es
Feedback
Ethio - ዜና 🇪🇹

Ethio - ዜና 🇪🇹

Ir al canal en Telegram

የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot

Mostrar mĂĄs

📈 Análisis del canal de Telegram Ethio - ዜና 🇪🇹

El canal Ethio - ዜና 🇪🇹 (@ethio_zena23) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 104 475 suscriptores, ocupando la posición 72 en la categoría Fotos y el puesto 285 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 104 475 suscriptores.

SegĂşn los Ăşltimos datos del 01 agosto, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los Ăşltimos 30 dĂ­as la variaciĂłn de miembros fue de -2 616, y en las Ăşltimas 24 horas de -70, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificaciĂłn: No verificado
  • Tasa de interacciĂłn (ER): El promedio de interacciĂłn de la audiencia es 3.21%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 2.29% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicaciĂłn recibe en promedio 3 358 visualizaciones. En el primer dĂ­a suele acumular 2 398 visualizaciones.
  • Reacciones e interacciĂłn: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicaciĂłn es 24.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot”

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (Ăşltimos datos recibidos el 02 agosto, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analĂ­tica demuestra que la audiencia interactĂşa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categorĂ­a Fotos.

104 475
Suscriptores
-7024 horas
-6387 dĂ­as
-2 61630 dĂ­as
Archivo de publicaciones
የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ። በአማራ ክልል የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል።ከሰኔ 3-5/2018 ዓ.ም የተሰጠውን የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ
የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ። በአማራ ክልል የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል።ከሰኔ 3-5/2018 ዓ.ም የተሰጠውን የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና 173,699 ተማሪዎች ውስደው ነበር። ፈተናውን ከወሰዱት ተማሪዎች መካከልም 135,003 (77.72%) ተማሪዎች 50% እና በላይ ውጤት አስመዝግበዋል። ተማሪዎችም ውጤታቸውን https://amhara.ministry.et/#/result የሚለውን አድራሻ በመፃፍ ፤ በሚመጣው ቅጽ ላይ  የተማሪ መለያ ቁጥር (Registration Number) እና ስም በአማርኛ በማስገባት ፤ ዉጤት ይመልከቱ (Check your result) የሚለውን ቁልፍ በመጫን ማየት ይችላሉ፡፡ በተጨማሪም @emacs_ministry_result_qmt_bot  ላይ መመልከት ይችላሉ። ተማሪዎች ማንኛውም ከውጤት ጋር የተያያዘ ቅሬታ ካላቸው https://amhara.ministry.et/#/complaint ላይ በመግባት ቅሬታቸው ማቅረብ እንደሚችሉ የክልሉ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል። 2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይደረጋል ተብሏል።

