es
Feedback
Ethio - ዜና 🇪🇹

Ethio - ዜና 🇪🇹

Ir al canal en Telegram

የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot

Mostrar mĂĄs

📈 Análisis del canal de Telegram Ethio - ዜና 🇪🇹

El canal Ethio - ዜና 🇪🇹 (@ethio_zena23) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 101 677 suscriptores, ocupando la posición 74 en la categoría Fotos y el puesto 313 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 101 677 suscriptores.

SegĂşn los Ăşltimos datos del 04 septiembre, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los Ăşltimos 30 dĂ­as la variaciĂłn de miembros fue de -2 426, y en las Ăşltimas 24 horas de -155, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificaciĂłn: No verificado
  • Tasa de interacciĂłn (ER): El promedio de interacciĂłn de la audiencia es 3.26%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 2.69% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicaciĂłn recibe en promedio 3 319 visualizaciones. En el primer dĂ­a suele acumular 2 731 visualizaciones.
  • Reacciones e interacciĂłn: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicaciĂłn es 23.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot”

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (Ăşltimos datos recibidos el 05 septiembre, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analĂ­tica demuestra que la audiencia interactĂşa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categorĂ­a Fotos.

101 677
Suscriptores
-15524 horas
-8107 dĂ­as
-2 42630 dĂ­as

Carga de datos en curso...

Atraer Suscriptores
septiembre '26
septiembre '260
en 4 canales
agosto '26
+377
en 6 canales
Get PRO
julio '26
+201
en 4 canales
Get PRO
junio '26
+64
en 9 canales
Get PRO
mayo '26
+129
en 11 canales
Get PRO
abril '26
+74
en 12 canales
Get PRO
marzo '26
+2 127
en 10 canales
Get PRO
febrero '26
+8
en 4 canales
Get PRO
enero '26
+2 108
en 54 canales
Get PRO
diciembre '25
+2 159
en 81 canales
Get PRO
noviembre '25
+4 183
en 51 canales
Get PRO
octubre '25
+4 892
en 3 canales
Get PRO
septiembre '25
+7 709
en 3 canales
Get PRO
agosto '25
+5 654
en 1 canales
Get PRO
julio '25
+6 591
en 2 canales
Get PRO
junio '25
+6 975
en 0 canales
Get PRO
mayo '25
+7 406
en 1 canales
Get PRO
abril '25
+7 575
en 1 canales
Get PRO
marzo '25
+8 127
en 1 canales
Get PRO
febrero '25
+7 065
en 3 canales
Get PRO
enero '25
+7 127
en 1 canales
Get PRO
diciembre '24
+9 050
en 4 canales
Get PRO
noviembre '24
+11 169
en 2 canales
Get PRO
octubre '24
+14 487
en 4 canales
Get PRO
septiembre '24
+12 613
en 0 canales
Get PRO
agosto '24
+11 528
en 5 canales
Get PRO
julio '24
+4 340
