es
Feedback
Ethio - ዜና 🇪🇹

Ethio - ዜና 🇪🇹

Ir al canal en Telegram

የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot

Mostrar mĂĄs

📈 Análisis del canal de Telegram Ethio - ዜና 🇪🇹

El canal Ethio - ዜና 🇪🇹 (@ethio_zena23) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 106 363 suscriptores, ocupando la posición 72 en la categoría Fotos y el puesto 272 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 106 363 suscriptores.

SegĂşn los Ăşltimos datos del 10 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los Ăşltimos 30 dĂ­as la variaciĂłn de miembros fue de -2 923, y en las Ăşltimas 24 horas de -138, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificaciĂłn: No verificado
  • Tasa de interacciĂłn (ER): El promedio de interacciĂłn de la audiencia es 3.45%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 2.36% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicaciĂłn recibe en promedio 3 674 visualizaciones. En el primer dĂ­a suele acumular 2 506 visualizaciones.
  • Reacciones e interacciĂłn: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicaciĂłn es 30.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot”

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (Ăşltimos datos recibidos el 11 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analĂ­tica demuestra que la audiencia interactĂşa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categorĂ­a Fotos.

106 363
Suscriptores
-13824 horas
-7247 dĂ­as
-2 92330 dĂ­as
Archivo de publicaciones
#እንዲያውቁት‼️ የኪራይ ውል ማሻሻያው ለ2 ዓመታት ጸንቶ ይቆያል። 11.5 በመቶ ሆኖ የጸደቀዉ በአዲስ አበባ የ2019 በጀት ዓመት የቤት #ኪራይ ዓመታዊ የጭማሪ ጣሪያ ለ2 ዓመታት የሚቆይ ሲሆን ከ
#እንዲያውቁት‼️ የኪራይ ውል ማሻሻያው ለ2 ዓመታት ጸንቶ ይቆያል። 11.5 በመቶ ሆኖ የጸደቀዉ በአዲስ አበባ የ2019 በጀት ዓመት የቤት #ኪራይ ዓመታዊ የጭማሪ ጣሪያ ለ2 ዓመታት የሚቆይ ሲሆን ከዚህ ተመን በላይ መጨመር በጥብቅ የተከለከለ ነው ሲል የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታውቋል። 📣ከህጋዊ አሰራር ውጪ የሚደረጉ "የመንደር ውሎች" የተከለከሉ ሲሆን ውል በማያድሱና ህግ በሚተላለፉ አካላት ላይ ቅጣት ይጣላል። የውል እድሳት ጊዜያቸው አልፎ አከራይም ተከራይም አብረው ኖረው እድሳት ሳይፈጽሙ የተገኙ፦ 💸እስከ 2 ወር ከቆዩ የ1 ወር የቤት ኪራይ፣ 💸3 ወር እና ከዚያ በላይ የቆዩ የ2 ወር የቤት ኪራይ ቅጣት ይከፍላሉ። 💸አዲስ ተከራይ አስገብተው ውል ያላደሱ እና ያላስመዘገቡ የ1 ወር የቤት ኪራይ ይቀጣሉ። 💸በጥቆማ ወይም በክትትል ውል ያላደሱ ወይም ያላስመዘገቡ መሆናቸው ከተረጋገጠ ደግሞ ከ1 እስከ 3 ወር የሚደርስ የኪራይ መጠን ቅጣት እንደሚጣልባቸው ቢሮው አሳውቋል። ‎

በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ጭልጋ ወረዳ ሰራቆ ቀበሌ በግ ሰር'ቆ ሲያ'ርድ በህብረተሰቡና በፀጥታ ሀይሎች ትብብር በቁጥጥር ስር የዋለው ሌባ መቀጣጫ ሆነ። ሰ'ርቆ በመግፈፍ ላይ የነበረውን በግ ተሸክ
+1
በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ጭልጋ ወረዳ ሰራቆ ቀበሌ በግ ሰር'ቆ ሲያ'ርድ በህብረተሰቡና በፀጥታ ሀይሎች ትብብር በቁጥጥር ስር የዋለው ሌባ መቀጣጫ ሆነ። ሰ'ርቆ በመግፈፍ ላይ የነበረውን በግ ተሸክ'ሞ ከተማውን እንዲዞር ተደርጓል። @Seledadotio @Seledadotio

ስፔን ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቅላለች:: ስፔን 2 - 1 ቤልጅየም ግማሽ ፍፃሜ ፈረንሳይ ከ ስፔን! @Addis_News @Addis_News
ስፔን ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቅላለች:: ስፔን 2 - 1 ቤልጅየም ግማሽ ፍፃሜ ፈረንሳይ ከ ስፔን! @Addis_News @Addis_News

