ዶሎ አዶ፣ ዳዋ፣ አሶሶ፣ ጎዴ፣ ቋራ፣ አዋሽ ፈንታሌ፣ ጭፍራ፣ ላሬ፣ መተሀራ እና፣ ላሬ፣ ፉኙዶ አካባቢዎች  ከሚኖረው የቀን ከፍተኛ የፀሀይ ሀይል ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ሙቀት ይኖራቸዋል። ኢንስቲትዩቱ በቀጣይ ቀናት የሚኖረውን መልካም አጋጣሚዎችን ለመጠቀም እና የሚጠበቁ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ለመከላከል የግብርና ሚቲዎሮሎጂ ምክር ሀሳብን ከወዲሁ መተግበር እንደሚያስፈልግ አሳስቧል። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23
1
8
ሞባይል ስልክ የሚቀሙ ወንጀል ፈፃሚዎችን እና ተቀባዩ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋሉ ሳሙኤል ደሳለኝ፣ ዮሴፍ መስፍን እና ዳግም አድነው የተባሉ ወንጀል ፈፃሚዎች ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ/ም ሁለት ግለሰቦ+4
ሞባይል ስልክ የሚቀሙ ወንጀል ፈፃሚዎችን እና ተቀባዩ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋሉ ሳሙኤል ደሳለኝ፣ ዮሴፍ መስፍን እና ዳግም አድነው የተባሉ ወንጀል ፈፃሚዎች ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ/ም ሁለት ግለሰቦችን በስለት በማስፈራራት ሞባይል ስልካቸውን ቀምተው ይሰወራሉ፡፡ የወንጀሉ መፈፀም ሪፖርት የደረሰው የቤተል አካባቢ ፖሊስ መምሪያ ወንጀል ፈፃሚዎችን ለመያዝ በክትትል ላይ እያለ ወንጀል ፈፃሚዎቹ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ/ም በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ልዩ ቦታው አንፎ ሮም ሰፈር ተብሎ ከሚጠራ አካባቢ አንድን ግለሰብ በስለት በማስፈራራት ሞባይል ስልክ ሲቀሙ በፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል፡፡ ፖሊስ ወንጀል ፈፃሚዎቹ የቀሙትን ሞባይል ስልክ እና የሚገዛውን የሌባ ተቀባይ ነጅብ ረሺድን በቁጥጥር ስር አውሎታል፡፡ መምሪያው የህግ አግባብን ተከትሎ በግለሰቡ የሞባይል ስልክ መሸጫ ሱቅ ባደረገው ብርበራ ከሦስቱ ግለሰቦች የተቀሙትን ሞባይል ስልኮች ማግኘቱን አስታውቋል፡፡ ከእነዚ ንብረቶች በተጨማሪ ግለሰቡ ማስረጃ ሊያቀርብባቸው ያልቻለ 3 ላፕቶፖች፣2 ታፕሌት እና 6 ስማርት ስልኮችም ተገኝተዋል፡፡ በተለያዩ ጊዚያት ላፕቶፕና ሞባይል የተሰረቀባቸው ግለሰቦች አስፈላጊውን ማስረጃ በማቅረብ ቤቴል አካባቢ ፖሊስ መምሪያ በአካል ቀርበው ንብረታቸውን መረከብ እንደሚችሉ ፖሊስ መምሪያው አስታውቋል፡፡ የህዝብን ሰላም የሚያውኩና ህጋዊ የንግድ ፍቃድን እንደሽፋን በማድረግ የተሰረቁ ንብረቶችን የሚቀበሉ ግለሰቦች በህግ አግባብ ለማስጠየቅ ህብረተሰቡ ጥቆማ ከመስጠት ጀምሮ እያደረገ ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል ፖሊስ ጥሪውን አቅርቧል። ምንጭ:- አአ ፖሊስ https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23
1 708
9
የድሮን ጥቃት‼️ በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ “በመካነ ሰላም ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም በድሮን ጥቃት የመነኮሳት ህይወት አለፈ”‼️ በዛሬው ዕለት ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም በምዕራብ ወሎ በመካነ ሰ+3
