ch
Feedback
Ethio - ዜና 🇪🇹

Ethio - ዜና 🇪🇹

前往频道在 Telegram

የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot

显示更多

📈 Telegram 频道 Ethio - ዜና 🇪🇹 的分析概览

频道 Ethio - ዜና 🇪🇹 (@ethio_zena23) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 105 715 名订阅者,在 图片 类别中位列第 73,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 273 位。

📊 受众指标与增长动态

自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 105 715 名订阅者。

根据 16 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -2 890,过去 24 小时变化为 -92,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 3.34%。内容发布后 24 小时内通常能获得 2.32% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 537 次浏览,首日通常累积 2 451 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 28。

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot”

凭借高频更新(最新数据采集于 17 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 图片 类别中的关键影响点。

105 715
订阅者
-9224 小时
-7417 夊
-2 89030 夊

数据加载中...

标签云
无数据
有任何问题?请刷新页面或联系我们的客服。
进出提及
---
---
---
---
---
---
吸引订阅者
䏃㜈 '26
䏃㜈 '260
在2个频道中
六月 '26
+64
在9个频道中
Get PRO
五月 '26
+129
在11个频道中
Get PRO
四月 '26
+74
在12个频道中
Get PRO
三月 '26
+2 127
在10个频道中
Get PRO
二月 '26
+8
在4个频道中
Get PRO
一月 '26
+2 108
在54个频道中
Get PRO
十二月 '25
+2 159
在81个频道中
Get PRO
十一月 '25
+4 183
在51个频道中
Get PRO
十月 '25
+4 892
在3个频道中
Get PRO
九月 '25
+7 709
在3个频道中
Get PRO
八月 '25
+5 654
在1个频道中
Get PRO
䏃㜈 '25
+6 591
在2个频道中
Get PRO
六月 '25
+6 975
在0个频道中
Get PRO
五月 '25
+7 406
在1个频道中
Get PRO
四月 '25
+7 575
在1个频道中
Get PRO
三月 '25
+8 127
在1个频道中
Get PRO
二月 '25
+7 065
在3个频道中
Get PRO
一月 '25
+7 127
在1个频道中
Get PRO
十二月 '24
+9 050
在4个频道中
Get PRO
十一月 '24
+11 169
在2个频道中
Get PRO
十月 '24
+14 487
在4个频道中
Get PRO
九月 '24
+12 613
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+11 528
在5个频道中
Get PRO
䏃㜈 '24
+4 340
在29个频道中
Get PRO
六月 '24
+871
在5个频道中
Get PRO
五月 '24
+1 669
在5个频道中
Get PRO
四月 '24
+1 824
在7个频道中
Get PRO
三月 '24
+3 958
在6个频道中
Get PRO
二月 '24
+1 530
在2个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
17 䏃㜈0
16 䏃㜈0
15 䏃㜈0
14 䏃㜈0
13 䏃㜈0
12 䏃㜈0
11 䏃㜈0
10 䏃㜈0
09 䏃㜈0
08 䏃㜈0
07 䏃㜈0
06 䏃㜈0
05 䏃㜈0
04 䏃㜈0
03 䏃㜈0
02 䏃㜈0
01 䏃㜈0
频道帖子
ነገ በአዲስ አበባ ለሚደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ሆኑ‼️ ሰልፉ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል። በትግራይ ክልል እየተባባሰ የመጣውን ቀውስ ለመቃወምና ለማስቆም እንዲሁም ለፌደራል መንግሥትና ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ለማሳወቅ ”አፈሳ ይቁም ሰላም ይስፈን” በሚል መሪ ቃል ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ በመስቀል አደባባይ ሰላማዊ ሰልፉ ይደረጋል። ሰልፉ ተጀምሮ  እስከ ሚጠናቀቅበት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ። በዚህም መሰረት:- 👉 ከመገናኛ በ22 አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ ቅ/ዑራኤል አደባባይ 👉 በቦሌ መንገድ ወደ መስቀል አደባባ ኦሎምፒያ አደባባይ 👉 ከጎተራ  ወደ መስቀል አደባባይ  ለከባድ ተሽከርካሪ  አጎና ሲኒማ መስቀለኛ ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ 👉 ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ መስቀል ለገሀር መብራት 👉 ከለገሀር ቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታዲዮም ለገሀር ቴሌ ማቋረጫ 👉 ከአራት ኪሎ ወደ መሰቀል አደባባይ ብሔራዊ ቤተ-መንግስት 👉ከካሳንቺስ በመቅረዝ ሆስፒታል ወደ መስቀል አደባባይ መቅረዝ ሆስፒታል አጠገብ 👉ከአምባሳደር ቴአትር ወደ መስቀል አደባባይ ሐራምቤ መብራት የሚወስዱ መንገዶች ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ መንገዶቹ ለተሽከርካሪ  ዝግ ይሆናሉ። ከዛሬ ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በመስቀል አደባባይና በዙሪያው ባሉ መንገዶች ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ተሽከርካሪ ለአጭርም ሆነ ረዥም ሠዓት ማቆም የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል። @Seledadotio @Seledadotio

