HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Открыть в Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Больше2 280
Подписчики
Нет данных24 часа
+77 дней
+3930 день
Загрузка данных...
Похожие каналы
Облако тегов
Нет данных
Возникли проблемы? Пожалуйста, обновите страницу или обратитесь к нашему support-менеджеру .
Входящие и исходящие упоминания
---
---
---
---
---
---
Привлечение подписчиков
июль '26
июль '26
+45
в 0 каналах
июнь '26
+79
в 0 каналах
Get PRO
май '26
+65
в 0 каналах
Get PRO
апрель '26
+71
в 0 каналах
Get PRO
март '26
+79
в 0 каналах
Get PRO
февраль '26
+51
в 0 каналах
Get PRO
январь '26
+55
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '25
+46
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '25
+74
в 1 каналах
Get PRO
октябрь '25
+45
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '25
+36
в 0 каналах
Get PRO
август '25
+49
в 0 каналах
Get PRO
июль '25
+62
в 0 каналах
Get PRO
июнь '25
+55
в 0 каналах
Get PRO
май '25
+94
в 0 каналах
Get PRO
апрель '25
+76
в 0 каналах
Get PRO
март '25
+70
в 0 каналах
Get PRO
февраль '25
+63
в 0 каналах
Get PRO
январь '25
+69
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '24
+114
в 1 каналах
Get PRO
ноябрь '24
+77
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '24
+62
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '24
+58
в 0 каналах
Get PRO
август '24
+48
в 1 каналах
Get PRO
июль '24
+62
в 0 каналах
Get PRO
июнь '24
+40
в 1 каналах
Get PRO
май '24
+34
в 0 каналах
Get PRO
апрель '24
+82
в 2 каналах
Get PRO
март '24
+59
в 0 каналах
Get PRO
февраль '24
+73
в 1 каналах
Get PRO
январь '24
+47
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '23
+39
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '23
+54
в 1 каналах
Get PRO
октябрь '23
+61
в 1 каналах
Get PRO
сентябрь '23
+47
в 0 каналах
Get PRO
август '23
+50
в 0 каналах
Get PRO
июль '23
+67
в 0 каналах
Get PRO
июнь '23
+71
в 0 каналах
Get PRO
май '23
+60
в 0 каналах
Get PRO
апрель '23
+133
в 0 каналах
Get PRO
март '23
+243
в 0 каналах
Get PRO
февраль '23
+127
в 0 каналах
Get PRO
январь '23
+197
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '22
+212
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '22
+110
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '22
+98
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '22
+70
в 0 каналах
Get PRO
август '22
+76
в 0 каналах
Get PRO
июль '22
+92
в 0 каналах
Get PRO
июнь '22
+121
в 0 каналах
Get PRO
май '22
+108
в 0 каналах
Get PRO
апрель '22
+138
в 0 каналах
Get PRO
март '22
+198
в 0 каналах
Get PRO
февраль '22
+102
в 0 каналах
Get PRO
январь '22
+131
в 0 каналах
Get PRO
декабрь '21
+113
в 0 каналах
Get PRO
ноябрь '21
+91
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '21
+55
в 0 каналах
Get PRO
сентябрь '21
+57
в 0 каналах
Get PRO
август '21
+72
в 0 каналах
Get PRO
июль '21
+75
в 0 каналах
Get PRO
июнь '21
+100
в 0 каналах
Get PRO
май '21
+166
в 0 каналах
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 11 июля | +2 | |||
| 10 июля | +3 | |||
| 09 июля | +4 | |||
| 08 июля | +3 | |||
| 07 июля | +6 | |||
| 06 июля | +3 | |||
| 05 июля | +7 | |||
| 04 июля | +2 | |||
| 03 июля | +4 | |||
| 02 июля | +5 | |||
| 01 июля | +6 |
Посты канала
| 2 | አባ ጊዮርጊስ በአርጋኖን መስጋናው ‹‹ከአንድ ምንጭ ጣፋጭ እና መራራ ውኃ አይወጣም›› ይላል፡፡ ከአንድ ምላስም ምርቃት እና ስድብ አይወጣም፡፡ ምርቃት፣ በጎ ቃላት ጣፋጭ ውኃ ነው፡፡ ስድብ ግን መራራ ውኃ ነው፡፡ ዛሬ ጸሎታችን ኃይል ያጣው፣ እግዚአብሔር ፊት አልደርስ ያለው፣ ችግራችንን አልፈታ እና አላርቅ ያለው ከአንደበታችን ጣፋጭ እና መራራ ውኃ ስለምናወጣ ነው፡፡
በአንዱ ምላሳችን ጸሎት እና ስድብ ይመነጭባቸዋል፡፡ ከአንዱ አንደበታችን ምርቃት እና እርግማን ይዘንብባቸዋል፡፡ አንደበታችን አፈጣጠሩ ለምስጋና ነበር እኛ ግን በስድብ ሰይጣን የሰይጣን አፍ አደረግነው፡፡
የመንፈሰ ጽርፈት ወይም የስድብ ሰይጣን ዋነኛው ሥራው አንደበታችን፣ ልቦናችን ላይ ሆኖ ሰውን እንድንሰድብ እና እንድናዋራድ፣ ከዚያም ባለፈ አፋችንን ወደ ሰማይ እንድንከፍት ያደርገናል፡፡ የስድብ ሰይጣን ስድብን ቀስ በቀስ በቀልድ መልክ ያለማምደናል ከዚያም ከጠባያችን አዋህዶ ስድብን ጠባያችን፣ መገለጫችን ያደርገዋል፡፡ ለአንዳንዶች ስድብ የጨዋታ፣ የቀልድ የወዳጅነት የመቀራረብ እና የፍቅር መገለጫ ሊመስለን ይችላል፡፡ ይህ ለአሕዛብ እንጂ ለእኛ ለኦርቶዶክሳውያን ስድብ የሰይጣን አፍ ነው፡፡
በጣም የሚገርመው በዚህ መልኩ የስድብ ሰይጣን ውስጣችን ይገባና እኛ ዓለማዊ ሕይወቱን እና ስድቡን ትተን ጥሩ መንፈሳዊ ሰው ስንሆን ያኔ የገባው የስድብ ሰይጣን በአንደበታችን መሳደቡን ይተውና ከውስጣችን ሆኖ ወደ ሰማይ ይሳደባል፡፡
ቤተ ክርስትያን ስናስቀድስ፣ ትምህርት ስንማር፣ ጸሎት ስናደርግ ድሮ ምላሳችን ላይ ሆኖ ሰዎችን የሚሳደበው ሰይጣን ውስጣችን ሆኖ እግዚአብሔርን፣ እመቤታችንን፣ ቅዱሳን መላእክትንና ቅዱሳንን በአስደንጋጭ እና በአጸያፊ ሁኔታ እራሳችንን መቆጣጠር እስኪያቅተንና ስድቡን ከውስጥ መስማት እስኪዘገንነን ድረስ ይሳደባል፡፡ ያኔ ትርፋችን ድንጋጤ እና ጭንቀት ብቻ ይሆናል፡፡
ውስጣችን ያለው የስድብ ሰይጣን ጉዳቱ ሁለት ነው፡፡ አንደኛ የምንሰድበውን ሰው ያስጎዳናል፡፡ ሁለተኛ እኛም ሰዳቢዎቹ እንጎዳለን፡፡ ማንም ሰው ሰውን ሰድቦ፣ ሰውን አንቋሾ፣ ሰውን አዋርዶ የሕሊናና የልቦና እረፍት አይኖረውም፡፡ የሰደበው ስድብ እንደ ቤተ ክርስትያት ደውል ውስጡ ያቃጭላል፡፡
የመንፈሰ ጽርፈት ወይም የስድብ ሰይጣን ልክ እንደ ዓይነ ጥላ አደገኛ የሚያደርገው ከጠባያችን፣ ከአስተዳደጋችን ጋር ተመሳስሎ እኛኑ አህሎ ተደብቆ አድፍጦ መኖሩ ነው፡፡ እኛ ስንበሳጭ አንደበታችን ላይ ከች ብሎ ጥርግርግ አድርጎ ሰውን ያሰድበናል፡፡ ከተሳደብን በኃላ እንድንጸጸት እና እንድንቆጭ ያደርገናል፡፡ የስድብ ሰይጣን አብሮን ካደገ እና ከኖረ መንፈሳዊ ሕይወታችን መገለጫው ሰውን መተቸት፣ ሰውን ማማት፣ ሰውን መስደብ ነው፡፡
ሌላው የስድብ ሰይጣን ያለበት ሰው በፍጹም መረጋጋት አይታይበትም፡፡ መገለጫው ብስጭት፣ ግልፍተኝነት፣ ስሜታዊነት እና ነገሮችን ከአንድ አቅጣጫ ማየት ብሎም የራሱን ብያኔ መስጠት እና መሳደብ ነው፡፡ ስለዚህ ከዚህ ከመንፈጸ ጽርፈት ለመላቀቅ እግዚአብሔር ይርዳን!
