uz
Feedback
Eliyah Mahmoud

Eliyah Mahmoud

Kanalga Telegram’da o‘tish
5 304
Obunachilar
+2424 soatlar
+547 kunlar
+30330 kunlar
Obunachilarni jalb qilish
Iyul '26
Iyul '26
+90
2 kanalda
Iyun '26
+427
2 kanalda
Get PRO
May '26
+353
14 kanalda
Get PRO
Aprel '26
+174
9 kanalda
Get PRO
Mart '26
+98
8 kanalda
Get PRO
Fevral '26
+61
3 kanalda
Get PRO
Yanvar '26
+97
1 kanalda
Get PRO
Dekabr '25
+107
1 kanalda
Get PRO
Noyabr '25
+96
3 kanalda
Get PRO
Oktabr '25
+176
6 kanalda
Get PRO
Sentabr '25
+71
2 kanalda
Get PRO
Avgust '25
+145
3 kanalda
Get PRO
Iyul '25
+275
1 kanalda
Get PRO
Iyun '25
+252
4 kanalda
Get PRO
May '25
+389
3 kanalda
Get PRO
Aprel '25
+521
5 kanalda
Get PRO
Mart '25
+554
2 kanalda
Get PRO
Fevral '25
+433
1 kanalda
Get PRO
Yanvar '25
+631
4 kanalda
Get PRO
Dekabr '24
+555
2 kanalda
Get PRO
Noyabr '24
+300
4 kanalda
Get PRO
Oktabr '24
+128
1 kanalda
Get PRO
Sentabr '24
+109
2 kanalda
Get PRO
Avgust '24
+134
3 kanalda
Get PRO
Iyul '24
+145
6 kanalda
Get PRO
Iyun '24
+299
5 kanalda
Get PRO
May '24
+140
3 kanalda
Get PRO
Aprel '24
+56
0 kanalda
Get PRO
Mart '24
+72
0 kanalda
Get PRO
Fevral '24
+61
3 kanalda
Get PRO
Yanvar '24
+45
1 kanalda
Get PRO
Dekabr '23
+64
1 kanalda
Get PRO
Noyabr '23
+45
5 kanalda
Get PRO
Oktabr '23
+29
2 kanalda
Get PRO
Sentabr '23
+89
0 kanalda
Get PRO
Avgust '23
+20
0 kanalda
Get PRO
Iyul '23
+15
0 kanalda
Get PRO
Iyun '23
+19
0 kanalda
Get PRO
May '23
+12
0 kanalda
Get PRO
Aprel '23
+25
0 kanalda
Get PRO
Mart '23
+47
0 kanalda
Get PRO
Fevral '23
+11
0 kanalda
Get PRO
Yanvar '23
+40
0 kanalda
Get PRO
Dekabr '22
+36
0 kanalda
Get PRO
Noyabr '22
+198
0 kanalda
Get PRO
Oktabr '22
+63
0 kanalda
Get PRO
Sentabr '22
+269
0 kanalda
Get PRO
Avgust '22
+786
0 kanalda
Sana
Obunachilarni jalb qilish
Esdaliklar
Kanallar
13 Iyul+7
12 Iyul+26
11 Iyul+9
10 Iyul+6
09 Iyul+12
08 Iyul+14
07 Iyul+9
06 Iyul0
05 Iyul+1
04 Iyul0
03 Iyul+2
02 Iyul+2
01 Iyul+2
Kanal postlari
የሰሞኑ የኬጂ ግራጁዌሽን .. መቼም ቀን ሄዶ ቀን ሲተካ የማናየው የማንሰማው ጉድ የለም፡፡ ድሮ ድሮ አንድ ተማሪ ኮሌጅ ወይም ዩኒቨርሲቲ ገብቶ ሲጨርስ ቤተሰቦቹ ደስታቻውን አጋፋሪ ጠርተው ድግስ በማብላት ያከብሩ ነበር፡፡ የቀድሞው ግራጁዌሽን ድግስ በትክክልም የኾኑ ዕንቅልፍ የታጣባቸው አድካሚ የሕይወት ምዕራፎች ታልፈው፣ ከዩኒቨርሲቲ የካምፕ ሕይወት ወደ ቀጣይና እረፍትም ወዳለበት የተሻለ ምዕራፍ መሸጋገሪያ ድልድይ ስለነበር፣በትክክለኛ ቦታው የሚደረግ ሷደቃ ነበር፡፡ ፊደል እየቆጠረና በመሐከልም እየተኛ ከኬጂ ወደ ክላስ የተላለፈን አንድ ተማሪ ምናልባት የተሻለ ንቃት ኖሮት ትምሕርቱን እንዲቀጥል ለማድረግ መጠነኛ የቤት ውስጥ መሰናዶ ማድረጉና በተቀረው ገንዘብ ደግሞ በዙሪያችን ላሉ ድሆች ምጽዋት ማድረጉ ተመረቀ ላልነው ሕጻን ትልቅ ማስታወሻ አዘል ትምህርት ይኾን ነበር፡፡ በተቃራኒው ግን የመቶ ሺህ ብሮች ስጦታና ድንኳን ተጥሎ፣ አሞራ የሚያወርድ ድል ያለ ድግስ ተደግሶ፤ድግሱ አልበቃ ብሎ በሙሽራ ልኬት ከሽንጠ ረዥም ሊሞዚን ውስጥ ጨቅላው አንገቱን አውጥቶ ዕጁን እያወዛወዘ ከተማ ላይ ሽር ብትን ሲል ማየት፣ ጉዳዩ የጉራና የታይታ ጥግና ጠርዝ ካልተባለ በቀር ምንም ሊባል አይችልም፡፡ እንዲያው እንዴት እንዴት ብንለካካ ነው ጃል በዚህ ልክ ገንዘብ ሰበሰብኹ ያለ ኹሉ ነጋሪት እየጎሰመ “በሃይ ሎጋ ሆ”፣ በክላክስና “በዓልምሽ ዛሬ ነው ዛሬ” የልጁን ፊደል ቆጠራ እንደ ሰርጋና ምላሽ የሚያከብረው? ገና ጎዞውን “ሀ” ብሎ ላልጀመረ ጨቅላ በዚሕ ልክ ያለንን ዕወቁልን በሚመስል መልኩ የሐብት ብክነት ሲፈጸም መንግስት ዝም ሊል አይገባውም፤ ይልቁን ብዙኃኑን ከርቸሌ ለማስገባት አጓጉል ሕግ እንዳረቀቁ ኹሉ ለዚሕም ብልግና የኾነ ሕግ ሊያበጁለት ይገባል፡፡ በዚሕ ሚሊዮኖች በቀን አንዴ መቀመስ እንኳ ተረት በኾነባቸው ሐገር ውስጥ ነገ ለኛ ይኹን አይኹን ጨርሶ ዕርግጣኛ ሳንኾን በቀቢጸ ተስፋ ብቻ እየኖርን ባለንበት ግልጽ ተጨባጭ እነ አባ ጉርምርሜ ገንዘባቸውን ሰፍተው መለበስ ከጀመሩ፣እንግዲያውስ ሳናየው ቀርተን እንጂ ደጃል ከደጃፋችን ቆሟል!!! ወዳጄ ኹላችንም በዘጠኝ ወር ተወለድን፤ከኛ መካካል አንድስ እንኳ በዘጠኝ ዓመት የተወለደ የለም፡፡ ኹላችንም ሰብዓዊ ስጋ የለበስን በተፈጥሮ ሕግ የምንዳኝ፣ ጅማሮአችን ምንም የነበረ መጨረሻችንም ትቢያ ኾኖ እስከ ትንሳኤ የሚቆይ እንጂ ከኛ መካከል በሰው አምሳል የተከሰተ መስሎ የመጣ መልዓክ የለም፡፡ ታዲያ ወዳጄ ይሕ እጅግ ቅጥ ያጣ ጎፈሬ ማበጠርና አጓጉል ቀረርቶ በመካከላችን ሐብት በቅጡ እየተሸከረከረ እንዳልኾነ፣ኹላችንም እኩል ተጠቃሚዎች እንዳልኾንና ጥቂቶች በሚሊዮኖች ተሰፍረው በኛ ላብ እየወዙ ያሉበት ዕውነታ ላይ እንደ ደረስን ያሳያል፡፡ እነ አባጉርምርሜ ለሰከሩት ድሃው የሚንገዳገድበት ዕውነታ ላይ እንዳለን አኹን በደንብ የገባን ይመስለኛል፡፡ በቀጣይ ሌላ ሰማያዊ ተዓምር እስካልመጣ ድረስ የነርሱ ስካር ከፍ ባለ ቁጥር በየገደሉ እስከ ወዲያኛው ወድቆ የሚያሸልበው ድሃ የትየለሌ እንደሚኾን ግልጽ ነው፡፡ https://t.me/E_M_ahmoud

2
ከስነ ልቦና አስተምህሮዎች ... በጣም ከባድ ቁጣ እጅግ መልካም በኾኑ ሰዎች ላይ ሊታይ ይችላል። እነዚህ ሰዎች እስከ ጥግ ድረስ ሄደው ይታገሳሉ፤ያልፋሉም። ትዕግስታቸው የተንጠፋጠፈ ጊዜ ምንም ባያደርጉም ላይመለሱ ግን ጥለው ይሄዳሉ። ስለዚህ ወዳጄ ብዙ ስናጠፋ ዝም የሚሉን ሰዎች ሳይሰማቸው ቀርቶ ወይም ስላላወቁብን እንዳይመስለን። ይልቁንም ጊዜ ሰጥተው ኹኔታችንን በጥንቃቄ እያጠኑ እንደኾነ ልብ ይሏል። በዚህ ዝምታቸው ውስጥ እያሉ ከነርሱ በኩሉ ምንም የባሕሪ ለውጥ አናይም። እንደ ኹሌውም ሊያገኙን ይሞክራሉ። እንደ ኹሌውም ሰላማችንና ጤንነታችን ሊያሳስባቸው ይችላል። በስተመጨረሻ ግን "ኦሮማይ" ብለው ከኛ ጋር የከፈቱትን ዶሴ ለዝንተ_ዓለም አቃጥለው ይሞቁታል። በነዚህ ሰዎች የመጨረሻ ውሳኔ ላይ መፍረድ እጅግ ያስቸግራል። ምክንያቱም ኹላችንም ተራ ሰብዓዊ ባሕራ እንጂ የመላዕክት ወይም የነብያት ማንነት የለንም። ታዲያ ወዳጄ የስጋ ዘመድም ቢኾን እኮ ዕድሜ ልክ ለኛ ምክንያት እየሰጠና ጥፋታችንን