2
ሴት መስሎ በመቅረብ ስርቆት ለመፈጸም ሲንቀሳቀስ የነበረ ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለ። 10/11/2018ዓ/ም | በሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ሴት መስሎ በመቅረብ ህብረተሰቡን ለመሸወድ እና የተለያ+2
ሴት መስሎ በመቅረብ ስርቆት ለመፈጸም ሲንቀሳቀስ የነበረ ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለ። 10/11/2018ዓ/ም | በሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ሴት መስሎ በመቅረብ ህብረተሰቡን ለመሸወድ እና የተለያየ ስርቆት ለመፈጸም ሲንቀሳቀስ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተደረገበት እንደሚገኝ የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ። ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ሊውል የቻለው በሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር በሜጦማ ቀበሌ ልዩ ስሙ መምህራን መንደር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ መሆኑ ታውቋል። አቡሽ የተባለውና የትውልድ ስፍራው በምዕራብ ባደዋቾ ቆቶ ቀበሌ የሆነው ይህ ግለሰብ ወንድነቱን በመደበቅ ራሱን ሙሉ በሙሉ ወደ ሴትነት በመለወጥ ህዝብን ሲያታልል እንደነበር ተገልጿል። ግለሰቡ የወንጀል ዓላማውን ለማሳካት የሴት ቀሚስ ፣ ሰው ሰራሽ ፀጉር (ዊግ) እና የሴት ጡት መያዣ በመጠቀም ራሱን በመለወጥ ስርቆት ለመፈጸም ሲንቀሳቀስ ነበር። የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ም/ኢ/ር አድማሱ ሱሎሮ እንደገለጹት ግለሰቡ በተደረገበት የህዝብ ጥቆማ በቁጥጥር ስር ሊውል የቻለ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም በጸጥታ ኃይሎች ተይዞ ጥልቀት ያለው ምርመራ እየተደረገበት ይገኛል። Via፦ ሺንሽቾ መንግስት ኮሙኒኬሽን @Seledadotio @Seledadotio
1 715
3
በቀን 3 ቴምር መብላት ለአእምሮ ጥንካሬና ከአልዛይመር ለመከላከል ፍቱን መፍትሔ _ጥናት ​በሎማ ሊንዳ ዩኒቨርሲቲ (ካሊፎርኒያ፣ አሜሪካ) ተመራማሪዎች የተጠናና በቅርቡ ‘ጆርናል ኦፍ ኒውትሪሽን’ ላይ
በቀን 3 ቴምር መብላት ለአእምሮ ጥንካሬና ከአልዛይመር ለመከላከል ፍቱን መፍትሔ _ጥናት ​በሎማ ሊንዳ ዩኒቨርሲቲ (ካሊፎርኒያ፣ አሜሪካ) ተመራማሪዎች የተጠናና በቅርቡ ‘ጆርናል ኦፍ ኒውትሪሽን’ ላይ የታተመ ጥናት እንደሚያመለክተው በቀን ሦስት ቴምር መመገብ ለአእምሮ ጤና ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው ከመሆኑም በላይ የትርሳን (የአልዛይመር) በሽታ የመያዝ ተጋላጭነትን በእጅጉ ይቀንሳል። ቴምር የአእምሮ ሴሎችን ከጉዳት የሚጠብቁና እብጠትን የሚከላከሉ እንደ ፍላቮኖይድስ እና ፌኖሊክ አሲድ ያሉ አንቲኦክሲዳንቶች እንዲሁም በርካታ ጠቃሚ ቪታሚኖች በውስጡ ይዟል። ​በሳይንሳዊ ምርምሮች መሠረት፣ ቴምር በአእምሮ ውስጥ የሚፈጠሩትንና ለአልዛይመር በሽታ መከሰት ዋነኛ መንስኤ የሆኑትን የ"አሚሎይድ ፕላኮች" (amyloid plaques) ክምችት የመከላከል ከፍተኛ አቅም አለው። ​ሆኖም ግን ቴምር ከፍተኛ የካሎሪና የስኳር መጠን ስላለው (በ100 ግራም ውስጥ ወደ 66 ግራም ስኳር ይገኛል)፣ በተለይ የስኳር ህመምተኞች እና የጨጓራ ወይም የአንጀት ችግር ያለባቸው ሰዎች በሚመገቡበት ጊዜ መጠን ማወቅና ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው ምሁራን ያሳስባሉ። @Seledadotio @Seledadotio
2 062
4
የአሜሪካ ግሪን ካርድ ለማግኘት የ100,000 ዶላር ቅድመ ክፍያ ሊጠየቅ ነው ​የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ስደተኞች ወደ ሀገሪቱ እንዳይገቡ ለመግታት አዲስ ጥብቅ መመሪያ እያዘጋ
የአሜሪካ ግሪን ካርድ ለማግኘት የ100,000 ዶላር ቅድመ ክፍያ ሊጠየቅ ነው ​የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ስደተኞች ወደ ሀገሪቱ እንዳይገቡ ለመግታት አዲስ ጥብቅ መመሪያ እያዘጋጀ መሆኑ ታወቀ። በታቀደው አዲስ ረቂቅ መመሪያ መሠረት፣ ከዩናይትድ ስቴትስ ውጪ ሆነው የቋሚ ነዋሪነት ፈቃድ (ግሪን ካርድ) የሚያመለክቱ ግለሰቦች የ100,000 ዶላር የገንዘብ ዋስትና በቅድሚያ እንዲያስይዙ ሊገደዱ ይችላሉ። ​ይህ የተያዘው ገንዘብ አመልካቾቹ የአሜሪካ ዜግነት ሲያገኙ የሚመለስላቸው ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም አዲሶቹ ስደተኞች በራሳቸው መተዳደር የሚችሉ መሆናቸውንና የመንግስትን ድጋፍ እንደማይጠብቁ ለማረጋገጫነት እንዲያገለግል ነው። ​ይህ አሰራር በተለይ ከድሃ ሀገራት ለሚመጡና የአሜሪካ ዜግነት ያላቸው የቅርብ ዘመዶቻቸውን (ትዳር አጋር፣ ወላጅና እህትማማቾች) ለማስገባት ለሚፈልጉ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች ትልቅ እንቅፋት እንደሚሆን ተገልጿል። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መመሪያውን መጀመሪያ በጥቂት ሀገራት ላይ ለመፈተሽ አቅዷል። @Seledadotio @Seledadotio
