ch
Feedback
Ethio - ዜና 🇪🇹

Ethio - ዜና 🇪🇹

前往频道在 Telegram

የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot

显示更多

📈 Telegram 频道 Ethio - ዜና 🇪🇹 的分析概览

频道 Ethio - ዜና 🇪🇹 (@ethio_zena23) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 105 880 名订阅者,在 图片 类别中位列第 72,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 272 位。

📊 受众指标与增长动态

自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 105 880 名订阅者。

根据 15 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -2 877,过去 24 小时变化为 -132,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 3.35%。内容发布后 24 小时内通常能获得 2.31% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 551 次浏览,首日通常累积 2 448 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 27。

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot”

凭借高频更新(最新数据采集于 16 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 图片 类别中的关键影响点。

105 880
订阅者
-13224 小时
-7297 夊
-2 87730 夊

数据加载中...

标签云
无数据
有任何问题?请刷新页面或联系我们的客服。
进出提及
---
---
---
---
---
---
吸引订阅者
䏃㜈 '26
䏃㜈 '260
在2个频道中
六月 '26
+64
在9个频道中
Get PRO
五月 '26
+129
在11个频道中
Get PRO
四月 '26
+74
在12个频道中
Get PRO
三月 '26
+2 127
在10个频道中
Get PRO
二月 '26
+8
在4个频道中
Get PRO
一月 '26
+2 108
在54个频道中
Get PRO
十二月 '25
+2 159
在81个频道中
Get PRO
十一月 '25
+4 183
在51个频道中
Get PRO
十月 '25
+4 892
在3个频道中
Get PRO
九月 '25
+7 709
在3个频道中
Get PRO
八月 '25
+5 654
在1个频道中
Get PRO
䏃㜈 '25
+6 591
在2个频道中
Get PRO
六月 '25
+6 975
在0个频道中
Get PRO
五月 '25
+7 406
在1个频道中
Get PRO
四月 '25
+7 575
在1个频道中
Get PRO
三月 '25
+8 127
在1个频道中
Get PRO
二月 '25
+7 065
在3个频道中
Get PRO
一月 '25
+7 127
在1个频道中
Get PRO
十二月 '24
+9 050
在4个频道中
Get PRO
十一月 '24
+11 169
在2个频道中
Get PRO
十月 '24
+14 487
在4个频道中
Get PRO
九月 '24
+12 613
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+11 528
在5个频道中
Get PRO
䏃㜈 '24
+4 340
在29个频道中
Get PRO
六月 '24
+871
在5个频道中
Get PRO
五月 '24
+1 669
在5个频道中
Get PRO
四月 '24
+1 824
在7个频道中
Get PRO
三月 '24
+3 958
在6个频道中
Get PRO
二月 '24
+1 530
在2个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
15 䏃㜈0
14 䏃㜈0
13 䏃㜈0
12 䏃㜈0
11 䏃㜈0
10 䏃㜈0
09 䏃㜈0
08 䏃㜈0
07 䏃㜈0
06 䏃㜈0
05 䏃㜈0
04 䏃㜈0
03 䏃㜈0
02 䏃㜈0
01 䏃㜈0
频道帖子
“ኢትዮጵያ ውስጥ ኮሽ ሲል፤ ያደፈጡ፣ የሚነቁ፣ የዘመናት ያልተቋረጠ የጠላትነት ስሜት ያላቸው ሀገራት አሉ” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። ኢትዮጵያ “በቀጣይ” አዲስ ህገ መንግስት ሊኖ
“ኢትዮጵያ ውስጥ ኮሽ ሲል፤ ያደፈጡ፣ የሚነቁ፣ የዘመናት ያልተቋረጠ የጠላትነት ስሜት ያላቸው ሀገራት አሉ” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። ኢትዮጵያ “በቀጣይ” አዲስ ህገ መንግስት ሊኖራት እንደሚችልም ዛሬ ረቡዕ ሐምሌ 8፤ በይፋ በተከፈተው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥቆማ ሰጥተዋል። ጠ/ሚኒስትሩ በዚሁ ንግግራቸው ከሀገራዊ ጉባኤው የሚጠበቁ ጉዳዮችን እና በምክክሩ ይሳካሉ ብለው የሚጠብቋቸውን ጉዳዮች አንስተዋል። “አሁን የምንመካከረው ስለ ትላንትናው አይደለም። የትላንትን ችግር ፈተን ለነገ መልካም መሰረት ለማኖር ነው” ሲሉ አብይ ከሀገራዊ ጉባኤው የሚጠበቀውን አመልክተዋል። “የአሜሪካ ህገ መንግስት በ55 ሰዎች ቢሰራም ልባም ነበሩና ለምዕተ ዓመታት የሚቆይ ስራ ሰርተዋል። የእኛ አራት ሺህ ሰዎች ከእነሱ በላይ፣ ከእነሱ በተሻለ ጊዜ ይበልጥ ልባም ሆነው፣ ሁሉን ወገን፣ መላው ኢትዮጵያን የሚሰበስብ ምክክር ቢያደርጉ፤ በቀጣይ የሚኖረን ህገመንግስት ከዚህ ቀደም እንደለመድነው የመጣ ሁሉ የሚቀደው ሳይሆን፤ እኛ በአራት ሺህ ጀምረናል፣ በ10 ሺህ ምክክር ሳይደርግ፤ አንድም ሰው መቀየር አይችልም ማለት ነው” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ተናግረዋል። ጠ/ሚኒስትሩ ስለ ቀይ ባህር ጉዳይ በተለይ ሲናገሩ፣ "ኢትዮጵያ ለሺ ዘመናት ያስተዳደረችውን፣ በባለቤትነት የያዘችውን፣ ለራሷም ለከባቢውም መጠቀሚያ ያኖረችውን ቀይ ባህር ያልተመረጠ መንግስት፣ ያልተወያየ መንግስት በሸፍጥ ኢትዮጵያን የጂኦግራፊ እስረኛ እንዲያደርግ ያደረገበት ዋናው ምክንያት በውስጥ ያለን ስንፍና እንጂ የኢትዮጵያን መሻትና ጥቅም ማስቆም የሚችል ኃይል ስለነበረ፣ ስላለ፣ ስለሚኖር አይደለም " ብለዋል። @Seledadotio @Seledadotio

