en
Feedback
شـبـاب السـلــفـــيـــيــن

شـبـاب السـلــفـــيـــيــن

Open in Telegram

👉«ሰለፍያ ቀጥተኛ የሀቅ መንገድ ብሎም አይነኬ ፅኑ ተራራ ነው።» ለአስተያዬትና እርማት

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel شـبـاب السـلــفـــيـــيــن

Channel شـبـاب السـلــفـــيـــيــن (@nuredinal_arebi) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 29 138 subscribers, ranking 2 505 in the Religion & Spirituality category and 1 172 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 29 138 subscribers.

According to the latest data from 23 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -158 over the last 30 days and by -3 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 15.73%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.75% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 584 views. Within the first day, a publication typically gains 2 549 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 50.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
👉«ሰለፍያ ቀጥተኛ የሀቅ መንገድ ብሎም አይነኬ ፅኑ ተራራ ነው።» ለአስተያዬትና እርማት

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 24 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

29 138
Subscribers
-324 hours
+257 days
-15830 days
Posts Archive
👉የውሳኔ ሰው እንሁን‼️ ✅ተነሽ ወስኝ‼️ ✅ተነስ ወስን‼️ የወሰንሽውን መኖር ጀምሪ በቃ ወስኝ ማግባት ትፈልጊያለሽ አይደል በቃ አግቢ ለመቼ ነው ቀጠሮሽ ...መውለድ ትፈልጊያለሽ አይደል በያ (የ
👉የውሳኔ ሰው እንሁን‼️ ✅ተነሽ ወስኝ‼️ ✅ተነስ ወስን‼️ የወሰንሽውን መኖር ጀምሪ በቃ ወስኝ ማግባት ትፈልጊያለሽ አይደል በቃ አግቢ ለመቼ ነው ቀጠሮሽ ...መውለድ ትፈልጊያለሽ አይደል በያ (የወሊድ መቆጣጠሪያ ምን ይሆንሻል።) በቃ የምታስቡትን መኖር ጀምሩ ወደዳችሁም ጠላችሁም በሰከንድ ቅፅበት ተፈላጊነታችሁ እየረከሰ የምትፈልጉት ከእናንተ ይበልጥ እየራቀ ይሄዳል ። 🔥 ወንድሜ ታሪክህን ለመቀየር የአንድ ቅጽበት ውሳኔ ይበቃልኮ በጌታህ ተመካ ከዚያ አድርገው በቃ አትግደርደር። ​በምስሉ ላይ እንደምናየው፣ የሁላችንም ጊዜ፣ ጉልበትና ወጣትነት ልክ እንደ ክብሪቱ እንጨት በየቀኑ እየነደደና እያለቀ ነው። ..... "ነገ እጀምራለሁ" እያልን የምናስተላልፈው ቀጠሮ የህይወታችንን እሳት በከንቱ እንዲበላሽ ያደርገዋል። ለውጥ የሚመጣው አሁኑኑ ሲወሰን ብቻ ነው! ​💡የዛሬው መልዕክቴ‼️ ​ጊዜህ እየነደደ ነው፦ ዛሬ በእጅህ ላይ አቅምና ብርሃን ሳለህ፣ ለህይወትህና ለወደፊት ስኬትህ ታላቅ ውሳኔን ዛሬውኑ ውሰድ። ✅​ስኬት የጋራ ነው፦ እውነተኛ ስኬት ብቻህን ጫፍ መውጣት ሳይሆን፣ ራስህ በትግል ውስጥ እያለህ እንኳ ሌሎችን የምታነሳበትና የምታበረታታበት ታላቅ መሪ መሆን ስትችል ነው። 🛑​አሁኑኑ ቁረጥ፦ ለመውደቅና ተስፋ ለመቁረጥ አንድ ሰከንድ ይበቃል... ተነስተህ አዲስ የስኬት ታሪክ ለመጻፍ ግን የአንድ ቅጽበት ጽኑ ውሳኔ አመርቂ ነው። ​ሰዓቱ ሳይረፍድ፣ እሳትህ ሳይጠፋ... ዛሬውኑ ወስነህ ተነስ እልሀለሁ። t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

