ch
Feedback
Ethio - ዜና 🇪🇹

Ethio - ዜና 🇪🇹

前往频道在 Telegram

የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot

显示更多

📈 Telegram 频道 Ethio - ዜና 🇪🇹 的分析概览

频道 Ethio - ዜና 🇪🇹 (@ethio_zena23) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 106 106 名订阅者,在 图片 类别中位列第 72,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 272

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 106 106 名订阅者。

根据 12 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -2 802,过去 24 小时变化为 -68,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 3.42%。内容发布后 24 小时内通常能获得 2.32% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 637 次浏览,首日通常累积 2 469 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 28

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot

凭借高频更新(最新数据采集于 13 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 图片 类别中的关键影响点。

106 106
订阅者
-6824 小时
-6617
-2 80230

数据加载中...

标签云
无数据
有任何问题?请刷新页面或联系我们的客服
进出提及
---
---
---
---
---
---
吸引订阅者
七月 '26
七月 '260
在2个频道中
六月 '26
+64
在9个频道中
Get PRO
五月 '26
+129
在11个频道中
Get PRO
四月 '26
+74
在12个频道中
Get PRO
三月 '26
+2 127
在10个频道中
Get PRO
二月 '26
+8
在4个频道中
Get PRO
一月 '26
+2 108
在54个频道中
Get PRO
十二月 '25
+2 159
在81个频道中
Get PRO
十一月 '25
+4 183
在51个频道中
Get PRO
十月 '25
+4 892
在3个频道中
Get PRO
九月 '25
+7 709
在3个频道中
Get PRO
八月 '25
+5 654
在1个频道中
Get PRO
七月 '25
+6 591
在2个频道中
Get PRO
六月 '25
+6 975
在0个频道中
Get PRO
五月 '25
+7 406
在1个频道中
Get PRO
四月 '25
+7 575
在1个频道中
Get PRO
三月 '25
+8 127
在1个频道中
Get PRO
二月 '25
+7 065
在3个频道中
Get PRO
一月 '25
+7 127
在1个频道中
Get PRO
十二月 '24
+9 050
在4个频道中
Get PRO
十一月 '24
+11 169
在2个频道中
Get PRO
十月 '24
+14 487
在4个频道中
Get PRO
九月 '24
+12 613
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+11 528
在5个频道中
Get PRO
七月 '24
+4 340
在29个频道中
Get PRO
六月 '24
+871
在5个频道中
Get PRO
五月 '24
+1 669
在5个频道中
Get PRO
四月 '24
+1 824
在7个频道中
Get PRO
三月 '24
+3 958
在6个频道中
Get PRO
二月 '24
+1 530
在2个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
13 七月0
12 七月0
11 七月0
10 七月0
09 七月0
08 七月0
07 七月0
06 七月0
05 七月0
04 七月0
03 七月0
02 七月0
01 七月0
频道帖子
የባንኮች የማበደር ገደብ ተነሳ‼ የብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ (ቁጥር 7) ስብሰባ ዋና ዋና ውሳኔዎችና የኢኮኖሚ አፈጻጸም አጭር መግለጫ:- ፩. ዋና ዋና የፖሊሲ ውሳኔዎች 📌የብድር ገደብ
የባንኮች የማበደር ገደብ ተነሳ‼ የብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ (ቁጥር 7) ስብሰባ ዋና ዋና ውሳኔዎችና የኢኮኖሚ አፈጻጸም አጭር መግለጫ:- ፩. ዋና ዋና የፖሊሲ ውሳኔዎች 📌የብድር ገደብ መነሳት፦ በባንኮች ላይ ተጥሎ የነበረው የዓመታዊ የብድር ዕድገት ገደብ (Credit Cap) ሙሉ በሙሉ እንዲነሳ ተወስኗል። 📌 የፖሊሲ ወለድ ምጣኔ ማሻሻያ፦ የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ወለድ ምጣኔ (Policy Rate) በ1.0 በመቶ ነጥብ ከፍ በማለት ከ15 በመቶ ወደ 16 በመቶ እንዲያድግ ተደርጓል። 