en
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Open in Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Show more
2 291
Subscribers
No data24 hours
+27 days
+3230 days

Data loading in progress...

Attracting Subscribers
July '26
July '26
+92
in 0 channels
June '26
+79
in 0 channels
Get PRO
May '26
+65
in 0 channels
Get PRO
April '26
+71
in 0 channels
Get PRO
March '26
+79
in 0 channels
Get PRO
February '26
+51
in 0 channels
Get PRO
January '26
+55
in 0 channels
Get PRO
December '25
+46
in 0 channels
Get PRO
November '25
+74
in 1 channels
Get PRO
October '25
+45
in 0 channels
Get PRO
September '25
+36
in 0 channels
Get PRO
August '25
+49
in 0 channels
Get PRO
July '25
+62
in 0 channels
Get PRO
June '25
+55
in 0 channels
Get PRO
May '25
+94
in 0 channels
Get PRO
April '25
+76
in 0 channels
Get PRO
March '25
+70
in 0 channels
Get PRO
February '25
+63
in 0 channels
Get PRO
January '25
+69
in 0 channels
Get PRO
December '24
+114
in 1 channels
Get PRO
November '24
+77
in 0 channels
Get PRO
October '24
+62
in 0 channels
Get PRO
September '24
+58
in 0 channels
Get PRO
August '24
+48
in 1 channels
Get PRO
July '24
+62
in 0 channels
Get PRO
June '24
+40
in 1 channels
Get PRO
May '24
+34
in 0 channels
Get PRO
April '24
+82
in 2 channels
Get PRO
March '24
+59
in 0 channels
Get PRO
February '24
+73
in 1 channels
Get PRO
January '24
+47
in 0 channels
Get PRO
December '23
+39
in 0 channels
Get PRO
November '23
+54
in 1 channels
Get PRO
October '23
+61
in 1 channels
Get PRO
September '23
+47
in 0 channels
Get PRO
August '23
+50
in 0 channels
Get PRO
July '23
+67
in 0 channels
Get PRO
June '23
+71
in 0 channels
Get PRO
May '23
+60
in 0 channels
Get PRO
April '23
+133
in 0 channels
Get PRO
March '23
+243
in 0 channels
Get PRO
February '23
+127
in 0 channels
Get PRO
January '23
+197
in 0 channels
Get PRO
December '22
+212
in 0 channels
Get PRO
November '22
+110
in 0 channels
Get PRO
October '22
+98
in 0 channels
Get PRO
September '22
+70
in 0 channels
Get PRO
August '22
+76
in 0 channels
Get PRO
July '22
+92
in 0 channels
Get PRO
June '22
+121
in 0 channels
Get PRO
May '22
+108
in 0 channels
Get PRO
April '22
+138
in 0 channels
Get PRO
March '22
+198
in 0 channels
Get PRO
February '22
+102
in 0 channels
Get PRO
January '22
+131
in 0 channels
Get PRO
December '21
+113
in 0 channels
Get PRO
November '21
+91
in 0 channels
Get PRO
October '21
+55
in 0 channels
Get PRO
September '21
+57
in 0 channels
Get PRO
August '21
+72
in 0 channels
Get PRO
July '21
+75
in 0 channels
Get PRO
June '21
+100
in 0 channels
Get PRO
May '21
+166
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
23 July+3
22 July+4
21 July+4
20 July+2
19 July+3
18 July+5
17 July+5
16 July+1
15 July+9
14 July+4
13 July+4
12 July+3
11 July+2
10 July+3
09 July+4
08 July+3
07 July+6
06 July+3
05 July+7
04 July+2
03 July+4
02 July+5
01 July+6
Channel Posts
ከደም ልገሳ እና ከመንፈሳዊነት ጋር ተያይዞ፡ በመወያያ ቡድኑ እየቀረቡ ያሉ መረጃዎች ግሩም ናቸው። እኔ በበኩሌ፡ ቤተክርስቲያን፡ "holistic" የኾነ ሕክምና የምትሰጥበት የራሷ ሆስፒታሎችና የሕክምና ኺደት ፕሮቶኮሎች ሊኖሯት ይገባል ባይ ነኝ። ባጋጣሚ አክስቴን ሳስታምም፡ አንዲት ድንገት ገብታ የሞተች አራስ እያየሁ ነበር። ሁኔታዋ ለቤተሰቦቿ ኹሉ ድንገተኛ ስለኾነባቸው፡ ድንጋጤያቸውና ጩኸታቸው እጅግ ያሳዝን ነበር። ደኅና የነበረች ልጅ ናት፡ ድንገት ከአራስ ቤት እየጮኸች መጥታ የሞተችው። የኾነ መንፈስ የመታት ትመስላለች እንጂ፡ ይኼ ነው የሚባል ግልጽ ችግር ያገኙላት አይመስለኝም። እንዲህ ያሉ ነገሮች ብዙ ጊዜ ይፈጠራሉ። የተሻለ ሕክምና ክርስቲያኖችም ኾኑ በጥቅሉ የሰው ልጆች የሚያገኙበት መንገድ መኖር አለበት። አንድ ሰው ማናቸውም ጉዳት ሲደርስበት፡ አስታማሚዎቹ "ጸበል እንውሰደው? ወይስ ባሕላዊ ባለመድኃኒት ጋር ይኺድ? ወይስ ሆስፒታል እንውሰደው?...."  ብለው ግራ መጋባት የለባቸውም። ከሥጋዊ ሐኪም ጋር አብረው መንፈሳዊ ሐኪምና ባሕላዊ ሐኪም እዚያው አንድ ሆስፒታል ውስጥ መገኘት አለባቸው ብዬ አምናለሁ። ጸሎት ለሚያስፈልገው ሰው፡ ግሉኮስ ብቻውን መፍትሔ አይሰጥም። ኦክስጂን ያጠረውን ሰው፡ ጸበል ለመውሰድ ጉዞ መጀመር ስኅተት ይፈጥራል። ምግብ በማጣት ስኳሩ ወርዶ ለወደቀ ሰው፡ የመድኃኒት ብዛት ነፍሱን አያተርፈውም። ሰው የሥጋ፣ የነፍስና የመንፈስ ውሕደት ነው። ሥጋውን ብቻ ማከም መፍትሔ አይሰጥም። ኹሉም ሕክምና በአንድ ቦታ መኖር አለበት። ከዚያም አልፎ፡ መንፈሳዊ ድንበሮችን ያልተላለፉ የሕክምና አሰጣጦችን ያከበረ ሕክምና ክርስቲያኖች ሊኖራቸው ይገባል። እውን የቆረበ ሰው፡ ካልቆረበ ሰው ደም መቀበል ይችላል? አንድ ሐኪም፡ አስቀድሞ ሳይጸልይ ቀዶ ጥገና ማድረግ አለበት? በዓይን የማይታዩ በሽታ አምጪ መናፍስትን፡ disinfect በማድረግ ብቻ ማጥፋት ይቻላል? ካህናትና መነኮሳት የሚታከሙበት መንገድ፡ አንዳንድ ነገሮች ላይ፡ ከምዕመናን ጋር ተመሳሳይ ነው? ....ብዙ ነገር አለ። መቼም መንፈሳዊውም፥ ሥጋዊውም እውቀት ያላቸው ሐኪሞች ብዙ ነገር ሊሉን እንደሚችሉ እገምታለሁ። ይኽን የሕክምና ፕሮቶኮል ወይም ኤቲክስ፡ የዓለም የጤና ድርጅት አይደለም የሚቀርጽልን፤ የኛው ኃላፊነት ነው። ያው... ለወደፊት.... ልብ ስንገዛ ማለቴ ነው። ባሁኑ አያያዝ ግን፡ አስተካክሎ መርፌ የሚወጋ ሐኪምም ማግኘት ትልቅ ነገር ነው።

2
ኮሜዲያን እሸቱ መለሰ ኮሚሽን መብላቱን የሚያሳዩ ማስረጃዎች ወጡ!! ጸበልተኛ ሆናችሁ መንፈስ አልጋለጥ ካላችሁ ይኼንን አድርጉ!! የተሐዲስዎቹ አድሱ ኑፋቄ! https://youtu.be/6y-E3I1TopI
200
3
ይኼንን 10 ምልክት ካያችሁ የማዘግየትና ዕድሜ ጨርስ መንፈስ አድፍጧልና እባካችሁ ንቁ!! አድፍጦ የሚያጠቃንን መንፈስና ሰይጣን ለማሸነፍ!! #አጋንንት #ጸሎት https://youtu.be/BUiTChNHjxA
202
4
በጽዋዕ እና በጽዋው ዣንጥላ የተመተተ አደገኛው የመተት ሴራ ሲገለጥ!! ጽዋው ቤተ ስገባ በረከትና ሰላም አጣሁ እጅግ ያሳዝናል!! #አስገራሚዋ ድንቅ እናት! https://youtu.be/O_mfynItzPs
226
5