ወደ መፍትሔው ስንመጣ ከዚህ ከመንፈጸ ጽርፈት ወይም ከስድብ መንፈስ ለመላቀቅ ምን እናድግር? የሚለውን ስናይ በመጀመሪያ ላንሳደብ ወስነን ንስሐ ልንገባ ይገባል፡፡ ሁለተኛ በንስሐችን ውስም የሰደብናቸውን ሰዎች አስታውሰን ልንጸጸት እና እግዚአብሔርን እና የሰደብናቸውን ሰዎችንም ይቅርታ ልንጠይቅ ይገባል፡፡
ሦስተኛ ስንጸልይ እንደ መዝሙረኛው ዳዊት ‹‹ስድብንና ነውር ከእኔ አርቅ›› እያልን መጸለይ ይገባናል፡፡ /መዝ 119÷22/ አራተኛ ስድብ የሰይጣን መሆኑንና የሚያሳድበን መንፈሰ ጽርፈት ወይም የስድብ ሰይጣን መሆኑን ልንረዳ ይገባል፡፡ አምስተኛ እራሳችንን እና አንደበታችንን መግዛት ይገባናል፡፡
ስድስተኛ አንደበታችን ላይ ሆኖ የሚሳደበውን የስድብ ሰይጣን በስግደት እና በመቁጠሪያ መቀጥቀጥ፡፡ ሰባተኛ መንፈሰ ጽርፈት አንደበታችን ላይ ሆኖ ሰው እንዳይሳደብ በጌታችን፣ በእመቤታችን፣ በቅዱሳን መላእክት እና በቅዱሳን ስም ማሰር መገዘት እና በአባቶች ማሳሰር እና ማስገዘት፡፡
ይህንን የማናደርግ ከሆነ ግን ሰውን እየተሳደብን ሺ ብንሰግድ፣ ሌሊቱን በሙሉ ስንጸልይ ብናድር፣ ብንዘክን ብንመጸውት፣ ብናስቀድስ ቅዱስ ቁርባን ብንቀበል በነፍሳችን ላይ ገሃነመ እሳትን እያወጅን እንጂ መንፈሳዊ ሕይወትን እየኖርን እንዳይመስለን፡፡ በመንፈሳዊ ምግባር የምንሰበስበውም በረከት፣ በመንፈሰ ጽርፈት፣ በስድብ አንደበት፣ በስድብ ሰይጣን እየበተንነው እንደሆነ ልናውቅ ይገባል፡፡
ቅዱስ ያዕቆብ ‹‹አንደበትም እሳት ነው፡፡ አንደበት በብልቶቻችን መካከል ዓመፀኛ ዓለም ሆኖአል፤ ሥጋን ያሳድፋልና፣ የፍጥረትንም ሩጫ ያቃጥላል፣ በገሃነምም ያቃጥላል›› ያለው ትምህርት ብቻ ሳይሆን ትልቅ ማስጠንቀቂያም ነው፡፡ /ያዕ 3÷6/
ስንቱን በእሳት አንደበታችን አቃጥለናል? አንደበታችን ለስንቶቻችን የዓመፃ ዓለም ሆኖብናል? ስድባችን ስንት ጊዜ አንደበታችንን አሳድፏል? ወለላይቱ እመቤት ከመንፈሰ ጽርፈት ትጠብቀን!
‹‹አሁን ግን እናንተ ደግሞ ቁጣንና ንዴትን ክፋትንም፣ ከአፋችሁም ስድብን የሚያሳፍርንም ንግግር እነዚህን ሁሉ አስወግዱ›› /ቆላስ 3÷8/ | 70 |
| 3 | "ከአንደበትህ የተነሳ ትጸድቃለህ ከአንደበትህ የተነሳ ትኮነናለህ"
ተወዳጆች ሆይ ስለ ስድብ ስናነሳ ብዙዎቻችን በአንድም በሌላ ሰውን እንሰድባለን፡፡ ስድብ ለሰዎች ጥላቻችንን፣ መጥፎነታችንን የምንገልጽበት ነው፡፡ ግን ስንቶቻችን ነን መንፈሰ ጽርፈት ወይም የስድብ ሰይጣን እንዳለ የምናውቀው? ስንቶቻችን ነን አንደበታችን ላይ የስድብ ሰይጣን ተቀምጦ ሰውን እንደሚሰድብ የምናውው? ስንቶቻችን ስለ መንፈሰ ጽርፈት ወይም ስለ ስድብ ሰይጣን እውቀቱ እና መጽሐፍ ቅዱሳዊ መረጃ ያለን? የሚያሳዝነው ደግሞ ስድብ ጠባያችን መገለጫችን የሆንን ሰዎች መንፈሳዊ መሆናችን ነው፡፡
መንፈሳዊ ሰው ሰውን ይመርቃል እንጂ አይሳደብም፡፡ መንፈሳዊ ሰው በጎ ቃላት እንጂ ስድብ ከአንደበቱ አይወጣም፡፡ እንኳን ልንሳደብ ለሚሰድቡን የስድብ መልስ እንድንሰጥ ጌታ አላዘዘንም፡፡ የተባልነው ‹‹ክፉን በክፉ ፈንታ ወይም ስድብን በስድብ ፈንታ አትመልሱ በዚህ ፈንታ ባርኩ እንጂ›› ነው፡፡ /1ኛ ጴጥ 3÷9/
ሰይጣን አጋንንት ለርኩሳን መናፍስት የወል ስማቸው ቢሆን ከሰይጣንም ስድብን ብቻ ተግባራዊ የሚያስደርግ የሚያሳድብ ሰይጣን አለ፡፡ ይህ የስድብ ሰይጣን አንደበቱ ላይ የተቀመጠበት ሰው ከውስጡ አውጥቶ ሰውን ይሰድባል፡፡
መንፈሰ ጽርፈት ወይም የስድብ ሰይጣን ያለበት ሰው ሰዎችን በሁለት መልኩ ይሳደባል፡፡ አንደኛው ከላይ እንዳልኩት ከሰውጣችን ወደ ውጭ አውጥተን ሰዎችን በመጥፎ እና በአጸያፊ ቃላት እንድንሳደብ ሲያደርገን፤ ሁለተኛው ውስጣችን ሆኖ በአንደበታችን ቃላት ሳያወጣ ከውስጣችን ሆኖ በልባችንን እና በአእምሮአችን ሰዎች እንድንሳደብ ያደርጋል፡፡
ለሰይጣን ከተሰጠውን አንዱ ክፉ ነገር ስድብ ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ በራዕዩ ‹‹ታላቅንም ነገርና ስድብን የሚናገርበት አፍ ተሰጠው›› ብሎ አስቀምጦልናል፡፡ /ራዕይ 13÷5/ ስለዚህ አንድ ሰው ሰውን የሚሳደብ ከሆነ በተዘዋዋሪ ሳይሆን በቀጥታ የሰይጣን አፍ ተሰጠው ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም ስድብ የተሰጠው ለሰይጣን ነውና፡፡ የሚገርመው ለሰይጣን ስድብ ብቻ ሳይሆን የስድብ ስምም ነው የተሰጠው፡፡ በራዕይ 13÷1 ላይ ‹‹በቀንዶቹም ላይ አሥር ዘውዶች በራሶቹም ላይ የስድብ ስም ነበረ›› ይለናል፡፡
እኛስ አንደበታችን ላይ የስድብ ስም የለም? ተሳድበት ያለ ስም ስም የሰጠነው የለም? ተሳድበን ስድባችን ለሰዎች ስማቸው እስከመሆን የደረሰ የለም? ተሳድበን ለሰዳቢ አሳልፈን የሰጠነው የለም? ዮሐንስ በራዕዩ ላይ ‹‹በራሶቹም ላይ የስድብ ስም ነበረ›› እንዳለ በእኛም ምላስ ላይ እጅግ ዘግናኝ፣ ቀፋፊ፣ አጸያፊ እንኳን የመንፈሳዊ የዓለማዊ ሰው መገለጫ የማይሆን የስድብ ስም አለብን፡፡
የሚያሳዝነው ብዙዎቻችን ስድብን እንደ ቀላል እያየን እየተሳደብን ስድባችን ለገሃነመ እሳት እንደሚዳርገን አለማወቃችን ነው፡፡ ጌታችን ‹‹ወንድሙን ጨርቃም የሚለው ሁሉ የሸንጎ ፍርድ ይገባዋል፤ ደንቆሮ የሚለውም ሁሉ የገሃነመ እሳት ፍርድ ይገባዋል›› ይላል፡፡ /ማቴ 5÷22/
እዚህ ላይ ልብ ልንለው የሚገባን ነገር ሰውን መስደብ በጌታ ፊት ለሸንጎ ፍርድ እና ለገሃነመ እሳት ፍርድ እንደሚያቆም ነው፡፡ ሰው በስድብ ኃጢአት ብቻ ገሃነመ እሳት ሊገባ እንደሚችል ልብ ይሏል? ምክንያቱም ሕንጻውን መናቅ መሃንዲሱን መናቅ እንደሆነ ሁሉ ሰውንም መስደብ እግዚአብሔርን መስደብ ነውና፡፡
መዝሙረኛው ዳዊት ‹‹ነፍሴ ስድብን ተሞልታለችና፣ ለሥጋዬም ጤና የላትምና›› እንዳለ የስንቶቻችን ነፍስ ከበረከት ይልቅ በስድብ ተሞልታለች? የሚገርመው መዝሙረኛው ዳዊት በዚህ ኃይለ ቃል ሰው ሰውን ሲሰድብ ነፍሱ በስድብ እንደምትሞላ እና ለሥጋውም ጤና እንደማይኖረው ነው የገለጸው፡፡ /መዝ 38÷7/
ወዳጆቼ መንፈሰ ጽርፈት ወይም የስድብ ሰይጣን እጅግ በጣም ክፉና ደፋር መንፈስ ነው፡፡ ችግሩ የስድብ ሰይጣን እኛ ላይ ሆኖ መሳደቡን አለማወቃችን ነው፡፡ ትእግስተኛው ኢዮብ ያ ሁሉ የመከራ እና የፈተና ዶፍ ሲዘንብበት ነገሮችን የተቆጣጠራቸው በትእግስት ነበር፡፡
ታዲያ መንፈሰ ጽርፈት ወይም የስድብ ሰይጣን ኢዮብ በፈተናና በመከራው ውስጥ ሆኖ እግዚአብሔርን ሲያመሰግን ተምቶ፣ የሚስቱ ምላስ ላይ ተጎልቶ ፈትኖት ነበር፡፡ የኢዮብ ሚስት ላይ የተቀመጠው የስድብ ሰይጣን በሚስቱ ላይ አድሮ ‹‹እስካሁን ፍጹምነትህን ይዘሃልን? እግዚአብሔርን ስደብ እና ሙት›› አለው፡፡ /መጽሐፈ ኢዮብ 2÷9/
እጅግ ከባዱ ነገር የስድብ ሰይጣን ሰውን ብቻ ተሳድብን እንድናስቀይምና እንድናሳዝና ሳይሆን አንደበታችን ላይ ሆኖ እግዚአብሔርን፣ ድንግል ማርያምን፣ ቅዱሳን መላእክትንና ቅዱሳንን እንድንሳደብ እና በነፍሳችን እንድንጎዳ የሚያደርገን ክፉ መንፈስ ነው፡፡ እኛ ተሳደብን ማለት ሰይጣን እኛ ላይ ሆኖ አፉን ከፈተ ማለት ነው፡፡ ይህንንም ቅዱስ ዮሐንስ በራዕዩ ላይ ‹‹እግዚአብሔርንም ለመሳደብ ስሙንና ማደሪያውንም በሰማይም የሚያድሩትን ሊሳደብ አፉን ከፈተ›› ይለናል፡፡ /ራዕይ 13÷6/
ወዳጆቼ ይሄ መናጢ የስንቶቻችን አፍ ላይ ሆኖ ሰዎችን ተሳድቦ ይሆን? የስንቶቻችን አፍ ላይ ሆኖ እግዚአብሔርን እና ማደሪያዬ ያላቸውን ቅዱሳንን ተሳድቦ ይሆን? ሰይጣን ለክፋት እረፍት ስለሌለው ጌታችንን በአይሁድ፣ በፈሪሳውያን እና በሰዱቃውያን አንደበት ላይ ሆኖ ሲሰድበው ነበር፡፡ ዛሬም በእኛ አንደበት ላይ ሆን ፈጣሪን እና ፍጡራንን ይሰድባል፡፡
ብዙዎቻችን መንፈሰ ጽርፈት ወይም የስድብ ሰይጣን መቼ እንደተጠናወተን አናውቅም፡፡ መሳደብ ደስ ስለሚለን የምንሳደብ፣ ስንበሳጭ የምንሳደብ እየመሰለን ሰይጣን ለረጅም ዓመታት ስድብን አለማምዶን ጥሩ ተሳዳቢ አደረገን፡፡ አንዳንዶቻንን የቤተ ክርስትያን፣ የቀኖና እና የዶግማ ጠበቃ ያደርገን እየመሰለን ልክ አይደሉም፣ ተሳስተዋል የምንላቸውን ሰዎች ከማስተማር ይልቅ የስድብ ሰይጣን አንደበታችን ላይ ተቀምጦ ሙልጭ አድርጎ ያሳድበናል፡፡ የሚያሳዝነው እና ጉዳቱ ደግሞ እኛን ልክ አስመስሎ ልክ አይደሉም ያልናቸውን ሰዎች ሰድበን እንድንኮነን ነው የሚያደርገን፡፡
ሌሎቻችንን ደግሞ ምላሳችን ላይ ጠቀምጦ አባቶችን፣ እናቶች፣ መምህራንን፣ ምዕመናንን እንድንሳደብ ያደርገናል፡፡ የስድብ ሰይጣን ያለበት ሰው አስቦ አይደለም የሚሳደበው ተሳድቦ ነው የሚያስበው፡፡ ሰው ለመሳደብ ቢያስብ በፍጹም አይሳደብም ምክንያቱም ኃጢአት እንደሆነ ያውቃልና፡፡
ነገር ግን አንደበቱ ላይ የተቀመጠው ሰይጣን ካሳደበው በኃላ ስድቡን እንደ ጽድቅ ያሳስበዋል ወይም በጸጸት ያስቆጨዋል፡፡ ሰይጣኑ ባለጌ ስለሆነ የብልግና ስድቦችን ያሳድባል፡፡ እንኳን ለሰሚው ለተሳዳቢው ጆሮ እና ነፍስ የሚቀፍ ስድብ ያሳድባል፡፡
የመንፈጸ ጽርፈት ወይም የስድብ ሰይጣን አንዱ ከሚያሳጣን ሰማያዊ መለኮታዊ ጸጋ አንዱ ቅዱስ ቁርባን ነው፡፡ መቼም ጌታችን የፈጠረውን ሰው እየተሳደብን ቅዱስ ሥጋው እና ክቡር ደሙን መቀበል አንችልም፡፡ በስድብ በተለወሰው ምላሳችን ቅዱስ ቁርባን የመቀበል መንፈሳዊ ሞራልም አይኖረንም፡፡
በምንሳደብበት አንደበታችን ቅዱስ ቁርባን ብንቀበል ጸጋ መለኮቱ ከእኛ ተነጥቆ በየነረሃው በአርምሞ በተአቅቦ ለሚኖሩት ቅዱሳን እናት አባቶቻችን ይሰጣል፡፡ ሰውን እየተሳደብን የምንጸልይ እና ቅዱስ ቁርባን የምንቀበል ከሆነ ውኃ የሌለው ባዶ ጋን ነን፡፡ ለራሳችንም ለሰውም በፍጹም አንጠቅምም አንተርፍም፡፡ | 56 |
| 4 | Нет текста... | 79 |