📌 የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ግዴታ (FX Surrender)፦ ላኪዎችና የውጭ ምንዛሬ አስገኚዎች ለባንኮች ገቢ የሚያደርጉት የውጭ ምንዛሬ ግዴታ ከ50 በመቶ ወደ 30 በመቶ ዝቅ እንዲል ተወስኗል። 📌 የኮሚሽን ምጣኔ ቅነሳ፦ ባንኮች ከውጭ ምንዛሬ ግዢ ጋር ተያይዞ የሚያስከፍሉት የኮሚሽን ምጣኔ ከ2.5 በመቶ ወደ 1.5 በመቶ እንዲቀንስ ተደርጓል።    ፪. የኢኮኖሚ አፈጻጸም ማጠቃለያ 📌 የኢኮኖሚ ዕድገት፦ በ2017 በጀት ዓመት አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ዕድገት 9.2 በመቶ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል። 📌የዋጋ ግሽበት፦ አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት በሰኔ ወር 2018 ዓ.ም. ወደ 13.4 በመቶ ዝቅ ብሏል። 📌 የበጀት ጉድለት፦ የአገሪቱ የበጀት ጉድለት ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) አንጻር ወደ 0.9 በመቶ ወርዷል። 📌 የውጭ ኢኮኖሚ ክምችት፦ አጠቃላይ የውጭ ክፍያ ሚዛን ትርፍ ያስመዘገበ ሲሆን፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ማሻሻያው ከመደረጉ በፊት ከነበረው አንጻር በ20 እጥፍ አድጓል። ‎ @Seledadotio @Seledadotio

2
የነዳጅ ዋጋ 4 በመቶ ጨመረ የአሜሪካ እና ኢራን ግጭት ማገርሸቱን ተከትሎ የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዘይት ዋጋ ጭማሪ አሳይቷል። በዓለማቀፍ ደረጃ 3.9% በመጨመር 78.96 ዶላር የገባ ሲሆን በአሜሪካ
የነዳጅ ዋጋ 4 በመቶ ጨመረ የአሜሪካ እና ኢራን ግጭት ማገርሸቱን ተከትሎ የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዘይት ዋጋ ጭማሪ አሳይቷል። በዓለማቀፍ ደረጃ 3.9% በመጨመር 78.96 ዶላር የገባ ሲሆን በአሜሪካ የነዳጅ ገበያው 4% በመጨመር 74.26 ዶላር መግባቱ ተገልጿል። ሁለቱ ሀገራት ግጭቱን ለማቆም እና የሆርሙዝ ሰርጥን በመክፈት የንግድ መርከቦች እንዲንቀሳቀሱ ለማድረግ የተደረገው ስምምነት እክል ገጥሞታል። በትናንትናው እለት አሜሪካ በኢራን የነዳጅ ማደያዎች ላይ ጥቃት ያደረሰች ሲሆን፣ ኢራንም በሰርጡ በሚያልፉ መርከቦች ላይ ጥቃት ማድረሷን አስታውቃለች። በተጨማሪ የኢራን አብዮታዊ ዘብ በጎረቤት ሀገራት ኩዌት፣ ባህሬን እና ጆርዳን ላይ የአሜሪካን ወታደራዊ ስፍራ ኢላማ ያደረገ ጥቃት ፈጽሟል። @Seledadotio @Seledadotio
1 575
3
በሳውዲ እስር ላይ ለነበሩ 1,971 ኢትዮጵያውያን ምሕረት ተደረገላቸው‼ ​ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ፣ በሳዑዲ አረቢያ በሕግ ሂደትና አስገዳጅ እርምጃዎች
በሳውዲ እስር ላይ ለነበሩ 1,971 ኢትዮጵያውያን ምሕረት ተደረገላቸው‼ ​ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ፣ በሳዑዲ አረቢያ በሕግ ሂደትና አስገዳጅ እርምጃዎች ውስጥ የነበሩ 1,971 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ባለሥልጣናት የንጉሣዊ ምሕረት አዋጅ (Royal Amnesties) ተጠቃሚ መሆናቸውን አስታወቀ። ​በሪያድ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲና በጅዳ ከሚገኘው ቆንስላ ጄኔራል ጋር በመተባበር የተደረጉት ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች አዎንታዊ ውጤት ማምጣታቸውን የገለጸው ሚኒስቴሩ፣ በምሕረቱ የተካተቱ ዜጎችን ወደ ሀገር ለመመለስ የሚያስችሉ ሥራዎች መጀመራቸውን ጠቁሟል። የኢትዮጵያ መንግሥት በውጭ ሀገራት የሚገኙ ዜጎቹን ደኅንነትና መብት ለማስጠበቅ ከሳዑዲ ባለሥልጣናት ጋር የሚያደርገውን ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ንግግር አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጧል። @Seledadotio @Seledadotio
1 931
4
በቦሌ አትላስ አካባቢ በጣለው ከባድ ዝናብና ንፋስ በአንድ ተሽከርካሪ ላይ ጉዳት ደረሰ በትናንትናው ዕለት ከላይ በቪዲዮ እንደምትመለከቱት በአስደንጋጭ ሁኔታበዋና ከተማዋ ቦሌ አትላስ ተብሎ በሚጠራው
በቦሌ አትላስ አካባቢ በጣለው ከባድ ዝናብና ንፋስ በአንድ ተሽከርካሪ ላይ ጉዳት ደረሰ በትናንትናው ዕለት ከላይ በቪዲዮ እንደምትመለከቱት በአስደንጋጭ ሁኔታበዋና ከተማዋ ቦሌ አትላስ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በጣለው ኃይለኛ ዝናብ እና በነፈሰው ብርቱ ንፋስ ምክንያት... ከአንድ የግንባታ ቦታ ላይ የብረት ቁሳቁሶች ተፈንቅለው በመውደቃቸው በአቅራቢያው በነበረ ዘመናዊ መኪና ላይ ጉዳት ማድረሳቸው ታውቋል። ምንም እንኳን በንብረት ላይ አደጋው ጉዳት ቢያስከትልም፣ በአምላክ ምስጋና ይግባና በአደጋው ወቅት በሰው ሕይወትም ሆነ አካል ላይ የደረሰ ምንም ዓይነት ጉዳት እንደሌለ ተረጋግጧል። @Seledadotio @Seledadotio
2 232
5
" አትገቡም !! " ግብረሰዶማውያንን የጫነችው የቅንጦት መርከብ በቱርክና ግብፅ ወደቦች እንዳትገባ ተከለከለች። ከሰሞኑን " አትላንቲስ ኢቨንትስ " በተባለ የአሜሪካ የጉዞ ድርጅት የተከራየችና 2,0+1
" አትገቡም !! " ግብረሰዶማውያንን የጫነችው የቅንጦት መርከብ በቱርክና ግብፅ ወደቦች እንዳትገባ ተከለከለች። ከሰሞኑን " አትላንቲስ ኢቨንትስ " በተባለ የአሜሪካ የጉዞ ድርጅት የተከራየችና 2,000 ገደማ ግብረሰዶማውያንን የጫነች " ስካርሌት ሌዲ " የተሰኘች የሜዲትራኒያን ባህር የቅንጦት መርከብ ወደ ቱርክ እና ግብፅ ወደቦች እንዳትገባ ተከልክላለች። መርከቧ በቱርክ ኩሻዳሲ እና ኢስታንቡል ወደቦች እንዳታርፍ የተከለከለች ሲሆን፣ የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ውሳኔው የጉዞው ዓላማ ከሀገሪቱ ሞራላዊና ሥነ-ምግባራዊ እሴቶች እንዲሁም ማኅበራዊ ደንቦችና እሴቶች ጋር ስለማይጣጣም መሆኑን ገልጸዋል። የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሪች ካምቤል በኩባንያው 36 ዓመታት ታሪክ ውስጥ እንዲህ ያለው ንገረ ሲገጥማቸው የመጀመሪያ እንደሆነ ገልጸዋል። መርከቧ ከቱርክ እገዳ በኋላ የጉዞ አቅጣጫዋን ወደ እስክንድርያ ግብፅ ብታዞርም፣ የግብፅ ባለሥልጣናትም መርከቧ ወደ ሀገሪቱ የባህር ክልል እንዳትገባ አግደዋታል። ግብፅ ለእገዳው የሰጠችው ይፋዊ ማብራሪያ ባይኖርም፣ ድርጅቱ ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጉዞ በተሳካ ሁኔታ ማድረጉን አስታውሶ በውሳኔው መደነቁን ገልጿል። በእነዚህ እገዳዎች ምክንያት ተሳፋሪዎች በግብፅ ሊያደርጓቸው የነበሩት የፒራሚድ እና የታሪክ ስፍራዎች ጉብኝቶች የተሰረዙ ሲሆን፣ መርከቧ መስመሯን ቀይራ ወደ ክሬት ግሪክ እና ኮቶር ሞንቴኔግሮ ለማምራት ተገድዳለች። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23
2 177
6
የዓለም ባንክ በቀጣዮቹ 10 ዓመታት በኢትዮጵያ ለሚያከናውናቸው ድጋፎች የፖሊሲ ለውጦች አደረገ የዓለም ባንክ ከ2027 እስከ 2036 ያለውን የ10 ዓመታት የአጋርነት ማዕቀፍ ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ በሚ
የዓለም ባንክ በቀጣዮቹ 10 ዓመታት በኢትዮጵያ ለሚያከናውናቸው ድጋፎች የፖሊሲ ለውጦች አደረገ የዓለም ባንክ ከ2027 እስከ 2036 ያለውን የ10 ዓመታት የአጋርነት ማዕቀፍ ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ በሚቀጥሉት 10ዓመታት ቅድሚያ ይሰጣቸው የነበሩ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን ሙሉ በሙሉ ከዕቅዱ ውጪ ማድረጉን አስታወቀ፡፡ ሪፖርተር የተመለከተው የዓለም ባንክ አዲስ የስትራቴጂ ሰነድ ትኩረቱን በዋናነት በየዓመቱ ወደ ሥራው ዓለም ለሚቀላቀሉ ወደ ሁለት ሚሊዮን ገደማ የሚሆኑ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር ላይ አድርጓል፡፡ ግዙፍ በመንግሥት የሚመሩ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን፣ ዋና ዋና የአስፋልት መንገዶችንና የቱሪዝም ዘርፍን በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ሙሉ በሙሉ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ፕሮጀክቶች ዝርዝር ውጪ አድርጓቸዋል፡፡ 👉የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ከዕቅዱ ውጪ እንዲሆኑ የተደረጉት ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ባደረገችው ኢንቨስትመንት በቂ የማመንጨት አቅም ስላላት ሲሆን፣ የቱሪዝም ዘርፍ ደግሞ በኢትዮጵያ ያለው የፀጥታና የመሠረተ ልማት ሁኔታ መሻሻል እስከሚታይበት ድረስ ከዝርዝሩ ውጪ እንዲሆን መደረጉን ጠቁሟል፡፡ የከተማ አውራ ጎዳናዎችን የመገንባት ዕቅድም ቀርቶ፣ በተመሳሳይ መልኩ የገጠር መንገዶችን ወደ ማስፋፋት እንዲዞር የተደረገ ሲሆን፣ ይህም አርሶአደሩ ምርቱን በቀላሉ ወደ ገበያ እንዲያቀርብ ለማገዝ፣ የጉምሩክ አሠራርን ለማዘመንና የወጪ ንግድ ወጪን ለመቀነስ ያለመ አዲስ መዋቅራዊ አቅጣጫ መሆኑ ተመልክቷል። 