es
Feedback
Ethio - ዜና 🇪🇹

Ethio - ዜና 🇪🇹

Ir al canal en Telegram

የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot

Mostrar mĂĄs

📈 Análisis del canal de Telegram Ethio - ዜና 🇪🇹

El canal Ethio - ዜና 🇪🇹 (@ethio_zena23) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 105 240 suscriptores, ocupando la posición 72 en la categoría Fotos y el puesto 276 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 105 240 suscriptores.

SegĂşn los Ăşltimos datos del 21 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los Ăşltimos 30 dĂ­as la variaciĂłn de miembros fue de -2 821, y en las Ăşltimas 24 horas de -87, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificaciĂłn: No verificado
  • Tasa de interacciĂłn (ER): El promedio de interacciĂłn de la audiencia es 3.26%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 2.24% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicaciĂłn recibe en promedio 3 438 visualizaciones. En el primer dĂ­a suele acumular 2 355 visualizaciones.
  • Reacciones e interacciĂłn: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicaciĂłn es 26.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot”

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (Ăşltimos datos recibidos el 22 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analĂ­tica demuestra que la audiencia interactĂşa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categorĂ­a Fotos.

105 240
Suscriptores
-8724 horas
-6967 dĂ­as
-2 82130 dĂ­as

Carga de datos en curso...

Nube de Etiquetas
Sin datos
ÂżAlgĂşn problema? Por favor, actualice la pĂĄgina o contacte a nuestro gerente de soporte.
Menciones Entrantes y Salientes
---
---
---
---
---
---
Atraer Suscriptores
julio '26
julio '260
en 3 canales
junio '26
+64
en 9 canales
Get PRO
mayo '26
+129
en 11 canales
Get PRO
abril '26
+74
en 12 canales
Get PRO
marzo '26
+2 127
en 10 canales
Get PRO
febrero '26
+8
en 4 canales
Get PRO
enero '26
+2 108
en 54 canales
Get PRO
diciembre '25
+2 159
en 81 canales
Get PRO
noviembre '25
+4 183
en 51 canales
Get PRO
octubre '25
+4 892
en 3 canales
Get PRO
septiembre '25
+7 709
en 3 canales
Get PRO
agosto '25
+5 654
en 1 canales
Get PRO
julio '25
+6 591
en 2 canales
Get PRO
junio '25
+6 975
en 0 canales
Get PRO
mayo '25
+7 406
en 1 canales
Get PRO
abril '25
+7 575
en 1 canales
Get PRO
marzo '25
+8 127
en 1 canales
Get PRO
febrero '25
+7 065
en 3 canales
Get PRO
enero '25
+7 127
en 1 canales
Get PRO
diciembre '24
+9 050
en 4 canales
Get PRO
noviembre '24
+11 169
en 2 canales
Get PRO
octubre '24
+14 487
en 4 canales
Get PRO
septiembre '24
+12 613
en 0 canales
Get PRO
agosto '24
+11 528
en 5 canales
Get PRO
julio '24
+4 340
en 29 canales
Get PRO
junio '24
+871
en 5 canales
Get PRO
mayo '24
+1 669
en 5 canales
Get PRO
abril '24
+1 824
en 7 canales
Get PRO
marzo '24
+3 958
en 6 canales
Get PRO
febrero '24
+1 530
en 2 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
22 julio0
21 julio0