en 29 canales
Get PRO
junio '24
+871
en 5 canales
Get PRO
mayo '24
+1 669
en 5 canales
Get PRO
abril '24
+1 824
en 7 canales
Get PRO
marzo '24
+3 958
en 6 canales
Get PRO
febrero '24
+1 530
en 2 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
05 septiembre0
04 septiembre0
03 septiembre0
02 septiembre0
01 septiembre0
Publicaciones del Canal
ኢትዮጵያ በ83 ቢ. ብር ወጪ 16 ግዙፍ መርከቦችን ልትገዛ ነው ኢትዮጵያ የውጪና የገቢ ምርቶቿን የሎጂስቲክስ አቅርቦት ለማቀላጠፍ በ83 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር ወጪ 16 አዳዲስ መርከቦችን ለመግዛት
ኢትዮጵያ በ83 ቢ. ብር ወጪ 16 ግዙፍ መርከቦችን ልትገዛ ነው ኢትዮጵያ የውጪና የገቢ ምርቶቿን የሎጂስቲክስ አቅርቦት ለማቀላጠፍ በ83 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር ወጪ 16 አዳዲስ መርከቦችን ለመግዛት አቅዳለች። በቀጣይ አምስት ዓመታት ውስጥ የሚከናወነው ይህ የግዥ እቅድ አሁን ካሉት 10 መርከቦች በተጨማሪ የሚከናወን ሲሆን፣ ቀደም ሲል ከነበሩት ከ25 ሺህ እስከ 28 ሺህ ቶን አቅም በበለጠ ከ50 ሺህ እስከ 63 ሺህ ቶን የመሸከም አቅም ያላቸው ግዙፍ መርከቦችን የሚያካትት ነው። የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ እንደገለጸው፣ በአሁኑ ወቅት ከስድስት መርከቦች በላይ ሕጋዊ የግዥ ሥርዓት በሂደት ላይ ይገኛል። አዲሶቹ መርከቦች ስትራቴጂክ ግብዓቶችን በብቃት በማስገባትና ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን በወቅቱ በመላክ የሀገሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ ውጤታማ ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖራቸዋል።

2
የሱዳኑ ጦር መሪ አብዱል ፋታህ አል-ቡርኻን አስመራ ገቡ‼️ 👉ምፅዋ በርካታ መሳሪያ እየተራገፈ ይገኛል። የሱዳን ጦር አዛዥ እና የሉዓላዊ ምክር ቤት ሊቀ-መንበር ጄነራል አብዱል ፋታህ አል-ቡርኻን
የሱዳኑ ጦር መሪ አብዱል ፋታህ አል-ቡርኻን አስመራ ገቡ‼️ 👉ምፅዋ በርካታ መሳሪያ እየተራገፈ ይገኛል። የሱዳን ጦር አዛዥ እና የሉዓላዊ ምክር ቤት ሊቀ-መንበር ጄነራል አብዱል ፋታህ አል-ቡርኻን ኤርትራ የገቡ ሲሆን አስመራ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም በፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። አል-ቡርኻን ከፈጥኖ ደራሽ ኃይል (RSF) ጋር ውጊያ ውስጥ ከገቡ ወዲህ ዋነኛ ደጋፊያቸው ወደ ሆነችው ኤርትራ ሲያቀኑ በቅርብ ጊዜያት ውስጥ የዛሬው ለሁለተኛ ጊዜ ነው። የኤርትራ የኢንፎርሜሽን ሚኒስትር የማነ ገብረ መስቀል እንደገለጹት፣ የጄነራል አል-ቡርኻን ጉብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል የሚደረግ መደበኛ የምክክር አካል ነው። ሁለቱ መሪዎች በቆይታቸው የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ማጠናከር እና በቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ እንደሚያተኩሩ ተናግረዋል።
1 356
3
ቡና አብዝቶ መጠጣት የእንቅልፍ ጊዜን ቢያሳጥርም ጥልቀቱን እንደሚጨምር ተነገረ ​በቀን አራት ወይም ከዚያ በላይ ሲኒ ቡና መጠጣት የእንቅልፍ ቆይታን ያሳጥራል፤ ሆኖም በእንቅልፍ ወቅት የሚገኘውን ጥልቅ እረፍት እንደሚጨምር አዲስ ጥናት ይፋ አደረገ። ​በስዊዘርላንዱ ተመራማሪ በቤንጃሚን ስተኪ የተመራው ይህ ጥናት፣ የዩኬ ባዮባንክ እና የHypnoLaus መረጃዎችን በመተንተን የተሰራ ነው። ተመራማሪዎቹ እንዳረጋገጡት፣ ከፍተኛ መጠን ያለው ካፌይን መውሰድ የእንቅልፍ ሰዓትን በ11 ደቂቃ ያህል ያሳጥራል። ​ነገር ግን፣ የሰውነት ህዋሳትን ለማደስ እና ኃይልን ለማገገም ወሳኝ የሆነው "የዝቅተኛ ሞገድ እንቅልፍ"  ጥልቀት ይጨምራል። ሳይንቲስቶች እንደሚሉት፣ ይህ የሰውነት ተፈጥሯዊ ምላሽ ሲሆን፣ ያጣውን አጭር የእንቅልፍ ሰዓት በጥልቅ እንቅልፍ ለማካካስ የሚያደርገው ጥረት ነው። ​ጥናቱ ቡና የእንቅልፍ መጠንን ቢቀንስም፣ የጥራት መጠኑ ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ እንደሚፈጥር አመልክቷል።
1 889
4