ኢትዮጵያ ለኢቦላ ወረርሽኝ የመጋለጥ እድሏ ከፍተኛ ነው ተባለ ዓለማቀፉ የፍልሠት ድርጅት ኢትዮጵያ ለበሽታው ከመጋለጥ አንጻር በከፍተኛ ደረጃ "ቅድሚያ" ከሚሠጣቸው አገራት መካከል አንዷ መኾኗን ሰሞኑ
ኢትዮጵያ ለኢቦላ ወረርሽኝ የመጋለጥ እድሏ ከፍተኛ ነው ተባለ ዓለማቀፉ የፍልሠት ድርጅት ኢትዮጵያ ለበሽታው ከመጋለጥ አንጻር በከፍተኛ ደረጃ "ቅድሚያ" ከሚሠጣቸው አገራት መካከል አንዷ መኾኗን ሰሞኑን ባወጣው ሪፖርት ላይ ገልጿል። ድርጅቱ ኢትዮጵያ ለበሽታው በከፍተኛ ደረጃ ተጋላጭ መኾኗን የገለጠው፣ ዓለማቀፍ ተጓዦች በብዛት የሚያልፉባት፣ ድንበር ተሻጋሪ የንግድና የመጓጓዣ ኮሪደሮች ያሉባትና በሽታው ከተከሠተባቸው አካባቢዎች ጋር ያላት ድንበር ክፍተት ያለበት መኾኑን በመጥቀስ ነው። በድርጅቱ ሪፖርት መሠረት፣ ቦሌ ዓለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ የድሬዳዋ፣ መቀሌ እና የባሕርዳር አውሮፕላን ማረፊያዎች፤ የሞያሌ፣ መተማ፣ ጋላፊ፣ ደዋሌ፣ ፓጋክ እና ኩርሙክ የድንበር መግቢያና መውጫዎች እንዲሁም የድሬዳዋ የባቡር ጣቢያ ቅድሚያ ትኩረት የሚሠጣቸው ቦታዎች ናቸው። ድርጅቱ፣ ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ ቀንድ፣ ምሥራቅና ደቡባዊ አፍሪካ ለ12 አገሮች በሽታውን ለመከላከልና ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የ55 ነጥብ 9 ሚሊዮን ዶላር እቅድ የነደፈ ሲኾን፣ ከድጋፉ ውስጥ 4 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላሩ የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓትና በድንበርናና ኮሪደሮች አካባቢ የጤና ተቋማትን ለማጠናከር እንደሚውል ገልጧል።

እንደገና ፈተና አለ‼️ ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 2015 ዓ.ም በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በሁለተኛ እና በሦስተኛ ዲግሪ የተመረቃችሁ ወይም የመውጫ ፈተና ሳትፈተኑ የዲግሪ ባለቤት የሆናችሁ በሙሉ እንደገና
+3
እንደገና ፈተና አለ‼️ ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 2015 ዓ.ም በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በሁለተኛ እና በሦስተኛ ዲግሪ የተመረቃችሁ ወይም የመውጫ ፈተና ሳትፈተኑ የዲግሪ ባለቤት የሆናችሁ በሙሉ እንደገና የትምህርት ማስረጃችሁን ለማረጋገጥ ሲባል ሊፈተኑ ነው ተብሏል። በጉዳዩ ላይ አስተያየት ለመስጠት በኢፌዴሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የፌስቡክ ገጽ ላይ በተለቀቀው ሊንክ እየገባችሁ መሙላት ትችላላችሁ። @Seledadotio @Seledadotio

የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ በመምሰል የማታለል (በተለምዶ ሿሿ) ተብሎ የሚጠራውን ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ 9 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ። ተጠርጣሪዎቹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት ሰኔ 28
የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ በመምሰል የማታለል (በተለምዶ ሿሿ) ተብሎ የሚጠራውን ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ 9 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ። ተጠርጣሪዎቹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ/ም ከጥዋቱ 1:40 በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ሪቼ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ነው። የግል ተበዳይ ከአጎና ወደ እስታዲየም ለመሄድ በማሰብ ኮድ 3-83620 ኦሮ ነጭ ሚኒባስ ተሽከርካሪ በማስቆም ትገባለች። ተጠርጣሪዎችም የግለሰቧን ወደ ተሽከርካሪው መግባት ተከትለው በማዋከብ እና ትኩረቷን በማሳጣት ይዛው ከነበረው ቦርሳ ውስጥ 32 ሺ ብር ግምት ያለው ሳምሰንግ ስልክ ሰርቀው ጥለዋት ይሄዳሉ። ይህን የተመለከቱ የትራፊክ ፖሊሶች ተሽከርካሪውን በማስቆም እና ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር የማዋል ስራ ሰርተዋል። ተጠርጣሪዎቹ ከተያዙ በኋላ በተሽከርካሪው ውስጥ በተደረገ ፍተሻ 7 ስልኮች መገኘታቸውን የቂርቆስ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ አስታውቋል። ከተጠርጣሪዎቹ መካከል ነፍሰ ጡር መኖሯ የተገለጸ ሲሆን የቀን ውሎ አበል በመክፈል እና ተሽከርካሪ በመከራየት ወንጀሉን የሚፈፅሙ ግለሰቦች እንዳሉ ህብረተሰቡ ተገንዝቦ ትራንስፖርት ሲጠቀም ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባም የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል። Addis Ababa police @Seledadotio @Seledadotio