2
ኢትዮጵያ ዛሬ 180 ሚሊየን ዶላር (29 ቢሊየን ብር) እዳዋን ዘጭ አድርጋ እንደምትከፍል የሚጠበቅበት ቀን ነው! 👉ሌላ 100 ሚሊየን ዶላር ሊኖር ይችላል ኢትዮጵያ እና የዩሮቦንድ ባለይዞታዎች ከሰሞኑ በደረሱበት የቴክኒክ ስምምነት መሰረት ኢትዮጵያ ካለባት እዳ ውስጥ 180 ሚሊየን ዶላሩን ዛሬ መክፈል ይጠበቅባታል፡፡ የእዳ መልሶ ማዋቀር ስምምነቱ ሲደረስ ከታህሳስ 2016 እስከ ታህሳስ 2017 ዓም መከፈል የሚገባቸው ሶስት የወለድ ክፍያዎች በጥቅሉ 100 ሚሊየን ዶላር በአንዴ መከፈል የሚገባው መሆኑ ይታወሳል፡፡ በመርህ ደረጃ በተደረሰው ስምምነት መሰረት ቀሪ 👉100 ሚሊዮን ዶላር – 15 ጁላይ 2027 👉300 ሚሊዮን ዶላር – 15 ጁላይ 2028 👉300 ሚሊዮን ዶላር – 15 ጁላይ 2029 የሚከፈል ይሆናል። አሁን ጥያቄው የዛሬውን እሺ ያንን የሚያክል ገንዘብ በአንዴ የመክፈል አቅም ይኖረናል ወይ? ነው ጥያቄው።
2 037
3
ትራምፕ ኢራንን በኃይል ማመንጫዎችና ድልድዮች ውድመት እያስፈራሩ ነው ​በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ወታደራዊ ውጥረት እያገረሸ ባለበት በዚህ ወቅት፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራ
ትራምፕ ኢራንን በኃይል ማመንጫዎችና ድልድዮች ውድመት እያስፈራሩ ነው ​በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ወታደራዊ ውጥረት እያገረሸ ባለበት በዚህ ወቅት፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን ወደ የውይይት ጠረጴዛ ካልተመለሰች ከፍተኛ ጥቃት እንደሚሰነዝሩ አስጠነቀቁ። ትራምፕ ከፎክስ ኒውስ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ በሚቀጥለው ሳምንት ለኢራን ሁኔታው እጅግ ከባድ እንደሚሆን ገልጸው፣ የሀገሪቱን የኃይል ማመንጫዎች እና ድልድዮች በሙሉ እንደሚያወድሙ ዝተዋል። ​ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሲቪል መሰረተ ልማቶችን ሆን ብሎ ማጥቃት የጦር ወንጀል መሆኑን አስታውሷል። አሜሪካ በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ ላይ ጥቃቷን ስትቀጥል፣ ኢራን በበኩሏ በባህሬን እና ኩዌት የሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮችን መምታቷንና የባህር ወሽመጡን ቁጥጥር እንደማትለቅ አስታውቃለች። የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኦባማ በትራምፕ ውሳኔ ላይ ያላቸውን ተቃውሞ ገልጸዋል
2 095
4
የአዲስ አበባ ታክሲዎች ጉዞ ከመጀመራቸው በፊት ክፍያ እንዲሰበስቡ ተወሰነ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የታክሲ አሽከርካሪዎች ከተወሰነው ታሪፍ በላይ እንዲሚያስከፍሉ ከማኅበረሰቡ የሚነሳውን ቅሬታ ለመፍታት ክፍያው ከመነሻው እንዲሰበሰብ የሚያስገድድ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋቱን አስታውቋል። አሽከርካሪዎች በታሪፍ መመሪያው መሠረት ብቻ ከመነሻው የትራንስፖርት ክፍያ እንዲሰበስቡ ለማስቻል ተቆጣጣሪዎች በመነሻ መጫኛ ቦታዎች ላይ ተመድበው ሥራ መጀመራቸውን የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው ተናግረዋል። ይህ አሠራር በጉዞ ወቅት "ሒሳብ ጨምሩ" በሚል ከአሽከርካሪዎች የሚነሳውን አግባብነት የሌለው ጥያቄ ለመግታት የጎላ ፋይዳ እንደሚኖረው ታምኖበታል። ይሁን እንጂ አዲሱ አሠራር ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ አንዳንድ ተግዳሮቶች መፈጠራቸውን የቢሮው ኃላፊዎች ጠቁመዋል። በከተማዋ በሚገኙ መነሻዎች ላይ ክፍያውን አስቀድሞ በመሰብሰብ ሂደት የተወሰነ ጊዜ እየወሰደ መሆኑ በማኅበረሰቡ በኩል ቅሬታ መፍጠሩ ተገልጿል። በተመሳሳይ አንዳንድ አሽከርካሪዎች መንገድ ከጀመሩ በኋላ ታሪፍ የመጨመር አዝማሚያዎችን እያሳዩ መሆናቸውን ቢሮው አስታውቋል። ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመቅረፍ ማኅበረሰቡ የጉዳዩን ፋይዳ በመገንዘብ ተገቢውን ትብብር እንዲያደርግና ህገ-ወጥ አሽከርካሪዎችን በተመለከተ ጥቆማዎችን በመስጠት የዜግነት ኃላፊነቱን እንዲወጣ አቶ ዳኛቸው አሳስበዋል። በሌላ በኩል ከዚህ ቀደም ያለ ረዳት በሚጭኑ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ሲገለጽ መቆየቱ የሚታወስ ቢሆንም፤ ቢሮው በአሁኑ ወቅት ትኩረቱን አዲሱ የአሠራር ሥርዓት ላይ ማድረጉን አመልክቷል። ይሁን እንጂ የረዳት አጠቃቀምን በተመለከተ ግልጽና ወጥ የሆነ የአሠራር ሥርዓት እንደሚያስፈልግ አቶ ዳኛቸው ገልጸዋል።
2 270
5