20 julio0
19 julio0
18 julio0
17 julio0
16 julio0
15 julio0
14 julio0
13 julio0
12 julio0
11 julio0
10 julio0
09 julio0
08 julio0
07 julio0
06 julio0
05 julio0
04 julio0
03 julio0
02 julio0
01 julio0
Publicaciones del Canal
የድሮን ጥቃት‼️ በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ “በመካነ ሰላም ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም በድሮን ጥቃት የመነኮሳት ህይወት አለፈ”‼️ በዛሬው ዕለት ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም በምዕራብ ወሎ በመካነ ሰ
+3
የድሮን ጥቃት‼️ በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ “በመካነ ሰላም ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም በድሮን ጥቃት የመነኮሳት ህይወት አለፈ”‼️ በዛሬው ዕለት ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም በምዕራብ ወሎ በመካነ ሰላም በዓባይ ወንዝ ዳርቻ በሚገኘው ዓባይ ገዳመ አስቀጤስ የሰማእቷ ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት ምክንያት በገዳሙ ውስጥ የሚኖሩ 2 ሴቶች ወዲያው ህይወታቸው ማለፉን እና ሌሎች መቁሰላቸውን ምንጮች ገልጸዋል። ጥቃቱ የተፈፀመው በአካባቢው የፋኖ ሀይሎች ከትመዋል በሚል ነው ተብሏል። ሰላም ለሀገራችን🕊🕊 @Seledadotio @Seledadotio

2
በሀዋሳ ከተማ 120 ሊትር ነዳጅ የሚይዝ ህገ-ወጥ ታንከር በባጃጁ ላይ አስገጥሞ ሲንቀሳቀስ የነበረው ሹፌር ተያዘ ​በሀዋሳ ከተማ በባለ ሦስት እግር (ባጃጅ) ተሽከርካሪ ላይ ህገ-ወጥ ተጨማሪ ታንከር+1
በሀዋሳ ከተማ 120 ሊትር ነዳጅ የሚይዝ ህገ-ወጥ ታንከር በባጃጁ ላይ አስገጥሞ ሲንቀሳቀስ የነበረው ሹፌር ተያዘ   ​በሀዋሳ ከተማ በባለ ሦስት እግር (ባጃጅ) ተሽከርካሪ ላይ ህገ-ወጥ ተጨማሪ ታንከር በመግጠም ነዳጅ ሲቀዳ የነበረው ሹፌር በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን የከተማው ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።ግለሰቡ  በባለ ሦስት እግር (ባጃጅ) ተሽከርካሪ ውስጥ የወንበር ቅርጽ ያለው ህገ-ወጥ ታንከር አስገጥሞ መገኘቱ ተገልጿል።   ​የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ምክትል አዛዥና የማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል ኃላፊ ኮማንደር አብስራ አመሎ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለፁት ግለሰቡ  በተሰራው ህገ-ወጥ ታንከር ውስጥ 120 ሊትር ነዳጅ የተገኘ ሲሆን ባጃጁ በመደበኛ ሁኔታ መያዝ የሚችለው 8 ሊትር ብቻ  ነዉ።   ​በዚህም  የባጃጅ ሹፌሩን ጨምሮ በጋራ ሲሰሩ የነበሩ የነዳጅ ማደያው ሰራተኞች በቁጥጥር ስር ውለዋል።ፖሊስ ከንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ጋር በመተባበር ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝ ገልጾ የክስ መዝገብ እየተዘጋጀ እንደሚገኝ አስረድቷል። መሰል ህገ-ወጥ የነዳጅ ዝውውርና የማከማቸት ተግባር በሀገር ኢኮኖሚ እና በህብረተሰብ ደህንነት ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያስከትል በመሆኑ  በድርጊቱ ላይ በሚሳተፉ አካላት ላይ የሚወሰደው ህጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ኮማንደር አብስራ አመሎ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።   በሳምራዊት ስዩም @Seledadotio @Seledadotio
1 701
3
ኤሌክትሮኒክስ ላይ ረጅም ሰዓት የሚያሳልፉ የልዩ ፍላጎት ልጆች የንግግር እና የመግባባት ክህሎታቸውን ሊጎዳ እንደሚችል ተነገረ ልዩ ፍላጎት የሚያስፈልጋቸው ታዳጊዎች በቤት ውስጥ ረጅም ጊዜን በሚያሳል
ኤሌክትሮኒክስ ላይ ረጅም ሰዓት የሚያሳልፉ  የልዩ ፍላጎት  ልጆች የንግግር እና የመግባባት ክህሎታቸውን ሊጎዳ እንደሚችል ተነገረ   ልዩ ፍላጎት የሚያስፈልጋቸው ታዳጊዎች በቤት ውስጥ ረጅም ጊዜን በሚያሳልፋበት የክረምት ወቅት ላይ ቴሌቭዥንን ጨምሮ ከሌሎች የኤሌክትሮኒክስ ነገሮች መራቅ ይኖርባቸዋል። ልዩ ፍላጎት ያላቸው ልጆች ለአእምሮ እድገታቸው  እንቅስቃሴ ያሏቸው ጨዋታዎችን እንዲጫወቱ ፣ በአእምሮ የሚሰሩና የሚገጣጠሙ  መጫዎቻዎች ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ማገዝ  ያስፈልጋል ሲሉ የፍቅር ኢትዮጵያ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ብሔራዊ ማህበር ዋና ስራ አስኪያጅ  ወ/ሮ ሸዋጌጥ ክብረት  ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ  ገልጸዋል።   