"ወደ አራት ኪሎ እንመለሳለን" የሚለውን ቅዠት በአስቸኳይ ማቆም ይገበዋል❗❗ "ግጭቱን ማንና መቼ እንደጀመረው ለማወቅ አስቀድሞ ተዘጋጅቶ የወጣውን የኋላቀሩ ቡድን መግለጫ ከመስማት ይልቅ፣ ገለልተኛ አካላት የሚያደርጉትን የሳተላይት ክትትልና የክትትሉን ውጤት መጠበቅ ተገቢ ነው"— ስምረት ፓርቲ❗ ​በቀድሞ የህወሓት አመራሮች የተመሰረተው ስምረት ፓርቲ፣ የትግራይ ሕዝብ የማይፈልገውና የማይመኘው አዲስ ወታደራዊ ግጭት መከሰቱን አስታወቀ። ፓርቲው ባወጣው መግለጫ፣ አሁን የተከፈተው ጦርነት በውጭ ኃይሎች ፍላጎትና እቅድ የሚመራ መሆኑን በመጥቀስ የሁኔታው ምስጢር አስቀድሞ የታወቀ በመሆኑ እንቅስቃሴው ሳይስፋፋ የሚከሽፍ እንደሆነና የዚህ አላስፈላጊ ግጭት ዋና ሰለባ እየሆነ ያለው የትግራይ ወጣት መሆኑ የሚያሳዝን ነው ብሏል። ​ፓርቲው አክሎም፣ ቡድኑ የፕሪቶሪያውን የሰላም ውል በመጣስና የጊዜያዊ አስተዳደሩን ሥልጣን በኃይል ገልብጦ ህገ-ወጥ አስተዳደር ከመሠረተ በኋላ፣ አሁን ደግሞ "ግዛታዊ አንድነትን ማስከበር" በሚል ሽፋን በውጭ ኃይሎች ተመክቶ አዲስ ጦርነት ደግሷል ሲል ከሷል። ቀደም ሲል ሲካሄዱ የነበሩ የዛቻና የትምክህት መግለጫዎችም ቡድኑ ለጦርነት የነበረውን ከፍተኛ ፍላጎት የሚያሳዩ በቂ ማስረጃዎች እንደሆኑ አመልክቷል። ​በሌላ በኩል የፓርቲው መሪ አቶ ጌታቸው ረዳ ለትግራይ ሠራዊት አመራሮችና አባላት ባስተላለፉት መልዕክት፣ አመራሮቹ የተሻለ ወታደራዊ እውቀት አላቸው ተብሎ ስለሚታመን ለሕዝቡ የሚጠቅም የበሰለ ውሳኔ መወሰን እንደነበረባቸው አስገንዝበዋል። የትግራይን ሕዝብ አንድነት በማበላሸትና በውጭ አካላት ተመክቶ የሚደረግ ፎከራ ሕዝብን ወደ ከፋ አደጋ ከመክተት ውጪ የሚያመጣው ለውጥ የለም ያሉት አቶ ጌታቸው፣ በግዳጅ ወጣቱን በመመልመል "ወደ አራት ኪሎ እንመለሳለን" የሚለውን ቅዠት በአስቸኳይ ማቆም እንደሚገባ ገልጸዋል። ​አቶ ጌታቸው አክለውም፣ ለሠራዊቱ አባላት ሊያሳስባቸው የሚገባው በጣት የሚቆጠሩ ወንጀለኞች ህልውና ሳይሆን የትግራይ ሕዝብ ሰላምና ህልውና በመሆኑ በሕይወታቸውና በአካላቸው ላይ የሚጫወቱ አካላትን "ይበቃል" ሊሏቸው እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። የሕዝቡ የመኖርና አለመኖር ህልውና ጥያቄ በሰላማዊ መንገድ ብቻ ሊመለስ እንደሚችል በመጠቆም፣ በሃውልቲ የመሸገው ቡድን የዲፕሎማሲ በሮችን ዘግቶና ከውጭ አካላት በሚጠበቅ እርዳታ ተመክቶ ሁኔታዎችን ካበላሸ በኋላ "ዓለም ስማኝ" ማለቱ የአስተዋይነት ማነስን የሚያሳይ ነው ሲሉ ኮንነዋል።

“በብር ደመወዝ የሚከፈላቸው ሰዎች ገቢያቸው እጅግ ቀንሷል”፦ የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት የ #ኢትዮጵያ የምንዛሬ ሪፎርም ድህነትን አባብሷል አሉ የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ዴቪድ ማልፓ
“በብር ደመወዝ የሚከፈላቸው ሰዎች ገቢያቸው እጅግ ቀንሷል”፦ የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት የ #ኢትዮጵያ የምንዛሬ ሪፎርም ድህነትን አባብሷል አሉ የቀድሞው የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ዴቪድ ማልፓስ የኢትዮጵያ ብር መዳከም እና የውጭ ምንዛሬ ማሻሻያዎች ድህነትን በከፍተኛ ሁኔታ ማባባሳቸውን በመግለጽ፤ በብር ደመወዝ የሚከፈላቸው ሰዎች «ገቢያቸው እጅግ ቀንሷል» ሲሉ ተናግረዋል። በተቃራኒው ጥቂት ቡድኖች የውጭ ምንዛሬን እና የሀገር ውስጥ ብድርን በልዩ ሁኔታ ማግኘት በመቻላቸው ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ማልፓስ፤ ስታንሊ ፊሸር መታሰቢያ በተሰኘ መድረክ ላይ ባቀረቡት የፖሊሲ ጥናት ላይ ኢትዮጵያን በዋና ምሳሌነት የተጠቀሙ ሲሆን፥ ሀገሪቱ የእርሻ መሬት፣ የተፈጥሮ ሀብት፣ የውኃ፣ ተስማሚ የአየር ንብረት እና የሰው ኃይል አቅም ያላት በመሆኗ «ትልቅ የእድገት አቅም» ያላት ሀገር እንደሆነች ገልጸዋል። የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ውስጥ ወደ 200 የሚጠጉ ፕሮጀክቶችን በገንዘብ መደገፉንና 43ቱ አሁንም በሂደት ላይ እንደሚገኙ የጠቆሙት ማልፓስ፤ ሆኖም የሀገሪቱ የነፍስ ወከፍ ገቢ አሁንም 1,100 ዶላር አካባቢ በመሆኑ «ከዓለም ደሃ ሀገራት አንዷ» አድርጓታል ብለዋል።