ስፔን ለፍፃሜ አለፈች ስፔን ፈረንሳይን 2 ለ 0 በማሸነፍ የፍፃሜ ተፋላሚ መሆኗን አረጋገጠች። ኦርያዛባል እና ፔድሮ ፖሮ ስፔንን አሸናፊ ያደረጉ ጎሎችን ከመረብ አሳርፈዋል። ስፔን ከአስራ ስድስት ዓ
ስፔን ለፍፃሜ አለፈች ስፔን ፈረንሳይን 2 ለ 0 በማሸነፍ የፍፃሜ ተፋላሚ መሆኗን አረጋገጠች። ኦርያዛባል እና ፔድሮ ፖሮ ስፔንን አሸናፊ ያደረጉ ጎሎችን ከመረብ አሳርፈዋል። ስፔን ከአስራ ስድስት ዓመታት በኋላ በዓለም ዋንጫው ለፍፃሜ አልፋለች። ስፔን በፍፃሜው ከአርጀንቲና እና እንግሊዝ አሸናፊ ጋር ትጫወታለች።
2 398
6
አሽከርካሪዎች #እንድታውቁት ነገ ሀምሌ 08/2018 ዓ.ም ታሪካዊ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በመዲናችን አዲስ አበባ ይጀመራል፡፡ ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ የጉባኤው ተሳታፊዎችም ወደ ከተማችን ገብተዋል፡፡
አሽከርካሪዎች #እንድታውቁት   ነገ ሀምሌ 08/2018 ዓ.ም ታሪካዊ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በመዲናችን አዲስ አበባ ይጀመራል፡፡ ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ የጉባኤው ተሳታፊዎችም ወደ ከተማችን ገብተዋል፡፡   የጉባኤው ተሳታፊዎች በሲኤምሲ መስመር የተባበሩት አደባባይ ወደ ሚገኘው አዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ሴንተር ጠዋትና ማታ ሲገቡና ሲወጡ የሚጓዙባቸው መስመሮች ማለትም ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ በሳህሊተ ምህረት አንዲሁም ከኢትዮ ቻይና መስመር በሳህሊተ ምህረት እስከ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ሴንተር የትራፊክ መጨናነቅ ያጋጥማል፡፡   በመሆኑም ከነገ ጀምሮ ጉባኤው እስከሚጠናቀቅበት ጊዜ ድረስ በመስመሮቹ የምትጓዙ አሽከርካሪዎች አስቀድማችሁ አማራጭ መንገዶችን እንድትጠቀሙ ከወዲሁ እናሳውቃለን፡፡   የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን   @Seledadotio @Seledadotio
2 682
7
ዛሬ የዓለም ዋንጫ ተጠባቂው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ በስፔን እና በፈረንሳይ መካከል ይከናወናል ይህ ጨዋታ በፊፋ የዓለም ደረጃ አንደኛ እና ሦስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙትን ሁለቱን የአውሮፓ ኃያላን የሚያገ+2
ዛሬ የዓለም ዋንጫ ተጠባቂው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ በስፔን እና በፈረንሳይ መካከል ይከናወናል ይህ ጨዋታ በፊፋ የዓለም ደረጃ አንደኛ እና ሦስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙትን ሁለቱን የአውሮፓ ኃያላን የሚያገናኝ በመሆኑ በመላው ዓለም የሚገኙ የስፖርት አፍቃሪያንን ቀልብ ስቧል። በዲዲዬ ዴሻምፕ የሚመራውና "ሌ ብሉዝ" በመባል የሚታወቀው የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን በሩብ ፍጻሜው የሞሮኮ ብሔራዊ ቡድንን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፎ ወደዚህ ደረጃ ተሸጋግሯል፡፡ በሉዊስ ዴ ላ ፎንቴ የሚሰለጥነው የስፔን ብሔራዊ ቡድንም በተመሳሳይ ሌላኛዋን የአውሮፓ ተፎካካሪ ሀገር ቤልጂየምን 2 ለ 1 በሆነ ጠባብ ውጤት በመርታት ለግማሽ ፍጻሜው አልፏል። ይህ ታላቅ ጨዋታ በውድድሩ እጅግ ጠንካራ የመከላከል መስመር ያላቸውን ሁለቱን ቡድኖች ፊት ለፊት የሚያገናኝ ሲሆን፤ በተለይም ፈረንሳይ በጥሎ ማለፍ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች ውስጥ እስካሁን አንድም ግብ ሳታስተናግድ ስድስት ግቦችን ማስቆጠሯ አስደናቂ ጥንካሬዋን ያሳያል። ስፔንም በበኩሏ በተመሳሳይ በጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ስድስት ግቦችን ከመረብ ያሳረፈች ሲሆን፥ ያስተናገደችው ግን አንድ ግብ ብቻ ነው። የሁለቱን ታሪካዊ ተቀናቃኝ ቡድኖች የእርስ በርስ ግንኙነት ስንመለከት፤ ስፔን በቅርብ ዓመታት የበላይነት መውሰድ የቻለች ሲሆን፥ በ2024ቱ የአውሮፓ ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ ፈረንሳይን 2 ለ 1 እንዲሁም በቅርቡ በ2025ቱ የኔሽንስ ሊግ ግማሽ ፍጻሜ በጎል ፌሽታ በተንበሸበሸው መርሐ-ግብር 5 ለ 4 በሆነ ውጤት ማሸነፏ ይታወሳል። ዛሬ ምሽት 4:00 ሰዓት በአርሊንግተን ቴክሳስ የሚገኘው AT&T ስታዲየም ጨዋታውን የሚያስተናግድ ሲሆን፥ ሳልቫዶሪያዊው ኢቫን ባርተን ጨዋታውን በመሀል ዳኝነት ይመሩታልል። @Addis_News @Addis_News