ለእናቱ የገባውን ቃል ለመጠበቅ አስክሬን ቤት አስቀምጦ ለተፈተነው ታዳጊ ካሊድ ቃሲም የመኖሪያ ቤት ሊገነባለት ነው:: ከሦስት ሳምንታት በፊት እናቱ ባረፉበት ዕለት የገባውን ቃል ለማክበር ሲል አስክ
+2
ለእናቱ የገባውን ቃል ለመጠበቅ አስክሬን ቤት አስቀምጦ ለተፈተነው ታዳጊ ካሊድ ቃሲም የመኖሪያ ቤት ሊገነባለት ነው:: ከሦስት ሳምንታት በፊት እናቱ ባረፉበት ዕለት የገባውን ቃል ለማክበር ሲል አስክሬን ቤት ውስጥ ትቶ የስምንተኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተናውን በመፈተን መላውን የሀገሪቱን ሕዝብ በከፍተኛ ሐዘን ያስለቀሰውና ያስደመመው ታዳጊ ካሊድ ቃሲም፣ አዲስ የመኖሪያ ቤት ሊገነባለት መሆኑ ተሰማ። በሸገር ከተማ አስተዳደር ኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ ከሁለት ታናናሽ ወንድሞቹ ጋር የሚኖረው ይህ የ14 ዓመት ታዳጊ፣ በወቅቱ እናቱ በጽኑ ታመው በነበሩበት ወቅት “እኔ አንድ ነገር ብሆን እንኳ ለዓመታት የለፋህበትን ፈተና እንዳታቋርጥ” በማለት ያስገቡትን ጥብቅ ቃል ለመጠበቅ የጠዋት ፈተናውን ተፈትኖ፣ ከሰዓት ደግሞ እናቱን አልቅሶና ቀብሮ በመመለስ የከሰዓት ፈተናውን ማጠናቀቁና “ቃልሽን አላጠፍኩም እማ!” ማለቱ ይታወሳል። ዛሬ በተሰማው አዲስና ተስፋ ሰጪ መረጃ መሠረት፣ ለታዳጊውና ለታናናሽ ወንድሞቹ ቋሚ የቤት መፍትሔ ለመስጠት የሸገር ከተማ የኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ለቤት ግንባታ የሚሆን መሬት በይፋ አዘጋጅቶ አስረክቧል። ከዚህ ጋር ተያይዞ የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ የመኖሪያ ቤቱን ሙሉ በሙሉ ገንብቶ ለታዳጊዎቹ ለማስረከብ ቃል ገብቷል። ወላጅ አባቱ ከእነርሱ ርቆ በጅጅጋ ከተማ ሌላ ትዳር መሥርቶ በመኖሩ ምክንያት እናታቸውን አጥተው ብቻቸውን ለቀሩት ለእነዚህ ወንድማማቾች የተደረገው ይህ የመሬትና የቤት ግንባታ ድጋፍ፣ የታዳጊውን ታማኝነትና ብርታት ያከበረ እንዲሁም ማኅበራዊ አጋርነትን በተግባር ያሳየ መሆኑ ተገልጿል። @Seledadotio @Seledadotio

ሕወኃት ኤርትራ እና ሱዳንን ያካተተ ጥምረት ፈጥሯል በማለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ያቀረቡበትን ክስ ውድቅ አደረገ! «እኛ በራሳችን ኃይል ነው የምንተማመነው» ብሏል ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (
ሕወኃት ኤርትራ እና ሱዳንን ያካተተ ጥምረት ፈጥሯል በማለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ያቀረቡበትን ክስ ውድቅ አደረገ! «እኛ በራሳችን ኃይል ነው የምንተማመነው» ብሏል ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕወኃት)ከኤርትራ እና ከሱዳን ጋር በጋራ እየሠራ ነው በማለትጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሰነዘሩበትን ክስ ውድቅ አደረገ። ቡድኑ ከየትኛውም የውጭ አካል ወታደራዊ ድጋፍ እንደማይፈልግ እና «በራሱ ኃይል እንደሚተማመን» ገልጿል። ይህ ምላሽ የተሰጠው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ባለፈው ማክሰኞ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ ላይ፥ ሱዳን፣ ሕወኃት እና ኤርትራ በጋራ እየሠሩ መሆኑን በመጥቀስ፤ ይህንን ሁኔታ እ.ኤ.አ. በ1991 የደርግ ሥርዓት እንዲወድቅ ካደረገው ጥምረት ጋር በማመሳሰል ከሰጡት አስተያየት በኋላ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህ የተባለው ጥምረት በኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ላይ የሚያመጣው አደጋ የለም ቢሉም፥ ስማቸውን ያልጠቀሷቸው የውጭ አካላት ከጀርባ ሆነው እየመሩት መሆኑን ጠቁመዋል። ለእነዚህ ክሶች ምላሽ የሰጡት የሕወኃት ቃል አቀባይ ሚካኤል አስገዶም፤ ድርጅታቸው አብረውት ተሰልፈው እንዲዋጉለት የውጭ አካላትን በፍጹም ጋብዞ አያውቅም ብለዋል። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23