ለአዲስ ዓመት የአንድ ኪሎ ሥጋ ዋጋ 1,200 ብር እንዲሆን ከሥጋ ቤቶቹ ጋር ስምምነት መደረጉ ተገለጸ ለተቃረበው የ2019 አዲስ ዓመት በዓል የሸማቹን እንግልትና ያልተገበበ የዋጋ ጭማሪ ለመግታት ያ
ለአዲስ ዓመት የአንድ ኪሎ ሥጋ ዋጋ 1,200 ብር እንዲሆን ከሥጋ ቤቶቹ ጋር ስምምነት መደረጉ ተገለጸ ለተቃረበው የ2019 አዲስ ዓመት በዓል የሸማቹን እንግልትና ያልተገበበ የዋጋ ጭማሪ ለመግታት ያለመ አዲስ ውሳኔ ተ አስተላለፈ። የአዲስ አበባ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን በመዲናዋ ከሚገኙ 274 የኅብረት ሥራ ማኅበራት ሥጋ ቤቶች ጋር ባደረገው ዝርዝር ውይይት፣ አንድ ኪሎ የበሬ ሥጋ በ1,200 ብር ብቻ ለሕዝብ እንዲቀርብ መግባባት ላይ መድረሱን አስታውቋል። የበዓላት ወቅት የመገበያያ ዋጋ ንረትና የአቅርቦት እጥረት የሚፈጥረውን ጫና ለማቃለል ሰፊ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን የገለጸው ኮሚሽኑ፣ ሸማቾች በየአካባቢያቸው በሚገኙ ማኅበራት በኩል ምርቱን በቀላሉ ማግኘት እንደሚችሉ አረጋግጧል። በሁሉም 274 የኅብረት ሥራ ማኅበራት ሥጋ ቤቶች አንድ ኪሎ ሥጋ ከ1,200 ብር በላይ እንዳይሸጥ ስምምነት ተደርሷል። መንግሥት ከአርሶ አደሮችና ከበሬ አቅራቢዎች ጋር ቀጥተኛ የገበያ ትስስር በመፍጠሩ በሥጋ ቤቶች በኩል የነዳጅና የአቅርቦት ምክንያት አቤቱታ እንደማይኖር ተገልጻል። ከሥጋ በተጨማሪ ሌሎች የበዓል ሸመታዎችን ከእሁድ ገበያዎችና ከኅብረት ሥራ ማኅበራት ሱቆች በቅናሽ ዋጋ መገበያየት እንደሚቻል ጥሪ ቀርቧል። ከተቀመጠው የዋጋ ተመን በላይ በሚሸጡ ሥጋ ቤቶች ላይ ኅብረተሰቡ ጥቆማ በመስጠት ትብብር እንዲያደርግ ተጠይቋል። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23
2 185
5
ያለፍላጎታቸው ሴቶችን በወሲብ ንግድ ላይ ያሰማሩት አምስት ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ፡፡ በባሌ ዞን ሮቤ ከተማ አስተዳደር በመጠጥ ግሮሰሪ ንግድ ፈቃድ ሽፋን ሴቶችን ያለ ፍላጎታቸው ለወሲብ ንግድ ሲዳር
ያለፍላጎታቸው ሴቶችን በወሲብ ንግድ ላይ ያሰማሩት አምስት ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ፡፡ በባሌ ዞን ሮቤ ከተማ አስተዳደር በመጠጥ ግሮሰሪ ንግድ ፈቃድ ሽፋን ሴቶችን ያለ ፍላጎታቸው ለወሲብ ንግድ ሲዳርጉና ጥቃት ሲፈጽሙ የነበሩ አምስት ግለሰቦች እስከ 23 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራትና የገንዘብ መቀጮ መቀጣታቸውን የከተማው ፖሊስ ዋና መምሪያ አስታውቋል። የሮቤ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ዋና መምሪያ የኮሙኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ኢንስፔክተር ጌታቸው ታምሩ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት፣ ተከሳሾቹ በዘይበላ ወላሼ ቀበሌ «ኤል ክላሲኮ» የተባለ የምሽት ጭፈራ ቤት በመክፈት ሴቶችን በአስተናጋጅነት ካስቀጠሩ በኋላ በግዳጅ ለዝሙት አዳሪነት እንዲሰማሩ አድርገዋል። ፖሊስ ባደረገው ማጣራት አንደኛ ተከሳሽ ተሬሳ ፍቃዱ የንግድ ፈቃዱን በማውጣትና ከሌሎች ተከሳሾች ጋር በመሆን የተቀጠሩ አስተናጋጆችን ያለፍላጎታቸው የግብረ-ሥጋ ድፍረት ጥቃት እንዲፈጸምባቸው ማድረጉ በበቂ ማስረጃ ተረጋግጧል።የቀረበውን የዐቃቤ ሕግ ክስና የፖሊስ ማስረጃ የመረመረው የሮቤ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት የጥፋተኝነት ውሳኔ አስተላልፋል። በዚህም መሰረት 1ኛ ተከሳሽ ተሬሳ ፍቃዱ ድርጊቱን በዋናነት በመምራትና በግዳጅ የመድፈር ጥቃት በመፈጸሙ በ23 ዓመት ፅኑ እስራት እና በ200 ሺህ ብር መቀጮ፤ 2ኛ ተከሳሽ ዳንኤል ደሴ በ10 ዓመት እስራት እና በ10 ሺህ ብር መቀጮ፤ 3ኛ ተከሳሽ ወርቁ ደሜ በ6 ዓመት እስራት እና በ45 ሺህ ብር መቀጮ፤ 4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች ተመስገን ፍቃዱ እና ቤክና መሐመድ ደግሞ እያንዳንዳቸው በ1 ዓመት ከ8 ወር እስራትእንዲቀጡ ተወስኖባቸዋል።
2 484
6
በክልል ንግድ ፈቃድ አዲስ አበባ ውስጥ መስራት አይቻልም ሲል ቢሮው አሳወቀ‼️ በክልል ፈቃድ አዲስ አበባ ውስጥ የሚሰሩ አስመጪዎች ንግድ ፈቃዳቸውን ወደ አዲስ አበባ ማዛዋወር አለባቸው ብሏል። የአዲ