2 798
8
ዶናልድ ትራምፕን የምትመስለው ስፔናዊቷ ገበሬ የመገናኛ ብዙኃን መነጋገሪያ ሆናለች! በሰሜን ምዕራብ ስፔን ገጠራማ ስፍራ (ጋሊሲያ) የምትኖረው ዶሎሬስ ሌይስ አንቴሎ የተባለችው አዛውንት፣ ከአሜሪካው
ዶናልድ ትራምፕን የምትመስለው ስፔናዊቷ ገበሬ የመገናኛ ብዙኃን መነጋገሪያ ሆናለች! በሰሜን ምዕራብ ስፔን ገጠራማ ስፍራ (ጋሊሲያ) የምትኖረው ዶሎሬስ ሌይስ አንቴሎ የተባለችው አዛውንት፣ ከአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ባላት አስገራሚ መመሳሰል የተነሳ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በድጋሚ ከፍተኛ ትኩረት እየሳበች ትገኛለች። እ.ኤ.አ. በ2018 ስለ ገጠር ህይወት የሚዘግብ አንድ ጋዜጠኛ የዕድሜ ባለጸጋዋን ዶሎሬስን በፈረንቃ (አካፋ) ተደግፋ በፎቶ ካሜራው አስቀርቷት ነበር። በፎቶው ላይ ያላት የፀጉር ቀለም፣ የፊት አወቃቀር እና አስተያየት ከዶናልድ ትራምፕ ጋር ፍጹም አንድ አይነት በመሆኑ በወቅቱ ዓለምን አስገርሞ የነበረ ሲሆን፣ ይህ ምስል አሁን በ2026 በድጋሚ በማህበራዊ ድረ-ገጾች ላይ በስፋት እየተጋራ ይገኛል። የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች የሁለቱን ምስሎች ጎን ለጎን በማነፃፀር "መንትዮች ናቸው" እስከማለት ደርሰዋል። ዶሎሬስ ይህንን አጋጣሚ በጣም በሚያስቅ ሁኔታ የተቀበለችው ሲሆን፣ በወቅቱ ለሀገር ውስጥ ጋዜጣ በሰጠችው አስተያየት፦ "ምስሌ በጣም ሩቅ ቦታ የተጓዘ ይመስላል፤ እኔ እንደማስበው ግን ይህ የሆነው በፀጉሬ ቀለም ምክንያት ነው" ስትል በፈገግታ ተናግራለች። ይህ ድንገተኛ ዝና በገጠሯ ስፔን የምትመራውን ቀለል ያለ የግብርና ህይወት አላስተጓጎላትም፤ ይልቁንም አሁንም ድረስ በደስታ ስራዋን እየቀጠለች ትገኛለች ነው የተባለው።
2 678
9
ትምህርት ሚኒስቴር በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና አዲስ ማዕቀፍ አዘጋጅቷል። ማዕቀፉ መምህራን በክረምት ስልጠና ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የሚሸጋገሩበት መሆኑ ተገልጿል። ሚ+1
ትምህርት ሚኒስቴር በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና አዲስ ማዕቀፍ አዘጋጅቷል። ማዕቀፉ መምህራን በክረምት ስልጠና ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የሚሸጋገሩበት መሆኑ ተገልጿል። ሚኒስቴሩ በቀን 06/11/2018 ዓ.ም ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች በጻፈው ደብዳቤ፣ ከአጠቃላይ ትምህርት ሥርዓተ ትምህርት ለውጥ ጋር ተያይዞ ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና ወደ ዩኒቨርሲቲዎች ማስገባት መቋረጡን አስታውሷል፡፡ ይሁን እንጂ በቀጣይ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት በተዘጋጀ የስልጠና ማዕቀፍ፣ በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና የሚሰጥ መሆኑን ገልጿል። በ2018 ዓ.ም የክረምት ስልጠናውን ለመስጠት ስምንት አሰልጣኝ ዩኒቨርሲቲዎች መመረጣቸውን ሚኒስቴሩ አሳውቋል። ለክረምት ስልጠናው የተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች፦ 1. ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ 2. ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ 3. ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ 4. መቐለ ዩኒቨርሲቲ 5. ጅማ ዩኒቨርሲቲ 6. ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ 7. ጎንደር ዩኒቨርሲቲ 8. አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተቋማት እና የስልጠናው አሰጣጥ አግባብነት ከትምህርት ሚኒስቴር እስከሚገለጽ ድረስ ከላይ ከተገለፁት ዩኒቨርሲቲዎች በስተቀር በክረምት መምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና መስጠት የማይቻል መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳስቧል። ከ2011 ዓ.ም በፊት ስልጠና ጀምረው ያላጠናቀቁ መምህራን ከዚህ በፊት በተሰጠው ውሳኔ መሰረት እንዲያጠናቅቁ እንዲደረግ በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ ተፈርሞ ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተላከው ደብዳቤ ይገልጻል።
2 677
10