2 152
5
በሀገራዊ ምክክር መድረክ ላይ የተገላገለችው እናት ልጇን "ምክክር" ስትል ሰየመችው:: የሀገር ፍቅር እና የቁርጠኝነት ትልቅ ማሳያ የሆነችው ወጣት ክርኑዶ ኡጁሉ፣ የመውለጃዋ ቀን ተቃርቦ ሳለ “ሀገሬ+8
በሀገራዊ ምክክር መድረክ ላይ የተገላገለችው እናት ልጇን "ምክክር" ስትል ሰየመችው:: የሀገር ፍቅር እና የቁርጠኝነት ትልቅ ማሳያ የሆነችው ወጣት ክርኑዶ ኡጁሉ፣ የመውለጃዋ ቀን ተቃርቦ ሳለ “ሀገሬ ጠርታኝ አልቀርም” በሚል ትልቅ አላማ ከጋምቤላ ክልል ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ላይ ስትሳተፍ ቆይታለች። በጉባኤው ሂደት ላይ እያለችም በዘውዲቱ ሆስፒታል ወንድ ልጅ በሰላም ተገላግላለች። ይህንን ተከትሎም የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወ/ሮ አለሚቱ ኡመድ እናቲቱ ባረፈችበት ቤት በአካል በመገኘት እንኳን ደስ አለሽ ብለዋታል። ወጣቷ እናት የተለመደውን የቤተሰብ ስም የማውጣት ባህል በመተው፣ የልጇን ስም የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ እንዲያወጣላት በጠየቀችው መሠረት የሕፃኑ ስም "ምክክር" ተብሎ ተሰይሟል። ከጥቂት ቀናት እረፍት በኋላ የመጣችበትን ታላቅ ሀገራዊ ዓላማ ለማሳካት ወደ ምክክር ጉባኤው በልበ ሙሉነት እንደምትመለስ ያረጋገጠች ሲሆን፣ ጉባኤውን አጠናቃ ወደ መጣችበት እስክትመለስ ድረስ ለእሷና ለልጇ የሚያስፈልገው ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እንደሚደረግላት ተገልጿል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ይህ ታሪክ ለሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ ትልቅ ማሳያ መሆኑን ጠቅሰው፣ እናቲቱ በሰላም ተገላግላ በደስታ እንደተሞላች ሁሉ ሀገሪቱም ከገጠሟት ፈተናዎች በምክክር እና በውይይት ተገላግላ ወደ ተሻለ የሽግግር ምዕራፍ እንደምትሻገር ፅኑ እምነታቸውን ገልጸው ለሕፃኑ እና ለኢትዮጵያ ሕፃናት በሙሉ መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል። @Seledadotio @Seledadotio
2 137
6
የአጭር ጊዜ ቪዲዮዎች (TikTok እና Reels) ራስን የመቆጣጠር እና የዲሲፕሊን ክህሎትን የሚገነባውን የአንጎል ክፍል ስራ እንደሚያደናቅፉ አዲስ ጥናት አመለከተ ተጠቃሚዎች በምስሎቹ ቢደሰቱም ባይ
የአጭር ጊዜ ቪዲዮዎች (TikTok እና Reels) ራስን የመቆጣጠር እና የዲሲፕሊን ክህሎትን የሚገነባውን የአንጎል ክፍል ስራ እንደሚያደናቅፉ አዲስ ጥናት አመለከተ ተጠቃሚዎች በምስሎቹ ቢደሰቱም ባይደሰቱም፥ ቪዲዮዎቹ በአንጎል ላይ የሚያሳድሩት አሉታዊ ተፅዕኖ አይቀሬ መሆኑ ተረጋግጧል። ​ጥናቱ እንደሚያሳየው፣ እነዚህ ምስል-ወለድ ይዘቶች የተመልካቹን ቀልብ አንዴ ከሳቡ በኋላ ፈጣን የዶፓሚን ሆርሞን መለቀቅን ያስከትላሉ። ይህም የአንጎልን የተፈጥሮ ውሳኔ ሰጪነት በማደንዘዝ፣ ከዕፅ ሱስ የጠነከረ ከፍተኛ የሱስ የመለከፍ አደጋ ይፈጥራል። ​ይህ የፈጣን መዝናኛ አባዜ የሰውን ልጅ ወደ ማገናዘብ የማይችል “ዞምቢ” እየቀየረው መሆኑን ተመራማሪዎች አስጠንቅቀዋል። ራስን የመግዛት አቅምን ለመጠበቅ ከማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም መገደብ ወሳኝ እንደሆነም ተመክሯል። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23
2 090
7
በአዲስ አበባ የተቃውሞ ሰልፍ‼️ ለሐምሌ 11 የተጠራው ሰልፍ ፈቃድ አገኘ‼️ በትግራይ ክልል እየተካሄደ ያለውን ወታደራዊ አፈሳ ለማውገዝ በአዲስ አበባ የተጠራው የተቃውሞ ሰልፍ የተፈናቀሉትን እንደሚ
