Ethio - ዜና 🇪🇹
የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot
Показати більше📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Ethio - ዜና 🇪🇹
Канал Ethio - ዜና 🇪🇹 (@ethio_zena23) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 105 377 підписників, посідаючи 71 місце в категорії Картинки та 275 місце у регіоні Ефіопія.
📊 Показники аудиторії та динаміка
З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 105 377 підписників.
За останніми даними від 20 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -2 810, а за останні 24 години на -118, загальне охоплення залишається високим.
- Статус верифікації: Не верифікований
- Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 3.28%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 2.26% реакцій від загальної кількості підписників.
- Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 3 455 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 381 переглядів.
- Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 25.
📝 Опис та контентна політика
Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
“የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ!
ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን
@Ethiozenaa_bot”
Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 21 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Картинки.
Триває завантаження даних...
| Дата | Залучення підписників | Згадування | Канали | |
| 21 липня | 0 | |||
| 20 липня | 0 | |||
| 19 липня | 0 | |||
| 18 липня | 0 | |||
| 17 липня | 0 | |||
| 16 липня | 0 | |||
| 15 липня | 0 | |||
| 14 липня | 0 | |||
| 13 липня | 0 | |||
| 12 липня | 0 | |||
| 11 липня | 0 | |||
| 10 липня | 0 | |||
| 09 липня | 0 | |||
| 08 липня | 0 | |||
| 07 липня | 0 | |||
| 06 липня | 0 | |||
| 05 липня | 0 | |||
| 04 липня | 0 | |||
| 03 липня | 0 | |||
| 02 липня | 0 | |||
| 01 липня | 0 |
| 2 | በአከራይ ተከራይ ውል መፈጸም የሌለባቸው እና የተከለከሉ ተግባራት...
በአዲስ አበባ ከተማ በአከራይ ተከራይ ውል የሚከተሉትን ተግባራት መፈጸም የተከለከለ ነው።
👉የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ሳያስመዘግቡ መከራየትና ማከራየት፤
👉በአከራይ ወይም ተከራይ ቸልተኝነት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል በአዋጁ የተቀመጠውን የጊዜ ገደብ አሳልፎ ማስመዝገብ፤
👉የመኖሪ ቤት ኪራይ ውል እድሳት አለማስመዝገብ፤
👉በአዋጁ ከተፈቀደው አግባብ ውጪ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ፤