በሱዳን የኩርሙክ ግንባር የቀጠለው ጦርነት በርካታ ተዋጊዎች ያለቁበት መሆኑ ተሰማ፤ የአርሚ 70 ተዋጊዎችም ከባድ ጉዳት ድርሶባቸዋል‼️ አዲስ አበባ/ካርቱም | ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም. በሱዳን
በሱዳን የኩርሙክ ግንባር የቀጠለው ጦርነት በርካታ ተዋጊዎች ያለቁበት መሆኑ ተሰማ፤ የአርሚ 70 ተዋጊዎችም ከባድ ጉዳት ድርሶባቸዋል‼️ አዲስ አበባ/ካርቱም | ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም. በሱዳን የብሉ ናይል ክልል በሚገኘው ስትራቴጂካዊ የኩርሙክ አካባቢ ያለው የጦርነት ሁኔታ የኢትዮጵያን ትኩረት እየሳበ ነው። ኩርሙክ በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ የምትገኝ ቁልፍ ስፍራ በመሆኗ፣ መንግሥት ጦርነቱን በንቃት እየተከታተለ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። በሱዳን የቀጠለው ግጭት በድንበር ደኅንነት፣ በሕዝብ እንቅስቃሴ፣ በስደተኞች ፍሰት እና በታጣቂ ቡድኖች እንቅስቃሴ ላይ ሊያሳድር የሚችለው ተፅዕኖ በኢትዮጵያ በኩል ክትትል የሚሻው ጉዳይ ከመሆኑ ጎን ለጎን፣ በጦርነቱ በተሰለፉ የ”አርሚ 70″ አባላት ላይ ጉዳት መድረሱም ተሰምቷል። ከሕወሓት የጦር ክንፍ ጋር ቅርበት ካለው ከፍተኛ ባለሥልጣን የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ አርሚ ሰባ ኩርሙክን ለመያዝ የጄነራል አልቡርሃን ጦር በሚያደርገው ውጊያ ላይ በግንባር ቀደምትነት ተሰልፏል። በዚሁ መረጃ መሠረት የአርሚ 70 አባላት በጦርነቱ ጉዳት ደርሶባቸዋል። መረጃውን ያጋሩ ምንጮች በውጊያው ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቀ አባላት መገደላቸውንና መቁሰላቸውን አመልክተዋል። የቆሰሉ የአርሚ 70 አባላት በመኪና ወደ ካርቱም ተወስደዋል። ከቆሰሉት መካከል አንዳንዶቹ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው እንዳሉም ተናግረዋል።

ከ738 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ (ዶ/ር) እንዳስታወቁት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 725.25 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ
ከ738 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ (ዶ/ር) እንዳስታወቁት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 725.25 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ 738.144 ቢሊዮን ብር  ተሰብስቧል። የጉምሩክ ህግ ተገዥነትን ለማረጋገጥ በተሰራው ሥራም 27 ቢሊዮን ብር የገቢ እና 1.9 ቢሊዮን ብር የወጪ በአጠቃላይ 28.9 ቢሊዮን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች እንዲሁም የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን ሲያዘዋውሩ የተገኙ 1 ሺህ 835 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋል እንደተቻለም ተናግረዋል። የጉምሩክ ኮሚሽን በ2019 የበጀት ዓመት ከአንድ ትሪሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ዕቅድ መያዙንም ጨምረው ገልጸዋል።

ምን ማስተዋወቅ ይፈልጋሉ❓ 📌 የምንሰጣቸው የማስታወቂያ አገልግሎቶች ➠ የ ሙዚቃ ማስታወቂያ ➠ የ ኮንሰርት ማስታወቂያ ➠ የ ድርጅት ማስታወቂያ ➠ የ ዩቲዩብ ቻናል ማስታወቂያ ➠ ትሪትመንቶች እና ሌሎችም የሽያጮች ማስታወቂያ ✔የትምህርት ተቋማት…... ✔የህክምና ማዕከላት (ባህላዊ /ዘመናዊ)…... ✔የትራንስፖርት አገልግሎት….... ✔የስራ አገናኝ ኤጀንሲዎች…… ✔ሆቴል፣ካፌና ሬስቶራንቶች...... ➲ እንዲሁም የተለያዩ የ Business ስራወችን ከእኛ ጋ መስራት ለምትፈልጉ አናግሩን 👇