"አንተ ራስህ ለገዛ ወንድምህ ጨካኝና ይቅር የማትል ኾነህ ሳለስ እግዚአብሔር እንዲራራልህና እንዲምርህ እንዴት መለመን ይቻልሃል? "ባልንጀራህ ምናልባት ንቆህ ሊኾን ይችላል፡፡ አዎ! አንተ ግን እግዚአብሔርን ኹልጊዜ እንደናቅኸው ነው፡፡ በባልንጀራና በእግዚአብሔር መካከልስ ምን ንጽጽር አለ? ባልንጀራህ ምናልባት ጉዳት ሲደርስበት ሰድቦህ ይኾናል፤ አንተም በዚህ ተበሳጭተህ ይኾናል፡፡ አንተ ግን ምንም ሳይጎዳህና በአንተ ላይ ክፉ ሳያስብ ይልቁንም ዕለት ዕለት በረከቱን እየተቀበልክ እያለ እግዚአብሔርን ሰድበኸዋል፡፡ እንግዲህ ተመልከት! ነቢዩ፡- “እመሰ ኃጢአተኑ ትትዐቀብ እግዚኦ መኑ ይቀውም - አቤቱ ኃጢአትንስ ብትጠባበቅ ማን ይቆማል?” ብሎ እንደ ተናገረ እግዚአብሔር በእርሱ ላይ የምንፈጽመውን በደል ቢመረምር ኖሮ አንዲት ቀንስ እንኳን በሕይወት መቆየት አንችልም ነበር (መዝ.129፡3)፡፡ እያንዳንዱ በደለኛ ሰው ለራሱ የሚያውቀውንና ሌላ ሰው የማይመሰክርበትን እግዚአብሔር ብቻዉን ግን የሚያውቀውንስ ይቅርና የተገለጠውና ሰው ኹሉ የሚያውቀው ኃጢአታችንን እንኳን እግዚአብሔር ቢቈጣጠር ኖሮ ከእነዚህ ኃጢአቶች በኋላ የምንጠብቀው ምንድን ነው? እግዚአብሔር ንዝህላልነታችንንና ጸሎት ስናደርስ የምናሳየው ግድየለሽነታችንን፣ ሠራተኞች ለአሠሪዎቻቸው ወታደሮችም ለአለቆቻቸው ጓደኛሞች ለጓደኞቻቸው የሚያሳዩትን ፍርሐትና ክብር ያህልስ እንኳን ለጸሎትና ለልመና በፊቱ በቆምን ጊዜ አለማሳየታችንን ቢቈጣጠር ኖሮ ምን ነበር የምንኾነው? አንተ ከጓደኛህ ጋር ስትነጋገር ለምታደርገው ማንኛውም ነገር ትጠነቀቃለህ፡፡ ስለ በደሎችህ እግዚአብሔርን ስትጠብቀው፣ ለብዙ መተላለፎችህ ይቅርታን ስትጠይቀው፣ ሥርየትን ለማግኘት ስታሳስበው ግን [በፊቱ ላይ] ኹልጊዜ ግድየለሽ ትኾናለህ፡፡ ጉልበትህ በምድር ላይ ተንበርክኮ ሳለ ልቡናህ ግን እዚህም እዚያም፣ በገበያ ሥፍራም፣ በቤት ውስጥም ይዋልላል፤ ከንፈርህ በከንቱና እንዲሁ ያነበንባል፤ ይህን የምንፈጽመው ደግሞ አንዴ ወይም ኹለቴ ሳይኾን ኹልጊዜ ነው። እንግዲህ እግዚአብሔር ይህን ብቻ እንኳን ቢመረምር ይቅርታን ወይም ምሕረትን እንደምናገኝ ታስባለህን? በእውነት አይመስለኝም!" #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
253
6
No text...
229
7
በክርስቲያኖች መካከል ለምን ጠብ በዛ? ቁም ነገር ተባብረው በመሥራት ፈንታ፡ ለምን ቡድንተኝነት፣ ክርክር፣ ክፍፍል ወዘተ ያዘወትራሉ? ይኽን ጥያቄ የሚጠይቁ ሰዎች፡ ሰላምና ፍቅር ወዳድ ሰዎች ተብለው ይሞገሱ ይኾናል። አዎ፤ ሰላም ይወዳሉ። ነገር ግን፡ ብዙ ጊዜ፡ ሰነፎች ናቸው። የነገሮችን ጥልቀትና የውትብትቡን ዓይነት ጊዜ ወስደው ለመረዳት ተነሳሽነቱ የላቸውም። በደፈናው ብቻ "ቤተእግዚአብሔር ውስጥ ቁጭ ብለው ይጣላሉ" እያሉ መታዘብ ደስ የሚላቸው ናቸው። "ሃይማኖተኛ ነኝ እያሉ ይጨቃጨቃሉ" እያሉ ያማሉ፤ ያላግጣሉ፤ ይታዘባሉ። "እኔ'ኮ ብዙም አልቀርብም፡ ከውጪ ተሳልሜ ብቻ ስለምኼድ፡ ነገር ውስጥ አልገባም" በማለትም በስንፍናቸው ይመካሉ። በውስጥ ኾኖ ግን፡ የተለያየ ሠርጎ ገብ ዓላማ ይዘው ከገቡ ፖለቲከኞች፣ መናፍቆች፣ ጠንቋዮችና ሌቦች ጋር ትንቅንቅ የገጠመ መኖሩን አይረዱም። ትክክለኛውን ሥርዓተ ቤተክርስቲያን ለማጥናትና በጠብ የተጎዱትን ወይም ተስፋ ቆርጠው ዝም ያሉትን ለማገዝ ፈቃደኝነት የላቸውም። ብቻ ግን ኹሉ ነገር ሰላም ኾኖላቸው፡ ሆቴል ሲኼዱ ጥሩ መስተንግዶ አግኝተው እንደሚወጡ ኹሉ፥ ቤተክርስቲያንም ሲመጡ ጥሩ መስተንግዶ አግኝተው መውጣት ነው የሚፈልጉት። ጠጋ ብለው ግን አያዩም። Tourist ናቸው። ብዙ ኦርቶዶክሳውያን እንዲህ ናቸው። ጠጋ ብለው፥ ጊዜ ወስደው፥ የቤተክርስቲያንን ትምህርት አጥንተው፥ ነገሮችን በጽሙና ቢገመግሙ ግን፡ ቤተክርስቲያን ብዙም ሰው እንደሌላት ይረዱ ነበር። ግልጽና ሥውር የኾነ ብዙ የዲያቢሎስ ተንኮል መኖሩን ያዩ ነበር። እንደ አገር፡ ከሦስቱ የኢትዮጵያውያን ዋና ዋና መርኆች መካካል አንዱ፡ "ጥበብን እያጠኑ መኖር" ነው። ይኽ፡ ሃይማኖትንና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን በሚችሉት ዓቅም ሲማሩና ሲያጠኑ መኖርን ያካትታል። ሐዋርያት እንዳስተማሩን፡ ይኽ፡ ለልጅ ልጅ የሚተርፍ ብዙ በረከትን የሚያስገኝ የኹሉ ክርስቲያን ግዴታ ነው። ብዙ ክርስቲያኖች ግን፡ አንድም ነገር ሳይገነዘቡ "ውይይይ! ኹል ጊዜ ጠብ ብቻ! በናታችሁ ተስማሙ?!" እያሉ እየታዘቡ ይኼዳሉ። ሰው በከፈለው መሥዋዕትነት እየኖሩ እንዳሉም አያውቁም። የጥፋት ርኩሰት፡ በተቀደሰው ቦታ፡ ነጠላ ለብሶ፡ ተመሳስሎ፡ ቆሞ ነገሮችን አንቆ እንዳለ አያስተውሉም። በእውነተኛውም፣ በሐሰተኛውም ላይ እኩል ፈርደው ይኼዳሉ። ከዚያም አልፈው፡ ሳያውቁት፡ ክፉውን ወገንም ሊያግዙ ይችላሉ። ብዙዎቹ እንዲህ ናቸው። አቋም ያላቸው ቢኾኑ ግን፥ እውነት ለአምላካቸው ፍቅር ቢኖራቸው ኖሮ፡ ከማን ጋር መቆም እንዳለባቸው ተረድተው፥ በአንድነት ቆመው፡ መኾን ያለበትን አስፈጽመው፥ መኾን የሌለበትን አስቁመው፡ ቤተክርስቲያን፡ ከእለት ጭቅጭቅ ወጥታ፡ በትውልዱ ላይ ያላትን ተልዕኮ መፈጸም እንድትችል ጉልበት ይኾኗት ነበር። የሐዋርያት ትምህርት ያ ነበረ!
