uk
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Відкрити в Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Показати більше
2 280
Підписники
Немає даних24 години
+117 днів
+3830 день

Триває завантаження даних...

Хмара тегів
Немає даних
Виникли проблеми? Будь ласка, оновіть сторінку або зверніться до нашого support-менеджера.
Вхідні та вихідні згадування
---
---
---
---
---
---
Залучення підписників
липень '26
липень '26
+39
в 0 каналах
червень '26
+79
в 0 каналах
Get PRO
травень '26
+65
в 0 каналах
Get PRO
квітень '26
+71
в 0 каналах
Get PRO
березень '26
+79
в 0 каналах
Get PRO
лютий '26
+51
в 0 каналах
Get PRO
січень '26
+55
в 0 каналах
Get PRO
грудень '25
+46
в 0 каналах
Get PRO
листопад '25
+74
в 1 каналах
Get PRO
жовтень '25
+45
в 0 каналах
Get PRO
вересень '25
+36
в 0 каналах
Get PRO
серпень '25
+49
в 0 каналах
Get PRO
липень '25
+62
в 0 каналах
Get PRO
червень '25
+55
в 0 каналах
Get PRO
травень '25
+94
в 0 каналах
Get PRO
квітень '25
+76
в 0 каналах
Get PRO
березень '25
+70
в 0 каналах
Get PRO
лютий '25
+63
в 0 каналах
Get PRO
січень '25
+69
в 0 каналах
Get PRO
грудень '24
+114
в 1 каналах
Get PRO
листопад '24
+77
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '24
+62
в 0 каналах
Get PRO
вересень '24
+58
в 0 каналах
Get PRO
серпень '24
+48
в 1 каналах
Get PRO
липень '24
+62
в 0 каналах
Get PRO
червень '24
+40
в 1 каналах
Get PRO
травень '24
+34
в 0 каналах
Get PRO
квітень '24
+82
в 2 каналах
Get PRO
березень '24
+59
в 0 каналах
Get PRO
лютий '24
+73
в 1 каналах
Get PRO
січень '24
+47
в 0 каналах
Get PRO
грудень '23
+39
в 0 каналах
Get PRO
листопад '23
+54
в 1 каналах
Get PRO
жовтень '23
+61
в 1 каналах
Get PRO
вересень '23
+47
в 0 каналах
Get PRO
серпень '23
+50
в 0 каналах
Get PRO
липень '23
+67
в 0 каналах
Get PRO
червень '23
+71
в 0 каналах
Get PRO
травень '23
+60
в 0 каналах
Get PRO
квітень '23
+133
в 0 каналах
Get PRO
березень '23
+243
в 0 каналах
Get PRO
лютий '23
+127
в 0 каналах
Get PRO
січень '23
+197
в 0 каналах
Get PRO
грудень '22
+212
в 0 каналах
Get PRO