በአዲስ አበባ የተቃውሞ ሰልፍ‼️ ለሐምሌ 11 የተጠራው ሰልፍ ፈቃድ አገኘ‼️ በትግራይ ክልል እየተካሄደ ያለውን ወታደራዊ አፈሳ ለማውገዝ በአዲስ አበባ የተጠራው የተቃውሞ ሰልፍ የተፈናቀሉትን እንደሚያሳትፍ ተሰምቷል። በአዲስ አበባ ከተማ ለመጪው ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም የተጠራውና በሕገ-ወጥ ወታደራዊ ምልመላ እንዲሁም በሰላማዊ ዜጎች እስር ላይ ያተኮረው የተቃውሞ ሰልፍ የመንግስትን ፈቃድ ማግኘቱንና በከተማዋ የሚገኙ በርካታ የትግራይ ተፈናቃዮችም በሰልፉ ላይ እንደሚሳተፉ ታውቋል።። የስምረት ፓርቲን ጨምሮ ሌሎች የፖለቲካ ኃይሎችን ያካተተው የትግራይ ሰላምና የለውጥ ምክር ቤት የጠራው ይህ ሰልፍ፤ በትግራይ ክልል እየተፈጸመ ነው ያሉትን ወታደራዊ አፈሳ ለማውገዝ፣ የታሰሩ እናቶችንና ገበሬዎችን ድምጽ ለማሰማት እንዲሁም ለአዲስ አበባ ተፈናቃዮች ተገቢው ድጋፍ እንዲደረግ ለመጠየቅ ያለመ መሆኑ ተገልጿል። የስምረት ፓርቲ ጽሕፈት ቤት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኃላፊ  ሃለፎም ምርአ ለአዲስ ማለዳ እንደተናገሩት፤ የሰልፉ ዋና ዓላማ በትግራይ ክልል ሕጋዊ ያልሆነ አዋጅን መነሻ በማድረግ በወጣቶች ላይ እየተፈጸመ ያለውን አስገዳጅ ወታደራዊ ምልመላና ያለአግባብ የታሰሩ እናቶችንና ገበሬዎችን በደል ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይፋ ማድረግ ነው። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዕውቅና የነፈገውን የህወሃት ቡድን “የፕሪቶሪያው ስምምነት ፈርሷል” በሚል እያከናወነ ያለውን ተግባር ለማውገዝ፣ የፌደራል መንግሥት የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ ለመጠየቅና በጦርነት ምክንያት ተፈናቅለው አዲስ አበባ የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች አስፈላጊውን ሰብአዊ ድጋፍ እንዲያገኙ ለማስቻል እንደሆነ ኃላፊው አስረድተዋል። ‎ @Seledadotio @Seledadotio
2 452
8
ነጋዴው አገልግሎት ሰጪ ተቋም የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ከ42 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ገለፀ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ በበጀት
ነጋዴው አገልግሎት ሰጪ ተቋም የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ከ42 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ገለፀ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ በበጀት አመቱ ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ፓስፖርት ለዜጎች መሰጠት መቻሉንና የአገልግሎት መስጫ ቅርንጫፎች 23 ማድረሳቸውን ገልጸዋል። አክለውም 1,046,286 ቪዛ፣ 32,952 ትውልደ ኢትዮጵያውያን መታወቂያ እንዲሁም 21,163 ጊዜያዊና ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ መሰጠቱን ተናግረዋል። በአጠቃላይ ከ42 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በመሰብሰብ ስኬታማ ስራ መሰራቱም የተገለፀ ሲሆን፥ በአየር እና በየብስ ድንበር አለማቀፍ ደረጃን በጠበቀ መልኩ በጉዞ ሰነድ ለ7,225,691 ገቢና ወጪ መንገደኞች አገልግሎት ተሰጥቷል ብለዋል።   ዋና ዳይሬክተሯ በመግለጫቸው፤ 433 የውጭ ዜጎችና 4ሺህ 450 ኢትዮጵያውያን በአጠቃላይ 4ሺህ 883 ዜጎች በሐሰተኛ ሰነድ የማጭበርበር ድርጊት ሲፈጽሙ ተይዘው እርምጃ እንደተወሰደባቸው ተናግረዋል። በተጨማሪም 25ሺህ 407 ኢትዮጵያውያን እና 29ሺህ 606 የውጭ ሀገር ዜጎች በህገወጥ መንገድ ወደ ሀገር ሊገቡና ሊወጡ ሲሉ ተይዘው ተጠያቂ መደረጋቸውን ገልጸዋል። በበጀት አመቱ ስድስት ሚሊዮን የሲቪል እና ቤተሰብ ምዝገባ የተካሄደ ሲሆን ይህን ሂደት ለመምራት የተለዩ የዲጂታል አማራጭ መተግበሪያ እና ስረአት መዘርጋቱን ዋና ዳይሬክተሯ ተናግረዋል።
2 560
9
ጥቆማ‼️ ያለጥርጥር በቴሌግራሙ አለም አሉ ከሚባሉ የመረጃ አቅራቢዎች መሀከል የተለያዩ ወቅታዊ እና እውነተኛ መረጃዎችን በታማኝነትና በፍጥነት ፈልፍሎ የሚያቀርብ የቴሌግራም ቻናል ልጠቁማቹ 👍 በጥቆ
ጥቆማ‼️ ያለጥርጥር በቴሌግራሙ አለም አሉ ከሚባሉ የመረጃ አቅራቢዎች መሀከል የተለያዩ ወቅታዊ እና እውነተኛ መረጃዎችን በታማኝነትና በፍጥነት ፈልፍሎ የሚያቀርብ የቴሌግራም ቻናል ልጠቁማቹ 👍 በጥቆማዬ ሙሉ በሙሉ እተማማናለሁ "የመረጃ ቋት ቻናል ነው "በዚህ ሊንክ ግቡ 👇👇 👇 https://t.me/seledadotio https://t.me/seledadotio
2 391
10
በሰሜን ኢትዮጵያ የዝናብ መጠን አነስተኛ ነው‼️ የሰሜንና የሰሜን ምስራቅ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ላይ በክረምቱ የሚኖረው ዝናብ አነስተኛ ነው ሲል የኢትዮጵያ ሜትሮሎጂ ኢንስቲትዩት ተናገረ፡፡ በዚህም
