en
Feedback
شـبـاب السـلــفـــيـــيــن

شـبـاب السـلــفـــيـــيــن

Open in Telegram

👉«ሰለፍያ ቀጥተኛ የሀቅ መንገድ ብሎም አይነኬ ፅኑ ተራራ ነው።» ለአስተያዬትና እርማት

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel شـبـاب السـلــفـــيـــيــن

Channel شـبـاب السـلــفـــيـــيــن (@nuredinal_arebi) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 28 744 subscribers, ranking 2 502 in the Religion & Spirituality category and 1 181 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 28 744 subscribers.

According to the latest data from 30 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -310 over the last 30 days and by 3 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 14.87%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 7.15% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 277 views. Within the first day, a publication typically gains 2 056 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 42.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
👉«ሰለፍያ ቀጥተኛ የሀቅ መንገድ ብሎም አይነኬ ፅኑ ተራራ ነው።» ለአስተያዬትና እርማት

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 31 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

28 744
Subscribers
+324 hours
-847 days
-31030 days
Posts Archive
አለማወቅ ደፋር ያደርጋል ------------------------ አንዳንድ ጊዜ ሰው ለምን ያለ ፍርሃት ወደ አደጋ እንደሚገባ ይገርመኝ ነበር። ለምን በድፍረት ሳያስብ ውሳኔ እንደሚሰጥ፣ ለምን የማያውቀውን ነገር እንደሚያሳንስ፣ ለምን ሁሉን እንደሚያውቅ ሆኖ ያለ ጥርጥር እንደሚናገር አገርም ነበር። መልሱ ግን ከምናስበው በተቃራኒ ነው። 👉አለማወቅ ደፋር ያደርጋል። ሰው አደጋውን ካላወቀ አይፈራውም። የጉዞውን መንገድ ካላወቀ ግንባሩን ሳይደፋ ይጓዛል። ጥልቀቱን የማያውቅ ሰው ወደ ውሃው ያለ ማመንታት ሊዘል ይችላል። ከፊቱ ያለውን ገደል የማያውቅ ሰው በፍጥነት ሊሮጥ ይችላል። ምክንያቱም ፍርሃት ብዙ ጊዜ ከእውቀት ይመጣል። አደጋውን የምታውቅ ከሆነ ትጠነቀቃለህ። ውጤቱን የምታውቅ ከሆነ ታስባለህ። አማራጩን የምታውቅ ከሆነ ትመርጣለህ። እውቀት ፍርሃትን ብቻ አይፈጥርም፤ ጥንቃቄንም ይፈጥራል። አለማወቅ ግን ሰውን ከእውነታው ይለያል። የማያውቀውን ነገር ቀላል ያደርገዋል። የማይችለውን እንደሚችል ያሳምነዋል። የማይገባውን እንደገባው ያስመስላል። የሚያስፈራውን እንደማያስፈራ ያሳየዋል። ከዚህ የተነሳ አንዳንድ ሰዎች የማያውቁትን ነገር ለመናገር በጣም ደፋሮች ናቸው። ስለማያውቁት ጉዳይ ይፈርዳሉ። ስለማያውቁት ሰው ይወስናሉ። ስለማያውቁት ነገር በእርግጠኝነት ይከራከራሉ። እውቀት ያለው ሰው ግን አንዳንድ ጊዜ ይቆማል። 👉"ምናልባት አላውቅም።" 👉"ምናልባት ተሳስቻለሁ።" 👉"በቂ መረጃ የለኝም።" 👉"በመጀመሪያ ልመርምር።" ይላል። ይህ ድክመት አይደለም። ይህ የእውቀት ትልቁ ምልክት ነው። እውነተኛ ብልህነት ሁሉን እንደምታውቅ መናገር አይደለም፤ የማታውቀውን መለየት መቻል ነው። ሰው የማያውቀውን ሲያውቅ የሚጀምረው እውነተኛ ጥንቃቄ ነው። እናም አንድ ነገር ልብ በል። አለማወቅ ደፋር ያደርጋል፤ እውቀት ግን ያስተውላል። የማያውቅ ሰው ወደ አደጋ ሊሮጥ ይችላል። የሚያውቅ ሰው ግን ከመሮጡ በፊት መንገዱን ይመረምራል። የማያውቅ ሰው በቀላሉ ይፈርዳል። የሚያውቅ ሰው ግን ጥያቄ ይጠይቃል። የማያውቅ ሰው በእርግጠኝነት ይናገራል። የሚያውቅ ሰው ግን እርግጠኛ ባልሆነበት ጊዜ ዝም ማለትን ያውቃል። ስለዚህ ከማናውቀው ነገር ጋር በድፍረት ከመጋፈጣችን በፊት እንጠይቅ። "ምን አላውቅም?" ይህንን ጥያቄ መጠየቅ ከፍርሃት የበለጠ የጥበብ መጀመሪያ ነው። እውቀት አንዳንድ ጊዜ ያስፈራል፤ ምክንያቱም የምናምንባቸውን ነገሮች እንድንመረምር ያስገድደናል። ነገር ግን ያ ፍርሃት የሚጠቅመን ፍርሃት ነው። ምክንያቱም እውቀት ወደ ጥንቃቄ ይመራል፤ ጥንቃቄ ደግሞ ከብዙ ስህተቶች ያድናል። ስለዚህ ሁሉን እንደምታውቅ አትቸኩል። ስለማታውቀው ጉዳይ ድምፅህን ከፍ ከማድረግ በፊት እውቀትህን አሳድግ። 👉ስለማታውቀው ሰው ከመፍረድህ በፊት ሁኔታውን ተረዳ። ወደማታውቀው መንገድ ከመግባትህ በፊት መንገዱን ጠይቅ። ምክንያቱም... አለማወቅ ደፋር ያደርጋል፤ እውቀት ግን ደፋርነትህን ከጥበብ ጋር ያጣምረዋል። በሕይወት ውስጥ የሚያስፈልገን ያለ ማሰብ የምንሮጥበት ድፍረት ሳይሆን፣ መቼ መሮጥ፣ መቼ መቆም፣ መቼ መጠየቅና መቼ መጠንቀቅ እንዳለብን የምናውቅበት ጥበብ ነው። ስለዚህ እውቀትን ፈልጉ፤ የማታውቁትን ጠይቁ። ምክንያቱም የማያውቅ ሰው ምንም ነገር አይፈራም፤ የሚያውቅ ሰው ግን ምን መፍራት እንዳለበት ያውቃል። አሏህ ልቦና ይስጠን አሚን t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

هذا اليوتيوبر ( الجاهِل ) كَـفَّــر الحافِظ السيوطي !! __ 🖋️ قال شيخ الإسلام ابن تيمية : فإنَّ تسليط الجُهَّال على تَكفير عل
هذا اليوتيوبر ( الجاهِل ) كَـفَّــر الحافِظ السيوطي !! __ 🖋️ قال شيخ الإسلام ابن تيمية : فإنَّ تسليط الجُهَّال على تَكفير علماء المسلمين مِن أعظَم المنكرات، وإنما أصلُ هذا مِن الخوارج والروافض الذين يُكفّرون أئمة المسلمين؛ لِما يَعتقدون أنهم أخطئوا فيه مِن الدين ، وقد اتفق أهل السُّنة والجماعة على أن علماء المسلمين لا يَجوز تَكفيرهم بمجرد الخطأ المحض؛ بل كل أحدٍ يُؤخذ مِن قوله و يُترك إلا رسول الله صلى الله عليه وسلم ، وليس كل مَن يُترك بعض كلامه لخطأٍ أخطأه يُكفّر ولا يُفسَّق بل ولا يُأثَّم؛ فإنَّ الله تعالى قال في دعاء المؤمنين : {ربنا لا تؤاخذنا إن نسينا أو أخطأنا} وفي الصحيح عن النبي صلى الله عليه وسلم «أن اللهَ تعالى قال : قد فَعلت». [مجموع الفتاوى - ١٠٠/٣٥] __ 🖋️ قال شيخ الإسلام ابن تيمية : دَفعُ التكفير عن علماء المسلمين وإن أخطئوا هو من أحقِّ الأغراض الشرعية. [مجموع الفتاوى - ١٠٣/٣٥] t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

አወቀብንና ለዱንያ እንደወጣን፡ ጭራሽ የያዝነውን አሶስደን መጣን ። «ዱንያ ህልማችን ላይ አኸይራን እንጨምር»

الدُنيا صَعبةٌ جدًا على الإنسَانِ الَّذي يَتأثر قَلبُهُ بِسهُولة.

«ያኔ የተከተበ ግን ሁሌ የሚነበብ» 👉ቀጣይ ዓመት ራሴ ላነበው ..... .. ለራሴ የጻፍኩት መፅናኛ!! .... ማንም እንዳያነበው እሽ⁉️ ሁሌም በፈገግታ አልሀምዱ ሊላህ በል #ኑር...አሏህ ዕድሜ ሠጥቶህ ይህን እንድታነብ ከፈቀደልህ፣ እንደ #ለህድ የጨለመውንና የጠበበውን መንገድ ማለፍህን እንደማትረሳ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ተስፋ መቁረጥ ጥርሱን አግጥጦ የገፋህን ቅጽበት፣ ቀናት ሁሉ በማይገለጥ ሸንኮፍ ተጋርደው አልነጋ ሲሉ፤በአኬልዳማ ተደልድለው መራመጃ የነፈጉህ መንገዶች፤ አቅም ባጣም በሹክሹክታ ‹‹ያልፋሉ!›› ስልህ ከመጣህበት በላይ የምትደርስበትን ጸዳል ጉብታ በከሲታ ተስፋ ውስጥ. . .ተስፋ አድርጌ ነው። #አልሃምዱሊላህ ፡፡ የዛሬ ዓመት በዚህ ሰዓት ደክሞህ ነበር፡፡ የአሏህ ውሳኔ ሆኖብህ በሕይወትህ ረግጠህ የማታውቃቸው አዚማም ሥፍራዎች ላይ ቆመሃል፡፡ ትዝ ይልሀል ጨለማን ተጋፍጠህ ነበር ሐኪም ቤት በፍርሀት እየተንቀጠቀጥክ ቆመሀል። ከሰው ፊት በጭንቀት ቆመሀል፡፡ ..ያኔ ከጎንህ አብሮ አደረሰ አልነበረም፣ ..የረጂም ጊዜ ጓደኛህ አልነበረም፣ ..በችግሬ ይደርሳል ያልከው ሰውን አልነበረም። የውስጥ ስሜትህን ለመናገር የሚረዳህ ጠፍቶ አይንህ ሰውን ፍለጋ ወዳና ወዲህ ሲያማትር ከጀሊሉ ብሎም ከአንድ ሰው ውጭ አብሮህ ማን ነበር!? ሐያሉ ጌታህ ፊት ወንጀሎችህን ረስተህ አይንህን በጨው አጥበህ የእንባ ዘለላ እያፈሰስክ #የዛሬን ብለህ ቆመሀል። (አዛኙ ጌታ ግን አላሳፈረህም) በሀሳብና በጭንቀት ሰውነትህ እያየኸው ይቀንስ ነበር ከእለት ወደ እለት ባዶነት እየተሰማህ ከሰው እየተደበቅክ ያለቀስክበትን ቅፅበት ትረሳዋለህ!? ህመምህን ደብቀህ ደህና ነኝ ብለህ ስራ የወጣህበትን አጋጣሚስ.... ምን ይህ ብቻ አፈር ልሰህ ወደ ሕልምህ እንዲያቀናህ ያበቀልከውን ፍሬ ሌባ ያለ ኀፍረት ወስዶብሃል፡፡ ...በአሏህ ከተመካህ ድፍረትና ጭስን ተመስለህ በመርፌ ቀዳዳ እንደምትወጣ ፍርሃት በዋጠው ለሆሳስ ነግሬህ ነበር፣ አላሳፈርከኝም…ዛሬ እዚህ ደርሰሃል፡፡#አልሃምዱሊላህ የዛሬ ዓመት በዚህ ሰዓት ዓለም ተገልብጦብህ ነበር፡፡በደም፣ በሥጋ በመንፈስ የተዛመዱህ በቅርበት ያሉ ወዳጆች ጀርባቸውን እንጂ ፊት አልሠጡህም፡፡ የሩቆቹ እንጂ የቅርቦቹ ከመቅረብ ይልቅ በጀርባ ማውራትን መርጠው ነበር..በዛ ስሜት ንግግራቸውን ሰምተህ.. ፈገግታህስ..ትዝ ይልሀል⁉️ የኋላ ታሪክህንና የሚደርስልህ ነገህን ረስተው በቆምክበት ሥፍራ መዝነው አቅልለውሃል፡፡ ይጎትቱኛል ያልካቸው መዳፎች ገፍተው ወደ መቀመቅ እንድትወርድ በይነውብሃል፡፡ ...የታመመ የማይድን የተሰበረ የማይጠግን የወደቀ የማይነሳ የተዋረደ ወደ ክብር የማይመለስ የሚመስላቸው ብዙዎች እንደሆኑ አስተውል ብዬ..ፍርሃት ባደበዘዘው ለሆሳስ ነግሬህ ነበር…..‹‹ያልፋል!›› ተብዬ ይሔው አለፈ፡፡ .....አልሃምዱሊላህ ‼️ «በመታመምህ ማዘናቸው ቀርቶ መታመሙን በምን እናረጋግጥ ይጣራ ሲሉ አልሰማህም!?ግን አለፈ አልሃምዱሊላህ ሊላህ» «ግን በደል ስለማይረሳ እንጂ እንደ ውሀ ሙላት አብሽር እያለ በሚችለው ሁሉ ከጎኔ የቆመ ተራራ የሆነ እጂግ አዛኝ #ወገን እንደነበረኝ በዛ ቅፅበት ሞት ቢመጣ ራሱን የምደሰትበት ለሰላምም ነበረው... «መልካሞች ሆይ ውለታችሁን ለመክፈል ባልችልም በልቤ ውስጥ ግን ሁሌም ትልቅ ቦታ አላችሁ» የዛሬ ዓመት በዚህ ሰዓት…..ደርሶብህ የማያውቀው የመከራ ፍላጻ ተወርውሮ ቤትህ ገብቶ ገርበብ ያለ በርህን ዘግቶ፣ ክፍት መስኮትህን ደፍኖ ከሁሉ አራርቆህ፣ የጨበጥከውን ነጥቆ፣ የጎረስከውን አስተፍቶህ ብዙ ቀናትና ወራት ሳይነጉልህ…በድቅድቅ ውስጥ ማንም ሳያይህ ከራስህ ጋር ስትታገል፣ ባልተዘጋጀ ትከሻ ላይ ሲህር ሌላ ሸክም ኾኖ ሲያጎብጥህ፤ ከገጠመህ ይልቅ የሚመጣውን ተዓምር አስቤ ፍርሃት ባደበዘዘው ለሆሳስ ‹‹አይዞህ! ይህም ያልፋል!›› ብዬህ ነበር፡፡(ይኸው! አለፍከው አይደል?)አልሃምዱሊላህ ሊላህ በላ...አልሃምዱሊላህ ‹‹ንገረኝ!›› ሲሉህ እንዴት እንደምትገልፀው ተቸግረህ፣ የምትወደውን ብዕር ጨለማ ውስጥ ጥለህ መናገር ከብዶህ….በዝምታ ከዝምታ ጋር ታግለሃል፡፡ ግን ያኔም በመሆን የምትተነፍስበትን ብዕር እንጂ ፈገግታህን እና ጨዋታህን አልጣልክም፡፡ያንኳኳሃቸው በሮች ወቅታቸው ስላልደረሰ እንጂ መከፈታቸው እንደ ቂያማ የማይቀር ቀጠሮ መሆኑን ከሕመሞችህ ልቀው ባይሰ´ሙህም ነግሬህ ነበር፣አላመንከኝም ነበር፡፡ ዛሬ እዚህ ስለደረስክ እኮራብሃለሁ፡፡ «ሁሉም የሆነው በአሏህ እዝነት ከዚያም በወገንህ እገዛ ነው።» ✅ስማ ኑር...‼️ አደራ እነዚያን እንደ ሻማ🕯 የቀለጡልህን የጨለማህ ቀን መብራቶች እንዳትረሳቸው» 🏷በተለይ ሦስት ነገር አትርሳ….‼️ 👉ትንሽ ሻማ ይዘው ጨለማህ ድረስ መጥተው ብርሃናቸውን ያካፈሉህን፣ 👉የተፈጠረው ሳይገባህ፣ የተናገርከው ሳይገባቸው ጆሮ የሠጡህን! 👉ደግሞም ችለው ያልቻሉትን፣ መንገድ መጠቆም ሲችሉ መንገድህን የዘጉትን፣ ጥሩ ቃል እንኳ እንደ ሰማይ የራቃቸውንና ወደቀ ብለው በደስታ በሌለህበት መርጠህ ባልተሰጠኸው ችግር የተሳለቁብህን... እንደማትፈፅመው እያወቁ በክፉ እንድትታይ ያደረጉህን፣ አምነሀቸው ጓደኛ አድርገሀቸው፣ የመከራ ቀን የውስጥ ክፋታቸውን ያሳዩህን #እንዳትረሳቸው... ግን እነሱ አንተ ላይ የሰሩትን ለመስራት ተፈፅሞ እንዳታስብ እነሱም ማንነታቸውን አስተዋወቁህ እንጂ ምንም ማድረግ አልቻሉም፡፡ 👉ሦስተኛ. . .ማን እንደኾንክ አትርሳ፡፡ አሁን ያለህበት ብሩህ ቀን ሲያዘናጋህ ይህን ጽሑፍ አንብብ፡፡ ያለ መሣሪያ ጦርነት ውስጥ ገብተህ የወጣህ፣ ያለ ምሽግ ከፈንጂ ጋር የተጋፈጥክ፣ ራስህን አጥተህ ራስህን ያገኘህ ልበ-ብረት ነህ፡፡ #እኮራብሃለሁ! እራስህን ከማንም በላይ ታውቀዋለህ አይዞህ አዛኝ እንደሆንክ፣ናፋቂ እንደሆንክ፣ተጫዋች እንደሆንክ፣የዋህ እንደሆንክ ቀጥል....... ክፋት፣ምቀኝነት፣ቂምና ጥላቻ ለማንም እንደማይጠቅም አውቀህ ደግነትን ሆነህ ስበከው.. እልሀለሁ... ይህ ቀን አልፎ የሆነ ስዓት በሙሉ ጤንነትህ ታነበዋለህ መንሻ አሏህ አይዞህ እሽ ኑር...«አሏህ ክፉ አይሰራም ትል የለ...አብሽር» «በፈገግታ ሁሉን ማለፍና ማስተናገድ ትችላለህ አልሃምዱሊላህ ሁሉም አለፈና አሁን አነበብኩት፡ ተማሩበት ብዬ ወደናንተ ላኩት፡ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

በርቱ አሏህ ይጠብቃችሁ «ለአሏህ ስል እወዳችኋለሁ የሆነ ትዝታ መጣብኝና አስታወስኳችሁ ደግሞ ናፍቃችሁኛል እሽ‼️
በርቱ አሏህ ይጠብቃችሁ «ለአሏህ ስል እወዳችኋለሁ የሆነ ትዝታ መጣብኝና አስታወስኳችሁ ደግሞ ናፍቃችሁኛል እሽ‼️

ወዳጅ እንደሌለህ! ....ታውቃለህ...!? ማንም ሰው አይልህም ምን ሆኖ ተከፋ፡ ሰው አይጠይቅህም ዘመናት ብትጠፋ፡ አይደለም እንባና ደምክን ብታፈሰው፡ ማንም ሰው አይልህም ምን ሆኖ ሆድ ባሰውን!! መሳቅ ስትጀምር ግን ይበዛል ጥያቄ፡ ለምን እንደሆነ እኔ ምን አውቄ!! 🕯ይገርመኛል!! ባጋጠመህ ጊዜ የመክሸፍ አደጋ፡ ምን ጨለማ ቢሆን ሀምሌ ቢሆን በጋ፡ ከየትም ይመጣል ለነገር ፍለጋ፡ ከች ይላል ከቤትህ ሌሊቱ አይነጋ፡ ...አይ ሰው..!! ትንሽ ሲያነቅፍህ የህይወትህ ስንጥር፡ ጠያቂህ ይበዛል ባለቀስክ ቁጥር፡ ግን ደግሞ ከአንጀቱ ምንም አያደርግም፡ ምን ሞልቶ የተረፈው መርዳት አይፈልግም፡ ስታለቅስ ደግሞ ለእንባህ ማድመቂያ፡ ሀዘን ስብራትህ እንዳይኖረው ማብቂያ፡ ባነር ይሰራሉ ትልቅ ማስታወቂያ፡ ......ይገርማል....!!! ሀዘንህ ሲሰማ ሁሉም ይታደማል፡ አስተናጋጅ ሆኖ ጠላትህ ይቆማል፡ ወዳጅ የምትለው አንተን ይጠቁማል፡ በሀዘንህ ቀን እንኳን አንተነት ይታማል፡ አስተውለህ ካየህ ሁሉም ነገር ያማል፡ ማስመሰል ማታለል እጂጉን ያደክማል፡ .....ባለቤት ይሰማል...!? በጣም እንዲታለቅስ ይነካሉ ቁስል፡ አብሽር በርታ ጠንክር ማለትን ይመስል፡ በጣም እንድታለቅስ ይጫናሉ ቁስል፡ ለእንባህ ማድመቂያ ይለብሳሉ ካኪ፡ ከወደቅክ ይላሉ ዘረፋና አካኪ፡ ደስተኛ ሁንና ሞክራቸው እስኪ...!? 👉....ሰምተሀል...ደስተኛ ሁን ማንም ስላንተ አይጨነቅም። ...ኑር....✍️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

....ስማ.... በሆነ አጋጣሚ ሲጠፋ ከደጂህ፡ ከጎኑ ባትቆምም አቅም አጥሮት እጂህ፡ ክፉ አንዳታወራ ስለዛ ወዳጅህ፡ .....Nur.....✍️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

.....ፅኑዎች ሆይ አብሽሩ ----------------------- የዉስጥን ስቃይ ባለቤቱ ብቻ ያዉቀዋል.... በሕይወት ጎዳና ላይ ስንጓዝ ሁላችንም የራሳችን የሆነ ከባድ ደመና ከራሳችን በላይ ያንዣብባል ብዙ የሀሳብና የህፀፅ አበባወችም የሲቃ እንባ ጠጥቶ ያፈራል። ....ግና በዙሪያችን ያሉ ሰዎች የዝናቡን መዉረድ እንጂ... ያ ዝናብ በዉስጣችን የሚፈጥረውን ቅዝቃዜና የሚቀሰቅሰዉን ትዝታ ፊጽሞ ሊረዱት አይችሉም። ብዙ ጊዜ ሰዎችን የምንፈርደዉ በምናየው ዉጫዊ ገጽታቸው ብቻ ነው። "እሱ/እሷ ምን ይጎድላቸዋል!?" እንላለን። .......ነገር ግን ከጥሩ ልብሶች፣ ከሚያምሩ ፈገግታዎች እና ከቀን ተቀን እንቅስቃሴዎች ጀርባ የሚደበቁ ስንት የተሰበሩ ልቦች አሉ⁉️ ስንት የሚደሙ ነፍሳትስ አሉ⁉️ 👉ሕመም የምሰማው ለቆሰለዉ ሰው ብቻ ነው። ሌላው ሰው ሊያዝንልህ፣ ሊያጽናናህ ወይም ሊራራልህ ይችላል፤ ነገር ግን በጨለማ ክፍል ዉስጥ ብቻህን የምታፈሰዉን የእንባ ዘለላ ትክክለኛ ክብደት ሊሰማው አይችልም። ያንተን ጫማ ተጭቶ ያልተጓዘ ሰው፣ መንገድህ ምን ያህል አሰቃቂ እንደነበረ ሊረዳ አይችልም። የሚያስለቅስህ ነገር ለሌላው ሰው ቀላል መስሎ ሊተይ ይችላል። "ለዚህ ነገር ነው የምታለቅሰው?" ሊሉህ ይችላሉ። ምክንያቱም እነሱ የሚያዩት የወደቀውን ጃንጥላና የራሰዉን መሬት ብቻ ነው፤ በልብህ ዉስጥ የፈረሰውን ዓለም አያዩትም። .....ነገር ግን ማስታወስ ያለብህ አንድ ታላቅ እዉነት አለ፦ ይህ በእንባ የራሰ መንገድ፣ ይሄ ብቻህን የተሸከምከዉ ከባድ ደመና ለዘላለም አይኖርም። አሁን የምታሳልፈው ስቃይ ጥንካሬህን የምትገነባበት፣ የነገ ማንነትህን የምታንጽበት ነበልባል እሳት ነው። 👉ማንም ባይረዳህ እንኳ፣ የራስህን ሕመም በራስህ ጽናት አክመህ እንደምትነሳ እመን። "የቁስሉ ሕመም የሚያዉቀዉ ባለቤቱ ብቻ ቢሆንም፣ ከሕመሙ በኋላ የሚመጣውን ብርሃንና ጥንካሬ የሚያጣጥመዉም ያው የጸናው ልብ ብቻ ነዉ።" «አሏህ ሆይ በመከራ ለፀኑ ልቦች ፈረጃውን አቅርቦላቸው አሚን።» ....ኑር....✍️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

 خَصائِصُ_الْمَرأَةِ_السَّلَفِيَّةِ.mp39.90 MB

لو أنَّ أحدَكم همَّ بإزالةِ جبلٍ، وهو واثقٌ باللهِ لأزالَه. ከእናንተ መካከል አንዱ ተራራን ለማንቀሳቀስ ቢያስብና በአሏህ ላይ ሙሉ እምነት ቢኖረው ያንቀሳቅሰዋል። ➛ሒማ ይኑረን..!! - ابن القيّم. t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

የቀብር ስነስርአት ነገ  ጊንባ  ቱላውሊያ ነው

انا لله وانا اليه راجعون አባቴ በዱንያ ላይመለስ ሞተብኝ ቅርብ የላችሁ እዲሰግዱበት ሩቅ ያላችሁ በዱአችሁ

انا لله وانا اليه راجعون አባቴ በዱንያ ላይመለስ ሞተብኝ ቅርብ የላችሁ እዲሰግዱበት ሩቅ ያላችሁ በዱአችሁ

ጀግናዬ ከአረቂ ገበያ የተገኘ ማር ያሰክራልና ቦታህን እወቅ !!

ማነው መጤው? ~ ሙስሊሙ መብቱን በጠየቀ፣ ጭቆናን በተቃወመ፣ እምነቱን ባስተማረ ቁጥር "እናንተ ሙስሊሞች ወደ ኢትዮጵያ ስትገቡ አክብረን በተቀበልን እንዴት ውለታችን ይረሳል?" እያሉ በቅጥፈት ለሚመፃደቁ አካላት "እንዴ! እኛ እኮ ኢትዮጵያውያን እንጂ መጤዎች አይደለንም" እያሉ በከንቱ መድከም አያስፈልግም ብዬ በፅኑ አምናለሁ። ሰዎቹ እንዲህ አይነት አመክንዮ የሚገባቸው አይደሉም። ድንጋይ ላይ ውሃ ማፍሰስ ነው። መፍትሔው ማጥቃት እንጂ መከላከል አይመስለኝም። በራሱ ቋንቋ አናግረው። በዚህ ድንቁ ^ ርና ላይ በሰፊው የሚታወቁት በዋናነት የአንድ እምነት ተከታዮች ናቸው። እነሱ ናቸው "የእስላም አገሩ መካ፣ የአሞራ አገሩ ዋርካ" የሚል ምሳሌያዊ አነጋገር ፈጥረው ድንቁርናቸውን ከትውልድ ትውልድ የሚያሻግሩት። እንዴት አድርገው እንደሚጠርቧቸው እንጃ በዚህ ዘመን እንኳ አልተቀየሩም። የለውጥ ተስፋ የሚታይባቸውም አይደሉም። አስቂኙ ነገር ደግሞ ራሳቸውን የአይ^ሁድ ዘር አድርገው መኮፈሳቸው ነው። ሃገሪቱን ለሰባት መቶ ዓመታት በላይ የቦጠቦጠው ራሱን "ሰለሞናዊ መንግስት" ብሎ የሚጠራው መዥገር ስርአትኮ ባህር ተሻግሮ የሰሎሞን ዘር ነኝ የሚል ነው። መጤ ነኝ ማለት አይደል ይሄ? አፄ ምኒልክ "ዳግማዊ" ምኒልክ የተባለው ጥንት ከንጉስ ሰለሞን የተገኘ "ቀዳማዊ" ምኒልክ ነበር ብለው ስለሚያምኑ ነው። "የናዝሬቱ እየሱስ፣ የዮርዳኖስ ወንዝ፣ ቃና ዘገሊላ፣ ቤተልሄም፣ እየሩሳሌም፣ ... " እያለ እምነቱን ከባህር ማዶ ጋር የሚያይዝ አካል እንዴት ሙስሊሞችን መጤ ሊያደርግ ይዳፈራል?! የሙስሊሙን ኢትዮጵያዊነት መቀበል የከበዳቸው ጭንቅላቶች "ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት ናት" የሚል ያረጀ ያፈጀ ተረት ዛሬም ይተርታሉ። ለመሆኑ እነሱ ዘንድ ኢትዮጵያ ማለት የቷ ናት? ለመሆኑ ኢትዮጵያ ሲሉ አፋርን፣ ሶማሊን፣ ሀረርን፣ ስልጤን፣ ከፊል ጉራጌን፣ ሰፊውን ኦሮሚያን፣ ሀላባን፣ አብዛኛው ወሎን፣ አብዛኛውን በኒሻንጉልን፣ ድሬዳዋን፣ አርጎባን፣ ... ይጨምራል ወይ? እስኪ እነዚህን አካባቢዎች ቆርጠው ያውጡና የደሴቷን ካርታ ይመልከቱ። ካርታው ላይ የሚታየው ቀዩ ክፍል ነው የሚቀራቸው። ከዚያ የቀራችሁን የክርስቲያን ደሴት ተመልከቷት! የምትዘምሩላት ኢትዮጵያ ይቺ ናት? ለማንኛውም "በቀዳማዊ ምኒልክ በኩል የሰለሞን ዘር ነን"፣ "ነገደ ይሁዳ ነን"፣ "የይሁዳ አንበሳ ነን" የሚለውን የአባቶቻችሁን ተረት የምታምኑበት ከሆነ መጤዎች እንደሆናችሁ በራሳችሁ ላይ መስክራችኋል። እኛ ሙስሊሞች ዐረቦች ነን አላልንም። ኢትዮጵያውያን ነን። እናንተ "የሁ^ዶች ነን" ካላችሁ እኛ ነን የተቀበልናችሁ። "አይ" ካላችሁ "አይ^ሁድ ነን" የሚለውን የአባቶቻችሁን ተረት ውሸት እንደሆነ አስረግጣችሁ ወርውራችሁ ጣሉ። ከዚያ በኋላ ራሳችሁን የኢትዮጵያዊነት አከፋፋይና ድርጎ ሰፋሪ አድርጋችሁ ማየታችሁን አቁሙ። የነውረኝነታችሁ ዳፋ ለደካሞች ይተርፋልና ጥፍራችሁን ሰብስቡ። በዚህ ዘመን እንዲህ አይነት የከረፋ ሃሳብ ስታንፀባርቁ ታንኩም ባንኩም በእጃችሁ በነበረበት የቀደመው ዘመን ያደረሳችሁትን ማሰብም ይሰቀጥጣል። = የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

4_5974501093026045717.mp37.28 KB

«إنّ القَلب لاَ يَطمئِنُّ إلاَّ بالإيمَـان واليقِـين، ولَا سَبيل إلَى حُصُول الإِيمَـان واليَقـين إلاَّ مِن القُرآن». -ابن القيم رحمهُ الله.

ተፍሲር    سورة    يس አንቀፅ   ቁጥር         77       ለይነን ሊጀመርነዉ  ተቀላቀሉ ባረከላሁ   ፊኩም ttps://t.me/SheihkAbuAmarAwolIbnuAhmed?livestream=f81a469cec1f0dbd65