листопад '22
+110
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '22
+98
в 0 каналах
Get PRO
вересень '22
+70
в 0 каналах
Get PRO
серпень '22
+76
в 0 каналах
Get PRO
липень '22
+92
в 0 каналах
Get PRO
червень '22
+121
в 0 каналах
Get PRO
травень '22
+108
в 0 каналах
Get PRO
квітень '22
+138
в 0 каналах
Get PRO
березень '22
+198
в 0 каналах
Get PRO
лютий '22
+102
в 0 каналах
Get PRO
січень '22
+131
в 0 каналах
Get PRO
грудень '21
+113
в 0 каналах
Get PRO
листопад '21
+91
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '21
+55
в 0 каналах
Get PRO
вересень '21
+57
в 0 каналах
Get PRO
серпень '21
+72
в 0 каналах
Get PRO
липень '21
+75
в 0 каналах
Get PRO
червень '21
+100
в 0 каналах
Get PRO
травень '21
+166
в 0 каналах
Дата
Залучення підписників
Згадування
Канали
09 липня+3
08 липня+3
07 липня+6
06 липня+3
05 липня+7
04 липня+2
03 липня+4
02 липня+5
01 липня+6
Дописи каналу
2
"አባት አገር"? ወይስ "እናት አገር?" * * * ብዙ ጥንታዊ የአውሮፓ፣ የዐረብ፣ እና የእስያ አገራት፡ አገራቸውን ለመጥራት፡ "አባት አገር" ("Fatherland") የሚለውን አገላለጽ ይጠቀማሉ። ለምሳሌ፦ የግሪኮ-ሮማን አገራት፥ የስካንዲኔቭያን አገራት፣ ጀርመንና ኦስትርያ፣ የእንግሊዝ ደሴቶች፣ የዐረብ አገራት፣ ወዘተ...። "አባት አገር" የሚሉት፡ ብዙውን ጊዜ፡ መሪውንና ተዋጊውን ክፍል (Imperial class) ለማመልከት ነው። እነዚህ፡ ማን እንደሚኖርና ማን እንደሚሞት የመወሰን አምባ ገነናዊ ሥልጣን ያላቸው ፈላጭ ቆራጮች ናቸው። የፈለጉትን ይነጥቃሉ፤ የፈለጉትን ተጠርጎ እንዲገደል ይወስናሉ፤ የፈለጉትን ይወርሳሉ፥ ያሥራሉ፥ ይፈታሉ። ሕግ አይገዛቸውም። በሕዝባቸው ላይ ብቻ ሳይኾን፡ በገዛ ልጆቻቸው ላይ ሳይቀር ጨካኞች ናቸው። አብዛኞቹ የአፍሪካ አገራት ደግሞ፡ "እናት አገር" ("Motherland") የሚለውን አገላለጽ ይጠቀማሉ። መሬቲቱን፥ የተፈጥሮ ሀብቶቿንና ሕዝቧን ለማመልከት ነው። በታሪክ፣ በባሕልና በደም ትሥሥር ላይ ያተኩራሉ። ከእስያም፡ ሕንድ፣ ቻይና እና አንዳንድ ትናንሽ ደሴቶችና አገራት፡ ይኽን የ"እናት አገር" አገላለጽ ይጠቀማሉ። አንዳንድ አገራት ደግሞ፡ በተለይ በቅርብ ክፍለ ዘመናት፡ በ"Romantic" ሥነ-ጽሑፍ ዘይቤ ምክንያት፡ ኹለቱንም አገላለጽ ይጠቀማሉ። ለምሳሌ፦ ፈረንሳይ፣ ጣልያን፣ የላቲን አሜሪካ አገራት፣ ወዘተ... ጥቂቶች ደግሞ፡ በዘመን ኺደት፡ በተለያዩ ፖለቲካዊ ምክንያቶች፡ "ከአባት አገር" ወደ "እናት አገር" አገላለጽ ከመጡ በኋላ፡ "ኹለቱም አያስፈልግም" በማለት፡ "አገር ቤት" (Homeland) የሚል አገላለጽ ይጠቀማሉ። ለምሳሌ፦ እንግሊዝ፣ አሜሪካ እና ሩሲያ ('ሶቭየት ኅብረት' ትባል በነበረችበት ጊዜ)። * * * ብዙዎቹ የ"እናት አገር" አገላለጽ ተጠቃሚዎች ታድያ፡ የ"እናት አገር" ተወካይ የኾኑ እንስት ገጸ ባሕሪዎችን ያመጡት፡ ከሴት ጣዖታት ነው። ለምሳሌ፦ Britannia, Mother India... "አባት አገር" የሚለውም አጠራር፡ በብዛት ጣአዖታዊ መሠረት አለው። ነገር ግን...! ከኹሉም አገራትና ሥልጣኔዎች፡ በመጽሓፍ ቅዱሳዊ የነገረ መለኮት ትምህርት የተደገፈ፣ በጣም የጠነከረ እና በዘመናት ውስጥ ያልተለዋወጠ "የእናት አገር" አጠራርን ይዛ የዘለቀችው፡ ኢትዮጵያ ስትኾን፡ የሕንደኬ (Kandake)፡ ማለትም የንጉሥ እናት ("Queen Mother") ምስልን ይዛ በሰው ሕሊና ስለተቀረጸች፡ ሌሎች የአፍሪካ አገራትን፡ በዚያ መልክ፡ የእናትነትና የጽዮንነትን ሥነ ልቦና አሳድራባቸዋለች ("Mother Africa", "African Zion")። ይኽም፡ ቀድሞ የመጀመሪያዋ "ሕንደኬ" በኾነችው በንግሥተ ሳባ፡ በምድር ላይ በይፋ ተገልጦ፡ በመጨረሻዋና በዋናዋ የንጉሥ እናት፡ በቅድስት ድንግል ማርያም መወለድና የአገሪቱ ባለዐሥራት መኾን ምክንያት፡ "እናት አገር" የሚለው አገላለጽ፡ የመጨረሻውን የጸና ዘለዓለማዊና ሰማያዊ ፍጻሜ አግኝቷል። ይኽ የአጠራር ምርጫ፡ የጠለቀ የወንጌል ቃል ድጋፍም አለው። ንጉሡ ኢየሱስ ክርስቶስ፡ በወንጌል ለደቀ መዛሙርቱ፡ እንዲህ ብሎ ተናግሯልና፦ "አባታችሁ አንዱ፡ እርሱም የሰማዩ ነውና፡ በምድር ላይ ማንንም 'አባት' ብላችሁ አትጥሩ።" (ማቴ 23፥ 9) "...እናንተ ኹላችሁ ወንድማማቾች ናችሁ። " (ማቴ 23፥ 8) በኢትዮጵያውያን ሥነ ልቦና፡ የአገር መሪ "አባት" አይባልም። ምክንያቱም፡ አባትየው ሰማያዊ ነው። "በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ..." ብላችሁ ጸልዩ የተባልነው ለዚያ ነው። "አባት" የሚለው ቃል፡ በምድር ጥቅም ላይ ከዋለ፡ በሐዋርያዊ ቅብብሎሽ ሕዝቡን በወንጌል ለሚወልዱ የሃይማኖት አባቶች ብቻ ነው። የእግዚአብሔርን ገጽ ስለምናይባቸው። ከዚያ ውጪ፡ የአገር መሪ ወይም ተዋጊው ክፍል፡ "አባት" ሳይኾን፡ "ባል" ወይም "እጮኛ" ይባላል። "ዐፄ" ማለትም አንዱ ትርጉሙ፡ "እጩ፥ የታጨ" ማለት ነው፤ የክርስቶስ ምሳሌ ነው። አገሪቱ ደግሞ "ለእግዚአብሔር የታጨች ድንግል መሬት" ትባላለች። የባል ሥራው መውደድ ነው። ሚስቱን እስከሞት ሊወድዳት ይገባል። ሌሎች ሲሰድቧት፡ እሱ ሊከላከልላት ይገባል። ሌሎች "ድኃ፣ ገልቱ፣ መልከ ጥፉ" ቢሏት "ተዉአት! የኔ ድኃ ናት! እኔ ወድጄ ባገባኋት፡ እናንተን ምን አገባችሁ?" ብሎ ጠላቶቿንና ምቀኞቿን ሊያሳፍራቸው ይገባል። ምክሩንና ተግሣጹን በጓዳ አድርጎ፥ በአደባባይ ግን፡ ስድቧን፥ ኀፍረቷንና መሸማቀቋን ዘወር አድርጎላት፡ በፍቅር ኃይል ለውጦ፡ ለርሱ ብቻ የሚታየውን ድብቅ ውበቷንና የታፈነ እምቅ ችሎታዋን እንድታወጣ ሊያበረታታት ይገባል። "አንቺ'ኮ አልቻልሽበትም እንጂ፡ እንዲህ እንዲህ ያለ በጎ ነገር አለሽ" ሊላት ይገባል። የባል ሥራ፡ ሌሎች የማያዩትን መልካም ነገር በርሷ ውስጥ ማየት መቻል ነው፤ ከርሷ ጋር የማይኼዱ ሞኝነቶቿንና ስንፍናዎቿን ደግሞ እንድታስወግድ ማንቃት ነው። መጀመሪያውኑ ያያት፥ ያጫትና ወድዶ ፈቅዶ ያገባትም ለዚያ ነው። የአገር መሪም፡ መኾን ያለበት እንደዚያው ነው። "ይኽቺ ድኃ፥ የተረት ተረት አገር፥ የተረገመች አገር፥ የጨለማ አገር፥ የሦስት ሺህ ዓመት ችጋር" የሚሉ ቡድኖች ወደሥልጣን ሲመጡ ያስደነገጠኝ ለዚያ ነው። የተደበቀ ውበቷን ካላዩ፡ እንዴት ያወጡታል? ነፍሷን ያወጡታል እንጂ! ወንድ የሚጠላትን ሴት ማግባት የለበትም። ይገድላታል። አልያም በብስጭት ራሷን አንቃ፥ ወይ መርዝ ጠጥታ ትሞታለች። ወይም ብን ብላ ከአገር ትጠፋለች፤ ወይም ከባሏ ጋር ስትጣላና ስትፈነካከት ትኖራለች። * * * "የእናት አገር" ነገር ጥልቅ ነው። እግዚአብሔር፡ ቅድስት ድንግል ማርያምን ለእናትነት ሲመርጣት፡ ማንም ምድራዊ ሰው ያላየውን የውስጣዊ ውበቷን ጥልቀት፡ እርሱ ስላየ ነው። "ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና።" (መዝ 44፥ 10-11) ሌላው ቀርቶ፡ እርሷ ራሷ እንኳ፡ የራሷን ማንነት ምን ያኽል የከበረ መኾኑን አላወቀችውም። መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል፡ "የእግዚአብሔርን ልጅ ትወልጃለሽ፤ እርሱም ለዘለዓለም ይነግሣል" ሲላት፡ "ይኽ እንዴት ይኾናል?" አለች እንጂ። ኢትዮጵያንም ያልተረዱ፥ እንደ እጮኛ በተለየ የፍቅር ዓይን የማያዩአት፥ ማንም ያላየውን መንፈሳዊ ውበቷን ያላወቁ፥ በመንፈስ ቅዱስም ሥውር መንፈሳዊ ሀብቷ ያልተገለጸላቸው፡ ሊመሯት አይችሉም። "ልምራ" ቢሉም፡ በምድር ላይ "አባትሽ ካልኾንኩ" ይሏትና ትቸገራለች። ከሰማያዊው አባት ጋር ያላት ግንኙነት ላይ ደንቃራ ይኾኑባታል። "ቄሣር ቄሣር ካልተጫወትን" ብለው ያስቸግሯታል። እንደ እጮኛዋ ዮሴፍ የድንግልናዋ ጠባቂ፥ የመከራዋ ተካፋይ፥ የልጇ ሞግዚት መኾን ያቆሙና፡ እንደሄሮድስ ወይም እንደፈሪሳውያን "ያ ጎረምሳ ልጅሽ የታለ? ለሥልጣናችን ሥጋት ኾኖ አስቸግሮናል፥ አውጪው!" እያሉ ሊገድሉት ያስጨንቋታል። እናም፡ በዘመናዊው ዓለም፡ ለጣዖታዊ "አባቶች" ልጇን አሳልፈው ይሰጡባታል። የሴት ልጆቿንም ድንግልና ይሸጡባታል። እነሱም የምሥጢር ማኅበራትና የglobalization መዋቅራቸው ነው።  የነርሱ አባት ደግሞ "ዲያቢሎስ" ይባላል። ደግነቱ ዲያቢሎስ ልጇን ገድሎትም አላሸነፈውም! በመስቀሉ ድል ኾነ! ገድሎ መሸነፍ የዲያቢሎስ ዕጣ ፈንታው ነው! * * * ከዲያቢሎስ አባትነት ይሠውረን፤ የእግዚአብሔርን አባትነት ይመልስልን! እግዚእ - ጌታ አብ - አባት ኄር - ቸር ቸር አባት ጌታ እርሱ ይምራን!
66
3
ሐምሌ ፪ /2/ በዚች ቀን ከዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት የአንዱ ሐዋርያ የቅዱስ ታዴዎስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው። ይህንንም ሐዋርያ ከዐሥራ ሁለቱ ጋራ ጌታችን አስቀድሞ መረጠው አጽናኝ መንፈስ ቅዱስ በላያቸ
ሐምሌ ፪ /2/ በዚች ቀን ከዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት የአንዱ ሐዋርያ የቅዱስ ታዴዎስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው። ይህንንም ሐዋርያ ከዐሥራ ሁለቱ ጋራ ጌታችን አስቀድሞ መረጠው አጽናኝ መንፈስ ቅዱስ በላያቸው በወረደ ጊዜ ወደ አገሮች ወጥቶ የወንጌልን ትምህርት አስተማረ ከአይሁድና ከአረማውያን ብዙዎቹን ወደ ፈጣሪያቸው እግዚአብሔር መልሶ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው። አንድ ቀንም ወደ ሶርያ ከተማ ሲጓዝ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መልኩ በሚአምር ጐልማሳ አምሳል ለእርሱ ተገልጦ ወዳጄ ታዴዎስ ቸር አለህን አትፍራ እኔ ከአንተ ጋራ እኖራለሁና አለው ሰላምታም ሰጥቶት ከእርሱ ዘንድ ዐረገ። ይህም ሐውርያ ብዙ ድንቅ ተአምራትን አድርጓል። እህል በአንድ ቀን ዘርቶ በአንድ ቀን አድርሷል። አንድ ባለጸጋም ሊፈትነው ፈልጎ ግመልን በመርፌ ቀዳዳ አሳልፈህ አሳየን ሲለው በእግዚአብሔር ተራዳይነት ግመሉን በመርፌ ቀዳዳ አሳልፏል። በብዙ አገሮችም ውስጥ ገብቶ ሰበከ ከአይሁድና ከአረማውያንም መከራ ደረሰበት። ከዚህም በኋላ በሰላም አረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ሐዋርያ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
78
4
Немає тексту...
180
5
ከተዋሕዶ እምነት ውጪ ያሉ ኹሉም እምነቶች፡ ተዋሕዶን የሚከስሱበት ነጥብ፡ "የ3000 ዓመት ድህነት" ሲኾን፡  ራሳቸውን የሚቆልሉበት ነጥብ ደግሞ "ሀብት" ነው። እነርሱ ሀብታም ባይኾኑ እንኳን፡ የነርሱ እምነት የተፈለሰፉባቸውን ቦታዎች እየጠሩ በሀብታቸው ይመጻደቃሉ። ካቶሊኩ በካቶሊክ አገራት ሀብትና ሥልጣኔ ይመጻደቃል። ሙስሊሙ በዐረብ አገራት ሀብት ይመጻደቃል። ፕሮቴስታንቱ በፕሮቴስታንት አገራት ሀብት ይመጻደቃል። አይሁዱ፡ እስራኤል በአጭር ጊዜ አንሠራርታ አገር በመኾኗና በጦር ሥርዓቷ ወዘተ ይመጻደቃል። በጥንቆላና በመተት ያለው ደግሞ፡ መጀመሪያም ገንዘብ አምላኩ መኾኑን ያመነና በድርጊቱም ያጸደቀ፡ የነዚህ ኹሉ ተመጻዳቂዎች ዋና role model ነው። የሚገርመው ነገር ግን፡ ኢየሱስ ክርስቶስ፡ ደግሞ ደጋግሞ በሐዲስ ኪዳን የተናገረው፡ የድኆች አምላክ መኾኑን፥ ገንዘብ የእግዚአብሔርን ቦታ የሚገዳደር ዋና ጣዖት መኾኑን፥ ሀብታም ወደ መንግሥተ ሰማያት ከሚገባ፡ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢሾልክ የሚቀል መኾኑን፥ ዲያቢሎስ የዓለሙ ገዢና የሀብቷና የገንዘቧ ዘዋሪ መኾኑን ወዘተ ነው። እርሱ የሚሰጠው ስጦታ የበለጠውን የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ እንደኾነና፡ ገንዘብ ከስጦታዎቹ ኹሉ መጨረሻ ላይ የሚመጣ በጣም ቀላሉና የማያሳስበው "ዳረጎት" እንደኾነ በተለያዩ መንገዶች በግልጽ ተናግሯል። ዲያቢሎስ፡ የእግዚአብሔር የኾኑትን፡ በማጣትና በድህነት ይፈትናል። እግዚአብሔር ደግሞ፡ በማጣትና በድህነት ውስጥ ቀርቶ፡ በሞትም ውስጥ ሙላት እንዳለ እያሳየ፡ የዲያቢሎስን ውሸት እያፈረሰ ያስተምራቸዋል። በተዋሕዶ እምነትና በሌሎች እምነቶች መካከል ያለውን  ልዩነት ባሰብኩት ቁጥር፡ በጣም በጣም የሰማይና የምድር ያኽል የተራራቀ ይኾንብኛል። በሌሎች እምነቶች መካከል ያለውን ልዩነት ስመረምረው ደግሞ፡ ልዩነታቸው ከሸረሪት ድርም የቀጠነ ይኾንብኛል። መሠረታቸው፣ ሥሪታቸውና አስተሳሰባቸው አንድ ነው። ኹሉም ፍጹም ዓለማዊ ናቸው። ተዋሕዶ ብቻ ሰማያዊት እምነት ናት። ሌላው ሙሉ ለሙሉ ከስሯል! "ሰው ዓለሙን ኹሉ ቢገዛ፡ ነፍሱን ግን ቢያጣ፡ ምን ይረባዋል? ሰውስ ለነፍሱ ቤዛ ምንን በሰጠ ነበር?" (ማቴ 16፥ 18)
181
6