👉ባንኩ በቀጣይ እቅዶቹ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ ማስተካከል፣ የኃይል መቆራረጥን መቀነስና በሚሊዮኖች ለሚቆጠር ሕዝብ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን አስተማማኝ ማድረግ የሚሉት ይገኙበታል፡፡ https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23
2 063
7
የሀይል ስርቆትን በተመለከተ ጥቆማ ለሚሰጥ  ከተጣለው ቅጣት የ25 በመቶ ኮሚሽን እንደሚያገኝ ተገለፀ ሀምሌ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. (አሐዱ ሬዲዮ)፦ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚፈጸሙ የኤሌክትሪክ ሀይል ስርቆትን ለመግታት እና በመሰረተ ልማት ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን ለመከላከል የተቀናጀ የቁጥጥር ስራ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል ። በአገልግሎቱ የሽያጭና የደንበኞች አገልግሎት  ዳይሬክተር አቶ ይሔይስ ስዩም የሀይል ስርቆቱ በዋናነት የኤሌክትሪክ ቆጣሪዎች በትክክል እንዳይቆጥሩ በማድረግ ወይም መስመር ወደ ቆጣሪው ከመግባቱ በፊት በቀጥታ በመጥለፍ ወደ መኖሪያ ቤቶችና የኢንዱስትሪ ማሽኖች በመውሰድ እንደሚፈጸም ተናግረዋል ። በ2017 በጀት ዓመት በተደረገው ከፍተኛ ክትትልና የቁጥጥር ስራ፣ የሃይል ስርቆት ጨምሮ ከባከነ ሃይል 259 ሚሊዮን ብር መሰብሰብ መቻሉንም ተናግረዋል። የኤሌክትሪክ ሃይል ስርቆትን በዘላቂነት ለመከላከል ህብረተሰቡ ጥቆማ እንዲሰጥ የተደራጀ የአሰራር ስርዓት፣ ፖሊሲና መመሪያ ተቀርጾ ወደ ስራ መገባቱን  ጠቁመዋል ። በዚህም መሰረት የሃይል ስርቆት ለሚጠቁሙ ደንበኞች ከተጣለው ቅጣት ላይ የ25 በመቶ ኮሚሽን ክፍያ ተግባራዊ መደረግ መጀመሩ አስረድተዋል ። ለአብነትም አንድ ከፍተኛ ኢንዱስትሪ በፈጸመው የቴክኒክ ስርቆት ምክንያት አንድ ሚሊዮን ብር ቢቀጣ፣ ጥቆማውን ያቀረበው ግለሰብ  የ250 ሺህ ብር የገንዘብ ማበረታቻ በህጋዊ አሰራር ያገኛል። የኤሌክትሪክ ኔትወርክ መሰረተ ልማት የጋራ ሀብት በመሆኑ ፣ የሃይል ስርቆት የሚፈጽሙ አካላትን በማጋለጥ ረገድ ህብረተሰቡ የበኩሉን ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪ ቀርቧል።
2 535
8
የሀይል ስርቆትን በተመለከተ ጥቆማ ለሚሰጥ  ከተጣለው ቅጣት የ25 በመቶ ኮሚሽን እንደሚያገኝ ተገለፀ ሀምሌ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. (አሐዱ ሬዲዮ)፦ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚፈጸሙ የኤሌክትሪክ ሀይል ስርቆትን ለመግታት እና በመሰረተ ልማት ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን ለመከላከል የተቀናጀ የቁጥጥር ስራ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል ። በአገልግሎቱ የሽያጭና የደንበኞች አገልግሎት  ዳይሬክተር አቶ ይሔይስ ስዩም የሀይል ስርቆቱ በዋናነት የኤሌክትሪክ ቆጣሪዎች በትክክል እንዳይቆጥሩ በማድረግ ወይም መስመር ወደ ቆጣሪው ከመግባቱ በፊት በቀጥታ በመጥለፍ ወደ መኖሪያ ቤቶችና የኢንዱስትሪ ማሽኖች በመውሰድ እንደሚፈጸም ተናግረዋል ። በ2017 በጀት ዓመት በተደረገው ከፍተኛ ክትትልና የቁጥጥር ስራ፣ የሃይል ስርቆት ጨምሮ ከባከነ ሃይል 259 ሚሊዮን ብር መሰብሰብ መቻሉንም ተናግረዋል። የኤሌክትሪክ ሃይል ስርቆትን በዘላቂነት ለመከላከል ህብረተሰቡ ጥቆማ እንዲሰጥ የተደራጀ የአሰራር ስርዓት፣ ፖሊሲና መመሪያ ተቀርጾ ወደ ስራ መገባቱን  ጠቁመዋል ። በዚህም መሰረት የሃይል ስርቆት ለሚጠቁሙ ደንበኞች ከተጣለው ቅጣት ላይ የ25 በመቶ ኮሚሽን ክፍያ ተግባራዊ መደረግ መጀመሩ አስረድተዋል ። ለአብነትም አንድ ከፍተኛ ኢንዱስትሪ በፈጸመው የቴክኒክ ስርቆት ምክንያት አንድ ሚሊዮን ብር ቢቀጣ፣ ጥቆማውን ያቀረበው ግለሰብ  የ250 ሺህ ብር የገንዘብ ማበረታቻ በህጋዊ አሰራር ያገኛል። የኤሌክትሪክ ኔትወርክ መሰረተ ልማት የጋራ ሀብት በመሆኑ ፣ የሃይል ስርቆት የሚፈጽሙ አካላትን በማጋለጥ ረገድ ህብረተሰቡ የበኩሉን ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪ ቀርቧል። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23
