HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Відкрити в Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Показати більше2 311
Підписники
+324 години
+157 днів
+4030 день
Триває завантаження даних...
Схожі канали
Хмара тегів
Немає даних
Виникли проблеми? Будь ласка, оновіть сторінку або зверніться до нашого support-менеджера.
Вхідні та вихідні згадування
---
---
---
---
---
---
Залучення підписників
серпень '26
серпень '26
+4
в 0 каналах
липень '26
+126
в 0 каналах
Get PRO
червень '26
+79
в 0 каналах
Get PRO
травень '26
+65
в 0 каналах
Get PRO
квітень '26
+71
в 0 каналах
Get PRO
березень '26
+79
в 0 каналах
Get PRO
лютий '26
+51
в 0 каналах
Get PRO
січень '26
+55
в 0 каналах
Get PRO
грудень '25
+46
в 0 каналах
Get PRO
листопад '25
+74
в 1 каналах
Get PRO
жовтень '25
+45
в 0 каналах
Get PRO
вересень '25
+36
в 0 каналах
Get PRO
серпень '25
+49
в 0 каналах
Get PRO
липень '25
+62
в 0 каналах
Get PRO
червень '25
+55
в 0 каналах
Get PRO
травень '25
+94
в 0 каналах
Get PRO
квітень '25
+76
в 0 каналах
Get PRO
березень '25
+70
в 0 каналах
Get PRO
лютий '25
+63
в 0 каналах
Get PRO
січень '25
+69
в 0 каналах
Get PRO
грудень '24
+114
в 1 каналах
Get PRO
листопад '24
+77
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '24
+62
в 0 каналах
Get PRO
вересень '24
+58
в 0 каналах
Get PRO
серпень '24
+48
в 1 каналах
Get PRO
липень '24
+62
в 0 каналах
Get PRO
червень '24
+40
в 1 каналах
Get PRO
травень '24
+34
в 0 каналах
Get PRO
квітень '24
+82
в 2 каналах
Get PRO
березень '24
+59
в 0 каналах
Get PRO
лютий '24
+73
в 1 каналах
Get PRO
січень '24
+47
в 0 каналах
Get PRO
грудень '23
+39
в 0 каналах
Get PRO
листопад '23
+54
в 1 каналах
Get PRO
жовтень '23
+61
в 1 каналах
Get PRO
вересень '23
+47
в 0 каналах
Get PRO
серпень '23
+50
в 0 каналах
Get PRO
липень '23
+67
в 0 каналах
Get PRO
червень '23
+71
в 0 каналах
Get PRO
травень '23
+60
в 0 каналах
Get PRO
квітень '23
+133
в 0 каналах
Get PRO
березень '23
+243
в 0 каналах
Get PRO
лютий '23
+127
в 0 каналах
Get PRO
січень '23
+197
в 0 каналах
Get PRO
грудень '22
+212
в 0 каналах
Get PRO
листопад '22
+110
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '22
+98
в 0 каналах
Get PRO
вересень '22
+70
в 0 каналах
Get PRO
серпень '22
+76
в 0 каналах
Get PRO
липень '22
+92
в 0 каналах
Get PRO
червень '22
+121
в 0 каналах
Get PRO
травень '22
+108
в 0 каналах
Get PRO
квітень '22
+138
в 0 каналах
Get PRO
березень '22
+198
в 0 каналах
Get PRO
лютий '22
+102
в 0 каналах
Get PRO
січень '22
+131
в 0 каналах
Get PRO
грудень '21
+113
в 0 каналах
Get PRO
листопад '21
+91
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '21
+55
в 0 каналах
Get PRO
вересень '21
+57
в 0 каналах
Get PRO
серпень '21
+72
в 0 каналах
Get PRO
липень '21
+75
в 0 каналах
Get PRO
червень '21
+100
в 0 каналах
Get PRO
травень '21
+166
в 0 каналах
| Дата | Залучення підписників | Згадування | Канали | |
| 02 серпня | 0 | |||
| 01 серпня | +4 |
Дописи каналу
ደስ ብሎኛል ደስ ይበላችሁ! 🕊️✨
"እነሆ፥ ልጆች የእግዚአብሔር ስጦታ ናቸው፤ የማኅፀንም ፍሬ የእርሱ ዋጋ ነው።" (መዝሙር 127፥3)
የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር በምሕረቱ ጎብኝቶኛልና ስሙ ለዘላለም የተመሰገነ ይሁን! ዛሬ በቸርነቱ ሁለተኛ ልጄን በወንድ ልጅ ስጦታ አበርክቶልኛል። እናቱ በሰላም ተገላግላለች፣ ሕፃኑም በጤና መጥቷል። የፈጣሪ ስራ ድንቅ ነውና አብራችሁኝ እግዚአብሔርን አመስግኑልኝ።
አሁን ደግሞ አንድ አደራ አለብኝ፤ ለዚህ በረከቴ የሚሆን መንፈሳዊና ትርጉም ያለው ስም እንድትጠቁሙኝ እፈልጋለሁ። እስቲ ለልጄ የምትመኙትን ስም ከነ ትርጉሙ በኮሜንት አሳውቁኝ።
እግዚአብሔር ቤታችሁን በበረከት ይሙላው! 🙌❤
| 2 | Dystopia = ገንዘብ አምላኪ መንግሥት
* * *
ገንዘብ የሚያመልክ ሰው፡ ድሃ ነው። ምክንያቱም፡ ገንዘቡ ካለቀበት፡ ሌላ ነገር የለውም።
ገንዘብ የሚያመልክ መንግሥትም፡ ድሃ ነው። ምክንያቱም፡ ገንዘቡ ካለቀበት፡ ሌላ የሚቆምበት እሴት፣ መርኅ፣ ዓላማ ወይም ታሪክ የለውም። መርኁ ገንዘብ ብቻ ስለኾነ፡ ከሕዝብም ኾነ ከሌላ፡ እንዴት ገንዘብ እንደሚሰበስብ ብቻ ያስባል።
ገንዘቡን (አምላኩን) ደግሞ በአደባባይ ማምለክ ይወዳል። አምላኩን የሚያመልከበት የዐደባባይ ሥርዓቱም፡ ይፋዊ ቅንጦት ነው።
እንዲያም ኾኖ ግን፡ ውስጡ ገንዘብ በማጣት ስጋት የተመታ ነው። ምክንያቱም፡ ገንዘቡ ካለቀ ምንም የለውም። ከገንዘቡ ውጪ፡ እሱ ማንነት የለውም። ገንዘቡ እሱ፥ እሱም ገንዘቡ ናቸው።
ይኽ "መካከለኛው ዘመን" ብለው በሚጠሩት በጨለማው ዘመን (Dark Age)፡ የአውሮፓ ነገሥታት የነበሩበት የወደቀ ስነ ልቦና ነው።
ነገሥታቱ፡ ከሕዝባቸውና ከወረሯቸው አገራት፡ ገንዘብ መሰብሰብ፣ መዝረፍ፣ መማረክ፣ መቀጮ መጣል፣ መውረስ ላይ ተጠምደው ነበር። ሕዝቡም፡ ከነሱ ተምሮ፡ ገንዘብ ወዳጅ ኾኖ፡ ከመሥረቅ በቀር፡ ሌላ ሥራ አልነበረውም። ለዳቦ ብሎ ይገድላል፤ ለዳቦ ብሎ ይገደላል።
በወቅቱ፡ በአውሮፓ ትልቅ ተጽዕኖ እያሳደሩ የነበሩት እምነቶች ደግሞ፡ እስልምና፣ ካቶሊክ፣ እና gnosticism/hermeticism (ኮከብ ቆጠራ) ናቸው።
በኋላ ግን፡ ሕዝቡ፡ "በቃኝ!" አለና፡ ከቄሱ ዮሓንስ አገር ኢትዮጵያ፡ ከነላሊበላና ይምርኃነ ክርስቶስ፡ ብዙ ክርስቲያናዊ የአስተዳደርና የአኗኗር ትምህርቶችን እየተማረ፡ ወደ Utopianism ገሠገሠ።
ተዋሕዶ/ዩቶፕያ፡ አገርን ከጨለማ ዘመን ሥርዓት ነፃ ታወጣለች።
በተዋሕዶ/ዩቶፕያ፡ የሚመለከው፡ ገንዘብ ሳይኾን፡ ሰው ነው።
በተዋሕዶ/ዩቶፕያ፡ ሰው ክቡር ነው። ምክንያቱም፡ የሚመለከው፡ ሰው የኾነው አምላክ ነውና፡ የሰው ባሕሪው ከብሯል።
በተዋሕዶ/ዩቶፕያ፡ ትግሉ ኹሉ፡ ሰውን፡ ወደ ሰብአዊ ብቻ ሳይኾን፡ ወደ አምላካዊ ክብሩ መመለስ ነው። ሰው፡ በክርስቶስ ምክንያት፡ የፀጋ አምላክ ኾኗልና።
በተዋሕዶ/ዩቶፕያ፡ ገንዘብ፡ የሰው መጠቀሚያ ብቻ ነው። የሰውን ባሕሪ የማማሰን (የማበላሸት) ዓቅም ስላለውም፡ ከትልልቅ ሰዎች በቀር፡ ልጆች ምን እንደኾነ እንዲያውቁት አይደረግም ነበር። "ልጅ ፍራንክ አይዝም!"