#የሕሊና_ጸሎት ጌታዬና መድኃኒቴ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፤ ከሁሉ አስቀድሜ ስለ እስትንፋሴ አመሰግንሃለሁ። ይህች አየር ወደ ሳንባዬ ስትገባና ስትወጣ ያንተን ስም በምስጢር እንድትጠራ እርዳኝ። በእያንዳንዱ ትንፋሼ ውስጥ አንተን ማሰብን ስጠኝ። አእምሮዬ እንደ ባዘነ ወፍ ከቦታ ቦታ ሲባክን፣ አንተ በቸርነትህ ወደ ሰላምህ ጎጆ መልሰው። አምላኬ ሆይ፤ ካንተ ውጭ የምታስበው ነፍስ ሰላም የላትምና፣ በሕሊናዬ ዙፋን ላይ አንተ ንገሥ። በሥራዬ መካከል ሳለሁ አብረኸኝ ሥራ። እጆቼ ቁሳቁሱን ሲነኩ፣ ልቤ ግን ያንተን ቅድስና ይንካ። በድካሜ መካከል ብርታት፣ በውጤቴ መካከል ደግሞ በረከት ሁነኝ። ስሠራ አብረኸኝ ሥራ፤ ያለ አንተ ረዳትነት ድካሜ ሁሉ ከንቱ ነውና። በላቤ ውስጥ ያንተን ምሕረት፣ በጥረቴ ውስጥ ደግሞ ያንተን ፈቃድ እንዳይ እርዳኝ። አቤቱ፥ በሕይወት መንገድ ስጓዝ አንተ መሪ ሁነኝ። የትኛው መንገድ ወደ አንተ እንደሚወስደኝ አላውቅምና፣ እንደ ብርሃን መብራት ከፊቴ ቅደም። ስሄድ መንገዱን ምራኝ፤ ስደክም ምርኩዝ ሁነኝ። ሕይወት በከበደችኝና ጉልበቶቼ በዝሉ ጊዜ፣ የማልወድቅበት ጽኑ ዓለት ሁነኝ። በፈተና አረንቋ ውስጥ እንዳልሰጥም እጅህን ዘርግተህ ያዘኝ። ጌታ ሆይ፤ በምድራዊ ሕይወቴ ግዴታዎች ቢበዙብኝም፣ እነዚያ ግዴታዎች ከአንተ ጋር እንዳያጋጩኝ ጠብቀኝ። ምድራዊ ስኬቴና ባለጠግነቴ አንተን እንዳያስረሳኝ አጥር ሁነኝ። በሰው ፊት ከፍ ስል በልቤ ውስጥ አንተን ዝቅ እንዳልል ሰውረኝ። ስም ስገኝ ስምህን፣ ሀብት ስገኝ ባለቤቱን እንዳልረሳ የትሕትናን ልብስ አልብሰኝ። ዓለም በውሸት ውበቷ ስታታልለኝ፣ አንተ እውነተኛው ውበቴ መሆንህን አስታውሰኝ። በሰዎች መካከል ስሆን ፍቅርህን እንድገልጥ ርዳኝ። አንደበቴን ከሐሜት፣ ዓይኖቼን ከክፋት፣ ልቤን ከምቀኝነት ጠብቅ። ብቻዬን በሆንኩበት ሰዓት ደግሞ፣ የሰዎችን ጫጫታ ትቼ ያንተን ቅድስና እንድናፍቅ አድርገኝ። በብቸኝነቴ ውስጥ ሙላቴ፣ በዝምታዬ ውስጥ ቃል ሁነኝ። በምንም ሰዓት፣ በምንም ሁኔታ አንተን ከመዘንጋት ሰውረኝ። ሕይወቴ ሁሉ ያንተ መታሰቢያ ይሁን። አቤቱ፤ ጸሎቴን እንደ መዓዛ እጣን ተቀበልልኝ። በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት፣ በቅዱሳን መላእክትና በጻድቃን ሁሉ ጸሎት ልመናዬን ስማኝ። አእምሮዬን ቀድሰህ፣ ልቤን አሳርፈህ፣ ሕይወቴን ባርከህ እስከ መጨረሻው አጽናኝ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር። አሜን።
222
7
"ብርቱው አምላኬ መድኃኔዓለም ሆይ፤ ጠላት ዲያብሎስ በሕሊናዬ ውስጥ የጥርጣሬን፣ የጭንቀትንና የትዕቢትን ዘር ሊዘራ ሲመጣ አንተ ጋሻ ሁነኝ። ሐሳቤ በፈተና ማዕበል እንዳይናወጥ በሃይማኖት ዓለት ላይ አጽናኝ። ጌታ ሆይ፤ አእምሮዬን በሚያውኩኝ ክፉ ምስሎችና ትዝታዎች ፋንታ፣ ያንተን ትሕትናና ፍቅር ሙላበት። በውስጤ ያለው የጨለማ ሠራዊት በቃልህ ብርሃንነት ይበተን። ነፍሴን ካንተ የሚለይ ሐሳብ በፊቴ ሲቆም፣ በመስቀልህ ኃይል በትነው።"
195
8
Немає тексту...