1
9
ቁፋሮ ማካሄድ ተከለከለ‼️ የአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን በከተማዋ ክልል ውስጥ የሚካሄደውን የኮንስትራክሽን ማዕድናት ፍለጋ፣ ምርት እና ስርጭት ሥርዓት ለማስያዝና ለመቆጣጠር የሚያስች
ቁፋሮ ማካሄድ ተከለከለ‼️ የአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን በከተማዋ ክልል ውስጥ የሚካሄደውን የኮንስትራክሽን ማዕድናት ፍለጋ፣ ምርት እና ስርጭት ሥርዓት ለማስያዝና ለመቆጣጠር የሚያስችል አዲስ መመሪያ አውጥቷል። በመመሪያው መሠረት የኅብረተሰቡን ደኅንነትና የተፈጥሮ ሀብትን ለመጠበቅ፦ 🛑የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶችን ከአደጋ ለመጠበቅ ሲባል ከከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች በ25 ሜትር ራዲየስ ውስጥ፣ 🛑ከመኖሪያ መንደሮችና ከኢንዱስትሪ ፓርኮች በ500 ሜትር ራዲየስ ውስጥ፣ 🛑ከወንዝ ዳርቻዎች በ30 ሜትር ራዲየስ ውስጥ ማንኛውንም ዓይነት ቁፋሮ ማካሄድ ሙሉ በሙሉ የተከለከለ ነው። "የኮንስትራክሽን ማዕድን ፈቃድ አፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 191/2018" በሚል ተግባራዊ እንዲሆን የፀደቀው ይህ መመሪያ፤ ከማዕድን ቁፋሮ ጋር በተያያዘ በከተማዋ ይታዩ የነበሩ የአሠራር ክፍተቶችን በመድፈን ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት ሥርዓት ለመዘርጋት ያለመ መሆኑ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። @Seledadotio @Seledadotio
2 814
10
“ለሻዕቢያ ከምገረድ፣ ለብልጽግና ብንበረከክ እመርጣለሁ”‼️ የቀድሞዋ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም መጠይቅ፣ ከህወሓት ጋር ተድርጎ ለሻዕቢያ ከመገረድ በብልጽግና አንገት መድፋት ይ
“ለሻዕቢያ ከምገረድ፣ ለብልጽግና ብንበረከክ እመርጣለሁ”‼️ የቀድሞዋ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም መጠይቅ፣ ከህወሓት ጋር ተድርጎ ለሻዕቢያ ከመገረድ በብልጽግና አንገት መድፋት ይሻለኛል ብለዋል፡፡ ኬሪያ ከፋና ቲቪ ጋር ባደረጉት ቃለ ትግራይን በበላይ የተቆጣጠሩትን እነ ደብረጽዮን ገ/ሚካኤልን የትግራይን ሕዝብ ለሻዕቢያ አሳልፈው በመስጠት ወንጅለዋል፡፡ ኬሪያ የቀድሞ ድርጅታቸው ህወሓት ትግራይን ለማጥፋት ይመኛል ላሉት ሻዕቢያ “ተላላኪ ሆኖ እየተገረደ” ነው ብለዋል፡፡ ህወሓት “የብልጽግና ተንበርካኪ መሆን የለብንም ነው የሚለን” ያሉት ኬሪያ፣ “ለሻዕቢያ ከምገረድ እዚህ ብንበረከክ ነው የምመርጠው” ብለዋል፡፡ @Seledadotio @Seledadotio
2 792
11
የማይሞተው ብቸኛው የምድር ፍጡር እርጅናን በመቀልበስ የሕይወት ዑደቱን ወደ ሕፃንነት በመመለስ ለዘላለም መኖር የሚችል “የማይሞት” አስገራሚ ፍጡር በባሕር ጥልቀት ውስጥ መገኘቱ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስ+3
የማይሞተው ብቸኛው የምድር ፍጡር እርጅናን በመቀልበስ የሕይወት ዑደቱን ወደ ሕፃንነት በመመለስ ለዘላለም መኖር የሚችል “የማይሞት” አስገራሚ ፍጡር በባሕር ጥልቀት ውስጥ መገኘቱ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶችን አስደምሟል። “ቱሪቶፕሲስ ዶርኒ” (Turritopsis dohrnii) የተባለውና በጣም አነስተኛ መጠን ያለው ይህ የጄሊፊሽ (Jellyfish) ዝርያ በሕይወት ዘመኑ ላይ አደጋ፣ በሽታ ወይም እርጅና ሲደቅንበት የራሱን ሴሎች ሙሉ በሙሉ በማደስ ወደ መጀመሪያው የፅንስ (Polyp) ደረጃ የመመለስ አስደናቂ የተፈጥሮ ብቃት አለው። ይህ ማለት ፍጡሩ ሲያረጅ ከመሞት ይልቅ ልክ እንደገና ተወልዶ ወደ ሕፃንነቱ ይመለሳል፤ ይህንን ሂደት ደግሞ ሳይሞት ለዘላለም ደጋግሞ ማከናወን ይችላል። ተመራማሪዎች የዚህን ፍጡር የዲኤንኤ (DNA) ምስጢር ለመፍታት ሌሊትና ቀን እየሠሩ የሚገኙ ሲሆን፣ ግኝቱ ለሰው ልጅ የእርጅና መከላከያ እና የካንሰር ሕክምና ምርምር ትልቅ ተስፋን የፈነጠቀ በመሆኑ በማኅበራዊ ሚዲያና በሳይንሱ ዓለም ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል። @Seledadotio @Seledadotio