«የተበደራችሁትን በሙሉ አውፍ ብያለሁ።» 👉«ቀይስ ኢብኑ ሰዕድ» .....ከእለታት አንድ ቀን ቀይስ ኢብኑ ሰዕድ ኢብኑ ዑባዳህ ..ችግር ገጠመው ይህ ታላቅ የነብዩ ሶሀባ በጠና ታመመ። ...ይህ ሶሀብይ እጂግ የናጠጠ ሀብታም ነበር ... በህመሙ ጊዜ ግን መጥተው የሚጠይቁት ሰዎች ቁጥር በጣም ቀነሰበት። 👉ይህኔ ግራ ተጋባ‼️ ✅ለምንድነው ሰዎች በብዛት መጥተው የማይጠይቁኝ ⁉️ እኔ መጥፎ ሰው ነኝ ማለት ነው ⁉️በማለት ጠየቀ‼️ 🛑ሰዎች መለሱለት፦ ➥ቀይስ ሆይ ጉዳዩ አንተ እንደምታስበው አይደለም ። ...ግና ሰዎች አንተ #ያበደርካቸውን ገንዘብ ስላልመለሱ አንተን ከመጠየቅ #ሀያዕ ይዟቸው ነው የቀሩት አሏቸው። 🛑ይህኔ የማይረሳ ቃል ተናገረ‼️ «أخزى الله مالا يمنع عنى الزوار» "ጎብኚዎች ወደ እኔ እንዳይመጡ የሚከለክል ገንዘብ የተዋረደ ይሁን አለ።" ثم أمر مناديا يصيح في المدينة »من كان لقيس عليه دين فهو في حل» (أي سامحهم جميعا) ➥#ከዚያም፦ በከተማው ውስጥ ሁሉ አንድ አዋጅ ነጋሪ እንዲጮህ አዘዘ። «ከቀይስ ገንዘብ የተበደረ በሙሉ ይቅር ብሎታል ብሎ አስነገረ። ✅ከዚያ በሚገርም መልኩ «ከዘያርተኛው ሰው ብዛት የቤቱ #ጉበን እስኪሰበር ድረስ ጠያቂው በረከተ ይላሉ።» «ለስንቶች ስንት ቢያበድር ነው አሏህ የዱንያ ፍቅር ከልቦ ወጣለትና አውፍ አላቸው።» ....ኑረዲን...✍️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

