አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ
በዚህ የንጽጽር አደባባይ በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክታት የተገለጸው እውነት ሲፈጸምና ይፈጸም ዘንድ በመላው ዓለም ሲንቀሳቀስ የሚከሰቱ ጉዳዮችን እናቀርባለን ! ስለእምነታችን እንማማራለን ! ስለመልዕክታቱ እንነጋገራለን ! ➝ ይህ የአልፋና ዖሜጋ ( @christian930 ) ገጽ ቅርንጫፍ የንጽጽርና የመማሪያ ገጽ ነው።
Show more4 376
Subscribers
-424 hours
+367 days
+11230 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
Show all...
የእመቤታችን ማርያም ኃዘን
ዓርብ ዘጠኝ ሰዓት የሚነበብ
❤ 13
✥ ••┈•┈•• ✞ ••┈•┈•• ✥
#ዘበእንቲአሃ_ለቤተክርስቲያን_ተጸፋእከ በውስተ ዐውድ ከመ ትቀድሳ በደምከ ክቡር ዘበእንቲአሃ ዝግሐታተ መዋቅሕት ፆረ ወተዐገሰ ምራቀ ርኩሰ እንዘ አልቦ ዘአበሰ #አምላክ_ዲበ_ዕፀ_መስቀል_ተሰቅለ።
❮ትርጉም❯
#ለቤተክርስቲያን_ብለህ
ልትቀድሳት በደምህ በአደባባይ በጥፊ ተመታህ።
ንጹሕ ክርስቶስ በአዳም ጥፋት ልትወቀስ በከንቱ ልትከሰስ አመላለሱህ ከጲላጦስ ወደ ሄሮድስ ሁሉን ቻይ ሳለህ ምንም ማድረግ ሳይሳንህ በአይሁድ እጅ ተገረፍህ!
ወዮ! ወሰን ለሌላት ትዕግስት ስለኛ ብለህ መከራ ተቀበልህ ምንም በደል ሳይኖርብህ አምላክ በእንጨት መስቀል ላይ ሰቀሉህ።
#ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ
❤ 20👍 5
Repost from ቅድስት በርባራ ዘኒቆመዲያ Saint BarBara Αγία Βαρβάρα
#በግብረ_ሕማማት ውስጥ የሚገኙ #እንግዳ_ቃላት_እና_ትርጉማቸው፦
በግብረ ሕማማት ውስጥ ወደ ግእዝም ሆነ በኋላ ወደ አማርኛ ሳይተረጎሙ የተቀመጡ የዕብራይስጥ፣ የቅብጥ እና የግሪክ ቃላት ይገኛሉ፡፡ የእነዚህ ቃላት ትርጉም የሚከተለው ነው፡፡
#ኪርያላይሶን፦
ቃሉ የግሪክ ሲሆን አጠራሩ "ኪርዬ ኤሌይሶን" ነው፡፡ "ኪርያ" ማለት "እግዝእትነ" ማለት ሲሆን "ኪርዬ" ማለት ደግሞ "እግዚኦ" ማለት ነው፡፡ ሲጠራም "ኪርዬ ኤሌይሶን" መባል አለበት፡፡ ትርጉሙ "አቤቱ ማረን" ማለት ነው፡፡ "ኪርያላይሶን" የምንለው በተለምዶ ነው፡፡ ይኼውም ኪርዬ ከሚለው "ዬ" ኤላይሶን ከሚለው ደግሞ "ኤ" በመሳሳባቸው በአማርኛ "ያ" ን ፈጥረው ነው፡፡
#ናይናን፦
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ "መሐረነ፣ ማረን" ማለት ነው፡፡
#እብኖዲ፦
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ "አምላክ" ማለት ነው፡፡ "እብኖዲ ናይናን" ሲልም "አምላክ ሆይ ማረን" ማለቱ ነው።
#ታኦስ፦
የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙ "ጌታ፣ አምላክ" ማለት ነው፡፡ "ታኦስ ናይናን" ማለትም "ጌታ ሆይ ማረን" ማለት ነው፡፡
#ማስያስ፦
የዕብራይስጥ ቃል ሲሆነ ትርጉሙ "መሲሕ" ማለት ነው፡፡ "ማስያስ ናይናን" ሲልም "መሲሕ ሆይ ማረን" ማለት ነው
#ትስቡጣ፦
"ዴስፓታ" ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም ደግ ገዥ ማለት ነው።
#አምነስቲቲ_ሙኪርያ_አንቲ_ፋሲልያሱ፦
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም "ተዘከረነ እግዚኦ በውስተ መንግሥትከ- አቤቱ በመንግሥትህ አስበኝ" ማለት ነው፡፡
#አምንስቲቲ_ሙዓግያ_አንቲ_ፋሲልያሱ፦
የቅብጥ ቃል ሲሆን "ተዘከረነ ኦ ቅዱስ በውስተ መንግሥትከ ቅዱስ ሆይ በመንግሥትህ አስበን" ማለት ነው፡፡
#አምንስቲቲ_ሙዳሱጣ_አንቲ_ፋሲልያሱ፦
የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም "ተዘከረነ እግዚአ ኩሉ በውስተ መንግሥትከ የሁሉ የበላይ የሆንክ ሆይ በመንግሥትህ አስበን" ማለት ነው፡፡
▰ ▰ ▰
❤ 16👍 5
Repost from አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ
#የሕማማት_አርብ
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
#_ዕለተ_ስቅለት
❨የድኅነት ቀን❩
#_አምነስቲቲ_ሙኪርያቱ_አንቲ_ፋሲልያሱ!
{ኦ እግዚኦ በመንግሥትኽ በመጣኽ ጊዜ አስበን}
#_ስገዱ_ጸልዩ_አልቅሱ ስለ ነፍሳት ኹሉ!
••┈•┈••
የወልድን መከራውን የሚናገር ምን አፍ ነው፧ ምን ከንፈር ነው፧ ምን አንደበት ነው፧ የፍቍር የጌታ ሕማማት በተነገረ ጊዜ፥ ልብ ይለያል፤ ኅሊናም ይመታል፤ ነፍስም ትንቀጠቀጣለች፤ ሥጋም ይደክማል። #_የማይሞተው_ሞተ! ሞትን ይሽረው ዘንድ ሞተ! ሙታንን ያድናቸው ዘንድ ሞተ! [ቅዳሴ ዘዮሐንስ አፈወርቅ]••┈•┈•• ▸ አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ | t.me/Ewnet1Nat
👍 4