ትርፍ አንጀት ምንድን ነው? በተለምዶ ትርፍ አንጀት እየተባለ የሚጠራው ችግር የሚከሰተው አፔንዲክስ (ትርፍ አንጀት) ሚባለው ትንሽ የአንጀት አካል ሲያብጥ ወይም ሲቆጣ ነው። ይህ ችግር በፍጥነት ካል
ትርፍ አንጀት ምንድን ነው? በተለምዶ ትርፍ አንጀት እየተባለ የሚጠራው ችግር  የሚከሰተው አፔንዲክስ (ትርፍ አንጀት) ሚባለው ትንሽ የአንጀት አካል ሲያብጥ ወይም ሲቆጣ ነው። ይህ ችግር በፍጥነት ካልታከሙ ሊፈነዳ እና አደገኛ ኢንፌክሽን ሊያስከትል ይችላል። የትርፍ አንጀት ቀዶ ህክምና ምንድን ነው? የትርፍ አንጀት ቀዶ ህክምና ትርፍ አንጀት ለማስወገድ የሚደረግ ቀዶ ጥገና ሲሆን ለትርፍ አንጀት ችግር በጣም የተለመደው ሕክምና ነው። ቀዶ ሕክምናው በክፍት (open) መንገድ ወይም በላፓሮስኮፒ ሊሰራ ይችላል። 🚨 የትርፍ አንጀት አደገኛ ምልክቶች፡ 👉 ከታች በቀኝ በኩል ባለው የሆድ ክፍል ላይ ድንገተኛ እና ከባድ ህመም ፣ 🔹ማቅለሽለሽ እና ማስታወክ ፣ 🔹ትኩሳት እና ብርድ ብርድ ማለት፣ 🔹 የምግብ ፍላጎት ማጣት እና 🔹 በእንቅስቃሴ የሚባባስ ህመም ሲኖር በፍጥነት ወደ ህክምና መሄድ ያስፈልጋል። ✨ የትርፍ አንጀት ቀዶ ህክምና ለምን ያስፈልጋል? ✅ ትርፍ አንጀት እንዳይፈነዳ እና ✅ ከባድ ኢንፌክሽን እንዳይፈጠር እንዲሁም ✅ በፍጥነት ለማገገም ይህ ቀዶ ህክምና ያስፈልጋል። ከቀዶ ጥገናው በኋላ ምን ማድረግ ያስፈልጋል? 🔹 በቀላሉ ሊፈጩ የሚችሉ ምግቦችን መመገብ፣ 🔹 ረጋ ያለ እንቅስቃሴ ማድረግ፣ 🔹 እረፍት ማድረግ እና 🔹 ውሃ በደንብ መጠጣት ቶሎ ለማገገም ይረዳል። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23

የጦርነት ውጤት አስከፊ ነው‼️ ዛሬ በሸረሪና የተፈፀመው እልቂት ዘግናኝ ነው። የህወሓት አርሚ 70 ታጣቂዎች በሸረሪና ግንባር ወደ ሁመራ ለመግባት ጥቃት የፈፀሙት ከታች የተዘረዘሩትን ሎጀስቲክ፣የሰው
+1
የጦርነት ውጤት አስከፊ ነው‼️ ዛሬ በሸረሪና የተፈፀመው እልቂት ዘግናኝ ነው። የህወሓት አርሚ 70 ታጣቂዎች በሸረሪና ግንባር ወደ ሁመራ ለመግባት ጥቃት የፈፀሙት ከታች የተዘረዘሩትን ሎጀስቲክ፣የሰው ሀይል እና መሳሪያ በመያዝ ነው። - ዙ-23       03 በፓትሮል የተጫነ - 107 ሮኬት   01 - ኮርኔት        02 - ሞርታር-120  01 - ሞርታር-82    01 - ሞርታር (ልዩ)  02 [በምርመራ ላይ ነው] - ድሽቃ          09 - የድሽቃ ሆ/እግር  01 - RPG            06 - ብሬን             54 - ስናይፐር          05 - ክላሽ            1347 - ሬድዮ            183 - ኦራል    02 - ፓትሮል  02 - ጄኔሬተር 02 ይህንን ጥቃት ተከትሎ በአካባቢው የሚገኘው መከላከያ ሰራዊት በወሰደው የአፀፋ ጥቃት:- - የተማረከ   01 ሻለቃ አዛዥ - የተማረከ  141 ታጣቂ እና የተለያየ የአመራር - የተገደለ እና የቆሰለ 1000+ መሆናቸውን የአዩዘሀበሻ ምንጮች አረጋግጠዋል። የተለያዩ ትጥቆች፣ የሕክምና ቁሳቁስ፣ ተተኳሾች፣ የደረት ትጥቆች፣ መድኃኒቶች፣ የመኪና መለዋወጫ፣ ነዳጅ ዘይትን ጨምሮ የጥይት ዴፖዎች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን ሸረሪና እና  አካባቢው ሙሉ ለሙሉ በመከላከያ ቁጥጥር ስር መሆኑ ተረጋግጧል። በዚሁ በቃ ይበለን።