189
9
"የዘላለም ብርሃን የሆንክ አምላኬ ሆይ፤ አእምሮዬን በአንተ ቅድስና ማኅተም አትመው። ዛሬ በልቤ መቅደስ ውስጥ አንተን ደስ የማይያሰኝ ሐሳብ እንዳይሰፍር ጠባቂ ሁነኝ። ሕሊናዬን እንደ ዕጣን መሠዊያ አድርገውና ምስጋናዬ ወደ አንተ ይውጣ። ጌታ ሆይ፤ በዓይኖቼ ስመለከት ያንተን ድንቅ ሥራ እንድታይ፣ በጆሮዎቼ ስሰማ ያንተን ድምፅ እንድለይ፣ በአንደበቴም ስናገር ያንተን እውነት እንድመሰክር ጸጋህን አልብሰኝ። በውጭ ሳይሆን በውስጤ አድረህ አስተምረኝ።"
179
10
"ያህዌ ይርኤ (አቅራቢው እግዚአብሔር) ሆይ፣ ባለሁበት የኑሮ መጣበብና እጥረት ውስጥ የሚያስፈልገኝን መውጫና በረከት አንተ አዘጋጅልኝ። አማኑኤል (እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው) ሆይ፣ በዚህ አስቸጋሪ ዘመን ብቻዬን እንዳልሆንኩ አሳየኝ፤ በነገሬ ሁሉ አብረኸኝ ሁን። ይህንን ሁሉ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እለምናለሁ፣ አሜን።"
205
11
"ሥላሴ ፆታ አላቸው" የሚል ሱሁት ስብከት ያስተማሩት ሊቀ ሊቃውንት አባ ገብረ ማርያም ስህተት እንደሆነ አምነው ይፋዊ ይቅርታ ጠየቁ *** ሊቀ ሊቃውንት አባ ገብረ ማርያም ቅድስት ሥላሴ ፆታ አላቸው
"ሥላሴ ፆታ አላቸው" የሚል ሱሁት ስብከት ያስተማሩት ሊቀ ሊቃውንት አባ ገብረ ማርያም ስህተት እንደሆነ አምነው ይፋዊ ይቅርታ ጠየቁ *** ሊቀ ሊቃውንት አባ ገብረ ማርያም ቅድስት ሥላሴ ፆታ አላቸው ብለው በሰበኩት ሱሁት አስተምሮህ ላይ በዛሬው ዕለት በሚዲያ በሰጡት ማብራሪያ እና የይቅርታ መግለጫ መሳሳታቸውን አምነው ይቅርታ ጠይቀዋብ። ''የተፈጠረው የእኔ ዳሕጸ ልሳን እንደሆነ ይታወቅልን፣ 40 ዓመት የተማርኩትን አበላሽቸዋለሁ ማለት ነው፡፡ ለሥላሴ በሦስትነት ጾታ አንናገርም፣ ለወልድ ከሆነ ግን እኛን መስሏልና ለእርሱ ይነገራል፡፡'' ''ለሥላሴ፣ ለመላእክት፣ ለነፍስ ጾታ አንናገርም፣ የእኔ ለሥላሴ ጾታ መናገሬ 100 በ100 ስሕተት ነው፡፡ ይኸ ለምእመናንም፣ ለሊቃውንትም የእኔ ዳሕጸ ልሳን መሆኑ ይታወቅልኝ፡፡ ሁሉንም በማሳሳቴም ይቅርታ እጠይቃለሁ፣ የእኔ ስሕተት እንጂ የቤተ ክርስቲያኗ ትምህርት አይደለም፣ አሕዛብና መና*ፍ* q ግን አይመለከተውም' ብለዋል፡፡ እንዲህ በእርጋታ እና በጥሞና ከራስ ጋር ተማክሮ እና አስተውሎ ይቅርታ ማለታቸው እና ስህተታቸውን ማረማቸውን የሊቃውንት ብስለታቻውን አሳይተዋል።
214
12
"የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ..." (ማቴዎስ 3፥3) ቅዱስ ዮሐንስ የተወለደው ለጌታ መንገድ ለመጥረግ ነው። የእርሱ ልደት ሲከበር እኛም ልባችንን
"የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ..." (ማቴዎስ 3፥3) ቅዱስ ዮሐንስ የተወለደው ለጌታ መንገድ ለመጥረግ ነው። የእርሱ ልደት ሲከበር እኛም ልባችንን ለክርስቶስ ማደሪያነት እንድንጠርግ ያስታውሰናል። ዮሐንስ በትሕትናው "እኔ የጫማውን ጠፍር ልፈታ አይገባኝም" በማለት ክርስቶስን ከፍ አድርጓል። እኛም በሕይወታችን ክርስቶስን የምናከብርበት፣ በጽድቅና በእውነት የምንመላለስበት ዘመን ይሁንልን። ታላቁ መጥምቅ በምልጃው ይጠብቀን! እንኳን አደረሳችሁ! ⛪️🙌
224
13
🌹 + + + 29 🕯️ + + +🌹 #እግዚአብሔር_እረኛዬ_ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም። #በለመለመ_መስክ_ያሳድረኛል፤ በዕረፍት ውኃ ዘንድ ይመራኛል። 🙏 ነፍሴን መለሳት፥ ስለ ስሙም በጽድቅ መንገድ
🌹 + + +    29 🕯️ + + +🌹 #እግዚአብሔር_እረኛዬ_ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም። #በለመለመ_መስክ_ያሳድረኛል፤ በዕረፍት ውኃ ዘንድ ይመራኛል። 🙏 ነፍሴን መለሳት፥ ስለ ስሙም በጽድቅ መንገድ መራኝ። በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፤ #በትርህና_ምርኵዝህ_እነርሱ_ያጸናኑኛል። 🙏 በፊቴ ገበታን አዘጋጀህልኝ፤ በጠላቶቼ ፊት ለፊት ራሴን በዘይት ቀባህ፥ ጽዋዬም የተረፈ ነው። 🙏 ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል፥ በእግዚአብሔርም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ። + +  +( መዝ  23 ፥ 1 - 6  ) + + 🙏 በአንተ መልካም እረኛነት አምነው ሁሉም አንድ መንጋ ይሆኑ ዘንድ መልካም ፍቃድህ ይሁንልን።