| 5 | «የቅዱስ ፡ ጴጥሮስ ፡ ደም ፡ በመስቀል ፡ ጽዋ ፡ ተቀዳ»
«የቅዱስ ፡ ጳውሎስ ፡ ደም ፡ ደግሞ ፡ ወደ ፡ ሰማያት ፡ ጮኸ»
#ሐምሌ_5_ቀን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሐዋርያቱን የቅዱስ ጴጥሮስንና የቅዱስ ጳውሎስን ሰማዕትነት በየዓመቱ በታላቅ ሥነ ሥርዐት ትዘክርዋለች ።
በዚች ዕለት ተጋድሏቸውን የፈጸሙት እነዚህ ሁለት ቅዱሳን አባቶች የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አእማድ ናቸው በመሠረትነት ባፀኗት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያላቸው ክብር ላቅ ያለ ነው ይህም የሆነው ለቤተ ክርስቲያን በፈጸሙት አገልግሎትና በተቀበሉት ሰማዕትነት ነው ።
ባሕረ ጥበባት ቅዱስ ያሬድ ሲመሰክር ‹ ቅዱስ ጴጥሮስ የሃይማኖት ዐለት ነው ቅዱስ ጳውሎስ ልሳነ እረፍት ነው በታወቀችው በዓላችሁ የምሕረት ዐስራታችሁን ያዙ ፤ በዚች ዕለት ለተሰየፈችው አንገታችሁ ሰላም ይሁን ፡፡ › በማለት መስክሯል ።(1ኛ ጴጥ 3 ፥18)
እደገናም ‹‹ ኢየሱስ ጴጥሮስን አለው በዚች ዐለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ የገሃነም ደጆች አይችሏትም የመንግሥተ ሰማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ ። ›› ሲል ከፈጣሪው የሰማይና የምድር ሥልጣን እንደተሰጠው መስክሯል ። እንዲሁም « የዮና ልጅ ጴጥሮስ ሆይ ደምህ በመስቀል ጽዋ ተቀዳ ፤ የጳውሎስ ደም ደግሞ ወደ ሰማያት ጮኸ » በማለት ገልጦታል ።
በመጨረሻም ቅዱስ ጴጥሮስ ከብዙ ....ተጋድሎ በውኋላም የሚሰቀልበት ሰዓት በደረሰ ጊዜ እጁን በሰንሠለት አስረው ፍርዱ ወደ ሚፈጸምበት ቦታ ሲወስዱት እንዲህ ብሎ ለመናቸው « ከጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ እኩል እንዳልሆን ራሴን ወደታች ዘቅዝቃቹ ስቀሉኝ » ብሎ ለመናቸው እነሱም እንደለመነው ራሱን ወደ ታች እግሩን ወደ ላይ አድርገው ዘቅዝቀው ሰማእትነት እንዲቀበል አድርገውታል ።
#ቅዱስ_ጴጥሮስ ጌታ በባሕር ላይ ሲሄድ በእምነት የተከተለው ነው
#ቅዱስ_ጴጥሮስ በደብረ ታቦር ብርሃነ መለኮቱን በገለጠ ጊዜ ከቀድሞቹ ከያዕቆብና ከዮሐንስ ጋር ነበረ ፡፡
#ቅዱስ_ጴጥሮስ በዕለተ ዐርብ በጌታ ላይ በደረሰው መከራ ለጌታው ፍቅር ቀንቶ ማልኮስ የተባለውን የአይሁድ ጭፍሮች ባልደረባ ጆሮውን በሠይፍ የቆረጠው ነው ።
#ቅዱስ_ጴጥሮስ በትንሳኤ ሌሊት የመቃብሩን አካባቢ እየተመላለሱ ሲጠብቁ ላደሩ ቅዱሳት አንስት ምሥጢረ ትንሣኤው ሲገለጥላቸው ከመቃብሩ ውስጥ ገብቶ ትንሣኤውን ያረጋገጠ የመጀመሪያው ሐዋርያ ነው። #ቅዱስ_ጴጥሮስ ከትንሣኤውም በኋላ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ በአንድ ቀን ትምህርት ሦስት ሺህ ሕዝብ አሳምኖ ያጠመቀ ታላቅ ሐዋርያ ነው ።
#ቅዱስ_ጴጥሮስ ፈጣን ነበር ጌታ ደቀ መዛሙርቱን በፊልጶስ ቂሣርያ ‹‹ ሰዎች ማን ይሉኛል ›› ብሎ በጠየቃቸው ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ሙሴ ነው ይሉሃል ፣ ኤልያስ ነው ይሉሃል ብለው መልስ ሰጡት ፤ እርሱም ጌታ መልሶ ‹‹ እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ ›› ብሎ በጠየቃቸው ጊዜ ፈጥኖ «አንተ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ ነህ » ብሎ የመለሰለት ታላቅ ሐዋርያ ነው ።
#ቅዱስ_ጴጥሮስ የዋህ ነበር ጌታ በባሕር ላይ ሲሄድ አይቶ « ጌታ አንተስ ከሆንክ ወደ አንተ እንድመጣ አሰናብተኝ » ብሎ በባሕር ላይ በእምነት ሊሄድ የሞከረ የዋህ ሐዋርያ ነው ።
ቅዱስ ጳውሎስም ከብዙ ....ተጋድሎ በውኋላ ለሁለት ዓመት ከስድስት ወር በጨለማ ቤት ታስሮ ከቆየ በውኋላ በኔሮን ቄሳር ፊት ቀርቦ በቀኝ እጁ ከሰንሰለቱ ጋር መስቀሉን ይዞ ሳይፈራ የክርስቶስን ነገር መሰከረ ኔሮን ቄሳርም በቁጣ ቃል በሠይፍ ይገድሉት ዘንድ ፍርድ ፈረደበት ።
ቅዱስ ጳውሎስን ወደ መሰዊያው ስፍራ ሲወስዱትም በንግግሩ በአስተያየቱ ምንም ፍርኀት አልነበረበትም እንዲያውም በጦርነት ላይ ድል አድርጎ ማርኮ እየፎከረ በደስታ ወደ ቤቱ የሚመለስ ወታደር ይመስል ነበር
በመጨረሻም በ 74 ዓመት ዕድሜው በሮም ከተማ በኦስትያ መንገድ አንገቱ ተሰይፎ በ 67 ዓ.ም #ሐምሌ_አምስት_ቀን በሰማዕትነት ዐረፈ።
#ቅዱስ_ጳውሎስ ለእውነትና ላመነበት ነገር ይሉኝታ ፍርኃት የሌለበት ደፋር
#ቅዱስ_ጳውሎስ ለጊዜው በሚሆነው ንቁ ለወደፊቱም አሳቢና ጠርጣሪነበር