አሁን ግን፡ ዕድሜ ለሌሎች እምነቶችና ለኮከብ ቆጣሪው ዓለም፡ ገንዘብ በቄሱ ዮሓንስ አገር አምላክ ኾኖ፡ ሰው ስለገንዘብ ጭዳ ግብር ይደረጋል።
ተዋሕዷዊ/ዩቶፕያዊ ዐብዮት ያስፈልገናል።
* * *
ይኽ በእንዲህ እንዳለ፡ የኢሉሚናቲ ዐብዮት አስጀማሪዋ ካቶሊኳ ፈረንሳይ ግን፡ በላሊበላ ምን እየሠራች ነው?
ዶ/ር መስከረም ለቺሳ | 213 |
| 3 | የራሳችሁ "መምህራን" አስበሏችሁ!
"ደብተራነት አይነካብን" ባዮች፥ የደቂቀ እስጢፋ ደጋፊዎች፥ ግዕዝ አዋቂ ተጠያቂ ሊቃውንት መሳዮች፥ የነፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ አድናቂዎች፣ የነ ሥርግው ሀብለሥላሴና የሌሎች ካቶሊኮች አለቅላቂዎች...
ስለ ሰንደቅ ዓላማው ሲነሳ፡ እንዴት ማላገጥ እንደሚቀናቸው ልብ ብላችሁ ተመልከቱ።
መንፈሳዊ ትርጉሙን፡ እንዲሁ በዘፈቀደ በማገናኘት የተተረጎመ አድርገው በማናናቅና በማጣጣል ይናገራሉ፤ ይጽፋሉ። "የኛ ቤተክርስቲያን ሊቃውንት፡ እንዲሁ ቀለምና ቁጥር እያገናኙ መተርጎም ይወዳሉ" ይላሉ። መንፈሳዊ ምሥጢሮችን፥ ኢትዮጵያዊ እሴቶችን፥ ረቂቅ እውነቶችን አቅልላችሁ እንድትመለከቷቸውና፡ "አንዳንድ ሰዎች የፈጠሯቸው ትምክህታዊ አስተሳሰቦች ናቸው" ብላችሁ እንድታልፏቸው፡ በቃልና በጽሑፍ ይጀነጅኗችኋል። ለራሳቸው በማናለብኝነት ሙሉ ሥልጣን ሰጥተው፡ "እንዲህ ያለ አስተምህሮ በቤተክርስቲያን የለም" ይሏችኋል። በዚያም አመዛዛኝ፣ ጽንፈኛ ያልኾነ የቤተክርስቲያን ምሑር መስለው ሊታዩዋችሁ ይሞክራሉ።
እናንተም ስትጀነጀኑ ትሰነብቱና፡ ስልብ ከኾናችሁ በኋላ፡ የማንም 666 እየተነሳ፡ አንዴ በሰንደቅ ዓላማ ላይ፥ አንዴ በቀን አቆጣጠር ላይ፥ አንዴ በእለታት ስያሜ ላይ አፉን ሲከፍት፡ በጠበቀ ወኔ መከራከር አቅቷችሁ ዝም ትላላችሁ። ምክንያቱም፡ "መምህሮቻችሁ"፡ አስቀድመው የኹለት ባሕሪ ምንፍቅናን በውስጣችሁ ተክለውባችኋልና። አንድ ጎናችሁ ሊመክት ይፈልጋል፤ አንድ ጎናችሁ ደግሞ፡ ከአሕዛብ አስተሳሰብ ጋር ይስማማና ሽባ ይኾናል።
ዱሮም፡ በዓለም ታሪክ፡ ኦርቶዶክስ የነበሩ አገራትን፡ ለአክራሪ እስልምና አሳልፋ የሰጠቸው፡ ካቶሊክ ናት። ለርሷ፡ ከተዋሕዶ ይልቅ እስልምና ይቀርባታል። ኹለቱም "ወልድ ፍጡር" ባዮች ናቸው። እስልምና ኢየሱስ ክርስቶስን "አምላክ አይደለም" ያለው፡ እናቱ ካቶሊክ፡ መለኮትና ትስብእትን ነጣጥላ ከምታስተምረው የኹለት ባሕሪ ትምህርት ተነሥቶ ነው። ነብዩ መሓመድ ስለክርስትና ያለውን ግንዛቤ የተማረው፡ ከካቶሊክ መነኩሴ መኾኑን ስንቶቻችሁ ታውቁ ይኾን? ካቶሊክ ማለት፡ መስቀል የያዘ እስላም ማለት ሲኾን፤ እስላም ማለት ደግሞ፡ መስቀል የማይዝ ካቶሊክ ማለት ነው። የነፍስ ማንነታቸው ከዚህ አይወጣም። ኹለቱም ከተዋሕዶ እምነትና ከኢትዮጵያዊነት እሴት በጣም ሩቅ ናቸው። እየተደጋገፉ፥ አንዳንዴም እየተነቃቀፉና እየተገፋፉ፡ የጋራ ጠላታቸውን ኦርቶዶክስ ተዋሕዶን፡ በአውሮፓ፥ በእስያ፣ በመካከለኛው ምሥራቅና በአፍሪካ ያዳከሙ፡ ኹለቱ እምነቶች ናቸው።
እነዚህ ስለኢትዮጵያዊነት በተነሳ ቁጥር የማናናቂያ ጽሑፍ የሚጽፉ "መምህራን"፡ለእናንተ፡ እውነተኛ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መምህራን፣ ሰባኪዎች ወይም ሊቃውንት ይመስሏችኋል። እነሱ ግን፡ ከተዋሕዶ በቀር፡ የማንም ደጋፊ ናቸው። ሥራቸውም፡ ሌሎች እምነቶች፡ በተዋሕዶ እምነት እና ኢትዮጵያዊ እሴቶች ላይ እንዲነሳሱ፡ ከውስጥ ኾነው የባንዳነት ሥራ መሥራት ነው። ረዘም አድርጋችሁ ብታወሯቸው ግራኝን ሲደግፉ ኹሉ ትሰሟቸዋላችሁ።
እነዚህ አሕዛብ "መምህራን፡" ከቅጠላ ቅጠል መንደር የማይጠፉ ድግምታሞች ናቸው። ጾም፣ ጸሎት፣ ስግደት ሰውነታቸውን የሚጎዳ ስለሚመስላቸው የሚፈሩት፥ ጸሎትና ምልጃ የማያውቁ፣ በሕይወታቸው ሳሉ የሞቱ ቅምጥሎች፥ ሰው መሳይ በሸንጎዎች፥ ውስጣቸው፡ ትልቅ የግብረሰዶም መንፈስ ቁጭ ብሎ "አባትህ ነኝ" እያለ የሚያስፈራራቸው፡ ለራሳቸው የማይኾኑ ውኃ ያልያዙ ደመናዎች ናቸው። መስቀል ይዘው፥ አስኬማ ጭነው፥ ወይም "ዲ/ን"፥ "መምህር"፥ "ደብተራ"፥ "መጋቤ ምናምን"፥ "ሊቀ ምናምን" የሚል ማዕረግ ተሸክመው ግን ያሞኟችኋል። እነሱ አንዴ ለዲያቢሎስ አድረዋል። ዓላማቸው ከገንዘብ፣ ከዝና እና ከቆንጆ ሴቶች ጋር አሼሼ ገዳሜ ከማለት አይዘልልም። አንዳንዴም ሕጻናትና እንስሳት ጋር ይኼዳሉ።
"አፍ አለኝ" ብለው ሲጽፉና ሲናገሩ፡ ከሊቅ ተርታ ተቆጥረው በትልቅ ይገመታሉ። ብትፍቋቸው ግን 666 ናቸው።
እንዲህ ያሉ መምህሮች በዝተውላችኋል። እናንተም ሰው መስለዋችሁ ትሰሟቸዋላችሁ።
ታድያ እነ አብዱጀሊልና እነ ጀበል ለምን አይንቋችሁ?!
ዶ/ር መስከረም ለቺሳ እንደጻፈቺው!! | 222 |
| 4 | የሰንደቅ ዓላማውን ቀለማት የሚቃወመው ማነው??