ልዩ ፍላጎት  ያላቸው ታዳጊዎች  ትምህርት ቤት ስለሄዱ ብቻ ውጤታማ መሆን ስለማይችሉ ብቻቸውን ከማዋል ይልቅ ልጆች ያሉባቸው እንዲሁም ሊደሰቱባቸው የሚችሉባቸው ቦታዎች ላይ እንዲሆኑ ማድረግ የመግባባት ክህሎታቸውን ለማዳበር ያግዛል። ከቴሌቪዥን እና ከሞባይል ጋር ረጅም ሰዓትን የሚያጠፉ የልዩ ፍላጎት ልጆች ከንግግር እና ከመግባባት ችሎታ ወደ ኋላ እንዲቀሩ ያደርጋቸዋል።   ይህ አይነቱ ችግር ያለባቸው ልጆች  ንዴታቸውን የሚገልጹት ራሳቸውን በመጉዳት ሊሆን ስለሚችል ከልጅነት ጀምሮ በሚኖራቸው አስተዳደግ  ላይ ከፍተኛ  ትኩረት ማድረግ እና ሊያናድዳቸዉ የሚችሉ ነገሮችን መቅረፍ  ያስፈልጋል።ዋና ስራ አስኪያጇ አክለውም ወላጆች ይህን ህመም የማመን ችግር እንደሚገጥማቸው ገልፀው፤ ስልጠና በመውሰድ  ለዚህ ጉዳይ መፍትሄ ማግኘት እንደሚችሉ  ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።   @Seledadotio @Seledadotio
2 099
4
37 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ለኢራን ጦርነት ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። አሜሪካ በኢራን እያካሄደች ባለው ጦርነት እስካሁን 37.5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ማድረጓ ተገለጸ። በኢራን እና በአሜሪካ መካ
37 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ለኢራን ጦርነት ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። አሜሪካ በኢራን እያካሄደች ባለው ጦርነት እስካሁን 37.5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ማድረጓ ተገለጸ። በኢራን እና በአሜሪካ መካከል ከተቀሰቀሰ ወዲህ ዋሽንግተን  እስከ አሁን 37 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ማድረጓን የአሜሪካው የመከላከያ ሚኒስትር ፒት ሄግሴት አስታውቀዋል። ይህ ወጪ ባለፈው ግንቦት ወር ከተደረገው ግምት ጋር ሲነጻጸር የ8 ቢሊዮን ዶላር ጭማሪ ያሳየ ሲሆን፣ ሚኒስትሩ አሁንም ተጨማሪ በጀት እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል። ሚኒስትሩ በሴኔት የገንዘብ ድልድል ኮሚቴ ፊት ቀርበው በሰጡት ማብራሪያ ፣ ኮንግረሱ አስቸኳይ ተጨማሪ በጀት ካላፀደቀ የሀገሪቱ ወታደራዊ ስልጠናዎች ሊስተጓጎሉ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል። ሄግሴት ለመከላከያ መስሪያ ቤታቸው (ፔንታጎን) 87 ቢሊዮን ዶላር እንዲፈቀድ የጠየቁ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 67 ቢሊዮን ዶላሩ በመካከለኛው ምስራቅ ለሚካሄዱ ወታደራዊ ዘመቻዎች የሚውል መሆኑን ገልጸዋል። ይህ የበጀት ጥያቄ የቀረበው በመካከለኛው ምስራቅ ሶስት የአሜሪካ ወታደሮች በተገደሉበት እና ጦርነቱ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ በደረሰበት ወቅት ነው። ዋይት ሃውስ ለቀጣዩ የበጀት ዓመት 1 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ዶላር ለፔንታገን እንዲመደብ መጠየቁ የሚታወስ ሲሆን፣ ይህም የአሜሪካን ወታደራዊ ወጪ በታሪክ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ያደርሰዋል። አሜሪካ በኢራን ላይ ለ11 ተከታታይ ቀናት ጥቃት መሰንዘሯን የቀጠለች ሲሆን ኢራንም በአሜሪካ እና በአጋሮቿ ላይ የአጸፋ ጥቃት በመሰንዘር ላይ ትገኛለች። ዘገባው የቢቢሲ ነው
2 167
5
ገላሽን በሙቅ ውሃ አጥብሻለሁ በማለት የ2 ዓመት ህፃን እንዳትጮህ አፉን በማፈን የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ በአሶሳ ዞን ባምባሲ ወረዳ ኤዳ ዳቡስ ቀበሌ ጎጥ አንድ በ
ገላሽን በሙቅ ውሃ አጥብሻለሁ በማለት የ2 ዓመት ህፃን እንዳትጮህ አፉን በማፈን የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ      በአሶሳ ዞን ባምባሲ ወረዳ ኤዳ ዳቡስ ቀበሌ ጎጥ አንድ በሚባል አካባቢ ነው የወንጀል ድርጊቱ ተፈፅሟል።የባምባሲ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤት አዛዥ ኮማንደር ሀሩን ሄረላ ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት ተከሳሽ አወድ አልሀሪብ የተባለ ሲሆን ግንቦት 16 ቀን  2018 ከረፍዱ 4፡00 ሰዓት የወንጀል ድርጊቱን ፈፅሟል። የ2 አመት ህፃን የሆነችውን ገላሽን በሙቅ ውሃ አጥብሻለሁ በማለት እናቷ ውሃ ልትቀዳ መሄዷን በማረጋገጥ ወደ ራሱ መኖሪያ ቤት ከወሰዳት በኋላ አፏን በማፈን የአስገድዶ መድፈር  ወንጀል መፈፀሙን ተናግረዋል፡፡  የባምባሲ ወረዳ ፖሊስ የምርመራ መዝገቡን በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች በማስደገፍ ለዐቃቤ ህግ ያቀርባል  ዐቃቤ ህጉም ተከሳሹ በኢፌዲሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 627(1) ስር በተደነገገው የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ክስ በመመስረት ለባምባሲ ወረዳ ፍርድ ቤት ያቀርባል፡፡   ፍርድ ቤቱ የቀረበውን ማስረጃ ከመረመረ በኋላ ተከሳሹን ጥፋተኛ መሆኑን በማረጋገጥ የወንጀሉን ክብደትና የቅጣት ማክበጃ እና ማቅለያ ሁኔታዎችን በማገናዘብ ሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. በዋለው ችሎት በ19 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል ሲሉ ኮማንደር ሀሩን ሄረላ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡   @Seledadotio @Seledadotio