አሳዛኝ ነው‼️ በሸረሪና አቅጣጫ የህወሓት አርሚ 70 በመከላከያ ሰራዊት ላይ ጥቃት መፈፀማቸውን ተከትሎ መከላከያ ሰራዊት በሜካናይዝድ ጦር የአፀፋ ምላሽ እየሰጠ ይገኛል። አንድ የአርሚ 70 አባል 'ኑ ቁስለኛ እናንሳ' ሲል ይሰማል። ጦርነት ይብቃ🕊🕊🕊

ተራዝሟል‼️ በመዲናዋ የመኖሪያ ቤት አከራይ ተከራይ ውል እድሳት ጊዜ ተራዘመ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመኖሪያ ቤት አከራይ ተከራይ ውል እድሳት እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ተራዝሟል
ተራዝሟል‼️ በመዲናዋ የመኖሪያ ቤት አከራይ ተከራይ ውል እድሳት ጊዜ ተራዘመ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመኖሪያ ቤት አከራይ ተከራይ ውል እድሳት እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ተራዝሟል፡፡ ከተማ አስተዳደሩ እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም እንዲካሄድ አስታውቆት የነበረውን የቤት ኪራይ ውል እድሳት ነው እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ያራዘመው፡፡ የከተማ አስተዳደሩ የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ እና በኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ ሕገ ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን በዘላቂነት ለመግታት የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11 ነጥብ 5 በመቶ እንዲሆን መወሰኑ ይታወቃል፡፡ ይህንን ተከትሎ በመላው ከተማዋ የሚገኙ የግል መኖሪያ ቤቶች የአከራይ ተከራይ የውል እድሳት ምዝገባ ጊዜ እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም የነበረው እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ መራዘሙን ቢሮው አስታውቋል። የውል እድሳት ጊዜው በሕብረተሰቡ ጥያቄ መሰረት የተራዘመ ሲሆን ÷  ይህም ነዋሪው ያለምንም መጨናነቅ እንዲዋዋል ያስችላል፡፡ ነዋሪው በሁሉም ክ/ከተማ ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት ፤ በየወረዳው በተዘጋጁ የውል ቦታዎች እና በሁሉም ክ/ከተማ አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አስፈላጊውን መረጃ በመያዝ አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችል መገለጹን የቢሮው መረጃ አመልክቷል፡፡

ሰበር ዜና በኢትዮ ሱዳን ድንበር መጠነ ሰፊ ውጊያ ተከፈተ፡፡ ውጊያ ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ የተቀሰቀሰ ሲሆን፤ ከበረኸት እስከ ሸረሪና የከባድ መሳሪያ ድምጽ በስፋት እንደሚሰማ ምንጮች አረጋግጠዋል
ሰበር ዜና በኢትዮ ሱዳን ድንበር መጠነ ሰፊ ውጊያ ተከፈተ፡፡ ውጊያ ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ የተቀሰቀሰ ሲሆን፤ ከበረኸት እስከ ሸረሪና የከባድ መሳሪያ ድምጽ በስፋት እንደሚሰማ ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡

በምዕራብ ትግራይ "አዲስ ግጭት መቀሰቀሱን" የትግራይ ባለሥልጣናት ገለጹ! የትግራይ ባለሥልጣናት የኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት በምዕራብ ትግራይ “አዲስ ወታደራዊ ጥቃት ከፍቷል” ሲሉ ከሰሱ። ግጭቱ ቅዳ
በምዕራብ ትግራይ "አዲስ ግጭት መቀሰቀሱን" የትግራይ ባለሥልጣናት ገለጹ! የትግራይ ባለሥልጣናት የኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት በምዕራብ ትግራይ “አዲስ ወታደራዊ ጥቃት ከፍቷል” ሲሉ ከሰሱ። ግጭቱ ቅዳሜ ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. ማለዳ በምዕራብ ትግራይ ዞን በሸረሪና አቅጣጫ መጀመሩን ገልጸዋል። ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) የሚመራው የክልሉ አስተዳደር ዛሬ á‰Łá‹ˆáŒŁá‹ መግለጫ፥ á‹¨áŒá‹°áˆŤáˆ መንግሥት በምዕራብ ትግራይ ዞን «ግልጽ ጦርነት ከፍቷል» ሲል በመክሰስ ከክልሉ ጋር የቆየውን ፍጥጫ አባብሶታል ብሏል። «በትግራይ ሕዝብ ላይ ሲያካሂድ የቆየውን አጠቃላይ እገዳ እና ከበባ፥ እንዲሁም በድሮን እና በውክልና የትጥቅ ኃይሎች የሚፈጸሙ ጥቃቶችን በማባባስ የብልፅግናው ሥርዓት ግልጽ ጦርነት ከፍቷል» ሲል መግለጫው ገልጿል። በትግራይ ባለሥልጣናት የቀረበው ይህ ክስ በፌደራል መንግሥቱ እና በክልሉ አስተዳደር መካከል ለወራት ሲካሄድ የቆየውን የፖለቲካ እና የወታደራዊ ውጥረት ተከተሎ የመጣ ነው። መግለጫው እ.ኤ.አ. በ2022 የፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት ከተፈረመ ወዲህ የፌደራል መንግሥት «የተለያዩ ሴራዎችን፣ እገዳዎችን፣ ከበባዎችን እና ወታደራዊ ዝግጅቶችን» ሲያካሂድ ቆይቷል ሲል የከሰሰ ቢሆንም ማስረጃ ግን አላቀረበም።