የድሮን ጥቃት‼️ በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ “በመካነ ሰላም ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም በድሮን ጥቃት የመነኮሳት ህይወት አለፈ”‼️ በዛሬው ዕለት ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም በምዕራብ ወሎ በመካነ ሰላም በዓባይ ወንዝ ዳርቻ በሚገኘው ዓባይ ገዳመ አስቀጤስ የሰማእቷ ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት ምክንያት በገዳሙ ውስጥ የሚኖሩ 2 ሴቶች ወዲያው ህይወታቸው ማለፉን እና ሌሎች መቁሰላቸውን ምንጮች ገልጸዋል። ጥቃቱ የተፈፀመው በአካባቢው የፋኖ ሀይሎች ከትመዋል በሚል ነው ተብሏል። ሰላም ለሀገራችን🕊🕊 @Seledadotio @Seledadotio
2 372
10
በሀዋሳ ከተማ 120 ሊትር ነዳጅ የሚይዝ ህገ-ወጥ ታንከር በባጃጁ ላይ አስገጥሞ ሲንቀሳቀስ የነበረው ሹፌር ተያዘ ​በሀዋሳ ከተማ በባለ ሦስት እግር (ባጃጅ) ተሽከርካሪ ላይ ህገ-ወጥ ተጨማሪ ታንከር+1
በሀዋሳ ከተማ 120 ሊትር ነዳጅ የሚይዝ ህገ-ወጥ ታንከር በባጃጁ ላይ አስገጥሞ ሲንቀሳቀስ የነበረው ሹፌር ተያዘ   ​በሀዋሳ ከተማ በባለ ሦስት እግር (ባጃጅ) ተሽከርካሪ ላይ ህገ-ወጥ ተጨማሪ ታንከር በመግጠም ነዳጅ ሲቀዳ የነበረው ሹፌር በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን የከተማው ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።ግለሰቡ  በባለ ሦስት እግር (ባጃጅ) ተሽከርካሪ ውስጥ የወንበር ቅርጽ ያለው ህገ-ወጥ ታንከር አስገጥሞ መገኘቱ ተገልጿል።   ​የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ምክትል አዛዥና የማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል ኃላፊ ኮማንደር አብስራ አመሎ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለፁት ግለሰቡ  በተሰራው ህገ-ወጥ ታንከር ውስጥ 120 ሊትር ነዳጅ የተገኘ ሲሆን ባጃጁ በመደበኛ ሁኔታ መያዝ የሚችለው 8 ሊትር ብቻ  ነዉ።   ​በዚህም  የባጃጅ ሹፌሩን ጨምሮ በጋራ ሲሰሩ የነበሩ የነዳጅ ማደያው ሰራተኞች በቁጥጥር ስር ውለዋል።ፖሊስ ከንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ጋር በመተባበር ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝ ገልጾ የክስ መዝገብ እየተዘጋጀ እንደሚገኝ አስረድቷል። መሰል ህገ-ወጥ የነዳጅ ዝውውርና የማከማቸት ተግባር በሀገር ኢኮኖሚ እና በህብረተሰብ ደህንነት ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያስከትል በመሆኑ  በድርጊቱ ላይ በሚሳተፉ አካላት ላይ የሚወሰደው ህጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ኮማንደር አብስራ አመሎ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።   በሳምራዊት ስዩም @Seledadotio @Seledadotio
2 409
11
ኤሌክትሮኒክስ ላይ ረጅም ሰዓት የሚያሳልፉ የልዩ ፍላጎት ልጆች የንግግር እና የመግባባት ክህሎታቸውን ሊጎዳ እንደሚችል ተነገረ ልዩ ፍላጎት የሚያስፈልጋቸው ታዳጊዎች በቤት ውስጥ ረጅም ጊዜን በሚያሳል