2 855
12
ሞጅታባ ኻሜኒ የአባታቸውን ግድያ ለመበቀል ቃል ገብተዋል❗️ የኢራን አዲሱ የበላይ መሪ አያቶላ ሞጅታባ ኻሜኒ የተገደሉትን አባታቸውን አሊ ኻሜኒን ደም መበቀል የመላው የኢራን ሕዝብ ፍላጎት በመሆኑ የ
ሞጅታባ ኻሜኒ የአባታቸውን ግድያ ለመበቀል ቃል ገብተዋል❗️ የኢራን አዲሱ የበላይ መሪ አያቶላ ሞጅታባ ኻሜኒ የተገደሉትን አባታቸውን አሊ ኻሜኒን ደም መበቀል የመላው የኢራን ሕዝብ ፍላጎት በመሆኑ የአጸፋው ርምጃ እንደሚወሰድ አስታወቁ። 👉ሞጅታባ ኻሜኒ የአባታቸው ሥርዓተ ቀብር መፈጸሙን ተከትሎ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ካለአግባብ የንጹሃንን ህይወት የቀጠፉ ወንጀለኛና ክብር የለሽ ነፍሰ ገዳዮችን ለመበቀል ቃል እንገባለን ብለዋል። ለሳምንት ያህል ሲካሄድ የቆየው የሽኝት ሥነ ስርዓት ተጠናቅቆ የኢራን የቀድሞው መሪ ሥርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል። 👉አሜሪካና እስራኤል በኢራን ላይ በሰነዘሩት ጥቃት አሊ ኻሜኒ መገደላቸውን ተከትሎ ኢራን ተከታታይ የአጸፋ ርምጃዎችን መውሰዷ ይታወሳል። በሌላ በኩል ኢራን የአሜሪካውን ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕን ለመግደል አዲስ እቅድ ማውጣቷን የሚያሳዩ መረጃዎች ደርሶኛል ስትል እስራኤል በቅርቡ ለአሜሪካ የደህንነት መረጃ ማጋራቷን ተገልጿል። ይህንን ተከትሎ ፕሬዚዳንት ትራምፕ በማህበራዊ ትሰስር ገጻቸው በኩል ኢራን በእሳቸው ላይ የግድያ ሙከራ ካደረገች በሺዎች የሚቆጠሩ ሚሳኤሎችን በኢራን ላይ እንደሚተኩሱ ማስጠንቀቃቸውን የዘገበው አናዶሉ ነው። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23
2 772
13
አሜሪካ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ለስድስት አገራት ዜጎች የተሰጠውን በአሜሪካ የመቆየትና የመሥራት ጊዜያዊ ሕጋዊ ከለላ ለተጨማሪ ቀናት አራዘመ። በአሜሪካ የአገር ውስጥ ደሕንነት መሥሪያ ቤት ሥር የሚገኘ
አሜሪካ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ለስድስት አገራት ዜጎች የተሰጠውን በአሜሪካ የመቆየትና የመሥራት ጊዜያዊ ሕጋዊ ከለላ ለተጨማሪ ቀናት አራዘመ።  በአሜሪካ የአገር ውስጥ ደሕንነት መሥሪያ ቤት ሥር የሚገኘው የዜግነትና የፍልሰት አገልግሎት በአገሪቱ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን የተሰጠው ከለላ በመጪው ሐምሌ 10 ቀን 2018 እንደሚያበቃ ትላንት አርብ አስታውቋል። ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ለሶርያ፣ ሶማሊያ፣ የመን፣ ደቡብ ሱዳን እና ምያንማር ዜጎች የተሰጠው ጊዜያዊ ከለላ በተመሣሣይ ቀን ያበቃል።  ውሳኔው የሚመለከታቸው የሔቲ ዜጎች ከቀሪዎቹ አምስት አገራት አንድ ሳምንት ቀደም ብሎ በአሜሪካ ለመቆየትና ለመሥራት የሚፈቅድላቸውን ከለላ ያጣሉ። ይህ ከለላ የተፈጥሮ አደጋ፣ የትጥቅ ግጭት ወይም ሌሎች ያልተለመዱ አስገዳጅ ሁኔታዎች ከገጠማቸው አገራት ወደ አሜሪካ የገቡ ሰዎች በአገሪቱ እንዲቆዩ እና በሕጋዊ መንገድ እንዲሠሩ የሚፈቅ ነው።  ከለላው የተሰጣቸው በአሜሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው ቢመለሱ “በግል ደሕንነታቸው ብርቱ ሥጋት አይገጥማቸውም” በሚል አመክንዮ በአገሪቱ የመቆየትና የመሥራት ዕድላቸው እንዲያበቃ የተወሰነው ባለፈው ታኅሳስ 2018 ነበር። 
2 840
14
#እንዲያውቁት‼️ የኪራይ ውል ማሻሻያው ለ2 ዓመታት ጸንቶ ይቆያል። 11.5 በመቶ ሆኖ የጸደቀዉ በአዲስ አበባ የ2019 በጀት ዓመት የቤት #ኪራይ ዓመታዊ የጭማሪ ጣሪያ ለ2 ዓመታት የሚቆይ ሲሆን ከ
#እንዲያውቁት‼️ የኪራይ ውል ማሻሻያው ለ2 ዓመታት ጸንቶ ይቆያል። 11.5 በመቶ ሆኖ የጸደቀዉ በአዲስ አበባ የ2019 በጀት ዓመት የቤት #ኪራይ ዓመታዊ የጭማሪ ጣሪያ ለ2 ዓመታት የሚቆይ ሲሆን ከዚህ ተመን በላይ መጨመር በጥብቅ የተከለከለ ነው ሲል የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታውቋል። 📣ከህጋዊ አሰራር ውጪ የሚደረጉ "የመንደር ውሎች" የተከለከሉ ሲሆን ውል በማያድሱና ህግ በሚተላለፉ አካላት ላይ ቅጣት ይጣላል። የውል እድሳት ጊዜያቸው አልፎ አከራይም ተከራይም አብረው ኖረው እድሳት ሳይፈጽሙ የተገኙ፦ 💸እስከ 2 ወር ከቆዩ የ1 ወር የቤት ኪራይ፣ 💸3 ወር እና ከዚያ በላይ የቆዩ የ2 ወር የቤት ኪራይ ቅጣት ይከፍላሉ። 💸አዲስ ተከራይ አስገብተው ውል ያላደሱ እና ያላስመዘገቡ የ1 ወር የቤት ኪራይ ይቀጣሉ። 💸በጥቆማ ወይም በክትትል ውል ያላደሱ ወይም ያላስመዘገቡ መሆናቸው ከተረጋገጠ ደግሞ ከ1 እስከ 3 ወር የሚደርስ የኪራይ መጠን ቅጣት እንደሚጣልባቸው ቢሮው አሳውቋል። ‎