2 065
6
ከንቲባ አዳነች አቤቤ፤ ታጥረው የተተዉ መሬቶች ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወሰድ አስታወቁ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ ታጥረው ያለምንም አገልግሎት የተቀመጡ መሬቶችን በማጣራት በሚቀጥሉት ሁለት ወ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ፤ ታጥረው የተተዉ መሬቶች ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወሰድ አስታወቁ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ ታጥረው ያለምንም አገልግሎት የተቀመጡ መሬቶችን በማጣራት በሚቀጥሉት ሁለት ወራት ውስጥ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስድ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታውቀዋል። ከንቲባዋ ይህን ያስታወቁት፣ በከተማ አስተዳደሩ የአምስት ዓመት ስትራቴጂካዊ ዕቅድና የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማ ማጠቃለያ መድረክ ላይ ነው። እንደ ከንቲባዋ ገለጻ፣ አዲስ አበባ መሬት ታጥሮ የሚቀመጥባት ከተማ መሆን እንደሌለባት ቀደም ሲል የተደረሰውን ስምምነት የሚጥሱ አካላት ተጨማሪ ዕድል እንደማይሰጣቸው አስጠንቅቀዋል። በሌላ በኩል፣ በከተማዋ የሰላምና ደህንነት ሁኔታ የተረጋጋ መሆኑን በመግለጽ፣ በርካታ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ዝግጅቶች ያለ የደህንነት ችግር በሰላም መጠናቀቃቸውን አስታውሰዋል። በተጨማሪም፣ የከተማዋ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓት መዘመኑ ውጤታማ መሆኑን ጠቅሰው፣ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ጥናት መሠረት የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በአፍሪካ ከተመረጡ ስድስት ምርጥ ከተሞች መካከል በአሠራር ደረጃ አንደኛ መሆኑን ገልጸዋል። ከንቲባ አዳነች አክለውም፣ በጤናው ዘርፍ የሕክምና ባለሙያዎች የሙያ ሥነ-ምግባርና የአገልግሎት ጥራት መሻሻሉን፣ ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ የጤና አገልግሎትና የመሠረተ ልማት ሥራዎችም ከቀደሙት ዓመታት ጋር ሲነጻጸሩ በእጥፍ መጨመራቸውን ገልጸዋል። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23
1 983
7
እየተባባሰ የመጣው የኦንላይን ማጭበርበር በማኅበራዊ ሚዲያዎች " ውጭ ሀገር እኖራለሁ " ፣ " የፍቅር ጓደኛ እፈልጋለሁ " ወይም " ለሞት የሚዳርግ በሽታ ይዞኛል፤ ሀብቴን የሚያስተዳድርልኝ ታማኝ ሰ
እየተባባሰ የመጣው የኦንላይን ማጭበርበር በማኅበራዊ ሚዲያዎች " ውጭ ሀገር እኖራለሁ " ፣ " የፍቅር ጓደኛ እፈልጋለሁ " ወይም " ለሞት የሚዳርግ በሽታ ይዞኛል፤ ሀብቴን የሚያስተዳድርልኝ ታማኝ ሰው እፈልጋለሁ " በሚሉ መልዕክቶች ተጠቃሚዎችን በማታለል እስከ 500 ሺህ ብር የሚደርስ ገንዘብ እያሳጡ መሆናቸውን የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል። በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ እጣወርቅ ተስፋዬ ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ እንዳሉት፣ አጭበርባሪዎቹ ፌስቡክ፣ ዋትስአፕ እና ቴሌግራምን በመጠቀም የውሸት ማንነት በመፍጠር ተጎጂዎችን ያጠምዳሉ። " ሀብታም ነኝ "፣ " ከሁሉም አንተን/አንቺን መርጫለሁ " የሚሉ መልዕክቶችም ከሚጠቀሙባቸው የማጭበርበሪያ ስልቶች መካከል ናቸው። ከተጎጂዎች ጋር ግንኙነታቸውን ካጠናከሩ በኋላ፣ ሌላ ሰው በተለየ ስልክ ቁጥር በመደወል " የላክነው ዕቃ ጉምሩክ ደርሷል፤ ነገር ግን ዶላር ወይም ወርቅ ስላለበት ክፍያ ያስፈልጋል " በማለት የታሸገ ዕቃ ፎቶ በመላክ ገንዘብ እንዲልኩ እንደሚያደርጉ ተገልጿል። በዚህ ሂደት ከ500 ሺህ እና ከዛ በላይ ገንዘብ ሰዎች እንደሚጭበረበሩ አመልክተዋል። ወ/ሮ እጣወርቅ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች " ከሁሉም ሰው እኔ ለምን ተመረጥኩ ? " እና " ለስጦታ እንዴት ክፍያ ይጠየቃል ? " የሚሉ ጥያቄዎችን ራሳቸውን በመጠየቅ ከመሰል ማጭበርበሮች እንዲጠነቀቁ አሳስበዋል። የኦንላይን ማጭበርበር ወንጀል እየተስፋፋ ሲሆን፣ ባለፈው የበጀት ዓመት ብቻ ከ100 ሺህ ብር በላይ ጉዳት ያስከተሉ ከ80 በላይ ዋና ዋና የክስ መዝገቦች በፌዴራል ዐቃቤ ሕግ መመስረታቸው ተገልጿል። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23
