Ethio - ዜና 🇪🇹
የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot
Больше📈 Аналитический обзор Telegram-канала Ethio - ዜና 🇪🇹
Канал Ethio - ዜና 🇪🇹 (@ethio_zena23) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 101 677 подписчиков, занимая 74 место в категории Картинки и 313 место в регионе Эфиопия.
📊 Показатели аудитории и динамика
С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 101 677 подписчиков.
Согласно последним данным от 04 сентября, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -2 426, а за последние 24 часа — -155, при этом общий охват остаётся высоким.
- Статус верификации: Не верифицирован
- Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 3.26%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 2.69% реакций от общего числа подписчиков.
- Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 319 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 731 просмотров.
- Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 23.
📝 Описание и контентная политика
Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
“የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ!
ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን
@Ethiozenaa_bot”
Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 05 сентября, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Картинки.
Загрузка данных...
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 05 сентября | 0 | |||
| 04 сентября | 0 | |||
| 03 сентября | 0 | |||
| 02 сентября | 0 | |||
| 01 сентября | 0 |
| 2 | የሱዳኑ ጦር መሪ አብዱል ፋታህ
አል-ቡርኻን አስመራ ገቡ‼️
👉ምፅዋ በርካታ መሳሪያ እየተራገፈ ይገኛል።
የሱዳን ጦር አዛዥ እና የሉዓላዊ ምክር ቤት ሊቀ-መንበር ጄነራል አብዱል ፋታህ አል-ቡርኻን ኤርትራ የገቡ ሲሆን አስመራ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም በፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። አል-ቡርኻን ከፈጥኖ ደራሽ ኃይል (RSF) ጋር ውጊያ ውስጥ ከገቡ ወዲህ ዋነኛ ደጋፊያቸው ወደ ሆነችው ኤርትራ ሲያቀኑ በቅርብ ጊዜያት ውስጥ የዛሬው ለሁለተኛ ጊዜ ነው።
የኤርትራ የኢንፎርሜሽን ሚኒስትር የማነ ገብረ መስቀል እንደገለጹት፣ የጄነራል አል-ቡርኻን ጉብኝት በሁለቱ ሀገራት መካከል የሚደረግ መደበኛ የምክክር አካል ነው። ሁለቱ መሪዎች በቆይታቸው የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ማጠናከር እና በቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ እንደሚያተኩሩ ተናግረዋል። | 1 356 |