ኤሌክትሮኒክስ ላይ ረጅም ሰዓት የሚያሳልፉ  የልዩ ፍላጎት  ልጆች የንግግር እና የመግባባት ክህሎታቸውን ሊጎዳ እንደሚችል ተነገረ   ልዩ ፍላጎት የሚያስፈልጋቸው ታዳጊዎች በቤት ውስጥ ረጅም ጊዜን በሚያሳልፋበት የክረምት ወቅት ላይ ቴሌቭዥንን ጨምሮ ከሌሎች የኤሌክትሮኒክስ ነገሮች መራቅ ይኖርባቸዋል። ልዩ ፍላጎት ያላቸው ልጆች ለአእምሮ እድገታቸው  እንቅስቃሴ ያሏቸው ጨዋታዎችን እንዲጫወቱ ፣ በአእምሮ የሚሰሩና የሚገጣጠሙ  መጫዎቻዎች ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ማገዝ  ያስፈልጋል ሲሉ የፍቅር ኢትዮጵያ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ብሔራዊ ማህበር ዋና ስራ አስኪያጅ  ወ/ሮ ሸዋጌጥ ክብረት  ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ  ገልጸዋል።   ልዩ ፍላጎት  ያላቸው ታዳጊዎች  ትምህርት ቤት ስለሄዱ ብቻ ውጤታማ መሆን ስለማይችሉ ብቻቸውን ከማዋል ይልቅ ልጆች ያሉባቸው እንዲሁም ሊደሰቱባቸው የሚችሉባቸው ቦታዎች ላይ እንዲሆኑ ማድረግ የመግባባት ክህሎታቸውን ለማዳበር ያግዛል። ከቴሌቪዥን እና ከሞባይል ጋር ረጅም ሰዓትን የሚያጠፉ የልዩ ፍላጎት ልጆች ከንግግር እና ከመግባባት ችሎታ ወደ ኋላ እንዲቀሩ ያደርጋቸዋል።   ይህ አይነቱ ችግር ያለባቸው ልጆች  ንዴታቸውን የሚገልጹት ራሳቸውን በመጉዳት ሊሆን ስለሚችል ከልጅነት ጀምሮ በሚኖራቸው አስተዳደግ  ላይ ከፍተኛ  ትኩረት ማድረግ እና ሊያናድዳቸዉ የሚችሉ ነገሮችን መቅረፍ  ያስፈልጋል።ዋና ስራ አስኪያጇ አክለውም ወላጆች ይህን ህመም የማመን ችግር እንደሚገጥማቸው ገልፀው፤ ስልጠና በመውሰድ  ለዚህ ጉዳይ መፍትሄ ማግኘት እንደሚችሉ  ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።   @Seledadotio @Seledadotio
2 463
12
37 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ለኢራን ጦርነት ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። አሜሪካ በኢራን እያካሄደች ባለው ጦርነት እስካሁን 37.5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ማድረጓ ተገለጸ። በኢራን እና በአሜሪካ መካ
37 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ለኢራን ጦርነት ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። አሜሪካ በኢራን እያካሄደች ባለው ጦርነት እስካሁን 37.5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ማድረጓ ተገለጸ። በኢራን እና በአሜሪካ መካከል ከተቀሰቀሰ ወዲህ ዋሽንግተን  እስከ አሁን 37 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ማድረጓን የአሜሪካው የመከላከያ ሚኒስትር ፒት ሄግሴት አስታውቀዋል። ይህ ወጪ ባለፈው ግንቦት ወር ከተደረገው ግምት ጋር ሲነጻጸር የ8 ቢሊዮን ዶላር ጭማሪ ያሳየ ሲሆን፣ ሚኒስትሩ አሁንም ተጨማሪ በጀት እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል። ሚኒስትሩ በሴኔት የገንዘብ ድልድል ኮሚቴ ፊት ቀርበው በሰጡት ማብራሪያ ፣ ኮንግረሱ አስቸኳይ ተጨማሪ በጀት ካላፀደቀ የሀገሪቱ ወታደራዊ ስልጠናዎች ሊስተጓጎሉ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል። ሄግሴት ለመከላከያ መስሪያ ቤታቸው (ፔንታጎን) 87 ቢሊዮን ዶላር እንዲፈቀድ የጠየቁ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 67 ቢሊዮን ዶላሩ በመካከለኛው ምስራቅ ለሚካሄዱ ወታደራዊ ዘመቻዎች የሚውል መሆኑን ገልጸዋል። ይህ የበጀት ጥያቄ የቀረበው በመካከለኛው ምስራቅ ሶስት የአሜሪካ ወታደሮች በተገደሉበት እና ጦርነቱ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ በደረሰበት ወቅት ነው። ዋይት ሃውስ ለቀጣዩ የበጀት ዓመት 1 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ዶላር ለፔንታገን እንዲመደብ መጠየቁ የሚታወስ ሲሆን፣ ይህም የአሜሪካን ወታደራዊ ወጪ በታሪክ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ያደርሰዋል። አሜሪካ በኢራን ላይ ለ11 ተከታታይ ቀናት ጥቃት መሰንዘሯን የቀጠለች ሲሆን ኢራንም በአሜሪካ እና በአጋሮቿ ላይ የአጸፋ ጥቃት በመሰንዘር ላይ ትገኛለች። ዘገባው የቢቢሲ ነው