በሰሜን ኢትዮጵያ የዝናብ መጠን አነስተኛ ነው‼️ የሰሜንና የሰሜን ምስራቅ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ላይ በክረምቱ የሚኖረው ዝናብ አነስተኛ ነው ሲል የኢትዮጵያ ሜትሮሎጂ ኢንስቲትዩት ተናገረ፡፡ በዚህም ምክንያት የሚኖረው የዝናብ መጠን አነስተኛ ነው ህብረተሰቡም በቂ ዝግጅት እንዲያደርግ ኢንስቲትዩቱ ተናግሯል፡፡ የክረምት ዝናብ አሁን ላይ ባላገኙ አንዳንድ አካባቢዎች በሚቀጥሉት ቀናት የተሻለ ዝናብ እንደሚያገኙ ጠቅሷል፡፡ የዝናብ እጥረት በሚታይባቸው አካባቢዎችም በመጪዎቹ ቀናት የተሻለ የዝናብ መጠን ሊያገኙ እንደሚችልም ኢንስቲትዩቱ ትንበያውን ነግሮናል፡፡ በመጪዎቹ 10 ቀናት በአብዛኛው የዝናብ ተጠቃሚ አካባቢዎች የሚኖረው የዝናብ መጠን ከቀላል እስከ መካከለኛ ነው ተብሏል፡፡ በመካከለኛው የአማራ አካባቢዎች ፣ የምዕራብ ሻዋ ፣ ምዕራብ ኦሮሚያ እና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አካባቢዎች ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ሊዘንብ እንደሚችል አስረድቷል፡፡ ህብረተሰቡን ከባድ ዝናብ በሚጥልባቸው አካባቢዎች አስፈላጊው ጥንቃቄ እንዲያደርግ ኢንስቲትዩቱ ጠይቋል፡፡ የዝናብ እጥረት ሊከሰትባቸው ይችላል በተባሉ አካባቢዎች ላይ ደግሞ የግብርና ስራዎች ሲሰራ አስፈላጊው ዝግጅትና አማራጮች እንዲወሰድም መክሯል፡፡ ‎ @Seledadotio @Seledadotio
2 485
11
ቤት ሰርቶ ያለማከራየት አይቻልም ተብሏል። 📌አከራዮች ተጠንቀቁ፤ በአዲስ አበባ አዲስ መመሪያ ወጥቷል። ቤት ሰርተው ወይም አድሰው ሳይጠቀሙበት ወይም ሳያከራዩ ለስድስት ወራት ካስቀመጡ፣ መንግስት ቢ
ቤት ሰርቶ ያለማከራየት አይቻልም ተብሏል። 📌አከራዮች ተጠንቀቁ፤ በአዲስ አበባ አዲስ መመሪያ ወጥቷል። ቤት ሰርተው ወይም አድሰው ሳይጠቀሙበት ወይም ሳያከራዩ ለስድስት ወራት ካስቀመጡ፣ መንግስት ቢከራይ ሊያገኝ የሚችለውን ገቢ አስልቶ ግብር እንዲከፍሉ ያደርጋል ተብሏል። ይባስ ብሎ ደግሞ ቤቱ ሳይከራይ ከአምስት አመት በላይ ከቆየ፣ አመታዊ የንብረት ግብሩ ላይ ሃያ አምስት በመቶ ተጨማሪ ቅጣትም ይጣልበታል። አከራዮች 'ቤቴ ነው፣ የፈለኩትን አደርጋለሁ' ማለት አይችሉም ተብሏል። የህግ ባለሙያዎችም ቤት ለማግኘት ህዝቡ እየተቸገረ፣ ቤት ዘግቶ ማስቀመጥ መብት አይደለም እያሉ ይገኛሉ። ቤታችሁን ዘግታችሁ ያስቀመጣችሁ አከራዮች ሰው ይኑርበት ተብላችኋል።
2 499
12
“ኢትዮጵያ ውስጥ ኮሽ ሲል፤ ያደፈጡ፣ የሚነቁ፣ የዘመናት ያልተቋረጠ የጠላትነት ስሜት ያላቸው ሀገራት አሉ” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። ኢትዮጵያ “በቀጣይ” አዲስ ህገ መንግስት ሊኖ
“ኢትዮጵያ ውስጥ ኮሽ ሲል፤ ያደፈጡ፣ የሚነቁ፣ የዘመናት ያልተቋረጠ የጠላትነት ስሜት ያላቸው ሀገራት አሉ” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። ኢትዮጵያ “በቀጣይ” አዲስ ህገ መንግስት ሊኖራት እንደሚችልም ዛሬ ረቡዕ ሐምሌ 8፤ በይፋ በተከፈተው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥቆማ ሰጥተዋል። ጠ/ሚኒስትሩ በዚሁ ንግግራቸው ከሀገራዊ ጉባኤው የሚጠበቁ ጉዳዮችን እና በምክክሩ ይሳካሉ ብለው የሚጠብቋቸውን ጉዳዮች አንስተዋል። “አሁን የምንመካከረው ስለ ትላንትናው አይደለም። የትላንትን ችግር ፈተን ለነገ መልካም መሰረት ለማኖር ነው” ሲሉ አብይ ከሀገራዊ ጉባኤው የሚጠበቀውን አመልክተዋል። “የአሜሪካ ህገ መንግስት በ55 ሰዎች ቢሰራም ልባም ነበሩና ለምዕተ ዓመታት የሚቆይ ስራ ሰርተዋል። የእኛ አራት ሺህ ሰዎች ከእነሱ በላይ፣ ከእነሱ በተሻለ ጊዜ ይበልጥ ልባም ሆነው፣ ሁሉን ወገን፣ መላው ኢትዮጵያን የሚሰበስብ ምክክር ቢያደርጉ፤ በቀጣይ የሚኖረን ህገመንግስት ከዚህ ቀደም እንደለመድነው የመጣ ሁሉ የሚቀደው ሳይሆን፤ እኛ በአራት ሺህ ጀምረናል፣ በ10 ሺህ ምክክር ሳይደርግ፤ አንድም ሰው መቀየር አይችልም ማለት ነው” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ተናግረዋል። ጠ/ሚኒስትሩ ስለ ቀይ ባህር ጉዳይ በተለይ ሲናገሩ፣ "ኢትዮጵያ ለሺ ዘመናት ያስተዳደረችውን፣ በባለቤትነት የያዘችውን፣ ለራሷም ለከባቢውም መጠቀሚያ ያኖረችውን ቀይ ባህር ያልተመረጠ መንግስት፣ ያልተወያየ መንግስት በሸፍጥ ኢትዮጵያን የጂኦግራፊ እስረኛ እንዲያደርግ ያደረገበት ዋናው ምክንያት በውስጥ ያለን ስንፍና እንጂ የኢትዮጵያን መሻትና ጥቅም ማስቆም የሚችል ኃይል ስለነበረ፣ ስላለ፣ ስለሚኖር አይደለም " ብለዋል። @Seledadotio @Seledadotio
2 782
13