* * *
ፖለቲከኞች፣ ብሔርተኞች፣ ጽንፈኞች ወዘተ... አረንጓዴ-ቢጫ-ቀዩን ሰንደቅ ዓላማ የሚቃወሙት፡ "የምኒሊክ" ወይም "የአማራ" ወይም "አቢሲንያውያን" ስለኾነ አይደለም። የሚቃወሙት፡ የቅድስት ድንግል ማርያም መቀነት ስለኾነ ነው። የአገሪቱ ባለቤትና ባለርስት፡ እርሷ መኾኗን የሚያሳይ የቃል ኪዳን ምልክት ስለኾነ ነው። ለዐሥራት ልጆቿ በመንፈስ የምትሰጣቸው ምልክት ስለኾነ ነው። በርሷ እናትነት አምነው፥ በልጇ ደም ታትመው ወደርሷ የሚመጡትን፡ ነፍሳቸውን የምትቀበልበት የፍቅር ማሠሪያዋ ስለኾነ ነው። ጠቡ ከርሷ ጋር ነው።
ተቃዋሚዎቹ የሚቃወሙት ደግሞ፡ በዋናነት፡ ኦሮሞ ስለኾኑ፣ ወይም ኩሽ ስለኾኑ፣ ወይም ሙስሊም ስለኾኑ፣ ወይም ፕሮቴስታንት ስለኾኑ (ብቻ) አይደለም። የ666 አባላት ስለኾኑ ነው። ዋና ጽንፈኛ የሰንደቅ ዓላማ ተቃዋሚዎች የሐሳዌ መሢህ መንገድ ጠራጊዎች፥ የሴቲቱ ጠላቶች፥ የዘንዶው መጠቀሚያዎች ናቸው። ለሰበብነት የሚጠቀሙት ግን ብሔርን፣ ወይም የውሸት የጭቆና ትርክትን ነው።
ለዚህ ጥሩ ማሳያ የሚኾነን፦ በጥንቆላ ውስጥ የተሰማሩና ከደብተራው ዓለም ጋር ንክኪ ያላቸው ሰዎች፡ የፈለገ "አማራ" ወይም "ኦርቶዶክስ" ነን ቢሉ፡ ለዚችው ሰንደቅ ዓላማ፡ ከጽንፈኞች ፖለቲከኞች ያልተናነሰ የጠላትነት ስሜት ያላቸው መኾኑ ነው። በግልጽ ወይም በሥውር ሰንደቅ ዓላማውን ይዋጉታል። ወደ 666ቱ ዓለም ተጠቃልለው ገብተዋልና።
"ዘንዶውም፡ በሴቲቱ ላይ ተቈጥቶ፡ የእግዚአብሔርን ትእዛዛት የሚጠብቁትን፡ የኢየሱስም ምስክር ያላቸውን፡ ከዘርዋ የቀሩትን ሊዋጋ ሄደ፤ በባሕርም አሸዋ ላይ ቆመ።" (ራእ 12:17)
እነዚህ ከዘርዋ የቀሩት የኢየሱስ ምስክር ያላቸው የተመረጡ የዐሥራት ልጆቿ ደግሞ፡ ምልክታቸው ሰንደቅ ዓላማው ነው። በመንፈሳዊ ዓይን ሲታዩ፡ ቀስተ ደመና ሰውነታቸው ላይ ተተክሎ ይታያል። ክርስቶስ በሰውነታቸው ላይ ነግሧልና። የርሱ ዙፋን ደግሞ፡ ምልክቱ ቀስተ ደመና ነው፦
«ተቀምጦም የነበረው በመልኩ የኢያስጲድንና የሰርዲኖን ዕንቍ ይመስል ነበር። በመልኩም መረግድን የመሰለ ቀስተ ደመና በዙፋኑ ዙሪያ ነበረ።» (ራእ 4:3)
ዘንዶው ባያቸው ቁጥር በቁጣ የሚወራጨው ለዚያ ነው።
በአገሪቱ ላይ ያለው የ666 መንፈስና አጠቃላይ ኔትወርክ፡ በይሁዳው አንበሳ፡ በመድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ የመስቀሉ ኃይል የተቀጠቀጠ ይኹን!
አሜን!
ዶ/ር መስከረም ለቺሳ | 210 |
| 5 | ይህችን አጭበርባሪ የሴት ደብተራ ጉዷን ተመልከቱ እጅግ ያሳዝናል!! ክፉ መንፈስ ይታሰራል እንጂ በጭራሽ አይሸኝም! በዙሪያችሁ ያሉ ሰዎችን እጅግ ተጠንቀቋቸው! https://youtu.be/e6F5i849CcU | 236 |
| 6 | "ዘራችሁ አይባረክ" የአቡነ ኤርሚያስ የእርግማን ቃልና መዘዙ!! ሴቶች ከበሮ መምታት በጭራሽ አትችሉም!! ከአንድ ጳጳስ እንዲህ ያለ እርግማን ይጠበቃል!? https://youtu.be/ugUiSqdeiug | 241 |
| 7 | ይሄንን በደንብ አዳምጡ ቤተሰቦቼ! https://youtu.be/ttVituXsD1E?si=Sqwdhld8h_5cHKIq | 246 |
| 8 | የእርግማን መንፈስ ያስከተለው እጅግ አደገኛው መዘዝና ጉድ ተመልከቱ!! ጳጳስ የሆነችው ሴት እጅግ አነጋጋሪው ጉዳይ!! የንስሐ አባት ልንቀይር የምንችልበት! https://youtu.be/L_EW5Y4e89M | 273 |
| 9 | Немає тексту... | 284 |
| 10 | Немає тексту... | 269 |
| 11 | Resigning, therefore, these baubles... እነዚህን ጌጣጌጦች ለክፉው መምህር ትተን፣ በዚህ የሐሰት ድምቀት አንካፈል፤ በሰበብ አስባብም ወደ ጣዖት አምልኮ አንግባ። ቅዱስ ጴጥሮስ በሚገባ እንደተናገረው፤ "እንዲሁም ደግሞ ሴቶች በሹሩባና በወርቅ ወይም በዕንቁ ወይም ዋጋው እጅግ በሚበዛ ልብስ ሳይሆን፥ እግዚአብሔርን እንፈራለን ለሚሉ ሴቶች እንደሚገባ በበጎ ሥራ ራሳቸውን ያስውቡ።" ራሳቸውን መሸለም ከእነርሱ ይራቅ። ተፈጥሮአቸው ውብ ከሆነ በቂ ነው። የሰው ጥበብ ከተፈጥሮ ጋር አይጣላ፤ ሐሰት ከእውነት ጋር አይከራከር። በተፈጥሮ ውበት የሌላቸው ከሆኑ ደግሞ፣ በራሳቸው ላይ በሚለጥፉት ጌጥ የሌላቸውን ውበት ለመተካት ሲጥሩ ውሸታቸው ይጋለጣል። ስለዚህ ክርስቶስን የሚያገለግሉ ሴቶች ቀላልነትን (Simplicity) ሊከተሉ ይገባል። ቀላልነት ለቅድስና መሠረት ነው። ቀላልነት አይመካም፣ አይታበይም፣ ከልክ በላይ አይሆንም፤ እርሱ ለሁሉ በቂ ነው።
እንግዲህ በእጃችሁ ፍሬ ውስጥ የተቀደሰ ሥርዓት፣ ለጋስነትና ቁጠባ ይኑር። "ለድሃ የሚመጸውት ለእግዚአብሔር ያበድራል" (ምሳሌ 19:17)። የወንድነት (የጥንካሬ) እጆች ባለጸጋ ይሆናሉ። ጠንካራ የሚላቸው ሀብትን የሚንቁና በነጻነት የሚመጸውቱትን ነው። በእግሮቻችሁ ላይ ደግሞ ለመልካም ሥራ ዝግጁ መሆንና ወደ ጽድቅ መጓዝ ይታይ። ጨዋነትና ንጽሕና እንደ አንገት ሐብል ይሁኑላችሁ፤ እግዚአብሔር የሚቀጠቅጣቸው ሰንሰለቶች እነዚህ ናቸው። "ጥበብን የሚያገኝ ሰው ምስጉን ነው... ከብርና ከወርቅ ይልቅ እሷ ትበልጣለችና፤ ከከበሩ ድንጋዮችም በላይ ዋጋ አላት።" (ምሳሌ 3:13-15)። እውነተኛው ጌጥ ይህ ነው።
