es
Feedback
ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

Ir al canal en Telegram

በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

El canal ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (@beteafework) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 55 943 suscriptores, ocupando la posición 916 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 588 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 55 943 suscriptores.

Según los últimos datos del 19 septiembre, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 686, y en las últimas 24 horas de 43, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 17.17%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 7.98% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 9 602 visualizaciones. En el primer día suele acumular 4 466 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 114.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 20 septiembre, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

55 943
Suscriptores
+4324 horas
+2507 días
+68630 días
Archivo de publicaciones
ወንድሞቼ ሆይ! ቃሉን ስታነቡ ዝም ብላችሁ ቃላትን ለመቁጠር ብቻ አይሁን። ነገር ግን በቃሉ ውስጥ ያለውን መንፈሳዊ ጣዕም ለማግኘት ጸልዩ። የምታነቡትን በተግባር ለመተርጎም ትጉ። 'ቃሉን የሚሰሙ ብቻ ሳይሆኑ የሚያደርጉት ይጸድቃሉ' ተብሏልና። አንድ ምዕራፍ እንኳ ብታነቡ ያቺ ለአንድ ቀን ስንቅ ትሆናችኋለች። ንስሐ የገባ ሰው ልቡ በቃለ እግዚአብሔር ካልታጠበ ዳግመኛ ወደ ኃጢአት ጭቃ መመለሱ አይቀርም። ቃሉ ግን ልባችሁን ይጠብቃል፤ አእምሮአችሁንም ያበራል። ሰዎች ሆይ! መጻሕፍትን አትናቁ። እነርሱ ከሰማይ ወደ እኛ የተላኩ ደብዳቤዎች ናቸው። የሰማዩ ንጉሥ የላከልህን ደብዳቤ ችላ ብለህ እንዴት ሰላምን ታገኛለህ? በመጻሕፍት ውስጥ የታመሙት ፈውስን፣ ያዘኑት መጽናናትን፣ የወደቁት መነሳትን፣ ንስሐ የገቡት ደግሞ የተስፋን ብርሃን ያገኛሉ። በቃለ እግዚአብሔር የምትታጠብ ነፍስ ዘወትር ለምለም ትሆናለች። ስለዚህ በቤታችሁ መጻሕፍትን ለማንበብ ጊዜ መድቡ። ልጆቻችሁንም በቃለ እግዚአብሔር ኮትኩቱ። ዓለማዊ እውቀት ለሥጋዊ ሕይወት ይጠቅም ይሆናል፤ መንፈሳዊ እውቀት ግን ለዘላለም ሕይወት ያበቃል። ንስሐችሁ ፍጹም ይሆን ዘንድ፣ ሕሊናችሁም ከክፉ ሐሳብ ይነጻ ዘንድ ዘወትር በመለኮታዊ መጻሕፍት ንባብ ተጉ። እግዚአብሔር ቃሉን በልባችን ይጻፍልን።" (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ንስሐ ባስተማረበት ድርሳኑ)

“በአውሎ ነፋስ መካከል ብትሆን እንኳ አትፍራ፤ መርከቧን የሚመራት ክርስቶስ እስካለ ድረስ ማዕበሉ አያሰምጥህም፤ እግዚአብሔር ፈተናውን ባያርቀው እንኳ ፈተናውን የምትችልበትን ኃይል ይሰጥሃል።’’ ሊቁ አውግስጢኖስ