እያለፈ አይዘልቅም። የኾነ ቀን ይቆርጥለታል። የተቆረጠ ነገር ደግሞ ዳግም በኾነ ተዓምር እንኳ ቢቀጠል፣በጭራሽ እንደ ወትሮው አያምርም። ኹሌም ነገራት መሰበራቸው ሳይኾን ዳግም መጠገን አለመቻላቸው ነው የመጨረሻ ሐዘን የሚኾነው። Thanks to Alan Paton in his novel "Cry, the Beloved Country" he said፦ "The tragedy is not that things are broken. The tragedy is that things are not mended again" ... https://t.me/E_M_ahmoud
660
3
ሙስሊሙ ላይ ያነጣጠሩ ... ... ከሰሞኑን ሙስሊሞች ላይ ያነጣጠረ ግድያ በተለይ በአማራ ክልል በሰፊው ዕየታየ ነው። ግድያውን ማንም ይፈጽመው እየኾነ ያለው ግን ይሕችን ሐገር እስከ ወዲያኛው የሚያፈርስ እንጂ የትኛውንም ኀይል የሚጠቅም አይደለም። አንድን ሃይማኖት ለማዳከም የእምነቱን ልሂቃን ማስወገድ አቋራጭና ስር ነቀል ለውጥ የሚያመጣ እንደኾነ ይታወቃል። በአሜሪካ በነ ማልኮም ኤክስ (ረሒመሁላህ) እየተቀጣጠለ የነበረው ኹሉን አቀፍ ኢስላማዊ ዐብዮት እንዲጠፋ የኾነው ራሱ ማልኮም በጥቁሮች እንዲገደል ከተደረገ በኋላ ነበር። እንደሚታወቀው ማልኮም ወደ ትክክለኛው ኢስላማዊ አስተምሕሮ ከመምጣቱ በፊት The nation of Islam በሚባል ነጭ ጠል እንቅስቃሴና ሃይማኖት ውስጥ የሚመላለስ ነበር። ማልኮም ሃጅ አድርጎ ከተመለሰ በኋላ ትክክለኛው ኢስላም ኹሉንም የሰው ልጆች በእኩል ዐይን እንደሚያይና እሱ የተዘፈቀበት ነጭ ጠል እንቅስቃሴ ስሕተት እንደኾነ ተረዳ። ወደ ሐገሩ ከተመለሰም በኋላ በThe nation of Islam ሃይማኖትና መሪው ኢላይጃህ ሙሐመድ ላይ ግልጽ ተቃውሞ ማሰማት ጀመረ። በ 1963 እ.ኤ.አ. ጆኔፍ ኬኔዲ ተገደለ። ግድያውን ተከትሎ የኢላይጃህ ሃይመኖታዊ ተቋም ምንም አስተያየት እንዳይሰጥ በራሱ በኢላይጃህ የተላለፈ ጥብቅ ትዕዛዝ ነበር። ይሕንን ትዕዛዞ በሚጻረር መልኩ ማልኮም "Chickens coming home to roost" በሚል መሪ ቃል በርቱዕ አንደበቱ ንግግር አደረገ። የንግግሩ ፍሬ ሐሳብ ነጮች ጥቁሮች ላይ የለኮሱት ጥቁር ጠል እሳት ራሳቸውን ይፈጃቸው ጀምሯል የሚል ነበር። የማልኮምን ንግግር ተከትሎ የNation of Islam መሪ ኢላይጃህ በማልኮም ላይ ነገር ማሳበቅ (ማቀሳሰር) ጀመረ። ብዙም ሳይቆይ ማልኮም መድረክ ላይ ገና "አሰላሙ ዐለይኩም..." ብሎ የአፉን ሳይጨርስ በኢላይጃህ ተከታዮች በተኩስ እሩምታ ተደብድቦ ተገሏል። የማልኮምን ሞት እንደ መልካም አጋጣሚ መጠቀም የፈለገው "The nation of islam" ከማልኮም ሞት በኋላ በአዲስ መልክ ማንሰራራት ጀመሮ ነበር። ኾኖም ግን በሚያሳዝን መልኩ ዛሬ ላይ አሜሪካን ውስጥ በኢስላማዊ ዕውቀቱ ጉምቱ የኾነ አንድ ጥቁር ሼኽ መጥራት ሊያስቸግር ይችላል። የማልኮምን ፈለግ የተከተለ አይደልም በራሱ The nation of Islam ተቋም ውስጥ እንኳ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስመ ጥር የኾነ አንድ ሰው መጥራት አይቻልም። ይሕንን የቅርብ ታሪክ ይዘን ወደ ሐገራችን ስንመለስ፣አኹን እየኾነብን ያለው ኹሉ ኢስላማዊ መሪና ንቁ ዜጋ የማሳጣት እንቅስቃሴ እንደኾነ ይሰመርበት። መሻይኽ መገደላቸው፣ በእምነታቸው ጠንካራ የኾኑ ሴቶች ከትምሕርት ገበታ መፈናቀላቸው ወዘተ በተመሳሳይ ዜማ የተቃኙ መዝመሮች መኾናቸውን ይረዷል። https://t.me/E_M_ahmoud
789
4
ፈጥኖ ማን ይመልስ! ⁉️ ✅በቁርዓን ውስጥ ስንት ነብያት በስም ተጠቅሷወሉ⁉️ የካፊሮች ቅጥፈት መልስ የሚሰጥበታ ቻናል ነው ተቀላቀሉ➢@mustefa_Apologetics
200
5
ዳዕዋና ዳዒዎች.m4a
836
6