ሸይኽ አቡል ሀሰን አርራዚሂይ ከመግሪብ እስከ ኢሻ ቦሌ ጃዕፈር መስጂድ ሙሓደራ ይኖራቸዋል። ታደሙ

የዐሹራእ ጾም‼ ========== (የነብዩ ﷺ ጉጉት እና የሰለፎች ጥልቅ ማስተንተን!) || በእስልምና አስተምህሮ ውስጥ የሙሐረም ወር፣ በተለይም የዐሹራእ (የሙሐረም 10ኛ) ቀን እጅግ የላቀ ደረጃ አለው። ይህ ቀን ያለፈውን አንድ ዓመት ወንጀል የሚያስምር ታላቅ ጸጋ ነው። የዚህን ቀን ታላቅነትና ጾሙን በተመለከተ ትክክለኛ ሐዲሦችን እና የዑለማዎችን ድንቅ ንግግሮች ከነ ምንጫቸው እንመልከት፦ ❶ የነብዩ ﷺ ብርቱ ጉጉት፦ ነብዩ ሙሐመድ ﷺ ይህን ቀን ለመጾም ልዩ ጉጉት ነበራቸው። ታላቁ ሶሐባህ ዐብዱ-ል'ሏህ ኢብኑ ዐባስ ይህን የነብዩን ﷺ ጉጉት ሲገልጹ እንዲህ ይላሉ፡- «مَا رَأَيْتُ النَّبِيَّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَتَحَرَّى صِيَامَ يَوْمٍ فَضَّلَهُ عَلَى غَيْرِهِ، إِلَّا هَذَا الْيَوْمَ ؛ يَوْمَ عَاشُورَاءَ، وَهَذَا الشَّهْرَ. يَعْنِي شَهْرَ رَمَضَانَ.» «ነብዩ ﷺ ከሌላው አብልጠው የዚህን ቀን (የዐሹራእን) እና የዚህን ወር (የረመዿንን) ጾም ለመጾም እንደሚጓጉት ለሌላ ቀን ሲጓጉ አላየሁም።» 📜[ሶሒሕ አል-ቡኻሪይ፡ 2006፣ ሶሒሕ ሙስሊም፡ 1132] ❷ «ካለፈ አይመለስም!» ✅የቀደምት ሰለፎች ለዐሹራእ ጾም የነበራቸው ቦታ አስገራሚ ነበር። ታላቁ ታቢዒይ ሙሐመድ ኢብኑ ሺሀብ አዝ-ዙህሪ በጉዞ ላይ እያሉ የዐሹራእን ቀን ጾሙ። በዚህ ጊዜ ሰዎች ተገረሙና እንዲህ ሲሉ ጠየቋቸው፡- (… فقيل له: لم تصوم وأنت تفطر في رمضان في السفر ؟! فقال: إن رمضان له عدة من أيام أخر، وإن عاشوراء يفوت.) «በረመዿን ወር በጉዞ ላይ ሆነህ ጾም እየፈታህ፣ ዛሬ (በጉዞ ላይ) ለምን ትጾማለህ?» ተብለው ሲጠየቁ፤ «ረመዿን በሌሎች ቀናት (ተቆጥሮ) ቀዷ ይወጣል (ይከፈላል)፤ የዐሹራእ ጾም ግን ካለፈ ያመልጣል (ቀዷ አይወጣም)!» ብለው መለሱ።» 🛑 [ሸዕቡል-ኢማን ሊል-በይሀቂይ፡ 3518] 👉በእርግጥም የረመዿንን ጾም በህመም ወይም በጉዞ ምክንያት የፈታ ሰው በሌላ ጊዜ መክፈል ይችላል። የዐሹራእ ጾም ግን ዓመት ጠብቆ የሚመጣና ቀዷ የሌለው በመሆኑ፣ ይህ ታላቅ ምንዳ እንዳያመልጠን ሰለፎች እስከዚህ ድረስ ይጓጉለት ነበር! ❸ዓመትን በዒባዳህ መዝጋትና በዒባዳህ መክፈት! 👉 ታላቁ ሊቅ ኢማም ኢብኑ ረጀብ አል-ሐንበሊ አላህ በሰጣቸው ጥልቅ እይታ፣ የዓመቱ መጨረሻ (ዙል-ሒጃ) እና የዓመቱ መጀመሪያ (ሙሐረም) ወራት ውስጥ ስላለው ጾም እንዲህ ይላሉ፡- «من صام من ذي الحجة وصام من المحرم، فقد ختم السنة بالطاعة وافتتحها بالطاعة فيرجى أن تكتب له سنته كلها طاعة، فإن من كان أول عمله طاعه وآخره طاعة فهو في حكم من استغرق بالطاعة ما بين العامين.» «ከዙል-ሒጃ (ባለፈው ዓመት መጨረሻ) እና ከሙሐረም (በአዲሱ ዓመት መጀመሪያ) የጾመ ሰው፤ ዓመቱን በዒባዳህ (በታዛዥነት) ዘግቶ፣ አዲሱን ዓመትም በዒባዳህ ከፈተ ማለት ነው። በመሆኑም ዓመቱ ሙሉ በዒባዳ እንዳሳለፈ ይጻፍለታል ተብሎ ተስፋ ይደረጋል። ምክንያቱም የመጀመሪያውም ሆነ የመጨረሻው ስራው አላህን መታዘዝ የሆነ ሰው፣ በሁለቱ ዓመታት መካከል ያለውን ጊዜ ሙሉ በዒባዳ እንዳሳለፈ ይቆጠርለታልና።» 📚 [ለጧኢፉል መዓሪፍ ሊብኒ ረጀብ] 👉የዚህ ዓመት የዐሹራእ ጾም ቀናት! ነብዩ ﷺ ዐሹራእን ጾመው፣ ከአይሁዶች ለመለየት ሲሉ ቀጣዩ ዓመት ከደረሰ 9ኛውንም ቀን (ታሱዓእን) አብረው እንደሚጾሙ ተናግረዋል። በመሆኑም፣ የዘንድሮውን የሙሐረም 9ኛ እና 10ኛ ቀን የጾም ቀጠሯችንን እንደሚከተለው አድርገን ይህን የዓመት ወንጀል የሚያስምር ታላቅ ጸጋ እንቋደስ፦ ታሱዓእ (9ኛው ቀን)፦ ረቡዕ፣ ጁን 24 ዐሹራእ (10ኛው ቀን)፦ ሐሙስ፣ ጁን 25 አላህ ያለፈውን ዓመት ወንጀላችንን የምንማርበት፣ አዲሱን ዓመትም በዒባዳና በኸይር የምንጀምርበት ያድርግልን! (እነዚህን ቀናት ጓደኛ እና ቤተሰባችሁ እንዳይረሱት ሼር በማድረግ የኸይር ሰበብ ሁኑ!) t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