2 169
8
የጦርነት ድባብ እየተሰማ ነው‼️ በትግራይ ክልል በሁሉም አካባቢዎች ከባለፈው እሁድ ጀምሮ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል። ህዝቡ እና ወጣቱ ለጦርነት እንዲዘጋጅ ከሁሉም አመራሮች በግልጽ እየተነገራቸው ይ
የጦርነት ድባብ እየተሰማ ነው‼️ በትግራይ ክልል በሁሉም አካባቢዎች ከባለፈው እሁድ ጀምሮ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል። ህዝቡ እና ወጣቱ ለጦርነት እንዲዘጋጅ ከሁሉም አመራሮች በግልጽ እየተነገራቸው ይገኛል። የህወሓት ዋና ፀሃፊ የሆኑት ፈትለወርቅ (ሞንጀሪኖ) ባካሄዱበት ስብሰባ ላይ "አዲስ አበባ እስክንገባ ብቻችን እንሸከመዋለን ማለት አይደለም፥ ብዙ አጋሮች አሉን ። አዲስ አበባ በር ላይ ፋኖ እና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር አለ ስለዚህ ብዙ ወዳጆች አሉን” ሲሉ ተደምጠዋል። ሰላም ለሀገራችን🕊🕊 @Seledadotio @Seledadotio
2 397
9
የነዳጅ ቦቴ ባለንብረቶች ከገበያ ልንወጣ እንችላለን ሲሉ ስጋታቸውን ገለጹ በሀገሪቱ እየታየ ያለው የመለዋወጫ እቃዎች ዋጋ መናር እና የታሪፍ ማሻሻያ አለመደረግ አክሳሪ እንደሆነባቸው የገለጹት የፈሳሽ
የነዳጅ ቦቴ ባለንብረቶች ከገበያ ልንወጣ እንችላለን ሲሉ ስጋታቸውን ገለጹ በሀገሪቱ እየታየ ያለው የመለዋወጫ እቃዎች ዋጋ መናር እና የታሪፍ ማሻሻያ አለመደረግ አክሳሪ እንደሆነባቸው የገለጹት የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች፣ ችግሩ ባልተፈታበት ሁኔታ ስራቸውን ማስቀጠል አስቸጋሪ እንደሆነባቸው በመግለጽ ከገበያው የመወጣት ስጋት እንደደቀነባቸው አስታወቁ። የኢትዮጵያ የፈሳሽ ጭነት ማጓጓዣ ባለንብረቶች ማህበር የነዳጅ ፍላጎት እድገትን እና የወጡ ወጪዎችን ያገናዘበ የታሪፍ ማሻሻያ እንዲደረግ ተደጋጋሚ ጥናቶችን ማቅረቡን ያስታወሰ ቢሆንም፣ በመንግስት በኩል ግን እስካሁን አዎንታዊ ምላሽ ማግኘት አለመቻሉን ገልጿል። የማህበሩ ፕሬዝደንት አቶ ፀጋ አስማረ እንደገለጹት፤ ጥናቱ ዝም ብሎ የቀረበ ሳይሆን ከነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን፣ ከትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር እንዲሁም ከንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከተወጣጡ ባለሙያዎች ጋር በጥጋቢ ሁኔታ ተጠናቆ የቀረበ ነው። ሆኖም ምላሽ በመዘግየቱ አባላቱ ለአላስፈላጊ ክሳራ መዳረጋቸውን አብራርተዋል። ከታሪፍ መዘገየት በተጨማሪ ባለንብረቶች ሌላ አጣብቂኝ ውስጥ የከተታቸው አሽከርካሪዎች ከባለንብረቱ እውቅና ውጪ በሚፈጽሙት የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ ምክንያት ተሽከርካሪዎች እና ነዳጅ የመወረስ እርምጃ እየተወሰደባቸው ይገኛል ብለዋል። ይህንን ተከትሎ የኢትዮጵያ የፈሳሽ ጭነት ትራንስፖርት ባለንብረቶች ማህበር አባላቱን በመጥራት በዘርፉ በተደቀኑ ዘርፈ-ብዙ ችግሮች እና በቀጣይ የጋራ አቋሞች ዙሪያ የምክክር ስብሰባ አካሂዷል። @Seledadotio @Seledadotio
2 588
10
በአከራይ ተከራይ ውል መፈጸም የሌለባቸው እና የተከለከሉ ተግባራት... በአዲስ አበባ ከተማ በአከራይ ተከራይ ውል የሚከተሉትን ተግባራት መፈጸም የተከለከለ ነው። 👉የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ሳያስመዘ
በአከራይ ተከራይ ውል መፈጸም የሌለባቸው እና የተከለከሉ ተግባራት... በአዲስ አበባ ከተማ በአከራይ ተከራይ ውል የሚከተሉትን ተግባራት መፈጸም የተከለከለ ነው። 👉የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ሳያስመዘግቡ መከራየትና ማከራየት፤ 👉በአከራይ ወይም ተከራይ ቸልተኝነት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል በአዋጁ የተቀመጠውን የጊዜ ገደብ አሳልፎ ማስመዝገብ፤ 👉የመኖሪ ቤት ኪራይ ውል እድሳት አለማስመዝገብ፤ 👉በአዋጁ ከተፈቀደው አግባብ ውጪ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ፤ 👉አዋጁ ከሚፈቅደው ውጪ የውል ዘመን ሳይጠናቀቅ ከቤት ማስወጣት፤ 👉በአዋጁ የተቀመጠውን የማስታወቂያ ወይም የማስጠንቀቂያ ጊዜ ሳይሰጥ ውል ማቋረጥ፤ 👉አዋጁ ላይ ከተቀመጠው መጠን በላይ የቅድመ ክፍያ እንዲፈፀም ማስገደድ፤ 👉 በባንክ ወይሞ በሌላ ሕጋዊ በሆነ የኤሌክትሮኒክ የክፍያ ስርዓት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ክፍያ አለመፈፀም 👉 ቀደም ሲል ሲከራይ የቆየ የመኖሪያ ቤት ወይም ግንባታው ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ አዲስ መኖሪያ ቤት ያለአገልግሎት እንዲቀመጥ ማድረግ እና ፤ 👉በአዋጁ ለአከራይ የተሰጠውን ማበረታቻ ያለአግባብ ለመጠቀሞ ሀሰተኛ መረጃ ወይም ማስረጃ ማቅረብ የተከለከለ መሆኑን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ @Seledadotio @Seledadotio