በአሜሪካ ጥገኝነት ጠያቂዎች ያለ ቃለ-መጠይቅ ወደ ፍርድ ቤት የሚላኩበት መመሪያ ጸደቀ። የትራምፕ አስተዳደር በሀገሪቱ ጥገኝነት የጠየቁ ስደተኞችን የሚመለከት አዲስ መመሪያ አውጥቷል። ይህን ተከትሎ በርካታ ጥገኝነት ጠያቂዎች ጉዳያቸው ሳይሰማ ቀጥታ ሊባረሩ የሚችሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል። አዲሱ አሰራር ከ1.4 ሚሊዮን በላይ የተከማቹ የጥገኝነት ማመልከቻዎችን ለማቃለል የታሰበ ነው ተብሏል። ቀደም ሲል የነበረው አሰራር አመልካቾች መጀመሪያ ጉዳያቸውን ለኢሚግሬሽን ኦፊሰር አቅርበው ጥያቄያቸው ውድቅ ከተደረገ ብቻ ወደ ፍርድ ቤት እንዲመሩ የሚያደርግ ነበር። በአዲሱ መመሪያ በርካታ የጥገኝነት አመልካቾች ከኢሚግሬሽን ኦፊሰሮች ጋር የሚደረገውን የመጀመሪያ ደረጃ ቃለ-መጠይቅ ሳያደርጉ ጉዳያቸው በቀጥታ ወደ ፍርድ ቤት ሊመራ ይችላል። 444,724 ያህል መዝገቦችን ይነካል የተባለው ይህ ውሳኔ የሕግ ባለሙያዎችና የኢሚግሬሽን ተከራካሪዎች አሰራሩ የስደተኞችን የመሰማትና የፍትህ የማግኘት መብት የሚጎዳና ውሳኔዎችን በማፋጠን ሰዎችን በፍጥነት ለማባረር ያለመ ነው በማለት ተችተውታል። በሌላ በኩል ፥ የአሜሪካ መንግሥት በሀገሪቱ በሚማሩ የውጭ ሀገር ተማሪዎች ላይ እስከ 100,000 ዶላር የሚደርስ አዲስ ክፍያ ለመጣል ማቀዱ ተሰምቷል። የታቀደው እርምጃ በተለይ ትምህርታቸውን አጠናቀው በአሜሪካ ለመቆየት ለሚፈልጉ ዓለም አቀፍ ተማሪዎች ፈተና ሊሆን እንደሚችል ተገልጿል። መንግሥት እርምጃው የቪዛ አጠቃቀምን ለማጥበቅና የሀገር ውስጥ የሥራ ገበያን ለመጠበቅ ያለመ መሆኑን ሲገልጽ፣ ተቃዋሚዎች ግን የውጭ ተማሪዎች ለአሜሪካ የትምህርትና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላቸውን አስተዋፅኦ ሊጎዳ ይችላል በማለት ስጋታቸውን ገልጸዋል። የትራምፕ አስተዳደር ከስደተኞች ጋር በተያያዝ እጅግ ጠንካራ እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑ ተደጋግሞ መገለጹ ይታወሳል።