| 3 | ቡና አብዝቶ መጠጣት የእንቅልፍ ጊዜን ቢያሳጥርም ጥልቀቱን እንደሚጨምር ተነገረ
በቀን አራት ወይም ከዚያ በላይ ሲኒ ቡና መጠጣት የእንቅልፍ ቆይታን ያሳጥራል፤ ሆኖም በእንቅልፍ ወቅት የሚገኘውን ጥልቅ እረፍት እንደሚጨምር አዲስ ጥናት ይፋ አደረገ።
በስዊዘርላንዱ ተመራማሪ በቤንጃሚን ስተኪ የተመራው ይህ ጥናት፣ የዩኬ ባዮባንክ እና የHypnoLaus መረጃዎችን በመተንተን የተሰራ ነው።
ተመራማሪዎቹ እንዳረጋገጡት፣ ከፍተኛ መጠን ያለው ካፌይን መውሰድ የእንቅልፍ ሰዓትን በ11 ደቂቃ ያህል ያሳጥራል።
ነገር ግን፣ የሰውነት ህዋሳትን ለማደስ እና ኃይልን ለማገገም ወሳኝ የሆነው "የዝቅተኛ ሞገድ እንቅልፍ" ጥልቀት ይጨምራል።
ሳይንቲስቶች እንደሚሉት፣ ይህ የሰውነት ተፈጥሯዊ ምላሽ ሲሆን፣ ያጣውን አጭር የእንቅልፍ ሰዓት በጥልቅ እንቅልፍ ለማካካስ የሚያደርገው ጥረት ነው።
ጥናቱ ቡና የእንቅልፍ መጠንን ቢቀንስም፣ የጥራት መጠኑ ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ እንደሚፈጥር አመልክቷል። | 1 889 |
| 4 | ለአዲስ ዓመት የአንድ ኪሎ ሥጋ ዋጋ 1,200 ብር እንዲሆን ከሥጋ ቤቶቹ ጋር ስምምነት መደረጉ ተገለጸ
ለተቃረበው የ2019 አዲስ ዓመት በዓል የሸማቹን እንግልትና ያልተገበበ የዋጋ ጭማሪ ለመግታት ያለመ አዲስ ውሳኔ ተ አስተላለፈ።
የአዲስ አበባ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን በመዲናዋ ከሚገኙ 274 የኅብረት ሥራ ማኅበራት ሥጋ ቤቶች ጋር ባደረገው ዝርዝር ውይይት፣ አንድ ኪሎ የበሬ ሥጋ በ1,200 ብር ብቻ ለሕዝብ እንዲቀርብ መግባባት ላይ መድረሱን አስታውቋል።
የበዓላት ወቅት የመገበያያ ዋጋ ንረትና የአቅርቦት እጥረት የሚፈጥረውን ጫና ለማቃለል ሰፊ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን የገለጸው ኮሚሽኑ፣ ሸማቾች በየአካባቢያቸው በሚገኙ ማኅበራት በኩል ምርቱን በቀላሉ ማግኘት እንደሚችሉ አረጋግጧል።
በሁሉም 274 የኅብረት ሥራ ማኅበራት ሥጋ ቤቶች አንድ ኪሎ ሥጋ ከ1,200 ብር በላይ እንዳይሸጥ ስምምነት ተደርሷል።
መንግሥት ከአርሶ አደሮችና ከበሬ አቅራቢዎች ጋር ቀጥተኛ የገበያ ትስስር በመፍጠሩ በሥጋ ቤቶች በኩል የነዳጅና የአቅርቦት ምክንያት አቤቱታ እንደማይኖር ተገልጻል።
ከሥጋ በተጨማሪ ሌሎች የበዓል ሸመታዎችን ከእሁድ ገበያዎችና ከኅብረት ሥራ ማኅበራት ሱቆች በቅናሽ ዋጋ መገበያየት እንደሚቻል ጥሪ ቀርቧል።
ከተቀመጠው የዋጋ ተመን በላይ በሚሸጡ ሥጋ ቤቶች ላይ ኅብረተሰቡ ጥቆማ በመስጠት ትብብር እንዲያደርግ ተጠይቋል።
https://t.me/Ethio_Zena23
https://t.me/Ethio_Zena23 | 2 185 |
| 5 | ያለፍላጎታቸው ሴቶችን በወሲብ ንግድ ላይ ያሰማሩት አምስት ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ፡፡
በባሌ ዞን ሮቤ ከተማ አስተዳደር በመጠጥ ግሮሰሪ ንግድ ፈቃድ ሽፋን ሴቶችን ያለ ፍላጎታቸው ለወሲብ ንግድ ሲዳርጉና ጥቃት ሲፈጽሙ የነበሩ አምስት ግለሰቦች እስከ 23 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራትና የገንዘብ መቀጮ መቀጣታቸውን የከተማው ፖሊስ ዋና መምሪያ አስታውቋል።