2 778
11
የኤሌክትሪክ ፍጆታ ማባዣ ጭማሪ ተደርጓል። ለመኖሪያ ቤት ከተያዘው ወር ሀምሌ ጀምሮ እስከ መስከረም ወር የሚፈፀም የኤሌክትሪክ ፍጆታ ታሪፍ ክፍያ ከላይ ተያይዟል። @Seledadotio @Seledado
የኤሌክትሪክ ፍጆታ ማባዣ ጭማሪ ተደርጓል። ለመኖሪያ ቤት ከተያዘው ወር ሀምሌ ጀምሮ እስከ መስከረም ወር የሚፈፀም የኤሌክትሪክ ፍጆታ ታሪፍ ክፍያ ከላይ ተያይዟል። @Seledadotio @Seledadotio
2 688
12
በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ከ1ሺህ 4መቶ በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል ተባለ ‎ ‎በሳምንቱ ውስጥ በተደረገ 6 ዙር በረራ 1ሺህ 4መቶ 81 ኢትዮጵያዊያን መመለሳቸ
በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ከ1ሺህ 4መቶ በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል ተባለ ‎ ‎በሳምንቱ ውስጥ በተደረገ 6 ዙር በረራ 1ሺህ 4መቶ 81 ኢትዮጵያዊያን መመለሳቸዉን የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታዉቋ፡፡ የተመለሱት 8መቶ79 ወንዶች፣ 5መቶ54 ሴቶች እና 48 ጨቅላ ህፃናት ሲሆኑ፤ከተመላሾች መካከል 82 እድሜያቸው ከአስራ ስምንት አመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ይገኙበታል። ‎ ‎መስከረም 5/ 2018 በተጀመረው ዜጎችን ወደ ሀገር ቤት የመመለስ ስራ እስካሁን ከ87 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገር መመለስ ተችሏል ተብሏል። ‎ ‎ሚኒስቴሩ ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ የማድረግ እና ከቤተሰብ ጋር የማቀላቀል ስራ ከሚመለከታቸው ባለድርሻና አጋር አካላት ጋር በመተባበር በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አስታዉቋል፡፡ ‎ ‎በተጨማሪም መደበኛ ባልሆነ ፍልሰት ወደ ተለያዩ ሀገራት ሄደው የሚመለሱ የፍልሰት ተጎጂዎችን ለመደገፍና መልሶ ለማቋቋም የሚያስችሉ ተግባራትን በትብብር እያከናወነ መሆኑን ገልጿ‎ል፡፡ ‎ወደፊትም በህገወጥ የሰዎች ዝውውር አስከፊነት ዙሪያ ህብረተሰቡን ለማስገንዘብ፣ መደበኛ ያልሆነ ፍልሰትን ለመከላከልና ደህንነቱ የተጠበቀ ፍልሰትን ለማበረታታት ሚኒስቴሩ የጀመራቸውን ስራዎች አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግሯል፡፡ @Seledadotio @Seledadotio
2 869
13
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ2018 ትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ተለቋል። ተማሪዎች ቀጥሎ ባለው ሊንክ መለያ ቁጥራችሁን እና ስማችሁን በማስገባት ውጤታችሁን ማየት ትችላላችሁ 👇 http
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ2018 ትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ተለቋል።   ተማሪዎች ቀጥሎ ባለው ሊንክ መለያ ቁጥራችሁን እና ስማችሁን በማስገባት ውጤታችሁን ማየት ትችላላችሁ 👇 http://ce.ministry.et   @Seledadotio @Seledadotio
2 739
14
ለሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ መናር ዋነኛው ምክንያት የቡና ነጋዴዎች ናቸው ተባለ ኢትዮጵያ ቀዳሚ የቡና አምራች ሀገር ብትሆንም፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለሚታየው የሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ መጨመር ዋነኛው ምክንያ
ለሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ መናር ዋነኛው ምክንያት የቡና ነጋዴዎች ናቸው ተባለ ኢትዮጵያ ቀዳሚ የቡና አምራች ሀገር ብትሆንም፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለሚታየው የሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ መጨመር ዋነኛው ምክንያት የቡና ላኪዎች ምርቱን በተጋነነ ዋጋ ማቅረባቸው መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል። የባለስልጣኑ የዋና ዳይሬክተር ጽህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ሰፊሳ አባቡ ለመናኸሪያ ሬድዮ እንደገለጹት፣ በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ለውጭ ገበያ ከቀረበው የቡና ምርት የተገኘው ገቢ ከፍተኛ ቢሆንም፣ በሀገር ውስጥ ገበያ ላይ ግን የዋጋ ጭማሪ ታይቷል። ባለስልጣኑ በዘርፉ የቁጥጥር ሥራ እያከናወነ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት የሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ ከአለም አቀፍ የገበያ ተመን ጋር ሲነጻጸር ሰፊ ልዩነት እንዳለው አስረድተዋል። ላኪዎች እርስ በርሳቸው በመነጋገር ተቀራራቢና የተረጋጋ ዋጋ እንዲያቀርቡ በተደጋጋሚ ቢነገራቸውም፤ ወዳልተገባ የዋጋ ሽሚያ በመግባታቸው ምክንያት በገበያው ላይ አለመረጋጋት መፈጠሩን ኃላፊው ገልጸዋል። ይህ የዋጋ መጋነን የሀገሪቱን የቡና ዘርፍ ወደ ኋላ የሚጎትት በመሆኑ ባለስልጣኑ ላኪዎችን በውይይት ለማስማማት ጥረት ማድረጉን ጠቅሰዋል።