#አሳዛኝ ለራሱ ምርቃት የተገዛው በሬ ወግቶት ህይወቱ ያለፈው ተመራቂ የቀብር ስነ-ስርዓት ተፈጸመ። የሰው ልጅ ህይወትና መጨረሻዋ ምንኛ የማይታወቅና ተለዋዋጭ ነው? ዛሬ በደስታና በፈገግታ የደመቀ ቤ
#አሳዛኝ ለራሱ ምርቃት የተገዛው በሬ ወግቶት ህይወቱ ያለፈው ተመራቂ የቀብር ስነ-ስርዓት ተፈጸመ። የሰው ልጅ ህይወትና መጨረሻዋ ምንኛ የማይታወቅና ተለዋዋጭ ነው? ዛሬ በደስታና በፈገግታ የደመቀ ቤት፣ በአንድ ጀንበር የልቅሶና የዋይታ ድምፅ ሲሰማበት ማየት ልብን እጅግ ይሰብራል። በቅርቡ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ በኤሌክትሪካል ኢንጅነሪንግ (Electrical Engineering) ዘርፍ በታላቅ ስኬት ተመርቆ፣ ለነገው ህይወቱ ትልቅ ተስፋ ሰንቆ የነበረው ወንድማችን ፍሰሐ አስማማው እጅግ ልብ በሚሰብር አደጋ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ስንሰማ የተሰማን ሀዘን ወሰን የለውም። የነገው የሀገር ተስፋ፣ ለቤተሰቦቹ መከታ እና የብዙዎች ኩራት የነበረው ፍሰሐ፣ የለፋበትን የድካሙን ፍሬ አይቶ ገና ሳይጠግብ እንዲህ በወጣትነቱ መቀጠፉ እጅግ ያማል። ይህ ተስፋ የተጣለበት ወጣት ከሳምንት በፊት ነበር የምርቃት ካባውን የደረበው። ወላጆችና ዘመድ አዝማድም የምርቃቱን ደስታ አብረውት ለማሳለፍ ከጎንደር ጋይንት (ጎብጎብ) ከተማ ወደ ተወለደበት አካባቢ ይዘውት አምርተው ነበር። ነገር ግን በትላንትናው ዕለት ለምርቃቱ ድግስ ተብሎ የተገዛው በሬ በድንገት ወግቶት ህይወቱ ሊያልፍ ችሏል። ለአምላክ ምስጋና ይሁን ተብሎ ለደስታ ማክበሪያ የተዘጋጀው በሬ፣ በአሳዛኝ ሁኔታ የቤተሰቡን ተስፋና ደስታ ይዞ ተጓዘ። የዚህ ወጣት ስኬትና ህልም በአጭር የተቀጨበት አሳዛኝ የቀብር ስነ-ስርዓት ዛሬ በጋይንት ጎብጎብ ቀራኒዮ መድሃኒዓለም ቤተክርስቲያን ወዳጅ ዘመዶቹ፣ የክፍል ጓደኞቹና የአካባቢው ማህበረሰብ በተገኙበት ተፈፅሟል። ለወላጆቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እንዲሁም ለጓደኞቹ በሙሉ ፈጣሪ ፍጹም መፅናናትን ይስጥልን። @Seledadotio @Seledadotio

የአዲግራት ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ፍርድ ቤት ቀረቡ! ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ በቁጥጥር ሥር የዋሉት የአዲግራት ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር የማነ ገብረማርያም ፍርድ ቤት መቅረባቸው ታውቋል።
የአዲግራት ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ፍርድ ቤት ቀረቡ! ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ በቁጥጥር ሥር የዋሉት የአዲግራት ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር የማነ ገብረማርያም ፍርድ ቤት መቅረባቸው ታውቋል። ፖሊስ በዶ/ር የማነ ላይ “ከፌደራል መንግሥቱና ከሐራ መሬት ታጣቂዎች ጋር ግንኙነት አላቸው” እንዲሁም “ወደ ሐራ መሬት ታጣቂዎች ሰዎችን እየመለመሉ ይልካሉ” የሚል ከባድ ክስ ማቅረቡን ጠበቃቸውን ጠቅሶ ቢቢሲ ዘግቧል። ይህንኑ ተከትሎ ፖሊስ ከጦርነቱ በፊት የነበረው የክልሉ ምክር ቤት ባወጣው አዋጅ መሠረት፤ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራውን ለማጠናቀቅ የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ (የቀጠሮ ቀናት) ፍርድ ቤቱን የጠየቀ ሲሆን፣ ጉዳዩ በክልሉ ከፍተኛ ትኩረትን ስቧል። @Addis_News @Addis_News