224
8
ትክክለኛ ጸሎትን ለመለማመድና ለማድረግ ይኼንን በማድረግ አሁኑኑ ጀምሩ!! መቅበዝበዝና ፍርሃት ካለባችሁ ማታ ማታ ይኼንን ጸልዩ! መንፈሳዊ ግዴለሽነትና መዘዙ! https://youtu.be/HGGq9RZcyBk
231
9
አዲስ ቪዲዮ ይኼው: https://youtu.be/IeRg0PZH4so?si=kxVKqkOraRF-WthN
234
10
ኢትዮጵያ፡ የአዳምና የሔዋን ተስፋ የኾነችው፡ የፅዮን አገር ናት። ገና ከጥንቱ፡ "ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" ብሎ ቃል ኪዳን ከገባበት ጊዜ አንሥቶ፡ "አምላክን ወልዳ ታድነናለች" ብሎ፡ ድንግል ማርያምን በተስፋ ሲጠባበቃት የኖረው፡ የሴም፣ የካም፥ የያፌት ድብልቅ ሕዝብ ያለባት አገር ናት። አብያተ መቅደሶች በምድሪቱ መታነጽ ሲጀምሩ፡ 7500 ዓመት አለፋቸው። ይኽ እንደመልከ ጼዴቅ ድብልቅ የኾነ አዳማዊ የአምላክ ሕዝብ፡ በዘመናት ሂደት፡ የአሁኗን ኢትዮጵያ ብቻ ሳይኾን፡ አብዛኛውን አፍሪካ እና የእስያ መካከለኛና ደቡብ ክፍሎች ጨምሮ የያዘ ሕዝብ ነው። ለዚህም ማረጋገጫ፡ በጄኔቲክ ጥናቶች እንደሚታየው፡ ከዚህ አዳማዊ የውሕደት የዘር ግንድ ጥንታዊ ዘረ መል ጋር የማይገናኝ የሰው ዘር የለም። "ኢትዮጵያውያን በጣም ጥንታዊ ዘረ መል አሁንም በሰውነታቸው ተሸክመዋል" ይላሉ - አጥኚዎች። ይኽ አዳማዊ ሕዝብ፡ "እግዚአብሔር በሴም ድንኳን ይደር" የተባለውን ምርቃታዊ ትንቢት ወድዶና አፍቅሮ፡ የአብርሃምን ዘር በመውደድ፣ በመዛመድ፣ በመዋለድ፣ ርስታቸውን በመጠበቅና በማስጠበቅ፡ ከሴቲቱና ከመሢሁ ገብቶ የተቆጠረ ትውልድ ለመኾን በቅቷል። ዲያቢሎስ፡ ኢትዮጵያዊውን የዓለም ሕዝብ የተዋጋው፡ በዘረኝነት ነው። በቅድሚያ፡ ነጩን የያፌት ዘር፡ "አንተ እኮ በኦሊምፐስ ተራራ ይኖሩ የነበሩ አማልእክት ዘር ነህ። እንዴት ከጠይም፣ ጥቁር፣ ቡኒ ሕዝብ ጋር ትቀላቀላለህ? ዘርህን አጥራ፤ አንተ እንደአማልእክት፡ ቆዳህ ነጭ፥ ዓይንህ ሰማያዊ፥ ጠጉርህ ቢጫ ነው። ይኽን ከምታጣ፡ እርስ በርስ ከቤተሰብ ተዋልደህም ቢኾን ዘርህን አስቀጥል" በማለት፡ ተቀላቅሎ መጠየምን እንዲጠየፍና የቆሸሸ እንዲመስለው በማድረግ፡ እስከ Nazi Aryan Race theory ድረስ ለዘለቀ ዘረኛ አስተሳሰብ አስተማቸው። የጥቁርን ሕዝብም ባርያ ማድረግ ሥራቸው መስሏቸው ቀረ። የእስያን ሕዝብ ደግሞ፡ "እናንተ እኮ ቀይ ሕዝብ ናችሁ? ከአማልእክት የተቀዳችሁ፡ የተለየ መንፈሳዊ ዘሮች ናችሁ። በመንፈሳዊ ጥበብ እናንተን የሚተካከል የለም። እንዴት ከድብልቅልቅ ኢትዮጵያውያን ጋር ትቀላቀላላችሁ? እናንተ ጥቁር ፀጉራችሁ ረዥም፥ ቆዳችሁ ቀይ፥ የሴቶቻችሁ ወገብ እንደደራጎን መጥመልመል የሚችል ቀጭን፥ ባሕላችሁና አምልኮታችሁ እስከ ፀሓይና ጨረቃ የሚደርስ ነው። እርስ በርስ በቤተሰብ ውስጥ እየተጋባችሁም ቢኾን፡ ዘራችሁን አጥሩ" እያለ፡ አዳማዊውን ኢትዮጵያዊ የውሕደት ዘር እንዲጠሉ፥ ጥቁር ሕዝብን እንዲጠየፉ፥ "የጠራን ዘሮች ነን" ብለው እንዲኮፈሱ አድርጎ ጣዖታት ሥር ገተራቸው። ጥቁሩን ሕዝብ ደግሞ፡ "እናንተ ጥቁሮች፡ የፀሐይ ኃይል በደማችሁ ያለ፡ የተለያችሁ ጠንካራ፡ ተፈጥሮ ብዙ ዓቅምና ችሎታ ያደለቻችሁ ሰፊ ሕዝቦች ናችሁ። እነዚህ አንዴ ጥቁር፥ አንዴ ቀይ፥ አንዴ ጠይም እየኾኑ ከሚዋለዷችሁ ኢትዮጵያውያን ጋር ምን ጉዳይ አላችሁ? እናንተ እኮ ኢትዮጵያውያን አይደላችሁም? አፍሪካውያን ናችሁ! ከዐረብ፥ ከፈረንጅ ከጥቁር እንደሁኔታው ከሚመሳሰል ድብልቅ ሐበሻ ጋር ምን ትሠራላችሁ?የነርሱ ዓላማ እኮ፡ ከቀያዮቹና ነጫጮቹ ጋር ተመሳጥረው እናንተን ባርያ አድርጎ መግዛት ነው? እናንተ ሙሉ ጥቁር ሕዝብ ናችሁ። ከግዛታችሁ ፈካ የሚሉትን አስወግዱ። እነሱ አቢሲንያውያን ናቸው" እያለ፡ እስከ ሩዋንዳው የቱትሲዎች ጭፍጨፋ ድረስ የዘለቀ የ"ሐበሽን ማጥፋት"ና በምትኹ የ"ንፁህ ኩሻዊነትን" የማስቀጠል ዘረኝነት አስተማራቸው። እንዲህ አድርጎ፡ እግዚአብሔር በዳግማዊው አዳም፥ በአማናዊው መልከጼዴቅ በክርስቶስ ሰውነት ውስጥ አንድ ያደረገውን ኢትዮጵያዊ ዘር፡ መልሶ ወደ ሴም፣ ካም፣ ያፌት ዘረኝነት ከፈለው። ከተዋሕዶ ውጭ የተመሠረቱ እምነቶች በሙሉ፡ ዲያቢሎስ፡ እንዲህ ላለ የዘረኝነት ፖለቲካ እንዲመቸው የፈጠራቸው ናቸው። ሃይማኖት ፖለቲካ ነው፤ ፖለቲካም ሃይማኖት ነው። ካቶሊክን ለነጩ ሕዝብ ፈጠረለት። እስልምናን ለዐረቡ ፈጠረለት። ባሕላዊ እምነትን ለጥቁሩ ሰጠ። አይሁዶችን፡ ወደ እውነተኛዋ ፅዮን እንዳይመጡ፡ በሌላ ፅዮናዊነት ለከፋቸው። ተዋሕዶ፥ እውነተኛዋ አዳማዊ የዓለም ሕዝብ ሃይማኖት ግን፡ ኢትዮጵያዊነታቸውን መካድ በማይፈልጉ ኢትዮጵያውያን ተይዛ ቀረች። ያሁኑ "እኔ ንፁሕ ኩሽ ነኝ"፥ "እኔ ንፁሕ ሴም ነኝ"፥ "እኔ ንፁሕ ያፌት/ጣልያን ነኝ" የሚያስብላቸው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ጠብ፡ ራሳቸውን፡ ልክ እንደ ሌላው ዓለም፡ ከዚህ ኢትዮጵያዊ ዘርነት ለማውጣት የሚታገሉበት ኺደት የወለደው የመጨረሻው መፍጨርጨር ነው። ግን፡ በእውኑ ኢትዮጵያዊ መልኩን፥ ነብር ዝንጉርጉርነቱን ይለውጥ ዘንድ ይችላልን? የሚገርመው፡ አንድነቱን የሚጠሉት፡ በእግዚአብሔር ሥር ሲኾን እንጂ፡ ለዓመፃ ሲኾን ግን፡ ኹሉም ጽንፈኛ ብሔርተኞች ኅብረት ይፈጥራሉ። ኦነግና ሻዕቢያ፥ ሕወኃትና ጀብሃ፥ ምንጥስና ምንጥስ፡ ኢትዮጵያዊነትን ለመዋጋት አንድ ላይ መቆም አይከብዳቸውም። ማፍያና አልቃይዳ፣ አልሻባብና ሲ አይ ኤ፣ ቦኮ ሃራምና ኒዮ ናዚ... ለጥፋት ሲኾን የኾነ ቦታ ይገናኛሉ። መንገዱ አይጠፋቸውም። በእግዚአብሔር ሥር በተዋሕዶ አንድ መኾን ግን፡ የሚገድላቸው ይመስላቸዋል። እኛ ፅዮናውያን ግን፡ የምናውቀው ንጹሕ ዘር፡ የድንግልን ዘር ነው። ኢየሱስ ክርስቶስን ነው።