👉አዋጁ ከሚፈቅደው ውጪ የውል ዘመን ሳይጠናቀቅ ከቤት ማስወጣት፤
👉በአዋጁ የተቀመጠውን የማስታወቂያ ወይም የማስጠንቀቂያ ጊዜ ሳይሰጥ ውል ማቋረጥ፤
👉አዋጁ ላይ ከተቀመጠው መጠን በላይ የቅድመ ክፍያ እንዲፈፀም ማስገደድ፤
👉 በባንክ ወይሞ በሌላ ሕጋዊ በሆነ የኤሌክትሮኒክ የክፍያ ስርዓት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ክፍያ አለመፈፀም
👉 ቀደም ሲል ሲከራይ የቆየ የመኖሪያ ቤት ወይም ግንባታው ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ አዲስ መኖሪያ ቤት ያለአገልግሎት እንዲቀመጥ ማድረግ እና ፤
👉በአዋጁ ለአከራይ የተሰጠውን ማበረታቻ ያለአግባብ ለመጠቀሞ ሀሰተኛ መረጃ ወይም ማስረጃ ማቅረብ የተከለከለ መሆኑን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
@Seledadotio
@Seledadotio | 1 426 |
| 3 | የኤሌክትሪክ ፍጆታ ማባዣ ጭማሪ ተደርጓል። ለመኖሪያ ቤት ከተያዘው ወር ሀምሌ ጀምሮ እስከ መስከረም ወር የሚፈፀም የኤሌክትሪክ ፍጆታ ታሪፍ ክፍያ ከላይ ተያይዟል።
@Seledadotio
@Seledadotio | 1 789 |
| 4 | በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ከ1ሺህ 4መቶ በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል ተባለ
በሳምንቱ ውስጥ በተደረገ 6 ዙር በረራ 1ሺህ 4መቶ 81 ኢትዮጵያዊያን መመለሳቸዉን የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታዉቋ፡፡
የተመለሱት 8መቶ79 ወንዶች፣ 5መቶ54 ሴቶች እና 48 ጨቅላ ህፃናት ሲሆኑ፤ከተመላሾች መካከል 82 እድሜያቸው ከአስራ ስምንት አመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ይገኙበታል።
መስከረም 5/ 2018 በተጀመረው ዜጎችን ወደ ሀገር ቤት የመመለስ ስራ እስካሁን ከ87 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገር መመለስ ተችሏል ተብሏል።
ሚኒስቴሩ ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ የማድረግ እና ከቤተሰብ ጋር የማቀላቀል ስራ ከሚመለከታቸው ባለድርሻና አጋር አካላት ጋር በመተባበር በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ አስታዉቋል፡፡
በተጨማሪም መደበኛ ባልሆነ ፍልሰት ወደ ተለያዩ ሀገራት ሄደው የሚመለሱ የፍልሰት ተጎጂዎችን ለመደገፍና መልሶ ለማቋቋም የሚያስችሉ ተግባራትን በትብብር እያከናወነ መሆኑን ገልጿል፡፡
ወደፊትም በህገወጥ የሰዎች ዝውውር አስከፊነት ዙሪያ ህብረተሰቡን ለማስገንዘብ፣ መደበኛ ያልሆነ ፍልሰትን ለመከላከልና ደህንነቱ የተጠበቀ ፍልሰትን ለማበረታታት ሚኒስቴሩ የጀመራቸውን ስራዎች አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግሯል፡፡
@Seledadotio
@Seledadotio | 2 172 |
| 5 | በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ2018 ትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ተለቋል።
ተማሪዎች ቀጥሎ ባለው ሊንክ መለያ ቁጥራችሁን እና ስማችሁን በማስገባት ውጤታችሁን ማየት ትችላላችሁ 👇 http://ce.ministry.et
@Seledadotio
@Seledadotio | 2 343 |
| 6 | ለሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ መናር ዋነኛው ምክንያት የቡና ነጋዴዎች ናቸው ተባለ
ኢትዮጵያ ቀዳሚ የቡና አምራች ሀገር ብትሆንም፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለሚታየው የሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ መጨመር ዋነኛው ምክንያት የቡና ላኪዎች ምርቱን በተጋነነ ዋጋ ማቅረባቸው መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል።