احذر أن تكون كحال صاحب سحنون فلا تناظر وأنت لست أهلًا لذلك!. مناظرة ابن سحنون المالكي -رحمه الله- لأحد اليهود، وقد أوردها القاضي عياض في كتابه: ترتيب المدارك ومفادها: (أن رجلًا من أصحاب الإمام محمد بن سحنون (ت ٢٥٦ هـ) دخل بمصر حمّامًا عليه رجل يهودي، فتناظر مع الرجل، فغلبه اليهودي؛ لقلة معرفة الرجل، فلما حجَّ محمد بن سحنون صَحِبه الرجلُ، فلما دخل ابن سحنون مصر، قال له: امضِ بنا -أصلحك الله- إلى الحمام الذي عليه اليهودي، فلما دنا خروج محمد بن سحنون سبقه الرجلُ، وأنشب المناظرة مع اليهودي، حتى حانت صلاة الظهر، فصلى محمد، ثم رجع معه إلى المناظرة، حتى كانت العصر، فصلاها، ثم كذلك المغرب، ثم إلى العشاء، ثم إلى الفجر، وقد اجتمع الناس، وشاع الخبر بمصر: الفقيه المغربي (ابن سحنون) يناظر اليهودي، فلما كانت صلاة الفجر، انقطع اليهودي، وتبيّن له الحق وأسلم، فكبّر الناس وعلت أصواتهم، فخرج محمد وهو يمسح العرق عن وجهه، وقال لصاحبه: لا جزاك الله خيرًا، كاد أن يجري على يديك فتنةٌ عظيمةٌ، تناظر يهوديًّا، وأنت بضعف، فإن ظهر عليك اليهودي لضعفك، افتتن من قدّر الله فتنته)!. (ترتيب المدارك وتقريب المسالك لمعرفة أعلام مذهب مالك ، جـ١، صـ٤٢٩) ... ዶ/ር ሑሴን ኹሌም ለምታጋራን መረጃዎች ጀዛከላሁ ኸይረል ጀዛእ
804
7
የዚህ ቤት ዓላማ.m4a
830
8
የዮሐንስ ወንጌል 14:28 •••••••••• ²⁸ እኔ እሄዳለሁ ወደ እናንተም እመጣለሁ እንዳልኋችሁ ሰማችሁ። የምትወዱኝስ ብትሆኑ ከእኔ አብ ይበልጣልና ወደ አብ በመሄዴ ደስ ባላችሁ ነበር። ... ይሕችን ጥቅስ ለክርስቲያኖች ጥያቄ አድርጎ ለማሚያነሳ ኹሉ ምላሹ "ኢየሱስ በሰብኣዊ ማንነቱ ከአብ እንደሚያንስ እየተናገረ ነው፤ እንጂማ በመለኮታዊ ማንነቱ ከአብ እኩሉ ነው" የሚል ነው። ከእኛ በኩሉ መነሳት የመልስ መልስ እንደሚከተለው ሊኾን ይችላል፦ ፩ኛ) ኢየሱስ ስጋዊ ማንነቱን ከአብ ጋር እያወዳደረ ከኾነ፣ማወዳደሩ አብን እጅግ ያረክሰዋል። ምክንያቱም ውድድር መወዳደር በማይችሉ አካላት መካከል ለምሳሌ አንድ ሕጻን ልጅ ከቀነኒሳ ጋር ተሸቀዳደመና ቀነኒሳ አሸነፈ ቢባል፣ቀነኒሳን በግልጽ መሳደብ ነው። ኢየሱስም ፈራሽና ለተፈጥሮ ሕግ ተገዢ የኾነውን ሰብአዊ ማንነቱን ከአብ ጋር እያወዳደረ ከነበር፣አብን በቀጥታ እያዋደቀ ነው። ይሕ ደግሞ ከባድ ኀጢአት ነው። ኦሪት ዘሌዋውያን 24:16 •••••••••• ¹⁶ የእግዚአብሔርንም ስም የሚሰድብ ፈጽሞ ይገደል፤ ማኅበሩም ሁሉ ይውገሩት፤ መጻተኛ ወይም የአገር ልጅ ቢሆን፥ የእግዚአብሔርን ስም በሰደበ ጊዜ ይገደል። ፪ኛ) ኢየሱስ ሲያርግ በስጋው ብቻ ነው ያረገው ወይስ በስጋና በ"መለኮታዊ" ማንነቱ ጭምር ነበር? መልሳቸው "በኹለቱም አርጓል፤ምክንያቱም ስጋና መለኮት በእናቱ ማሕጸን እያለ ተዋሕደዋል" የሚል ከኾነ፣ስለዚህ ኢየሱስን በመለኮታዊ ማንነቱ የሚበልጥ አብ አለ ማለት ነው። ይሕ ደግሞ የሚበልጥና የሚበለጥ ኹለት የተለያየ እርከን ያላቸው አማልክት እንዲኾኑ ያደርጋቸዋል። ፫ኛ) አብ ከወልድ ይበልጣል ካልን፣መንፈስ ቅደስስ ከወልድና ከአብ አኳያ ያለው ደረጃ ምን ዓይነት ነው? ከኹለቱም ይበልጣል? ወይስ ያንሳል? ወይስ ከኹለቱም ጋር እኩል ነው?