ጆሮዎቻቸውም ጌጣጌጥ ለማንጠልጠል ሲባል ከተፈጥሮ ውጭ አይበሱ። ተፈጥሮን ከፍላጎቷ ውጭ ማስገደድ ተገቢ አይደለምና። ለጆሮ ከእውነተኛ ትምህርት (ቃለ እግዚአብሔር) የተሻለ ጌጥ የለም፤ እርሱ በተፈጥሯዊ መንገድ ወደ መስማት ይገባልና። በቃሉ የተቀቡ ዓይኖችና ለመረዳት የተበሱ ጆሮዎች ሰውን መለኮታዊና ቅዱሳን ነገሮችን ተመልካች ያደርጉታል፤ ያን ጊዜ ዓይን ያላየውንና ጆሮ ያልሰማውን እውነተኛ ውበት ቃሉ ይገልጥላችኋል። (1 ቆሮንቶስ 2:9)
የእስክንድርያው ቅዱስ ቀሌምንጦስ (St. Clement of Alexandria)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር! | 263 |
| 12 | "ከመጠን ያለፈ የጌጣጌጥና የወርቅ ድምቀት ፍቅርን ስለመቃወም"
ጥቁር ወይም አረንጓዴ ድንጋዮችን፣ በባሕር ማዕበል ወደ ባዕድ ዳርቻዎች የተጣሉ የምድር ቅንጣቶችን አብዝቶ ማድነቅ የልጅነት አሳብ ነው። ግልጽ የሆኑና ልዩ ቀለም ያላቸውን ድንጋዮች እንዲሁም ያሸበረቁ መስታወቶችን ለማግኘት መሯሯጥ ለውጫዊ ትዕይንት በሚማረኩ ሰነፍ ሰዎች ዘንድ ብቻ የሚታወቅ ባሕርይ ነው። ልክ ሕፃናት የእሳትን ብርሃን አይተው ብሩህነቱ ስለሳባቸው ወደ እሱ እንደሚሮጡና እሳቱን የመንካቱን አደጋ ካለማስተዋል እንደማይረዱት ሁሉ፤ ሰነፍ ሴቶችም በሰንሰለት የታሰሩና በአንገት ሐብል ላይ የተቀረጹ ልዩ ልዩ የከበሩ ድንጋዮችን ሲያደርጉ ሁኔታቸው እንደዚሁ ነው።
ውድ የሆነው ዕንቁም የሴቶችን ማደሪያ ክፍል በከፍተኛ ደረጃ ወርሯል። ይህ ዕንቁ የሚገኘው በትናንሽ የባሕር ፍጥረታት (አይይስትር) ውስጥ ሲሆን፣ መጠኑም በትልቅ ዓሣ ዓይን ያህል ነው። እነዚህ ምስኪን ፍጥረታት (ሴቶች) በዚህች ትንሽ የባሕር ፍጥረት ላይ እንዲህ ያለ ከፍተኛ ጥረት ሲያደርጉ፣ ነገር ግን በቅዱሱ ዕንቁ ማለትም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ "ዕንቁ" ተብሎ በተጠራው በእግዚአብሔር ቃል ራሳቸውን ሊያስውቡ ባለመቻላቸው አያፍሩም። ንጹሕና ብሩህ የሆነው ኢየሱስ — በሥጋ የሚጠብቅ ዓይን — እውነተኛው ቃል እርሱ ነው፤ በእርሱም አማካኝነት በውኃ ዳግመኛ የተወለደ ሥጋ የከበረ ይሆናል።
ሰማያዊቷ ኢየሩሳሌም በቅዱሳን ድንጋዮች የታጠረች መሆኗን ሰምተናል። የሰማያዊቷ ከተማ አሥራ ሁለቱ ደጆች በከበሩ ድንጋዮች መመሰላቸው የሐዋርያትን ድምፅ ታላቅ ጸጋ ያመለክታል። እነዚህ ቀለማት በከበሩ ድንጋዮች ላይ የተቀቡና የከበሩ ናቸው፤ ሌላው ክፍል ግን ምድራዊ ቁስ ሆኖ ይቀራል። በምሳሌያዊ አነጋገር በመንፈስ የታነጸችው የቅዱሳን ከተማ በእነዚህ የታጠረች ናት። በእነዚያ ድንጋዮች ብሩህነት የሚመሰለው የመንፈስ ድምቀት፣ የማይሞት ባሕርይና የቅድስና ሕይወት ነው።
ነገር ግን የመጽሐፍ ቅዱስን ምሳሌያዊነት የማይረዱ እነዚህ ሴቶች፤ "እግዚአብሔር ያሳየውን ለምን አልጠቀምበትም? በእጄ ካለ ለምን ደስ አይለኝም? እነዚህ ነገሮች ለእኛ ካልሆኑ ለማን ተፈጠሩ?" የሚሉ አስገራሚ ሰበቦችን በማቅረብ ለጌጣጌጥ አፋቸውን ይከፍታሉ። እንዲህ ያሉ ንግግሮች የእግዚአብሔርን ፈቃድ ፈጽሞ ካለማወቅ የሚመነጩ ናቸው። እግዚአብሔር እንደ ውኃና አየር ያሉ መሠረታዊ ነገሮችን ለሁሉ በነጻ ሰጥቷል፤ አስፈላጊ ያልሆኑትን ግን በመሬትና በውኃ ውስጥ ቀብሯቸዋል። ለዚህም ነው ጉንዳኖች ወርቅን የሚቆፍሩት፣ ባሕርም የዕንቁ ድንጋይን የሚደብቀው። እናንተ ግን ለማያስፈልጋችሁ ነገር ትደክማላችሁ። እነሆ ሰማይ ሁሉ በርቷል እናንተ ግን እግዚአብሔርን አትፈልጉትም፤ ነገር ግን ለሞት የተፈረደባቸው ሰዎች ተደብቆ ያለውን ወርቅና ጌጣጌጥ ይቆፍራሉ።
ደግሞም "አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል" (ማቴዎስ 6:33) የሚለውን ቅዱስ ቃል ትቃወማላችሁ። ሐዋርያው እንደተናገረው፤ "ሁሉ ተፈቅዶልኛል ሁሉ ግን አይጠቅምም" (1 ቆሮንቶስ 10:23)። እግዚአብሔር የሰው ልጅ እንዲግባባ ያደረገው የራሱ የሆነውን ቃል ለሁሉ በጋራ በመስጠት ነው። ስለዚህ ነገሮች ሁሉ የጋራ ናቸው እንጂ ባለጸጋው ብቻ ያለ አግባብ ድርሻውን የሚወስድባቸው መሆን የለባቸውም። "ሀብት አለኝ፣ በትርፍም አለኝ፤ ታዲያ ለምን አልጠቀምበትም?" የሚለው አነጋገር ለሰው ልጅም ሆነ ለማኅበረሰቡ የሚመጥን አይደለም። ይልቁንም "ሀብት አለኝ፤ ታዲያ ለሚቸገሩት ለምን አልሰጥም?" የሚለው ንግግር ለፍቅር የተገባ ነው። እንዲህ ያለ ሰው — "ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ" የሚለውን ትእዛዝ የሚፈጽም — እርሱ ፍጹም ነው። እውነተኛው ቅንጦትና የከበረ ሀብት ይህ ነው። በሰነፍ ፍትወት ላይ የሚባክን ሀብት ግን እንደ ወጪ ሳይሆን እንደ ብክነት ሊቆጠር ይገባል። እግዚአብሔር የመጠቀም ነፃነትን ቢሰጠንም፣ ይህ የሆነው ለአስፈላጊ ነገሮችና ለጋራ ጥቅም ብቻ ነው። ብዙዎች እየተራቡ አንዱ በቅንጦት መኖሩ እጅግ አስጸያፊ ነው። በቅንጦት ከመኖር ይልቅ ለብዙዎች መልካም ማድረግ ምንኛ የከበረ ነው! ከጌጣጌጥና ከወርቅ ይልቅ በሰው ልጆች ላይ ገንዘብን ማዋል ምንኛ ብልህነት ነው!
ባጭሩ፤ ሴቶች እነዚህን ጌጣጌጦች እንደ ሕፃናት መጫወቻ አድርገው ፈጽመው ሊጥሏቸው ይገባል። ምክንያቱም ሊያጌጡ የሚገባው በውስጥ ማንነታቸው ነው፤ የውስጥ ሴትነታቸው ውብ መሆኑን ሊያሳዩ ይገባል። ውበትም ሆነ አስጠሊታነት የሚታየው በነፍስ ውስጥ ብቻ ነውና። ለዚህም ነው መልካም ባሕርይ ያለው ሰው ብቻ በትክክል ውብና ጥሩ የሚባለው። የሰው ልጅ ልዕልና የሚገለጠው በጽድቅ፣ በመጠን መኖር (Self-control)፣ በጽናትና እግዚአብሔርን በመፍራት ነው። ውብ ሰው ማለት ጻድቅና ደግ የሆነው ነው እንጂ ባለጸጋው አይደለም።
የጌጥ ፍቅር ግን ከቅድስና የራቀ ነው፤ ለውበት ያለንን ፍቅር ወደ ከንቱ ትርዒት በመለወጥ ሥጋን ለራሱ ባሪያ ያደርጋል። ይህ የውሸትና የሐሰት ልማድን ይወልዳል። እነዚህ ሴቶች እውነተኛውን ውበት በወርቅ ይጋርዱታል። በራሳቸው ላይ አሥር ሺህ የሀብት ሰንሰለቶችን ሲያስሩ በደላቸው ምን ያህል ታላቅ እንደሆነ አያውቁም፤ በአሕዛብ ዘንድ ወንጀለኞች በወርቅ ሰንሰለት እንደሚታሰሩ ይነገራል። እነዚህ ሴቶች እነዚያን እስረኞች የሚመስሉ ይመስለኛል። የወርቅ አንገት ሐብል እንደ አንገት ብረት (Collar) አይደለምን? በእግራቸው ላይ የሚያደርጉት ጌጥስ እንደ እግር ብረት (Fetters) አይደለምን? የተባረካችሁ ሴቶች ሆይ፤ ይህ ለጌጥ የምትመኙት ነገር ራሳችሁን በሰንሰለት ታስራችሁ እንደ ማሳየት ካልሆነ በቀር ሌላ ምን ሊባል ይችላል? እባብ ሔዋንን እንዳታለላት ሁሉ፣ የወርቅ ጌጥም ሌሎች ሴቶችን ለእባብ ቅርጽ (በአምባርና በጌጥ መልክ) እንደ ማጥመጃ በመጠቀም ወደ ክፉ ልማድ እንዲሳቡ አድርጓቸዋል።
የጌጣጌጦችን ብዛት መዘርዘር ሰልችቶኛል፤ እንዲህ ያለውን ሸክም የሚሸከሙ ሰዎች በጭንቀት አለመሞታቸው ይገርመኛል። ይህ ምንኛ የሰነፍ ጥረት ነው! ለውዳሴ ከንቱ ያለ ምንኛ የሞኝ አምልኮ ነው! ለውርደት በሚሆን ነገር ላይ ሀብታቸውን ያባክናሉ፤ እግዚአብሔር የሰጣቸውን የተፈጥሮ ውበት በማበላሸት የክፉውን (የሰይጣንን) ጥበብ ይከተላሉ። በጎተራው ሀብት አከማችቶ "ነፍሴ ሆይ ብዪ፣ ጠጪ፣ ደስ ይበልሽ" ያለውን ባለጸጋ ጌታችን በወንጌል "ሰነፍ" ብሎታል። ምክንያቱም በዚያች ሌሊት ነፍሱ ትወሰድ ነበርና። (ሉቃስ 12:19-20)። ሰዓሊው አፔለስ አንዱ ደቀ መዝሙሩ የሄሌን ምስል ውብ አድርጎ መሳል ሲያቅተው በወርቅ ቀለም አጥለቅልቆት ሲያይ እንዲህ አለው፦ "ልጄ ሆይ፤ ውብ አድርገህ መሳል ስለማትችል ባለጸጋ አደረግሃት።" የዛሬዎቹ ሴቶችም እንደዚሁ ናቸው፤ በትክክል ውብ ከመሆን ይልቅ በሀብት ተለጥፈው ይታያሉ። ነቢዩ ሶፎንያስ ስለ እነዚህ እንዲህ ሲል ትንቢት ተናግሯል፦ "ብርና ወርቃቸው በእግዚአብሔር ቍጣ ቀን ሊያድናቸው አይችልም።" (ሶፎንያስ 1:18)
በክርስቶስ ትምህርት ለታነጹ ሴቶች ግን ተገቢው ጌጥ ወርቅ ሳይሆን የእግዚአብሔር ቃል ነው። | 205 |
| 13 | እባካችሁ ይሄንን ምልክት ካያችሁ የጊዜ ሰላቢ መተት ውስጣችን አድፍጧልና ንቁ!! ወንዶች እንዳይቀርቧት የተደረገው አደገኛው መተትና መዘዙ!! #መተት #ሰይጣን https://youtu.be/olgpcpcdjFI | 285 |
| 14 | Немає тексту... | 337 |
| 15 | ...ስለ አለባበስ (የቅዱስ ቀሌምንጦስ ትምህርት)
"ውድ ልብስን ማከማቸት እንደ ምግብ ብርቅ አስፈላጊ አይደለም። ጌታችን ራሱ ትእዛዛቱን ለሦስት ከፍሎታል፦ ስለ ነፍስ፣ ስለ ሥጋና ስለ ውጫዊ ነገሮች። ጌታ ሥጋን በነፍስ ይመራዋል፣ ነፍስንም በሥርዓት ይገሥጻታል፤ እንዲህም ይላል፦ 'ለነፍሳችሁ በምትበሉት ወይም ለሥጋችሁ በምትለብሱት አትጨነቁ፤ ነፍስ ከመብል ሥጋም ከልብስ ይበልጣልና።' (ሉቃስ ፲፪፥፳፪-፳፫)። ለዚህም ግልጽ ምሳሌ ሲሰጥ፦ 'ቁራዎችን ተመልከቱ፤ አይዘሩም አያጭዱም... እግዚአብሔርም ይመግባቸዋል፤ እናንተስ ከወፎች እንዴት ትበልጣላችሁ!' (ሉቃስ ፲፪፥፳፬) ይላል። ስለ ምግብ እንዲህ ካለ፣ ስለ አለባበስም እንዲሁ ይላል፦ 'አበቦችን ተመልከቱ፤ እንዴት እንደሚያድጉ፤ አይፈትሉምም አይሸምኑምም፤ ነገር ግን እላችኋለሁ ሰሎሞንስ እንኳ በክብሩ ሁሉ ከነዚህ እንደ አንዱ አልለበሰም።' (ሉቃስ ፲፪፥፳፯)። ሰሎሞን ንጉሥ በሀብቱ እጅግ ይመካ ነበር።
እጠይቃችኋለሁ፤ ከአበቦች ይልቅ ይበልጥ የሚያምርና ደስ የሚል ቀለም ያለው ምን አለ? እግዚአብሔር ዛሬ ያለውንና ነገ ወደ እቶን የሚጣለውን ሣር እንዲህ የሚያለብሰው ከሆነ፣ እናንተ እምነት የጎደላችሁ፣ እናንተንማ እንዴት አብልጦ አያለብሳችሁም! (ሉቃስ ፲፪፥፳፰)። ቅዱስ ቃሉ እንደሚነግረን፣ ስለ ምግብና መጠጥ ከመጠን በላይ መጨነቅ የስስትና የቅንጦት ምልክት ነው። መብላትና መጠጣት ለሰው ልጅ አስፈላጊ (Necessity) ቢሆንም፣ ከዚያ በላይ የሆነው ግን ከመጠን ያለፈ (Superfluity) ሲሆን፤ መጽሐፍ ቅዱስ ደግሞ ከመጠን ያለፈ ነገር ሁሉ 'ከክፉው (ከዲያብሎስ) ነው' ይላል። ጌታ 'አትጨነቁ' ሲል 'ልባችሁም አይታበይ' ማለቱ ነው። ትዕቢትና ቅንጦት ሰውን ከእውነት ያርቃሉ። ለዚህም ነው ጌታ 'ይህንስ ሁሉ የዓለም አሕዛብ ይፈልጉታል' ያለው። (ማቴዎስ ፮፥፴፪)። አሕዛብ የተባሉት ሥርዓተ አልባና ሰነፎች ናቸው። እነርሱ የሚፈልጉት ቅንጦትን፣ መብላትንና ሆድ አምላኪነትን ነው። አባታችሁ ግን እነዚህ ሁሉ እንደሚያስፈልጓችሁ ያውቃል። ስለዚህ የእግዚአብሔርን መንግሥት ፈልጉ፣ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።
ጌታ ስለ ምግብና ልብስ መጨነቅን ካስወገደልን፣ ታዲያ ስለ ጌጣጌጥ፣ ስለ ልብስ ቀለም ብዛት፣ ስለ ዕንቁዎች ጥራት፣ ስለ ወርቅ ጥልፍ፣ እንዲሁም ስለ ሰው ሠራሽ ጸጉርና ሽሩባ ምን ሊባል ነው? በተጨማሪም ዓይንን ስለ መኳኳል፣ ጸጉርን ስለ መንቀልና ስለ መቀለም፣ እንዲሁም በእነዚህ የማታለያ ጥበቦች ውስጥ ስላሉት ክፉ ሥራዎች ምን እንላለን? ቅዱስ ቃሉ ስለ ሣር የተናገረው ለእነዚህ ውበት ለሌላቸው የጌጥ አፍቃሪዎች ሳይሆን አይቀርም። ሜዳው ዓለም ነው፤ እኛ በእግዚአብሔር ጸጋ የረካን 'ሣሮች' ነን። ነገር ግን 'ጭድ' (Hay) ተብሎ የተገለጠው ዓለማዊ እርካታን የሚከተሉ፣ ለጥቂት ጊዜ ደምቀው የሚጠፉ፣ ውዳሴ ከንቱን የሚወዱና መጨረሻቸው ለእሳት የሚሆን ሰነፎችን ነው። ጌታ በምሳሌው እንደተናገረው፤ በሐምራዊና በቀጭን የተልባ እግር ልብስ የሚለብስ አንድ ባለጸጋ ነበረ፣ በየቀኑም በድል ያጌጥ ነበር። ይህ 'ጭድ' ነው። አልዓዛር የተባለ ደሃ ግን በደጁ ወድቆ ነበር፤ ይህ 'ሣር' ነው። ባለጸጋው በሲኦል በእሳት ሲቀጣ፣ አልዓዛር ግን በአብርሃም እቅፍ (በአምላክ ዘንድ) ለመለም።