2 443
13
ገላሽን በሙቅ ውሃ አጥብሻለሁ በማለት የ2 ዓመት ህፃን እንዳትጮህ አፉን በማፈን የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ በአሶሳ ዞን ባምባሲ ወረዳ ኤዳ ዳቡስ ቀበሌ ጎጥ አንድ በ
ገላሽን በሙቅ ውሃ አጥብሻለሁ በማለት የ2 ዓመት ህፃን እንዳትጮህ አፉን በማፈን የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ      በአሶሳ ዞን ባምባሲ ወረዳ ኤዳ ዳቡስ ቀበሌ ጎጥ አንድ በሚባል አካባቢ ነው የወንጀል ድርጊቱ ተፈፅሟል።የባምባሲ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤት አዛዥ ኮማንደር ሀሩን ሄረላ ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት ተከሳሽ አወድ አልሀሪብ የተባለ ሲሆን ግንቦት 16 ቀን  2018 ከረፍዱ 4፡00 ሰዓት የወንጀል ድርጊቱን ፈፅሟል። የ2 አመት ህፃን የሆነችውን ገላሽን በሙቅ ውሃ አጥብሻለሁ በማለት እናቷ ውሃ ልትቀዳ መሄዷን በማረጋገጥ ወደ ራሱ መኖሪያ ቤት ከወሰዳት በኋላ አፏን በማፈን የአስገድዶ መድፈር  ወንጀል መፈፀሙን ተናግረዋል፡፡  የባምባሲ ወረዳ ፖሊስ የምርመራ መዝገቡን በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች በማስደገፍ ለዐቃቤ ህግ ያቀርባል  ዐቃቤ ህጉም ተከሳሹ በኢፌዲሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 627(1) ስር በተደነገገው የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ክስ በመመስረት ለባምባሲ ወረዳ ፍርድ ቤት ያቀርባል፡፡   ፍርድ ቤቱ የቀረበውን ማስረጃ ከመረመረ በኋላ ተከሳሹን ጥፋተኛ መሆኑን በማረጋገጥ የወንጀሉን ክብደትና የቅጣት ማክበጃ እና ማቅለያ ሁኔታዎችን በማገናዘብ ሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. በዋለው ችሎት በ19 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል ሲሉ ኮማንደር ሀሩን ሄረላ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡   @Seledadotio @Seledadotio
2 308
14
ከንቲባ አዳነች አቤቤ፤ ታጥረው የተተዉ መሬቶች ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወሰድ አስታወቁ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ ታጥረው ያለምንም አገልግሎት የተቀመጡ መሬቶችን በማጣራት በሚቀጥሉት ሁለት ወ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ፤ ታጥረው የተተዉ መሬቶች ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወሰድ አስታወቁ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ ታጥረው ያለምንም አገልግሎት የተቀመጡ መሬቶችን በማጣራት በሚቀጥሉት ሁለት ወራት ውስጥ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስድ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታውቀዋል። ከንቲባዋ ይህን ያስታወቁት፣ በከተማ አስተዳደሩ የአምስት ዓመት ስትራቴጂካዊ ዕቅድና የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ ማጠቃለያ መድረክ ላይ ነው። እንደ ከንቲባዋ ገለጻ፣ አዲስ አበባ መሬት ታጥሮ የሚቀመጥባት ከተማ መሆን እንደሌለባት ቀደም ሲል የተደረሰውን ስምምነት የሚጥሱ አካላት ተጨማሪ ዕድል እንደማይሰጣቸው አስጠንቅቀዋል። በሌላ በኩል፣ በከተማዋ የሰላምና ደህንነት ሁኔታ የተረጋጋ መሆኑን በመግለጽ፣ በርካታ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶች ያለ የደህንነት ችግር በሰላም መጠናቀቃቸውን አስታውሰዋል። በተጨማሪም፣ የከተማዋ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓት መዘመኑ ውጤታማ መሆኑን ጠቅሰው፣ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ጥናት መሠረት የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በአፍሪካ ከተመረጡ ስድስት ምርጥ ከተሞች መካከል በአሠራር ደረጃ አንደኛ መሆኑን ገልጸዋል። ከንቲባ አዳነች አክለውም፣ በጤናው ዘርፍ የሕክምና ባለሙያዎች የሙያ ሥነ-ምግባርና የአገልግሎት ጥራት መሻሻሉን፣ ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ የጤና አገልግሎትና የመሠረተ ልማት ሥራዎችም ከቀደሙት ዓመታት ጋር ሲነጻጸሩ በእጥፍ መጨመራቸውን ገልጸዋል። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23
2 198
15
እየተባባሰ የመጣው የኦንላይን ማጭበርበር በማኅበራዊ ሚዲያዎች " ውጭ ሀገር እኖራለሁ " ፣ " የፍቅር ጓደኛ እፈልጋለሁ " ወይም " ለሞት የሚዳርግ በሽታ ይዞኛል፤ ሀብቴን የሚያስተዳድርልኝ ታማኝ ሰ
እየተባባሰ የመጣው የኦንላይን ማጭበርበር በማኅበራዊ ሚዲያዎች " ውጭ ሀገር እኖራለሁ " ፣ " የፍቅር ጓደኛ እፈልጋለሁ " ወይም " ለሞት የሚዳርግ በሽታ ይዞኛል፤ ሀብቴን የሚያስተዳድርልኝ ታማኝ ሰው እፈልጋለሁ " በሚሉ መልዕክቶች ተጠቃሚዎችን በማታለል እስከ 500 ሺህ ብር የሚደርስ ገንዘብ እያሳጡ መሆናቸውን የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል። በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ እጣወርቅ ተስፋዬ ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ እንዳሉት፣ አጭበርባሪዎቹ ፌስቡክ፣ ዋትስአፕ እና ቴሌግራምን በመጠቀም የውሸት ማንነት በመፍጠር ተጎጂዎችን ያጠምዳሉ። " ሀብታም ነኝ "፣ " ከሁሉም አንተን/አንቺን መርጫለሁ " የሚሉ መልዕክቶችም ከሚጠቀሙባቸው የማጭበርበሪያ ስልቶች መካከል ናቸው። ከተጎጂዎች ጋር ግንኙነታቸውን ካጠናከሩ በኋላ፣ ሌላ ሰው በተለየ ስልክ ቁጥር በመደወል " የላክነው ዕቃ ጉምሩክ ደርሷል፤ ነገር ግን ዶላር ወይም ወርቅ ስላለበት ክፍያ ያስፈልጋል " በማለት የታሸገ ዕቃ ፎቶ በመላክ ገንዘብ እንዲልኩ እንደሚያደርጉ ተገልጿል። በዚህ ሂደት ከ500 ሺህ እና ከዛ በላይ ገንዘብ ሰዎች እንደሚጭበረበሩ አመልክተዋል። ወ/ሮ እጣወርቅ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች " ከሁሉም ሰው እኔ ለምን ተመረጥኩ ? " እና " ለስጦታ እንዴት ክፍያ ይጠየቃል ? " የሚሉ ጥያቄዎችን ራሳቸውን በመጠየቅ ከመሰል ማጭበርበሮች እንዲጠነቀቁ አሳስበዋል። የኦንላይን ማጭበርበር ወንጀል እየተስፋፋ ሲሆን፣ ባለፈው የበጀት ዓመት ብቻ ከ100 ሺህ ብር በላይ ጉዳት ያስከተሉ ከ80 በላይ ዋና ዋና የክስ መዝገቦች በፌዴራል ዐቃቤ ሕግ መመስረታቸው ተገልጿል። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23
2 415
16
የጦርነት ድባብ እየተሰማ ነው‼️ በትግራይ ክልል በሁሉም አካባቢዎች ከባለፈው እሁድ ጀምሮ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል። ህዝቡ እና ወጣቱ ለጦርነት እንዲዘጋጅ ከሁሉም አመራሮች በግልጽ እየተነገራቸው ይ