ከ 68 ዓመት በኋላ የዓለም ዋንጫ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብር ወሰን ይሰበር ይሆን? በዓለም ዋንጫ ታሪክ በአንድ መድረክ 13 ግቦችን በማስቆጠር በርቀት የተቀመጠው ተጨዋች ፈረንሳዊው ጀስት ፎንቴ
ከ 68 ዓመት በኋላ የዓለም ዋንጫ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብር ወሰን ይሰበር ይሆን? በዓለም ዋንጫ ታሪክ በአንድ መድረክ 13 ግቦችን በማስቆጠር በርቀት የተቀመጠው ተጨዋች ፈረንሳዊው ጀስት ፎንቴን ነው፡፡ በ1958 ዓለም ዋንጫ 13 ግቦችን ካስቆጠረ በኋላ የትኛውም ተጨዋች እዚህ ቁጥር ላይ መድረስ አይደልም ተጠግቶ አያውቅም፡፡ ሩብ ፍጻሜ ላይ በደረሰው የ2026 ዓለም ዋንጫ ሦስት ተጨዋቾች በጋራ 22 ግቦችን አስቆጥረዋል፡፡ ሊዮኔል ሜሲ በ8 ግቦች ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱነ ሲመራ ኤርሊንግ ሃላንድ እና ኪሊያን ምባፔ በእኩል ሰባት ግቦች ሲከተሉ፣ ሃሪ ኬን በ6 ግቦች 4ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡ ምን አልባት ገና የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ላይ ሳይደርሱ እዚህ ቁጥር ላይ መድርሳቸው ለ68 ዓመታት ተይዞ የቆየውን ክብረ ወሰን የሚሰብሩበት ዕድል ሊኖር እንደሚችል ማሳያ ነው፡፡ በተለይ ከቡድኖቻቸው ጋር እስከ ፍጻሜ የሚጓዙ ከሆነ ይህንን ለማድረግ ብዙም የሚቸገሩ አይመስሉም፡፡ ከዚህ በፊት በአንድ የዓለም ዋንጫ 8 እና ከዚያ በላይ ግቦችን ያስቆጠሩት ስምንት ተጫዋቾች ብቻ ናቸው፡፡ ጀስት ፎንቴይን፣ ሳንዶር ኮሲስ፣ ገርድ ሙለር፣ አዴሚር፣ ኤውሴቢዮ፣ ጉለርሞ ስታቢሌ፣ ሮናልዶ እና ምባፔ በዚሀ ዓመት ደግሞ ሊዮኔል ሜሲ ብቻ ናቸው፡፡ @Addis_Reporter @Addis_Reporter

ኢትዮጵያዊ አማካኝ ጋቶች ፓኖም ለኩዌት ክለብ ፈረመ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የመሐል ሜዳ ተጫዋች ጋቶች ፓኖም ወደ ኩዌት ሊግ ማምራቱ ለማወቅ ተችሏል። በሳውዲው ክለብ አል አረቢ ጥሩ ጊዜን በግሉ ያ
ኢትዮጵያዊ አማካኝ ጋቶች ፓኖም ለኩዌት ክለብ ፈረመ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የመሐል ሜዳ ተጫዋች ጋቶች ፓኖም ወደ ኩዌት ሊግ ማምራቱ ለማወቅ ተችሏል። በሳውዲው ክለብ አል አረቢ ጥሩ ጊዜን በግሉ ያሳለፈው ጋቶች ፓኖም ለኩዌቱ አል ፋሂሊ ክለብ ፊርማውን ማኖር ችሏል። ጋቶች ፓኖም በክለቡ ለአንድ አመት ለመቆየት ለአል ፋሂሊ ስፖርት ክለብ ፊርማውን አኑሯል። ጋቶች ፓኖም ከሳምንታት በኃላ ወደ ግብፅ በማቅናት በቅድመ ውድድት ዝግጅት ቡድን እንደሚቀላቀል ይጠበቃል። ጋቶች ፓኖም ከሀገራችን ሊግ አልፎ :- በሩሲያ ኢራቅ ግብፅ እና ሳውዲ አረቢያ ሊጎች ላይ ባለፉት አመታት ተጫውቶ አሳልፏል። “ ጭልፊቶቹ “ የሚል መጠርያ ያለው ክለቡ አስር ክለቦች በሚሳተፉበት የሀገሪቱ ሊግ በተጠናቀቀው የውድድር ዘመን 6ኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23