የባለስልጣኑ የዋና ዳይሬክተር ጽህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ሰፊሳ አባቡ ለመናኸሪያ ሬድዮ እንደገለጹት፣ በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ለውጭ ገበያ ከቀረበው የቡና ምርት የተገኘው ገቢ ከፍተኛ ቢሆንም፣ በሀገር ውስጥ ገበያ ላይ ግን የዋጋ ጭማሪ ታይቷል።
ባለስልጣኑ በዘርፉ የቁጥጥር ሥራ እያከናወነ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት የሀገር ውስጥ የቡና ዋጋ ከአለም አቀፍ የገበያ ተመን ጋር ሲነጻጸር ሰፊ ልዩነት እንዳለው አስረድተዋል።
ላኪዎች እርስ በርሳቸው በመነጋገር ተቀራራቢና የተረጋጋ ዋጋ እንዲያቀርቡ በተደጋጋሚ ቢነገራቸውም፤ ወዳልተገባ የዋጋ ሽሚያ በመግባታቸው ምክንያት በገበያው ላይ አለመረጋጋት መፈጠሩን ኃላፊው ገልጸዋል።
ይህ የዋጋ መጋነን የሀገሪቱን የቡና ዘርፍ ወደ ኋላ የሚጎትት በመሆኑ ባለስልጣኑ ላኪዎችን በውይይት ለማስማማት ጥረት ማድረጉን ጠቅሰዋል። | 2 386 |
| 7 | የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሰናል-ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል‼️
ዛሬ ሐምሌ 12/2018 ዓ.ም በመቀሌ ህዝቡን እና አመራሩን ሰብስበው አወያይተዋል።
የትግራይ ህዝብ ጭቆናን የመሸከም ታሪክ የለውም ያሉት ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል፤ ይልቁንም መብቶቹ ለማረጋገጥ በመደራጀት ታግሏል፣ መብቶቹን አስከብሯል እንዲሁም የሌሎች ብሔረሰቦችን መብቶች አክብሮ የመጣ ህዝብ ነው ብለዋል።
ለ17 ዓመታት በተደረገው የትጥቅ ትግል ውስጥ የትግራይ ህዝብ ከባድ መስዋእትነት በመክፈል አንባገነኑ የደርግ ስርዓት መደምሰሱን ያወሱት ዶክተር ደብረፅዮን፤ በአንባገነኑ መቃብር በሃገር ደረጃ ሰላም፣ ልማትና የዴሞክራሲ ግንባታ ማረጋገጡን ጠቅሷል፡፡
ሆኖም፣ ይህንን መቀበል ያልቻሉ ሐይሎች ጊዜና አጋጣሚውን በመጠበቅ፣ የትግራይን ህዝብ ከምድረገፅ ለማጥፋት በህዝባችን ላይ ጀኖሳይድ ፈፅሟል ያሉት ፕረዝዳንቱ፤ የትግራይ ህዝብ አንድነቱ በመጠበቅ ልህልውናው በከፈለው መስዋዕትነት ጭቆናን እና ህልውናውን ለማጥፋት ለመጣው ሐይል የማይቀበል መሆኑ በዓለም አደባባይ ያስመሰከረ እንደሆነ ጠቅሷል፡፡
የፕሪቶሪያው ስምምነት ሲፈረም፤ የትግራይ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ፣ ተፈናቃዮችን ለመመለስ እና ልማትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ ተስፋ አድርገን ነበረ ያሉት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፤የፌደራል መንግሥቱ በታቀደ ሁኔታ ትግራይን ዳግም ወደ ከበባና ክልከላ በማስገባት ለዳግም ጀኖሳይድ እየተዘጋጀ እንደሚገኝ አብራርቷል፡፡
እንደ ትግራይ፣ ለሰላም ስንል ከፍተኛ ትዕግስትና መስዋዕትነት እየከፈልን ነው፤ ይሁን እኛ ብቻ ሰላም ስለ ፈለግን ሊሳካልን አልቻለም ያሉት ዶ/ር ደብረፅዮን፤ አንድነታችን አጠናክረን የትግራይ መሰረታዊ ጥያቄዎች ማረጋገጥ ብቸኛ መፍትሔ ሆኖ መገኘቱ ተናግሯል፡፡
አሁን ባለንበት ሁኔታ መቀጠል አንችልም ያሉ ሲሆን እንደህዝብ የመከተ ዓቅሞቻችን በማደራጀት ህልውናችን ለማረጋገጥ በምንወስንበት ምዕራፍ ላይ እንገኛለን ብሏል፡፡
የፌደራል መንግስቱ ለሰላም በፍጹም ዝግጁ አይደለም፤ ስለዚህ ብሔራዊ ክብራችንና ሉዓላዊነታችንን ለመመለስ እንዲሁም የተፈናቀሉ ወገኖቻችንን መልሶ ለማቋቋም ትግላችንን ወደ ተጨባጭና ውጤታማ ደረጃ ማሸጋገር ይገባናል ብሏል፡፡ | 2 490 |
| 8 | ላ ሮሃ በድጋሚ የአለም ንግሥት፡ ስፔን አርጀንቲናን ጥላ የ2026ቱን ዋንጫ አነሳች!