እኔ የምለው፤ ሰው ልብስ የሚያስፈልገው ለሰውነቱ መሸፈኛ ብቻ ነው፤ ይኸውም ከብርድና ከሙቀት ለመከላከል ነው። የልብስ ዓላማ መሸፈን ከሆነ፣ በወንድና በሴት መካከል (በመሠረቱ) ልዩነት ሊኖር አይገባም። መሸፈን ለሁለቱም የጋራ ፍላጎት እንደመሆኑ፣ አቅርቦቱም ተመሳሳይ መሆን አለበት። እርግጥ ነው፣ ለሴቶች ዓይን የመሸፈኛ ጥንቃቄ ሊታከልበት ይገባል። ሴቶች በደካማነታቸው ምክንያት ይበልጥ ካለሙ፣ ይህ በክፉ ሥልጠና የመጣ መጥፎ ልማድ ነው። የሰውነትን ቅርጽ የሚገልጥ፣ እጅግ ቀጭን የሆነና የሰውነትን ነውር የማይሸፍን ልብስ መሸፈኛ ሊባል አይችልም። እንዲህ ያለው ልብስ ከሥጋ ጋር ተጣብቆ የሴቲቱን ቅርጽ ለተመልካች የሚያሳይ በመሆኑ ነውር ነው።
ልብስን ማቅለም (Dyeing) ሊወገድ ይገባል። ይህ ከአስፈላጊነትና ከእውነት የራቀ ነው። ቀለማት ከብርድ አይከላከሉም፣ ከመሸፈንም ረገድ ከሌላው ልብስ የተለየ ጥቅም የላቸውም። ይልቁንም የስስት ዓይኖችን በማቃጠል ወደ ዕውርነት ይመራሉ በውስጣቸው ንጹሕና ነጭ ለሆኑት ግን ነጭና ተራ ልብሶችን መጠቀም እጅግ ተስማሚ ነው። ነቢዩ ዳንኤል 'ዙፋኖች ተዘረጉ፥ በዘመናት የሸመገለውም ተቀመጠ፤ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ነበረ' ይላል። (ዳንኤል ፯፥፱)። በራእይም ጌታ እንዲህ ባለ ልብስ ታይቷል። ሰማዕታትም ነጭ ልብስ ተሰጣቸው። (ራእይ ፮፥፱፣ ፲፩)። ስለዚህ እውነተኛው ቀለም የእውነት ተፈጥሯዊ ቀለም (ነጭ) ነው።
መምህሩ (ፔዳጎጉ) በግልጽ ይመክረናል፦ 'በልብስህ አትመካ፥ በክብርህም አትታበይ፤ ይህ ሕግ አይደለምና።' (ሲራክ ፲፩፥፬)። በቅንጦት ልብስ የሚሽሞነሞኑትን ጌታ በወንጌል እንዲህ ሲል ተሳልቆባቸዋል፦ 'እነሆ፥ ያጌጠ ልብስ የሚለብሱና በቅንጦት የሚኖሩ በነገሥታት ቤት አሉ።' (ሉቃስ ፯፥፳፭)። በሰማያዊው ንጉሥ ፊት የሚቆሙ ግን በማይጠፋው በመንፈስ ልብስ (በቅድስና) ያጌጡ ናቸው።
ያላገባች ሴት ለፈጣሪዋ ብቻ ትሰጣለች፤ ያገባች ንጽሕት ሴት ደግሞ ሕይወቷን በእግዚአብሔርና በባሏ መካከል ትከፍላለች። ነገር ግን ጌጥ የምትወድ ሴት ከእግዚአብሔርና ከንጹሕ ትዳር ትርቃለች፤ ባሏን በዓለም ትለውጣለች። እውነተኛ ሚስት በጨዋነት (Modesty) ልታጌጥ ይገባል። ቃሉን የሚከተል ሰው ግን ወደ ርካሽ እርካታ አይሳብም። መጥምቁ ዮሐንስ የበግ ጸጉርን እንደ ቅንጦት በመቁጠር፣ የግመል ጸጉርን መረጠ፤ ይህም ለትሕትናና ለቀላል ሕይወት ምሳሌ ሆነ። አንበጣና የበረሃ ማር እየበላ ለጌታ መንገድ ጠረገ። ነቢዩ ኤልያስ የበግ ቆዳ ይለብስ ነበር። (፪ኛ ነገሥት ፩፥፰)። ነቢዩ ኢሳይያስ ዕራቁቱንና በባዶ እግሩ ይሄድ ነበር፣ አንዳንዴም የትሕትና መለያ የሆነውን ማቅ ይለብስ ነበር። (ኢሳይያስ ፳፥፪)። ኤርምያስም የተልባ እግር መታጠቂያ ብቻ ነበረው። (ኤርምያስ ፲፫፥፩)።
ልብስን እየጎተቱ እስከ እግር ጥፍር ድረስ ማውረድ የትዕቢት ምልክት ነው፤ ይህም አረማመድን ያስቸግራል፣ ልክ እንደ መጥረጊያ የመሬቱን ቆሻሻ ይዝቃል። እንዲህ ያለው አለባበስ የሥርዓተ አልባነትና የሴሰኝነት መገለጫ ነው። ጌታችን እስከ እግሩ የሚደርስ ልብስ መልበሱ ግን የጥበብ አበባዎች፣ የማይጠወልጉ ቅዱሳት መጻሕፍትና የእውነት ጨረር ምሳሌ ነው። ልብሳችን ከጉልበት በላይ መሆን የለበትም፣ የሴት አካልም ለሰው መታየት የለበትም። ለአንቺ ውብ የሆነው ለባልሽ ብቻ፣ ፊትሽም ለሚያውቅሽ ብቻ ሊሆን ይገባል። ጨዋ ሴቶች በውበታቸው ለወንዶች ወጥመድ ሊሆኑ አይገባም። ጭንቅላት መሸፈን፣ ፊትም መከለል አለበት። ሐምራዊ (Purple) ልብስ መልበስ ለሰው ዓይን መጋበዝ ስለሆነ ሊቀነስ ይገባል።
ልብስ የሚሸፍነውን አካል ሊያስከብር ይገባል፤ ምክንያቱም ምስል ከመቅደስ፣ ነፍስ ከሥጋ፣ ሥጋ ደግሞ ከልብስ ይበልጣል። አሁን ግን ነገሩ ተገልብጧል። የብዙ ሴቶች ሥጋ በገንዘብ ቢገመት ዋጋው ዝቅተኛ ነው፤ ልብሳቸው ግን በአሥር ሺህ ታላንት ይገዛል። ለምን ቅርብና ርካሽ የሆነውን ትታችሁ ብርቅና ውድ የሆነውን ትፈልጋላችሁ? ይህ የሚሆነው እውነተኛውን ውበትና እውነተኛውን በጎነት ካለማወቅ የተነሣ ነው። ጥቁሩን ነጭ ነው ብለው እንደሚያስቡ እብዶች፣ እናንተም በእውነት ፋንታ ጥላውን ትከተላላችሁ።" | 305 |
| 16 | "ባለቤትን (ባልን) ለማስደሰት ስለሚቀርብ ሰበብ"
"እግዚአብሔርን ለማያውቁ (ለአሕዛብ) እንደምናገር ሆኜ፣ በእነርሱም ዘንድ የተለመደውንና ለሁሉም የሚስማማውን ሕግ ብጠቅስላችሁ፤ 'እናንተ መውደድና ማስደሰት ያለባችሁ ባሎቻችሁን ብቻ ነው' እላችኋለሁ። ነገር ግን ሌሎችን ሰዎች ደስ ለማሰኘት በምትተዉት ልክ፣ ባሎቻችሁን ይበልጥ ደስ ታሰኛላችሁ።
የተባረካችሁ እህቶች ሆይ፣ አትጨነቁ፤ ለማንኛውም ባል ሚስቱ አስጠሊታ አይደለችም። እርሱ አንቺን ሚስቱ አድርጎ ሲመርጥሽ፣ ወይ በውበትሽ ወይ በባሕርይሽ ተማርኮ ደስ ተሰኝቶብሻልና ያ ራሱ በቂው ነው። ከእናንተ መካከል ማንም ቢሆን፤ 'ራሴን ማስዋብ (መኳኳል) ካቆምኩ ባሌ ይጠላኛል ወይም ይጸየፈኛል' ብላ አታስብ።
ማንኛውም ባል ከሚስቱ አጥብቆ የሚፈልገው ንጽሕናንና ታማኝነትን ነው፤ አማኝ (ክርስቲያን) የሆነ ባል ግን ሰው ሠራሽ ውበትን አይጠይቅሽም፤ ምክንያቱም እኛ የምንማረከው አሕዛብ ውበት ነው ብለው በሚያስቡት ዓይነት ሥጋዊ ድምቀት አይደለም። ያላመነ (አረማዊ) ባል ደግሞ፤ ሚስቱ ራሷን አብዝታ ስታስውብ 'ለሌላ ሰው ነው' በሚል በጥርጣሬ ይመለከታታል።
ታዲያ ይህን ውበትሽን የምትጠብቂውና የምትመገቢው ለማን ነው? ለአማኝ ባል ከሆነ እርሱ ይህን አይፈልግም፤ ላላመነ ባል ከሆነ ደግሞ ውበትሽ ተፈጥሯዊና ያለ ኩል (ያለ መሸላለም) ካልሆነ በቀር 'ንጽሕት ናት' ብሎ አያምንሽም። በጥርጣሬ የሚመለከትሽን ወይም ደግሞ ይህን ውበት የማይፈልገውን ሰው ለማስደሰት ለምን እንዲህ ትጨነቂያለሽ?" | 222 |