5 የነዳጅ ማደያዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ ​በአዲስ አበባ ከተማ በተደረገ ድንገተኛ ቁጥጥርና ክትትል ህገ-ወጥ አሰራር ሲተገብሩ የተገኙ አምስት የነዳጅ ማደያዎች ላይ እንደ ጥፋት ደረጃቸው የዕገዳ እና የመጨረሻ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ እርምጃ ተወሰደባቸው። ​በተደረገው የክትትል ስምሪት መሠረት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ጋርመንት አካባቢ የሚገኘው ኖክ ነዳጅ ማደያ እና በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የሚገኘው አልፋ ነዳጅ ማደያ ህገ-ወጥ አሰራር በማከናወናቸው ከነዳጅ አቅርቦት እንዲታገዱ ተደርጓል። በተመሳሳይ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የሚገኘው ተባረክ ነዳጅ ማደያ ከተፈጸመው ጥሰት አሳሳቢነት አንጻር ከነዳጅ አቅርቦት ለአንድ ወር ሙሉ እንዲታገድ ውሳኔ ተላልፎበታል። ​በሌላ በኩል በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቱሉ ዲምቱ የሚገኘው የተባበሩት ነዳጅ ማደያ እና በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በካዛንቺስ ሱፐር ማርኬት አካባቢ የሚገኘው ኦላ ነዳጅ ማደያ ከዚህ ድርጊታቸው ተቆጥበው ወደ ትክክለኛ አሰራር እንዲመለሱ የመጨረሻ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የከተማው አስተዳደር በነዳጅ ስርጭት ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችን እና መደበኛ አሰራርን የሚያስተጓጉሉ አሰራሮችን ለመግታት የሚደረገው ቁጥጥር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ታውቋል።

5 የነዳጅ ማደያዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ ​በአዲስ አበባ ከተማ በተደረገ ድንገተኛ ቁጥጥርና ክትትል ህገ-ወጥ አሰራር ሲተገብሩ የተገኙ አምስት የነዳጅ ማደያዎች ላይ እንደ ጥፋት ደረጃቸው የዕገዳ እና የመጨረሻ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ እርምጃ ተወሰደባቸው። ​በተደረገው የክትትል ስምሪት መሠረት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ጋርመንት አካባቢ የሚገኘው ኖክ ነዳጅ ማደያ እና በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የሚገኘው አልፋ ነዳጅ ማደያ ህገ-ወጥ አሰራር በማከናወናቸው ከነዳጅ አቅርቦት እንዲታገዱ ተደርጓል። በተመሳሳይ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የሚገኘው ተባረክ ነዳጅ ማደያ ከተፈጸመው ጥሰት አሳሳቢነት አንጻር ከነዳጅ አቅርቦት ለአንድ ወር ሙሉ እንዲታገድ ውሳኔ ተላልፎበታል። ​በሌላ በኩል በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቱሉ ዲምቱ የሚገኘው የተባበሩት ነዳጅ ማደያ እና በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በካዛንቺስ ሱፐር ማርኬት አካባቢ የሚገኘው ኦላ ነዳጅ ማደያ ከዚህ ድርጊታቸው ተቆጥበው ወደ ትክክለኛ አሰራር እንዲመለሱ የመጨረሻ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የከተማው አስተዳደር በነዳጅ ስርጭት ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችን እና መደበኛ አሰራርን የሚያስተጓጉሉ አሰራሮችን ለመግታት የሚደረገው ቁጥጥር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ታውቋል። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23

የቤት ኪራይ ጭማሪ ይፋ ሆነ በአዲስ አበባ የቤት ኪራይ ውል ምዝገባ ተጀመረ፤ የጭማሪው ጣሪያ 11.5% ሆነ ​በአዲስ አበባ ከተማ የግል መኖሪያ ቤቶች የአከራይ-ተከራይ አዲስ የውል ምዝገባ ዛሬ ሐምሌ
የቤት ኪራይ ጭማሪ ይፋ ሆነ በአዲስ አበባ የቤት ኪራይ ውል ምዝገባ ተጀመረ፤ የጭማሪው ጣሪያ 11.5% ሆነ ​በአዲስ አበባ ከተማ የግል መኖሪያ ቤቶች የአከራይ-ተከራይ አዲስ የውል ምዝገባ ዛሬ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም በሁሉም ክፍለ ከተሞች በይፋ ተጀምሯል። ለ2019 በጀት ዓመት የሚተገበረው ፍትሐዊ የቤት ኪራይ ዓመታዊ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ መጽደቁን የከተማዋ የቤቶች አስተዳደር ቢሮ አስታውቋል። ​ይህ አሰራር በኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን ለመግታትና የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ ያለመ ነው። ውሳኔው የነዋሪዎችን የመክፈል አቅም ያገናዘበ ሳይንሳዊ ጥናት ላይ የተመሰረተ ሲሆን፣ አከራዮች ፍትሐዊ ገቢ እንዲያገኙ፣ ተከራዮች ደግሞ ከስነ-ልቦና ስጋትና መፈናቀል ድነው እንዲረጋጉ ይረዳል ተብሏል። ​ይሁን እንጂ አዲሱ የዋጋ ተመን ከመጣሉ በፊት በርካታ አከራዮች በተከራዮቻቸው ላይ አስቀድመው ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ማድረጋቸው በነዋሪዎች ዘንድ ቅሬታ እየቀሰቀሰ ይገኛል። @Seledadotio @Seledadotio