ወይስ ከአንዱ ይበልጣል፣ከሌላኛው ያንሳል? ፬ኛ) በስጋው ነው ያረገው ከተባለ ደግሞ በእርገቱ ወቅት መለኮታዊ ማንነቱ የት ገባ? ... እነዚህና መሰል መጠይቆች ኢየሱስ ከአብ የሚያንስ ፍጡር ብቻ እንደኾነ እንድንቀበል ያስገድዳሉ። ... ጋራ ቦሎ አካባቢ ልትሰብኩኝ የመጣችኹ ሶስት ወንጌላውያን ይሕ ጥያቄ ምን ያሕል ግር እንዳደረጋችኹ አስታወስኹ። በተለይ አንደኛቸው ለማስረዳት የሄድክበት ርቀትና መሐል መሐል ላይ "መንፈስ" እንዳደረበት ሰው ስትውረገረግ ሳይ ይሕ ትወና መንገድ ላይም ተጀመረ እንዴ? እንድል አስገድዶኛል። https://t.me/E_M_ahmoud
1 078
9
ከሰሞኑን የኦርቶው ስብስብ በስላሴ ባሕራያት ዙሪያ እርስ በርስ መነታረክ ይዟል። ከነርሱ ጋር በተደረገ አንድ ውይይት ሙስሊሙን ወክሎ የገባው ተወያይ አንዳንድ ከአላህ ባሕሪያት አኳያ ለተነሱለት ጥያቄዎች አልተገለጸም እያለ መመለሱ አስፈንጥዟቸው ነበር። እንዴት ማንነቱ ያልተገለጸ አምላክ ታመልካላችኹም እያሉ ሲያፌዙ ቆዩ። በኋላ ላይ ጉዳዩ በራሳቸው ላይ ሲነሳና ሊቃውንታቸውም "ለሰው ያለው ኹሉ ጾታን ጨምሮ ለስላሴም አላቸው" ብለው መጨቃጨቅ ጀመሩ። ይሕንን አስተምሕሮ ተከትሎ ራሱ ከሙስሊሙ ጋር ሲወያይ የነበረው ግለሰብ በሚዲያ ብቅ ብሎ "ለሰው ያለው ኹሉ ለእግዚአብሄር አለው" የሚለውን አስተምሕሮ እንደማይቀበል አወጀ። መቼም ቢኾን ሰው አምላክ አንድም ሶስትም ነው፤ ሰውም አምላክም ነው፤ ብሎ ሊስማማም ሌላውንም ሊያሳምን አይችልም። ኦርቶዎቹ አኹን ላይ ሚዲያ ላይ እያደረጉት ያለው ውይይት እንደ ቀድሞው ውይይቶቻቸው በድምጽ ብዛት ወደ አንድ አቋም እንዳመጡ ካላደረጉ በፍጹም አይስማሙም። https://t.me/E_M_ahmoud
1 284
10
ክፉ አፍ … ኹሉን ቢናገሩት ሆድ ባዶ ይቀራል ሆድ ባዶ ከቀረስ እንዴት ይታደራል ማደር ከተሳነ ጎጆስ ከየት ይቃናል ያልተቃና ጎጆም ቅንቅን ይበላዋል ድንገት ይናድና ጓዝ ከደጅ ይባላል እልፍ ማለት ሲቻል እልፍ ቃል ተመዞ አፍ በተከፈተ ሕብረ-ቃል ተሰርቶ-ቅኔ ተቀንቅኖ ኹሉም በቤት ሲነግስ ኹሉንም ተርጉሞ ከቁንጫ ሌጦ እያወጡ ዛሬ ላይለበስ ከርሞ ስንቱ ባፉ ጠፋ ስንቱስ በቃል ሞተ በፍጹማን መንፈስ ራሱን ቆልሎ ከንቱ እየገመተ ጀብደኞች ፎከሩ፤ በአንድነት መከኑ ባልዋለ የቃል ገበያ ዋጋ እየተመኑ …. ሐሙስ/25/2018 ከጠዋቱ 1 ሰዓት ከ36 ላይ ተሰነኘ
1 443
11
በመተውና ባለመረዳት መካከል … መልዕክተኛው (ሰለላሁ ዐለይሒ ወሰለም) ለሚስታቸው ለሓፍሷ ቢነት ዑመር (ረዷየላሁ ዓንሃ) አንድን ጉዳይ ሚስጥር አድርገው ነገሯት፡፡ ሓፍሷም መጠበቅ የነበረባትን ሚስጢር ለዓኢሻ (ረዷየላሁ አንሁማ) ዘርግፋ አወራቻት፡፡ ብዙም ሳይቆይ መልዕክተኛው (ሰለላሁ ዐለይሒ ወሰለም) ይሕንን ጉዳይ ሓፍሷ ለዓኢሻ እንደነገረቻት በወሕይ አማካኝነት ዐወቁ፡፡እንዳወቁም ሓፍሷን በጉዳዩ በተወሰነው ክፍል ላይ ብቻ ትኩረት አድርገው ለምን ተናገርሽ በሚል ወቀሷት፡፡ የጉዳዩን ቀሪውን ክፍል ግን ባላወቀ ዘለሉት፡፡ ይሕንን ጉዳይ አሏህ (ሱብሓነሁ ወተዓላ) በቃሉ እንዲሕ ሲል ነገረን፡- “ ነብዩ ከሚስቶቹ ወደ አንዷ ሚስጥርን በተናገረ ጊዜ፤እርሱንም በነገረችና አላህ እርሱን ባሳወቀው ጊዜ "ከፊሉን አስታወቀ"፡፡ "ከፊሉንም ተወ”" አተሕሪም/3 ይሕ የመልዕክተኛው (ሰለላሁ ዐለይሒ ወሰለም) ድንቅ አካሄድ ዛሬ ላይ ከኛ ውጪ ካለ ከየትኛውም አካል ጋር አብሮ ለመኖር እጅግ አስፈላጊ የሕይወት መርሆ ነው፡፡ ሰዎች በየትኛውም ልኬት ከበባድ የሚባሉ ጥፋቶችን ሊያጠፉብን ይችላሉ፡፡ ያ ጥፋት ግን ሰፍቶ ድንበር የለሽ እንዳይኾን ሰዎቹን የመመከርና የመውቀስ ዕድሉን ካገኘን በኹሉም አጠፉት ባልናቸው ጉዳዮች ውስጥ እየገባን መውቀስ አላስፈላጊ እንደኾነ ባስቀደምነው የመልዕክተኛው (ሰለላሁ ዐለይሒ ወሰለም) ታሪክ መማር እንችላለለን፡፡ ይህ ማለት ጥፋት የጠፋበት አካል