የጦርነት ድባብ እየተሰማ ነው‼️ በትግራይ ክልል በሁሉም አካባቢዎች ከባለፈው እሁድ ጀምሮ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል። ህዝቡ እና ወጣቱ ለጦርነት እንዲዘጋጅ ከሁሉም አመራሮች በግልጽ እየተነገራቸው ይገኛል። የህወሓት ዋና ፀሃፊ የሆኑት ፈትለወርቅ (ሞንጀሪኖ) ባካሄዱበት ስብሰባ ላይ "አዲስ አበባ እስክንገባ ብቻችን እንሸከመዋለን ማለት አይደለም፥ ብዙ አጋሮች አሉን ። አዲስ አበባ በር ላይ ፋኖ እና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር አለ ስለዚህ ብዙ ወዳጆች አሉን” ሲሉ ተደምጠዋል። ሰላም ለሀገራችን🕊🕊 @Seledadotio @Seledadotio
2 596
17
የነዳጅ ቦቴ ባለንብረቶች ከገበያ ልንወጣ እንችላለን ሲሉ ስጋታቸውን ገለጹ በሀገሪቱ እየታየ ያለው የመለዋወጫ እቃዎች ዋጋ መናር እና የታሪፍ ማሻሻያ አለመደረግ አክሳሪ እንደሆነባቸው የገለጹት የፈሳሽ
የነዳጅ ቦቴ ባለንብረቶች ከገበያ ልንወጣ እንችላለን ሲሉ ስጋታቸውን ገለጹ በሀገሪቱ እየታየ ያለው የመለዋወጫ እቃዎች ዋጋ መናር እና የታሪፍ ማሻሻያ አለመደረግ አክሳሪ እንደሆነባቸው የገለጹት የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች፣ ችግሩ ባልተፈታበት ሁኔታ ስራቸውን ማስቀጠል አስቸጋሪ እንደሆነባቸው በመግለጽ ከገበያው የመወጣት ስጋት እንደደቀነባቸው አስታወቁ። የኢትዮጵያ የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች ማህበር የነዳጅ ፍላጎት እድገትን እና የወጡ ወጪዎችን ያገናዘበ የታሪፍ ማሻሻያ እንዲደረግ ተደጋጋሚ ጥናቶችን ማቅረቡን ያስታወሰ ቢሆንም፣ በመንግስት በኩል ግን እስካሁን አዎንታዊ ምላሽ ማግኘት አለመቻሉን ገልጿል። የማህበሩ ፕሬዝደንት አቶ ፀጋ አስማረ እንደገለጹት፤ ጥናቱ ዝም ብሎ የቀረበ ሳይሆን ከነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን፣ ከትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር እንዲሁም ከንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከተወጣጡ ባለሙያዎች ጋር በጥጋቢ ሁኔታ ተጠናቆ የቀረበ ነው። ሆኖም ምላሽ በመዘግየቱ አባላቱ ለአላስፈላጊ ክሳራ መዳረጋቸውን አብራርተዋል። ከታሪፍ መዘገየት በተጨማሪ ባለንብረቶች ሌላ አጣብቂኝ ውስጥ የከተታቸው አሽከርካሪዎች ከባለንብረቱ እውቅና ውጪ በሚፈጽሙት የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ ምክንያት ተሽከርካሪዎች እና ነዳጅ የመወረስ እርምጃ እየተወሰደባቸው ይገኛል ብለዋል። ይህንን ተከትሎ የኢትዮጵያ የፈሳሽ ጭነት ትራንስፖርት ባለንብረቶች ማህበር አባላቱን በመጥራት በዘርፉ በተደቀኑ ዘርፈ-ብዙ ችግሮች እና በቀጣይ የጋራ አቋሞች ዙሪያ የምክክር ስብሰባ አካሂዷል። @Seledadotio @Seledadotio
2 743
18
በአከራይ ተከራይ ውል መፈጸም የሌለባቸው እና የተከለከሉ ተግባራት... በአዲስ አበባ ከተማ በአከራይ ተከራይ ውል የሚከተሉትን ተግባራት መፈጸም የተከለከለ ነው። 👉የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ሳያስመዘ