ኢትዮጵያ ዛሬ 180 ሚሊየን ዶላር (29 ቢሊየን ብር) እዳዋን ዘጭ አድርጋ እንደምትከፍል የሚጠበቅበት ቀን ነው! 👉ሌላ 100 ሚሊየን ዶላር ሊኖር ይችላል ኢትዮጵያ እና የዩሮቦንድ ባለይዞታዎች ከሰሞኑ በደረሱበት የቴክኒክ ስምምነት መሰረት ኢትዮጵያ ካለባት እዳ ውስጥ 180 ሚሊየን ዶላሩን ዛሬ መክፈል ይጠበቅባታል፡፡ የእዳ መልሶ ማዋቀር ስምምነቱ ሲደረስ ከታህሳስ 2016 እስከ ታህሳስ 2017 ዓም መከፈል የሚገባቸው ሶስት የወለድ ክፍያዎች በጥቅሉ 100 ሚሊየን ዶላር በአንዴ መከፈል የሚገባው መሆኑ ይታወሳል፡፡ በመርህ ደረጃ በተደረሰው ስምምነት መሰረት ቀሪ 👉100 ሚሊዮን ዶላር – 15 ጁላይ 2027 👉300 ሚሊዮን ዶላር – 15 ጁላይ 2028 👉300 ሚሊዮን ዶላር – 15 ጁላይ 2029 የሚከፈል ይሆናል። አሁን ጥያቄው የዛሬውን እሺ ያንን የሚያክል ገንዘብ በአንዴ የመክፈል አቅም ይኖረናል ወይ? ነው ጥያቄው።
2 805
14
ትራምፕ ኢራንን በኃይል ማመንጫዎችና ድልድዮች ውድመት እያስፈራሩ ነው ​በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ወታደራዊ ውጥረት እያገረሸ ባለበት በዚህ ወቅት፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራ
ትራምፕ ኢራንን በኃይል ማመንጫዎችና ድልድዮች ውድመት እያስፈራሩ ነው ​በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ወታደራዊ ውጥረት እያገረሸ ባለበት በዚህ ወቅት፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን ወደ የውይይት ጠረጴዛ ካልተመለሰች ከፍተኛ ጥቃት እንደሚሰነዝሩ አስጠነቀቁ። ትራምፕ ከፎክስ ኒውስ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ በሚቀጥለው ሳምንት ለኢራን ሁኔታው እጅግ ከባድ እንደሚሆን ገልጸው፣ የሀገሪቱን የኃይል ማመንጫዎች እና ድልድዮች በሙሉ እንደሚያወድሙ ዝተዋል። ​ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሲቪል መሰረተ ልማቶችን ሆን ብሎ ማጥቃት የጦር ወንጀል መሆኑን አስታውሷል። አሜሪካ በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ ላይ ጥቃቷን ስትቀጥል፣ ኢራን በበኩሏ በባህሬን እና ኩዌት የሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮችን መምታቷንና የባህር ወሽመጡን ቁጥጥር እንደማትለቅ አስታውቃለች። የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኦባማ በትራምፕ ውሳኔ ላይ ያላቸውን ተቃውሞ ገልጸዋል
2 803
15
የአዲስ አበባ ታክሲዎች ጉዞ ከመጀመራቸው በፊት ክፍያ እንዲሰበስቡ ተወሰነ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የታክሲ አሽከርካሪዎች ከተወሰነው ታሪፍ በላይ እንዲሚያስከፍሉ ከማኅበረሰቡ የሚነሳውን ቅሬታ ለመፍታት ክፍያው ከመነሻው እንዲሰበሰብ የሚያስገድድ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋቱን አስታውቋል። አሽከርካሪዎች በታሪፍ መመሪያው መሠረት ብቻ ከመነሻው የትራንስፖርት ክፍያ እንዲሰበስቡ ለማስቻል ተቆጣጣሪዎች በመነሻ መጫኛ ቦታዎች ላይ ተመድበው ሥራ መጀመራቸውን የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው ተናግረዋል። ይህ አሠራር በጉዞ ወቅት "ሒሳብ ጨምሩ" በሚል ከአሽከርካሪዎች የሚነሳውን አግባብነት የሌለው ጥያቄ ለመግታት የጎላ ፋይዳ እንደሚኖረው ታምኖበታል። ይሁን እንጂ አዲሱ አሠራር ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ አንዳንድ ተግዳሮቶች መፈጠራቸውን የቢሮው ኃላፊዎች ጠቁመዋል። በከተማዋ በሚገኙ መነሻዎች ላይ ክፍያውን አስቀድሞ በመሰብሰብ ሂደት የተወሰነ ጊዜ እየወሰደ መሆኑ በማኅበረሰቡ በኩል ቅሬታ መፍጠሩ ተገልጿል። በተመሳሳይ አንዳንድ አሽከርካሪዎች መንገድ ከጀመሩ በኋላ ታሪፍ የመጨመር አዝማሚያዎችን እያሳዩ መሆናቸውን ቢሮው አስታውቋል። ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመቅረፍ ማኅበረሰቡ የጉዳዩን ፋይዳ በመገንዘብ ተገቢውን ትብብር እንዲያደርግና ህገ-ወጥ አሽከርካሪዎችን በተመለከተ ጥቆማዎችን በመስጠት የዜግነት ኃላፊነቱን እንዲወጣ አቶ ዳኛቸው አሳስበዋል። በሌላ በኩል ከዚህ ቀደም ያለ ረዳት በሚጭኑ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ሲገለጽ መቆየቱ የሚታወስ ቢሆንም፤ ቢሮው በአሁኑ ወቅት ትኩረቱን አዲሱ የአሠራር ሥርዓት ላይ ማድረጉን አመልክቷል። ይሁን እንጂ የረዳት አጠቃቀምን በተመለከተ ግልጽና ወጥ የሆነ የአሠራር ሥርዓት እንደሚያስፈልግ አቶ ዳኛቸው ገልጸዋል።
2 867
16