353
11
እባካችሁ ይኼንን ምልክት ካያችሁ የዛር አይነጥላ አጋንንት ውስጣችን አድፍጧልና ንቁበት!! አጋንንት ክርስቲያኖችን የሚፈትንባቸው መንገዶች!! #አጋንንት #ጸሎት https://youtu.be/GHgu08p2tgU
251
12
ስለአገር ባለቤትነት የእስልምና እምነት መምህራን ስለ አገር ባለቤትነት እያወሩ ነው። በጣም እናመሰግናለን! በሩ ተከፍቶልናል! እኛም እናውራ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች የአገር
ስለአገር ባለቤትነት የእስልምና እምነት መምህራን ስለ አገር ባለቤትነት እያወሩ ነው። በጣም እናመሰግናለን! በሩ ተከፍቶልናል! እኛም እናውራ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች የአገር ባለቤትነታቸውን ማን ሰጣቸው? ከየት አገኙት? አገሩ የማነው? የመሠረታት ማነው? በምን መርኆች ላይ ተመሠረተች? "የክርስቲያን ደሴት" ለምን ተባለች? የተሟላ፤ የተተነተነ፤ የታወቀ፤ የተራቀቀ ታሪክና መልስ ስላለን፡ ስለአገራችንና እኛ ስለምናውቃቸው ባለቤቶቿ እናውራ። እኔ ቀድሜ ነው ማውራት የጀመርኩት። ኦርቶዶክሳዊ ኹሉ ማውራት አለበት። በሩ ተከፍቶልናል። ተፈቅዷል። አውሩ!! የባለቤትነት መብት መጠየቅ ይቻላል። ባለቤትም መኾን ይቻላል። ባለቤቶችም ነን። በኢትዮጵያዊነትና በአገር ባለቤትነት መብት፡ እኛን ጽዮናውያንን  የሚቀድመን የለም። ለትንሽ ጊዜ ባለቤት መኾናችንን ረስተነው ነበር። አሁን እያስታወስን ነው። በገዛ እጃቸው ቆስቁሰው እያስታወሱን ነው። እንኳን የኢትዮጵያ፡ የአፍሪካ ባለቤቶች ነን። ኹልሽም በማርያም መቀነት ልትጠቀለዪ ነው፤ ተዘጋጂ።
275
13
https://youtu.be/5Zv3elhs_aY?si=S_9bg9u83sz1PgKW
254
14
በትክክል መስገድና መጸለይ ስትጀምር የሚገለጥልህ አስደናቂ ምስጢር!! በሰው ውስጥ አጋንንት እንዴት ያድራል ከባባድ እውነቶች!! @nkutamirtsion https://youtu.be/HlMDYEJ97-k
308
15
ሌላውን እንተወውና፦ ደም፣ ወተት፣ ሥጋስ ይሁን ቆዳ እና ቀንድ ግን መድኃኒትነታቸው ለመጋረፍና ለመዋጋት ነው ይሆን? 😂 ማስታወሻ፡ ባሕላዊ ሕክምናን እና ጥንቊልናን እየለየን ወገን!! እባካችሁን መ
ሌላውን እንተወውና፦ ደም፣ ወተት፣ ሥጋስ ይሁን ቆዳ እና ቀንድ ግን መድኃኒትነታቸው ለመጋረፍና ለመዋጋት ነው ይሆን? 😂 ማስታወሻ፡ ባሕላዊ ሕክምናን እና ጥንቊልናን እየለየን ወገን!! እባካችሁን መንቃት ያለብን ጊዜ አሁን ነው!!
328
16
No text...