2 988
15
በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ጭልጋ ወረዳ ሰራቆ ቀበሌ በግ ሰር'ቆ ሲያ'ርድ በህብረተሰቡና በፀጥታ ሀይሎች ትብብር በቁጥጥር ስር የዋለው ሌባ መቀጣጫ ሆነ። ሰ'ርቆ በመግፈፍ ላይ የነበረውን በግ ተሸክ+1
በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ጭልጋ ወረዳ ሰራቆ ቀበሌ በግ ሰር'ቆ ሲያ'ርድ በህብረተሰቡና በፀጥታ ሀይሎች ትብብር በቁጥጥር ስር የዋለው ሌባ መቀጣጫ ሆነ። ሰ'ርቆ በመግፈፍ ላይ የነበረውን በግ ተሸክ'ሞ ከተማውን እንዲዞር ተደርጓል። @Seledadotio @Seledadotio
2 898
16
ስፔን ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቅላለች:: ስፔን 2 - 1 ቤልጅየም ግማሽ ፍፃሜ ፈረንሳይ ከ ስፔን! @Addis_News @Addis_News
ስፔን ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቅላለች:: ስፔን 2 - 1 ቤልጅየም ግማሽ ፍፃሜ ፈረንሳይ ከ ስፔን! @Addis_News @Addis_News
2 966
17
ኢትዮጵያ ለኢቦላ ወረርሽኝ የመጋለጥ እድሏ ከፍተኛ ነው ተባለ ዓለማቀፉ የፍልሠት ድርጅት ኢትዮጵያ ለበሽታው ከመጋለጥ አንጻር በከፍተኛ ደረጃ "ቅድሚያ" ከሚሠጣቸው አገራት መካከል አንዷ መኾኗን ሰሞኑ
ኢትዮጵያ ለኢቦላ ወረርሽኝ የመጋለጥ እድሏ ከፍተኛ ነው ተባለ ዓለማቀፉ የፍልሠት ድርጅት ኢትዮጵያ ለበሽታው ከመጋለጥ አንጻር በከፍተኛ ደረጃ "ቅድሚያ" ከሚሠጣቸው አገራት መካከል አንዷ መኾኗን ሰሞኑን ባወጣው ሪፖርት ላይ ገልጿል። ድርጅቱ ኢትዮጵያ ለበሽታው በከፍተኛ ደረጃ ተጋላጭ መኾኗን የገለጠው፣ ዓለማቀፍ ተጓዦች በብዛት የሚያልፉባት፣ ድንበር ተሻጋሪ የንግድና የመጓጓዣ ኮሪደሮች ያሉባትና በሽታው ከተከሠተባቸው አካባቢዎች ጋር ያላት ድንበር ክፍተት ያለበት መኾኑን በመጥቀስ ነው። በድርጅቱ ሪፖርት መሠረት፣ ቦሌ ዓለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ የድሬዳዋ፣ መቀሌ እና የባሕርዳር አውሮፕላን ማረፊያዎች፤ የሞያሌ፣ መተማ፣ ጋላፊ፣ ደዋሌ፣ ፓጋክ እና ኩርሙክ የድንበር መግቢያና መውጫዎች እንዲሁም የድሬዳዋ የባቡር ጣቢያ ቅድሚያ ትኩረት የሚሠጣቸው ቦታዎች ናቸው። ድርጅቱ፣ ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ ቀንድ፣ ምሥራቅና ደቡባዊ አፍሪካ ለ12 አገሮች በሽታውን ለመከላከልና ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የ55 ነጥብ 9 ሚሊዮን ዶላር እቅድ የነደፈ ሲኾን፣ ከድጋፉ ውስጥ 4 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላሩ የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓትና በድንበርናና ኮሪደሮች አካባቢ የጤና ተቋማትን ለማጠናከር እንደሚውል ገልጧል።
3 057
18
እንደገና ፈተና አለ‼️ ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 2015 ዓ.ም በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በሁለተኛ እና በሦስተኛ ዲግሪ የተመረቃችሁ ወይም የመውጫ ፈተና ሳትፈተኑ የዲግሪ ባለቤት የሆናችሁ በሙሉ እንደገና+3
እንደገና ፈተና አለ‼️ ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 2015 ዓ.ም በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በሁለተኛ እና በሦስተኛ ዲግሪ የተመረቃችሁ ወይም የመውጫ ፈተና ሳትፈተኑ የዲግሪ ባለቤት የሆናችሁ በሙሉ እንደገና የትምህርት ማስረጃችሁን ለማረጋገጥ ሲባል ሊፈተኑ ነው ተብሏል። በጉዳዩ ላይ አስተያየት ለመስጠት በኢፌዴሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የፌስቡክ ገጽ ላይ በተለቀቀው ሊንክ እየገባችሁ መሙላት ትችላላችሁ። @Seledadotio @Seledadotio
3 361
19
የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ በመምሰል የማታለል (በተለምዶ ሿሿ) ተብሎ የሚጠራውን ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ 9 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ። ተጠርጣሪዎቹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት ሰኔ 28
የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ በመምሰል የማታለል (በተለምዶ ሿሿ) ተብሎ የሚጠራውን ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ 9 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ። ተጠርጣሪዎቹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ/ም ከጥዋቱ 1:40 በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ሪቼ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ነው። የግል ተበዳይ ከአጎና ወደ እስታዲየም ለመሄድ በማሰብ ኮድ 3-83620 ኦሮ ነጭ ሚኒባስ ተሽከርካሪ በማስቆም ትገባለች። ተጠርጣሪዎችም የግለሰቧን ወደ ተሽከርካሪው መግባት ተከትለው በማዋከብ እና ትኩረቷን በማሳጣት ይዛው ከነበረው ቦርሳ ውስጥ 32 ሺ ብር ግምት ያለው ሳምሰንግ ስልክ ሰርቀው ጥለዋት ይሄዳሉ። ይህን የተመለከቱ የትራፊክ ፖሊሶች ተሽከርካሪውን በማስቆም እና ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር የማዋል ስራ ሰርተዋል። ተጠርጣሪዎቹ ከተያዙ በኋላ በተሽከርካሪው ውስጥ በተደረገ ፍተሻ 7 ስልኮች መገኘታቸውን የቂርቆስ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ አስታውቋል። ከተጠርጣሪዎቹ መካከል ነፍሰ ጡር መኖሯ የተገለጸ ሲሆን የቀን ውሎ አበል በመክፈል እና ተሽከርካሪ በመከራየት ወንጀሉን የሚፈፅሙ ግለሰቦች እንዳሉ ህብረተሰቡ ተገንዝቦ ትራንስፖርት ሲጠቀም ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባም የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል። Addis Ababa police @Seledadotio @Seledadotio
2 992
20
ለእናቱ የገባውን ቃል ለመጠበቅ አስክሬን ቤት አስቀምጦ ለተፈተነው ታዳጊ ካሊድ ቃሲም የመኖሪያ ቤት ሊገነባለት ነው:: ከሦስት ሳምንታት በፊት እናቱ ባረፉበት ዕለት የገባውን ቃል ለማክበር ሲል አስክ+2
ለእናቱ የገባውን ቃል ለመጠበቅ አስክሬን ቤት አስቀምጦ ለተፈተነው ታዳጊ ካሊድ ቃሲም የመኖሪያ ቤት ሊገነባለት ነው:: ከሦስት ሳምንታት በፊት እናቱ ባረፉበት ዕለት የገባውን ቃል ለማክበር ሲል አስክሬን ቤት ውስጥ ትቶ የስምንተኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተናውን በመፈተን መላውን የሀገሪቱን ሕዝብ በከፍተኛ ሐዘን ያስለቀሰውና ያስደመመው ታዳጊ ካሊድ ቃሲም፣ አዲስ የመኖሪያ ቤት ሊገነባለት መሆኑ ተሰማ። በሸገር ከተማ አስተዳደር ኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ ከሁለት ታናናሽ ወንድሞቹ ጋር የሚኖረው ይህ የ14 ዓመት ታዳጊ፣ በወቅቱ እናቱ በጽኑ ታመው በነበሩበት ወቅት “እኔ አንድ ነገር ብሆን እንኳ ለዓመታት የለፋህበትን ፈተና እንዳታቋርጥ” በማለት ያስገቡትን ጥብቅ ቃል ለመጠበቅ የጠዋት ፈተናውን ተፈትኖ፣ ከሰዓት ደግሞ እናቱን አልቅሶና ቀብሮ በመመለስ የከሰዓት ፈተናውን ማጠናቀቁና “ቃልሽን አላጠፍኩም እማ!” ማለቱ ይታወሳል። ዛሬ በተሰማው አዲስና ተስፋ ሰጪ መረጃ መሠረት፣ ለታዳጊውና ለታናናሽ ወንድሞቹ ቋሚ የቤት መፍትሔ ለመስጠት የሸገር ከተማ የኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ለቤት ግንባታ የሚሆን መሬት በይፋ አዘጋጅቶ አስረክቧል። ከዚህ ጋር ተያይዞ የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ የመኖሪያ ቤቱን ሙሉ በሙሉ ገንብቶ ለታዳጊዎቹ ለማስረከብ ቃል ገብቷል። ወላጅ አባቱ ከእነርሱ ርቆ በጅጅጋ ከተማ ሌላ ትዳር መሥርቶ በመኖሩ ምክንያት እናታቸውን አጥተው ብቻቸውን ለቀሩት ለእነዚህ ወንድማማቾች የተደረገው ይህ የመሬትና የቤት ግንባታ ድጋፍ፣ የታዳጊውን ታማኝነትና ብርታት ያከበረ እንዲሁም ማኅበራዊ አጋርነትን በተግባር ያሳየ መሆኑ ተገልጿል። @Seledadotio @Seledadotio
3 023