#ቅዱስ_ጳውሎስ መጻሕፍትን ለማንበብና ለመተርጎም መልእክትን ለመጻፍና የሰውን ልብን በፍቅር ለመሳብ ሁሉንም ለመምሰልና ደስ ለማሰኘት ከመንፈስ ቅዱስ ሥጦታ ነበረው ።
#ቅዱስ_ጳውሎስ ለድንገተኛ ነገር ምላሽ መስጠት የሚችልና ንግግር አዋቂ ነበር ።
©✎﹏ዳዊት ተስፋዬ | 87 |
| 6 | Нет текста... | 211 |
| 7 | ባለፈው ከAI ጋር ካደረግሁት ውይይት፡ ከረሳኋቸው ነጥቦች መካከል፡ አንዱ ትዝ አለኝ።
"ምዕራቡ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች በሥልጣን መዋቅር ውስጥ እንዳይኖሩ የሚፈልገው ለምንድነው?" ስለው፡ ከመለሰልኝ መልሶች መካከል አንዱ "corrupt ለማድረግ አይመቹም" የሚል ነበረ።
በገንዘብ በደንብ ሊባልጉ የቻሉ በርካቶች እንዳሉና እንደነበሩ፥ አሁንም በብዛት እንዳሉ ግልጽ ስለኾነ፡ ይኽንኑ ነጥብ እንዲያብራራልኝ ጠየቅሁት።
በረዣዥም ማብራሪያዎቹ ውስጥ ደጋግሞ ያሰመረበት ነጥብ ምን መሰላችሁ? "ኦርቶዶክስ ባለሥልጣናትን (ወይም በማናቸውም ደረጃ ያሉ ኦርቶዶክስ የኾኑ ውሳኔ ሰጪዎችን)፡ የፈለገ በገንዘብ ደልሎ ለጥፋት ማሠማራት ቢቻል፡ የኾነ ሰዓት ላይ፡ አንዳች ሊበጥሱት የማይችሉት የአገር ፍቅር ስሜት ይመጣባቸውና፡ እንደታዘዙት፡ አገራቸውን ጨርሰው አሳልፈው ለመስጠት ይቸግራቸውና፡ እንቢተኞች እየኾኑ ይመጣሉ። ስለዚህ፡ የተባለውን ኹሉ ለመፈጸም፡ ከኢትዮጵያዊ ታሪኩ፥ ከእምነቱ፥ ከባሕሉ የተቆራረጠ ( 'completely detached' የኾነ) ሰው፡ ምዕራቡ በየመዋቅሩ ይፈልጋል" አለኝ።
አይገርምም?
ምንም እንኳ "Google AI can make mistakes. Please double-check responses" እያለኝ ቢመልስም፡ AI እንኳ፡ በዚህ ደረጃ ዐውቆናል። የምዕራቡን አካኼድም እንዲህ በግልጽ ይናገራል።
ይኽ ምን ያኽል common knowledge እንደኾነ ታዘቡ!
እኔ፡ በዚህ ምላሹ ትዝ ያለኝ፡ የበላኤ ሰብ ታሪክ ነው። በውሳኔ ሰጪ መዋቅር ውስጥ ያለ አንድ ኦርቶዶክስ፡ የፈለገ ባሕሪው ማስኖ እንደበላኤ ሰብ 78 ሰው "ቢበላ"፡ የማርያም ስም ሲጠራ ሲሰማ፡ "እሷንስ በልጅነቴ ስሟ ሲጠራ ሰምቻለሁ፤ ደግ ፍጥረት ናት" ብሎ፡ አገራዊ ነገሮችን ለማትረፍ ይሞክራል እንደማለት ነው።
ንቡረ እድ ኤርምያስ ከበደ ወልደ ኢየሱስ እንዲህ ይሉ ነበር፦ "የትም ኼደን አልለቅ የሚለን፡ በደማችን ውስጥ ሠርጾ ያለው፡ ልናብራራው የማንችለው የአገር ፍቅር ስሜት፡ ለእመቤታችንና ለልጇ ያለን ጥልቅ ፍቅር ነጸብራቅ ነው" ይሉ ነበር።
አእምሯችን በብዙ የሐሰት ፕሮፓጋንዳዎች ቢወናበድም፡ ነፍሳችን ግን፡ ይኽን ጥልቅ እውነታ ታውቀዋለች።
በርቱ ጽዮናውያን! | 212 |
| 8 | ወንድማችን 5000 ብር አስገብቷል እግዚአብሔር ያክብርልኝ። ሌሎቻችሁም ቤተሰቦቼ ባቻላችሁት መጠን ትንሽ ነው ትልቅ ነው ሳትሉ ያላችሁን በመስጠት የበረከቱ ተካፋይ ሁኑ። በርቱልኝ እግዚአብሔር ሁላችንንም ያግዘን። | 181 |
| 9 | https://t.me/Online24_VPN_bot?start=_tgr_3JLjwo9lYWQ0 | 216 |
| 10 | ውድ ቤተሰቦቼ እንዴት ናችሁ መዝሙረ ተጋበዙልኝ የእህታችንን ዘማሪት ዊንታ አጽብሐ መዝሙር ገብታችሁ ሁላችሁም አዳምጡ!! https://youtu.be/qFpM2Hdu83w | 233 |
| 11 | Нет текста... | 222 |
| 12 | "አባት አገር"? ወይስ "እናት አገር?"
* * *
ብዙ ጥንታዊ የአውሮፓ፣ የዐረብ፣ እና የእስያ አገራት፡ አገራቸውን ለመጥራት፡ "አባት አገር" ("Fatherland") የሚለውን አገላለጽ ይጠቀማሉ። ለምሳሌ፦ የግሪኮ-ሮማን አገራት፥ የስካንዲኔቭያን አገራት፣ ጀርመንና ኦስትርያ፣ የእንግሊዝ ደሴቶች፣ የዐረብ አገራት፣ ወዘተ...። "አባት አገር" የሚሉት፡ ብዙውን ጊዜ፡ መሪውንና ተዋጊውን ክፍል (Imperial class) ለማመልከት ነው። እነዚህ፡ ማን እንደሚኖርና ማን እንደሚሞት የመወሰን አምባ ገነናዊ ሥልጣን ያላቸው ፈላጭ ቆራጮች ናቸው። የፈለጉትን ይነጥቃሉ፤ የፈለጉትን ተጠርጎ እንዲገደል ይወስናሉ፤ የፈለጉትን ይወርሳሉ፥ ያሥራሉ፥ ይፈታሉ። ሕግ አይገዛቸውም። በሕዝባቸው ላይ ብቻ ሳይኾን፡ በገዛ ልጆቻቸው ላይ ሳይቀር ጨካኞች ናቸው።
አብዛኞቹ የአፍሪካ አገራት ደግሞ፡ "እናት አገር" ("Motherland") የሚለውን አገላለጽ ይጠቀማሉ። መሬቲቱን፥ የተፈጥሮ ሀብቶቿንና ሕዝቧን ለማመልከት ነው። በታሪክ፣ በባሕልና በደም ትሥሥር ላይ ያተኩራሉ። ከእስያም፡ ሕንድ፣ ቻይና እና አንዳንድ ትናንሽ ደሴቶችና አገራት፡ ይኽን የ"እናት አገር" አገላለጽ ይጠቀማሉ።
አንዳንድ አገራት ደግሞ፡ በተለይ በቅርብ ክፍለ ዘመናት፡ በ"Romantic" ሥነ-ጽሑፍ ዘይቤ ምክንያት፡ ኹለቱንም አገላለጽ ይጠቀማሉ። ለምሳሌ፦ ፈረንሳይ፣ ጣልያን፣ የላቲን አሜሪካ አገራት፣ ወዘተ...