በክልል ንግድ ፈቃድ አዲስ አበባ ውስጥ መስራት አይቻልም ሲል ቢሮው አሳወቀ‼️ በክልል ፈቃድ አዲስ አበባ ውስጥ የሚሰሩ አስመጪዎች ንግድ ፈቃዳቸውን ወደ አዲስ አበባ ማዛዋወር አለባቸው ብሏል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በመኪና ሽያጭ ዘርፍ በሚደረጉ ህገወጥ አሰራሮች እና የታክስ ስወራዎች ላይ ጥብቅ እርምጃና ቁጥጥር እንደሚያደርግ አስታወቀ። በክልል ፈቃድ አዲስ አበባ ውስጥ የሚሰሩ አስመጪዎች ንግድ ፈቃዳቸውን ወደ አዲስ አበባ ማዛወር አለባቸው ተብሏል። ደረሰኝ መለየት የሽያጭ ማሽን ማስተካከል እና ወርሃዊና ዓመታዊ ግብር መክፈል አለባቸው ነው የተባለው። ህገወጥ ደረሰኝ መጠቀም ወይም የውጭ ሀገር ፈቃድ ብቻ ይዞ መንቀሳቀስ በህግ ያስጠይቃል። አስመጪዎችና የመኪና ማሳያ ባለቤቶች ፈቃድ ከሌላቸው ደላሎች ጋር በመተባበር ህገወጥ የሽያጭ ሰነድ ከመፈራረም እንዲቆጠቡ ተሳስቧል። ቢሮው ከዚህ አሰራር ውጭ በሚንቀሳቀሱ አስመጪዎች ፈቃድ የሌላቸው ደላሎች በኦንላይን ህገወጥ ንግድ የሚያካሂዱ ግለሰቦች እና ከተዋናዮቹ ጋር በሚተባበሩ አካላት ላይ ቢሮው ክትትልና ምርመራ በማድረግ ህጋዊ እርምጃ ይወስዳል ሲል አሳስቧል።
2 639
7
ህወሃት የፌደራል መንግስትን በድሮን ጥቃት ሲከስ የአላማጣ ባለስልጣናት ደግሞ ህወሃትን ወቀሱ ህወሃት የፌደራል መንግስት ባለስልጣናት በሲቪል መሠረተ ልማቶች ላይ ተደጋጋሚ የአየር ጥቃቶችን እየፈጸሙ
ህወሃት የፌደራል መንግስትን በድሮን ጥቃት ሲከስ የአላማጣ ባለስልጣናት ደግሞ ህወሃትን ወቀሱ   ህወሃት የፌደራል መንግስት ባለስልጣናት በሲቪል መሠረተ ልማቶች ላይ ተደጋጋሚ የአየር ጥቃቶችን እየፈጸሙ ነው ሲል የከሰሰ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ የህወሃት ታጣቂዎች የህዝብ ትምህርት ቤቶችን ወደ ወታደራዊ ካምፕነት ቀይረዋል የሚሉ የአካባቢው ሪፖርቶች መውጣታቸውን ዶቼ ቬሌ  ዘግቧል።   የህወሃት ቃል አቀባይ ሚካኤል አሰግዶም በድሮን እና በሚግ ተዋጊ አውሮፕላኖች የታገዘው የአየር ጥቃት በአምስት ዞኖች በሚገኙ የህዝብ ተቋማት ላይ ማረፉን የገለጹ ሲሆን፣ በሰሜን ምዕራብ ዞን ደጀን ከተማ የሚገኝ አንድ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለሁለተኛ ጊዜ ተመትቶ ሙሉ በሙሉ መውደሙን፣ እንዲሁም በእንደርታ እና በራያ አዘቦ አርሶ አደሮችና የመኖሪያ መንደሮች መመታታቸውን ጠቅሰዋል።   ይሁን እንጂ ከአላማጣ ከተማ የተገኙ አንድ የቀድሞ የአካባቢው ባለስልጣን ለዶቼ ቬሌ በሰጡት ተቃራኒ መረጃ፣ የህወሃት ኃይሎች አራት የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ በአላማጣ የሚገኙ ስምንት ትምህርት ቤቶችን፣ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን እና የማዘጋጃ ቤት ህንፃዎችን በአሁኑ ወቅት ወደ ታጠቁ ወታደራዊ ይዞታነት እና መፈጠሪያነት ቀይረዋቸዋል ሲሉ ከሰዋል።
2 790
8
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በናሚቢያ አዲስ ብሔራዊ አየር መንገድን በሽርክና ለማቋቋም ከሀገሪቱ መንግሥት ጋር ድርድር ጀመረ። የናሚቢያ ሥራና ትራንስፖርት ሚኒስትር ጆናስ ሼሎንጎ እንደገለጹት፤ ውይይቱ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በናሚቢያ አዲስ ብሔራዊ አየር መንገድን በሽርክና ለማቋቋም ከሀገሪቱ መንግሥት ጋር ድርድር ጀመረ። የናሚቢያ ሥራና ትራንስፖርት ሚኒስትር ጆናስ ሼሎንጎ እንደገለጹት፤ ውይይቱ ቀደም ሲል "ኤር ናሚቢያ" ላይ ደርሶ የነበረውን የፋይናንስ ውድቀትና መዘጋት ዳግም እንዳይከሰት ለመከላከልና ጠንካራ አየር መንገድ ለመገንባት ያለመ ነው። ሚኒስትሩ፣ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር የተደረጉት ውይይቶች ሰፊ የቴክኒክ እና የንግድ ጉዳዮችን ያካተቱ ቢሆንም እስካሁን የተፈረመ አስገዳጅ ስምምነት የለም ብለዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዚህ ቀደም በቶጎ፣ በማላዊ፣ በዛምቢያ እና በኮንጎ አየር መንገዶች ምሥረታ ላይ አሻራውን ማሳረፉ ይታወሳል ሲል ስፑትኒክ አፍሪካ ።
2 829
9
አስተማማኝ መረጃ በማጣት እና በተዛቡ ዜናዎች ተስፋ ቆርጠዋል‼️ እውነትን መሰረት ያደረጉ ተጨባጭ መረጃዎችን ወቅታዊ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ዜናዎችን JOIN ብለዉ ይከታተሉ! JOIN CHANNEL👇JOIN CHANNEL👇 👇 https://t.me/seledadotio https://t.me/seledadotio
207
10