🔖 የአሹራ ፆምን በተመለከተ..! አቡ ቀታዳ አል አንሷርይ አላህ መልካም ስራው ይውደድለትና እንዲህ አለ፦ የአላህ መልእክተኛ ﷺ ስለ አሹራ ቀን ፆም ተጠይቀው እንዲህም አሉ፦ 【ያለፈውን አንድ አመት ወንጀል ያብሳል】ብለዋል። 📚 (ሙስሊም ዘግቦታል።) ~የሚፆመዉ 10ኛዉ ቀን ሲሆን ነገር ግን አህለል ኪታቦችን ለመሀለፍ 9ኛዉ(ዘጠነኛዉን) ቀን መፆም የፈለገ  በላጩ ይህ ነዉ። ~የአሹራ ቀን ፆም የሚጀመረው ነገ እሮብ እና ሐሙስ ይሆናል ማለት ነዉ።  ዘጠንኛዉን ቀን መፆም ያልቻለ 10ኛዉ እና 11ኛዉ ቀን መፆም ይችላል። مَنْ دَلَّ عَلَى خَيْرٍ فَلَهُ مِثْلُ أَجْرِ فَاعِلِهِ }.      (ሌሎችን) ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የተገበረውን ሰው አምሳያ ምንዳ ይኖረዋል።     https://t.me/nuredinal_arebi

➤እንቅልፋችን ጠፋ.... 🔸«ህልም ፈች በዛብን»🔸 -------------------------- ከቀኙ ጎዳና ወደ ግራ ወድቀን፡ ሀሳባችን በዛ እንቅልፍ ናፈቀን፡ መቀመጥ መነሳት ሁሉም አሳቀቀን፡ መኖርም መሞትም እኩል አስጨነቀን፡ ምንም አለማድረግ እጂግ በጣም ያማል፡ ውስጥህ ሰላም ሲያጣ ሰው መሆን ይደክማል፡ -------------------------------------------- በህይወት ለመኖር ከኛ ሰላም ጠፋ፡ ውሰደን ለማለት ወንጀላችን ከፋ፡ ቃል ከተግባር ጋራ ልዩነቱ ሰፋ፡ ህሌናችን ዝሎ አካል ሲደነድን፡ ከማየት ቦዝኖ አይናችን ሲከድን፡ ማስተዋል ሲሳነን ነፍስ ስቶን በድን፡ ጣታችን አይናችን ሲዝሉ በቡድን፡ መተኛት ስናቅድ እንቅልፍን አስበን፡ ጎን ምድር ሲይዝ አንድት ትራስ ስበን፡ እንቅልፋችን ጠፍቶ በሀሳብ ዘመቻ፡ ከሰው ተለይተን ሆነን ለየብቻ፡ ቋጠሮ ሰብስበን ቀልቀሎ ስልቻ፡ የእቅድ ፈረስ ጋልበን በተስፋ ኮርቻ፡ እንደዚህ ሆነናል ያሳዝናል ብቻ‼️ .....ይደክማልኮ..ጃል..!! ስንት ቀን ቆይተን ድካም ሲበረታ፡ ስጋና አጥንታችን መንፈስም ሲረታ፡ አረፍ ያልን እንደሆን ለትንሽ ቆይታ፡ እንሔዳለን በህልም ወደ ሆነ ቦታ፡ በቃ እንዲህ ነው ህይወት እንድህ ነው መኝታ!! ከዚያ እንነሳለን በፍርሀት ደንግጠን፡ ሰላማችን ጠፍቶ ተጨናንቀን ቀልጠን፡ የምንይዘው ጠፍቶን በስጋት ተንጠን፡ ለኔ ዘመን ወጣት ይሔ ነው መሰልጠን፡ ከዛ ያየውን ጉድ ይናገራል ሔዶ ፡ ላላፊው ላግዳሚው በነገር ተዛምዶ፡ ዜና ያሰራጫል እስከ ባህር ማዶ፡ ፍቹን የሰማ ቀን ይሆናል በረዶ፡ ከቀናት በኋላ ይታሰራል አብዶ‼️ ....በቃ ይሔው ነው!! ያዬነውን ትተው ባልታዬ ሲመሩን፡ ሁላችን ተስማማን መደነጋገሩን፡ በቅዠት ሀገር ውስጥ ህልም ፈቹ በዝቶ፡ ሰላም እየራቀን መርሀችን ባዝቶ፡ ታጥቆ እየፎከረ አንዱ ባንዱ ዝቶ፡ ለተወሰነ እድሜ እቅዳችን ሰፍቶ፡ ሳንተኛ እናድራለን እንቅልፋችን ጠፍቶ፡ .....በኑረዲን አል-ዓረብ..✍️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