የጠፋበትን ጥፋት ልክና ዓይነት አላወቀም ወይም አልተረዳም ማለት አይደለም፡፡ ግን መሰረታዊ በኾነው ጉዳይ ላይ ብቻ ማተኮሩ ግለሰቡ በጣም ነገራትን ማለፍ የሚችል ሰፊ ልብ ያለው መኾኑን የሚያሳይ ነው፡፡ በዚህ መልኩ ጥፋት ያጣፋብንን ሰው በስሱ መውቀስ አስፋላጊ ከመኾኑ ጋር በእያንዳንዱ ስብርባሪ ነገር ውስጥ ገብተን ግለሰቡን አለመነዝነዛችን ደግሞ ሰውዬው እንዲጸጸትና ተውባውም እንዲያደርግ ይገፋፋል፡፡ ኢማሙል ቢቃዒ በዚህ ጉዳይ ላይ ሲናገር እንዲህ ይላል፡- `` هذا أبعث إلى حياء المعتب وأقرب إلى توبته`` “ይሕንን ማድረግ ተወቃሹ ግለሰብ እንዲያፍር የሚያነሳሳና እንዲጸጸትም ለማድረግ የቀረበ ነው” ወዳጄ ልብ ማለት ያለብን ከባድ የምንለውን ጥፋት ባጠፋብን ግለሰብ ላይ ተመሳሳይ ጥፋት አለማጥፋት ትልቅነት ሲኾን ወቀሳውም ቢኾን በግርድፉ መኾኑ ጅልነት ወይም ተላላነት (ዝንጉነት) አይደለም፤ ይልቁንም ከፍ ያለ ስብዕና ነው፡፡ ሙዓዊያ (ረዷየላሁ ዐንሁ) ሲናገር “ ሕሊና ሚዛን ነው፡፡ሲሶው ብልሕነት ሲኾን፣ሲሶው ደግሞ ችላ ብሎ ማለፍ ነው” ይላል፡፡ ወዳጄ ዐዋቂና ብልሕ የኾነ ሰው እያንዳንዱ ስሕተት ላይ እየቆመ ሕጸጽ የሚያወጣ ሳይኾን መሰረታዊ በኾኑ ጉዳዮች ላይ ብቻ የሚያተኩር ነው፡፡ ዛሬ ላይ በርካታ ትዳሮችን ከሚያናጋው ነገር አንዱ ኹለቱም በእያንዳንዱ ደቂቅ ጉዳይ ላይ ገብተው ለምን? እንዴት? የሚል ጥያቄ ማንሳታቸውና ለኹሉም ነገር በሚፈልጉት መልኩ መልስ መፈላጋቸው ነው፡፡ ዓሊይ ቢን አቢ ጣሊብ (ረዷየላሁ ዐንሁ) ተናግሮታል ከሚባለው ድንቅ አባባል መካከል፡- من لم يتغافل تنغصت عيشته “ነገሮችን ማለፍ የማይችል ሕይወቱ ምስቅቅል ይላል” ቸርነት የተላበሰ ማንነት በፍጹም በእያንዳንዱ ፍርክስካሽ ነገር ገብቶ አይፈላፈልም፡፡ ስንት ትዳሮች “ለአንድ ቁርስ እንዴት ይሕን ያሕል ክብሪት ይነኮሳል” በሚል እንቶፈንቶ ሓሳብ ላይገነቡ ፈርሰዋል፡፡ ኢማሙ አሕመድ (ረሒመሁ አሏህ) ይጠየቃል-፡ أين نجدوا العافية؟ قال "تسعة أعشار العافية في التغافل" ثم قال "بل العافية كلها في التغافل " ሰላምና ደሕንነት እንዴት ነው ማግኘት የሚቻለው? ኢማሙም ሲናገር “ ዘጠኝ ዐስርኛው የሰላምና ደሕንነት መገኛ ችላ በማለት ውስጥ አለ፡፡” ካለ በኋላ “ እንዲያውም ሰላምና ደሕንነት በሙሉ የሚገኘው ችላ በማለት ውስጥ ብቻ ነው” ብሏል፡፡ ዛሬ ላይ ሙስሊሙ ማሕበረሰብ ለዓርኣያነት መብቃት አይደለም ሻል ያለ ኾኖ መገኘት ያልቻለበት ትልቁ ምክንያት መሰል ድንቅ የመልዕክተኛውን (ሰለላሁ ዐለይሒ ወሰለም) እና የሰለፎችን የሕይወት መርሆዎች በመጣሱ እንደኾነ ልብ ይሏል፡፡
1 535
12
videoው ተለቋል ገብታቹህ ኻድሙ። https://vt.tiktok.com/ZSCSbhS8K/
1 299
13
Matn yo'q...
2 105
14
New Project 20 [7D5F4E2].png
141
15
ክረምቱ በደንብ ሲጀምር... ... ገና ከማለዳው ሰማዩ ምድር ላይ ድፍት ብሎ ልውደቅባችኹ እያለ አልፎ አልፎም አምልጠው የመጡ በሚስሉ የዝናብ ጠብታዎች እያረጠበን ከቤት እንዳንወጣ የሚያስፈራራ ይመስላል። መቼም ክረምት ሲገባ ብዙዃኑ እግረኛ እንዳማረበት ወጥቶ አይመለስም። ወይ በዝናብ በስብሶ እየተርገፈገፈ አሊያም በጭቃ ተለዋውሶ ዳቦ በማርማላታ መስሎ ነው ከቤቱ የሚመለሰው። በደሕና የሐበሻ እግር ከኮልፌ ጉለሌ በቀላሉ ያቀና የነበረ ኹሉ ክረምቱ ይዞት ከሱቅ ሱቅ እየተጠለለ ሰዓታት መፍጀት ይዟል። በርግጥ የትም መሄጃ ያጣ ሕዝብ በዝናብ አስታኮ መዋያውን ከሱቅ ደጅ ማድረጉ ነሮን ለመሸወድ ሳይጠቅመው አይቀርም። ዘንድሮ እንደኾነ ኮሪደር በኮሪደር የኾነችው አዲስ በባዶ ሆዱ የሚማላለስባትን እግረኛ እንደጉድ እያፈራች ነው። አንዲት እጅግ ወጣት የኾነች ዘመዴ ምነው