209
14
በርቱ ሁላችንም እንሳተፍ!! 🙏🙏🙏
በርቱ ሁላችንም እንሳተፍ!! 🙏🙏🙏
209
15
እናመሰግናለን! ለሎቻችሁም ቤተሰቦቼ ተሳተፋ በተቻላችሁ በጠን ትንሽ የምባል ነገር የለም ተሳተፉ የበረከት ሥራ ነውና። 🙏
እናመሰግናለን! ለሎቻችሁም ቤተሰቦቼ ተሳተፋ በተቻላችሁ በጠን ትንሽ የምባል ነገር የለም ተሳተፉ የበረከት ሥራ ነውና። 🙏
195
16
🙏 ይህን ያደረገ እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን! አባታችን ቀሲስ ሄኖክ ተፈራ በዛሬው ዕለት በቲዎሎጂ በመጀመሪያ ድግሪ ተመርቀዋል። እንኳን ደስ አላችሁ! 🙏🙏🙏+2
🙏 ይህን ያደረገ እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን! አባታችን ቀሲስ ሄኖክ ተፈራ በዛሬው ዕለት በቲዎሎጂ በመጀመሪያ ድግሪ ተመርቀዋል። እንኳን ደስ አላችሁ! 🙏🙏🙏
183
17
#የበረከት_ሥራ 🙏 ውድ ቤተሰቦቼ እንዴት ናችሁ። እንኳን ለቅዱስ አማኑኤል ወርሃዊ መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ። በዚህ የበረከት ሥራ ተሳተፉ በምትችሉት አቅም ይሄንን ቤተክርስቲያን እናግዝ። በዚህ+5
#የበረከት_ሥራ 🙏 ውድ ቤተሰቦቼ እንዴት ናችሁ። እንኳን ለቅዱስ አማኑኤል ወርሃዊ መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ። በዚህ የበረከት ሥራ ተሳተፉ በምትችሉት አቅም ይሄንን ቤተክርስቲያን እናግዝ። በዚህ ቦታ ከካሳንችዝ በተለይም ከመሀል አዲስ አበባ በኮርደር ምክንያት የተነሱ ምዕመናን የሚኖሩበት የሚገርም ትብብር ያለበት ሠፈር ነው። የቦለ አራብሳ ሠፈራ ማሪያም ቤተክርስቲያንን እናግዝ፣ እንተባበር የመረትና የቦታ ቸግሮች አሉና ሁላችሁም የበረከቱ ተካፋይ ሁኑ። 🙏 ገንዘቡን ከላካችሁ በኋላ ሁላችሁም screenshot አድርጋችሁ ደረሰኙን ላኩልኝ። የአቅማችንን እናድርግ። መልካም ዕለተ ሰንበት 🙏
249
18
መድኃኔዓለም "በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው። እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም
መድኃኔዓለም "በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው። እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን። እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ። ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤  እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም። በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ ስለ ሕዝቤ ኃጢአት ተመትቶ ከሕያዋን ምድር እንደ ተወገደ ከትውልዱ ማን አስተዋለ?         (ኢሳ 53 ፥ 4 - 8) በከመ ምህረትከ አምላክነ ወአኮ በከመ አበሳነ። አምላካችን ሆይ እንደቸርነትህ ነው እንጂ እንደበደላችን አይሁን።
389
19
3 ዲያቆናትን ድንግልናቸውን ያስፈረሰች እጅግ አደገኛዋ ሴትና የጥንቃቄ መልዕክት!! በጸበልና ገዳማት ቦታዎች ይሄ ይሆናል ብሎ ማን ያምናል!! በጸበል ቦታዎች እየታዩ ያሉ አደገኛ ችግሮችና ልምምዶች!! https://youtu.be/Z7CoFmr-Xk8
422
20
መስገድ መጸለይ ከጀመሩ በኋላ ተከራዮቹ ያዩት እጅግ ከባድና አስደንጋጭ ነገር!! መረትና ንብረታችሁ አልሸጥ ካላችሁ ይኼንን በደንብ አዳምጡ!! #የዋህ #ጸሎት https://youtu.be/1gZD_BTdjbA
449