በአከራይ ተከራይ ውል መፈጸም የሌለባቸው እና የተከለከሉ ተግባራት... በአዲስ አበባ ከተማ በአከራይ ተከራይ ውል የሚከተሉትን ተግባራት መፈጸም የተከለከለ ነው። 👉የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ሳያስመዘግቡ መከራየትና ማከራየት፤ 👉በአከራይ ወይም ተከራይ ቸልተኝነት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል በአዋጁ የተቀመጠውን የጊዜ ገደብ አሳልፎ ማስመዝገብ፤ 👉የመኖሪ ቤት ኪራይ ውል እድሳት አለማስመዝገብ፤ 👉በአዋጁ ከተፈቀደው አግባብ ውጪ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ፤ 👉አዋጁ ከሚፈቅደው ውጪ የውል ዘመን ሳይጠናቀቅ ከቤት ማስወጣት፤ 👉በአዋጁ የተቀመጠውን የማስታወቂያ ወይም የማስጠንቀቂያ ጊዜ ሳይሰጥ ውል ማቋረጥ፤ 👉አዋጁ ላይ ከተቀመጠው መጠን በላይ የቅድመ ክፍያ እንዲፈፀም ማስገደድ፤ 👉 በባንክ ወይሞ በሌላ ሕጋዊ በሆነ የኤሌክትሮኒክ የክፍያ ስርዓት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ክፍያ አለመፈፀም 👉 ቀደም ሲል ሲከራይ የቆየ የመኖሪያ ቤት ወይም ግንባታው ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ አዲስ መኖሪያ ቤት ያለአገልግሎት እንዲቀመጥ ማድረግ እና ፤ 👉በአዋጁ ለአከራይ የተሰጠውን ማበረታቻ ያለአግባብ ለመጠቀሞ ሀሰተኛ መረጃ ወይም ማስረጃ ማቅረብ የተከለከለ መሆኑን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ @Seledadotio @Seledadotio
2 939
19
የኤሌክትሪክ ፍጆታ ማባዣ ጭማሪ ተደርጓል። ለመኖሪያ ቤት ከተያዘው ወር ሀምሌ ጀምሮ እስከ መስከረም ወር የሚፈፀም የኤሌክትሪክ ፍጆታ ታሪፍ ክፍያ ከላይ ተያይዟል። @Seledadotio @Seledado
የኤሌክትሪክ ፍጆታ ማባዣ ጭማሪ ተደርጓል። ለመኖሪያ ቤት ከተያዘው ወር ሀምሌ ጀምሮ እስከ መስከረም ወር የሚፈፀም የኤሌክትሪክ ፍጆታ ታሪፍ ክፍያ ከላይ ተያይዟል። @Seledadotio @Seledadotio
2 800
20
በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ከ1ሺህ 4መቶ በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል ተባለ ‎ ‎በሳምንቱ ውስጥ በተደረገ 6 ዙር በረራ 1ሺህ 4መቶ 81 ኢትዮጵያዊያን መመለሳቸ
በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ከ1ሺህ 4መቶ በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል ተባለ ‎ ‎በሳምንቱ ውስጥ በተደረገ 6 ዙር በረራ 1ሺህ 4መቶ 81 ኢትዮጵያዊያን መመለሳቸዉን የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታዉቋ፡፡ የተመለሱት 8መቶ79 ወንዶች፣ 5መቶ54 ሴቶች እና 48 ጨቅላ ህፃናት ሲሆኑ፤ከተመላሾች መካከል 82 እድሜያቸው ከአስራ ስምንት አመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ይገኙበታል። ‎ ‎መስከረም 5/ 2018 በተጀመረው ዜጎችን ወደ ሀገር ቤት የመመለስ ስራ እስካሁን ከ87 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገር መመለስ ተችሏል ተብሏል። ‎ ‎ሚኒስቴሩ ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ የማድረግ እና ከቤተሰብ ጋር የማቀላቀል ስራ ከሚመለከታቸው ባለድርሻና አጋር አካላት ጋር በመተባበር በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አስታዉቋል፡፡ ‎ ‎በተጨማሪም መደበኛ ባልሆነ ፍልሰት ወደ ተለያዩ ሀገራት ሄደው የሚመለሱ የፍልሰት ተጎጂዎችን ለመደገፍና መልሶ ለማቋቋም የሚያስችሉ ተግባራትን በትብብር እያከናወነ መሆኑን ገልጿ‎ል፡፡ ‎ወደፊትም በህገወጥ የሰዎች ዝውውር አስከፊነት ዙሪያ ህብረተሰቡን ለማስገንዘብ፣ መደበኛ ያልሆነ ፍልሰትን ለመከላከልና ደህንነቱ የተጠበቀ ፍልሰትን ለማበረታታት ሚኒስቴሩ የጀመራቸውን ስራዎች አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግሯል፡፡ @Seledadotio @Seledadotio
3 024