የሮቤ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ዋና መምሪያ የኮሙኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ኢንስፔክተር ጌታቸው ታምሩ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት፣ ተከሳሾቹ በዘይበላ ወላሼ ቀበሌ «ኤል ክላሲኮ» የተባለ የምሽት ጭፈራ ቤት በመክፈት ሴቶችን በአስተናጋጅነት ካስቀጠሩ በኋላ በግዳጅ ለዝሙት አዳሪነት እንዲሰማሩ አድርገዋል።
ፖሊስ ባደረገው ማጣራት አንደኛ ተከሳሽ ተሬሳ ፍቃዱ የንግድ ፈቃዱን በማውጣትና ከሌሎች ተከሳሾች ጋር በመሆን የተቀጠሩ አስተናጋጆችን ያለፍላጎታቸው የግብረ-ሥጋ ድፍረት ጥቃት እንዲፈጸምባቸው ማድረጉ በበቂ ማስረጃ ተረጋግጧል።የቀረበውን የዐቃቤ ሕግ ክስና የፖሊስ ማስረጃ የመረመረው የሮቤ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት የጥፋተኝነት ውሳኔ አስተላልፋል።
በዚህም መሰረት 1ኛ ተከሳሽ ተሬሳ ፍቃዱ ድርጊቱን በዋናነት በመምራትና በግዳጅ የመድፈር ጥቃት በመፈጸሙ በ23 ዓመት ፅኑ እስራት እና በ200 ሺህ ብር መቀጮ፤ 2ኛ ተከሳሽ ዳንኤል ደሴ በ10 ዓመት እስራት እና በ10 ሺህ ብር መቀጮ፤ 3ኛ ተከሳሽ ወርቁ ደሜ በ6 ዓመት እስራት እና በ45 ሺህ ብር መቀጮ፤ 4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች ተመስገን ፍቃዱ እና ቤክና መሐመድ ደግሞ እያንዳንዳቸው በ1 ዓመት ከ8 ወር እስራትእንዲቀጡ ተወስኖባቸዋል። | 2 484 |
| 6 | በክልል ንግድ ፈቃድ አዲስ አበባ ውስጥ መስራት አይቻልም ሲል ቢሮው አሳወቀ‼️
በክልል ፈቃድ አዲስ አበባ ውስጥ የሚሰሩ አስመጪዎች ንግድ ፈቃዳቸውን ወደ አዲስ አበባ ማዛዋወር አለባቸው ብሏል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በመኪና ሽያጭ ዘርፍ በሚደረጉ ህገወጥ አሰራሮች እና የታክስ ስወራዎች ላይ ጥብቅ እርምጃና ቁጥጥር እንደሚያደርግ አስታወቀ።
በክልል ፈቃድ አዲስ አበባ ውስጥ የሚሰሩ አስመጪዎች ንግድ ፈቃዳቸውን ወደ አዲስ አበባ ማዛወር አለባቸው ተብሏል።
ደረሰኝ መለየት የሽያጭ ማሽን ማስተካከል እና ወርሃዊና ዓመታዊ ግብር መክፈል አለባቸው ነው የተባለው።
ህገወጥ ደረሰኝ መጠቀም ወይም የውጭ ሀገር ፈቃድ ብቻ ይዞ መንቀሳቀስ በህግ ያስጠይቃል።
አስመጪዎችና የመኪና ማሳያ ባለቤቶች ፈቃድ ከሌላቸው ደላሎች ጋር በመተባበር ህገወጥ የሽያጭ ሰነድ ከመፈራረም እንዲቆጠቡ ተሳስቧል።
ቢሮው ከዚህ አሰራር ውጭ በሚንቀሳቀሱ አስመጪዎች ፈቃድ የሌላቸው ደላሎች በኦንላይን ህገወጥ ንግድ የሚያካሂዱ ግለሰቦች እና ከተዋናዮቹ ጋር በሚተባበሩ አካላት ላይ ቢሮው ክትትልና ምርመራ በማድረግ ህጋዊ እርምጃ ይወስዳል ሲል አሳስቧል። | 2 639 |
| 7 | ህወሃት የፌደራል መንግስትን በድሮን ጥቃት ሲከስ የአላማጣ ባለስልጣናት ደግሞ ህወሃትን ወቀሱ
ህወሃት የፌደራል መንግስት ባለስልጣናት በሲቪል መሠረተ ልማቶች ላይ ተደጋጋሚ የአየር ጥቃቶችን እየፈጸሙ ነው ሲል የከሰሰ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ የህወሃት ታጣቂዎች የህዝብ ትምህርት ቤቶችን ወደ ወታደራዊ ካምፕነት ቀይረዋል የሚሉ የአካባቢው ሪፖርቶች መውጣታቸውን ዶቼ ቬሌ ዘግቧል።
የህወሃት ቃል አቀባይ ሚካኤል አሰግዶም በድሮን እና በሚግ ተዋጊ አውሮፕላኖች የታገዘው የአየር ጥቃት በአምስት ዞኖች በሚገኙ የህዝብ ተቋማት ላይ ማረፉን የገለጹ ሲሆን፣ በሰሜን ምዕራብ ዞን ደጀን ከተማ የሚገኝ አንድ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለሁለተኛ ጊዜ ተመትቶ ሙሉ በሙሉ መውደሙን፣ እንዲሁም በእንደርታ እና በራያ አዘቦ አርሶ አደሮችና የመኖሪያ መንደሮች መመታታቸውን ጠቅሰዋል።