የባንኮች የማበደር ገደብ ተነሳ‼ የብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ (ቁጥር 7) ስብሰባ ዋና ዋና ውሳኔዎችና የኢኮኖሚ አፈጻጸም አጭር መግለጫ:- ፩. ዋና ዋና የፖሊሲ ውሳኔዎች 📌የብድር ገደብ
የባንኮች የማበደር ገደብ ተነሳ‼ የብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ (ቁጥር 7) ስብሰባ ዋና ዋና ውሳኔዎችና የኢኮኖሚ አፈጻጸም አጭር መግለጫ:- ፩. ዋና ዋና የፖሊሲ ውሳኔዎች 📌የብድር ገደብ መነሳት፦ በባንኮች ላይ ተጥሎ የነበረው የዓመታዊ የብድር ዕድገት ገደብ (Credit Cap) ሙሉ በሙሉ እንዲነሳ ተወስኗል። 📌 የፖሊሲ ወለድ ምጣኔ ማሻሻያ፦ የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ወለድ ምጣኔ (Policy Rate) በ1.0 በመቶ ነጥብ ከፍ በማለት ከ15 በመቶ ወደ 16 በመቶ እንዲያድግ ተደርጓል። 📌 የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ግዴታ (FX Surrender)፦ ላኪዎችና የውጭ ምንዛሬ አስገኚዎች ለባንኮች ገቢ የሚያደርጉት የውጭ ምንዛሬ ግዴታ ከ50 በመቶ ወደ 30 በመቶ ዝቅ እንዲል ተወስኗል። 📌 የኮሚሽን ምጣኔ ቅነሳ፦ ባንኮች ከውጭ ምንዛሬ ግዢ ጋር ተያይዞ የሚያስከፍሉት የኮሚሽን ምጣኔ ከ2.5 በመቶ ወደ 1.5 በመቶ እንዲቀንስ ተደርጓል።    ፪. የኢኮኖሚ አፈጻጸም ማጠቃለያ 📌 የኢኮኖሚ ዕድገት፦ በ2017 በጀት ዓመት አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ዕድገት 9.2 በመቶ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል። 📌የዋጋ ግሽበት፦ አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት በሰኔ ወር 2018 ዓ.ም. ወደ 13.4 በመቶ ዝቅ ብሏል። 📌 የበጀት ጉድለት፦ የአገሪቱ የበጀት ጉድለት ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) አንጻር ወደ 0.9 በመቶ ወርዷል። 📌 የውጭ ኢኮኖሚ ክምችት፦ አጠቃላይ የውጭ ክፍያ ሚዛን ትርፍ ያስመዘገበ ሲሆን፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ማሻሻያው ከመደረጉ በፊት ከነበረው አንጻር በ20 እጥፍ አድጓል። ‎ @Seledadotio @Seledadotio
2 786
11
የነዳጅ ዋጋ 4 በመቶ ጨመረ የአሜሪካ እና ኢራን ግጭት ማገርሸቱን ተከትሎ የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዘይት ዋጋ ጭማሪ አሳይቷል። በዓለማቀፍ ደረጃ 3.9% በመጨመር 78.96 ዶላር የገባ ሲሆን በአሜሪካ
የነዳጅ ዋጋ 4 በመቶ ጨመረ የአሜሪካ እና ኢራን ግጭት ማገርሸቱን ተከትሎ የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዘይት ዋጋ ጭማሪ አሳይቷል። በዓለማቀፍ ደረጃ 3.9% በመጨመር 78.96 ዶላር የገባ ሲሆን በአሜሪካ የነዳጅ ገበያው 4% በመጨመር 74.26 ዶላር መግባቱ ተገልጿል። ሁለቱ ሀገራት ግጭቱን ለማቆም እና የሆርሙዝ ሰርጥን በመክፈት የንግድ መርከቦች እንዲንቀሳቀሱ ለማድረግ የተደረገው ስምምነት እክል ገጥሞታል። በትናንትናው እለት አሜሪካ በኢራን የነዳጅ ማደያዎች ላይ ጥቃት ያደረሰች ሲሆን፣ ኢራንም በሰርጡ በሚያልፉ መርከቦች ላይ ጥቃት ማድረሷን አስታውቃለች። በተጨማሪ የኢራን አብዮታዊ ዘብ በጎረቤት ሀገራት ኩዌት፣ ባህሬን እና ጆርዳን ላይ የአሜሪካን ወታደራዊ ስፍራ ኢላማ ያደረገ ጥቃት ፈጽሟል። @Seledadotio @Seledadotio
2 706
12
በሳውዲ እስር ላይ ለነበሩ 1,971 ኢትዮጵያውያን ምሕረት ተደረገላቸው‼ ​ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ፣ በሳዑዲ አረቢያ በሕግ ሂደትና አስገዳጅ እርምጃዎች
በሳውዲ እስር ላይ ለነበሩ 1,971 ኢትዮጵያውያን ምሕረት ተደረገላቸው‼ ​ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ፣ በሳዑዲ አረቢያ በሕግ ሂደትና አስገዳጅ እርምጃዎች ውስጥ የነበሩ 1,971 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ባለሥልጣናት የንጉሣዊ ምሕረት አዋጅ (Royal Amnesties) ተጠቃሚ መሆናቸውን አስታወቀ። ​በሪያድ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲና በጅዳ ከሚገኘው ቆንስላ ጄኔራል ጋር በመተባበር የተደረጉት ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች አዎንታዊ ውጤት ማምጣታቸውን የገለጸው ሚኒስቴሩ፣ በምሕረቱ የተካተቱ ዜጎችን ወደ ሀገር ለመመለስ የሚያስችሉ ሥራዎች መጀመራቸውን ጠቁሟል። የኢትዮጵያ መንግሥት በውጭ ሀገራት የሚገኙ ዜጎቹን ደኅንነትና መብት ለማስጠበቅ ከሳዑዲ ባለሥልጣናት ጋር የሚያደርገውን ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ንግግር አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጧል። @Seledadotio @Seledadotio