2 844
15
የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሰናል-ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል‼️ ዛሬ ሐምሌ 12/2018 ዓ.ም በመቀሌ ህዝቡን እና አመራሩን ሰብስበው አወያይተዋል። የትግራይ ህዝብ ጭቆናን የመሸከም ታሪክ የለውም ያሉት ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል፤ ይልቁንም መብቶቹ ለማረጋገጥ በመደራጀት ታግሏል፣ መብቶቹን አስከብሯል እንዲሁም የሌሎች ብሔረሰቦችን መብቶች አክብሮ የመጣ ህዝብ ነው ብለዋል። ለ17 ዓመታት በተደረገው የትጥቅ ትግል ውስጥ የትግራይ ህዝብ ከባድ መስዋእትነት በመክፈል አንባገነኑ የደርግ ስርዓት መደምሰሱን ያወሱት ዶክተር ደብረፅዮን፤ በአንባገነኑ መቃብር በሃገር ደረጃ ሰላም፣ ልማትና የዴሞክራሲ ግንባታ ማረጋገጡን ጠቅሷል፡፡ ሆኖም፣ ይህንን መቀበል ያልቻሉ ሐይሎች ጊዜና አጋጣሚውን በመጠበቅ፣ የትግራይን ህዝብ ከምድረገፅ ለማጥፋት በህዝባችን ላይ ጀኖሳይድ ፈፅሟል ያሉት ፕረዝዳንቱ፤  የትግራይ ህዝብ አንድነቱ በመጠበቅ ልህልውናው በከፈለው መስዋዕትነት ጭቆናን እና ህልውናውን ለማጥፋት ለመጣው ሐይል የማይቀበል መሆኑ በዓለም አደባባይ ያስመሰከረ እንደሆነ ጠቅሷል፡፡  የፕሪቶሪያው ስምምነት ሲፈረም፤ የትግራይ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ፣ ተፈናቃዮችን ለመመለስ እና ልማትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ተስፋ አድርገን ነበረ ያሉት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፤የፌደራል መንግሥቱ በታቀደ ሁኔታ ትግራይን ዳግም ወደ ከበባና ክልከላ በማስገባት ለዳግም ጀኖሳይድ እየተዘጋጀ እንደሚገኝ አብራርቷል፡፡ እንደ ትግራይ፣ ለሰላም ስንል ከፍተኛ ትዕግስትና መስዋዕትነት እየከፈልን ነው፤ ይሁን እኛ ብቻ ሰላም ስለ ፈለግን ሊሳካልን አልቻለም ያሉት ዶ/ር ደብረፅዮን፤ አንድነታችን አጠናክረን የትግራይ መሰረታዊ ጥያቄዎች ማረጋገጥ ብቸኛ መፍትሔ ሆኖ መገኘቱ ተናግሯል፡፡ አሁን ባለንበት ሁኔታ መቀጠል አንችልም ያሉ ሲሆን እንደህዝብ የመከተ ዓቅሞቻችን በማደራጀት ህልውናችን ለማረጋገጥ በምንወስንበት ምዕራፍ ላይ እንገኛለን ብሏል፡፡ የፌደራል መንግስቱ ለሰላም በፍጹም ዝግጁ አይደለም፤ ስለዚህ ብሔራዊ ክብራችንና ሉዓላዊነታችንን ለመመለስ እንዲሁም የተፈናቀሉ ወገኖቻችንን መልሶ ለማቋቋም ትግላችንን ወደ ተጨባጭና ውጤታማ ደረጃ ማሸጋገር ይገባናል ብሏል፡፡
2 845
16
ላ ሮሃ በድጋሚ የአለም ንግሥት፡ ስፔን አርጀንቲናን ጥላ የ2026ቱን ዋንጫ አነሳች! ​ስፔን አስጨናቂ በሆነው የጭማሪ ሰዓት ጨዋታ አርጀንቲናን 1ለ0 በማሸነፍ ለሁለተኛ ጊዜ የዓለም ዋንጫ ባለቤት መ
ላ ሮሃ በድጋሚ የአለም ንግሥት፡ ስፔን አርጀንቲናን ጥላ የ2026ቱን ዋንጫ አነሳች! ​ስፔን አስጨናቂ በሆነው የጭማሪ ሰዓት ጨዋታ አርጀንቲናን 1ለ0 በማሸነፍ ለሁለተኛ ጊዜ የዓለም ዋንጫ ባለቤት መሆን ችላለች። በኒው ዮርክ ኒው ጀርሲ ስታዲየም በተደረገው በዚህ ታሪካዊ ጨዋታ፣ የባርሴሎናው ኮከብ ፌራን ቶሬስ በ106ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ብቸኛ ግብ ለስፔን ድል አብስራለች። ​ጨዋታው በአርጀንቲናዎች ጠንካራ መከላከያ የታጀበ ሲሆን፣ ኤንዞ ፈርናንዴዝ በሁለት ቢጫ ካርድ ከሜዳ መውጣቱ ለሊዮኔል ሜሲ የመጨረሻ የዓለም ዋንጫ ስንብት መራር ኪሳራ ሆኗል። ስፔን 20 ለ 2 የጎል ሙከራ በማድረግ ጨዋታውን በበላይነት ብትመራም፣ የአርጀንቲናው ግብ ጠባቂ ኤሚ ማርቲኔዝ ድንቅ ብቃቱን አሳይቷል። ከመጨረሻው ፊሽካ በኋላ በተፈጠረ ግጭት ሌአንድሮ ፓሬዴስ በቀይ ካርድ ተባሯል። ​ይህ በታዋቂ ሰዎችና በዶናልድ ትራምፕ የክብር ቦክስ እይታ የተደረገው የፊፋ የጥበብ ድግስ፣ በስፔን ደስታና ታሪክ ሰሪነት ተደምድሟል።
2 755
17
"ኔታንያሁ ኒዮርክ ከተማ ከገቡ ይታሰራሉ" - ከንቲባ ማምዳኒ የኒዮርክ ከንቲባ ዞህራን ማምዳኒ በእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ የወጣውን የእስር ትዕዛዝ ተግባራዊ አደርጋለሁ አሉ። ዓለማቀፍ የወንጀለ