አሊኮ ዳንጎቴ ከሃብታቸው ሲሶውን ለበጎ አድራጎት ድርጅት ሊያውሉት ነው። የአፍሪካ ቁጥር አንድ ባለሀብት የሆኑት ናይጄሪያዊው ቢሊየነር አሊኮ ዳንጎቴ፣ ከሀብታቸው ውስጥ አንድ ሦስተኛውን (35 ቢሊዮን
አሊኮ ዳንጎቴ ከሃብታቸው ሲሶውን ለበጎ አድራጎት ድርጅት ሊያውሉት ነው። የአፍሪካ ቁጥር አንድ ባለሀብት የሆኑት ናይጄሪያዊው ቢሊየነር አሊኮ ዳንጎቴ፣ ከሀብታቸው ውስጥ አንድ ሦስተኛውን (35 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ) ኃብታቸውን ለበጎ አድራጎት ሥራዎች ሊለግሱ መሆኑ ተገልጿል። ልጃቸው ፋጢማ ዳንጎቴ በቅርቡ ከብሉምበርግ ጋር በነበራት ቃለ-መጠይቅ ድጋፉን በስማቸው በተቋቋመው ፋውንዴሽን በኩል ለበጎ አድራጎት ሥራዎች እንደሚያውሉት ይፋ አድርጋለች።

አሐዱ ራዲዮ እና አርትስ ቲቪ ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ለሁለቱ ሚዲያዎች የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱን አስታውቋል። አሐዱ ኤፍ ኤም 94.3 እና አርትስ ቴሌቪዥን
+1
አሐዱ ራዲዮ እና አርትስ ቲቪ ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ለሁለቱ ሚዲያዎች የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱን አስታውቋል። አሐዱ ኤፍ ኤም 94.3 እና አርትስ ቴሌቪዥን የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው፣ "ውል የገቡበትን የይዘት ግዴታዎች በመተላለፍ፣ ለተከታታይ ጊዜ ያልተረጋገጠ፣ ሚዛናዊ ያልሆነ እንዲሁም የሕዝብን ጥቅም የሚጎዳ መረጃ በማሰራጨታቸው" ነው ተብሏል። ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ከሬድዮ እና ከቴሌቪዥን ጣቢያዎቹ ኃላፊዎች ጋር "ተደጋጋሚ የህግና የሙያ ጥሰቶች" መፈጸማቸውን በተመለከተ፣ ወይይት ቢደረግም "ጉልህ ለውጥ ሳይታይ በመቅረቱ" ማስጠንቀቂያ መስጠቱን አስታውቀዋል፡፡

ጥቆማ‼️ ምንም ውሸት አልተቀላቀለበትም!! በትኩሱ ስለወቅታዊ ጉዳይ ፈጣን እና ታማኝ መረጃ ለማግኘት ይሄንን ቻናል ዝምብላቹህ ተቀላቀሉ!! 👇👇👇 https://t.me/seledadotio https
ጥቆማ‼️ ምንም ውሸት አልተቀላቀለበትም!! በትኩሱ ስለወቅታዊ ጉዳይ ፈጣን እና ታማኝ መረጃ ለማግኘት ይሄንን  ቻናል ዝምብላቹህ ተቀላቀሉ!! 👇👇👇 https://t.me/seledadotio https://t.me/seledadotio

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከነገ ጀምሮ ከጎንደር ሁመራ ቋሚ በረራ ይጀምራል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከነገ ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ከጎንደር ወደ ሁመራ ቋሚ የበረራ አገልግሎት ይጀመራል አ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከነገ ጀምሮ ከጎንደር ሁመራ ቋሚ በረራ ይጀምራል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከነገ ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ከጎንደር ወደ ሁመራ ቋሚ የበረራ አገልግሎት ይጀመራል አለ፡፡ በዚህም መሰረት ዘወትር ቅዳሜ ከጎንደር ወደ ሁመራ እንዲሁም ዘወትር ሰኞ ከሁመራ ወደ ጎንደር የበረራ አገልግሎት ይሰጣል። የሀገር ውስጥ በረራ መዳረሻዎችን በማስፋት ሕዝብን ለማገልገል እንደሚራ የገለጸው አየር መንገዱ ይህ የበረራ አገልግሎት መጀመር ማኅበራዊ ግንኙነትን ከፍ ያደርጋል ብሏል።

የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ!! ​በኦሮሚያ ክልል የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ሰኔ 08 - 09/2018 ዓ.ም ተሰጥቶ የነበረ ሲሆን፣ ዛሬ የተማሪዎች ውጤ
የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ!! ​በኦሮሚያ ክልል የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ሰኔ 08 - 09/2018 ዓ.ም ተሰጥቶ የነበረ ሲሆን፣ ዛሬ የተማሪዎች ውጤት ይፋ ሆኗል። ​👉 የማለፊያ ነጥብ 50% እና ከዚያ በላይ እንዲሆን ተወስኗል። ​👉 ፈተናውን ከተቀመጡ 517,209 ተማሪዎች ውስጥ የማለፊያ ነጥብ (50% እና ከዚያ በላይ) በማስመዝገብ ወደ ሚቀጥለው ክፍል የተሸጋገሩት 464,839 (89.9%) ተማሪዎች መሆናቸው ታውቋል። ​ከተፈተኑት ተማሪዎች መካከል፡ 📍 ወንድ 267,307 ውስጥ 91.2% እና 📍 ሴት 249,902 ውስጥ 88.4% አልፈዋል። ​በዚሁ መሠረት ውጤት ለማየት ከዚህ በታች የቀረበውን ሊንክ በመክፈት፤ የመፈተኛ ቁጥርዎን (Registration Number) ማስገባት፤ ቀጥሎም የመጀመሪያ ስምዎን በማስገባት ውጤትዎን መመልከት ትችላላችሁ።👇 ​ሊንክ፦ https://oromia6.ministry.et

በግል ትምህርት ቤቶች የክፍያ ጭማሪና የምዝገባ አሰራር ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ ነው፡- የአዲስ አበባ ትምህርትና ሥልጠና ቁጥጥር ባለስልጣን በ2019 ዓመተ ምህረት የትምህርት ዘመን በግል ትምህ
በግል ትምህርት ቤቶች የክፍያ ጭማሪና የምዝገባ አሰራር ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ ነው፡- የአዲስ አበባ ትምህርትና ሥልጠና ቁጥጥር ባለስልጣን በ2019 ዓመተ ምህረት የትምህርት ዘመን በግል ትምህርት ቤቶች በሚካሄደው የተማሪዎች ምዝገባ፣ የክፍያ ጭማሪና የግብዓት ጥያቄ ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እየተካሄደ መሆኑን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አስታወቀ:: ባለፉት ዓመታት የግል ትምህርት ቤቶች በወርሃዊ ክፍያ፣ በምዝገባ፣ በዩኒፎርም እንዲሁም በዓይነት በሚጠይቋቸው እንደ ሳሙና እና ሶፍት ባሉ ቁሳቁሶች ምክንያት በወላጆች ዘንድ ሰፊ ቅሬታ ሲነሳ መቆየቱ ይታወሳል፡፡

ትራምፕ በኢራን ላይ ጥቃት ይቀጥሉ ‼ - የአሜሪካ ሴኔት የአሜሪካ የህግ መወሰኛ ምክር ቤት (የላይኛው ምክር ቤት፣ ሴኔት)ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ የመውሰድ ስልጣናቸው
ትራምፕ በኢራን ላይ ጥቃት ይቀጥሉ ‼ - የአሜሪካ ሴኔት የአሜሪካ የህግ መወሰኛ ምክር ቤት (የላይኛው ምክር ቤት፣ ሴኔት)ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ የመውሰድ ስልጣናቸውን ለማገድ የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ በ 49 ለ 50 በሆነ በጠበበ የድምፅ ልዩነት  ውድቅ አደረገ። ​በሴናተር ኪርስተን ጊሊብራንድ የቀረበው ይህ ጥያቄ፣ ኮንግረሱ የጦርነት አዋጅ ሳያወጣ የአሜሪካ ጦር በኢራን ውስጥ የሚያደርገውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ እንዲያቆም የሚጠይቅ ነበር። ​ውሳኔው ውድቅ መደረጉን ተከተሎ፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በቀጣናው ላይ ያላቸው ወታደራዊ እርምጃ የመውሰድ ሙሉ ስልጣን እንደተጠበቀ ይቆያል። ​በድምፅ አሰጣጡ ላይ ሦስት የሪፐብሊካን ዓባላት ሃሳቡን ሲደግፉ፣ አንድ የዲሞክራቲክ አባል ደግሞ ተቃውሞ ድምፅ ሰጥቷል። ‎

ትራምፕ በኢራን ላይ ጥቃት ይቀጥሉ ‼ - የአሜሪካ ሴኔት የአሜሪካ የህግ መወሰኛ ምክር ቤት (የላይኛው ምክር ቤት፣ ሴኔት)ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ የመውሰድ ስልጣናቸው
ትራምፕ በኢራን ላይ ጥቃት ይቀጥሉ ‼ - የአሜሪካ ሴኔት የአሜሪካ የህግ መወሰኛ ምክር ቤት (የላይኛው ምክር ቤት፣ ሴኔት)ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ የመውሰድ ስልጣናቸውን ለማገድ የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ በ 49 ለ 50 በሆነ በጠበበ የድምፅ ልዩነት  ውድቅ አደረገ። ​በሴናተር ኪርስተን ጊሊብራንድ የቀረበው ይህ ጥያቄ፣ ኮንግረሱ የጦርነት አዋጅ ሳያወጣ የአሜሪካ ጦር በኢራን ውስጥ የሚያደርገውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ እንዲያቆም የሚጠይቅ ነበር። ​ውሳኔው ውድቅ መደረጉን ተከተሎ፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በቀጣናው ላይ ያላቸው ወታደራዊ እርምጃ የመውሰድ ሙሉ ስልጣን እንደተጠበቀ ይቆያል። ​በድምፅ አሰጣጡ ላይ ሦስት የሪፐብሊካን ዓባላት ሃሳቡን ሲደግፉ፣ አንድ የዲሞክራቲክ አባል ደግሞ ተቃውሞ ድምፅ ሰጥቷል። ‎ @Addis_News @Addis_News