| 17 | "ነውረ-አልባነት (ጨዋነት) በባሕርይው ብቻ ሳይሆን በጓዞቹም ጭምር ሊጠበቅ ይገባል"
"የሕያው እግዚአብሔር አገልጋዮች (ገረዶች)፣ የሥራ ባልደረቦቼና እህቶቼ ሆይ፤ በእናንተ መካከል — ከሁሉ የማንሰውና ትንሹ ብሆንም — ባለኝ የወንድማማችነትና የአገልጋይነት መብት ተጠቅሜ፣ ለፍቅር ሲባል ለነፍሳችሁ ደኅንነት የሚሆን ንግግር ለማቅረብ እደፍራለሁ። ያ ደኅንነት — ለሴቶች ብቻ ሳይሆን ለወንዶችም ጭምር — የሚገኘው በዋናነት ነውረ-አልባነትን (Modesty) በተግባር በማሳየት ነው።
መንፈስ ቅዱስ በእኛ ውስጥ ስላደረና እኛን ገንዘብ ስላደረገ፣ ሁላችንም የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ነን። 'ነውረ-አልባነት' (Modesty) ደግሞ የዚያ መቅደስ ጠባቂና አገልጋይ (ካህን) ናት። በውስጡ የሚያድረው አምላክ እንዳይቆጣና የቆሸሸውን ማደሪያ ፈጽሞ ትቶ እንዳይወጣ፣ ማንኛውም ንጹሕ ያልሆነ ወይም የረከሰ ነገር ወደ መቅደሱ እንዳይገባ የመከላከል ኃላፊነት የሷ ነው።
አሁን ግን የምናገረው ስለ ነውረ-አልባነት (Modesty) አስፈላጊነት አይደለም፤ እርሱንማ በየአቅጣጫው የሚጫኑን መለኮታዊ ትእዛዛት በሚገባ ያስረዱናል። ይልቁንም ትኩረቴ ከእርሱ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ ነው፤ ይኸውም እናንተ ልትመላለሱበት (ልትኖሩበት) በሚገባው አኳኋን ላይ ነው። አብዛኞቹ ሴቶች (ይህንን ጉዳይ እግዚአብሔር እንድገሥጽ ይፍቀድልኝ) ወይ ካለማወቅ ወይም ደግሞ እያወቁ ችላ በማለት፣ 'ነውረ-አልባነት' ማለት ሥጋን ከዝሙት መጠበቅ ብቻ ይመስላቸዋል። ከውጭ የሚታየው የአለባበስ ሥርዓት፣ ጌጣጌጥ፣ ሰው ሠራሽ ውበትና ድምቀት ግን ምንም ጉዳት የሌለው ይመስላቸዋል። አረማመዳቸውና አኳኋናቸው እውነተኛው ነውረ-አልባነት ከማይታወቅባቸው ከአሕዛብ ሴቶች ጋር አንድ ዓይነት ሆኗል። እውነትን የሚያውቁትን አምላክ በማያውቁ ሰዎች ዘንድ እውነተኛ ነገር ሊኖር አይችልምና።
በአሕዛብ ዘንድ ‘ጨዋነት’ አለ ተብሎ ቢታመን እንኳ፣ እርሱ ያልሰለጠነና ያልተሟላ ነው። በአእምሮ ደረጃ ‘እጠብቀዋለሁ’ ቢሉም፣ በአለባበስ ረገድ ግን ለፍትወት በሚያነሳሳ ዝርክርክነት ውስጥ ይወድቃሉ። ይህም የአሕዛብ ጠማማነት ነው፤ ውጤቱን (ዝሙትን) እየፈሩ፣ ምክንያቱን (የሚያነሳሳ አለባበስን) ግን ይፈልጉታል። ባጭሩ፤ በማያውቋቸው ሰዎች ፊት ለመወደድና ለመታየት የማይመኝ ማን አለ? ለዚህም ሲሉ ራሳቸውን ይቀባባሉ (ይኳኳላሉ)፤ ነገር ግን ‘ለፍትወት አላነሳሳሁም’ ብለው ይክዳሉ።
ይህ በአሕዛብ ዘንድ የተለመደ ነው—ኃጢአቱን በቀጥታ ባይፈጽሙትም፣ ለኃጢአቱ ፈቃደኛ መሆን፣ ወይም ደግሞ ፈቃደኛ ባይሆኑም እንኳ ሙሉ በሙሉ አለመቃወም ይታይባቸዋል። የእግዚአብሔር ያልሆነ ነገር ሁሉ ጠማማ መሆኑ ምን ይደንቃል? ስለዚህ፤ ሙሉ በሙሉ በበጎነት ላይ የማይጸኑና ያሏቸውን መልካም ነገሮች ከክፋት ጋር የሚያቀላቅሉ ሴቶች ራሳቸውን ይመርምሩ። ልክ በሌሎች ነገሮች ሁሉ እንደሚደረገው፣ በአኗኗራችሁና በአለባበሳችሁም ከእነርሱ መለየት (መራቅ) ይገባችኋል። የሰማዩ አባታችሁ ፍጹም እንደሆነ እናንተም ፍጹማን ልትሆኑ ይገባልና።"
=> ተርቱሊያን (Tertullian) | 183 |
| 18 | "የሴቶች ጌጣጌጥ አመጣጥ፤ ከሰማይ ወደ ወደቁት መላእክት የሚመነጭ"
"እነዚህን የጌጥ ሥርዓቶች የፈጠሩትና መመሪያ የሰጡት፣ በሞት ፍርድ ኩነኔ ሥር የወደቁት እነዚያ መላእክት ናቸው፤ ይኸውም ከሰማይ ወርደው የሰውን ልጆች ሴቶች ልጆች የተመኙት መላእክት ናቸው። በመሆኑም ይህ ውርደት ከሴት ባሕርይ ጋር ተያይዟል። ምክንያቱም እነዚያ መላእክት፣ ከእኛ ዘመን ይልቅ እጅግ ምንም ለማያውቀው የጥንቱ ትውልድ፣ በምስጢር ተደብቀው የነበሩ ቁሳቁሶችንና ያልተገለጡ የጥበብ ሥራዎችን ይፋ አደረጉ።
የብረታ ብረት አሠራርን (metallurgy) ገለጡ፤ የዕፅዋትን ተፈጥሯዊ ባሕርይና ኃይል አሳወቁ፤ የመተትና የድግምትን ኃይል አሰራጩ፤ እንዲሁም እስከ ኮከብ ቆጠራ ድረስ ያሉትን ጉጉት ቀስቃሽ ጥበባት ሁሉ አስረዱ። በተለይም ደግሞ ለሴቶች ውጫዊ ትዕቢትና ድምቀት የሚሆኑትን መሣሪያዎች ሰጡ፤ ይኸውም የአንገት ሐብል የሚሠራባቸውን የሚያብለጨልጩ ዕንቁዎች፣ እጆችን የሚያስሩ የወርቅ አምባሮችን፣ ጸጉርና ልብስ የሚቀለሙባቸውን ማቅለሚያዎች፣ እንዲሁም የዓይን ሽፋሽፍትንና ቅንድብን ጎልቶ እንዲታይ የሚያደርገውን ያንን ጥቁር የኩል ዱቄት ጭምር አስተማሩ።
እነዚህ ነገሮች ምን ያህል አደገኛ እንደሆኑ ለማወቅ፣ መጀመሪያ ያስተማሩትን መምህራን ማንነትና ሁኔታ ማየት ይበቃል። ኃጢአተኞች ለቅድስናና ለጽኑ ምግባር የሚሆን ነገር ሊያሳዩ ወይም ሊያቀርቡ አይችሉም፤ ሕገ-ወጥ አፍቃሪዎች (መላእክቱ) ለንጽሕና የሚሆን ነገር አይሰጡም፤ ዓማፂያን መናፍስትም እግዚአብሔርን ለመፍራት የሚረዳ ጥበብ አያስተምሩም። እነዚህ ትምህርት ከተባሉ፣ ክፉ መምህራን ክፉ ነገርን ማስተማራቸው ግድ ነው፤ የፍትወት ደመወዝ ከተባሉ ደግሞ፣ መሠረቱ የረከሰ ነገር ደመወዙ የከበረ ሊሆን አይችልም።
ታዲያ እነዚህን ነገሮች ማሳየትና መስጠት ለምን አስፈለጋቸው? ሴቶች ያለ እነዚህ ውጫዊ ድምቀቶችና ሰው ሠራሽ ውበቶች ወንዶችን ማስደሰት አይችሉም ብለው ነው? እነዚያ መላእክት እኮ ሴቶቹን የወደዷቸው ገና ሳይሸለሙ፣ ባልተለወጠ የተፈጥሮ ውበታቸው ሳሉ ነበር። ወይስ መላእክቱ አፍቃሪ መስለው ለመታየትና በሴቶቹ ላይ የነበራቸውን ሥልጣን ለማጽናት ሲሉ እነዚህን 'ስጦታዎች' ሰጡ? እነዚህ መላእክት ከየት እንደወደቁ ያውቁ ነበር፤ ከፍትወታቸው በኋላ ወደ ሰማይ ሲመለከቱ፣ የሴቶችን ተፈጥሯዊ ውበት ለክፋት መሣሪያነት ተጠቀሙበት። ዓላማቸውም ሴቶች ከቅንነትና ከእውነተኛነት ወጥተው፣ እንደነርሱ በእግዚአብሔር ፊት የተጠሉ እንዲሆኑ ለማድረግ ነው። በሥጋዊ መንገድ ሰውን ለማስደሰት የሚደረግ ማንኛውም ትዕቢትና ምኞት በእግዚአብሔር ፊት የተጠላ መሆኑን ያውቁ ነበር።