ስፔን አስጨናቂ በሆነው የጭማሪ ሰዓት ጨዋታ አርጀንቲናን 1ለ0 በማሸነፍ ለሁለተኛ ጊዜ የዓለም ዋንጫ ባለቤት መሆን ችላለች።
በኒው ዮርክ ኒው ጀርሲ ስታዲየም በተደረገው በዚህ ታሪካዊ ጨዋታ፣ የባርሴሎናው ኮከብ ፌራን ቶሬስ በ106ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ብቸኛ ግብ ለስፔን ድል አብስራለች።
ጨዋታው በአርጀንቲናዎች ጠንካራ መከላከያ የታጀበ ሲሆን፣ ኤንዞ ፈርናንዴዝ በሁለት ቢጫ ካርድ ከሜዳ መውጣቱ ለሊዮኔል ሜሲ የመጨረሻ የዓለም ዋንጫ ስንብት መራር ኪሳራ ሆኗል።
ስፔን 20 ለ 2 የጎል ሙከራ በማድረግ ጨዋታውን በበላይነት ብትመራም፣ የአርጀንቲናው ግብ ጠባቂ ኤሚ ማርቲኔዝ ድንቅ ብቃቱን አሳይቷል።
ከመጨረሻው ፊሽካ በኋላ በተፈጠረ ግጭት ሌአንድሮ ፓሬዴስ በቀይ ካርድ ተባሯል።
ይህ በታዋቂ ሰዎችና በዶናልድ ትራምፕ የክብር ቦክስ እይታ የተደረገው የፊፋ የጥበብ ድግስ፣ በስፔን ደስታና ታሪክ ሰሪነት ተደምድሟል። | 2 506 |
| 9 | "ኔታንያሁ ኒዮርክ ከተማ ከገቡ ይታሰራሉ" - ከንቲባ ማምዳኒ
የኒዮርክ ከንቲባ ዞህራን ማምዳኒ በእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ የወጣውን የእስር ትዕዛዝ ተግባራዊ አደርጋለሁ አሉ።
ዓለማቀፍ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) እስራኤል በጋዛ ጦርነት የጦር ወንጀል ፈፅማለች በሚል በኔታንያሁና ሌሎች ሁለት ባለስልጣናት ላይ የእስር ትዕዛዝ ማውጣቱ ይታወቃል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቀጣይ ሳምንት ከፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ለመወያየት ወደ አሜሪካ ይጓዛሉ።
ከንቲባ ዞህራን ማምዳኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያም ኔታንያሁ በሚመሯት የኒዮርክ ከተማ ከገቡ እንደሚታሰሩ ተናግረዋል።
"በጉዳዩ ዙሪያ እየተወያየን ነው፤ ግን ህግ እንደ አዲስ አይፃፍም" ሲሉ አይሲሲ ያወጣውን መመሪያ እንደሚተገብሩ ጠቁመዋል።
"በኒውዮርክ እስካለው ድረስ የከተማ ህግ አድርገው ብሎ የሚፈቅድልኝን ለማድረግ ዝግጁ ነኝ" ብለዋል። ማምዳኒ "ኔታንያሁ የጦር ወንጀል ፈፅመዋል ብየ አምናለሁ"ሲሉ ገልጸዋል።
"እሱ ባለፉት አመታት በሰራቸው ወንጀሎች መቅረብ ያለበት ሄግ በሚገኘው ፍርድቤት ነው" ብለዋል። ከንቲባ ማምዳኒ ወደ ኃላፊነት እንደመጡ ተመሳሳይ አስተያየት ሰጥተው ነበር።
ኔታንያሁ ከማምዳኒ ሹመት በኋላ ወደ አሜሪካ ቢያቀኑም ኒዮርክ ከተማ ግን አልገቡም።
ነገር ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከንቲባው ወደ ሚያስተዳድሯት ኒዮርክ የሚገቡት በመጪው መስከረም ወር በሚካሄደው የተመድ አመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ነው።
@Seledadotio
@Seledadotio | 2 767 |
| 10 | ትምህርት ሚኒስቴር በዩኒቨርሲቲዎች አዲስ የአመራር ሹመት መምሪያ ይፈ አደረገ‼️
ትምህርት ሚኒስቴር በመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚሾሙ ፕሬዝዳንቶችና ምክትል ፕሬዝዳንቶች አሰያየምን የሚገዛ አዲስ መመሪያ ይፋ አድርጓል።
መመሪያው በብቃትና በውድድር ላይ የተመሰረተ አሰራርን ለማስፈን ያለመ ሲሆን፣የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የአንድ ጊዜ የስራ ዘመን 6 ዓመት እና የምክትል ፕሬዝዳንቶች 4 ዓመት መሆኑ ተነግሯል።
በማንኛውም የመንግስት ዩኒቨርሲቲ በተከታታይ ሁለት ጊዜ በፕሬዝዳንትነት ያገለገለ አመራር በድጋሚ መወዳደር እንደማይችልም ተገልጿል።
ለፕሬዝዳንትነት የሚወዳደሩ ወንድ እጩዎች ቢያንስ የረዳት ፕሮፌሰርነትና ከዚያ በላይ ማዕረግ ሊኖራቸው የሚገባ ሲሆን፣ቢያንስ 2 ዓመት በፕሬዝዳንትነት ወይም 3 ዓመት በምክትል ፕሬዝዳንትነት/ዲንነት ያገለገሉ መሆን እንደለባቸው ገልጿል።
አመራሩ በየ 3 ወሩ በቦርዱ የሚገመገም መሆኑ እና ። ውጤቱ በሁለት ተከታታይ የስድስት ወር ግምገማዎች ከ60% በታች ከሆነ፣ በጤና እክል ወይም በዲሲፕሊን ጉድለት ከሃላፊነቱ እንዲነሳ ለሚኒስቴሩ ሀሳብ ይቀርባል ተብሏል።
በምልመላና ምርጫ ሂደቱ ላይ ቅሬታ ያለው ተወዳዳሪ፣ ውጤቱ በይፋ በተገለጠ በ10 ቀናት ውስጥ ለዩኒቨርሲቲው ቦርድ ቅሬታውን ማቅረብ እንደሚችል አረጋግጧል።
@Seledadotio
@Seledadotio | 2 804 |
| 11 | "የድሬክ እርግማን/መጥፎ እድል" አርጀንቲናን ከአለምሻምፒዮንነት ያስቀራት ይሆን?
ድሬክ የምሽቱን የአለምዋንጫ ፍጻሜ ጨዋታ አርጀንቲና ታሸንፋለች ሲል 1.5 ሚሊዮን ዶላር አስይዟል።
ድሬክ በተደጋጋሚ እሱ ያሸንፋሉ ሲል ገንዘብ ያስያዘባቸዉ ቡድኖች ሲሸነፉ ታይቷል። በቅርቡ እንኳ በአዉሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ አርሰናል ፤ ፒኤስጂን ያሸንፋል ሲል አስይዞ ገንዘቡን ተበልቷል።
ድሬክ በሌሎች ጨዋታዎችም እድል የማይቀናዉ ሲሆን የዛሬዉን ዉርርድ ካሸነፈ ግን 5.2 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ያሸንፋል። | 2 770 |
| 12 | የኢራን ሚሴኤሎች ኢላማቸውን መቱ‼️
ኢራን በጆርዳን በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ቤዝ ላይ በቀጥታ ጥቃት ስትፈፅም የሚያሳይ ምስል ይፋ አድርጋለች።
በዚህ ጥቃት በርካታ ሰው አልባ አውሮፕላኖች እና ቅንጡ የሆነውን Hawk helicopter (21million dollar) ማውደሟን፣በርካታ ወታደሮች መገደላቸውን ገልፃለች።
ለዚህ ኢላማውን ለጠበቀ ጥቃት አሜሪካ ራሺያን እና ቻይናን እየወቀሰች ትገኛለች።
አሜሪካም በሆርሙዝ ዳርቻ በሚገኘው የኢራን ነዳጅ ማከማቻ ላይ በሬክተር ስኬል 5 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ማድረሱን ገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter | 2 739 |
| 13 | በ2026 ዓለም ዋንጫ እንግሊዝ ፈረንሳይን በመርታት የነሐስ ሜዳሊያ አሸነፈች
በ2026 የዓለም ዋንጫ ትናንት ሌሊት የሶስተኛ ደረጃን ለማግኘት በተደረገ እጅግ አስደናቂ እና ታሪካዊ ጨዋታ እንግሊዝ ፈረንሳይን 6 ለ 4 በማሸነፍ የነሐስ ሜዳሊያ ባለቤት ሆናለች።
ጨዋታው በጎል ናዳ የታጀበና በርካታ አዳዲስ ክብረወሰኖች የተመዘገቡበት ነበር።
በመጀመሪያው አጋማሽ እንግሊዝ ፍጹም ብልጫ በመውሰድ 4 ለ 0 መሪ መሆን የቻለች ቢሆንም፣ በሁለተኛው አጋማሽ ፈረንሳይ ጠንካራ ፉክክር በማድረግ እስከ 5 ለ 4 ማጥበብ ችላ ነበር።
ይሁን እንጂ በጭማሪ ሰዓት ጁድ ቤሊንግሃም ያስቆጠራት ስድስተኛ ጎል የእንግሊዝን ድል አረጋግጣለች።
በጨዋታው ላይ ቡካዮ ሳካ ሀትሪክ የሰራ ሲሆን፣ ጁድ ቤሊንግሃም በዓለም ዋንጫ ታሪክ 7 ጎሎችን በማስቆጠር የመጀመሪያው እንግሊዛዊ ሆኗል።
በፈረንሳይ በኩል ኪሊያን ምባፔ ጎል በማስቆጠር የዓለም ዋንጫ የምንግዜም ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪነቱን ሲያጠናክር፣ ሚካኤል ኦሊሴ ደግሞ የፔሌን የለጋሽነት (assist) ክብረወሰን እኩል አድርጓል።
ይህ ድል እንግሊዝ ላለፉት 60 ዓመታት በዓለም ዋንጫ ያገኘችው ምርጥ ውጤት ሲሆን፣ አሰልጣኝ ቶማስ ቱሄልም ቡድናቸውን ለታላቅ ስኬት አብቅተዋል። | 2 754 |
| 14 | አሜሪካ የኢራንን ድልድዮች ማጥቃት ጀመረች‼️
አሜሪካ የኢራንን ዋና ድልድዮች እንዲሁም የውሃ ማጣሪያ ተቋሟት ላይ ጥቃት በመፈፀም ጉዳት አድርሳለች።
@Seledadotio
@Seledadotio | 2 784 |
| 15 | በደብረ ማርቆስ ከተማ ፍርድ ቤት ውስጥ የጠበቃውን ስልክ የሰረቀችው ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዋለች !
በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በአብማ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 13 ከሚገኘው ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሀምሌ 9 ቀን 2018 ዓም ከቀኑ 5 ሰአት በሚሆንበት ግዜ የወንጀል ድርጊቱ መፈፀሙን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።
የግል ጠበቃ ከሆነው ግለሰብ ስራውን ጨርሶ ጋውን በማውለቅ ላይ እያለ ጉዳይ ለማስፈፀም የመጣችው ተጠርጣሪ ከጠበቃው ቴክኖ ሞባይል ሰርቃ ብትሰወርም....
ፖሊስ ከአካባቢው ማህበረሰብ እና በወቅቱ ከነበሩ የህግ ባለሙያዎች ያገኘውን መረጃ መሰረት አድርጎ ባከናወነው ያልተቋረጠ ክትትል ወዲያውኑ ሞባይሉን የገዛውን ጨምሮ በወንጀሉ የተጠረጠረችዋን ግለሰብ በቁጥጥጥር ስር አውሎ በተፋጠነ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የ1ኛ ፖሊስጣቢያ የወንጀል ምርመራ ክፍል ሀላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ልጃለም ውበቴ ገልፀዋል ፡፡ | 3 021 |
| 16 | "ኦሮሚያ ክልል 'ጠፍቶ' ለማየት የሚመኙ አሉ፤ ምኞታቸው ግን በፍጹም አይሳካም" አቶ ሽመልስ አብዲሳ
የኦሮሚያ ክልል "ጠፍቶ" ለማየት የሚመኙና "ኦሮሚያ" የሚለውን ቃል መስማት የማይፈልጉ አካላት እንዳሉ የክልሉ ርዕሰ መሥተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ።
በአዳማ ከተማ በተካሄደ የመንግሥት አመራሮች መድረክ ላይ ርዕሰ መሥተዳድሩ በኦሮምኛ ቋንቋ ባደረጉት ንግግር፣ ይህ ምኞት "በፍጹም" ሊሳካ እንደማይችልና ክልሉ ይበልጥ እየጠነከረና ውጤታማ እየሆነ እንደሚሄድ አረጋግጠዋል።
አቶ ሽመልስ የእነዚህን አካላት ማንነት በስም ባይጠቅሱም፣ ንግግሩን ያደረጉት የክልሎች አወቃቀር ጉዳይ ለአገራዊ ምክክር ጉባኤ በአጀንዳነት በቀረበ ማግስት ነው። | 2 973 |
| 17 | #ጤናመረጃ
የሀበሻ ጎመን ዋና ዋና የጤና ጥቅሞች!