295
17
"ፀረ-ተዋሕዶ እምነቶች የሚስፋፉት በተንኮል ብቻ ነው፤ የሚያሸንፉበት እውነት ስለሌላቸው!" መንግሥት፡ የቤት አጋዦች፡ በቀን ከ8 ሰዓት በላይ እንዳይሠሩ የሚያግድ መመሪያ ሊያወጣ እየመከረበት እንደኾነ፡ ዜናውን ሰማሁ። እናንተስ ሰምታኋል? "ረቂቁ፡ የተወሰኑ የተቃውሞ ድምፆች ቀርበውበታል" ይላል ዜናው። "የእያንዳንዱ ቤት ነባራዊ ሁኔታ የተለያየ ነው፤ ይኽ በአሠሪና በሠራተኛ መካከል በሚደረስበት ስምምነት መወሰን ያለበት ነው" ወዘተ ... የሚሉ የተቃውሞ ሃሳቦች ተነሥተዋል። የቤት ሠራተኞች ጉዳይ ላይ፡ በከፍተኛ ትኩረት፡ በዚህ እስላማዊ-ፕሮቴስታንታዊ መንግሥት እየተሠራ ነው። ብዙዎች ወደ ዐረብ አገራት እንዲጎርፉ፡ ከባድ ሥራ እየተሠራ ነው። በተለይ ደግሞ ክርስቲያኖች እንዲኼዱ ነው በምዝገባ እየተሠራ ያለው። ሙስሊም ሴቶች ደግሞ በብዛት እንዳይኼዱ እየተነገራቸው ነው። ይኽ፡ ክፍለ አገር ላይ ከሚሠራ ደላላ የሰማሁት ነው። "ክርስቲያን የቤት ሠራተኛ የለኝም፤ ሙስሊም ትፈልጊያለሽ?" መባል ተጀምሯል። ስሌቱ ግልጽ ነው። ከዚህ የሚኼዱት ክርስቲያኖች፡ ዐረብ አገር ኼደው በተጽዕኖ ይሰልማሉ። እዚህ ደግሞ፡ በብዛት ሙስሊሞች ይቀራሉ ነው። የመንግሥት ረቂቅ ደግሞ፡ ይኽንኑ የእስልምና ማስፋፋት ፍላጎት የሚያግዝ ነው። በቀን 8 ሰዓት የሚል ሕግ ቢወጣ፡ ብዙ ቤቶች ሊረበሹ ነው። ሠራተኛዋ፡ ሰዓቷን አይታ፡ ቀጣሪዋን፡ "ከዚህ በኋላ አታዢኝም" ማለት ልትጀምር ነው። ያም ኾኖ ግን፡ ቀጣሪዋ፡ የቤት አጋዧን፡ በቤቷ ልታኖራት፣ ምግብ ልታበላትና እንደቤተሰብ ልታያት ተጨማሪ ግፊት አለባት። እያበላች፣ እያጠጣች፣ እያኖረች፣ ደግሞም እየከፈለች፣ ምናልባትም እንደቤተሰብ እያሳከመቻት ጭምር፡ "ከ8 ሰዓት በላይ ልታሠሪያት አትችዪም" ልትባል ነው። "በቀን 8 ሰዓት ገደብ" የሚል ነገር ከመጣ፡ የቤት አጋዦች፡ ቤት ተከራይተው፥ ውጭ እያደሩ፥ ምግባቸውንና የግል ጣጣቸውን ኹሉ ራሳቸው ችለው፡ ለሥራ ብቻ ነው መምጣት ያለባቸው። ያ ከኾነ ደግሞ፡ ኹሉም ተመላላሽ ሠራተኛ ሊኾን ነው። እንዲያ ከኾነ፡ በጥቅሉ፡ የቤት ሠራተኞችና አሠሪዎች ግንኙነት መሠረታዊ ቅርጹ ይዛባል። ጠቅላላ ሥራ አንድ ነገር ነው፤ ደመወዙም የተሻለ ነው። ተመላላሽ ደግሞ፡ ደመወዙ ዝቅተኛ መኾን አለበት። ይኽ ግን፡ በውጭው ዓለም እንኳ የሌለ አሠራር ነው። በውጭው ዓለም፡ አጋዦች (house maids)፡ አንዴ በደመወዝ ተስማምተው ከተቀጠሩና ጠቅልለው ወደአሠሪዎቻቸው ቤት ከገቡ በኋላ፡ በጉዞ "አብረሽኝ ኼደሽ አግዢኝ" ቢባሉ እንኳ፡ አብረው የመጓዝ የውዴታ ግዴታ አለባቸው። ለመኾኑ፡ እያንዳንዱ ቤት፡ የትኛው ሰዓት ላይ የበለጠውን እገዛ እንደሚፈልግ፥ የትኛው ሰዓት ላይ ደግሞ የሥራ ጫና እንደማይኖርበት፡ መንግሥት ዐውቆ ወጥ የኾነ ሕግ ማውጣት ይችላልን? በጭራሽ እኮ አይችልም? እንዲህ ያለው ሕግ ዓላማው አንድ ነው። የቤት ሠራተኞች፡ በቤት ሠራተኝነት ስለተቀጠሩ ብቻ እንደተበደሉ እንዲሰማቸው፥ ኢትዮጵያ ውስጥ መቀጠር እንቢ እንዲሉ፥ ወደ ዐረብ አገራት ብቻ እንዲኼዱ፤ ሙስሊም ሠራተኞች ደግሞ ሙስሊም ቤተሰቦችን እዚሁ ኾነው እንዲረዱና እንዲደግፉ፤ በኢትዮጵያ ያሉ ክርስቲያን ቤተሰቦች ደግሞ፡ በሥራ ጫና እንዲዳከሙና ማንሠራራት እንዳይችሉ፥ ቁጥራቸውም እንዲቀንስ ነው። ይኽን አይቶ፡ አመራር የሚሰጥ የቤተክርስቲያን አባት ግን የለም። እግዚአብሔር ግን አለ። እርሱም ፍርድ ይሰጣል። በዚህ ኹሉ ሤራ ውስጥ፡ እርሱም የራሱ ዕቅድ አለው። የሤራ መዓት ሲጎነጉኑ ቢኖሩ፡ ተዋሕዶ የዓለም ሕዝብ ሃይማኖት ትኾናለች። የኢትዮጵያ ትንሣኤ የተዋሕዶ እምነት ትንሣኤ ነው። ግፈኞችና ተንኮለኞች የዘለዓለም ፍርድን ይቀበላሉ። የተዋሕዶ እምነት፡ የተዋጓትን ኹለ ትፋረዳቸዋለች። ፅዮን፥ ሕንደኬ፥ ንግሥተ አዜብ፡ ኹሉንም ታሳፍራለች። የድንግል ማርያም ዐሥራት አገር፡ ያሤሩባትን ኹሉ ታሸንፋለች። እኔ በግሌ ደስ የሚለኝ ግን፡ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ የኖሩ የተለያዩ እምነቶች፡ ከተዋሕዶ በቀር፡ የተስፋፉት፡ ውስጣቸው ባለው እውነት ወይም አምላካዊ ኃይል ሳይኾን፡ እንዲህ በሤራና በተንኮል መኾኑን እንድናውቅ እግዚአብሔር እያሳየን መኾኑ ነው። ከተዋሕዶ በቀር ሌሎች እምነቶች መሠረታቸው አሸዋ መኾኑን እርግጠኛ ኾነን ማየት ችለናል። በአሸዋ ላይ የተሠራ ቤት ደግሞ፡ ይፈራርሳል!