ጥቂቶች ደግሞ፡ በዘመን ኺደት፡ በተለያዩ ፖለቲካዊ ምክንያቶች፡ "ከአባት አገር" ወደ "እናት አገር" አገላለጽ ከመጡ በኋላ፡ "ኹለቱም አያስፈልግም" በማለት፡ "አገር ቤት" (Homeland) የሚል አገላለጽ ይጠቀማሉ። ለምሳሌ፦ እንግሊዝ፣ አሜሪካ እና ሩሲያ ('ሶቭየት ኅብረት' ትባል በነበረችበት ጊዜ)።
* * *
ብዙዎቹ የ"እናት አገር" አገላለጽ ተጠቃሚዎች ታድያ፡ የ"እናት አገር" ተወካይ የኾኑ እንስት ገጸ ባሕሪዎችን ያመጡት፡ ከሴት ጣዖታት ነው። ለምሳሌ፦ Britannia, Mother India... "አባት አገር" የሚለውም አጠራር፡ በብዛት ጣአዖታዊ መሠረት አለው።
ነገር ግን...!
ከኹሉም አገራትና ሥልጣኔዎች፡ በመጽሓፍ ቅዱሳዊ የነገረ መለኮት ትምህርት የተደገፈ፣ በጣም የጠነከረ እና በዘመናት ውስጥ ያልተለዋወጠ "የእናት አገር" አጠራርን ይዛ የዘለቀችው፡ ኢትዮጵያ ስትኾን፡ የሕንደኬ (Kandake)፡ ማለትም የንጉሥ እናት ("Queen Mother") ምስልን ይዛ በሰው ሕሊና ስለተቀረጸች፡ ሌሎች የአፍሪካ አገራትን፡ በዚያ መልክ፡ የእናትነትና የጽዮንነትን ሥነ ልቦና አሳድራባቸዋለች ("Mother Africa", "African Zion")። ይኽም፡ ቀድሞ የመጀመሪያዋ "ሕንደኬ" በኾነችው በንግሥተ ሳባ፡ በምድር ላይ በይፋ ተገልጦ፡ በመጨረሻዋና በዋናዋ የንጉሥ እናት፡ በቅድስት ድንግል ማርያም መወለድና የአገሪቱ ባለዐሥራት መኾን ምክንያት፡ "እናት አገር" የሚለው አገላለጽ፡ የመጨረሻውን የጸና ዘለዓለማዊና ሰማያዊ ፍጻሜ አግኝቷል።
ይኽ የአጠራር ምርጫ፡ የጠለቀ የወንጌል ቃል ድጋፍም አለው። ንጉሡ ኢየሱስ ክርስቶስ፡ በወንጌል ለደቀ መዛሙርቱ፡ እንዲህ ብሎ ተናግሯልና፦
"አባታችሁ አንዱ፡ እርሱም የሰማዩ ነውና፡ በምድር ላይ ማንንም 'አባት' ብላችሁ አትጥሩ።" (ማቴ 23፥ 9)
"...እናንተ ኹላችሁ ወንድማማቾች ናችሁ። " (ማቴ 23፥ 8)
በኢትዮጵያውያን ሥነ ልቦና፡ የአገር መሪ "አባት" አይባልም። ምክንያቱም፡ አባትየው ሰማያዊ ነው። "በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ..." ብላችሁ ጸልዩ የተባልነው ለዚያ ነው። "አባት" የሚለው ቃል፡ በምድር ጥቅም ላይ ከዋለ፡ በሐዋርያዊ ቅብብሎሽ ሕዝቡን በወንጌል ለሚወልዱ የሃይማኖት አባቶች ብቻ ነው። የእግዚአብሔርን ገጽ ስለምናይባቸው።
ከዚያ ውጪ፡ የአገር መሪ ወይም ተዋጊው ክፍል፡ "አባት" ሳይኾን፡ "ባል" ወይም "እጮኛ" ይባላል። "ዐፄ" ማለትም አንዱ ትርጉሙ፡ "እጩ፥ የታጨ" ማለት ነው፤ የክርስቶስ ምሳሌ ነው። አገሪቱ ደግሞ "ለእግዚአብሔር የታጨች ድንግል መሬት" ትባላለች።
የባል ሥራው መውደድ ነው። ሚስቱን እስከሞት ሊወድዳት ይገባል። ሌሎች ሲሰድቧት፡ እሱ ሊከላከልላት ይገባል። ሌሎች "ድኃ፣ ገልቱ፣ መልከ ጥፉ" ቢሏት "ተዉአት! የኔ ድኃ ናት! እኔ ወድጄ ባገባኋት፡ እናንተን ምን አገባችሁ?" ብሎ ጠላቶቿንና ምቀኞቿን ሊያሳፍራቸው ይገባል። ምክሩንና ተግሣጹን በጓዳ አድርጎ፥ በአደባባይ ግን፡ ስድቧን፥ ኀፍረቷንና መሸማቀቋን ዘወር አድርጎላት፡ በፍቅር ኃይል ለውጦ፡ ለርሱ ብቻ የሚታየውን ድብቅ ውበቷንና የታፈነ እምቅ ችሎታዋን እንድታወጣ ሊያበረታታት ይገባል። "አንቺ'ኮ አልቻልሽበትም እንጂ፡ እንዲህ እንዲህ ያለ በጎ ነገር አለሽ" ሊላት ይገባል። የባል ሥራ፡ ሌሎች የማያዩትን መልካም ነገር በርሷ ውስጥ ማየት መቻል ነው፤ ከርሷ ጋር የማይኼዱ ሞኝነቶቿንና ስንፍናዎቿን ደግሞ እንድታስወግድ ማንቃት ነው። መጀመሪያውኑ ያያት፥ ያጫትና ወድዶ ፈቅዶ ያገባትም ለዚያ ነው።
የአገር መሪም፡ መኾን ያለበት እንደዚያው ነው። "ይኽቺ ድኃ፥ የተረት ተረት አገር፥ የተረገመች አገር፥ የጨለማ አገር፥ የሦስት ሺህ ዓመት ችጋር" የሚሉ ቡድኖች ወደሥልጣን ሲመጡ ያስደነገጠኝ ለዚያ ነው። የተደበቀ ውበቷን ካላዩ፡ እንዴት ያወጡታል? ነፍሷን ያወጡታል እንጂ! ወንድ የሚጠላትን ሴት ማግባት የለበትም። ይገድላታል። አልያም በብስጭት ራሷን አንቃ፥ ወይ መርዝ ጠጥታ ትሞታለች። ወይም ብን ብላ ከአገር ትጠፋለች፤ ወይም ከባሏ ጋር ስትጣላና ስትፈነካከት ትኖራለች።
* * *
"የእናት አገር" ነገር ጥልቅ ነው። እግዚአብሔር፡ ቅድስት ድንግል ማርያምን ለእናትነት ሲመርጣት፡ ማንም ምድራዊ ሰው ያላየውን የውስጣዊ ውበቷን ጥልቀት፡ እርሱ ስላየ ነው።
"ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን ያባትሽንም ቤት እርሺ፤ ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና።" (መዝ 44፥ 10-11)
ሌላው ቀርቶ፡ እርሷ ራሷ እንኳ፡ የራሷን ማንነት ምን ያኽል የከበረ መኾኑን አላወቀችውም። መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል፡ "የእግዚአብሔርን ልጅ ትወልጃለሽ፤ እርሱም ለዘለዓለም ይነግሣል" ሲላት፡ "ይኽ እንዴት ይኾናል?" አለች እንጂ።
ኢትዮጵያንም ያልተረዱ፥ እንደ እጮኛ በተለየ የፍቅር ዓይን የማያዩአት፥ ማንም ያላየውን መንፈሳዊ ውበቷን ያላወቁ፥ በመንፈስ ቅዱስም ሥውር መንፈሳዊ ሀብቷ ያልተገለጸላቸው፡ ሊመሯት አይችሉም። "ልምራ" ቢሉም፡ በምድር ላይ "አባትሽ ካልኾንኩ" ይሏትና ትቸገራለች። ከሰማያዊው አባት ጋር ያላት ግንኙነት ላይ ደንቃራ ይኾኑባታል። "ቄሣር ቄሣር ካልተጫወትን" ብለው ያስቸግሯታል። እንደ እጮኛዋ ዮሴፍ የድንግልናዋ ጠባቂ፥ የመከራዋ ተካፋይ፥ የልጇ ሞግዚት መኾን ያቆሙና፡ እንደሄሮድስ ወይም እንደፈሪሳውያን "ያ ጎረምሳ ልጅሽ የታለ? ለሥልጣናችን ሥጋት ኾኖ አስቸግሮናል፥ አውጪው!" እያሉ ሊገድሉት ያስጨንቋታል። እናም፡ በዘመናዊው ዓለም፡ ለጣዖታዊ "አባቶች" ልጇን አሳልፈው ይሰጡባታል። የሴት ልጆቿንም ድንግልና ይሸጡባታል። እነሱም የምሥጢር ማኅበራትና የglobalization መዋቅራቸው ነው። የነርሱ አባት ደግሞ "ዲያቢሎስ" ይባላል።
ደግነቱ ዲያቢሎስ ልጇን ገድሎትም አላሸነፈውም! በመስቀሉ ድል ኾነ! ገድሎ መሸነፍ የዲያቢሎስ ዕጣ ፈንታው ነው!
* * *
ከዲያቢሎስ አባትነት ይሠውረን፤ የእግዚአብሔርን አባትነት ይመልስልን!
እግዚእ - ጌታ
አብ - አባት
ኄር - ቸር
ቸር አባት ጌታ እርሱ ይምራን! | 202 |
| 13 | ሐምሌ ፪ /2/
በዚች ቀን ከዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት የአንዱ ሐዋርያ የቅዱስ ታዴዎስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው።
ይህንንም ሐዋርያ ከዐሥራ ሁለቱ ጋራ ጌታችን አስቀድሞ መረጠው አጽናኝ መንፈስ ቅዱስ በላያቸው በወረደ ጊዜ ወደ አገሮች ወጥቶ የወንጌልን ትምህርት አስተማረ ከአይሁድና ከአረማውያን ብዙዎቹን ወደ ፈጣሪያቸው እግዚአብሔር መልሶ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው።
አንድ ቀንም ወደ ሶርያ ከተማ ሲጓዝ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መልኩ በሚአምር ጐልማሳ አምሳል ለእርሱ ተገልጦ ወዳጄ ታዴዎስ ቸር አለህን አትፍራ እኔ ከአንተ ጋራ እኖራለሁና አለው ሰላምታም ሰጥቶት ከእርሱ ዘንድ ዐረገ።
ይህም ሐውርያ ብዙ ድንቅ ተአምራትን አድርጓል። እህል በአንድ ቀን ዘርቶ በአንድ ቀን አድርሷል። አንድ ባለጸጋም ሊፈትነው ፈልጎ ግመልን በመርፌ ቀዳዳ አሳልፈህ አሳየን ሲለው በእግዚአብሔር ተራዳይነት ግመሉን በመርፌ ቀዳዳ አሳልፏል። በብዙ አገሮችም ውስጥ ገብቶ ሰበከ ከአይሁድና ከአረማውያንም መከራ ደረሰበት። ከዚህም በኋላ በሰላም አረፈ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ሐዋርያ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
💚 @ortodoxmezmur 💚
💛 @ortodoxmezmur 💛
❤️ @ortodoxmezmur ❤ | 190 |
| 14 | Нет текста... | 229 |
| 15 | ከተዋሕዶ እምነት ውጪ ያሉ ኹሉም እምነቶች፡ ተዋሕዶን የሚከስሱበት ነጥብ፡ "የ3000 ዓመት ድህነት" ሲኾን፡ ራሳቸውን የሚቆልሉበት ነጥብ ደግሞ "ሀብት" ነው። እነርሱ ሀብታም ባይኾኑ እንኳን፡ የነርሱ እምነት የተፈለሰፉባቸውን ቦታዎች እየጠሩ በሀብታቸው ይመጻደቃሉ። ካቶሊኩ በካቶሊክ አገራት ሀብትና ሥልጣኔ ይመጻደቃል። ሙስሊሙ በዐረብ አገራት ሀብት ይመጻደቃል። ፕሮቴስታንቱ በፕሮቴስታንት አገራት ሀብት ይመጻደቃል። አይሁዱ፡ እስራኤል በአጭር ጊዜ አንሠራርታ አገር በመኾኗና በጦር ሥርዓቷ ወዘተ ይመጻደቃል። በጥንቆላና በመተት ያለው ደግሞ፡ መጀመሪያም ገንዘብ አምላኩ መኾኑን ያመነና በድርጊቱም ያጸደቀ፡ የነዚህ ኹሉ ተመጻዳቂዎች ዋና role model ነው።
የሚገርመው ነገር ግን፡ ኢየሱስ ክርስቶስ፡ ደግሞ ደጋግሞ በሐዲስ ኪዳን የተናገረው፡ የድኆች አምላክ መኾኑን፥ ገንዘብ የእግዚአብሔርን ቦታ የሚገዳደር ዋና ጣዖት መኾኑን፥ ሀብታም ወደ መንግሥተ ሰማያት ከሚገባ፡ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢሾልክ የሚቀል መኾኑን፥ ዲያቢሎስ የዓለሙ ገዢና የሀብቷና የገንዘቧ ዘዋሪ መኾኑን ወዘተ ነው። እርሱ የሚሰጠው ስጦታ የበለጠውን የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ እንደኾነና፡ ገንዘብ ከስጦታዎቹ ኹሉ መጨረሻ ላይ የሚመጣ በጣም ቀላሉና የማያሳስበው "ዳረጎት" እንደኾነ በተለያዩ መንገዶች በግልጽ ተናግሯል። ዲያቢሎስ፡ የእግዚአብሔር የኾኑትን፡ በማጣትና በድህነት ይፈትናል። እግዚአብሔር ደግሞ፡ በማጣትና በድህነት ውስጥ ቀርቶ፡ በሞትም ውስጥ ሙላት እንዳለ እያሳየ፡ የዲያቢሎስን ውሸት እያፈረሰ ያስተምራቸዋል።
በተዋሕዶ እምነትና በሌሎች እምነቶች መካከል ያለውን ልዩነት ባሰብኩት ቁጥር፡ በጣም በጣም የሰማይና የምድር ያኽል የተራራቀ ይኾንብኛል። በሌሎች እምነቶች መካከል ያለውን ልዩነት ስመረምረው ደግሞ፡ ልዩነታቸው ከሸረሪት ድርም የቀጠነ ይኾንብኛል። መሠረታቸው፣ ሥሪታቸውና አስተሳሰባቸው አንድ ነው። ኹሉም ፍጹም ዓለማዊ ናቸው።
ተዋሕዶ ብቻ ሰማያዊት እምነት ናት።
ሌላው ሙሉ ለሙሉ ከስሯል!
"ሰው ዓለሙን ኹሉ ቢገዛ፡ ነፍሱን ግን ቢያጣ፡ ምን ይረባዋል? ሰውስ ለነፍሱ ቤዛ ምንን በሰጠ ነበር?" (ማቴ 16፥ 18) | 251 |
| 16 | #የሕሊና_ጸሎት
ጌታዬና መድኃኒቴ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ፤ ከሁሉ አስቀድሜ ስለ እስትንፋሴ አመሰግንሃለሁ። ይህች አየር ወደ ሳንባዬ ስትገባና ስትወጣ ያንተን ስም በምስጢር እንድትጠራ እርዳኝ። በእያንዳንዱ ትንፋሼ ውስጥ አንተን ማሰብን ስጠኝ። አእምሮዬ እንደ ባዘነ ወፍ ከቦታ ቦታ ሲባክን፣ አንተ በቸርነትህ ወደ ሰላምህ ጎጆ መልሰው። አምላኬ ሆይ፤ ካንተ ውጭ የምታስበው ነፍስ ሰላም የላትምና፣ በሕሊናዬ ዙፋን ላይ አንተ ንገሥ። በሥራዬ መካከል ሳለሁ አብረኸኝ ሥራ። እጆቼ ቁሳቁሱን ሲነኩ፣ ልቤ ግን ያንተን ቅድስና ይንካ። በድካሜ መካከል ብርታት፣ በውጤቴ መካከል ደግሞ በረከት ሁነኝ። ስሠራ አብረኸኝ ሥራ፤ ያለ አንተ ረዳትነት ድካሜ ሁሉ ከንቱ ነውና። በላቤ ውስጥ ያንተን ምሕረት፣ በጥረቴ ውስጥ ደግሞ ያንተን ፈቃድ እንዳይ እርዳኝ።
አቤቱ፥ በሕይወት መንገድ ስጓዝ አንተ መሪ ሁነኝ። የትኛው መንገድ ወደ አንተ እንደሚወስደኝ አላውቅምና፣ እንደ ብርሃን መብራት ከፊቴ ቅደም። ስሄድ መንገዱን ምራኝ፤ ስደክም ምርኩዝ ሁነኝ። ሕይወት በከበደችኝና ጉልበቶቼ በዝሉ ጊዜ፣ የማልወድቅበት ጽኑ ዓለት ሁነኝ። በፈተና አረንቋ ውስጥ እንዳልሰጥም እጅህን ዘርግተህ ያዘኝ። ጌታ ሆይ፤ በምድራዊ ሕይወቴ ግዴታዎች ቢበዙብኝም፣ እነዚያ ግዴታዎች ከአንተ ጋር እንዳያጋጩኝ ጠብቀኝ። ምድራዊ ስኬቴና ባለጠግነቴ አንተን እንዳያስረሳኝ አጥር ሁነኝ። በሰው ፊት ከፍ ስል በልቤ ውስጥ አንተን ዝቅ እንዳልል ሰውረኝ። ስም ስገኝ ስምህን፣ ሀብት ስገኝ ባለቤቱን እንዳልረሳ የትሕትናን ልብስ አልብሰኝ። ዓለም በውሸት ውበቷ ስታታልለኝ፣ አንተ እውነተኛው ውበቴ መሆንህን አስታውሰኝ።
በሰዎች መካከል ስሆን ፍቅርህን እንድገልጥ ርዳኝ። አንደበቴን ከሐሜት፣ ዓይኖቼን ከክፋት፣ ልቤን ከምቀኝነት ጠብቅ። ብቻዬን በሆንኩበት ሰዓት ደግሞ፣ የሰዎችን ጫጫታ ትቼ ያንተን ቅድስና እንድናፍቅ አድርገኝ። በብቸኝነቴ ውስጥ ሙላቴ፣ በዝምታዬ ውስጥ ቃል ሁነኝ። በምንም ሰዓት፣ በምንም ሁኔታ አንተን ከመዘንጋት ሰውረኝ። ሕይወቴ ሁሉ ያንተ መታሰቢያ ይሁን። አቤቱ፤ ጸሎቴን እንደ መዓዛ እጣን ተቀበልልኝ። በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት፣ በቅዱሳን መላእክትና በጻድቃን ሁሉ ጸሎት ልመናዬን ስማኝ። አእምሮዬን ቀድሰህ፣ ልቤን አሳርፈህ፣ ሕይወቴን ባርከህ እስከ መጨረሻው አጽናኝ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር። አሜን። | 282 |
| 17 | "ብርቱው አምላኬ መድኃኔዓለም ሆይ፤ ጠላት ዲያብሎስ በሕሊናዬ ውስጥ የጥርጣሬን፣ የጭንቀትንና የትዕቢትን ዘር ሊዘራ ሲመጣ አንተ ጋሻ ሁነኝ። ሐሳቤ በፈተና ማዕበል እንዳይናወጥ በሃይማኖት ዓለት ላይ አጽናኝ። ጌታ ሆይ፤ አእምሮዬን በሚያውኩኝ ክፉ ምስሎችና ትዝታዎች ፋንታ፣ ያንተን ትሕትናና ፍቅር ሙላበት። በውስጤ ያለው የጨለማ ሠራዊት በቃልህ ብርሃንነት ይበተን። ነፍሴን ካንተ የሚለይ ሐሳብ በፊቴ ሲቆም፣ በመስቀልህ ኃይል በትነው።" | 253 |
| 18 | Нет текста... | 249 |
| 19 | "የዘላለም ብርሃን የሆንክ አምላኬ ሆይ፤ አእምሮዬን በአንተ ቅድስና ማኅተም አትመው። ዛሬ በልቤ መቅደስ ውስጥ አንተን ደስ የማይያሰኝ ሐሳብ እንዳይሰፍር ጠባቂ ሁነኝ። ሕሊናዬን እንደ ዕጣን መሠዊያ አድርገውና ምስጋናዬ ወደ አንተ ይውጣ። ጌታ ሆይ፤ በዓይኖቼ ስመለከት ያንተን ድንቅ ሥራ እንድታይ፣ በጆሮዎቼ ስሰማ ያንተን ድምፅ እንድለይ፣ በአንደበቴም ስናገር ያንተን እውነት እንድመሰክር ጸጋህን አልብሰኝ። በውጭ ሳይሆን በውስጤ አድረህ አስተምረኝ።" | 227 |
| 20 | "ያህዌ ይርኤ (አቅራቢው እግዚአብሔር) ሆይ፣ ባለሁበት የኑሮ መጣበብና እጥረት ውስጥ የሚያስፈልገኝን መውጫና በረከት አንተ አዘጋጅልኝ። አማኑኤል (እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው) ሆይ፣ በዚህ አስቸጋሪ ዘመን ብቻዬን እንዳልሆንኩ አሳየኝ፤ በነገሬ ሁሉ አብረኸኝ ሁን። ይህንን ሁሉ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እለምናለሁ፣ አሜን።" | 290 |