ሊቨርፑል ከኢፕስዊች ታውን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሦስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት በሚደረግ አንድ ጨዋታ ይጀምራል፡፡ በዚህም ሊቨርፑል ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ከኢፕስዊች ታ
ሊቨርፑል ከኢፕስዊች ታውን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሦስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት በሚደረግ አንድ ጨዋታ ይጀምራል፡፡ በዚህም ሊቨርፑል ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ከኢፕስዊች ታውን ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡ በአንዶኒ ኢራኦላ የሚመራው ሊቨርፑል የውድድር ዓመቱን የመጀመሪያ ድል ለማሳካት ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡ ሊቨርፑል በሊጉ ያደረጋቸውን ያለፉትን ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ሁለት አቻ በሆነ ተመሳሳይ ውጤት ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡ ተጋጣሚው ኢፕስዊች ታውን በበኩሉ ወደ ድል ለመመለስ የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡ በመጀመሪያ ሳምንት የሊጉ ጨዋታ ድል የቀናው ኢፕስዊች ታውን በሁለተኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር በማንቼስተር ዩናይትድ 5 ለ 2 በሆነ ሰፊ ውጤት መሸነፉ አይዘነጋም፡፡
2 720
11
በአዲስ አበባ ከተማ በህገ-ወጥ የማዕድን ቁፋሮ ላይ የተሰማሩ አካላት እስከ ግማሽ ሚሊዮን ብር እንደሚቀጡ የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ። ባለስልጣኑ እንደገለጸው፤ ያለፈቃድ ማዕድን
በአዲስ አበባ ከተማ በህገ-ወጥ የማዕድን ቁፋሮ ላይ የተሰማሩ አካላት እስከ ግማሽ ሚሊዮን ብር እንደሚቀጡ የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ።   ባለስልጣኑ እንደገለጸው፤ ያለፈቃድ ማዕድን የሚያመርቱ፣ ከፈቃድ ውጭ የሚንቀሳቀሱ እና የአካባቢ ጥበቃ ህጎችን የማይተገብሩ አካላት ተጠያቂ ይሆናሉ።   በዚህም መሰረት፡-ያለፈቃድ ማዕድን ሲያመርቱ የተገኙ አካላት ከ300,000 እስከ 400,000 ብር ቅጣት እንደሚጠበቅባቸው ተገልጿል።   ህገ-ወጥ ድርጊቱን የፈጸሙ አካላት የገንዘብ ቅጣቱ እንደ ጥፋቱ ክብደት እስከ 500,000 ብር ሊደርስ እንደሚችልና መሳሪያዎቻቸውም በመንግስት እንደሚወረሱ ተመላክቷል።   ከተማዋንና መሰረተ ልማቶችን ለመጠበቅ በማዕድን ማምረቻ ቦታዎች ላይ የሲሲቲቪ ካሜራዎችን የመግጠም ስራ የግዴታ እንደሚሆንና አልሚዎችም የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርት ማቅረብ እንዳለባቸው ተሳስቧል።   ይህ ጥብቅ የህግ ማዕቀፍ የከተማዋን ደህንነትና ሰላም ለማረጋገጥ የታለመ መሆኑ ተገልጿል።
2 633
12
የ2018 ዓ.ም. የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሃ ግብር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ውጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፡-  የከ
የ2018 ዓ.ም. የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና  ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሃ ግብር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ውጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፡-  የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን ከነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ከታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ (Link) በመጠቀም ምርጫችሁን ት/ቤት መሄድ ሳይጠበቅባችሁ ባላችሁበት ቦታ እራሳችሁ በመሙላት እንድታሳውቁ እንገልጻለን።  ማስፈንጠሪያ (Link)  https://student.ethernet.edu.et/ ማሳሰቢያ፡-  የህክምና፣ የአካል ጉዳተኝነት፣ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች እና ከ6 ወር በታች ህፃን የሚያጠቡ እናቶች አስፈላጊውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ ይኖርባችኋል። ትምህርት ሚኒስቴር