#የሐዲስ_ኪዳን_መምህሩን_ሕይወት_እንታደግ በሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ትርጓሜ በርካታ ደቀ መዛሙርትን እያነፁ የሚገኙት መምህር ቀለመወርቅ አመሃ ዛሬ የእኛን የደግነት እጅ መዘርጋት የሚሻ ከባድ የልብ ሕመም ገጥሟቸዋል። በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ጉባላፍቶ ወረዳ በድጎ ደብረ ኢየሱስ አዳሪ ትምህርት ቤት ለ5 ዓመታት ተምረው ከተመረቁ በኋላ፣ በጉባላፍቶ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሐዲስ ኪዳን ትርጓሜን ወንበር  ዘርግተው በማስተማር ላይ ይገኛሉ። አሁን ላይ መምህሩ በገጠማቸው የልብ ሕመም ምክንያት በወልድያ ሆስፒታል ቢታከሙም ከአቅም በላይ በመሆኑ ወደ አዲስ አበባ ለከፍተኛ የልብ ሕክምና ተልከዋል። ሕይወታቸውንም ለማዳን ለሚደረገውን አስቸኳይ የልብ ቀዶ ጥገና ከ300,000 (ሦስት መቶ ሺህ) ብር በላይ ያስፈልጋቸዋል። ሰውን ለማዳን ሰው መሆን በቂ ነውና መምህሩ እንደገና ወደ ወንበራቸው ተመልሰው ደቀመዛሙርትን ማፍራት እንዲችሉ፣ በሀገር ውስጥና በውጭ የምትገኙ ኦርቶዶክሳውያንና ደግ አሳቢዎች በሙሉ የቻላችሁትን በሚከተለው አካውንት ድጋፍ ታደርጉ ዘንድ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም እንጠይቃለን።              #በኢትዮጵያ_ንግድ_ባንክ      ለመምህር ቀለመወርቅ አመሃ በላይ               1000513559821 #ለበለጠ_መረጃ፦ ➛ መምህር ቀለመወርቅ - +251920120104 ሼር በማድርግ ይተባበሩ

ንስሐና ምጽዋት የነፍስ ሁለት ዓይኖች ናቸው። አንዱ ቢጠፋ ሌላኛው ብቻውን ሙሉ እይታ አይሰጠውም። ኃጢአትህ እንዲፋቅልህ ትፈልጋለህን? እንኪያስ የምሕረት በርን በምጽዋት አንኳኳ። 'የሚምሩ ብፁዓን ናቸው፤ ምሕረትን ያገኛሉና' ተብሏል። አንተ ለባልንጀራህ ካልራራህ እግዚአብሔር እንዲራራልህ እንዴት ትጠይቃለህ? ምጽዋት ሰጪውን ከኃጢአት እስራት ትፈታዋለች፤ ተቀባዩንም ከችግር ታሳርፈዋለች። ወንድሞቼ ሆይ! አትሳሳቱ፤ ገንዘባችሁ እዚህ ምድር ላይ ይቀራል። ይዛችሁት የምትሄዱት ምጽዋታችሁን ብቻ ነው። በሕይወት እያላችሁ ለነፍሳችሁ ስንቅ አዘጋጁ። ድሆች የእግዚአብሔር መሠዊያዎች ናቸው። በቤተክርስቲያን ያለውን መሠዊያ እንደምታከብሩ ሁሉ፣ እነዚህን ሕያው መሠዊያዎች (ድሆችን) አክብሩ። በድሃው እጅ ላይ የምታስቀምጠው ስጦታ በቀጥታ ወደ እግዚአብሔር እጅ ይደርሳል። ስለዚህ ንስሐችሁ ፍሬ እንዲያፈራ፣ ጸሎታችሁም እንዲሰማ ዘወትር በምጽዋት ትጉ።" ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ንስሐ ባስተማረበት ድርሳኑ)

#የሐዲስ_ኪዳን_መምህሩን_ሕይወት_እንታደግ በሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ትርጓሜ በርካታ ደቀ መዛሙርትን እያነፁ የሚገኙት መምህር ቀለመወርቅ አመሃ ዛሬ የእኛን የደግነት እጅ መዘርጋት የሚሻ ከባድ የልብ ሕ
+2
#የሐዲስ_ኪዳን_መምህሩን_ሕይወት_እንታደግ በሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ትርጓሜ በርካታ ደቀ መዛሙርትን እያነፁ የሚገኙት መምህር ቀለመወርቅ አመሃ ዛሬ የእኛን የደግነት እጅ መዘርጋት የሚሻ ከባድ የልብ ሕመም ገጥሟቸዋል። በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ጉባላፍቶ ወረዳ በድጎ ደብረ ኢየሱስ አዳሪ ትምህርት ቤት ለ5 ዓመታት ተምረው ከተመረቁ በኋላ፣ በጉባላፍቶ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሐዲስ ኪዳን ትርጓሜን ወንበር ዘርግተው በማስተማር ላይ ይገኛሉ። አሁን ላይ መምህሩ በገጠማቸው የልብ ሕመም ምክንያት በወልድያ ሆስፒታል ቢታከሙም ከአቅም በላይ በመሆኑ ወደ አዲስ አበባ ለከፍተኛ የልብ ሕክምና ተልከዋል። ሕይወታቸውንም ለማዳን ለሚደረገውን አስቸኳይ የልብ ቀዶ ጥገና ከ300,000 (ሦስት መቶ ሺህ) ብር በላይ ያስፈልጋቸዋል። ሰውን ለማዳን ሰው መሆን በቂ ነውና መምህሩ እንደገና ወደ ወንበራቸው ተመልሰው ደቀመዛሙርትን ማፍራት እንዲችሉ፣ በሀገር ውስጥና በውጭ የምትገኙ ኦርቶዶክሳውያንና ደግ አሳቢዎች በሙሉ የቻላችሁትን በሚከተለው አካውንት ድጋፍ ታደርጉ ዘንድ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም እንጠይቃለን። #በኢትዮጵያ_ንግድ_ባንክ ለመምህር ቀለመወርቅ አመሃ በላይ 1000513559821 #ለበለጠ_መረጃ፦ ➛ መምህር ቀለመወርቅ - +251920120104 ሼር በማድርግ ይተባበሩ

ሰይጣን ኃጢአት እንድትሠራ ሲገፋፋህ 'ድፍረትን' ይሰጥሃል። 'እግዚአብሔር መሐሪ ነው፣ አንድ ጊዜ ብትሠራው ምን ይልሃል? ቆይተህ ንስሐ ትገባለህ' እያለ በኃጢአት ላይ እንድትደፋፈር ያደርግሃል። አንተ ተሸንፈህ ኃጢአቱን ከፈጸምክ በኋላ ግን ሰይጣን ስልቱን ይቀይራል። ያን ጊዜ ደግሞ 'እፍረትንና ተስፋ መቁረጥን' ያመጣብሃል። 'እንዲህ ያለ ኃጢአት ሠርተህ እንዴት እግዚአብሔር ፊት ትቆማለህ? አንተ ረክሰሃል፣ ንስሐህ ተቀባይነት የለውም፣ ሞትህም ለገሃነም ነው' እያለ በልብህ ይጮኻል። አንተ ግን የሰይጣንን ተንኮል አሸንፈው። ኃጢአት ልትሠራ ስትል 'እፈር'፤ ንስሐ ልትገባ ስትል ግን 'ደፋር ሁን'። ሰይጣን ግን ኃጢአት ስትሠራ እንድትደፍር፣ ንስሐ ስትገባ ደግሞ እንድታፍር ያደርግሃል። ይህ ትልቅ ስህተት ነው። ኃጢአት ቍስል ነው፣ ንስሐ ግን መድኃኒት ነው። ቍስል ያለው ሰው ቍስሉን ለሐኪም ለማሳየት አያፍርም፤ ካሳየው ይፈወሳል፣ ከሸሸገው ግን ይበሰብሳል። አንተም ኃጢአትህን ለእግዚአብሔር ንገረው፤ እርሱም ይፈውስሃል። (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ንስሐ ባስተማረበት ድርሳኑ)

አንተ ሰው እስኪ ንገረኝ! በዓይንህ ውስጥ ጉድፍ እንዲገባ የማትፈቅድ ኾነህ ሳለ በነፍስህ ላይ እልፍ ወትእልፊት የጉድፍ ክምሮች እንዲገቡ ቸለል ትላለህን? ታዲያ ዕለት ዕለት በነፍሳችን ብሌን ላይ እያከማቸነው ያለነውን ቆሻሻ የምናጸዳው መቼ ይኾን? እሾኾቹን የምንቆርጣቸው መቼ ይኾን? አረሞችን የምንነቅላቸው መቼ ይኾን? እንግዲህ ወዲህ መከሩ እንደ ቀረበ አታውቅምን? እኛ ግን እርሻችንን እንኳን ገና አላረስንም፣ አላለሰለስንም፡፡ እንግዲህ ገበሬው (የወይኑ ባለቤት) በመጣ ጊዜ ስሕተት ቢያገኝ ምንድን ነው የምንለው? እኮ የምንመልሰው ምን ይኾን? ዘር የሚሰጠንን ሰው አጥተን ነው ብለን ነው የምንለው? በፍጹም! ዘሩ'ማ ዕለት ዕለት እየተዘራ ነው፡፡ እሾኾቹን የሚቆርጥ ሰው አጥተን ነው የምንለው? ኧረ በጭራሽ! ዕለት ዕለት ማጭዱን እንደ ሳልን ነው፡፡ የዚህ ዓለም ሕይወት ውጣ ውረድ ይዞህ ነውን? ለምን ታዲያ ይህ ዓለም በአንተ ዘንድ ስቁል አልኾነም? የተበደረውን ዕጥፍ ሳያደርግ ያንኑ ብቻ መልሶ የሚከፍል እርሱ ክፉ አገልጋይ ከኾነ ይህቺውን ብትኾን የሚያጠፋስ ምን ብለን ነው ልንጠራው የምንችለው? ያ ሰው እጁና እግሩ ታስሮ ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት ከተጣለ፥ ሠናያትን ገንዘብ እናደርግ ዘንድ የሚያነሣሡን እልፍ ምክንያቶች እያሉ ወደ ኋላ የምንልና የማንፈቅድ እኛ ታዲያ እንደ ምን ያለ መከራ ይገባን ይኾን? እንዲህ እንዳታደርግ አንተን ለማሳመን የማይበቃው እስኪ የትኛው ነው? የዓለሙን ርኵሰት አላየህምን? የዚህን ዓለም ሕይወት ርግጠኛ ያለመኾን አልተመለከትክምን? የዚህን ዓለም ድካም፣ በዚህ ዓለም ለሚቀር ደመወዝ የሚወጣውን ላብ አላየህምን? እኮ እስኪ ንገረኝ! ምግባር ሲሠራ ላብ ጠብ ርግፍ የሚያደርግ ክፋት ሲሠራ ግን ምንም ምን ድካምና መከራ የሌለው ነውን? በፍጹም! ታዲያ በኹለቱም ዘንድ ውጣ ውረድ ካለው ይህን ያህል ትርፍ ያለውን ለምን አትመርጥም? እንዲያውም አንዳንድ ሠናያት ድካምን የሚጠይቁ አይደሉም፡፡ እስኪ ንገረኝ! የስድብ ቃልን ላለመናገር፣ በባልንጀራህ ላይ ላለመቈጣት፤ ላለመዋሸት፤ ላለመማል የሚፈልግብህ ድካም እንደ ምን ያለ ድካም ነው? ምንም ድካምን አይጠይቅም! ይልቅስ እጅጉን ድካም ያለውና ብዙ የሚያስጨንቀው እነዚህን ለማድረግ ነው፡፡ እንግዲህ እነዚህን እንኳን ላለማድረጋችን ልናቀርበው የምንችል ሰበብ እንደ ምን ያለ ሰበብ እንደ ምን ያለ ምክንያት ይኾን? ከስንፍናችንና ከልል ዘሊልነታችን የተነሣ ድካም የሚጠይቁትንም እንደማንሠራቸው በዚህ ግልፅ ነውና፡፡ ስለዚህ ከዘለዓለም እስከ ዘለዓለም ድረስ ክብርና ኃይል የባሕርይገንዘቡ በሚኾን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ቸርነቱና ሰውን መውደዱ በዚህም ዓለም በወዲያኛውም ዓለም ለዚህ የበቃን እንኾን ዘንድ ይህን ኹሉ ልብ ብለን አስተውለን፥ ከክፉ እንሽሽ፤ ሠናያትንም እንምረጥ፡፡ አሜን! (የማቴዎስ ወንጌል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደተረጎመው ቅጽ 2 ድርሳን 42 ገጽ 368-370 ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተረጎመው)

ሁለቱን ሐሳቦች ተረዷቸውና ተጠንቀቋቸው አንደኛው "አንተ ቅዱስ ነህ" የሚለው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ "መቼም ቢሆን ልትድን አትችልም" የሚለው ነው፡፡ ሁለቱም ሐሳቦች ከጠላት ናቸው፤ በትዕቢትና ተስፋ በመቁረጥ የተሞሉ እውነት የሌላቸው ናቸው፡፡ አንተ ግን ለራስህ ይህን በለው "እኔ ታላቅ ኃጢአተኛ ነኝ ሥራዬ በፊቴ ነው ግን አምላክ መሐሪ ነው! ሰዎችንም በጣም ይወዳል፤ ስለዚህ ኃጢአቴን ይቅር ይለኛል፡፡" አባ ስልዋኖስ ዘአምድ

#ከንስሐ_ርቀን_ይቅርታን_አናገኝም ንስሐ ለተጠመቁ ሰዎች ከጥምቀት በኋላ የተሰጠች ሀብት ናት፡፡ ይህንንም የሚያስረዳ ነገር በጥምቀት ከእግዚአብሔር ከምትገኝ ልጅነት ሁለተኛ ማዕረግ ናት፡፡ በሃይማኖት ገንዘብ ያደረግነው  የመንግስተ ሰማይ መያዣ ከናት፡፡ በንስሐ ምክንያት የእግዚአብሔርን ቸርነት እናገኛለን፡፡ ንስሐ ለሚሿት ሰዎች የተከፈተች የይቅርታ በር ናት፡፡ በንስሐ በርነት ከፈጣሪ ወደሚገኝ ቸርነት እንቀርባለን፡፡ መከላከያ ከሚሆን ከንስሐ ርቀን ይቅርታን አናገኝም፡፡ አምላክ የጻፈው መጽሐፍ እንደተናገረ ሁላችን በድለናልና ያለ ዋጋ በይቅርታው ከኃጢአት እንነጻለን፡፡ ንስሐ እግዚአብሔርን በመፍራት፣ በሃይማኖትና በልቡና የምትገኝ ሁለተኛ ጸጋ ናት፡፡ ሀብታተ ምስጢራት ከሚገኙበት ከመንፈሳዊ ፍቅር እስክንደርስ ድረስ የሚጠብቀን መንፈሳዊ ዕውቀት ነው፡፡ (ምክር ወተግሣጽ ዘማር ይስሐቅ)

እግዚአብሔር የሚወዳችሁ አንድም እግዚአብሔርን የምትወዱት ወንድም እኅቶቼ ሆይ! እግዚአብሔር በሥጋ ከባረከን በላይ በነፍስ የባረከን ይበልጣልና ስለዚሁ ልናመሰግነው ይገባናል፤ ምድራዊ መጠጥን አንድም ምድራዊ መብልን ከመስጠት መንፈሳዊ መጠጥንና መብልን መስጠት ይበልጣልና፡፡ እግዚአብሔር አስቀድሞ ለእሥራኤላውያን መናውን የሰጣቸው በኋላም እስራኤል ዘነፍስ ለምንባል ለእኛ ቅዱስ ሥጋዉንና ክቡር ደሙን የሰጠንም ስለዚሁ ነውና በሥጋ ከሰጠን ይልቅ በነፍስ የሰጠን ስለሚበልጥ እግዚአብሔርን እጅግ ልናመሰግነው ይገባናል፡፡ እግዚአብሔር በሥጋ ሲባርከን በዚያው (በሥጋዊው ነገር ላይ ብቻ) እንድንቀር አይደለም፤ የበለጠ ወደርሱ እንድንቀርብ ነው እንጂ፡፡ ሥጋዊውን ስጦታ ይዘን የምንቀር ከሆነ ግን ዓላማውን ስተናልና ልናስተካክል ይገባናል፡፡ ተወዳጆች ሆይ! በአፍአ ከተባረክነው ይልቅ በነፍስ የተባረክነው ይበልጣልና ስለዚያ እግዚአብሔርን ልናመሰግነው ይገባናል ብዬ እማልዳችኋለሁ፡፡ ለምን? መንፈሳዊው ነገር ከእኛ ዘንድ ካለ፥ ሥጋዊ ነገር ቢቀርም ምንም አናጣምና፡፡ መንፈሳዊውን ካጣን ግን ከእኛ ዘንድ ምን ተስፋ፥ ምንስ መጽናናት ይቀርልናል? አስቀድመን መንግሥቱንና ጽድቁን እንድንሻ የተፈለገውም ስለዚሁ ነው፡፡ የምወዳችሁ ልጆቼ! አስቀድመን እውነተኛውን ሀብት ይኸውም ሰማያዊውን ሀብት እንለምን፤ ርሱንም ለማግኘት እንጣጣር ብዬ እማልዳችኋለሁ፡፡ ሌላው ከዚያ በኋላ ይቀጥላል፡፡ እኛ ስለለመንን ሳይሆን ልቡናችን ዋናውን ስለፈለገ፡፡ ጸሎታችንን የምናገላብጠው ከሆነ ግን በነፍስ በሥጋ የተጐዳን እንኾናለን፡፡” (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ- የክርስቲያን መከራ እና ሌሎች ገጽ 27)

እግዚአብሔር የሚወዳችሁ እናንተም የምትወዱት ልጆቼ! አዲሱ ዓመት የእውነት አዲስ ዓመት እንዲኾንላችሁ ካሻችሁ ነፍሳችሁን ከኀጢአት ቀንበር አላቋት እንጂ ድጋሜ በኀጢአት ሸክም አትጫኗት፡፡ አሮጌው ዓመት እንዳለቀ ስታዩ እግዚአብሔርን አመስግኑት፡፡ ወደሌላ ዘመን አሸጋግሯቸዋልና እግዚአብሔርን አመስግኑት፡፡ ልቡናችሁንም ውቀሱት፡፡ በዕሜአችሁ ስንት ጊዜ እያለፈ እንደ ኾነ እያሰባችሁም ራሳችሁን እንዲህ ብላችሁ ጠይቁት፡- “ቀናት እየሮጡ ነው፡፡ ዓመታቱም እየነጐዱ ነው፡፡ የዕድሜዬ መንገድም እየተጋመሰ ነው፡፡ ታዲያ ምን በጐ ምግባር ያዝኩ? ከዚህ ምድር የማልፍበት ቀን እየቀረበ ነው፡፡ ታዲያ ምን የጽድቅ ሥራ ሠራሁ? በዚህ ዕድሜዬ መሥራት የነበረብኝ ምግባር ትሩፋት ዕድሜዬ ሲገፋ ማድረግ አልችልም፡፡ ታዲያ ዕድሜዬ ሲገፋ ማድረግ የማልችላቸውም የጽድቅ ሥራዎች (ፆም፣ ጸሎት፣ ስግደት፣ አገልግሎት፣… ዕድሜ ሲገፋ ይከብዳሉና) እንዳቅሜ እያደረግኩ ነውን?” ተወዳጆች ሆይ! አዲስ ዓመት ሲመጣ እነዚህን ነገሮች በጥንቃቄ ልናስብባቸው ይገባናል፡፡ ይህን እያደረግንም ስለ ቀጣዩ ዓመት እናስብ፡፡ ይህን የምናደርግ ከኾነ “ቀኖቻቸውም በከንቱ አለቁ፤ ዓመቶቻቸውም በችኰላ” አይባልብንም (መዝ.78፡3)፡፡ ዕለት ዕለት በዓልን እናድርግ ብዬ የገለጥኩላችሁም ይኸው ነው፡፡ የእኛ በዓል ዘወትር መኾን ይገባዋል፡፡ የክርስቲያኖች በዓል በዓመታትና በቀናት ብቻ መወሰን የለበትም፡፡ ቤተ ክርስቲያንም በሳምንት፣ በወር፣ በዓመት የሚከበሩ በዓላት እንዲኖሩ ማድረጓ ዘወትር ከዚሁ ልንርቅ እንደማይገባ ማሳሰቧ እንጂ ሌላ አይደለምና፡፡ ይህን በዓል በየዕለቱ ማድረግም ለኹሉም ይቻላል፤ ለድኻውም ለባለጸጋውም ይቻላል፡፡ በዓልን ለማድረግ (የጽድቅ ሥራን ሠርቶ ሐሴት ለማድረግ) የሚያስፈልገው ቅን ልቡና እንጂ ገንዘብ አይደለምና፡፡ (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ  ሰማዕትነት አያምለጣችሁ ገጽ 13-19 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመው)

“ፊተኛ ኑሮአችሁን እያሰባችሁ እንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዱ፥ በአእምሮአችሁም መንፈስ ታደሱ፥ ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ።” ኤፌ 4፥22

#የአዲስ_ዓመት_ጸሎት_በአቡነ_ሺኖዳ አቤቱ ጌታ ሆይ፦ ዓመቱን የተባረከ አድርገው። አንተን ደስ የሚያሰኝ ንጹሕ ዓመት ይሁን። መንፈስ የሚገለጥበት ዘመን ይሁን፣ ከእኛ ጋራም ይሥራ፤ እጆቻችንን ያዝና አሳቦቻችንን ከዓመቱ መጀመሪያ እስከ ማብቂያው ድረስ አንተ ምራቸው። አንተ ደስ ያሰኝህ ዘንድ ይህ ዓመት የአንተ ይሁን፡፡ ይህ አመት አዲስ ዓመት ስለሆነ በኃጢአታችንና በበደላችን አናርክሰው። እግዚአብሔር ሆይ፦ በዚህ ዓመት ልንሠራው ባቀድነው በማንኛውም ሥራ ውስጥ አንተ ከእኛ ጋር ሁን፤ እኛ ዝም እንላለን አንተ ሁሉንም ነገር ታደርጋለህ፡፡ አቤቱ ጌታ ሆይ፦ ይህ ዓመት መልካም ይሁን። በእያንዳንዳችን ላይ ፈገግታን ግለጥ፤ የሁላችንንም ልብ አስደስት፤ በችግራችን ውስጥ ጸጋህ ይገለጥ፤ የተፈተኑትንም አንተ እርዳቸው፤ የአሳብ ሰላምንና ጸጥታን አድለን፡፡ ለተቸገሩት ስጣቸው፤ የታመሙትን ፈውሳቸው፣ ያዘኑትን አጽናናቸው፡፡ ጌታችን ሆይ፦ ለራሳችን ብቻ አንጠይቅህም ያንተ ስለሆኑት ስለሁሉም እንጠይቃለን የፈጠርኻቸው ባንተ ደስ እንዲሰኙ ነው ይህ ከሆነ በአንተ ደስ እንዲሰኙ አድርጋቸው ቃልህ ለሁሉም ልብ ይደርስ ዘንድ ስለ ወንጌል አገልግሎትና ስለ ቤተ-ክርስቲያናችን እንጠይቅሃለን፤ ስለሃገራችንም እንጠይቅሃለን፡፡ መንግሥትህ በሁሉ ስፍራ እንድትመጣም ስለ ዓለም ሰላም እንጠይቅሃለን፡፡ ዓመቱ ፍሬያማና በመልካም ነገሮች የተሞላ ይሁን፡፡ እያንዳንዱ ቀንና ሰዓት የራሱ የሆነ ስራ አለው አንተ የሚባክን ጊዜ ይኖርህ ዘንድ አትፍቀድ፡፡ ሕይወታችንን በእንቅስቃሴ በሥራና በምርት የተሞላ አድርግ፤ ለምርታማና ለተቀደሰ ልፋታችን በረከትህን አድለን፡፡ በተግባራችን ውስጥ ሁሉ የመንፈስ ቅዱስ ኅብረት ከእኛ ጋር ይሁን። አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ እስከዚች ሰዓት ድረስ ጠብቀህ ስላቆየኸንና ይህንን ዓመት ስላደልከን እናመሰግንሃለን፣ እንባርክህማለን፡፡