እኛ ወደፊት የምንፈርድባቸው መላእክት እነዚህ ናቸው፤ በጥምቀት ጊዜ የካድናቸው መላእክት እነዚህ ናቸው፤ በሰው ልጅ እንዲፈረድባቸው ያደረጋቸው አንዱ ምክንያትም ይኸው ነው። ታዲያ በእነርሱ (በተፈራጅ መላእክት) እና በዳኞቻቸው (በእኛ) መካከል ምን ግንኙነት አለ? በሚፈርድና በሚፈረድበት መካከል ምን ዓይነት ንግድ ይኖራል? በክርስቶስና በቤልሆር መካከል ምን ስምምነት አለ? አሁን ስጦታቸውን እየፈለግን፣ ነገ በዙፋን ላይ ተቀምጠን በእነርሱ ላይ ለመፍረድ እንዴት እንችላለን? እናንተ ሴቶችም ብትሆኑ፣ እንደ ወንዶች ሁሉ የመላእክትን ባሕርይ የመውረስና የመፍረድ ክብር ተስፋ ተሰጥቷችኋል። ስለዚህ ገና ከዚህ ምድር ጀምረን በእነርሱ ዕቃዎች ላይ ካልፈረድንና ካልተውነው፣ ነገ በእነርሱ ላይ መፍረድ አንችልም። ይልቁንም እነርሱ በእኛ ላይ ይፈርዱብናል፤ ይረክሱብናልም።
=> ተርቱሊያን (Tertullian) | 177 |
| 19 | Немає тексту... | 199 |
| 20 | "በመናንያን ላይ እጅን ማንሣት በእግዚአብሔር ዘንድ የተከለከለ፣ በታሪክ ፊትም የሚያሳፍር ድርጊት ነው።" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ
ቅዱስነታቸው በወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዳዮች ላይ አባታዊ መልእክት አስተላላፉ።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ወቅታዊ ጉዳዮች በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።
ሓምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ መልእክት እንደሚከተለው ነው፦
መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
"ገባሬ ሣህል እግዚአብሔር፥ ወይፈትህ ለኩሉ ግፉዓን፦
እግዚአብሔር ይቅርታ አድራጊ ነው፤ ለተበደሉ ሁሉ ይፈርዳል።"
(መዝሙር ፻፪፥፮)
ከሁሉ በማስቀደም በሀገር ውስጥ እና በመላው ዓለም የምትኖሩ ኦርቶዶክሳውያን የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንን ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓመተ ምሕረት በከፍተኛ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ለሚከበረው፤ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተልኮ በእምነታቸው የጸኑትን ቅዱስ ቂርቆስንና ቅድስት ኢየሉጣን በመከራቸው መካከል እየተራዳ የእሳቱን ነበልባል እንደክረምት ውኃ ላቀዘቀዘበት፤ በእግዚአብሔር ቃል ኪዳን የታመኑትንም እስከ ሰማዕትነት ፍጻሜ ድረስ የሚያጸና መሆኑን ለምንዘክርበት ታላቅ በዓል እንኳን አደረሳችሁ ለማለት እንወዳለን።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከዘመነ ሐዋርያት ጀምሮ የወንጌልን ብርሃን በማብራት፣ የሰላምን መንገድ በማስተማር፣ ፍትሕን በማጽናት፣ የተጨነቁትንም በማጽናናት፣ ሕዝብንና ሀገርን እየደገፈች የኖረች ናት።
በዚህ ቅዱስ ተልእኮ ውስጥም መናንያን መነኮሳት እና መነኮሳይያት ዓለምንና ከዓለም የሚገኘውን ጊዜያዊ ክብር፣ ጥቅም፣ ምቾትና የመሳሰሉትን በፈቃዳቸው ትተው፤ በየገዳማቱ በበአታቸው በጾም፣ በጸሎት ተወስነው፤ ሕይወታቸውን በትሕትና ለእግዚአብሔር በመስጠት፤ ስለ ራሳቸው ብቻ ሳይሆን ስለ ሀገር፣ ስለ ሕዝብ፣ ስለ ሰላምና ስለ ዓለም ደኅንነት በመዓልትና በሌሊት የሚጸልዩ የምድራችን በረከቶች ናቸው።
መስቀልን በተሸከሙ፣ ጸሎትን መከታ ባደረጉ፣ ለፍጥረት ሁሉ ምሕረትን በሚለምኑ፣ ራሳቸውን ለመከላከልም ምንም ዓይነት ቁሳዊ ዝግጅት በሌላቸው በእነዚህ መናንያን ላይ እጅን ማንሣት በእግዚአብሔር ዘንድ የተከለከለ፣ በታሪክ ፊትም የሚያሳፍር ድርጊት ነው።
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን!
በደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት በቦረና ወረዳ በግዮን አባይ ገዳመ አስቄጥስ ቅድስት አርሴማ፣ አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶችና የእናቶች አንድነት ገዳም ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓመተ ምሕረት በተፈጸመው ጥቃት የመናንያን መነኮሳይያት ሕይወት በግፍ መጥፋቱን፤ በርካቶች መቁሰላቸውን፤ በገዳሙና በንዋየ ቅድሳቱ ውድመት መድረሱን ከሀገረ ስብከቱ መግለጫ በከፍተኛ ሐዘን የሰማን ሲሆን፤ በተመሳሳይም በዚሁ ዕለት በሀድያና ስልጤ ሀገረ ስብከት የአምልኮ ሥፍራ በኃይል መፍረሱና በምእመናን ላይ ጥቃት መድረሱ የሚያሳዝንና በፍጹም ተቀባይነት የሌለው የተወገዘ ተግባር ነው።
በመሆኑም የጸሎት፣ የትምህርት፣ የሰላምና የመንፈሳዊ እሴት ማዕከል የሆኑትን ገዳማት መጠበቅ የአንድ ሃይማኖት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፣ የሰው ልጅ ክብርን፣ የሕግ የበላይነትንና የሀገር ሰላምን የማስጠበቅ ሓላፊነት ያላቸው በየደረጃው የሚገኙ ባለሥልጣናትና የሕግ አስከባሪ አካላት ጭምር እንደመሆኑ አሰቃቂ ጥቃት የፈጸሙት ተጠያቂዎች ለፍትሕ እንዲቀርቡ፤ ሌሎች ገዳማትና አድባራት ደኅንነታቸው እንዲጠበቅልን፤ ለተጎዱትም ተገቢው ድጋፍ እንዲደረግልን ዛሬም አበክረን እንጠይቃለን ።
በመጨረሻም ሕዝበ ክርስቲያንና መላው ኢትዮጵያውያን የጥቃት ሰለባ ከሆኑት ወገኖች ጋር በመንፈሳዊም ሆነ በሰብአዊ ድጋፍ አብራችሁ እንድትቆሙ ከአደራ ጭምር እያሳሰብን፤ በጽድቅ የሚፈርደው እግዚአብሔር አምላካችን ለተበደሉት ፍትሕን፣ ለቆሰሉት ፈውስን፣ በግፍ ሕይወታቸውን ለተነጠቁት ዕረፍተ ነፍስን፣ ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን ፍጹም ሰላምን ይስጥልን እያልን አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
© የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት | 260 |