የሀበሻ ጎመን በቪታሚኖች (C, A, K) በማዕድናት (ካልሲየም፣ ብረት) እና በፀረ-ኦክሲዳንት ንጥረ ነገሮች እጅግ የበለፀገ ነው።
1. ለአጥንት ጥንካሬና ጤንነት፦ የሀበሻ ጎመን እጅግ ከፍተኛ የካልሲየም (Calcium) እና የቪታሚን ኬ (Vitamin K) ይዘት ስላለው፣ ለአጥንት መገንባት፣ ለጥንካሬ እና የአጥንት መሳሳትን ለመከላከል አስተዋጽኦ አለው።
2. በሽታ የመከላከል አቅምን ለማጠናከር፦ በውስጡ ባለው ከፍተኛ የቪታሚን ሲ መጠን ምክንያት፣ የሰውነትን በሽታ የመከላከል ሥርዓት በማገዝ ከኢንፌክሽኖች እና ከተለያዩ በሽታዎች ይጠብቃል።
3. የደም ማነስን ለመከላከል፦ ጎመን በውስጡ ከፍተኛ የiron ማዕድን ይዟል። ይህም የሰውነታችንን ቀይ የደም ሴል ምርት በማገዝ የደም ማነስ ችግር እንዳይከሰት ትልቅ እገዛ ያደርጋል።
4. ለምግብ መፈጨት ሥርዓት፦ ልክ እንደ ጥቅል ጎመን ሁሉ፣ የሀበሻ ጎመንም ከፍተኛ የፋይበር (የቃጫ) ይዘት ስላለው የሆድ ድርቀትን ለመከላከል እና የአንጀትን ጤንነት ለመጠበቅ ይረዳል።
5. ለአይን ጤንነትና እይታ፦ በአይን ላይ የሚመጡ የዕድሜ መግፋት ጉዳቶችን እና ሌሎች የዓይን በሽታዎችን የመከላከል አቅም ያላቸውን ሉቲን እና ቪታሚን ኤ በበቂ መጠን ይዟል።
6.ለቆዳና ለፀጉር ውበት፦ በውስጡ የሚገኙት ቪታሚኖች (A,C,E) እና ፀረ-ኦክሲዳንቶች ለቆዳ ጤንነት፣ ለወጣትነት ገጽታ እና ለፀጉር ጥንካሬ አስተዋጽኦ ያደርጋሉ።
ጠቃሚ ምክር :- የሀበሻ ጎመንን ከመጠን በላይ ሳያበስሉ (ሳይሞት) በመጠኑ አብስሎ መመገብ በውስጡ ያሉትን ጠቃሚ ንጥረ ነገሮች ሙሉ በሙሉ ለማግኘት ይረዳል።(ኢትዮ-መረጃ)
ጠቃሚ ነውና ለወዳጆ ያካፍሉ! ሼር!
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter | 2 963 |
| 18 | ''አዳዲስ ቀረጦች ሊጣሉ ነው‼️
በነዳጅ፣ በሪል እስቴት፣ በአልኮልና በትምባሆ እንዲሁም በኢንቨስትመንት ታክስ ነፃ መብቶች ላይ አዳዲስ ቀረጦች ሊጣሉ መሆኑ ተሰምቷል።
IMF እንደገለጸው የኢትዮጵያ መንግሥት 5 ቢሊዮን ዶላር አዲስ የውጭ ብድር ለማግኘት ሲል እነዚህን ሰፊ የታክስ ማሻሻያዎች ተግባራዊ ለማድረግ ወስኗል። ይህ የሆነው የብድሩ ቅድመ ሁኔታ የሀገሪቱን የውስጥ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ስለሚጠይቅ እንደሆነም ተብራርቷል።
በዚህም መሠረት የነዳጅ ድጎማው ሙሉ በሙሉ ተነስቶ ዋጋው በገበያ እንዲወሰን የሚደረግ ሲሆን፣ በሪል እስቴት፣ በመኪና ባለቤትነት እና በተለያዩ ምርቶች ላይ አዳዲስ ቀረጦች የሚጣሉ ይሆናል ተብሏል።
• ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በአንድ ወቅት የዓለም አቀፉን የገንዘብ ድርጅት (IMF) ብድር ቀላልነት ሲገልጹ «ከአይ.ኤም.ኤፍ መበደር ከእናት መቀነት እንደ መፍታት ነው...» ማለታቸው ይታወሳል። ይሁን እንጂ ዛሬ ላይ የዚያ "ቀላል" ብድር ዋጋና ቅድመ-ሁኔታዎች በዜጎች ኪስ ላይ እየፈጠሩት ያለው ጫና ቀላል አለመሆኑን ብዙዎች እየተናገሩ ይገኛሉ።
በየጊዜው የሚጨመሩ ታክሶች፣ አዳዲስ ቀረጦች እና የዋጋ ንረቱ «ለመሆኑ ለብድር ተብሎ በሕዝብ ላይ ታክስ መጫን ተለመደ እንዴ?» የሚል ጥያቄ አስነስቷል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገሪቱ እየተተገበሩ ያሉ የፖሊሲ ለውጦች (የኤክሳይዝ ታክስ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ማሻሻያዎች እና የተለያዩ የአገልግሎት ክፍያ ጭማሪዎች) ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ያለውን ማህበረሰብ ክፉኛ እየፈተኑት ይገኛሉ።
ከውጭ ምንዛሬ ተመን መለቀቅ ጋር ተዳምሮ የሸቀጦች ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል።
https://t.me/Ethio_Zena23
https://t.me/Ethio_Zena23 | 2 766 |
| 19 | ነገ በአዲስ አበባ ለሚደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ሆኑ‼️