ካነበብኳቸው ውብ ነገሮች አንዱ፦ ----------------------------- ➥«የመለያየት ስቃይ የሚገባው ለተከበረች ነፍስ ብቻ ነው።» ✍️ፀሀፊው እንዲህ ይላል፡- በመለያየት የሚነኩት የሚተክዙ
ካነበብኳቸው ውብ ነገሮች አንዱ፦ -----------------------------
➥«የመለያየት ስቃይ የሚገባው ለተከበረች ነፍስ ብቻ ነው።»
✍️ፀሀፊው እንዲህ ይላል፡- በመለያየት የሚነኩት የሚተክዙትና የሚያስቡት የተከበሩ ነፍሶች ብቻ ናቸው ። ➥አህያ ከፈረስ ጋር ብታስሩትና ከዚያም ብታለያዩዋቸው ምን እንደሚፈጠር አስባችሁታል? በመለያየታቸው #አህያው አይነካም አያዝንም በቃ ምንም አይመስለውም። ነገር ግን ፈረሱ በጣም ይናፍቃል፣በጣም ይተክዛል የመለያየትን ስቃይ የሚረዱት #የተከበረች ነፍስ ያለቻቸው ሰዎች ብቻ ናቸው። 👉ለአህዮች መለያየት ምን እንደሆነ አያውቁትምና ለነሱ ምንም ነው። ➥ስለዚህም እመክርሀለሁ አብረህ የምትሄድበትን ቦታ በቸልተኝነት በሚመለከቱ ሰዎች አትደነቅ። ➥ጓደኝነትህ ጉርብትናህ በቀለለባቸውና ዋጋህን ባላወቁት ሰዎች አትገረም። ➥«አብራችሁ ስንት ጣፋጭ ጊዜ እንዳላሳለፋችሁ ሁሉ ከተለየህ በኋላ እንደማያውቅህ በሚያደርግስ ሰው አትገረም።» የሰው ልጆች እንድህ ናቸው ልዩነቱን በፈረሱና በአህያው አነፃፅረው ። 🛑አልገባኝም እንደማትል ተስፋ አለኝ‼️ ....ኑር... t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

ከሰማችሁኝ መተማመን ራሱ ችግር ነው...#እውነት ቢሆን ኑሮ ውሀ አሳን ባልቀቀለው ነበር....እናማ ከቻልክ ከአሏህ በታች በራስህ ላይ ብቻ ተማመን ጀግናው...!! .....ኑር... t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

«ባለትዳሮች አስተውሉ» .....ትዳር ውስጥ ብዙ አለመግባባቶች የሚፈጠሩት አንዱ ሌላውን ለመጉዳት ስለሚፈልግ ሳይሆን የተፈጥሮ ባህሪያቸውን ስለማያውቁ ነው። ✅ለምሳሌ፦ አንዳንዴ በተለያዩ ጉዳዮች ዝም ብሎ ቢቆይ «ሚስቱ በቃ አይወደኝም» ለኔ ቦታ የለውም፣አይፈልገኝም ብላ ልትረዳው ትችላለች ....ነገር ግን ብዙ ጊዜ ይህ ችግር #ወንድ_ልጅ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ለማሰብና በትኩረት ለመመልከት ብሎም ግራ ቀኝ ለማስተዋል የሚጠቀምበት የተፈጥሮ መስመር ነው። ...«ስለሆነም ሚስት ይህንን የወንድ ልጅ የተፈጥሮ ባህሪ ልትረዳ ግድ ነው ።» ✅በሌላ በኩል #ሴቷ ደግሞ ፦ ለባሏ ያላትን ፍቅር፣ ለሱ ያላትን ስሜት ..በብዙ ቃላት ብትገልፅለት....#ባለቤቷ ብዙ ታወራለች ፣ተጨቃጫቂ ነች ብሎ ሊያስብ ይችል ይሆናል...ግና ይህ በአብዛኛው የሴትነት ገፀ-ባህሪ የተገነባበት የህይወት ዑደቴ ነውና ልንረዳ ይገባል። 🛑መፍትሔው‼️ ባል ሆይ፦ 👉ሚስትህን እንደ ወንድ አታስብ ሚስትህን እንደ ሴት ተረዳት። 🛑ሚስት ሆይ፦ 👉ባልሽን እንደ ሴት አትሰቢው ወንድ ነውና ሞራሉን ፕላኑን ፀባዩን አክብረሽ ጠብቂው። አወ የተፈጥሮ ልዩነት መረዳትን የሚጠይቅ ሐቅ እንጂ ስህተት አይደለም። t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

«ልቤ ሆይ ይቅርታ» በምን ቦታ እንዳለፍክ ስታውቀው ጠንቅቀህ፡ ስንት የሐዘን እንባን በፈገግታ ስቀህ፡ ለጠላት አታብር ወርደህ አታስንቀኝ፡ ያለፈ አልፏል ብለህ በነፃ ታረቀኝ!? .....ይቅርታ...!! ስንት ነገር ሆነህ አልተረዳሁህም፡ በተደጋጋሚ ታገስ ግደለህም፡ እያልኩኝ ዘወትር ቦታ አልሰጠሁህም፡ ስንቱን አሳልፌ አንተን በድያለሁ፡ አሁን ግን ይቅርታ ያው ተመልሻለሁ፡ ብርሀን በሌለበት በጨለማው ቦታ፡ እኔና አንተ ብቻ ጀምረን ጨዋታ፡ እንታረቅ በቃ ልቤ ሆይ ይቅርታ፡ ....ኑር t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

🎉 ቀጥታ ስርጭት የዳእዋ  ፕሮግራም    〰🎊〰🎊〰🎊〰🎊〰🎊〰 🎙በወንድም አቡ ሒበቲላህ ጀ        መ                ረ    ↷↷↷↷↷⇊🎙⇊↶↶↶↶ https://t.me/MohamedAliEdris?livestream

በጥሩነትህ እንድትቆጭ የሚያደርጉ ሰዎች! ---------------------------------------- አንዳንድ ጊዜ በሕይወት ውስጥ የሚያሳዝነው ክፉ ሰዎችን ማግኘት ብቻ አይደለም... ጥሩ ሆነህ በመኖርህ ብቻ ደጋግመው እየበደሉህ እንድትቆጭ ሲያደርጉህ ያኔ ጥሩ በመሆንህ እንድትፀፀት ይገፉሀል ቢሆንም አደራ በክፋታቸው እንዳትቀና ። ሰውን በሙሉ ልብህ ታምናለህ...!! በችግሩ ጊዜ ከጎኑ ትቆማለህ...!! ሲወድቅ ታነሳዋለህ...!! ሲያለቅስ ታጽናናዋለህ...!! ሲያጣ ታካፍለዋለህ...!! ነገር ግን አንድ ቀን ዞሮ ሲወጋህ፣ ሲክድህ፣ ሲጎዳህ ልብህ ውስጥ የሚነሳው ጥያቄ አንድ ነው...“ጥሩ መሆኔ ስህተት ነበር⁉️”የሚል የህሌና ጩኸት‼️ እና ያ ጥያቄ ከሕመሙ በላይ ያቆስላል። ምክንያቱም ክፉ ሰው ልብህን ብቻ አይጎዳም...። በሰውነትህ ያለውን ጥሩነት እንድትጠራጠር ያደርግሃል። ከዚያ በኋላ ሰውን ለማመን ትፈራለህ...!! ለመርዳት ሁለት ጊዜ ታስባለህ...!! ልብህን ለመክፈት ትቸገራለህ...!! ምክንያቱም ያለፈው ቁስል አሁንም በውስጥህ አለ። ⭕️ነገር ግን... አንድ እውነት ፈጽሞ መርሳት የለብህም። የሰዎች መጥፎነት የአንተን ጥሩነት ስህተት አያደርገውም። 👉ፀሐይ በቆሻሻ ቦታ ላይ ስለምታበራ ቆሻሻ አትሆንም። 👉ወንዝ ድንጋይ ስለሚያገኝ መፍሰሱን አያቆምም። #እንዲሁም... አንተ የተሳሳተ ሰው ስላገኘህ ጥሩ ሰው መሆንህን መተው የለብህም። ⭕️አዎ... 👉በልብህ የሚጫወቱ ሰዎች አሉ። 👉ጥሩነትህን እንደ ድክመት የሚያዩ አሉ። 👉ዝምታህን እንደ ፍርሃት የሚተረጉሙ አሉ። 👉ርህራሄህን ተጠቅመው የሚጎዱህም አሉ። ግን ችግሩ በጥሩነትህ ውስጥ አይደለም... ችግሩ ጥሩነትን ማየት በማይችል ልባቸው ውስጥ ነው። #ሕይወት_አንድ_ቀን_ታስተምርሃለች። 👉ጥሩ ሰው መሆን ማለት ሁሉንም ማመን አይደለም። ሁሉንም መታገስም አይደለም። ሁሉንም ማስደሰትም አይደለም። 👉#ጥሩ_ሰው_መሆን_ማለት... ⭕️ጥሩ ልብ እያለህ ጥበብ ያለው ድንበር ማበጀት ነው። ✅እርዳታ እየሰጠህ ክብርህን መጠበቅ ነው። ✅ፍቅር እየሰጠህ ራስህን አለማጣት ነው። ✅ሰውን እያከበርክ ራስህንም ማክበር ነው። 🛑ስለዚህ...‼️ ዛሬ በጥሩነትህ አትቆጭ። ያጋጠሙህ መጥፎ ሰዎች ጥሩነትህን እንጂ ማንነትህን አይገልጹም። አንተ የሰጠኸው ፍቅር፣ ያሳየኸው ርህራሄ፣ ያደረግኸው መልካምነት... ምናልባት በተሳሳተ ሰው እጅ ወድቆ ይሆናል። ግን ያ ማለት ዋጋ የለውም ማለት አይደለም። 👉ምክንያቱም በመጨረሻ... መጥፎ ሰዎች ጥሩነትህን ሊጎዱት ይችላሉ ይሆናል እንጂ ሊያጠፉት ግን አይችሉም። .....አንዳንድ ጊዜ የሕይወት ትልቁ ድል... መጥፎ ሰዎች ካጋጠሙህ በኋላም ጥሩ ሰው ሆነህ መቀጠል ነው ብዬ አምናለሁ። t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

     ጥበብና ዕውቀት ሲያብሩ!!.... ------------------------------   ደሓክ ኢብኑ ሙዛሂም ጋር የሚመላለስ አንድ ነሷራ ነበር። "ወደ እስልምና ለምን አትገባም⁉️" ብሎ ጠየቀው‼️ ✅ "ለኸምር ያለኝ ፍቅር ነው ከመስለም የከለከለኝ" አለው።   "እሱማ አያሳስብህ: ሰልመህም ትጠጣለህ" አለው።    ነስራኒው ሰለመ። ከሰለመ በኋላ ደሓክ "አሁን ሰልመሃል: ኸምር ከጠጣህ ሓድ እናቆምብሃለን፤ ከተመለስክ ደግሞ በሙርተድ ሑክም እንገድልሃለን!!" አለው።    ሰውየው ግን ከሰለመ በኋላ እስልምናው አምሮለት ሷሊሕ ሰው ሆኖ ኖሮ ሞተ ይባላል። .....ኑር....✍️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

Voice message00:15

«ትዳርሽን እወቂበት» የቀኑብሽም ወዳጅ መስለው ይቀርቡሻልና ጠንቀቅ በይ #ሀይ ለምትልሽ ሁሉ የቤትሽን ገመና አትዘርዝሪ 👉አንድት ሴት ቤቷን በገዛ እጇ የምታፈርሰው «ከባሏ ይልቅ የሌሎችን ወሬ አጥብቃ በሰማች ጊዜ ነው።» t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

ከንጋቱ ጀርባ ያለው ሚስጥር --------------------------- «አብሽሩ ይነጋልኮ ግን የሚነጋው በአሏህ ላይ ባለን ፅኑ ተስፋ እና በጥረታችን በቆራጥነታችን ልክ ነው። የሻማ መብራት የባትሪ ሀይልና የኤሌክትሪክ ሞገድ እኩል ጨለማ ይገፉም ....ስልህ‼️ ህይወት ልክ እንደ ጠዋት ፀሀይ አድስ ተስፉ፣ አድስ ጀማሬ፣ አድስ ሩጫ፣ አድስ እቅድ ይዛልን ብቅ ትላለች። ለዚህ ምሳሌ የሚሆን አንድ ቁም ነገር ላካፍላችሁ…⁉️ 👉በአፍሪካ ጫካዎች ውስጥ እንደሌሎቹ የዱር እንስሳት ሁሉ በቁመቷ ረጅሟ በፍጥነት ግን ዘገምተኛዋ ቀጭኔ እንደተለመደው በጠዋት መነሳት አለባት። ይህን ስታስብ በቅድሚያ የምታስተውለው ነገር የሚያድናት አንበሳ ፈልጓት እንደሚመጣ ነው። አንበሳውም ለማደን በጠዋት ሩጫውን ይጀምራል....ቀጭኔዋም ላለመታደን ሩጫዋን ትጀምራለች። ⭕️አሁን አስተውሉ‼️ ......አንበሳው ትላንት አንድኖ ስለበላ የዛሬ አደኑን አያቆምም። ....ቀጭኔዋም ትላንት ስላመለጠች ዛሬም ነፃ መሆን አትችልም። በሁለቱም ቦታ እራስህን መመልከት ትችላለህ በነጋልህ ቅፅበት ጉዞህ ወደ አዲስ ስራ ነው፤ ወደ አዲስ ተግባር፣ ወደ ተለየ እርምጃ ነው። መንጋቱ ብቻ ወደፊት እንድትጓዝ ያደርግሃል፤ አዲስ ቀን መመልከትህ ብቻ በአዲስ ወኔና...በተለየ መንፈስ ወደ ተግባር ያስገባሃል። .....ትላንት ምንም ይፈጠር፣ ምንም ስራ፣ ምንም አድርግ፣ ምንም ገንባ ምንም አፍርስ ዋናው የዛሬ እቅድህ ምን እንደሆነ ጠንቅቀህ ማወቅህ ነው። ✅ምናልባትም ዛሬ የምትሮጠው ለማምለጥ፣ ላለመታደን ወይም አባሮ ለመያዝ ወይም ለማደን ሊሆን ይችላል። ⭕️#ምክንያትህ ምንም ቢሆን ሩጫህ የህልውና ጉዳይ ነውና ሩጫህን እንዳታቆም፣ ሙከራህን እንዳትገታ፣ ከትክክለኛው የመሮጫ መስመር እንዳትወጣ። 👉#ጀግናዬ ከአሏህ በኋላ እጣፋንታህ በእጅህ ላይ ነው። ⭕️በየለቱ ጠንክረህ የምትሮጥ ከሆነ የሚያድኑህን ስንፍና፣ ሰበበኝነት፣ ውጤት አልባነት፣ ጭንቀትና የበታችነት የማታመልጥበት ምክንያት አይኖርም። ✅#በምትኩ ጥንካሬን፣ ብርታትን፣ ስኬትንና ከፍታን በእጅህ ታስገባለህ። በጠዋት ተነስቶ ባሰበው መንገድ፣ በአቀደው ፍጥነት የሚጓዝ ሰው ከመዳረሻውም በፍጥነት ይደርሳል። ......በእያንዳንዷ ቀናት ወይ የተሻልክ እየሆንክ ትሔዳለህ....ወይም ደግሞ ከነበረህ እቋም እየወረድክ ትመጣለህ። ⭕️ሁሉም በእጅህ ነው። ጠዋት ተነስተህ ማደን ያለብህን አድነህ የተሻልክ እየሆንክ ትሔዳለህ ወይም በተኛህበት አዳኝህ መጥቶ እንዲያድንህ ትፈቅዳለህ። #ምርጫህ ወድቆ መቅረት ካልሆነ፣ እራስህን ወደ ጥልቁ መወርወር፣ ለአስከፊው የባሰ ትግል ህይወት አሳልፎ መስጠት ካልሆነ በጉብዝናህ ወቅት ንቃ.....በጥንካሬህ ጊዜ ሩጥ፤ በብርታትህ ወቅት ጠንክረህ ስራ....። «አምስት ነገሮችን ከአምስት ክስተቶች በፊት ተጠቀምበት የሚለውን ነብያዊ ትንቢት አስተውል‼️» ❶👉ወጣትነትን ከእርጂና በፊት ❷👉ጤናህን ከመታመምህ በፊት ❸👉ሀብትህን ከድህነትህ በፊት ❹👉ነፃነትህን ከመጨናነቅህ በፊት ➎👉ህይወትህን ከመሞትህ በፊት ተጠቀምበት ተብለሀል። ⭕️ስለዚህ ልብ በል ጀግናው‼️ ........የዛሬዋ ንጋት እንደመጪዎቹ ንጋት አይደለችም፤የዛሬዋ ቀን እንደ ነገና ከነገ ወዲያ አይደለችም ዛሬ ብርታትን ከመረጥክ፣ ዛሬ ለጥንካሬ ከተዘጋጀህ ቀጣዮቹም መልካም፣ አስደሳችና የተሻሉ ቀናት ይሆናሉ ኢንሻ አሏህ። ካለሆነ ግን መጥፎዎቹ አሰልቺ ቀናት ከፊትህ ይጠብቁሃል ። 🌱ወደፊት የሚወስዱህ እዚህ ያደረሱህ ደረጃዎች አይደሉም፤በቀድሞ ማንነትህ የተሻለ ስፍራ አትደርስምና... የተለየ መንገድ፣ የተለየ እርምጃ፣ የተጠና ፍጥነት ያስፈልግሃል። ✅ጥረትህን እንዳትገታ፤ ✅ሩጫህን እንዳታቆም፤ 👉ወይ ከአዳኙ አምልጥ ወይም ማደን የምትፈልገውን ነገር አሳደህ ይዘህ ተገኝ ነው የምልህ። ⭕️አሁን የት ላይ ነህ⁉️ ለጓደኞችህ ላክላቸውና ሁሉም ሰው ይማርበት ዘንድ ሸር ....Nur.....✍️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

✍……🖊 ....የባከነ ዘመን....🖊 የዘመን ቁልቁለት         በዘመን ተሟሽቶ፣ ወደ ምስራቅ ስሮጥ          ወደ ምዕራብ መሽቶ፣ ያዝኩት ባልኩት ቁጥር           አንድ እርምጃ  ሸሽቶ፣ ሲገፋኝ ስገፋው           ሲሸሽ ስከተለው፣ ሰዶ በማሳደድ          ቀኔን  ዘመን በላው።🖊