329
18
በጸሎትና ስግደት ህይወታችሁ ይኼንን ግዴታ ሁላችሁም ልታውቁ ይገባል!! ይቅርታ መጠየቅ ሽንፈት የሚመስላችሁ ይሄን አዳምጡ!! #ቤተክርስቲያናችን #ጥንቃቄ #ንቁ https://youtu.be/3Rf7pMivKfE
297
19
No text...
343
20
አንድ ነገር እንድታስቡ ልጋብዛችሁ፦ በአገራችን ሙስና ስለበዛ፣ ሞጭላፋነት ስለተንሠራፋ፣ የሥራ ethics ስለጠፋ፣ ሥርዓት ስለሌለን፣ ጋጠወጥ ስለኾንን፡ በሌላው ዓለም ያሉ የተለያዩ በጐ ሃሳብና ገንዘብ ያላቸው ድርጅቶችና ግለሰቦች፡ ገንዘባቸውን ይዘው መጥተው ከእኛ ጋር ለመሥራት ካሰቡ በኋላ፡ ሁኔታችንን ሲያዩ  ሃሳባቸውን እንደሚሠርዙ ታውቃላችሁ? እና፡ እኛ፡ የገንዘብ ችግር ነው ወይ ትልቁ ችግራችን? አይደለም! የስብዕና ችግር እንጂ!! የኢትዮጵያ አየር መንገድን ያኽል ትልቅ ተቋም በማቋቋም ካገዙን ወሳኝ ሰዎች መካከል እኮ፡ በኢትዮጵያውያን የጀግንነት፣ የሉዓላዊነት፣ የዕድገት ፈላጊነትና የሥራ ባሕል ጥንካሬ የተማመኑ ጥቁር አሜሪካውያንም ነበሩበት!? ስነ ሥርዓት ቢኖረን፡  አብሮን የሚሠራ ብዙ ፍላጐት ያለው ነበረ እኮ?! ሞጭላፋ፣ ባለጌ፣ ቀጣፊ፣ ዱርዬ፣ ከሐዲና ገንዘብ-አምላኪ ስብዕናችን ነው እኮ ገንዘብ እንዳይኖረን ያደረገን?!  የዘር ፖለቲካና የዛርና የመተት ሥራ ተብትቦ አደኸየን እንጂ፡ ገንዘብ መች ይቸግረን ነበር? እኔ እንኳን፡ አንድ ጊዜ፡ በዚሁ መድረክ ላይ፡ አስተዛዝና "በሚካኤል በገብርኤል" ብላ ለምናኝ፡ "እመልሳለሁ" ብላ ምላ ተገዝታ፡ ገንዘብ አምኜ አበድሬያት፡ block ያደረገችኝ ከሐዲ ገጥማኛለች። "ትንሽ ቆዪኝ፤ አሁን የለኝም፤ ቆይቼ ልክፈልሽ" ብትለኝ አልጫናትም ነበር። ባለጌ ስለኾነች block አደረገችኝ። አሁን እሷ "ልሞት ነው፤ 10 ብር ስጪኝ" ብትለኝም፡ አምኜ የምሰጣት አይመስለኝም። እንዲህ ወራዳ ባሕሪ እንዲኖረን ተደርገን ተቀርጸናል። እና እኛ ችግራችን ገንዘብ ነው? አይደለም! በጐ ስብዕና ነው የጠፋብን። "እነዚህ ሰዎች፡ ገንዘብ ብንናበድራቸው ይክዱናል፤ ብንሰጣቸው፡ ከክፋታቸው የተነሣ፡ ቁም ነገር ላይ አያውሉትም" ብለው ገንዘብ የሚከለክሉን ብዙዎች ኢትዮጵያውያንም፥ ሌሎችም አሉ። "ድህነት ጠላታችን ነው" ሲባል፡ "የቱ ድህነት?" ብለን መጠየቅ አለብን። የቁስ ድህነት በራሱ ሰውን ከስብዕና ክብር አያወርደውም።  በየመንገዱ ወድቀው ዳዊታቸውን እየደገሙ፡ ለሕዝብና ለአገር እየጸለዩ፡ ሰዎችን በምክራቸውና በፀጋቸው የረዱ፡ ዳግማዊ ገብረ ክርስቶስ የኾኑ ብዙ "የኔ ቢጤዎችን" ዓይናችን አይታለች። ሰውን ከክብር የሚያወርደው፡ የአስተሳሰብና የመንፈሳዊነት ድህነት ነው። እግዚአብሔርን የካደ፡ ምን ገንዘብ ቢኖረው፡ እርሱ ምስኪን ድሃ ነው! በርሱ ምክንያት ድህነት ይስፋፋል እንጂ፡ አይቀንስም።
355