2 778
13
በቦሌ አትላስ አካባቢ በጣለው ከባድ ዝናብና ንፋስ በአንድ ተሽከርካሪ ላይ ጉዳት ደረሰ በትናንትናው ዕለት ከላይ በቪዲዮ እንደምትመለከቱት በአስደንጋጭ ሁኔታበዋና ከተማዋ ቦሌ አትላስ ተብሎ በሚጠራው
በቦሌ አትላስ አካባቢ በጣለው ከባድ ዝናብና ንፋስ በአንድ ተሽከርካሪ ላይ ጉዳት ደረሰ በትናንትናው ዕለት ከላይ በቪዲዮ እንደምትመለከቱት በአስደንጋጭ ሁኔታበዋና ከተማዋ ቦሌ አትላስ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በጣለው ኃይለኛ ዝናብ እና በነፈሰው ብርቱ ንፋስ ምክንያት... ከአንድ የግንባታ ቦታ ላይ የብረት ቁሳቁሶች ተፈንቅለው በመውደቃቸው በአቅራቢያው በነበረ ዘመናዊ መኪና ላይ ጉዳት ማድረሳቸው ታውቋል። ምንም እንኳን በንብረት ላይ አደጋው ጉዳት ቢያስከትልም፣ በአምላክ ምስጋና ይግባና በአደጋው ወቅት በሰው ሕይወትም ሆነ አካል ላይ የደረሰ ምንም ዓይነት ጉዳት እንደሌለ ተረጋግጧል። @Seledadotio @Seledadotio
2 880
14
" አትገቡም !! " ግብረሰዶማውያንን የጫነችው የቅንጦት መርከብ በቱርክና ግብፅ ወደቦች እንዳትገባ ተከለከለች። ከሰሞኑን " አትላንቲስ ኢቨንትስ " በተባለ የአሜሪካ የጉዞ ድርጅት የተከራየችና 2,0+1
" አትገቡም !! " ግብረሰዶማውያንን የጫነችው የቅንጦት መርከብ በቱርክና ግብፅ ወደቦች እንዳትገባ ተከለከለች። ከሰሞኑን " አትላንቲስ ኢቨንትስ " በተባለ የአሜሪካ የጉዞ ድርጅት የተከራየችና 2,000 ገደማ ግብረሰዶማውያንን የጫነች " ስካርሌት ሌዲ " የተሰኘች የሜዲትራኒያን ባህር የቅንጦት መርከብ ወደ ቱርክ እና ግብፅ ወደቦች እንዳትገባ ተከልክላለች። መርከቧ በቱርክ ኩሻዳሲ እና ኢስታንቡል ወደቦች እንዳታርፍ የተከለከለች ሲሆን፣ የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ውሳኔው የጉዞው ዓላማ ከሀገሪቱ ሞራላዊና ሥነ-ምግባራዊ እሴቶች እንዲሁም ማኅበራዊ ደንቦችና እሴቶች ጋር ስለማይጣጣም መሆኑን ገልጸዋል። የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሪች ካምቤል በኩባንያው 36 ዓመታት ታሪክ ውስጥ እንዲህ ያለው ንገረ ሲገጥማቸው የመጀመሪያ እንደሆነ ገልጸዋል። መርከቧ ከቱርክ እገዳ በኋላ የጉዞ አቅጣጫዋን ወደ እስክንድርያ ግብፅ ብታዞርም፣ የግብፅ ባለሥልጣናትም መርከቧ ወደ ሀገሪቱ የባህር ክልል እንዳትገባ አግደዋታል። ግብፅ ለእገዳው የሰጠችው ይፋዊ ማብራሪያ ባይኖርም፣ ድርጅቱ ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጉዞ በተሳካ ሁኔታ ማድረጉን አስታውሶ በውሳኔው መደነቁን ገልጿል። በእነዚህ እገዳዎች ምክንያት ተሳፋሪዎች በግብፅ ሊያደርጓቸው የነበሩት የፒራሚድ እና የታሪክ ስፍራዎች ጉብኝቶች የተሰረዙ ሲሆን፣ መርከቧ መስመሯን ቀይራ ወደ ክሬት ግሪክ እና ኮቶር ሞንቴኔግሮ ለማምራት ተገድዳለች። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23
2 673
15
የዓለም ባንክ በቀጣዮቹ 10 ዓመታት በኢትዮጵያ ለሚያከናውናቸው ድጋፎች የፖሊሲ ለውጦች አደረገ የዓለም ባንክ ከ2027 እስከ 2036 ያለውን የ10 ዓመታት የአጋርነት ማዕቀፍ ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ በሚ
የዓለም ባንክ በቀጣዮቹ 10 ዓመታት በኢትዮጵያ ለሚያከናውናቸው ድጋፎች የፖሊሲ ለውጦች አደረገ የዓለም ባንክ ከ2027 እስከ 2036 ያለውን የ10 ዓመታት የአጋርነት ማዕቀፍ ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ በሚቀጥሉት 10ዓመታት ቅድሚያ ይሰጣቸው የነበሩ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን ሙሉ በሙሉ ከዕቅዱ ውጪ ማድረጉን አስታወቀ፡፡ ሪፖርተር የተመለከተው የዓለም ባንክ አዲስ የስትራቴጂ ሰነድ ትኩረቱን በዋናነት በየዓመቱ ወደ ሥራው ዓለም ለሚቀላቀሉ ወደ ሁለት ሚሊዮን ገደማ የሚሆኑ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር ላይ አድርጓል፡፡ ግዙፍ በመንግሥት የሚመሩ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን፣ ዋና ዋና የአስፋልት መንገዶችንና የቱሪዝም ዘርፍን በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ሙሉ በሙሉ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ፕሮጀክቶች ዝርዝር ውጪ አድርጓቸዋል፡፡ 