ይሁን እንጂ ከአላማጣ ከተማ የተገኙ አንድ የቀድሞ የአካባቢው ባለስልጣን ለዶቼ ቬሌ በሰጡት ተቃራኒ መረጃ፣ የህወሃት ኃይሎች አራት የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ በአላማጣ የሚገኙ ስምንት ትምህርት ቤቶችን፣ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን እና የማዘጋጃ ቤት ህንፃዎችን በአሁኑ ወቅት ወደ ታጠቁ ወታደራዊ ይዞታነት እና መፈጠሪያነት ቀይረዋቸዋል ሲሉ ከሰዋል። | 2 790 |
| 8 | የኢትዮጵያ አየር መንገድ በናሚቢያ አዲስ ብሔራዊ አየር መንገድን በሽርክና ለማቋቋም ከሀገሪቱ መንግሥት ጋር ድርድር ጀመረ።
የናሚቢያ ሥራና ትራንስፖርት ሚኒስትር ጆናስ ሼሎንጎ እንደገለጹት፤ ውይይቱ ቀደም ሲል "ኤር ናሚቢያ" ላይ ደርሶ የነበረውን የፋይናንስ ውድቀትና መዘጋት ዳግም እንዳይከሰት ለመከላከልና ጠንካራ አየር መንገድ ለመገንባት ያለመ ነው።
ሚኒስትሩ፣ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር የተደረጉት ውይይቶች ሰፊ የቴክኒክ እና የንግድ ጉዳዮችን ያካተቱ ቢሆንም እስካሁን የተፈረመ አስገዳጅ ስምምነት የለም ብለዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዚህ ቀደም በቶጎ፣ በማላዊ፣ በዛምቢያ እና በኮንጎ አየር መንገዶች ምሥረታ ላይ አሻራውን ማሳረፉ ይታወሳል ሲል ስፑትኒክ አፍሪካ ። | 2 829 |
| 9 | አስተማማኝ መረጃ በማጣት እና በተዛቡ ዜናዎች ተስፋ ቆርጠዋል‼️
እውነትን መሰረት ያደረጉ ተጨባጭ መረጃዎችን ወቅታዊ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ዜናዎችን JOIN ብለዉ ይከታተሉ!
JOIN CHANNEL👇JOIN CHANNEL👇
👇
https://t.me/seledadotio
https://t.me/seledadotio | 207 |
| 10 | ሊቨርፑል ከኢፕስዊች ታውን
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሦስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት በሚደረግ አንድ ጨዋታ ይጀምራል፡፡
በዚህም ሊቨርፑል ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ከኢፕስዊች ታውን ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
በአንዶኒ ኢራኦላ የሚመራው ሊቨርፑል የውድድር ዓመቱን የመጀመሪያ ድል ለማሳካት ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡
ሊቨርፑል በሊጉ ያደረጋቸውን ያለፉትን ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ሁለት አቻ በሆነ ተመሳሳይ ውጤት ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡
ተጋጣሚው ኢፕስዊች ታውን በበኩሉ ወደ ድል ለመመለስ የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
በመጀመሪያ ሳምንት የሊጉ ጨዋታ ድል የቀናው ኢፕስዊች ታውን በሁለተኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር በማንቼስተር ዩናይትድ 5 ለ 2 በሆነ ሰፊ ውጤት መሸነፉ አይዘነጋም፡፡ | 2 720 |
| 11 | በአዲስ አበባ ከተማ በህገ-ወጥ የማዕድን ቁፋሮ ላይ የተሰማሩ አካላት እስከ ግማሽ ሚሊዮን ብር እንደሚቀጡ የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ።
ባለስልጣኑ እንደገለጸው፤ ያለፈቃድ ማዕድን የሚያመርቱ፣ ከፈቃድ ውጭ የሚንቀሳቀሱ እና የአካባቢ ጥበቃ ህጎችን የማይተገብሩ አካላት ተጠያቂ ይሆናሉ።
በዚህም መሰረት፡-ያለፈቃድ ማዕድን ሲያመርቱ የተገኙ አካላት ከ300,000 እስከ 400,000 ብር ቅጣት እንደሚጠበቅባቸው ተገልጿል።
ህገ-ወጥ ድርጊቱን የፈጸሙ አካላት የገንዘብ ቅጣቱ እንደ ጥፋቱ ክብደት እስከ 500,000 ብር ሊደርስ እንደሚችልና መሳሪያዎቻቸውም በመንግስት እንደሚወረሱ ተመላክቷል።
ከተማዋንና መሰረተ ልማቶችን ለመጠበቅ በማዕድን ማምረቻ ቦታዎች ላይ የሲሲቲቪ ካሜራዎችን የመግጠም ስራ የግዴታ እንደሚሆንና አልሚዎችም የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርት ማቅረብ እንዳለባቸው ተሳስቧል።
ይህ ጥብቅ የህግ ማዕቀፍ የከተማዋን ደህንነትና ሰላም ለማረጋገጥ የታለመ መሆኑ ተገልጿል። | 2 633 |
| 12 | የ2018 ዓ.ም. የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሃ ግብር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ውጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፡-
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን ከነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ከታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ (Link) በመጠቀም ምርጫችሁን ት/ቤት መሄድ ሳይጠበቅባችሁ ባላችሁበት ቦታ እራሳችሁ በመሙላት እንድታሳውቁ እንገልጻለን።
ማስፈንጠሪያ (Link) https://student.ethernet.edu.et/
ማሳሰቢያ፡-
የህክምና፣ የአካል ጉዳተኝነት፣ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች እና ከ6 ወር በታች ህፃን የሚያጠቡ እናቶች አስፈላጊውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ ይኖርባችኋል።
ትምህርት ሚኒስቴር | 2 762 |
| 13 | "ጦርነቱ ከተጀመረ የኤርትራ ጄኔራሎች ይደመሰሳሉ፤ተመለሱ የሚለንም የለም!" - ኮሎኔል ነጋሽ‼️
የኤርትራ አመራሮች እጣ-ፈንታ፦** ጦርነት ከተቀሰቀሰ የኤርትራ ጄኔራሎች እና አመራሮች ሙሉ በሙሉ እንደሚደመሰሱና ኤርትራም በአጭር ጊዜ ውስጥ በኢትዮጵያ ቁጥጥር ሥር እንደምትገባ ኮሎኔል ነጋሽ አስጠንቅቀዋል።
የኢትዮጵያ የማያዳግም እርምጃ፦** የኢትዮጵያ ቀዳሚ ፍላጎት ሰላም መሆኑ ቢገለጽም፤ ሀገርን የሚያፈርሱ እና የሚያበጣብጡ ኃይሎችን ግን ዝም ብሎ ከመመልከት አልፎ፣ባሉበት ቦታ ድረስ በመሄድ ተገቢውን ዋጋ እንደሚያስከፍሏቸው ቁርጡን ተናግረዋል።
የተቀየረው የጦርነት አውድ፦** እንደ ቀደመው ጊዜ "ተራራ የመያዝ፣ የመልቀቅ፣የማፈግፈግና የማጥቃት" ዘመን አብቅቷል። አሁን ያለው ውጊያ ከፍተኛ የሰው ኃይልን ማዕከል ያደረገ ሳይሆን፣በአንድ ቦታ ላይ ሆኖ በዘመናዊ የቴክኖሎጂ አቅም ጦርነቱን ማጠናቀቅ ወደሚቻልበት ደረጃ መሸጋገሩን አብራርተዋል።
የ1990ው ታሪክ አይደገምም፦** በ1990 ዓ.ም ኤርትራ ሙሉ በሙሉ ተከባ የነበረ ቢሆንም፤የኤርትራ አመራሮች ከሞት የዳኑት "በጥቂት የኛ አመራሮች" (ወደ ኋላ ተመለሱ ባሉ) ምክንያት እንደነበር ኮሎኔሉ አስታውሰዋል። አሁን ግን ያ ታሪክ እንደማይደገምና "ተመለሱ የሚሉንም የሉም" ሲሉ የማያዳግም መልዕክት አስተላልፈዋል።
https://t.me/Ethio_Zena23
https://t.me/Ethio_Zena23 | 2 858 |
| 14 | ህፃን አግታ 3 ሚ. ብር የጠየቀችው
የቤት ሰራተኛ በጎንደር ተያዘች!
አዲስ አበባ ውስጥ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ የሰባት ዓመቷን ህፃን ፊዮና ሰለሞንን በማገት ወደ ጎንደር ከተማ የወሰደችው መቅደስ ሞገስ የተባለች ወጣት፣ በቁጥጥር ስር መዋሏን የጎንደር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።
ተጠርጣሪዋ ህፃኗን በጎንደር ከተማ ማራኪ ክፍለ ከተማ ዩኒቨርሲቲ አካባቢ በሚገኝ ጫካ ውስጥ ደብቃ በነበረበት ወቅት በህብረተሰቡ ጥቆማና በፖሊስ ጥብቅ ክትትል በቁጥጥር ስር መዋል ችላለች።
ከአክስቷ ልጅ ጋር በመተባበር ወንጀሉን የፈፀመችው ተጠርጣሪዋ፣ ለቤተሰብ በመደወል 3 ሚሊዮን ብር የጠየቀች ሲሆን፣ ከ370 ሺህ ብር በላይ መቀበሏ ተረጋግጧል፤ ፖሊስም ቀሪ ተባባሪዎችን ለመያዝ ክትትል እያደረገ ነው። | 3 076 |
| 15 | "ሜሲ" የሚለው የስም መጠርያ ለማንም እንዳይሰጥ!
የሊዮኔል ሜሲ የትውልድ ከተማ የሆነችው ሮሳሪዮ ወላጆች ለልጆቻቸው "ሜሲ" የሚለውን ስም እንዳይሰጡ ከለከለች።
በአርጀንቲናዋ ሮሳሪዮ ከተማ ወላጆች ለልጆቻቸው "ሜሲ" የሚለውን ስም የመጀመሪያ ስም አድርገው እንዳይሰጡ መከልከሏ ተገለጸ።
አርጀንቲና "ሊዮኔል ሜሲ" የሚለውን ስም በእግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ለማንም የማይሰጥ እና ወደፊትም የማይደገም ልዩ አድርጋዋለች።
በ2014 ከሮዛሪዮ ውጪ የሚኖር አንድ አባት ልጁን "ሜሲ ዳንኤል ቫሬላ" ብሎ ለመሰየም ልዩ ፈቃድ ካገኘ በኋላ ነበር ይህ ክልከላ የወጣው።
ይህንን ተከተሎ የሮሳሪዮ ከተማ ባለሥልጣናት ተመሳሳይ ነገር በከተማቸው መደበኛ በሆነ መንገድ የማይፈቀድ መሆኑን የሚገልጽ መመርያ ያወጡት።
ይህ ለእሱ ያላቸውን ፍቅር እና አድናቆት መግለጫ ነው ተብሏል።
በሜሲ በትውልድ ከተማ ሮዛሪዮ አካባቢ ግራ መጋባትን ለመቀነስ የሕፃናትን ስም "ሜሲ" ብሎ መሰየምን የሚከለክል ሕግ በ2014 ነበር ተደንግጎ የወጣው። | 3 152 |
| 16 | እየተጠናከረ የመጣው ኤል ኒኖ ከባድ የአየር ሁኔታ ስጋት እያሳደረ እንደሆነ ተገለጸ
የዓለም ሜትሮሎጂ ድርጅት እንደገለጸው አሁን ላይ እየተስተዋለ የሚገኘው የኤል ኒኖ ክስተት በ70 ዓመታት ውስጥ ከታዩት በጣም ኃይለኛ ክስተቶች አንዱ ሊሆን እንደሚችል ያስታወቀ ሲሆን፥ክስተቱም ቢያንስ እስከ የካቲት 2027 ሊቀጥል እንደሚችል ተገልጿል።
የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ዓለም ከፍተኛ የአየር ሁኔታ አደጋ ወደሚበዛበት ደረጃ እየገባች መሆኑን አንስተው፥ኤል ኒኖ እየጠነከረ በመምጣቱ የድርቅ፣ የጎርፍ፣ የመሬት ናዳ እና የከፍተኛ ሙቀት አደጋዎች ሊባባሱ እንደሚችሉ ተናግረዋል።
በፓሲፊክ ውቅያኖስ ማዕከላዊና ምሥራቃዊ ክፍል የባሕር ሙቀት በቅርብ ወራት በከፍተኛ ሁኔታ የጨመረ ሲሆን፥በተለይም የባሕር ወለል ሙቀት ከመደበኛው በ2 ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል ።
የኤል ኒኖ ተጽዕኖ በሰው ልጅ ከሚመነጨው የረጅም ጊዜ የአየር ንብረት ሙቀት መጨመር ላይ ተደምሮ የከፋ የአየር ሁኔታ ሊያስከትል እንደሚችል ሳይንቲስቶች ገልጸዋል።
ባለሙያዎች በበኩላቸው የኤል ኒኖ ተጽዕኖ በሰዎች ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ ቅድመ ማስጠንቀቂያ፣ የሕክምና ድጋፍና የአደጋ ዝግጅት ሥርዓቶችን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። | 3 013 |
| 17 | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አዲስ የቤት ፋይናንስ ኩባንያ ይፋ አደረጉ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) ጋር በመተባበር 100 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያለው የመጀመሪያውን የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ አቋቋመ።
በዚሁ ስምምነት መሠረት IFC የ 200 ሚሊዮን ዶላር አስተዋፅኦ የሚያደርግ ሲሆን፤ ተቋሙ በባንክ ዘርፍ ያለውን የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠን በመቅረፍ በመላ አገሪቱ ተደራሽ የሆነ የቤት ፋይናንስ ስርዓት እንደሚዘረጋ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታውቀዋል።
ይህ አጋርነት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገነቡና የኢትዮጵያውያንን ክብር የጠበቁ 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብ እንዲሁም በፋይናንስ ሥርዓቱ ውስጥ የግል ዘርፉን ተሳትፎ ለማስፋት ያለውን ግብ እንደሚያሳካ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ፈጣን፣ ጠንካራ እና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ መገንባቷን አጠናክራ እንደምትቀጥልም አጽንኦት ሰጥተዋል። | 2 906 |
| 18 | 🌼ምን ማስተዋወቅ ይፈልጋሉ❓🌼
📌 የምንሰጣቸው የማስታወቂያ አገልግሎቶች
➠ የ ሙዚቃ ማስታወቂያ
➠ የ ኮንሰርት ማስታወቂያ
➠ የ ድርጅት ማስታወቂያ
➠ የ ዩቲዩብ ቻናል ማስታወቂያ
➠ ትሪትመንቶች እና ሌሎችም የሽያጮች ማስታወቂያ
✔የትምህርት ተቋማት…...
✔የህክምና ማዕከላት (ባህላዊ /ዘመናዊ)…...
✔የትራንስፖርት አገልግሎት…....
✔የስራ አገናኝ ኤጀንሲዎች……
✔ሆቴል፣ካፌና ሬስቶራንቶች......
➲ እንዲሁም የተለያዩ የ Business ስራወችን ከእኛ ጋ መስራት ለምትፈልጉ አናግሩን
ምርትና አገልግሎቶን በተመጣጣኝ ዋጋ ተደራሽ በማድረግ በእጥፍ ያትርፉ።
👝 በአልን አስመልክቶ ልዩ ቅናሽ አድርገን አየጠበቅንዎት ነው
አሁኑኑ ያናግሩን 🫴
👇
@Ethiozenaa_bot | 2 781 |
| 19 | የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 63 ታራሚዎች ውስጥ 62 የህግ ታራሚዎች ሙሉ በሙሉ ማለፋቸው ተነገረ።
የ12 ክፍል ማለፊያ ነጥብ ካመጡት ውስጥ 7ቱ ሴት ታራሚዎች ይገኙበታልም ተብላል፡፡
በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በከፍተኛ ጥበቃና በሴቶች ማረሚያና ማረፊያ ማዕከል እና በዘዋይ ማረሚያ ማእከላት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰዱት ተፈታኞች 63 ሲሆኑ ከእነዚህ ውስጥ 62 ማለፋቸውን ማረመያ ቤቱ አስታውቋል፡፡
በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ማዕከል ፣ በሴቶች ማረሚያ ማዕከላት በመደበኛ የትምህርት መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ እና ለፈተና የተቀመጡት 31 የህግ ታራሚዎች ሙሉ በሙሉ ወደ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችለውን ውጤት ማስመዝገብ ችለዋል፤ከነዚህም ውስጥ 7ቱ ሴቶች መሆናቸው ታውቋል፡፡
በተመሳሳይ የዝዋይ ማረሚያ ማዕከል ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ካስፈተናቸው 23 የህግ ተማሪዎች መካከል 22ቱን ማሳለፍ መዘገባችን የሚታወስ ሲሆን በአጠቃላይ በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ፈተና ከወሰዱ 63 ታራሚስች 62 ማለፋችው ተነግራል፡፡የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ካስፈተናቸው በሁለቱ ማዕከላት አጠቃላይ ተፈታኝ ተማሪዎች መቶ በመቶ ወደ ዩኒቨርስቲ መግባት የሚያስችላቸውን ውጤት ማስመዘገብ ተችሏል፡፡
የሕግ ታራሚ ተማሪዎች ያስመዘገቡትን ውጤት ተከትሎ የቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል የመጀመሪያ ደረጃና አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ሳምሶን ወንድሜነህ እንደተናገሩት ማረሚያ ቤቱ ለታራሚዎች የፈጠረው ምቹ የትምህርት ከባቢ እና የታሪሚዎች ጠንካራ ተነሳሽነት ለዚህ አስደናቂ 100 ከመቶ ውጤት ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸውን ተናግረዋል።
በማዕከላቱ የሚገኙት ትምህርት ቤቶች እንደማንኛውም የህዝብ ት/ቤት ደረጃውን የጠበቀና የተሟላ መምህራን የተመደቡለት መሆኑን የገለፁት አቶ ሳምሶን የህግ ታራሚ ተማሪዎችም በህግ ጥላ ስር ቢሆኑም ትምህርታቸውን በአግባቡ ሲከታተሉ መቆየታቸውንና ለውጤት እንደበቁም አመላክተዋል፡፡
አቶ ሳምሶን አክለውም በማረሚያ ቤት ውስጥ የሚገኙ ሌሎች ታራሚዎች ተስፋና መነሳሳትን የፈጠረ ሲሆን ማረሚያ ቤት የህይወት ማብቂያ ሳይሆን አዲስ ምዕራፍ መጀመሪያ መሆኑን በተግባር ያሳየ ነው፤ ብለዋል።
የህግ ታራሚ ተማሪዎች ያመጡት ውጤት መታረምና መታነፃቸውን ማሳያ በመሆኑን ገልፀው መንግስት በይቅርታና ምህረት መልቀቅ የሚችልበትን መንገድ አሊያም የትምህርት ሚኒስቴር የሕግ ታራሚ መሆናቸውን በመረዳት ትምህርታቸውን በርቀት እንዲከታተሉ ዩኒቨርሲቲዎችን
እንዲያመቻችላቸው ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡
| 2 790 |
| 20 | ለጊዜው ከስራ ታገዱ‼️
2ቱ የትራፊክ የቁጥጥር ባለሙያዎች ለጊዜው ከስራ እንዲታገዱ መደረጉ ተገለፀ::
የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን በከተማዋ የመንገድ ተጠቃሚዎችን ደህንነት ለማስጠበቅና የትራፊክ እንቅስቃሴን ለማስፈጸም በሚያከናውናቸው የመስክ ቁጥጥር ስራዎች ወቅት ከመንገድ ተጠቃሚዎች ጋር አለመግባባቶች እንደሚከሰቱ ገልጿል።
በትናንትናው ዕለት (ነሀሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም) በማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ ሲሰራጭ የዋለውን ምስል አስመልክቶ ተቋሙ ባወጣው መረጃ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች አብራርቷል፦
• የቁጥጥር ባለሙያዎች ደንብ የተላለፈን አሽከርካሪ የመንጃ ፈቃድ በሚጠይቁበት ወቅት "አልሰጥም" በማለት ስራ ማስተጓጎል፣ ስድብ፣ ዛቻ ወይም ሃይል መጠቀም በህግ የሚያስጠይቅ ተግባር መሆኑ ተመልክቷል።
• ተቋሙ በምስሉ ላይ የታየውን አለመግባባት ግራና ቀኝ ያለውን አካል ሚዛናዊ በሆነ መንገድ በማጣራት ላይ እንደሚገኝና እስከዚያው ድረስ በክስተቱ ላይ የተሳተፉት ሁለቱ የቁጥጥር ባለሙያዎች ለጊዜው ከስራ እንዲታገዱ ማድረጉን አስታውቋል።
ህብረተሰቡ የችግሩን የማጣራት ሂደት በስክነት እንዲከታተልና ትክክለኛ ካልሆኑ መረጃዎች እንዲቆጠብ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጥሪ አቅርቧል። | 2 815 |