በመንግሥት በተገነቡ መንገዶች ላይ የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ግብር ሊከፍሉ ነዉ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ የሆኑት አቶ ዋሲሁን በላይ ይህ ግብር በተሽከርካሪ ባለቤቶች ላይ የሚጣል ሲሆን፥ተሽከርካሪዎቹ በ
በመንግሥት በተገነቡ መንገዶች ላይ የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ግብር ሊከፍሉ ነዉ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ የሆኑት አቶ ዋሲሁን በላይ ይህ ግብር በተሽከርካሪ ባለቤቶች ላይ የሚጣል ሲሆን፥ተሽከርካሪዎቹ በመንግስት በተገነቡ መንገዶች ላይ ስለሚንቀሳቀሱ በየዓመቱ የሚከፈል ይሆናል ብለዋል። ይህም ከመደበኛው የተሽከርካሪ ዓመታዊ ምርመራ ወይም ቦሎ ጋር ተያይዞ ሊመጣ የሚችል ግዴታ ነው። የምጣኔ ሀብት ባለሙያዉ እንደገለፁት፥ግብር አጣጣሉም እንደ ተሽከርካሪዎቹ ዓይነትና እንደሚያመነጩት ጭስ (ካርቦን) ሊለያይ እንደሚችል ተናግረዋል። ይህ ማለት ብዙ ጭስ የሚለቁ አሮጌ ተሽከርካሪዎች ከፍተኛ ግብር እንዲከፍሉ አዳዲሶች ደግሞ ዝቅተኛ እንዲከፍሉ ሊደረግ ይችላል ተብሏል። ይህ አሰራር በሌሎች አገራት ለምሳሌ በኬንያ፣ በሩዋንዳና በአውሮፓ አገራት የተለመደ ሲሆን፥መንግስት ለመንገድ ጥገና የሚውል ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኝ ያስችለዋል። ግብሩ በከተሞችና በክልሎች የሚሰበሰብ በመሆኑ የአካባቢ መስተዳድሮች የራሳቸውን የልማት በጀት እንዲያሳድጉ ትልቅ ዕድል ስለሚፈጥርላቸው በፌዴራል መንግስት ላይ ያለውን የገንዘብ ጫና ይቀንሳል። ይህ የታክስ ፕሮፖዛል በሚኒስትሮች ምክር ቤት ተዘጋጅቶ  ለምክር ቤቱ ለማቅረብ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡ አቶ ዋሲሁን አክለዉም ዝርዝር ደንቦችና መመሪያዎች ወጥተውለት ወደ ተግባር እንደሚገባና የኢኮኖሚው የገቢ ምንጭ እንደሚሆን እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። ከዚህ ግብር የሚገኘው ገቢ ከአጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት 0.2 በመቶ ድርሻ ይኖረዋል ተብሎ ይገመታል።

ግብጾች የአባይን ውሃ ስለሚጠቀሙ ለኢትዮጵያ ሊከፍሉን ይገባል ዶክተር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖ
ግብጾች የአባይን ውሃ ስለሚጠቀሙ ለኢትዮጵያ ሊከፍሉን ይገባል ዶክተር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ባደረጉት ልዩ ቆይታ፣ ግብፅ የአባይን ውኃ በነፃ እየተጠቀመች አገሯን እያለማች በመሆኗ ለኢትዮጵያ ተገቢውን ክፍያ ልትፈጽም እንደሚገባ ገለጹ። ሚኒስትሩ በቆይታቸው እንደጠቆሙት፤ ኢትዮጵያ የጎርፍ አደጋ በታችኞቹ የተፋሰሱ አገራት—በተለይም በግብፅ ላይ እንዳይደርስ ከፍተኛ የክትትልና የእንክብካቤ ሥራ እያከናወነች ትገኛለች። ሆኖም አገራቱ የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ሀብት ያለምንም ክፍያ በመጠቀም አገራቸውን እያለሙ በመሆናቸው፣ ለሚጠቀሙበት ውኃ ለኢትዮጵያ ክፍያ ሊፈጽሙ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።