ትምሕርት ላይ ማተኮሩን ቀነሽሳ? ብዬ ብጠይቃት "የእናንተ ዕጣ ፈንታ እንዲደርስብኝ አልፈልግም" ስትለኝ፣በትክክል እኔ የማላውቀው እሷ ብቻ የምታውቀው የኾንኩት አንዳች ነገር ይኖር ይኾን ብዬ ራሴን ለማየት (ቼክ ለማድረግ) ሞከርኹ። እኔ ምንም ሳልኾን በየቀኑና በየሳምንቱ ኪሎ ሜትሮችን እየሮጥኩና እየተራመድኹ በሙሉ ጤንነት አለኹ። ታዲያ ምን ኾኜ ነው ይሕች ወጣት በዚህ ልክ የታዘበችኝ? ነገሩ ወዲሕ ነው ወዳጄ! "እንደ እናንተ ተማርን የምትሉ አካላት ኗሪ እንጂ አኗኗሪ መኾን አልፈልግም" ማለቷ ነው። እንደዛስ ከኾነ ደግ ብላለች ቀድሞውኑ እንደዚህ ልክ ልካችንን የሚነግረን ብናገኝ ኖሮ በእሳት ባልተጫወትን!!! ዛሬ ምንስ ብትል ማን ቁብ ሊሰጠው ኖሯል!? ፍርጥ አድርገን እናውራ ካልን ተወደደም ተጠላም የአስኳላ በር የረገጠ አይደለም መካከለኛ ገቢ አለኝ የሚል ኹሉ ነገራት በዚህ ከቀጠሉ የአኗኗሪነትንም ማዕረግ ማግኘቱ አጠያያቂ ነው። ወዳጄ ምንም ቢራብ አንበሳ መቼም ሳር ግጦ ከከብቶች ጋር ውሎም አያውቅም። ግን አኹን አኹን ለመጋጥም ለመቀንጠብም ሳይገደድ የሚቀር አይመስለኝም። አስኳላ ስብር አድርጓችኹ ትላንት ዘካት ትሰጡ የነበራችኹ የዛሬዎች በድብቅ ተቀባዮች ሰላም በናንተ ይኹን!!! ዱንያ እንደኾነ አንዴ እንዲህ አንዴ እንዲያ ናትና ነገን በታላቅ ተስፋ መጠበቅ ቢያንስ የዛሬን እንቅልፍ አይነሳምና ተስፋ ምግባችኹ ይኹን። ከቤት ተቸገራችኹ የተቆራመታችኹ የቲሞችንም ኾነ የምስኪን ልጆችን ችለን ኹላችኹንም ሆዳችኹን በእህል ብንዳብስ በወደድን...ግን በነፍሶች አምላክ እምላለኹ መስፈሪያው አንጠባጠበና መጠገኑ እጅግ ተሳነን። እናንተ ስታለቅሱ ምድርም አብራ ታለቅሳለች። በትክክል ከምታለቅሰዋ ምድር የተገኙ ልቦችም አብረው ያለቅሳሉ!!! ካላችኹበት ኾናችኹ "​ያ አላህ ጸሚእና ኢና ኣስቲየና ጠሚእና ኢና ኣብልዓና" "አላህ ሆይ ተረበናል አብላን ተጠምተናልም አጠጣን" ብለው የሚያለቅሱ ዐይኖቻችኹን የሚያይ አላህ ድምጻችኹን ይስማ!!! https://t.me/E_M_ahmoud
1 678
16
ጥያቄ ተሳተፉ‼ ከአላህ ውጭ ባለ ፍጡር መማል "ሺርክ" ነው።⁉ የካፊሮች ቅጥፈት መልስ የሚሰጥበታ ቻናል ነው ጎራ በሉ ➢@mustefa_Apologetics
56
17
ቁርአንያዎችና እምነታቸው.m4a
1 516
18
ችግሩ የት ነው ያለው? … በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኒቃብ ለብሰው የሚማሩ እህቶቻችን በዚህ ዓመት ከትምሕርታቸው እንደተፈናቀሉ ዓለም ያውቃል፡፡ ለዚሕ ችግር ከኛ በኩል የሚመለከታቸው የመጅሊስ አካላት እስከ አኹንም ምንም መፍትሔ ይዘው ብቅ ማለት አልቻሉም፡፡ ሐገር አቀፍ ምርጫ ተጠናቆ፤ መመረጥ ያለበት አካል ተመርጦ፤ ከዚያም መፍትሔ ይኖራል የሚል ቀቢጸ-ተስፋ የተጎነጩ በርካታ የዋሕ ሙስሊሞች እንደነበሩ ግልጽ ነው፡፡ እንዴት እንዴት የኒቃብ ጉዳይ ከሐገር አቀፍ ምርጫ ጋር እንደተገናኘ ባይገባኝም በዚህ ልክ ግን ሙስሊሙ ማሕበረሰብ በሕልም እንጀራ ቁምጣን ሲያሰቃየው ማየት ያሳዝናል፡፡ ቀጠለና ደግሞ የቁርኣንያ አንጃ ፍልፍሎች በየሚዲያው አቋማቸውንና ተቋማቸውን ሲያስተዋውቁና ሲሰብኩ ያንን ተከትሎ የዑለማው ምክር ቤት በተጠናና በተደራጀ መልኩ በተነሳው የኩፍር አካሄድ ላይ ስራ ሲሰራ አላየንም፡፡ የመጅሊሱ የዑለማእ ስብስብ ይሕንን ሐገራዊ መቅሰፍት መንግሎ ለመጣል የተጠናከረ ስራ መስራት ካልቻለ በግለሰብ ደረጃ ወጣቶች ተሰባስበው እጅግ በተገደበ ሚዲያ ላይ ለመስራት መሞከራቸው ችግሩን ሙሉ በሙሉ መቅረፍ አይደለም በበቂ መልኩ የችግሩን አሳሳቢነት ማሳወቅ እንኳ አይቻላቸውም፡፡ የዑለማው ምክር ቤትና ሌሎችም በድፍረት የሃይማኖቱ መሪ ነን የሚሉ አካላት በዚህ አጥፊ አንጃ ዙሪያ በየመድረኮቻቸውና ሚዲያዎቻቸው ላይ ለምን ሕዝቡን የማንቃት ስራ አልሰሩም? ከዚህ ቀደም የተክፊር ጀመዓ በወጣቱ ላይ ያደረሰው መፈረካከስ የቅርብ ትዝታ ኾኖ መሰል እጀግ አሳሳቢ አስተሳሰቦች ሲነሱ ዑለማእ ነን የሚለው ስብስብ ለምን በመጅሊሱ ወጪና አበል ለሓጅ ስራ በሚል በየዓመቱ ወደ መካ ለመትምም ከሚሽቀዳደም ይልቅ መሰል ስራዎች ላይ ጊዜውን ሰጥቶና በጥልቅ አጥንቶ የማያዳግም መልስ እንደማይሰጥ ዓላውቅም፡፡ ሌላው ደግሞ ቁርኣንን እናስተምራለን በሚል ስም እስከዛሬ በሐበሻ ምድር ተሰምቶ በማይታወቅ መልኩ ቁርኣንን በቅጡ እንኳ ማንበብ የማይችሉ ግብዝ አካላት በማዕከል ደረጃ ተደራጅተው ብቅ ማለታቸው በመጅሊሱ ላይ ተጨማሪ ወፈር ያለ ጥያቄ እንድናነሳ አድርጓል ፡፡ የግለሰቦቹ የዕውቀት ልክ በራሱ ያንን ፈቃድ እንዲሰጡ የማያደርግ ኾኖ ሳለ የባሰው ነገር ግን ግለሰቦቹ የለበሱት ለምድ መገለጥ ሲጀምር እጅግ አደገኛ አመለካከት ያላቸው አጥፊዎች መኾናቸው ነው፡፡ ይህ ደግሞ አኹንም ለነርሱ አስተምሩ በሚል ፈቃድ የሰጠው መጅሊስ ጥያቄ ውስጥ እንዲወድቅ ያስገድዳል፡፡ በእንግሊዘኛ ተጠምዳችኹ በእነዚያ አካላት የተማራችኹ ሳይኾን የተማረካችኹ እንስቶች ጥቂት ወንዶችም ብትኾኑ ሰላም ለናንተ ይኹን እያልኩ!!! ተማርን የምትሉትን ኹሉ ዐዋቂዎች ፊት ቀርባችኹ ብታርሙት በቀጣይ ፈንጂ ኾኖ (time bombing) አያጠፋችኹም፡፡ ወዳጄ ነገር እያወሳሰብኹ እንዳይመስሎ፡፡ ግን “የቁርአን ጥናት ማዕከል” ማለት ተፍሲርን ማስተማር ብቻ ማለት አይደለም፡፡ ከዛም በጣም ከፍ ያለ ነው፡፡ ታዲያ ጉዳዩ ትልቅ ጥያቄ የሚያስነሳው እዚህ ጋር ነው፡፡ እነማን ናቸው የቁርኣን ጥናት የሚያደርጉት? በየትኛው የቃልችነት ሕይወታቸው ነው ቁርኣንን ነሕውን፣ሷርፉን፣በላጋውን፣ሰበበ አኑዙልን፣የተለያዩ ቂርኣቶችን/ሪዋያዎቹን ወዘተ አካተው የሚያጠኑት? ወይስ በረመዳን አንዳስለመዱን የተለያዩ በእንግሊዘኛ መሰል ስራዎችን የሰሩ ግለሰቦችን ቪዲዮዎች ሰብስበው በኣመርኛ ሊተረጉሙልን ነው የታሰበው? ለመኾኑ ቁርኣንን ለመፈሰርና ለማጥናት ጥልቅ የቋንቋ ዕውቀት ብሎም የሐዲስ ትምህርት እንደሚያስፈልግ መጅሊስ ላይ ያሉ ሰዎች ጠፍቷቸው ነው ወይስ ተፍሲር እናስተምር ላሉ አካላት የተሰጠው ፈቃድ በጓሮ በር የተገኘ ኾኖ ነው? ስለምን ነው “የማዕከሉ” ቆርቋሪና አስተማሪ ነኝ ያለውን ግለሰብ የዑለማው ምክር ቤት ቁኝ አድርጎ መፈተን፣እነማን ሼኽ ዘንድ እንደቀራ ማጣራትና ለጠየቀው ፈቃድ በቂ ዕውቀት አለው ወይስ የለውም የሚለውን ማጣራት ያቃተው? እኔ እንደገባኝ በዑለማ ምክር ቤት ስር የተሰባሰቡ ብዙኃን ስራ ፈላጊ ግለሰቦች እንጂ በትክክል ሰፋ ያለ ሐገራዊ ዕይታ ኖሯቸው ከዛም አኳያ መስራት የሚችሉ ግለሰቦች አይደሉም፡፡ በዚህ ተጨባጭ ውስጥ ትንሽ ከቆየን በንቀት እየተነቃነቀ ያለው አጥር ሙሉ በሙሉ ይፈርስና ድፈን የሐበሻ ሙስሊም የሚሰበስበው ያጣ የንብ መንጋ ኾኖ እንዳይቀር ያሰጋል፡፡ https://t.me/E_M_ahmoud
2 076
19
ቁርአንያዎች ሐራም የሚያደርጓቸው.m4a
2 707
20
ምርጥ ብቀላ ... ... ብቀላ ልትድነው ከምትፈልገው በሽታ ጋር ዳግም እንድትቆራኝና በቀጣይነት እንድትሰቃይ ያደርጋል። ርቀትኽን መጠበቅ ግን ከበሽታኽ እንድታገግም አበክሮ ያግዝኻል። መርዝማ ከኾኑ አካላት መሸሽ በራሱ ላደረጉብኽ ነገሮች ኹሉ ዕውቅና አለምስጠትኽን ያሳያል። የጎዱኽ የመሰላቸውን ሰዎች ከመበቀል ይልቅ መሸሽ የነርሱ ሴራና ተንኮል በጉዞኽ ላይ ይህ ነው የሚባል ሚና እንደሌለው ማሳያ ነው። ወዳጄ ጻድቅ ኾነኽ በሰላም መኖር በራሱ ትልቅ ኪነት/ጥበብ ነው። ጥበብን/ሒክማን የሚወድ ደግሞ ጥበብ ከሌላቸው መርዛማ መርዶኞች ኹሉ ይርቃል። ወዳጄ ሕይወት እኮ በጣም አጭር ናት!! ታዲያ በበቀል የሚባክን ጊዜ ሊኖረን እንዴት ይገባል?! Always the best revenge is to forgive. https://t.me/E_M_ahmoud
2 194