en
Feedback
شـبـاب السـلــفـــيـــيــن

شـبـاب السـلــفـــيـــيــن

Open in Telegram

👉«ሰለፍያ ቀጥተኛ የሀቅ መንገድ ብሎም አይነኬ ፅኑ ተራራ ነው።» ለአስተያዬትና እርማት

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel شـبـاب السـلــفـــيـــيــن

Channel شـبـاب السـلــفـــيـــيــن (@nuredinal_arebi) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 29 138 subscribers, ranking 2 505 in the Religion & Spirituality category and 1 172 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 29 138 subscribers.

According to the latest data from 23 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -158 over the last 30 days and by -3 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 15.73%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.75% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 584 views. Within the first day, a publication typically gains 2 549 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 50.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
👉«ሰለፍያ ቀጥተኛ የሀቅ መንገድ ብሎም አይነኬ ፅኑ ተራራ ነው።» ለአስተያዬትና እርማት

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 24 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

29 138
Subscribers
-324 hours
+257 days
-15830 days
Posts Archive
ለሚፆሙ ሁሉ ጠቃሚ ማስታወሻ❗️ ~ የአላህ መልእክተኛ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለምእንዲህ ብለዋል፡- ❝ሱሁርን መብላት በረካ አለው፤ ስለዚህ ከእናንተ አንዳችሁ አንዲት ጉንጭ ውሃ እንኳን ቢሆን ሳይጎነጭ
ለሚፆሙ ሁሉ ጠቃሚ ማስታወሻ❗️ ~ የአላህ መልእክተኛ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለምእንዲህ ብለዋል፡- ❝ሱሁርን መብላት በረካ አለው፤ ስለዚህ ከእናንተ አንዳችሁ አንዲት ጉንጭ ውሃ እንኳን ቢሆን ሳይጎነጭ እንዳይተወው። ምክንያቱም አላህና መላኢካዎቹ ሱሁር በሚበሉ ሰዎች ላይ ሰለዋት ያወርዳሉ (ዱዓ ያደርጋሉ)።❞ (ሐሰን - ሰሒሕ አል-ጃሚዕ፡ 3683) t.me/AbuSufiyan_Albenan t.me/AbuSufiyan_Albenan

📨السلام عليكم ورحمة الله وبركاته ✅የቁርኣን ኽትሚያ ፕሮግራም እና ሙሀደራ 💎📚የእህታችን ሰዓዳ ኡሙ ሁዘይፋ📖 ✅የፊታችን ቅዳሜ ✅ 🖼ተጋባዥ ኡስታዞቻችን 🎙ኡስታዝ አቡ ሂበ
📨السلام عليكم ورحمة الله وبركاتهየቁርኣን ኽትሚያ ፕሮግራም እና ሙሀደራ       💎📚የእህታችን ሰዓዳ ኡሙ ሁዘይፋ📖          ✅የፊታችን ቅዳሜ ✅    🖼ተጋባዥ ኡስታዞቻችን 🎙ኡስታዝ  አቡ ሂበቲላህ حفظه الله           ↬🔖  ርእስ በሰዓቱ ይነገራል 🎙ኡስታዝ አቡ ፋሩቅ حفظه الله         ↬🔖 ርእስ በሰዓቱ ይነገራል 🎙ኡስታዝ  ጀማል ሰይድ حفظه الله       ↬ 🔖 ርእስ በሰዓቱ ይነገራል 🎙ወንድማችን አቡ ዑበይዳ  حفظه الله        ↬📩 ርእስ በሰዓቱ ይነገራል 🎙ኡስታዝ አቡ ሹራ حفظه الله     ↬📩 ርእስ በሰዓቱ ይነገራል    ፕሮግራሙ የሚጀመረዉ ሰዓት          ⏰በኢትዮ 🇪🇹 3-30 ሰዓት          ⏰ በስኡድ 🇸🇦 9-30 ሰዓት         ⏰በኢማራት 🇦🇪 10-30 ሰዓት ነዉ 🎙ፕሮግራሙን የሚመራው ወንድማችን አቡ ዓብዲረሂም  ሀፊዘሁላህ ↣የሚተላለፍበት ቻናል ሸር አድርጉት ባረከላሁ ፊኩም ጆይን እያሉ ይቀላቀሉ ቤተሰብ ይሁኑ       ↶↶⇲↶⇊↶↶↶↶⇊⇊ https://t.me/abuabdirehim https://t.me/abuabdirehim

❍ ذكر الإمام ابن رجب الحنبلي في كتابه النفيس لطائف المعارف أنَّ كثيراً من سلفنا الصالح كانوا يحبذون الصوم في شدَّة الحر، (فلقد وصَّى عمر - رضي الله عنه - عند موته ابنه عبد الله فقال له: عليك بخصال الإيمان، وسمى أولها: الصوم في شدة الحر في الصيف.." 📚لطائف المعارف لابن رجب (٣٢٨) ❍ وذكر أيضا في لطائف المعارف: عن ابن عمر - رضي الله عنهما – أنَّه خرج في سفر معه بعض أصحابه فوضعوا سفرة لهم، فمر بهم راع، فدعوه إلى أن يأكل معهم فقال: «‏إني صائم، فقال ابن عمر: في مثل هذا اليوم الشديد حره وأنت بين هذه الشعاب في آثار هذه الغنم وأنت صائم؟! فقال: أُبادر أيامي هذه الخالية. »​​ 📚لطائف المعارف لابن رجب (٣٢٣). فأجر الصيام عظيم ولكنه في شدة الحر يكون أعظم أجرا. ☚ فاحرص أيها المسلم على صيام عاشوراء اتباعا لسنة المصطفى ﷺ واحتساباً للأجر والمثوبة، وضمّ إليه التاسع مخالفة لأهل الكتاب، واقتداءً بهدي النبيﷺ وأصحابه رضي الله عنهم. ⚘ "فطوبى لمن جوَّع نفسه وأظمأها، وترك شهوةً حاضرة لموعد غيبٍ لم يره، وطوبى لمن ترك طعامًا ينفد في دارٍ تنفد، لدارٍ ﴿أُكُلُها دائِمٌ وَظِلُّها﴾". فالدنيا كله شهر صيام المتقين، وموسم عمل لهم ويوم عيد فطرهم يوم يلقون ربهم جل وعلا، فيفوزون برضوانه وجناته. أسأل الله أن يوفقني وإياك لصيام عاشوراء إيمانًا واحتساباً، وأن يتقبل منا جميعا صالح الأعمال، وأن يجعلني وإياك من عباده المتقين الفائزين. t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

📢 #أيها_الموفق: احرص على صيام يوم عاشوراء واعتنِ به عنايةً عظيمةً، فإ شأنه كبير وفضله وأجره وثوابه عند الله عظيم. وقد كان نبينا وقدوتنا محمد ﷺ يتحرى صيامه، ويحث عليه ويعتني به عناية عظيمة؛ لما فيه من الأجر الجزيل والثواب العظيم. ❒ سُئِلَ ابنَ عباسٍ -رضي الله عنهما- عن صيامِ يومِ عاشُورَاءَ، فقال: «ما عَلِمْتُ أنَّ رسولَ اللهِ -ﷺ- صامَ يومًا يَطلُبُ فَضْلَهُ على الأيامِ إلَّا هذا اليومَ، ولا شهرًا إلَّا هذا الشَّهرَ» يعني: رمضانَ. 📚 رواه البخاري برقم: (2006) مسلم برقم: (1132) واللفظ له. ولفظُ البخاري: «ما رأيتُ النبيَّ -ﷺ- يتحرَّى صيامَ يومٍ فضَّله على غيرِه إلا هذا اليومَ، يومَ عاشوراءَ، وهذا الشهرَ»، يعني: شهرَ رمضان. ❒ وعن ابن عباس - رضي الله عنهما- قال قال رسول الله ﷺ (لئن بقيت إلى قابلٍ لأصومنَّ اليومَ التاسع. ) قال أبو علي رواه أحمد بن يونس عن ابن أبي ذئب زاد فيه مخافة أن يفوته عاشوراء. 📚 سنن ابن ماجه ( ٣/٢١٦), رقم: (١٧٣٦). ❒ فعن ابن عباس رضي الله عنهما قال: "لما صام رسول الله ﷺ يوم عاشوراء وأمر بصيامه، قالوا: يا رسول الله إنه يوم تعظمه اليهود والنصارى، قال: (فإذا كان العام المقبل إن شاء الله صمنا اليوم التاسع،) قال فلم يأت العام المقبل حتى توفي رسول الله ﷺ. " 📚 صحيح مسلم (٧٩٧/٢)، رقم: (١١٣٤) ❁ وكان الصحابي الجليل عبد الله بن عباس- رضي الله عنهما- يصوم اليومين ( التاسع والعاشر) ويوالي بينها تحقيقا لسنة النبيﷺ في مخالفة أهل الكتاب، واحتياطا مخافة فوات الأجر؛ وحتى يتيقن إدراك فضل يوم عاشوراء. ❍ عن ابن عباس - رضي الله عنهما- "أنه كان يصوم يوم عاشوراء في السفر ويوالي بين اليومين مخافة أن يفوته" 📚 مصنف ابن أبي شيبة - (٢٣٥/٦) ❍ قال الإمام ابن رجب - رحمه الله - "وكان طائفة من السلف يصومون عاشوراء في السفر منهم ابن عباس وأبو اسحاق والزهري وقال: رمضان له عدة من أيام أخر وعاشوراء يفوت ونص أحمد على أن يصام عاشوراء في السفر." 📚 لطائف المعارف لابن رجب (٥٢) ❍ كان الإمام الزهري يصوم عاشوراء في السفر فعن أبي جبلة قال: "كنتُ مع ابن شهابٍ في سفرٍ، فصام يومَ عاشوراءَ، فقيل له: تصومُ يومَ عاشوراء في السّفر، وأنت تُفطرُ في رمضانَ؟ قال:إنّ رمضانَ له عِدّةٌ من أيّام أُخر، وإنّ عاشوراء يفوتُ" 📚شعب الإيمان للبيهقي (٣٣٥/٥)، رقم: (٣٥١٨), التّمهيد لابن عبد البر(٧/ ٢١٥)، ☑️ وأكثر من الصوم في شهر الله المحرم: ❒ عَنْ ‌‏أَبِي هُرَيْرَةَ ‌‏رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ ‌‏قَالَ : ‏قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ‌‏ﷺ ‏: ‏«أَفْضَلُ الصِّيَامِ بَعْدَ رَمَضَانَ شَهْرُ اللَّهِ الْمُحَرَّمُ » 📚 أخرجهُ مسلمٌ (١١٦٣) . ❍ قال الإمام ابن باز -رحمه الله-: «‏الشهر كله، وإذا ما صامه كله وصام العاشر والتاسع أو العاشر والحادي، كله خير إن شاء الله.»​​ 📚 فتاوى الدروس, الموقع الرسمي. 🌱 وجاء في الترغيب في الصوم مطلقاً، وما جاء في فضله: ❒ عن سهلِ بنِ سعدٍ رضي الله عنه- عن النَّبِيِّ ﷺ قَالَ:« إِنَّ فِي الجَنَّة بَابًا يُقَالُ لَهُ: الرَّيَّانُ، يدْخُلُ مِنْهُ الصَّائمونَ يومَ القِيامةِ، لاَ يدخلُ مِنْه أَحدٌ غَيرهُم، يقالُ: أَينَ الصَّائمُونَ؟ فَيقومونَ لاَ يدخلُ مِنهُ أَحَدٌ غَيْرُهُمْ، فإِذا دَخَلوا أُغلِقَ فَلَم يدخلْ مِنْهُ أَحَدٌ» 📚 متفقٌ عَلَيْهِ. البخاري (١٨٩٦)، مسلم (١١٥٢). ❒ قال النبي ﷺ: «من صام يوماً في سبيل الله بعَّد الله وجهه عن النار سبعين خريفاً» 📚متفق عليه. البخاري(٢٨٤٠)، مسلم (١١٥٣). ⚘وثواب الصيام في الحر الشديد عظيم.. 🔹وكان الصحابي الجليل أبو سعيد الخدري - رضي الله عنه - ينتقي اليوم الشديد الحرارة للصيام لأجل هذا الحديث. ❒ عَنْ أَبي سَعيدٍ الخُدْريِّ رضي الله عنه قال: قالَ رسولُ اللَّهِ: «مَا مِنْ عبْدٍ يصُومُ يَومًا في سبِيلِ اللَّه إِلاَّ باعَدَ اللَّه بِذلك اليَومِ وجهَهُ عَن النَّارِ سبعينَ خرِيفًا » 📚 متفقٌ عليه. البخاري (٢٨٤٠)، مسلم (١١٥٣). ❒ وعن أبي الدرداء - رضي الله عنه- قال: قال رسول الله ﷺ: «‌‎من صام يومًا فى سبيلِ اللهِ ؛ جعل اللهُ بينه وبين النارِ خندقًا كما بين السماءِ والأرضِ .» 📚 وأخرجه جامع الترمذي في "جامعه" (٥٢٢/١)، رقم: (١٦٢٤)، من حديث أبي أمامة الباهلي- رضي الله عنه. ✅ صححه الإمام الألباني في صحيح الترغيب (٥٠١/١)، رقم: (٩٩٠-٩٩١). ❒ عن حذيفة بن اليمان رضي الله عنه قال: قال النبيَّ ﷺ «من صام يومًا ابتغاء وجه الله خُتم له به دخل الجنة.. » 📚رواه الإمام احمد في المسند (٣٥٠/٣٨) رقم: (٢٣٣٢٤). ✅ صححه الإمام الألباني في صحيح الترغيب والترهيب (٥٧٩/١)، رقم: (٩٨٤). ❍ يقول الصحابي الجليل أبو ذر الغفاري- رضي الله عنه-: (صوموا يوماً شديداً حره لطول يوم النشور وصلوا ركعتين في سواد الليل لوحشة القبور). 📚 حلية الأولياء (١٦٥/١)

👉የውሳኔ ሰው እንሁን‼️ ✅ተነሽ ወስኝ‼️ ✅ተነስ ወስን‼️ የወሰንሽውን መኖር ጀምሪ በቃ ወስኝ ማግባት ትፈልጊያለሽ አይደል በቃ አግቢ ለመቼ ነው ቀጠሮሽ ...መውለድ ትፈልጊያለሽ አይደል በያ (የ
👉የውሳኔ ሰው እንሁን‼️ ✅ተነሽ ወስኝ‼️ ✅ተነስ ወስን‼️ የወሰንሽውን መኖር ጀምሪ በቃ ወስኝ ማግባት ትፈልጊያለሽ አይደል በቃ አግቢ ለመቼ ነው ቀጠሮሽ ...መውለድ ትፈልጊያለሽ አይደል በያ (የወሊድ መቆጣጠሪያ ምን ይሆንሻል።) በቃ የምታስቡትን መኖር ጀምሩ ወደዳችሁም ጠላችሁም በሰከንድ ቅፅበት ተፈላጊነታችሁ እየረከሰ የምትፈልጉት ከእናንተ ይበልጥ እየራቀ ይሄዳል ። 🔥 ወንድሜ ታሪክህን ለመቀየር የአንድ ቅጽበት ውሳኔ ይበቃልኮ በጌታህ ተመካ ከዚያ አድርገው በቃ አትግደርደር። ​በምስሉ ላይ እንደምናየው፣ የሁላችንም ጊዜ፣ ጉልበትና ወጣትነት ልክ እንደ ክብሪቱ እንጨት በየቀኑ እየነደደና እያለቀ ነው። ..... "ነገ እጀምራለሁ" እያልን የምናስተላልፈው ቀጠሮ የህይወታችንን እሳት በከንቱ እንዲበላሽ ያደርገዋል። ለውጥ የሚመጣው አሁኑኑ ሲወሰን ብቻ ነው! ​💡የዛሬው መልዕክቴ‼️ ​ጊዜህ እየነደደ ነው፦ ዛሬ በእጅህ ላይ አቅምና ብርሃን ሳለህ፣ ለህይወትህና ለወደፊት ስኬትህ ታላቅ ውሳኔን ዛሬውኑ ውሰድ። ✅​ስኬት የጋራ ነው፦ እውነተኛ ስኬት ብቻህን ጫፍ መውጣት ሳይሆን፣ ራስህ በትግል ውስጥ እያለህ እንኳ ሌሎችን የምታነሳበትና የምታበረታታበት ታላቅ መሪ መሆን ስትችል ነው። 🛑​አሁኑኑ ቁረጥ፦ ለመውደቅና ተስፋ ለመቁረጥ አንድ ሰከንድ ይበቃል... ተነስተህ አዲስ የስኬት ታሪክ ለመጻፍ ግን የአንድ ቅጽበት ጽኑ ውሳኔ አመርቂ ነው። ​ሰዓቱ ሳይረፍድ፣ እሳትህ ሳይጠፋ... ዛሬውኑ ወስነህ ተነስ እልሀለሁ። t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

«የተበደራችሁትን በሙሉ አውፍ ብያለሁ።» 👉«ቀይስ ኢብኑ ሰዕድ» .....ከእለታት አንድ ቀን ቀይስ ኢብኑ ሰዕድ ኢብኑ ዑባዳህ ..ችግር ገጠመው ይህ ታላቅ የነብዩ ሶሀባ በጠና ታመመ። ...ይህ ሶሀብይ እጂግ የናጠጠ ሀብታም ነበር ... በህመሙ ጊዜ ግን መጥተው የሚጠይቁት ሰዎች ቁጥር በጣም ቀነሰበት። 👉ይህኔ ግራ ተጋባ‼️ ✅ለምንድነው ሰዎች በብዛት መጥተው የማይጠይቁኝ ⁉️ እኔ መጥፎ ሰው ነኝ ማለት ነው ⁉️በማለት ጠየቀ‼️ 🛑ሰዎች መለሱለት፦ ➥ቀይስ ሆይ ጉዳዩ አንተ እንደምታስበው አይደለም ። ...ግና ሰዎች አንተ #ያበደርካቸውን ገንዘብ ስላልመለሱ አንተን ከመጠየቅ #ሀያዕ ይዟቸው ነው የቀሩት አሏቸው። 🛑ይህኔ የማይረሳ ቃል ተናገረ‼️ «أخزى الله مالا يمنع عنى الزوار» "ጎብኚዎች ወደ እኔ እንዳይመጡ የሚከለክል ገንዘብ የተዋረደ ይሁን አለ።" ثم أمر مناديا يصيح في المدينة »من كان لقيس عليه دين فهو في حل» (أي سامحهم جميعا) ➥#ከዚያም፦ በከተማው ውስጥ ሁሉ አንድ አዋጅ ነጋሪ እንዲጮህ አዘዘ። «ከቀይስ ገንዘብ የተበደረ በሙሉ ይቅር ብሎታል ብሎ አስነገረ። ✅ከዚያ በሚገርም መልኩ «ከዘያርተኛው ሰው ብዛት የቤቱ #ጉበን እስኪሰበር ድረስ ጠያቂው በረከተ ይላሉ።» «ለስንቶች ስንት ቢያበድር ነው አሏህ የዱንያ ፍቅር ከልቦ ወጣለትና አውፍ አላቸው።» ....ኑረዲን...✍️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

ሸይኽ አቡል ሀሰን አርራዚሂይ ከመግሪብ እስከ ኢሻ ቦሌ ጃዕፈር መስጂድ ሙሓደራ ይኖራቸዋል። ታደሙ

የዐሹራእ ጾም‼ ========== (የነብዩ ﷺ ጉጉት እና የሰለፎች ጥልቅ ማስተንተን!) || በእስልምና አስተምህሮ ውስጥ የሙሐረም ወር፣ በተለይም የዐሹራእ (የሙሐረም 10ኛ) ቀን እጅግ የላቀ ደረጃ አለው። ይህ ቀን ያለፈውን አንድ ዓመት ወንጀል የሚያስምር ታላቅ ጸጋ ነው። የዚህን ቀን ታላቅነትና ጾሙን በተመለከተ ትክክለኛ ሐዲሦችን እና የዑለማዎችን ድንቅ ንግግሮች ከነ ምንጫቸው እንመልከት፦ ❶ የነብዩ ﷺ ብርቱ ጉጉት፦ ነብዩ ሙሐመድ ﷺ ይህን ቀን ለመጾም ልዩ ጉጉት ነበራቸው። ታላቁ ሶሐባህ ዐብዱ-ል'ሏህ ኢብኑ ዐባስ ይህን የነብዩን ﷺ ጉጉት ሲገልጹ እንዲህ ይላሉ፡- «مَا رَأَيْتُ النَّبِيَّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَتَحَرَّى صِيَامَ يَوْمٍ فَضَّلَهُ عَلَى غَيْرِهِ، إِلَّا هَذَا الْيَوْمَ ؛ يَوْمَ عَاشُورَاءَ، وَهَذَا الشَّهْرَ. يَعْنِي شَهْرَ رَمَضَانَ.» «ነብዩ ﷺ ከሌላው አብልጠው የዚህን ቀን (የዐሹራእን) እና የዚህን ወር (የረመዿንን) ጾም ለመጾም እንደሚጓጉት ለሌላ ቀን ሲጓጉ አላየሁም።» 📜[ሶሒሕ አል-ቡኻሪይ፡ 2006፣ ሶሒሕ ሙስሊም፡ 1132] ❷ «ካለፈ አይመለስም!» ✅የቀደምት ሰለፎች ለዐሹራእ ጾም የነበራቸው ቦታ አስገራሚ ነበር። ታላቁ ታቢዒይ ሙሐመድ ኢብኑ ሺሀብ አዝ-ዙህሪ በጉዞ ላይ እያሉ የዐሹራእን ቀን ጾሙ። በዚህ ጊዜ ሰዎች ተገረሙና እንዲህ ሲሉ ጠየቋቸው፡- (… فقيل له: لم تصوم وأنت تفطر في رمضان في السفر ؟! فقال: إن رمضان له عدة من أيام أخر، وإن عاشوراء يفوت.) «በረመዿን ወር በጉዞ ላይ ሆነህ ጾም እየፈታህ፣ ዛሬ (በጉዞ ላይ) ለምን ትጾማለህ?» ተብለው ሲጠየቁ፤ «ረመዿን በሌሎች ቀናት (ተቆጥሮ) ቀዷ ይወጣል (ይከፈላል)፤ የዐሹራእ ጾም ግን ካለፈ ያመልጣል (ቀዷ አይወጣም)!» ብለው መለሱ።» 🛑 [ሸዕቡል-ኢማን ሊል-በይሀቂይ፡ 3518] 👉በእርግጥም የረመዿንን ጾም በህመም ወይም በጉዞ ምክንያት የፈታ ሰው በሌላ ጊዜ መክፈል ይችላል። የዐሹራእ ጾም ግን ዓመት ጠብቆ የሚመጣና ቀዷ የሌለው በመሆኑ፣ ይህ ታላቅ ምንዳ እንዳያመልጠን ሰለፎች እስከዚህ ድረስ ይጓጉለት ነበር! ❸ዓመትን በዒባዳህ መዝጋትና በዒባዳህ መክፈት! 👉 ታላቁ ሊቅ ኢማም ኢብኑ ረጀብ አል-ሐንበሊ አላህ በሰጣቸው ጥልቅ እይታ፣ የዓመቱ መጨረሻ (ዙል-ሒጃ) እና የዓመቱ መጀመሪያ (ሙሐረም) ወራት ውስጥ ስላለው ጾም እንዲህ ይላሉ፡- «من صام من ذي الحجة وصام من المحرم، فقد ختم السنة بالطاعة وافتتحها بالطاعة فيرجى أن تكتب له سنته كلها طاعة، فإن من كان أول عمله طاعه وآخره طاعة فهو في حكم من استغرق بالطاعة ما بين العامين.» «ከዙል-ሒጃ (ባለፈው ዓመት መጨረሻ) እና ከሙሐረም (በአዲሱ ዓመት መጀመሪያ) የጾመ ሰው፤ ዓመቱን በዒባዳህ (በታዛዥነት) ዘግቶ፣ አዲሱን ዓመትም በዒባዳህ ከፈተ ማለት ነው። በመሆኑም ዓመቱ ሙሉ በዒባዳ እንዳሳለፈ ይጻፍለታል ተብሎ ተስፋ ይደረጋል። ምክንያቱም የመጀመሪያውም ሆነ የመጨረሻው ስራው አላህን መታዘዝ የሆነ ሰው፣ በሁለቱ ዓመታት መካከል ያለውን ጊዜ ሙሉ በዒባዳ እንዳሳለፈ ይቆጠርለታልና።» 📚 [ለጧኢፉል መዓሪፍ ሊብኒ ረጀብ] 👉የዚህ ዓመት የዐሹራእ ጾም ቀናት! ነብዩ ﷺ ዐሹራእን ጾመው፣ ከአይሁዶች ለመለየት ሲሉ ቀጣዩ ዓመት ከደረሰ 9ኛውንም ቀን (ታሱዓእን) አብረው እንደሚጾሙ ተናግረዋል። በመሆኑም፣ የዘንድሮውን የሙሐረም 9ኛ እና 10ኛ ቀን የጾም ቀጠሯችንን እንደሚከተለው አድርገን ይህን የዓመት ወንጀል የሚያስምር ታላቅ ጸጋ እንቋደስ፦ ታሱዓእ (9ኛው ቀን)፦ ረቡዕ፣ ጁን 24 ዐሹራእ (10ኛው ቀን)፦ ሐሙስ፣ ጁን 25 አላህ ያለፈውን ዓመት ወንጀላችንን የምንማርበት፣ አዲሱን ዓመትም በዒባዳና በኸይር የምንጀምርበት ያድርግልን! (እነዚህን ቀናት ጓደኛ እና ቤተሰባችሁ እንዳይረሱት ሼር በማድረግ የኸይር ሰበብ ሁኑ!) t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

🔖 የአሹራ ፆምን በተመለከተ..! አቡ ቀታዳ አል አንሷርይ አላህ መልካም ስራው ይውደድለትና እንዲህ አለ፦ የአላህ መልእክተኛ ﷺ ስለ አሹራ ቀን ፆም ተጠይቀው እንዲህም አሉ፦ 【ያለፈውን አንድ አመት ወንጀል ያብሳል】ብለዋል። 📚 (ሙስሊም ዘግቦታል።) ~የሚፆመዉ 10ኛዉ ቀን ሲሆን ነገር ግን አህለል ኪታቦችን ለመሀለፍ 9ኛዉ(ዘጠነኛዉን) ቀን መፆም የፈለገ  በላጩ ይህ ነዉ። ~የአሹራ ቀን ፆም የሚጀመረው ነገ እሮብ እና ሐሙስ ይሆናል ማለት ነዉ።  ዘጠንኛዉን ቀን መፆም ያልቻለ 10ኛዉ እና 11ኛዉ ቀን መፆም ይችላል። مَنْ دَلَّ عَلَى خَيْرٍ فَلَهُ مِثْلُ أَجْرِ فَاعِلِهِ }.      (ሌሎችን) ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የተገበረውን ሰው አምሳያ ምንዳ ይኖረዋል።     https://t.me/nuredinal_arebi

➤እንቅልፋችን ጠፋ.... 🔸«ህልም ፈች በዛብን»🔸 -------------------------- ከቀኙ ጎዳና ወደ ግራ ወድቀን፡ ሀሳባችን በዛ እንቅልፍ ናፈቀን፡ መቀመጥ መነሳት ሁሉም አሳቀቀን፡ መኖርም መሞትም እኩል አስጨነቀን፡ ምንም አለማድረግ እጂግ በጣም ያማል፡ ውስጥህ ሰላም ሲያጣ ሰው መሆን ይደክማል፡ -------------------------------------------- በህይወት ለመኖር ከኛ ሰላም ጠፋ፡ ውሰደን ለማለት ወንጀላችን ከፋ፡ ቃል ከተግባር ጋራ ልዩነቱ ሰፋ፡ ህሌናችን ዝሎ አካል ሲደነድን፡ ከማየት ቦዝኖ አይናችን ሲከድን፡ ማስተዋል ሲሳነን ነፍስ ስቶን በድን፡ ጣታችን አይናችን ሲዝሉ በቡድን፡ መተኛት ስናቅድ እንቅልፍን አስበን፡ ጎን ምድር ሲይዝ አንድት ትራስ ስበን፡ እንቅልፋችን ጠፍቶ በሀሳብ ዘመቻ፡ ከሰው ተለይተን ሆነን ለየብቻ፡ ቋጠሮ ሰብስበን ቀልቀሎ ስልቻ፡ የእቅድ ፈረስ ጋልበን በተስፋ ኮርቻ፡ እንደዚህ ሆነናል ያሳዝናል ብቻ‼️ .....ይደክማልኮ..ጃል..!! ስንት ቀን ቆይተን ድካም ሲበረታ፡ ስጋና አጥንታችን መንፈስም ሲረታ፡ አረፍ ያልን እንደሆን ለትንሽ ቆይታ፡ እንሔዳለን በህልም ወደ ሆነ ቦታ፡ በቃ እንዲህ ነው ህይወት እንድህ ነው መኝታ!! ከዚያ እንነሳለን በፍርሀት ደንግጠን፡ ሰላማችን ጠፍቶ ተጨናንቀን ቀልጠን፡ የምንይዘው ጠፍቶን በስጋት ተንጠን፡ ለኔ ዘመን ወጣት ይሔ ነው መሰልጠን፡ ከዛ ያየውን ጉድ ይናገራል ሔዶ ፡ ላላፊው ላግዳሚው በነገር ተዛምዶ፡ ዜና ያሰራጫል እስከ ባህር ማዶ፡ ፍቹን የሰማ ቀን ይሆናል በረዶ፡ ከቀናት በኋላ ይታሰራል አብዶ‼️ ....በቃ ይሔው ነው!! ያዬነውን ትተው ባልታዬ ሲመሩን፡ ሁላችን ተስማማን መደነጋገሩን፡ በቅዠት ሀገር ውስጥ ህልም ፈቹ በዝቶ፡ ሰላም እየራቀን መርሀችን ባዝቶ፡ ታጥቆ እየፎከረ አንዱ ባንዱ ዝቶ፡ ለተወሰነ እድሜ እቅዳችን ሰፍቶ፡ ሳንተኛ እናድራለን እንቅልፋችን ጠፍቶ፡ .....በኑረዲን አል-ዓረብ..✍️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

ካነበብኳቸው ውብ ነገሮች አንዱ፦ ----------------------------- ➥«የመለያየት ስቃይ የሚገባው ለተከበረች ነፍስ ብቻ ነው።» ✍️ፀሀፊው እንዲህ ይላል፡- በመለያየት የሚነኩት የሚተክዙ
ካነበብኳቸው ውብ ነገሮች አንዱ፦ -----------------------------
➥«የመለያየት ስቃይ የሚገባው ለተከበረች ነፍስ ብቻ ነው።»
✍️ፀሀፊው እንዲህ ይላል፡- በመለያየት የሚነኩት የሚተክዙትና የሚያስቡት የተከበሩ ነፍሶች ብቻ ናቸው ። ➥አህያ ከፈረስ ጋር ብታስሩትና ከዚያም ብታለያዩዋቸው ምን እንደሚፈጠር አስባችሁታል? በመለያየታቸው #አህያው አይነካም አያዝንም በቃ ምንም አይመስለውም። ነገር ግን ፈረሱ በጣም ይናፍቃል፣በጣም ይተክዛል የመለያየትን ስቃይ የሚረዱት #የተከበረች ነፍስ ያለቻቸው ሰዎች ብቻ ናቸው። 👉ለአህዮች መለያየት ምን እንደሆነ አያውቁትምና ለነሱ ምንም ነው። ➥ስለዚህም እመክርሀለሁ አብረህ የምትሄድበትን ቦታ በቸልተኝነት በሚመለከቱ ሰዎች አትደነቅ። ➥ጓደኝነትህ ጉርብትናህ በቀለለባቸውና ዋጋህን ባላወቁት ሰዎች አትገረም። ➥«አብራችሁ ስንት ጣፋጭ ጊዜ እንዳላሳለፋችሁ ሁሉ ከተለየህ በኋላ እንደማያውቅህ በሚያደርግስ ሰው አትገረም።» የሰው ልጆች እንድህ ናቸው ልዩነቱን በፈረሱና በአህያው አነፃፅረው ። 🛑አልገባኝም እንደማትል ተስፋ አለኝ‼️ ....ኑር... t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

ከሰማችሁኝ መተማመን ራሱ ችግር ነው...#እውነት ቢሆን ኑሮ ውሀ አሳን ባልቀቀለው ነበር....እናማ ከቻልክ ከአሏህ በታች በራስህ ላይ ብቻ ተማመን ጀግናው...!! .....ኑር... t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

«ባለትዳሮች አስተውሉ» .....ትዳር ውስጥ ብዙ አለመግባባቶች የሚፈጠሩት አንዱ ሌላውን ለመጉዳት ስለሚፈልግ ሳይሆን የተፈጥሮ ባህሪያቸውን ስለማያውቁ ነው። ✅ለምሳሌ፦ አንዳንዴ በተለያዩ ጉዳዮች ዝም ብሎ ቢቆይ «ሚስቱ በቃ አይወደኝም» ለኔ ቦታ የለውም፣አይፈልገኝም ብላ ልትረዳው ትችላለች ....ነገር ግን ብዙ ጊዜ ይህ ችግር #ወንድ_ልጅ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ለማሰብና በትኩረት ለመመልከት ብሎም ግራ ቀኝ ለማስተዋል የሚጠቀምበት የተፈጥሮ መስመር ነው። ...«ስለሆነም ሚስት ይህንን የወንድ ልጅ የተፈጥሮ ባህሪ ልትረዳ ግድ ነው ።» ✅በሌላ በኩል #ሴቷ ደግሞ ፦ ለባሏ ያላትን ፍቅር፣ ለሱ ያላትን ስሜት ..በብዙ ቃላት ብትገልፅለት....#ባለቤቷ ብዙ ታወራለች ፣ተጨቃጫቂ ነች ብሎ ሊያስብ ይችል ይሆናል...ግና ይህ በአብዛኛው የሴትነት ገፀ-ባህሪ የተገነባበት የህይወት ዑደቴ ነውና ልንረዳ ይገባል። 🛑መፍትሔው‼️ ባል ሆይ፦ 👉ሚስትህን እንደ ወንድ አታስብ ሚስትህን እንደ ሴት ተረዳት። 🛑ሚስት ሆይ፦ 👉ባልሽን እንደ ሴት አትሰቢው ወንድ ነውና ሞራሉን ፕላኑን ፀባዩን አክብረሽ ጠብቂው። አወ የተፈጥሮ ልዩነት መረዳትን የሚጠይቅ ሐቅ እንጂ ስህተት አይደለም። t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

«ልቤ ሆይ ይቅርታ» በምን ቦታ እንዳለፍክ ስታውቀው ጠንቅቀህ፡ ስንት የሐዘን እንባን በፈገግታ ስቀህ፡ ለጠላት አታብር ወርደህ አታስንቀኝ፡ ያለፈ አልፏል ብለህ በነፃ ታረቀኝ!? .....ይቅርታ...!! ስንት ነገር ሆነህ አልተረዳሁህም፡ በተደጋጋሚ ታገስ ግደለህም፡ እያልኩኝ ዘወትር ቦታ አልሰጠሁህም፡ ስንቱን አሳልፌ አንተን በድያለሁ፡ አሁን ግን ይቅርታ ያው ተመልሻለሁ፡ ብርሀን በሌለበት በጨለማው ቦታ፡ እኔና አንተ ብቻ ጀምረን ጨዋታ፡ እንታረቅ በቃ ልቤ ሆይ ይቅርታ፡ ....ኑር t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

🎉 ቀጥታ ስርጭት የዳእዋ  ፕሮግራም    〰🎊〰🎊〰🎊〰🎊〰🎊〰 🎙በወንድም አቡ ሒበቲላህ ጀ        መ                ረ    ↷↷↷↷↷⇊🎙⇊↶↶↶↶ https://t.me/MohamedAliEdris?livestream

በጥሩነትህ እንድትቆጭ የሚያደርጉ ሰዎች! ---------------------------------------- አንዳንድ ጊዜ በሕይወት ውስጥ የሚያሳዝነው ክፉ ሰዎችን ማግኘት ብቻ አይደለም... ጥሩ ሆነህ በመኖርህ ብቻ ደጋግመው እየበደሉህ እንድትቆጭ ሲያደርጉህ ያኔ ጥሩ በመሆንህ እንድትፀፀት ይገፉሀል ቢሆንም አደራ በክፋታቸው እንዳትቀና ። ሰውን በሙሉ ልብህ ታምናለህ...!! በችግሩ ጊዜ ከጎኑ ትቆማለህ...!! ሲወድቅ ታነሳዋለህ...!! ሲያለቅስ ታጽናናዋለህ...!! ሲያጣ ታካፍለዋለህ...!! ነገር ግን አንድ ቀን ዞሮ ሲወጋህ፣ ሲክድህ፣ ሲጎዳህ ልብህ ውስጥ የሚነሳው ጥያቄ አንድ ነው...“ጥሩ መሆኔ ስህተት ነበር⁉️”የሚል የህሌና ጩኸት‼️ እና ያ ጥያቄ ከሕመሙ በላይ ያቆስላል። ምክንያቱም ክፉ ሰው ልብህን ብቻ አይጎዳም...። በሰውነትህ ያለውን ጥሩነት እንድትጠራጠር ያደርግሃል። ከዚያ በኋላ ሰውን ለማመን ትፈራለህ...!! ለመርዳት ሁለት ጊዜ ታስባለህ...!! ልብህን ለመክፈት ትቸገራለህ...!! ምክንያቱም ያለፈው ቁስል አሁንም በውስጥህ አለ። ⭕️ነገር ግን... አንድ እውነት ፈጽሞ መርሳት የለብህም። የሰዎች መጥፎነት የአንተን ጥሩነት ስህተት አያደርገውም። 👉ፀሐይ በቆሻሻ ቦታ ላይ ስለምታበራ ቆሻሻ አትሆንም። 👉ወንዝ ድንጋይ ስለሚያገኝ መፍሰሱን አያቆምም። #እንዲሁም... አንተ የተሳሳተ ሰው ስላገኘህ ጥሩ ሰው መሆንህን መተው የለብህም። ⭕️አዎ... 👉በልብህ የሚጫወቱ ሰዎች አሉ። 👉ጥሩነትህን እንደ ድክመት የሚያዩ አሉ። 👉ዝምታህን እንደ ፍርሃት የሚተረጉሙ አሉ። 👉ርህራሄህን ተጠቅመው የሚጎዱህም አሉ። ግን ችግሩ በጥሩነትህ ውስጥ አይደለም... ችግሩ ጥሩነትን ማየት በማይችል ልባቸው ውስጥ ነው። #ሕይወት_አንድ_ቀን_ታስተምርሃለች። 👉ጥሩ ሰው መሆን ማለት ሁሉንም ማመን አይደለም። ሁሉንም መታገስም አይደለም። ሁሉንም ማስደሰትም አይደለም። 👉#ጥሩ_ሰው_መሆን_ማለት... ⭕️ጥሩ ልብ እያለህ ጥበብ ያለው ድንበር ማበጀት ነው። ✅እርዳታ እየሰጠህ ክብርህን መጠበቅ ነው። ✅ፍቅር እየሰጠህ ራስህን አለማጣት ነው። ✅ሰውን እያከበርክ ራስህንም ማክበር ነው። 🛑ስለዚህ...‼️ ዛሬ በጥሩነትህ አትቆጭ። ያጋጠሙህ መጥፎ ሰዎች ጥሩነትህን እንጂ ማንነትህን አይገልጹም። አንተ የሰጠኸው ፍቅር፣ ያሳየኸው ርህራሄ፣ ያደረግኸው መልካምነት... ምናልባት በተሳሳተ ሰው እጅ ወድቆ ይሆናል። ግን ያ ማለት ዋጋ የለውም ማለት አይደለም። 👉ምክንያቱም በመጨረሻ... መጥፎ ሰዎች ጥሩነትህን ሊጎዱት ይችላሉ ይሆናል እንጂ ሊያጠፉት ግን አይችሉም። .....አንዳንድ ጊዜ የሕይወት ትልቁ ድል... መጥፎ ሰዎች ካጋጠሙህ በኋላም ጥሩ ሰው ሆነህ መቀጠል ነው ብዬ አምናለሁ። t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi