ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን። YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8 Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR
Mostrar más📈 Análisis del canal de Telegram ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit
El canal ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit (@ortodoxmezmur) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 167 805 suscriptores, ocupando la posición 149 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 140 en la región Etiopía.
📊 Métricas de audiencia y dinámica
Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 167 805 suscriptores.
Según los últimos datos del 13 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 422, y en las últimas 24 horas de -51, conservando un alto alcance.
- Estado de verificación: No verificado
- Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 12.58%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 5.93% de reacciones respecto al total de suscriptores.
- Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 21 116 visualizaciones. En el primer día suele acumular 9 954 visualizaciones.
- Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 143.
📝 Descripción y política de contenido
El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ።
ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን።
YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8
Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR”
Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 14 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.
አዝጠፈሩም እርሱ መሠረቱም እርሱ ፍጥረታት በሙሉ ስሙን አውድሱ ሱራፌልን ልክህ ከንፋሮቼን ዳሰኝ ለምፄን ተመልክተህ አምላክ አትጣለኝ ለምፄን ተመልክተህ ጌታዬ አትጣለኝ
አዝእንዴት ያለ አንደበት ስምህን ይጠራል ግርማህን አይቼ ልቤ ተሸብሯል ኦዝያን አለፈ ክፋት እጅግ በዝቶ አምላኬን አየሁት በዙፋኑ ፀንቶ/2/
አዝአልአዛር ያንተ ነው መንገድ የወደቀ ከእጅ ያላመለጠ ነዌ ባለፀጋ ንገሥታትም ያንተ በሥልጣን ያሉት ለስምህ ይንበርከክ ይህ ሁሉ ፍጥረት/2/
አዝበድቅድቅ ጨለማ ተስፋ በሌለበት ብርሃን ሆኖ አየሁት የጌታዬን ምሕረት ኃይል ማሸነፍን ጽናትንም ስጠኝ ጠላት እንዳይጥለኝ ፀጋህን አልብሰኝ/2/ ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
አዝጠፈሩም እርሱ መሠረቱም እርሱ ፍጥረታት በሙሉ ስሙን አውድሱ ሱራፌልን ልክህ ከንፋሮቼን ዳሰኝ ለምፄን ተመልክተህ አምላክ አትጣለኝ ለምፄን ተመልክተህ ጌታዬ አትጣለኝ
አዝእንዴት ያለ አንደበት ስምህን ይጠራል ግርማህን አይቼ ልቤ ተሸብሯል ኦዝያን አለፈ ክፋት እጅግ በዝቶ አምላኬን አየሁት በዙፋኑ ፀንቶ/2/
አዝአልአዛር ያንተ ነው መንገድ የወደቀ ከእጅ ያላመለጠ ነዌ ባለፀጋ ንገሥታትም ያንተ በሥልጣን ያሉት ለስምህ ይንበርከክ ይህ ሁሉ ፍጥረት/2/
አዝበድቅድቅ ጨለማ ተስፋ በሌለበት ብርሃን ሆኖ አየሁት የጌታዬን ምሕረት ኃይል ማሸነፍን ጽናትንም ስጠኝ ጠላት እንዳይጥለኝ ፀጋህን አልብሰኝ/2/ ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
አዝምሳሌ የሌለሽ ነይ እመቤቴ ዘመዴ ነሽ ነይ እመቤቴ ያን ክፉ ዘመንን ነይ እመቤቴ ያለፍኩብሽ ነይ እመቤቴ በፍቅርሽ እሳት ነይ እመቤቴ ልቤ ነደደ ነይ እመቤቴ እናትነትሽን ነይ እመቤቴ ስለወደደ ነይ እመቤቴ
አዝየሰውስ ውበት ነይ እመቤቴ ምን ይረባኛል ነይ እመቤቴ ሰረገላዬስ ነይ እመቤቴ መች ያድነኛል ነይ እመቤቴ ከተሠወረ ነይ እመቤቴ ክፉ መከራ ነይ እመቤቴ እድናለሁኝ ነይ እመቤቴ አንችን ስጠራ ነይ እመቤቴ
አዝለስንፍናዬስ ነይ እመቤቴ መቼ ልክ አለው ነይ እመቤቴ ስለ በደሌ ነይ እመቤቴ እተክዛለው ነይ እመቤቴ ለአነጋገሬ ነይ እመቤቴ ማጣፈጫ ነሽ ነይ እመቤቴ ተሰምቻለው ነይ እመቤቴ ድንግል ሆይ ስልሽ ነይ እመቤቴ
አዝለመንገዴ ስንቅ ነይ እመቤቴ ለራቤ መርሻ ነይ እመቤቴ ለታመመ ሰው ነይ እመቤቴ ነሽ መፈወሻ ነይ እመቤቴ የተማጸነ ነይ እመቤቴ በስምሽ አምኖ ነይ እመቤቴ ማን አፍሮ ያውቃል ነይ እመቤቴ ፊትሽ ለምኖ ነይ እመቤቴ ዘማሪት ፋንቱ ወልዴ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
ሐምሌ ፮ /6/በዚችም ዕለት ቅድስት ንስተሮኒን አረፈች። እርሷም ከኢየሩሳሌም ሰዎች ውስጥ ነበረች። እርሷም አስቀድማ ኃጢአተኛ ነበረች ከዚያም በኋላ ንስሓ ገብታ ወደ እግዚአብሔር በተቃጠለ ልብ ተመለሰች የሥጋን ፍላጐቶች ሁሉ ናቀች እመምኔት እስከ ሆነች ድረስ በበጎ ሥራ ሁሉ ትሩፋትንና ተጋድሎን አበዛች። እኀቶችም ከገድል ብዛትና ምግብን ከመተው የተነሣ ሥጋዋ እንዳለቀ አይተው ሥጋሽን እንድትረጂ ጥቂት እህል በወጥ ብዪ አሏት። አብዝተውም ግድ ባሏት ጊዜ ልጆቼ ሆይወደ ቀድሞ ልማዴ እንዳልመለስ ጥቂት ወጥ ስለመብላት አትድከሙ ስለዚህ ወጥ አልበላም አለቻቸው። ከዚህ በኋላ በሰላም አረፈች። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቷ ይማረን ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
አዝእረዳት እርሱ ነው ከሰማያት እግዚአብሔር ጠባቂ የኔን ሕይወት ብርሃኑን በፊቴ የሚያበራ አምላኬ ድንቅ ነው የእርሱ ስራ
አዝበመንገዴ ሁሉ የሚመራኝ ስነሳ ስወድቅም የሚያስበኝ ማንም አልመጣልኝ ከወገኔ ከሁሉም ይበልጣል እርሱ ለኔ
አዝየእዳዬን ደብዳቤ ውድቅ አድርጎ ሕይወቴን መራልኝ ወደ በጎ ኧረ እንደእግዚአብሔር ማን ይሆናል እሱን ለሚፈሩት ይታመናል
አዝእንድ ቀን አስቤ ተጨንቄ ለመኖር አልቻልኩም ተጠንቅቄ ሁሉን ነገር ለእርሱ ትቼዋለሁ በምሕረቱ ጥላ እኖራለሁ ዘማሪ እንዳልካቸው 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
አዝበኢያሪኮ መንገድ ስለምን ቁጭብዬ ብርሃን እጅግ ናፍቆኝ ከሰው ተገልዬ የብርሃን ጌታ ወደ እኔ መጣና ዓይኔን አበራልኝ በእጁ ዳሰሰና
አዝለብዙ ዘመናት አልጋ ላይ ተኝቼ የሚረዳኝ አጣሁ ጠሉኝ ዘመዶቼ የእኔ ጌታ አምላኬ ወደ እኔ መጣና አልጋህን ተሸከም አለኝ ፈወሰና
አዝአሥራ ሁለት ዓመት ደም የፈሰሰኝ ምራቅ እየተፋ ሁሉም ቢያንቋሽሹኝ የጌታዬ ልብሱን ጫፉን ብዳስሰው ኃይልም ከእርሱ ወጣ ደሜን ቀጥአረገው
አዝሰካራም ዘማዊ ወንበዴ ነበርኩኝ የአመጸኞች መሪ ደምን ያፈሰስኩኝ ዛሬ ግን ታሪኬን ጌታ ቀይሮታል ለኃያሉ ጌታ ምስጋና ይገባል ዘማሪ ዳግማዊ ደርቤ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
ሐምሌ ፬ /4/አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሐምሌ አራት በዚች ቀን የቅዱሳን አቡቂርና ዮሐንስ የሥጋቸው ፍልሰት ሆነ። ይህም እንዲህ ነው እሊህ ቅዱሳን የካቲት ስድስት ቀን ሰማዕታት ሆነው በሞቱ ጊዜ ምእመናን ሥጋቸውን ተሸክመው ወስደው በእስክንድርያ ከተማ በስተሰሜን ባለች በቅዱስ ወንጌላዊ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሥውር አኖሩዋቸው እስከ ሊቀ ጳጳሳት ቄርሎስ ዘመንም በዚያ ኖሩ። የእግዚአብሔር መልአክም ለቅዱስ ቄርሎስ ተገለጸለት ወደ ወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያንም ሔዶ የቅዱሳን የአቡቂርንና የዮሐንስን ሥጋቸውን አውጥቶ እንዲሸከም አዘዘው። እርሱም ተነሥቶ ሔደ ከእርሱም ጋራ ብዙ ሕዝቦች ነበሩ በደረሱም ጊዜ ጸለዩ ምድሩንም ሲቆፍሩ ሥጋቸው በውስጡ ያለበት ቦታ ተገለጠላቸው በባሕር ዳርቻ ወደ አለች ወደ ሌላዪቱም የቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ክብርየቅዱሳኑን ሥጋቸውን ተሸክመው አድርሰው በዚያ አኖሩ። በዚያም ቤተ ክርስቲያን ሠሩላቸው በዚችም ቀን ታላቅ በዓል አደረጉ ከሥጋዎቻቸውም ድንቆች ተአምራት ተገለጡ አረማውያንም ተሰበሰቡ ይህንንም ድንቅ ተአምር በአዩ ጊዜ ጣዖቶቻቸውን ትተው ክርስቲያኖች ሆኑ ። በዚያቺም የጣዖቶች ቤት አሸዋ በላይዋ ተከመረባት ታላቅ ኮረብታም ሆነ። የቅዱሳንም ሥጋቸው ታምራትንና ለበሽተኞች ታላቅ ፈውስን ያደርጋል። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
አዝአንተ መዝሙረኛ ነብዩ ዳዊት እንድታሸበሽብ በታቦቱ ፊት ሜልኮም ብትንቅህ ሰገነት ላይ ሆና እግዚያብሔር አይትዋታል ሳትናገር ገና እኔስ ለመቤቴ እዘምራለሁ ፍቅርዋ በደሜ ውስጥ እንዳለ አውቃለሁ ስምዋን ለምን ጠራህ ተብየ ስተየቅ አድምጡልኝ መልሴን ድንግልን እኔ አለቅ በአማን /2/እረዳቴ ናት እመቤታችን
አዝየኤልዛቤት ጭፍሮች መጥተው ይዘውኝ ጭው ያለ በረሃ እስርቤት ጣሉኝ ስለ እስራቴ ጌታየ አይቶልኛል ሁሉን ተመልክቶ ተበቅሎልኛል ከዝምታየ የተነሳ እንደ ዲዳ ሆንኩኝ ለበጎ ነገርን እንኩዋ ዝምም ያልኩኝ በእኩለ ለሊት ሊያስፈራሩኝ መጥተው ሳህሊለነ ብዬ ብርታትን አገኘሁ በአማን /2/እረዳቴ ናት እመቤታችን
አዝእረበናት ዛሬም መስክረው ሀሰት ወደ ፍርድ ወሰዱኝ ከማላውቅበት ከሳሾችም ቀርበው ሲከራከሩኝ እውነተኛው ዳኛ አሰናብበተኝ የምስጋናም ዘውድም ጌታ ደፍቶልኛል ለድንግል ውዳሴን ላቀርብ ፈቅዶልኛል ባለምዋልናትና ለቅድስት ስላሴ እስከ መጨረሻው ታመስግናት ነፍሴ በአማን /2/እረዳቴ ናት እመቤታችን ዝማሬ በቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
አዝተጨንቄአለሁ ልንገርሽ ምስጢረኛዬ እናቴ ነሽ ሰው ያልሰማውን ብርቱ ምስጢር ድንግል ሆይ ላንቺ ላማክር የቁስለኛው መድኃኒቱ የአዳም ዘር ሁሉ ነሽ ህይወቱ መፍትሄ አለ በእጅሽ ተንበርክኬ ልማጸንሽ
አዝሳልናገረው ይገባሻል የውስጤ ሁሉ ይታይሻል ድረሽ እናቴ ተራጅኝ ያላንቺ ለኔ ማን አለኝ ደስታዬ ደሰታ የሚሆነው በሀዘኔ የምጽናናው አንቺ ከእኔ ጋር ስለሆንሽ ተጽናንቻለው በስምሽ
አዝወንድሞቼ እንኳን ቢሸጡኝ ሰው ሁሉ ጠላት ቢሆነኝ በእመ አምላክ ኃይል ከብሬአለሁ በጠላቴ ላይ ሰልጥኛለሁ የረሰኙ ሁሉ ያስቡኛል የተጣሉኝም ያከብሩኛል አንቺ አንግሰሽኝ አልወድቅም እቆማለሁኝ ዘለዓለም
አዝመንገዴ እረዝሞ ደክሜብሽ መከራው በዝቶ ታምሜብሽ ወድቄ ሳዝን ድረሽልኝ ለባሪያሽ ሃይሉን እንድትሰጭኝ ፍቅርሽ በውስጤ ተንሰራፋ በእናትነትሽ ልቤ ሰፋ የሚለያየን ማንም የለም ማርያም ልበልሽ ለዘለዓለም ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
ሐምሌ ፫ /3/በዚች ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሃያ አራተኛ የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ቅዱስ አባት ቄርሎስ አረፈ። ይህም ቅዱስ የእናቱ ወንድም በሆነው በአባ ቴዎፍሎስ ዘንድ አደገ ጥቂት ከፍ ባለ ጊዜም ወደ አስቄጥስ ወደ መቃርስ ገዳም ላከው በዚያም አምላካውያት የሆኑ መጻሕፍትን ተማረ እግዚአብሔርም መጽሐፍን አንድ ጊዜ አንብቦ እስከሚአጸናው ድረስ ዕውቀትንና ማስተዋልን ሰጠው። ከዚህም በኃላ ደግሞ ያስተምረው ዘንድ ለአባ ሰራብዮን ሰጠው ከእርሱም ዘንድ ያለውን ትምህርቱን በፈጸመ ጊዜ ወደ ሊቀ ጳጳሳት ቴዎፍሎስ መለሰው ። እርሱም እጅግ ደስ ተሰኘበት እግዚአብሔርንም አመሰገነው። ከዚህም በኃላ ሁልጊዜ መጻሕፍትን እንዲያነብና ሕዝቡን እንዲያስተምር በሊቀ ጵጵስና ሥራ ውስጥ ሾመው። ከትምህርቱም ጣዕም የተነሣ ዝም ይል ዘንድ ማንም አይወድም ነበር። አባ ቴዎፍሎስም ከአረፈ በኃላ በእስክንድርያ ከተማ ላይ ይህን አባ ቄርሎስን ሊቀ ጵጵስና ሾሙት በዘመኑም በትምህርቱ ቤተ ክርስቲያን በራች። ይኸው አባት ቄርሎስ የቁስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳሳት የነበረው ንስጥሮስ በካደ ጊዜ ተከራከረው ከስሕተቱም ባልተመለሰ ጊዜ አውግዘው ከመንበረ ሢመቱ አሳደዱት። ከዚህ በኋላ ብዙዎች ድርሳናትን ተግሣጻትንና መልእክቶችን ደረሰ። በወንጌላዊ ማርቆስ መንበር ላይ ሠላሳ ሁለት ዓመት ኖረ መልካም የሆነ ሥራውንም ፈጽሞ በሰላም አረፈ ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት ጸሎተወ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