ሰልፉ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል።
በትግራይ ክልል እየተባባሰ የመጣውን ቀውስ ለመቃወምና ለማስቆም እንዲሁም ለፌደራል መንግሥትና ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ለማሳወቅ ”አፈሳ ይቁም ሰላም ይስፈን” በሚል መሪ ቃል ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ በመስቀል አደባባይ ሰላማዊ ሰልፉ ይደረጋል።
ሰልፉ ተጀምሮ እስከ ሚጠናቀቅበት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።
በዚህም መሰረት:-
👉 ከመገናኛ በ22 አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ ቅ/ዑራኤል አደባባይ
👉 በቦሌ መንገድ ወደ መስቀል አደባባ ኦሎምፒያ አደባባይ
👉 ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ መስቀለኛ ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ
👉 ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ መስቀል ለገሀር መብራት
👉 ከለገሀር ቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታዲዮም ለገሀር ቴሌ ማቋረጫ
👉 ከአራት ኪሎ ወደ መሰቀል አደባባይ ብሔራዊ ቤተ-መንግስት
👉ከካሳንቺስ በመቅረዝ ሆስፒታል ወደ መስቀል አደባባይ መቅረዝ ሆስፒታል አጠገብ
👉ከአምባሳደር ቴአትር ወደ መስቀል አደባባይ ሐራምቤ መብራት የሚወስዱ መንገዶች ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ መንገዶቹ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።
ከዛሬ ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በመስቀል አደባባይና በዙሪያው ባሉ መንገዶች ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ተሽከርካሪ ለአጭርም ሆነ ረዥም ሠዓት ማቆም የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል።
@Seledadotio
@Seledadotio | 2 841 |
| 20 | ሴት መስሎ በመቅረብ ስርቆት ለመፈጸም ሲንቀሳቀስ የነበረ ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለ።
10/11/2018ዓ/ም | በሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ሴት መስሎ በመቅረብ ህብረተሰቡን ለመሸወድ እና የተለያየ ስርቆት ለመፈጸም ሲንቀሳቀስ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተደረገበት እንደሚገኝ የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ።
ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ሊውል የቻለው በሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር በሜጦማ ቀበሌ ልዩ ስሙ መምህራን መንደር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ መሆኑ ታውቋል።
አቡሽ የተባለውና የትውልድ ስፍራው በምዕራብ ባደዋቾ ቆቶ ቀበሌ የሆነው ይህ ግለሰብ ወንድነቱን በመደበቅ ራሱን ሙሉ በሙሉ ወደ ሴትነት በመለወጥ ህዝብን ሲያታልል እንደነበር ተገልጿል።
ግለሰቡ የወንጀል ዓላማውን ለማሳካት የሴት ቀሚስ ፣ ሰው ሰራሽ ፀጉር (ዊግ) እና የሴት ጡት መያዣ በመጠቀም ራሱን በመለወጥ ስርቆት ለመፈጸም ሲንቀሳቀስ ነበር።
የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ም/ኢ/ር አድማሱ ሱሎሮ እንደገለጹት ግለሰቡ በተደረገበት የህዝብ ጥቆማ በቁጥጥር ስር ሊውል የቻለ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም በጸጥታ ኃይሎች ተይዞ ጥልቀት ያለው ምርመራ እየተደረገበት ይገኛል።
Via፦ ሺንሽቾ መንግስት ኮሙኒኬሽን
@Seledadotio
@Seledadotio | 3 308 |