ስፔን ለፍፃሜ አለፈች ስፔን ፈረንሳይን 2 ለ 0 በማሸነፍ የፍፃሜ ተፋላሚ መሆኗን አረጋገጠች። ኦርያዛባል እና ፔድሮ ፖሮ ስፔንን አሸናፊ ያደረጉ ጎሎችን ከመረብ አሳርፈዋል። ስፔን ከአስራ ስድስት ዓ
ስፔን ለፍፃሜ አለፈች ስፔን ፈረንሳይን 2 ለ 0 በማሸነፍ የፍፃሜ ተፋላሚ መሆኗን አረጋገጠች። ኦርያዛባል እና ፔድሮ ፖሮ ስፔንን አሸናፊ ያደረጉ ጎሎችን ከመረብ አሳርፈዋል። ስፔን ከአስራ ስድስት ዓመታት በኋላ በዓለም ዋንጫው ለፍፃሜ አልፋለች። ስፔን በፍፃሜው ከአርጀንቲና እና እንግሊዝ አሸናፊ ጋር ትጫወታለች።
2 856
17
አሽከርካሪዎች #እንድታውቁት ነገ ሀምሌ 08/2018 ዓ.ም ታሪካዊ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በመዲናችን አዲስ አበባ ይጀመራል፡፡ ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ የጉባኤው ተሳታፊዎችም ወደ ከተማችን ገብተዋል፡፡
አሽከርካሪዎች #እንድታውቁት   ነገ ሀምሌ 08/2018 ዓ.ም ታሪካዊ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በመዲናችን አዲስ አበባ ይጀመራል፡፡ ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ የጉባኤው ተሳታፊዎችም ወደ ከተማችን ገብተዋል፡፡   የጉባኤው ተሳታፊዎች በሲኤምሲ መስመር የተባበሩት አደባባይ ወደ ሚገኘው አዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ሴንተር ጠዋትና ማታ ሲገቡና ሲወጡ የሚጓዙባቸው መስመሮች ማለትም ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ በሳህሊተ ምህረት አንዲሁም ከኢትዮ ቻይና መስመር በሳህሊተ ምህረት እስከ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ሴንተር የትራፊክ መጨናነቅ ያጋጥማል፡፡   በመሆኑም ከነገ ጀምሮ ጉባኤው እስከሚጠናቀቅበት ጊዜ ድረስ በመስመሮቹ የምትጓዙ አሽከርካሪዎች አስቀድማችሁ አማራጭ መንገዶችን እንድትጠቀሙ ከወዲሁ እናሳውቃለን፡፡   የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን   @Seledadotio @Seledadotio
3 084
18
ዛሬ የዓለም ዋንጫ ተጠባቂው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ በስፔን እና በፈረንሳይ መካከል ይከናወናል ይህ ጨዋታ በፊፋ የዓለም ደረጃ አንደኛ እና ሦስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙትን ሁለቱን የአውሮፓ ኃያላን የሚያገ+2
ዛሬ የዓለም ዋንጫ ተጠባቂው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ በስፔን እና በፈረንሳይ መካከል ይከናወናል ይህ ጨዋታ በፊፋ የዓለም ደረጃ አንደኛ እና ሦስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙትን ሁለቱን የአውሮፓ ኃያላን የሚያገናኝ በመሆኑ በመላው ዓለም የሚገኙ የስፖርት አፍቃሪያንን ቀልብ ስቧል። በዲዲዬ ዴሻምፕ የሚመራውና "ሌ ብሉዝ" በመባል የሚታወቀው የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን በሩብ ፍጻሜው የሞሮኮ ብሔራዊ ቡድንን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፎ ወደዚህ ደረጃ ተሸጋግሯል፡፡ በሉዊስ ዴ ላ ፎንቴ የሚሰለጥነው የስፔን ብሔራዊ ቡድንም በተመሳሳይ ሌላኛዋን የአውሮፓ ተፎካካሪ ሀገር ቤልጂየምን 2 ለ 1 በሆነ ጠባብ ውጤት በመርታት ለግማሽ ፍጻሜው አልፏል። ይህ ታላቅ ጨዋታ በውድድሩ እጅግ ጠንካራ የመከላከል መስመር ያላቸውን ሁለቱን ቡድኖች ፊት ለፊት የሚያገናኝ ሲሆን፤ በተለይም ፈረንሳይ በጥሎ ማለፍ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች ውስጥ እስካሁን አንድም ግብ ሳታስተናግድ ስድስት ግቦችን ማስቆጠሯ አስደናቂ ጥንካሬዋን ያሳያል። ስፔንም በበኩሏ በተመሳሳይ በጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ስድስት ግቦችን ከመረብ ያሳረፈች ሲሆን፥ ያስተናገደችው ግን አንድ ግብ ብቻ ነው። የሁለቱን ታሪካዊ ተቀናቃኝ ቡድኖች የእርስ በርስ ግንኙነት ስንመለከት፤ ስፔን በቅርብ ዓመታት የበላይነት መውሰድ የቻለች ሲሆን፥ በ2024ቱ የአውሮፓ ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ ፈረንሳይን 2 ለ 1 እንዲሁም በቅርቡ በ2025ቱ የኔሽንስ ሊግ ግማሽ ፍጻሜ በጎል ፌሽታ በተንበሸበሸው መርሐ-ግብር 5 ለ 4 በሆነ ውጤት ማሸነፏ ይታወሳል። ዛሬ ምሽት 4:00 ሰዓት በአርሊንግተን ቴክሳስ የሚገኘው AT&T ስታዲየም ጨዋታውን የሚያስተናግድ ሲሆን፥ ሳልቫዶሪያዊው ኢቫን ባርተን ጨዋታውን በመሀል ዳኝነት ይመሩታልል። @Addis_News @Addis_News