👉የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ከዕቅዱ ውጪ እንዲሆኑ የተደረጉት ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ባደረገችው ኢንቨስትመንት በቂ የማመንጨት አቅም ስላላት ሲሆን፣ የቱሪዝም ዘርፍ ደግሞ በኢትዮጵያ ያለው የፀጥታና የመሠረተ ልማት ሁኔታ መሻሻል እስከሚታይበት ድረስ ከዝርዝሩ ውጪ እንዲሆን መደረጉን ጠቁሟል፡፡ የከተማ አውራ ጎዳናዎችን የመገንባት ዕቅድም ቀርቶ፣ በተመሳሳይ መልኩ የገጠር መንገዶችን ወደ ማስፋፋት እንዲዞር የተደረገ ሲሆን፣ ይህም አርሶአደሩ ምርቱን በቀላሉ ወደ ገበያ እንዲያቀርብ ለማገዝ፣ የጉምሩክ አሠራርን ለማዘመንና የወጪ ንግድ ወጪን ለመቀነስ ያለመ አዲስ መዋቅራዊ አቅጣጫ መሆኑ ተመልክቷል። 👉ባንኩ በቀጣይ እቅዶቹ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ ማስተካከል፣ የኃይል መቆራረጥን መቀነስና በሚሊዮኖች ለሚቆጠር ሕዝብ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን አስተማማኝ ማድረግ የሚሉት ይገኙበታል፡፡ https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23
2 576
16
የሀይል ስርቆትን በተመለከተ ጥቆማ ለሚሰጥ  ከተጣለው ቅጣት የ25 በመቶ ኮሚሽን እንደሚያገኝ ተገለፀ ሀምሌ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. (አሐዱ ሬዲዮ)፦ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚፈጸሙ የኤሌክትሪክ ሀይል ስርቆትን ለመግታት እና በመሰረተ ልማት ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን ለመከላከል የተቀናጀ የቁጥጥር ስራ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል ። በአገልግሎቱ የሽያጭና የደንበኞች አገልግሎት  ዳይሬክተር አቶ ይሔይስ ስዩም የሀይል ስርቆቱ በዋናነት የኤሌክትሪክ ቆጣሪዎች በትክክል እንዳይቆጥሩ በማድረግ ወይም መስመር ወደ ቆጣሪው ከመግባቱ በፊት በቀጥታ በመጥለፍ ወደ መኖሪያ ቤቶችና የኢንዱስትሪ ማሽኖች በመውሰድ እንደሚፈጸም ተናግረዋል ። በ2017 በጀት ዓመት በተደረገው ከፍተኛ ክትትልና የቁጥጥር ስራ፣ የሃይል ስርቆት ጨምሮ ከባከነ ሃይል 259 ሚሊዮን ብር መሰብሰብ መቻሉንም ተናግረዋል። የኤሌክትሪክ ሃይል ስርቆትን በዘላቂነት ለመከላከል ህብረተሰቡ ጥቆማ እንዲሰጥ የተደራጀ የአሰራር ስርዓት፣ ፖሊሲና መመሪያ ተቀርጾ ወደ ስራ መገባቱን  ጠቁመዋል ። በዚህም መሰረት የሃይል ስርቆት ለሚጠቁሙ ደንበኞች ከተጣለው ቅጣት ላይ የ25 በመቶ ኮሚሽን ክፍያ ተግባራዊ መደረግ መጀመሩ አስረድተዋል ። ለአብነትም አንድ ከፍተኛ ኢንዱስትሪ በፈጸመው የቴክኒክ ስርቆት ምክንያት አንድ ሚሊዮን ብር ቢቀጣ፣ ጥቆማውን ያቀረበው ግለሰብ  የ250 ሺህ ብር የገንዘብ ማበረታቻ በህጋዊ አሰራር ያገኛል። የኤሌክትሪክ ኔትወርክ መሰረተ ልማት የጋራ ሀብት በመሆኑ ፣ የሃይል ስርቆት የሚፈጽሙ አካላትን በማጋለጥ ረገድ ህብረተሰቡ የበኩሉን ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪ ቀርቧል።
2 955
17
የሀይል ስርቆትን በተመለከተ ጥቆማ ለሚሰጥ  ከተጣለው ቅጣት የ25 በመቶ ኮሚሽን እንደሚያገኝ ተገለፀ ሀምሌ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. (አሐዱ ሬዲዮ)፦ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚፈጸሙ የኤሌክትሪክ ሀይል ስርቆትን ለመግታት እና በመሰረተ ልማት ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን ለመከላከል የተቀናጀ የቁጥጥር ስራ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል ። በአገልግሎቱ የሽያጭና የደንበኞች አገልግሎት  ዳይሬክተር አቶ ይሔይስ ስዩም የሀይል ስርቆቱ በዋናነት የኤሌክትሪክ ቆጣሪዎች በትክክል እንዳይቆጥሩ በማድረግ ወይም መስመር ወደ ቆጣሪው ከመግባቱ በፊት በቀጥታ በመጥለፍ ወደ መኖሪያ ቤቶችና የኢንዱስትሪ ማሽኖች በመውሰድ እንደሚፈጸም ተናግረዋል ። በ2017 በጀት ዓመት በተደረገው ከፍተኛ ክትትልና የቁጥጥር ስራ፣ የሃይል ስርቆት ጨምሮ ከባከነ ሃይል 259 ሚሊዮን ብር መሰብሰብ መቻሉንም ተናግረዋል። የኤሌክትሪክ ሃይል ስርቆትን በዘላቂነት ለመከላከል ህብረተሰቡ ጥቆማ እንዲሰጥ የተደራጀ የአሰራር ስርዓት፣ ፖሊሲና መመሪያ ተቀርጾ ወደ ስራ መገባቱን  ጠቁመዋል ። በዚህም መሰረት የሃይል ስርቆት ለሚጠቁሙ ደንበኞች ከተጣለው ቅጣት ላይ የ25 በመቶ ኮሚሽን ክፍያ ተግባራዊ መደረግ መጀመሩ አስረድተዋል ። ለአብነትም አንድ ከፍተኛ ኢንዱስትሪ በፈጸመው የቴክኒክ ስርቆት ምክንያት አንድ ሚሊዮን ብር ቢቀጣ፣ ጥቆማውን ያቀረበው ግለሰብ  የ250 ሺህ ብር የገንዘብ ማበረታቻ በህጋዊ አሰራር ያገኛል። የኤሌክትሪክ ኔትወርክ መሰረተ ልማት የጋራ ሀብት በመሆኑ ፣ የሃይል ስርቆት የሚፈጽሙ አካላትን በማጋለጥ ረገድ ህብረተሰቡ የበኩሉን ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪ ቀርቧል። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23