የኤርትራ መንግስት ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ዛሬ በፓርላማ ቀርበው ለሰጡት ማብራሪያ እና በተለይ ከኤርትራ (ሻዕቢያ)፣ ከሕወሓት እና ከሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ላነሷቸው ነጥቦች
የኤርትራ መንግስት ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ዛሬ በፓርላማ ቀርበው ለሰጡት ማብራሪያ እና በተለይ ከኤርትራ (ሻዕቢያ)፣ ከሕወሓት እና ከሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ላነሷቸው ነጥቦች በማስታወቂያ ሚኒስቴሩ በኩል ፈጣንና ጠንከር ያለ ምላሽ ሰጥቷል። ሁለቱ ወገኖች በቀጠናው ሰላምና በጎረቤት ሀገራት ጣልቃ ገብነት ዙሪያ እርስ በርሳቸው ተቃራኒ የሆኑ ክሶችን ሰንዝረዋል። ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ በፓርላማ ንግግራቸው በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ወጣቶችን በጉልበት እያፈሱ ለሱዳን ጦርነት "እየሸጡ" መሆኑን ገልጸዋል። "የትግራይ ወጣቶች በማያውቁት ጉዳይ በሱዳን ጦርነት ውስጥ ህይወታቸውን እያጡ ነው" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ይህ ድርጊት የህዝቡን መከራ የሚያባብስ ነው ሲሉ ወቅሰዋል። በተቃራኒው የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ ለሱዳን ግጭት መባባስ ተጠያቂው የኢትዮጵያ መንግስት ልሹ ነው ሲል ገልጿል። ኢትዮጵያ ለሱዳኑ ፈጣን ደጋፊ ኃይሎች (RSF) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ ሚስጥራዊ የጦር ሰፈርና ማሰልጠኛ በመስጠት በቀጥታ በጦርነቱ ውስጥ ተሳትፎ እያደረገች መሆኑንና ለዚህም "ግልጽ ማስረጃዎች አሉ" ሲል አጸፋዊ ክስ ሰንዝሯል። ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ በንግግራቸው የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት አደጋ ላይ የሚጥል ማንኛውንም አይነት "ትንኮሳ" ለመመከት መንግስታቸው ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። የኤርትራ መንግስት በበኩሉ፣ ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ ህግጋትንና የቀጠናውን ሀገራት ሉዓላዊነት እየጣሰች ያለችው "የባህር በር ባለቤትነት" በሚል በምታሳየው የግዛት ማስፋፋት ፍላጎት ነው ብሏል።  የኢትዮጵያ መንግስት በአንድ በኩል "ጥቃት አድራሽ" በሌላ በኩል ደግሞ "ተጠቂ" ሆኖ የመቅረብ ድራማ እየሰራ ነው ስትልም ወርፋለች። @Seledadotio @Seledadotio

"ሮናልዶን ለመውደድ ሜሲን መጥላት አይጠበቅባችሁም" — አርቲስት ሄኖክ ድንቁ ታዋቂው የኢትዮጵያ ሲኒማ ተዋናይ ሄኖክ ድንቁ ባስተላለፈው መልዕክት በረጅም ጊዜ የእግር ኳስ ደጋፊነት ባህል እና በአሁኑ
"ሮናልዶን ለመውደድ ሜሲን መጥላት አይጠበቅባችሁም" — አርቲስት ሄኖክ ድንቁ ታዋቂው የኢትዮጵያ ሲኒማ ተዋናይ ሄኖክ ድንቁ ባስተላለፈው መልዕክት በረጅም ጊዜ የእግር ኳስ ደጋፊነት ባህል እና በአሁኑ የሜሲ እና ሮናልዶ ደጋፊዎች ፉክክር ዙሪያ ያለውን እውነታ በግልፅ ተናግሯል። ሄኖክ ከልጅነቱ ጀምሮ የአፍሪካ ዋንጫ ሲታይ ኢትዮጵያ ውስጥ የግብፅ ደጋፊ እንዳልነበረና አብዛኛው ሰው እንደ * ኮትዲቯር፣ * ጋና እና * ናይጄሪያ ያሉ ጥቁር አፍሪካውያን ቡድኖችን በመደገፍ እንዳደገ አስታውሷል። አሁን ላይ የሚታየው የአንዳንድ ወገኖች የግብፅ ድጋፍ ግን ከእውነተኛ ስሜት የመነጨ ሳይሆን የሜሲ ጠላት በመሆን የሚደረግ እንደሆነ ገልጿል። “ ሮናልዶን ለመውደድ ሜሲን በዚህ ደረጃ መጥላት አይጠበቅባችሁም፤ እኔ ሮናልዶንም ሜሲንም እወደዋለሁ" በማለት ለሜሲ ደጋፊዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፏል።