cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

Advertising posts
1 203Subscribers
+124 hours
+17 days
+2330 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Once in Persia reigned a king Who upon his signet ring Graved a maxim true and wise, Which if held before the eyes Gave him counsel at a glance Fit for every change and chance. Solemn words, and these are they: "Even this shall pass away." Theodore Tilton ቴዎዶር ቲልቶን የጻፈው ድንቅ ጽሑፍ ነው። ፐርሺያ ላይ የነበረ ንጉስ ጣቱ ላይ ባለ ቀለበት ጥበብንና ዕውነትን ተሰጥቶ ነበር። ንጉሱ ቀለበቱን በጨረፍታ ሲያይ ምክር ነገር በልቡ ውስጥ ታፈስለታለች። ታዲያ በዚህ ኹኔታ የተናገረው ከመሬት ጠብ አይለይም ነበር አሉ። "ይህም ያልፋል" የሚለው አባባል የዛ ንጉሥ ድንቅ አባባል ነበር። ይህ ዜና ከተረት ዓለም ቢኾንም ተረቱን የነገሩን፥ ጸሐፊውም አልፈዋል። ነገ እኛም ከነ ዛሬ ጣጣዎቻችንና ሕልሞቻችን እናልፋለን። ይህን ጽሑፍ ካነበብኹት ቆየ _1993 ገና ታች ተማሪ እያለኹ ነበር። የደራሲውን ቃላት ቅሸራ ከስነጽሑፍ ክህሎቱ ጋር አድንቄ ግጥሙን ሸመመደድኹት። እነሆ 23 ዓመታት እንደ ዋዛ ሽውውውውው ብለው አልፈዋል። ዛሬ ላይ የተሾሙብን ኹሉ ነገ ታሪክ ናቸው። ክፉ ወይም መልካም ታሪክ። ችግሩ ኹሉም ከዙፋኑ ላይ ሲወጣ ትላንት የነበረውን ዐፈርማ ሕይወት ይረሳል። የተሰቀለበት መወጣጫ ይዞት እንደሚወርድ ይዘነጋል። كل من عليها فان ويبقى وجه ربك ذو الجلال والاكرام https://t.me/E_M_ahmoud
Show all...
መስጋብር ..... ሰው ምንም ያህል በዕውቀት ቢነጠቅ ከየትኛውም የዘር ሐረግ ቢመዘዝ ሰብዓዊ ግብረገብነቱ የሰዎች አይነታ ያደርገዋል። ከሰዎች በቀለም ትምህርታቸው እጅግ ከፍ ያሉ፣በሰበሰቡት ንዋይ ሆዳቸው የከበደ አንገታቸውም የደነደነ አሉ። ታዲያ ምን ዋጋ አለው ስብዕናቸው የጭድ ቃንቄ(ፍም) ነው። የጭድ ቃንቄ የነፋስ ሽውታ ይቀሰቅሰዋል። የትም ደርሶም ሐገር ያጠፋል። የነዚህም ሰዎች ባህሪ እንዲሁ ነው። ኢስላም በወፍራሙ ካሰመረበት ቁም ነገር ውስጥ ግብረ - ገብ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። መልክተኛው (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ) የነብይነት መቀምቀሚያቸው (ማጠቃለያ) መልካም ስብዕናን ማሟላት ነው። إنما بعثت لأتمم مكارم الأخلاق በውሸት የተካበ ስብዕና በካፊያ ዕውነት ይሸረሽራል። በአጓጉል መተናነሰ የተቀለመ ገጽታ በቀሊል ጉዳይ ይገለጣል።
Show all...
7👍 2
Show all...

Show all...

👍 8
ዘርኝነት እዚህ ሲደርስ… …… ወዳጄ እንደምን ከረሙ!? ከሰሞኑን ከሰሜን ከላው አለመረጋጋት አንጻር ኣንዳንድ አካላት ድንበር ያለፈ ነገር መናገራቸው እየተሰማ ነው፡፡ ሰው ይወክለኛል ያለውን ጎሳ/ብሄር መውደዱ ምናልባት ምናልባት ተፈጥሮኣዊ ሊኾን ይመቻል፡፡ ግን ደግሞ በዚህ ልክ ሃይማኖቱን እስኪያስበልጥና ምናልባትም ከኢስላም ሊያስወጣው የሚችልን ነገር ከዘሩ አኳያ መናገሩ ይህ አውላጥ (ጎርፍ ያመጣው ቆሻሻ) በዚህ ልክ ከተከመረ ጨርሶ መንገዱን እንዳይዘጋውና ሕዝቤ መውጫ መግቢያ እንዳያጣ ያሰጋል፡፡ በዚህ ልክ የተለጠጠ ራስ ወዳድነትና በለሌሎች ሕዝቦች ላይ ያነጣጠረ ንቀት ደም ከማቃባት በዘለለ አላህ ዕርም ያደረገውን ነፍስ ማጥፋት ሐላል እስከማድረግ ከደረሰ በቀጥታ ከኢስላም ሊያስወጣ እንደሚችል ይሰመርበት፡፡ አንዲትን ኣማኝ ሙስሊም እንስት ማግባት ከሺህ ኢኣማኝ እንስቶች እንደሚበልጥ መወዳደርም በፍጹም እንደማይችል እየታወቀ፣ እነ ኣባ ጉርምርሜ ለቃርሚያ በወጣበት የጌሾ ቅጠል አላምጦ እንደ ሰከረ ውርንጭላ ከሙስሊሟ ሴት ከኔ ጎሳ ናት የሚሏትን ኢኣማኝ ማስበለጣቸው የዘረኝነት በሽታቸው የት እንደ ደረሰ ያሳያል፡፡ ኣንዳንዶች ደግሞ አልፈው ሄደው የራሳቸውን “ሐዲስ” ፈጥረው መልክተኛው (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ስለ እኛ እንዲህ ብለዋል የሚል ንግግር ተናግረዋል፡፡ ሆድ እያወቀ በመልክተኛው ላይ መዋሸት ከትላልቅ ወንጀል ስለኾነ የዛ ሰፈር ሙሾ አውራጆች በጊዜ ተውባው ቢቀድማችኹ ያዋጣል፡፡ የተቀራችኹት ደግሞ ከዛ ሰፈር ኢስላማዊ ነጻነትን እየጠበቃችኹ ከኾነ፣ እስኪ ወደ ኋላ ሂዱና አጼዎቹ በሙስሊሙ ላይ ምን እንዳደረጉ የታሪክ ግረባ ያድርጉ፡፡ ዛሬም ጭምር በዛ አካባቢ ሙስሊም ላይ ምን እየኾነ እንደኾነ ለማየት ሞክሩ፡፡ በሞጣ ከተማ ሙስሊም ላይ የኾነው ኹሉ ዛሬም ድረስ ፋናው፣ጭሱና ረመጡ አለ፡፡ ታዲያ እንደምነው ይህንን ረመጥ መዝገን ይከጀላችኹት? ወይስ ያ ኹሉ ውሸት ነበር?! መንገድና ኔት ተዘግቶ በሙስሊሙ ንብረትና መስጂድ ላይ ያ ኹሉ ውድመት ደርሶ፣ለተፈጠረውም ጥፋት የክልሉ መንግስት ምንም ይቅርታ ሳይጠይቅ በቀረበት ኹኔታ ዛሬ ምን ተገኘና ነው ከዛ ስብስብ ነጻነትን የምትጠብቁት ጃል? ሰዎቹ ከሞጣ ማስወጣት የቻሉትን ኹሉ ሙስሊም ንበረቱን አስቀርተው አንዳስወጡት፣የንግዱን ዓለም ክርስቲያን በሚሏቸው እንደተኩት በፉከራ ሲናገሩ ታይቷል፣ ተስምቷል፡፡ እዛ ሰፈር ያለ ሙስሊም ኹሉ ኩነኔ ውስጥ እንደሚማቅቅ ነፍስ የሰርክ ሞት እየሞተ ባለበት፣ እነዴት ኾኖ ነው እነ ሙሄ አበጋዝ ከዛ ሰፈር የሉዓላዊነት መለከት እንዲነፋላችኹ የምታስቡት?! የፈሰሰው የሙስሊሙ ደም፣ በከንቱ የጠፋው የሙስሊሙ ነብረት ካልከነከናችኹ፣ በተመሳሳይ በናንተ ላይ ይህ መኾኑ ቅርብ ነው፤ ነገ ልጆቻችኹ የሚያፍሩበትንም ታሪክ እየጻፋችኹ እንደኾነ ዕወቁ፤በጨቀየው ልቦቻችኹም ያዙ፡፡ አራት ነጥብ፡፡
Show all...
👍 11💯 3
ቁርአን ከአላህ ለመኾኑ አሳማኝ ነጥቦች (19) https://youtube.com/watch?v=kac4HLnyBCc&feature=shared
Show all...

💯 5👍 1
ቁርአን ከአላህ ለመኾኑ አሳማኝ ነጥቦች (18) https://youtube.com/watch?v=BOekKrCT4k4&feature=shared
Show all...

👍 7
ከረመዳን በኋላ .... ገና ረመዳን ሲገባደድ መመናመን የጀመረው መስጂድ ከረመዳን በኋላ ለምን በዚህ ልክ ሰፍቶ ተሰራ በሚያስብል ልክ ለገባበት ጥቂት ሰጋጅ በጉጉግስ ሜዳ ልክ ሰፍቷል። የመጀመሪያ ሰልፍ ካልኾነ የማይሳካላቸው ኹሉ የመጨረሻውም እርማቸው ኾኖ ማየት አላህ በሰውዬውና በልቦናው መካከል እንደሚለያይ ዕውን ማሳያ ነው። ሰላቱን ከመስጂድ መስገድ የተሳነው ኅልቆ መሳፍርት የባሕር አሸዋ ሕዝብ ከፍ ላለ ተልዕኮ እንደምን ወኔ ሊኖረው ይችላል?! እንደምን ነው ይህ ቁጥር ብቻ የኾነ ጥርቅም ከራሱ አልፎ ስለሌላው ድምጹን አንስቶ የሚጮኸው?! ወጣቱ ተመልሶ ከሚያመነዥከውና ከሚያቦለው ከዋለ፣ረመዳን ስቦት ዲኑን ለመማር አንድ እርምጃ መራመድ ካልቻለና አህያ ቢታጠብ ካመዱ ከኾነ፣ ይህ ስብስብ የበላይነትን ማሰቡ ሐጢአት እንዳይኾን ያሰጋል። إن الله لا يغير ما بقوم حتى يغير ما بأنفسهم ወዳጄ በስህተት ለተረገጠ ጫማችን ሰማይ ይታረስልን እያልን እንደምን ነው መልክተኛው (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) መስጂድ ያልመጡትን ቤታቸውን ላቃጥልባቸው አሰብኹ ያሉትን በዚህ ልክ ችላ ያልነው? ኡኡቴ! ድንቄም የጋራ ኢፍጣር! ድንቄም በኢስላማዊ አለባበስ እንገናኝ አዋጅ! ድንቄም የዒድ አደባባይ! አላህ ዘንድ ጨዋታው መኾን አለመኾን ብቻ ነው። የልቦች ጌታ የኾነው አላህ የታይታ አምላክ በፍጹም አይደለም። ወደድንም ጠላንም ዒዛ የሚገኘው ኢስላምን በመኖር ብቻ ነው። እናት ተመናቅራ ልጅት እንደምን ትሰተራለች?አባት እንደ በሽተኛ ከንፋሰ_ምስሉ (ቴሌቪዥን) ፊት እያጮለቀ እያየ እሰግዳለኹ ቢል ልጅ በየትኛው ልኬት ነው ከመስጂድ የሚመላለሰው?!
Show all...
👏 5👍 3