3 433
19
ዶናልድ ትራምፕን የምትመስለው ስፔናዊቷ ገበሬ የመገናኛ ብዙኃን መነጋገሪያ ሆናለች! በሰሜን ምዕራብ ስፔን ገጠራማ ስፍራ (ጋሊሲያ) የምትኖረው ዶሎሬስ ሌይስ አንቴሎ የተባለችው አዛውንት፣ ከአሜሪካው
ዶናልድ ትራምፕን የምትመስለው ስፔናዊቷ ገበሬ የመገናኛ ብዙኃን መነጋገሪያ ሆናለች! በሰሜን ምዕራብ ስፔን ገጠራማ ስፍራ (ጋሊሲያ) የምትኖረው ዶሎሬስ ሌይስ አንቴሎ የተባለችው አዛውንት፣ ከአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ባላት አስገራሚ መመሳሰል የተነሳ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በድጋሚ ከፍተኛ ትኩረት እየሳበች ትገኛለች። እ.ኤ.አ. በ2018 ስለ ገጠር ህይወት የሚዘግብ አንድ ጋዜጠኛ የዕድሜ ባለጸጋዋን ዶሎሬስን በፈረንቃ (አካፋ) ተደግፋ በፎቶ ካሜራው አስቀርቷት ነበር። በፎቶው ላይ ያላት የፀጉር ቀለም፣ የፊት አወቃቀር እና አስተያየት ከዶናልድ ትራምፕ ጋር ፍጹም አንድ አይነት በመሆኑ በወቅቱ ዓለምን አስገርሞ የነበረ ሲሆን፣ ይህ ምስል አሁን በ2026 በድጋሚ በማህበራዊ ድረ-ገጾች ላይ በስፋት እየተጋራ ይገኛል። የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች የሁለቱን ምስሎች ጎን ለጎን በማነፃፀር "መንትዮች ናቸው" እስከማለት ደርሰዋል። ዶሎሬስ ይህንን አጋጣሚ በጣም በሚያስቅ ሁኔታ የተቀበለችው ሲሆን፣ በወቅቱ ለሀገር ውስጥ ጋዜጣ በሰጠችው አስተያየት፦ "ምስሌ በጣም ሩቅ ቦታ የተጓዘ ይመስላል፤ እኔ እንደማስበው ግን ይህ የሆነው በፀጉሬ ቀለም ምክንያት ነው" ስትል በፈገግታ ተናግራለች። ይህ ድንገተኛ ዝና በገጠሯ ስፔን የምትመራውን ቀለል ያለ የግብርና ህይወት አላስተጓጎላትም፤ ይልቁንም አሁንም ድረስ በደስታ ስራዋን እየቀጠለች ትገኛለች ነው የተባለው።
3 158
20
ትምህርት ሚኒስቴር በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና አዲስ ማዕቀፍ አዘጋጅቷል። ማዕቀፉ መምህራን በክረምት ስልጠና ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የሚሸጋገሩበት መሆኑ ተገልጿል። ሚ+1
ትምህርት ሚኒስቴር በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና አዲስ ማዕቀፍ አዘጋጅቷል። ማዕቀፉ መምህራን በክረምት ስልጠና ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የሚሸጋገሩበት መሆኑ ተገልጿል። ሚኒስቴሩ በቀን 06/11/2018 ዓ.ም ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች በጻፈው ደብዳቤ፣ ከአጠቃላይ ትምህርት ሥርዓተ ትምህርት ለውጥ ጋር ተያይዞ ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና ወደ ዩኒቨርሲቲዎች ማስገባት መቋረጡን አስታውሷል፡፡ ይሁን እንጂ በቀጣይ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት በተዘጋጀ የስልጠና ማዕቀፍ፣ በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና የሚሰጥ መሆኑን ገልጿል። በ2018 ዓ.ም የክረምት ስልጠናውን ለመስጠት ስምንት አሰልጣኝ ዩኒቨርሲቲዎች መመረጣቸውን ሚኒስቴሩ አሳውቋል። ለክረምት ስልጠናው የተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች፦ 1. ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ 2. ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ 3. ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ 4. መቐለ ዩኒቨርሲቲ 5. ጅማ ዩኒቨርሲቲ 6. ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ 7. ጎንደር ዩኒቨርሲቲ 8. አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተቋማት እና የስልጠናው አሰጣጥ አግባብነት ከትምህርት ሚኒስቴር እስከሚገለጽ ድረስ ከላይ ከተገለፁት ዩኒቨርሲቲዎች በስተቀር በክረምት መምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና መስጠት የማይቻል መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳስቧል። ከ2011 ዓ.ም በፊት ስልጠና ጀምረው ያላጠናቀቁ መምህራን ከዚህ በፊት በተሰጠው ውሳኔ መሰረት እንዲያጠናቅቁ እንዲደረግ በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ ተፈርሞ ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተላከው ደብዳቤ ይገልጻል።
3 282