"ኔታንያሁ ኒዮርክ ከተማ ከገቡ ይታሰራሉ" - ከንቲባ ማምዳኒ የኒዮርክ ከንቲባ ዞህራን ማምዳኒ በእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ የወጣውን የእስር ትዕዛዝ ተግባራዊ አደርጋለሁ አሉ። ዓለማቀፍ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) እስራኤል በጋዛ ጦርነት የጦር ወንጀል ፈፅማለች በሚል በኔታንያሁና ሌሎች ሁለት ባለስልጣናት ላይ የእስር ትዕዛዝ ማውጣቱ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቀጣይ ሳምንት ከፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ለመወያየት ወደ አሜሪካ ይጓዛሉ። ከንቲባ ዞህራን ማምዳኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያም ኔታንያሁ በሚመሯት የኒዮርክ ከተማ ከገቡ እንደሚታሰሩ ተናግረዋል። "በጉዳዩ ዙሪያ እየተወያየን ነው፤ ግን ህግ እንደ አዲስ አይፃፍም" ሲሉ አይሲሲ ያወጣውን መመሪያ እንደሚተገብሩ ጠቁመዋል። "በኒውዮርክ እስካለው ድረስ የከተማ ህግ አድርገው ብሎ የሚፈቅድልኝን ለማድረግ ዝግጁ ነኝ" ብለዋል። ማምዳኒ "ኔታንያሁ የጦር ወንጀል ፈፅመዋል ብየ አምናለሁ"ሲሉ ገልጸዋል። "እሱ ባለፉት አመታት በሰራቸው ወንጀሎች መቅረብ ያለበት ሄግ በሚገኘው ፍርድቤት ነው" ብለዋል። ከንቲባ ማምዳኒ ወደ ኃላፊነት እንደመጡ ተመሳሳይ አስተያየት ሰጥተው ነበር። ኔታንያሁ ከማምዳኒ ሹመት በኋላ ወደ አሜሪካ ቢያቀኑም ኒዮርክ ከተማ ግን አልገቡም። ነገር ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከንቲባው ወደ ሚያስተዳድሯት ኒዮርክ የሚገቡት በመጪው መስከረም ወር በሚካሄደው የተመድ አመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ነው።   @Seledadotio @Seledadotio
2 995
18
ትምህርት ሚኒስቴር በዩኒቨርሲቲዎች አዲስ የአመራር ሹመት መምሪያ ይፈ አደረገ‼️ ትምህርት ሚኒስቴር በመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚሾሙ ፕሬዝዳንቶችና ምክትል ፕሬዝዳንቶች አሰያየምን የ
ትምህርት ሚኒስቴር በዩኒቨርሲቲዎች አዲስ የአመራር ሹመት መምሪያ ይፈ አደረገ‼️ ትምህርት ሚኒስቴር በመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚሾሙ ፕሬዝዳንቶችና ምክትል ፕሬዝዳንቶች አሰያየምን የሚገዛ አዲስ መመሪያ ይፋ አድርጓል። መመሪያው በብቃትና በውድድር ላይ የተመሰረተ አሰራርን ለማስፈን ያለመ ሲሆን፣የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የአንድ ጊዜ የስራ ዘመን 6 ዓመት እና የምክትል ፕሬዝዳንቶች 4 ዓመት መሆኑ ተነግሯል። በማንኛውም የመንግስት ዩኒቨርሲቲ በተከታታይ ሁለት ጊዜ በፕሬዝዳንትነት ያገለገለ አመራር በድጋሚ መወዳደር እንደማይችልም ተገልጿል። ለፕሬዝዳንትነት የሚወዳደሩ ወንድ እጩዎች ቢያንስ የረዳት ፕሮፌሰርነትና ከዚያ በላይ ማዕረግ ሊኖራቸው የሚገባ ሲሆን፣ቢያንስ 2 ዓመት በፕሬዝዳንትነት ወይም 3 ዓመት በምክትል ፕሬዝዳንትነት/ዲንነት ያገለገሉ መሆን እንደለባቸው ገልጿል። አመራሩ በየ 3 ወሩ በቦርዱ የሚገመገም መሆኑ እና ። ውጤቱ በሁለት ተከታታይ የስድስት ወር ግምገማዎች ከ60% በታች ከሆነ፣ በጤና እክል ወይም በዲሲፕሊን ጉድለት ከሃላፊነቱ እንዲነሳ ለሚኒስቴሩ ሀሳብ ይቀርባል ተብሏል። በምልመላና ምርጫ ሂደቱ ላይ ቅሬታ ያለው ተወዳዳሪ፣ ውጤቱ በይፋ በተገለጠ በ10 ቀናት ውስጥ ለዩኒቨርሲቲው ቦርድ ቅሬታውን ማቅረብ እንደሚችል አረጋግጧል። ‎ @Seledadotio @Seledadotio
2 991
19
"የድሬክ እርግማን/መጥፎ እድል" አርጀንቲናን ከአለምሻምፒዮንነት ያስቀራት ይሆን? ድሬክ የምሽቱን የአለምዋንጫ ፍጻሜ ጨዋታ አርጀንቲና ታሸንፋለች ሲል 1.5 ሚሊዮን ዶላር አስይዟል። ድሬክ በተደጋጋሚ
"የድሬክ እርግማን/መጥፎ እድል" አርጀንቲናን ከአለምሻምፒዮንነት ያስቀራት ይሆን? ድሬክ የምሽቱን የአለምዋንጫ ፍጻሜ ጨዋታ አርጀንቲና ታሸንፋለች ሲል 1.5 ሚሊዮን ዶላር አስይዟል። ድሬክ በተደጋጋሚ እሱ ያሸንፋሉ ሲል ገንዘብ ያስያዘባቸዉ ቡድኖች ሲሸነፉ ታይቷል። በቅርቡ እንኳ በአዉሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ አርሰናል ፤ ፒኤስጂን ያሸንፋል ሲል አስይዞ ገንዘቡን ተበልቷል። ድሬክ በሌሎች ጨዋታዎችም እድል የማይቀናዉ ሲሆን የዛሬዉን ዉርርድ ካሸነፈ ግን 5.2 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ያሸንፋል።
2 997
20
የኢራን ሚሴኤሎች ኢላማቸውን መቱ‼️ ኢራን በጆርዳን በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ቤዝ ላይ በቀጥታ ጥቃት ስትፈፅም የሚያሳይ ምስል ይፋ አድርጋለች። በዚህ ጥቃት በርካታ ሰው አልባ አውሮፕላኖች እና ቅንጡ
የኢራን ሚሴኤሎች ኢላማቸውን መቱ‼️ ኢራን በጆርዳን በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ቤዝ ላይ በቀጥታ ጥቃት ስትፈፅም የሚያሳይ ምስል ይፋ አድርጋለች። በዚህ ጥቃት በርካታ ሰው አልባ አውሮፕላኖች እና ቅንጡ የሆነውን Hawk helicopter (21million dollar) ማውደሟን፣በርካታ ወታደሮች መገደላቸውን ገልፃለች። ለዚህ ኢላማውን ለጠበቀ ጥቃት አሜሪካ ራሺያን እና ቻይናን እየወቀሰች ትገኛለች። አሜሪካም በሆርሙዝ ዳርቻ በሚገኘው የኢራን ነዳጅ ማከማቻ ላይ በሬክተር ስኬል 5 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ማድረሱን ገልጿል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter
2 932