2 762
13
"ጦርነቱ ከተጀመረ የኤርትራ ጄኔራሎች ይደመሰሳሉ፤ተመለሱ የሚለንም የለም!" - ኮሎኔል ነጋሽ‼️ የኤርትራ አመራሮች እጣ-ፈንታ፦** ጦርነት ከተቀሰቀሰ የኤርትራ ጄኔራሎች እና አመራሮች ሙሉ በሙሉ እን
"ጦርነቱ ከተጀመረ የኤርትራ ጄኔራሎች ይደመሰሳሉ፤ተመለሱ የሚለንም የለም!"  - ኮሎኔል ነጋሽ‼️ የኤርትራ አመራሮች እጣ-ፈንታ፦** ጦርነት ከተቀሰቀሰ የኤርትራ ጄኔራሎች እና አመራሮች ሙሉ በሙሉ እንደሚደመሰሱና ኤርትራም በአጭር ጊዜ ውስጥ በኢትዮጵያ ቁጥጥር ሥር እንደምትገባ ኮሎኔል ነጋሽ አስጠንቅቀዋል። የኢትዮጵያ የማያዳግም እርምጃ፦** የኢትዮጵያ ቀዳሚ ፍላጎት ሰላም መሆኑ ቢገለጽም፤ ሀገርን የሚያፈርሱ እና የሚያበጣብጡ ኃይሎችን ግን ዝም ብሎ ከመመልከት አልፎ፣ባሉበት ቦታ ድረስ በመሄድ ተገቢውን ዋጋ እንደሚያስከፍሏቸው ቁርጡን ተናግረዋል። የተቀየረው የጦርነት አውድ፦** እንደ ቀደመው ጊዜ "ተራራ የመያዝ፣ የመልቀቅ፣የማፈግፈግና የማጥቃት" ዘመን አብቅቷል። አሁን ያለው ውጊያ ከፍተኛ የሰው ኃይልን ማዕከል ያደረገ ሳይሆን፣በአንድ ቦታ ላይ ሆኖ በዘመናዊ የቴክኖሎጂ አቅም ጦርነቱን ማጠናቀቅ ወደሚቻልበት ደረጃ መሸጋገሩን አብራርተዋል። የ1990ው ታሪክ አይደገምም፦** በ1990 ዓ.ም ኤርትራ ሙሉ በሙሉ ተከባ የነበረ ቢሆንም፤የኤርትራ አመራሮች ከሞት የዳኑት "በጥቂት የኛ አመራሮች" (ወደ ኋላ ተመለሱ ባሉ) ምክንያት እንደነበር ኮሎኔሉ አስታውሰዋል። አሁን ግን ያ ታሪክ እንደማይደገምና "ተመለሱ የሚሉንም የሉም" ሲሉ የማያዳግም መልዕክት አስተላልፈዋል። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23
2 858
14
ህፃን አግታ 3 ሚ. ብር የጠየቀችው የቤት ሰራተኛ በጎንደር ተያዘች! አዲስ አበባ ውስጥ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ የሰባት ዓመቷን ህፃን ፊዮና ሰለሞንን በማገት ወደ ጎንደር ከተማ የወሰደችው መቅደስ
ህፃን አግታ 3 ሚ. ብር የጠየቀችው የቤት ሰራተኛ በጎንደር ተያዘች! አዲስ አበባ ውስጥ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ የሰባት ዓመቷን ህፃን ፊዮና ሰለሞንን በማገት ወደ ጎንደር ከተማ የወሰደችው መቅደስ ሞገስ የተባለች ወጣት፣ በቁጥጥር ስር መዋሏን የጎንደር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ። ተጠርጣሪዋ ህፃኗን በጎንደር ከተማ ማራኪ ክፍለ ከተማ ዩኒቨርሲቲ አካባቢ በሚገኝ ጫካ ውስጥ ደብቃ በነበረበት ወቅት በህብረተሰቡ ጥቆማና በፖሊስ ጥብቅ ክትትል በቁጥጥር ስር መዋል ችላለች። ከአክስቷ ልጅ ጋር በመተባበር ወንጀሉን የፈፀመችው ተጠርጣሪዋ፣ ለቤተሰብ በመደወል 3 ሚሊዮን ብር የጠየቀች ሲሆን፣ ከ370 ሺህ ብር በላይ መቀበሏ ተረጋግጧል፤ ፖሊስም ቀሪ ተባባሪዎችን ለመያዝ ክትትል እያደረገ ነው።
3 076
15
"ሜሲ" የሚለው የስም መጠርያ ለማንም እንዳይሰጥ! የሊዮኔል ሜሲ የትውልድ ከተማ የሆነችው ሮሳሪዮ ወላጆች ለልጆቻቸው "ሜሲ" የሚለውን ስም እንዳይሰጡ ከለከለች። በአርጀንቲናዋ ሮሳሪዮ ከተማ ወላጆች+2
"ሜሲ" የሚለው የስም መጠርያ ለማንም እንዳይሰጥ! የሊዮኔል ሜሲ የትውልድ ከተማ የሆነችው ሮሳሪዮ ወላጆች ለልጆቻቸው "ሜሲ" የሚለውን ስም እንዳይሰጡ ከለከለች። በአርጀንቲናዋ ሮሳሪዮ ከተማ ወላጆች ለልጆቻቸው "ሜሲ" የሚለውን ስም የመጀመሪያ ስም አድርገው እንዳይሰጡ መከልከሏ ተገለጸ። አርጀንቲና "ሊዮኔል ሜሲ" የሚለውን ስም በእግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ለማንም የማይሰጥ እና ወደፊትም የማይደገም ልዩ አድርጋዋለች። በ2014 ከሮዛሪዮ ውጪ የሚኖር አንድ አባት ልጁን "ሜሲ ዳንኤል ቫሬላ" ብሎ ለመሰየም ልዩ ፈቃድ ካገኘ በኋላ ነበር ይህ ክልከላ የወጣው። ይህንን ተከተሎ የሮሳሪዮ ከተማ ባለሥልጣናት ተመሳሳይ ነገር በከተማቸው መደበኛ በሆነ መንገድ የማይፈቀድ መሆኑን የሚገልጽ መመርያ ያወጡት። ይህ ለእሱ ያላቸውን ፍቅር እና አድናቆት መግለጫ ነው ተብሏል። በሜሲ በትውልድ ከተማ ሮዛሪዮ አካባቢ ግራ መጋባትን ለመቀነስ የሕፃናትን ስም "ሜሲ" ብሎ መሰየምን የሚከለክል ሕግ በ2014 ነበር ተደንግጎ የወጣው።
3 152
16
እየተጠናከረ የመጣው ኤል ኒኖ ከባድ የአየር ሁኔታ ስጋት እያሳደረ እንደሆነ ተገለጸ የዓለም ሜትሮሎጂ ድርጅት እንደገለጸው አሁን ላይ እየተስተዋለ የሚገኘው የኤል ኒኖ ክስተት በ70 ዓመታት ውስጥ ከታ
እየተጠናከረ የመጣው ኤል ኒኖ ከባድ የአየር ሁኔታ ስጋት እያሳደረ እንደሆነ ተገለጸ የዓለም ሜትሮሎጂ ድርጅት እንደገለጸው አሁን ላይ እየተስተዋለ የሚገኘው  የኤል ኒኖ ክስተት በ70 ዓመታት ውስጥ ከታዩት በጣም ኃይለኛ ክስተቶች አንዱ ሊሆን እንደሚችል ያስታወቀ ሲሆን፥ክስተቱም ቢያንስ እስከ የካቲት 2027 ሊቀጥል እንደሚችል ተገልጿል። የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ዓለም ከፍተኛ የአየር ሁኔታ አደጋ ወደሚበዛበት ደረጃ እየገባች መሆኑን አንስተው፥ኤል ኒኖ እየጠነከረ በመምጣቱ የድርቅ፣ የጎርፍ፣ የመሬት ናዳ እና የከፍተኛ ሙቀት አደጋዎች ሊባባሱ እንደሚችሉ ተናግረዋል። በፓሲፊክ ውቅያኖስ ማዕከላዊና ምሥራቃዊ ክፍል የባሕር ሙቀት በቅርብ ወራት በከፍተኛ ሁኔታ  የጨመረ ሲሆን፥በተለይም የባሕር ወለል ሙቀት ከመደበኛው በ2 ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል ። የኤል ኒኖ ተጽዕኖ በሰው ልጅ ከሚመነጨው የረጅም ጊዜ የአየር ንብረት ሙቀት መጨመር ላይ ተደምሮ የከፋ የአየር ሁኔታ ሊያስከትል እንደሚችል ሳይንቲስቶች ገልጸዋል። ባለሙያዎች በበኩላቸው የኤል ኒኖ ተጽዕኖ በሰዎች ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ ቅድመ ማስጠንቀቂያ፣ የሕክምና ድጋፍና የአደጋ ዝግጅት ሥርዓቶችን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።
3 013
17
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አዲስ የቤት ፋይናንስ ኩባንያ ይፋ አደረጉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) ጋር በመተባበር 100 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያለው የመጀመሪያው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አዲስ የቤት ፋይናንስ ኩባንያ ይፋ አደረጉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) ጋር በመተባበር 100 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያለው የመጀመሪያውን የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ አቋቋመ።  በዚሁ ስምምነት መሠረት IFC የ 200 ሚሊዮን ዶላር አስተዋፅኦ የሚያደርግ ሲሆን፤ ተቋሙ በባንክ ዘርፍ ያለውን የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠን በመቅረፍ በመላ አገሪቱ ተደራሽ የሆነ የቤት ፋይናንስ ስርዓት እንደሚዘረጋ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታውቀዋል። ይህ አጋርነት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገነቡና የኢትዮጵያውያንን ክብር የጠበቁ 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብ እንዲሁም በፋይናንስ ሥርዓቱ ውስጥ የግል ዘርፉን ተሳትፎ ለማስፋት ያለውን ግብ እንደሚያሳካ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።  ኢትዮጵያ ፈጣን፣ ጠንካራ እና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ መገንባቷን አጠናክራ እንደምትቀጥልም አጽንኦት ሰጥተዋል።
2 906
18
🌼ምን ማስተዋወቅ ይፈልጋሉ❓🌼 📌 የምንሰጣቸው የማስታወቂያ አገልግሎቶች ➠ የ ሙዚቃ ማስታወቂያ ➠ የ ኮንሰርት ማስታወቂያ ➠ የ ድርጅት ማስታወቂያ ➠ የ ዩቲዩብ ቻናል ማስታወቂያ ➠ ትሪትመንቶች እና ሌሎችም የሽያጮች ማስታወቂያ ✔የትምህርት ተቋማት…... ✔የህክምና ማዕከላት (ባህላዊ /ዘመናዊ)…... ✔የትራንስፖርት አገልግሎት….... ✔የስራ አገናኝ ኤጀንሲዎች…… ✔ሆቴል፣ካፌና ሬስቶራንቶች...... ➲ እንዲሁም የተለያዩ የ Business ስራወችን ከእኛ ጋ መስራት ለምትፈልጉ አናግሩን ምርትና አገልግሎቶን በተመጣጣኝ ዋጋ ተደራሽ በማድረግ በእጥፍ ያትርፉ። 👝 በአልን አስመልክቶ ልዩ ቅናሽ አድርገን አየጠበቅንዎት ነው አሁኑኑ ያናግሩን  🫴 👇 @Ethiozenaa_bot
2 781
19
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 63 ታራሚዎች ውስጥ 62 የህግ ታራሚዎች ሙሉ በሙሉ ማለፋቸው ተነገረ። የ12 ክፍል ማለፊያ ነጥብ ካመጡት ውስጥ 7ቱ ሴት ታራሚዎች ይገኙበታልም ተብላል፡፡   በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በከፍተኛ ጥበቃና በሴቶች ማረሚያና ማረፊያ ማዕከል እና በዘዋይ ማረሚያ ማእከላት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰዱት ተፈታኞች 63 ሲሆኑ ከእነዚህ ውስጥ 62 ማለፋቸውን ማረመያ ቤቱ አስታውቋል፡፡   በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ማዕከል ፣ በሴቶች ማረሚያ ማዕከላት በመደበኛ የትምህርት መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ እና ለፈተና የተቀመጡት 31 የህግ ታራሚዎች ሙሉ በሙሉ ወደ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችለውን ውጤት ማስመዝገብ ችለዋል፤ከነዚህም ውስጥ 7ቱ ሴቶች መሆናቸው ታውቋል፡፡   በተመሳሳይ የዝዋይ ማረሚያ ማዕከል ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ካስፈተናቸው 23 የህግ ተማሪዎች  መካከል 22ቱን ማሳለፍ መዘገባችን የሚታወስ ሲሆን በአጠቃላይ በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ፈተና ከወሰዱ 63 ታራሚስች 62 ማለፋችው ተነግራል፡፡የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ካስፈተናቸው በሁለቱ ማዕከላት አጠቃላይ ተፈታኝ ተማሪዎች መቶ በመቶ ወደ ዩኒቨርስቲ መግባት የሚያስችላቸውን ውጤት ማስመዘገብ ተችሏል፡፡ የሕግ ታራሚ ተማሪዎች ያስመዘገቡትን ውጤት ተከትሎ የቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል የመጀመሪያ ደረጃና አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ሳምሶን ወንድሜነህ እንደተናገሩት ማረሚያ ቤቱ ለታራሚዎች የፈጠረው ምቹ የትምህርት ከባቢ እና የታሪሚዎች ጠንካራ ተነሳሽነት ለዚህ አስደናቂ 100 ከመቶ ውጤት ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸውን ተናግረዋል። በማዕከላቱ የሚገኙት ትምህርት ቤቶች እንደማንኛውም የህዝብ ት/ቤት ደረጃውን የጠበቀና የተሟላ መምህራን የተመደቡለት መሆኑን የገለፁት አቶ ሳምሶን የህግ ታራሚ ተማሪዎችም በህግ ጥላ ስር ቢሆኑም ትምህርታቸውን በአግባቡ ሲከታተሉ መቆየታቸውንና ለውጤት እንደበቁም አመላክተዋል፡፡ አቶ ሳምሶን አክለውም በማረሚያ ቤት ውስጥ የሚገኙ ሌሎች ታራሚዎች ተስፋና መነሳሳትን የፈጠረ ሲሆን ማረሚያ ቤት የህይወት ማብቂያ ሳይሆን አዲስ ምዕራፍ መጀመሪያ መሆኑን በተግባር ያሳየ ነው፤ ብለዋል። የህግ ታራሚ ተማሪዎች  ያመጡት ውጤት መታረምና መታነፃቸውን ማሳያ በመሆኑን ገልፀው መንግስት በይቅርታና ምህረት መልቀቅ የሚችልበትን መንገድ አሊያም የትምህርት ሚኒስቴር የሕግ ታራሚ መሆናቸውን በመረዳት ትምህርታቸውን በርቀት እንዲከታተሉ ዩኒቨርሲቲዎችን እንዲያመቻችላቸው ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡  
2 790
20
ለጊዜው ከስራ ታገዱ‼️ 2ቱ የትራፊክ የቁጥጥር ባለሙያዎች ለጊዜው ከስራ እንዲታገዱ መደረጉ ተገለፀ:: የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን በከተማዋ የመንገድ ተጠቃሚዎችን ደህንነት ለማስጠበቅ
ለጊዜው ከስራ ታገዱ‼️ 2ቱ የትራፊክ የቁጥጥር ባለሙያዎች ለጊዜው ከስራ እንዲታገዱ መደረጉ ተገለፀ:: የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን በከተማዋ የመንገድ ተጠቃሚዎችን ደህንነት ለማስጠበቅና የትራፊክ እንቅስቃሴን ለማስፈጸም በሚያከናውናቸው የመስክ ቁጥጥር ስራዎች ወቅት ከመንገድ ተጠቃሚዎች ጋር አለመግባባቶች እንደሚከሰቱ ገልጿል። በትናንትናው ዕለት (ነሀሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም) በማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ ሲሰራጭ የዋለውን ምስል አስመልክቶ ተቋሙ ባወጣው መረጃ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች አብራርቷል፦ • የቁጥጥር ባለሙያዎች ደንብ የተላለፈን አሽከርካሪ የመንጃ ፈቃድ በሚጠይቁበት ወቅት "አልሰጥም" በማለት ስራ ማስተጓጎል፣ ስድብ፣ ዛቻ ወይም ሃይል መጠቀም በህግ የሚያስጠይቅ ተግባር መሆኑ ተመልክቷል። • ተቋሙ በምስሉ ላይ የታየውን አለመግባባት ግራና ቀኝ ያለውን አካል ሚዛናዊ በሆነ መንገድ በማጣራት ላይ እንደሚገኝና እስከዚያው ድረስ በክስተቱ ላይ የተሳተፉት ሁለቱ የቁጥጥር ባለሙያዎች ለጊዜው ከስራ እንዲታገዱ ማድረጉን አስታውቋል። ህብረተሰቡ የችግሩን የማጣራት ሂደት በስክነት እንዲከታተልና ትክክለኛ ካልሆኑ መረጃዎች እንዲቆጠብ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።
2 815