1
18
ቁፋሮ ማካሄድ ተከለከለ‼️ የአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን በከተማዋ ክልል ውስጥ የሚካሄደውን የኮንስትራክሽን ማዕድናት ፍለጋ፣ ምርት እና ስርጭት ሥርዓት ለማስያዝና ለመቆጣጠር የሚያስች
ቁፋሮ ማካሄድ ተከለከለ‼️ የአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን በከተማዋ ክልል ውስጥ የሚካሄደውን የኮንስትራክሽን ማዕድናት ፍለጋ፣ ምርት እና ስርጭት ሥርዓት ለማስያዝና ለመቆጣጠር የሚያስችል አዲስ መመሪያ አውጥቷል። በመመሪያው መሠረት የኅብረተሰቡን ደኅንነትና የተፈጥሮ ሀብትን ለመጠበቅ፦ 🛑የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶችን ከአደጋ ለመጠበቅ ሲባል ከከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች በ25 ሜትር ራዲየስ ውስጥ፣ 🛑ከመኖሪያ መንደሮችና ከኢንዱስትሪ ፓርኮች በ500 ሜትር ራዲየስ ውስጥ፣ 🛑ከወንዝ ዳርቻዎች በ30 ሜትር ራዲየስ ውስጥ ማንኛውንም ዓይነት ቁፋሮ ማካሄድ ሙሉ በሙሉ የተከለከለ ነው። "የኮንስትራክሽን ማዕድን ፈቃድ አፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 191/2018" በሚል ተግባራዊ እንዲሆን የፀደቀው ይህ መመሪያ፤ ከማዕድን ቁፋሮ ጋር በተያያዘ በከተማዋ ይታዩ የነበሩ የአሠራር ክፍተቶችን በመድፈን ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት ሥርዓት ለመዘርጋት ያለመ መሆኑ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። @Seledadotio @Seledadotio
3 150
19
“ለሻዕቢያ ከምገረድ፣ ለብልጽግና ብንበረከክ እመርጣለሁ”‼️ የቀድሞዋ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም መጠይቅ፣ ከህወሓት ጋር ተድርጎ ለሻዕቢያ ከመገረድ በብልጽግና አንገት መድፋት ይ
“ለሻዕቢያ ከምገረድ፣ ለብልጽግና ብንበረከክ እመርጣለሁ”‼️ የቀድሞዋ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም መጠይቅ፣ ከህወሓት ጋር ተድርጎ ለሻዕቢያ ከመገረድ በብልጽግና አንገት መድፋት ይሻለኛል ብለዋል፡፡ ኬሪያ ከፋና ቲቪ ጋር ባደረጉት ቃለ ትግራይን በበላይ የተቆጣጠሩትን እነ ደብረጽዮን ገ/ሚካኤልን የትግራይን ሕዝብ ለሻዕቢያ አሳልፈው በመስጠት ወንጅለዋል፡፡ ኬሪያ የቀድሞ ድርጅታቸው ህወሓት ትግራይን ለማጥፋት ይመኛል ላሉት ሻዕቢያ “ተላላኪ ሆኖ እየተገረደ” ነው ብለዋል፡፡ ህወሓት “የብልጽግና ተንበርካኪ መሆን የለብንም ነው የሚለን” ያሉት ኬሪያ፣ “ለሻዕቢያ ከምገረድ እዚህ ብንበረከክ ነው የምመርጠው” ብለዋል፡፡ @Seledadotio @Seledadotio
3 077
20
የማይሞተው ብቸኛው የምድር ፍጡር እርጅናን በመቀልበስ የሕይወት ዑደቱን ወደ ሕፃንነት በመመለስ ለዘላለም መኖር የሚችል “የማይሞት” አስገራሚ ፍጡር በባሕር ጥልቀት ውስጥ መገኘቱ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስ+3
የማይሞተው ብቸኛው የምድር ፍጡር እርጅናን በመቀልበስ የሕይወት ዑደቱን ወደ ሕፃንነት በመመለስ ለዘላለም መኖር የሚችል “የማይሞት” አስገራሚ ፍጡር በባሕር ጥልቀት ውስጥ መገኘቱ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶችን አስደምሟል። “ቱሪቶፕሲስ ዶርኒ” (Turritopsis dohrnii) የተባለውና በጣም አነስተኛ መጠን ያለው ይህ የጄሊፊሽ (Jellyfish) ዝርያ በሕይወት ዘመኑ ላይ አደጋ፣ በሽታ ወይም እርጅና ሲደቅንበት የራሱን ሴሎች ሙሉ በሙሉ በማደስ ወደ መጀመሪያው የፅንስ (Polyp) ደረጃ የመመለስ አስደናቂ የተፈጥሮ ብቃት አለው። ይህ ማለት ፍጡሩ ሲያረጅ ከመሞት ይልቅ ልክ እንደገና ተወልዶ ወደ ሕፃንነቱ ይመለሳል፤ ይህንን ሂደት ደግሞ ሳይሞት ለዘላለም ደጋግሞ ማከናወን ይችላል። ተመራማሪዎች የዚህን ፍጡር የዲኤንኤ (DNA) ምስጢር ለመፍታት ሌሊትና ቀን እየሠሩ የሚገኙ ሲሆን፣ ግኝቱ ለሰው ልጅ የእርጅና መከላከያ እና የካንሰር ሕክምና ምርምር ትልቅ ተስፋን የፈነጠቀ በመሆኑ በማኅበራዊ ሚዲያና በሳይንሱ ዓለም ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል። @Seledadotio @Seledadotio
3 274