en
Feedback
شـبـاب السـلــفـــيـــيــن

شـبـاب السـلــفـــيـــيــن

Open in Telegram

👉«ሰለፍያ ቀጥተኛ የሀቅ መንገድ ብሎም አይነኬ ፅኑ ተራራ ነው።» ለአስተያዬትና እርማት

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel شـبـاب السـلــفـــيـــيــن

Channel شـبـاب السـلــفـــيـــيــن (@nuredinal_arebi) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 28 481 subscribers, ranking 2 503 in the Religion & Spirituality category and 1 222 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 28 481 subscribers.

According to the latest data from 06 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -187 over the last 30 days and by 9 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 15.16%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 7.50% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 316 views. Within the first day, a publication typically gains 2 135 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 44.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
👉«ሰለፍያ ቀጥተኛ የሀቅ መንገድ ብሎም አይነኬ ፅኑ ተራራ ነው።» ለአስተያዬትና እርማት

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

28 481
Subscribers
+924 hours
-287 days
-18730 days
Posts Archive
2026-09-06-22-50-42-770_Church.mp36.17 MB

📌حب الصحابة للخير قال الصحابي ابن عبّاس رضي الله عنهما: " إني لأمرُّ بالآية من القرآن فأفهمها، فأودُّ أن الناس كلهم فهموا منها ما أفهمُ". [فتح الباري، لابن رجب ٧٨/١] t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

መካ ጂዳ ሪያድ ለእህቶቻችን ማንኛውንም ስራ ከሰማችሁ ንገሩኝ ብዙ እህቶች በከባድ ችግር ውስጥ ነው ያሉት እባካችሁ በመረጃ እንኳን እናግዛቸው⁉️

«አሁን የመጡት መሪያችን (ዶር አብይ አሕመድ ዓሊ) የአባታቸውና የአያታቸው ስም የእኛ እምነት ስለማይመስል ከተመረጡ ጀምሮ እንቅልፍ አልወሰደንም» የአፓርታይዷ ቄስ የኢትዮጵያን መሪ ስሙ ከሱ ስም ጋር አንድ ዓይነት መሆን አለበት፣ መለየት የለበትም ብሎ ያምናል😎 ለማንኛውም ከእነዚህ ጋር ነው እየኖርን ያለነው። እነዚህ በሙስሊሙ ላይ በአከባቢያቸው እየፈጸሙት ያለ ግፍ መፈጠርን ያስጠላል። መረጃው ከ ትግራይ ሙስሊም ሚድያ ገፅ የተወሰደ ነው። ህወሓትም ቢሆን ከዚህ የተሻለ አመለካከት የለውም። በፌዴራል መንግስት ተገፍቻለሁ እያለ ዞሮ የክልሉን ሙስሊሞች በሃይማኖታቸው ሰበብ በያይነቱ የግፍ አይነት ያወርድባቸዋል። አቅሙ በቀለለበት በዚህ ጊዜ በደል ከመፈፀም ያልተመለሰ ድርጅት ያለ ተቀናቃኝ አገር ቢቆጣጠር ክፋቱ ከዚህም የባሰ ነው የሚሆነው። = የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

አሁን ደግሞ ከመርከዝ ኢብኑ አብባስ ሁነን ወንድማችን ኡስታዝ አቡ አዩብ ከኮምቦልቻ https://t.me/AbuOubeida?livestream=f283df569a83e901cc

«ኢኽዋን ማለት ይህ ነው ።» የግብፁ ፈርጥ ሸይኽ ሙዘሚል ፈቂሪ ሀፊዞሁሏህ ስሟቸው ይህን ጀግና t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

2026-09-06-08-10-48-357_Church.mp33.29 MB

​✨ የመርከዝ መናሩ ሱና ታላቅ የደስታ እና የምረቃ ጥሪ! ✨ ​📖 "ቁርኣንን የተማረና ያስተማረ ከሁሉ በላጭ ሰው ነው! ​ተማሪዎችን ከቃዒዳ ጀምሮ ቁርኣንን በነዞር የሚያስተምረው መርከዝ መናሩ ሱና
​✨ የመርከዝ መናሩ ሱና ታላቅ የደስታ እና የምረቃ ጥሪ!​📖 "ቁርኣንን የተማረና ያስተማረ ከሁሉ በላጭ ሰው ነው! ​ተማሪዎችን ከቃዒዳ ጀምሮ  ቁርኣንን በነዞር የሚያስተምረው መርከዝ መናሩ ሱና፤ ለረጅም ጊዜያት በፅናትና በትጋት ሲማሩ የቆዩ፣ ቃዒዳ ኑራኒያን በአግባቡ ያጠናቀቁ እና ቁርኣንን በነዞር ያኸተሙ ውድ ተማሪዎቹን ለመጀመሪያ ጊዜ (#1) በታላቅ ድምቀት ያስመርቃል። ​በዚህ ታላቅ የኸይር እና የደስታ መድረክ ላይ እርሶም የክብር ተጋባዣችን ነዎት! ​🎙 በዕለቱ በዳዕዋ እና በሙሀደራ የሚያደምቁን ውድ ኡስታዞቻችን፦ ❶❶ ​ሸይኽ አወል ቢን አሕመድ (ከተመቻቸው) ❶ ​ኡስታዝ ኸዲር ቢን አሕመድ ➋ ​ኡስታዝ አሚር ቢን ሙሀመድ ➌ ​ኡስታዝ አብዱል መሊክ ➍​ ኡስታዝ አቡ አዩብ ➎ ​ኡስታዝ አቡ ኢምራን ➏ ​ኡስታዝ አቡ ረያን ➐ ​ኡስታዝ አቡ ሉቅማን ➑ ​ኡስታዝ አቡ ሂባ ➒ ​ኡስታዝ አቡ ሀፍሷ ➓ ​ወንድም አቡ ማሒ 11,ወንድም አቡ ሹራ (እንዲሁም ሌሎች በርካታ ድንቅ ወንድሞቻችን የዕለቱ ድምቀቶች ይሆናሉ!) ​🌟 የዕለቱ ልዩ ልዩ ፕሮግራሞች፦ ●​በተማሪዎች የሚቀርቡ ልብ የሚነኩ የቁርኣን ቂርኣቶችና ልዩ ልዩ ፕሮግራሞች ●​በኡስታዞች የሚሰጡ ጠቃሚና አነቃቂ የዳዕዋ መልእክቶች ●​የተማሪዎች የምረቃና የሽልማት ሥነ-ሥርዓት ​📍 ቦታ፦ ከሚሴ በኢማሙ ሻፊዒይ መስጅድ 📅 ቀን፦ 01/ ነገ/ እሑድ ሰዓት፦ ጠዋት 2፡30 ጀምሮ
​🧕 ማስታወሻ፦ ለእናቶችና ለ እህቶች በቂና ምቹ ቦታ ተዘጋጅቷል።
ኧረ ምን ምን ይቀርባል ካሉን! ቤተሰብዎንና ወዳጅ ዘመድዎን ይዘው ይምጡ እና እዚያው ያዩታል ። አቡ ዑበይዳ t.me/AbuOubeida

«መንሐጀን አትንኩብኝ እኔን እንደፈለጋችሁ» .....ሰለፍያ.... ጥመት በሙሉ ደቆ በስርሽ ይሁን ብናኝ፡ ዝናሽ አፅናፉን ያዳርስ ስምሽ በአለም ይናኝ፡ እኔም በአንች ልታወቅ ስሞትም ጀነትን ይቅናኝ፡ አንች ነሽ የኔ ማንነት ስምሽ ነው የኔ ሰላሜ፡ የወንድነቴ መለኪያ የውስጤ ውብ ልምላሜ፡ ማንም በስሜት ጡዞ አይናገሩሽ አለሜ፡ አንች ነሽ የስንኘ ጫፍ አንች ነሽ ጌጥም ቀለሜ፡ ..ሰለፍያ..... ፍኪልኝ ልዩ መንሀጄ አድምቂኝ በፍቅርሽ ጠረን፡ በህግሽ ተቆጣጠሪኝ ፈር ለቅቄ እንዳልሔድ ምረን፡ ሰምና ወርቅ ነን እኛ መግለጫ ቃላት ያጠረን፡ አንችን እንድከተልሽ አሏህ ነው ያስተሳሰረን፡ .....ሰለፍያ.....!! ድመቂ ነግሰሽ በምሽት ሆነሽ እንደ ጨረቃ፡ በቀን እንደ ፀሀይ ፍኪ የለሽም አንች ፈረቃ፡ ማን አለ አንጀት የሚያርስ እንደ አንች የሚያጠረቃ፡ ምርጥ ነው በአንች የሚመረጥ ከሰዎች ቀድሞ የነቃ፡ ፍቅር ትግስት የሆንሽኝ መንሐጄ አንች ነሽ በቃ‼️ .....ሰለፍያ.... ከፍ በይ ለዘላለሙ ክበሪ በልቤ ዙፋን፡ ፅኑ ነን ታላቅ አለቶች፤ ማዕበል ደፍሮ እማይገፋን፡ ወላሒ በአንች ከፀናን፤ መቼም ነው ውሉ እማይጠፋን፡ ከጥመት ከሽርክ ጋራ፤ ምን አለን ከቶ እሚያጋፋን⁉️ ልጆችሽ በአንች ላይ ቆመን፤ ማንም ላይ በደል አንሰራም፡ ግን ደግሞ ልንገርሽ፤ አንችን ከመጡብን መልስ አለን ሰዎች አንፈራም፡ ለሚዲያ ጯሒ ለፌስ-ቡክ አርበኛ፡ ለፌክ ባለሙያ ለቲክቶክ ግንበኛ፡ ታብ ታብ አርጉ እያለ ሲያላዝን ለሚውል፡ እውቅና ለበላው ለዛ እማያስተውል፡ ለቁጥብያ ሙሪድ ለበናዕይ አሽከር፡ ሱሩርይ ሆኖ ጠሞ ሲከራከር፡ ቁርዓንና ሀዲስ በጥርሳችን ነክሰን፡ መልካሙን አረዳድ ከሰለፎች ጠቅሰን፡ ውብ መንሀጃችንን ሀሰዝቡ ላይ አንግሰን፡ ውድ ነፍሳችንን ለሐቅሽ ለግሰን፡ ላንች ክብር መኖር ይህ ነው አላማችን፡ አብረቅራቂ ሰንደቅ ከፍ በይ አርማችን፡ አንፈልግም ኢኽዋን የኮተት ገለባ፡ አንጠጋም ሱፍይ ለጫታም ገሪባ፡ ሱና ነው ሐቃችን ጀነት እስክንገባ፡ ስለሆነም ባንች አንደራደርም፡ ካንች ውጭ ሌላ መስመር አናሰምርም፡ በአንች ላይ እንፅና ሌት ቀን ሳንሳቀቅ፡ ባንድራሽን ይዘን ዱንያን እንላቀቅ፡ እንደ ጥመት ሙሪድ የለንም ኮፍያ፡ አቂዳ ሱና ነው ደዕዋ ሰለፍያ፡ ....በኑረዲን አል-አረብ..✍️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

እስኪ «ለሰለፍያ ያላችሁን ፍቅር» በግጥም ግለፁልኝ እኔ ላንብብልላችሁ⁉️

«ከጀርባዬ አንድ ግዙፍ ተራራ!!» --------------------------- .......✍አባትነት ግዙፍ ተራራ ነው ስሙ የደመቀ፡ ለልጁ ነፍስ ሰጭ ወኔው የታመቀ፡ በህይወት እስካለ ይደምቃል ልጅነት፡ ጋሻ መከታ ነው ማዕረግ ነው ወንድነት፡ የጥበብ መነሻ ይህ ነው አባትነት፡ ልጄ የሚል ጥሪ አባት ሲያስተጋባ፡ አበጥሮ ሲለይ ምርቱን ከገለባ፡ ልጁን እንዳይደፍረው ዱርየና ሌባ፡ አለኝ ማለት ብቻ ማዕረግ ነው አባ። «አባት ሳለ አጊጥ ጀንበር ሳለ ሩጥ» ........ ከኔ የበዙ ደስታዎች ጀርባ አንድ የሆዱን በሆዱ አምቆ የያዘ የኔን ሳቅ ብቻ በጉጉት የሚጠብቅ አንድ ግዙፍ ሰው አለ።ከኔ የወጣትነት ውበትና መሽቀርቀር ጀርባ አንድ የተበሳቆለ፣የተንከራተተ፣ያደፈ ልብስ የለበሰ አንድ እምቅ ወኔ ያለው ሰው አለ። ......ከኔ የለሰለሱ እጆች ጀርባ አንድ የሻከሩ መዳፎች ያሉት ሰው አለ። .......ከኔ በሁለት እግር መቆም እና በራስ መተማመን ጀርባ አንድ ጠንካራ ሰው አለ ። ........ከኔ የመኖር ትርጉም እና ሰው የመሆን ማንነት ጀርባ አንድ ብልህ ሰው አለ ። .......ከኔ ዛሬና የተስፋ ነገዎቼ ጀርባ አንድ ለኔ ሲል ትናንቱን ያጣ ሰው አለ ። ......ከኔ ሂዎት መቃናት ጀርባ አንድ የጎበጠ ሰው አለ ። ......➢ከኔ ምርጥ አባወራ የመሆን ምኞት እና ለሰው የመኖር ጥበብ ጀርባ አንድ ለቤተሰቡ እንደ ሻማ እየበራ እራሱን በማቃጠል ለቤቱ ብርሀን ሁኖ የቆመ ሰው አለ። ያ አንድ ሁኖ ብዙ የሆነ ጀግና ያ እናትም አባትም በመሆን ፍቅርን ሳይሰስት እየለገሰ ሁሌም እና በምንም ሁኔታ ከጎኔ ሳይለይ የመከታ ክንዱን የሚዘረጋልኝ ድንቅ ሰው ውድ አባቴ ነው ። «ሌላውን ተውት ካርድ እንደልብ በማይገኝበት በገጠር ህይወት እየገፋ ለኔ በቀጥታ ስልክ የደወለልኝ ማንም ሳይሆን አባቴ ነው ።» .....ከእማዬ የዘጠኝ ወር ሸክም በኋላ እስከ አሁኗ ጊዜዬ ድረስ አርግዞ አምጦ ወልዶ አዝሎ ልጄ አንቀልባህኮ ዛሬም ከወገቤ አልተፈታም መቼ ይሆን ከሀሳብ የማርፈው እያለ እንባው በአይኑ ሲያቀር አሁን እየፃፍኩ ከሆሄወቹ ጋር ምስሉ የሚታየኝ ይመስለኛል። «የኔ አባት ለማንም ክፉ እንዳልመኝ፣የማንም ማግኘት እንዳስደስተኝ፣ምቀኝነትና ክፋት ከውስጤ እንድጠፋ እና የተሰማኝን ነገር ሳልደብቅ በነፃነትና በድፍረት እንድናገር ሳትማር ያስተማርከኝ የኔ ንጉስ አንተ ነህ ዲግር ተሸክመህ ለኔ ድግሪ የምትጨነቅ የገጠር ግዙፍ ካንፓሴ አባ.....!!! ሁሉም አልፎ በልጅህ ኮርተህ እንደኖርክልኝ እንድኖርልህ አላህ ረጂም ሀያት ይስጥህ አባ ኢንሻ አሏህ ሁሉ ይሳካል አንድ ቀን ሰርፕራይዝ አለህ እሽ የኔ አባት እወድሀለሁ። .....ኑረዲን አል-አረብ http://t.me/nuredinal_arebi http://t.me/nuredinal_arebi

ሪዝቅ ገንዘብ ብቻ ነው ያለህ ማን ነው? || - ዶር ደጘሽ ብኑ ሸቢብ አልዐጅሚ = የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/UstazAbuMuhammed

Voice message00:27

🛑#ለባለፊልተሮች‼️ «አትመን ካሜራ»
ፊታቸው የአረብ እግራቸው የሱዳን፡ ያውም ፆታቸውን አሏህ እየረዳን፡
ቅባቱ ከቻይና ዊጉ ከአሜሪካ፡ ተቀይሯል አሉ ውበት በፈረንካ፡ ሁሉ በቅባት ነው ማንንም አትንካ፡ http://t.me/nuredinal_arebi http://t.me/nuredinal_arebi

«አትመን ካሜራ» የቻፕስቲክ ውበት ሲታጠብ ይጠፋል፡ የኔቃብ ድምቀት ግን እያደር ይፋፋል፡ አርቲፊሻል ነገር በበዛበት ዘመን፡ ብርቱካን ነኝ ያለው ስለሆነ ጎመን፡ ቀርበህ በአካል እንጂ በፊልተር አትመን፡ ፊታቸው የአረብ እግራቸው የሱዳን፡ ያውም ፆታቸውን አሏህ እየረዳን፡ ቅባቱ ከቻይና ዊጉ ከአሜሪካ፡ ተቀይሯል አሉ ውበት በፈረንካ፡ ሁሉ በቅባት ነው ማንንም አትንካ፡ የኔ ያልካትን ሴት ፈትሽ በጨው አጥበህ፡ ህይወት ስለሆነ አትለፍ ታዝበህ፡ ሰው ተጨካክኗል አረጋግጥ ቀርበህ፡ ንፁህ እቅድ ካለህ የስኬት አዝመራ፡ በደስታ ከፈለክ ህይወትን ልትመራ፡ ነገ የሚፀፅት መጥፎ ስራ አትስራ፡ ማንም ምንም ቢልህ አትመን ካሜራ፡   ነገርኩህ....✍️ኑር http://t.me/nuredinal_arebi http://t.me/nuredinal_arebi

መድ'ኸሊይ እንዳትሆን! ~ ሸይኽ ረቢዕ አልመድ'ኸሊይ - ረሒመሁላህ - እንደማንኛውም ዓሊም ናቸው። ይሄ ደረጃቸውን ዝቅ ማድረግ አይደለም። ከሳቸው የሚበልጡ ታላላቅ ዑለማኦችን በጭፍን መከተል አይፈቀድም ስንል ደረጃቸውን ዝቅ ማድረግ እንደማይሆነው ማለት ነው። ረቢዕ ልክ እንደሌሎቹ ዓሊሞች በየትኛውም ርእስ ላይ ቢሆን ፍፁም አይደሉም። በትንሽ በትልቁ በሸይኽ ረቢዕ ንግግር የሚያስፈራራ ቢኖር ራሱን ነው የሚሸውደው። ሱናን እከተላለሁ የሚል አካል በየትኛውም ዓሊም ላይ ያለው ምልከታ ለከት ሊኖረው ይገባል። አንድን ዓሊም መለኪያም፣ መስፈሪያም፣ መቁረጫም ማድረግ አይገባም። ሸይኽ ዐብዱልዐዚዝ አራጂሒይ - ሐፊዞሁላህ - የሌሎች ዓሊሞችን ንግግር ገሸሽ በማድረግ የሸይኽ ረቢዕን ንግግር በተለዬ የሚይዙ ስለሆኑ ሰዎች ሲጠየቁ እንዲህ ነበር ያሉት፦ يعني جعلوه رسولا، جعلوا ربيع رسولا، جعلوه رسولا، وهذا باطل، هذا باطل، ربيع ... يخطيء و يصيب و لا هو المييزان، الميزان: كلام الله و كلام الرسول، فمن قال: الميزان ربيع، هذا باطل. "መልእክተኛ አደረጉት ማለት ነው?! ረቢዕን መልእክተኛ አደረጉት?! ይሄ ውድቅ ነው። ይሄ ውድቅ ነው። ረቢዕ ... ይስታል፣ ያገኛል። ሚዛን አይደለም። ሚዛኑ የአላህ ንግግር እና የመልእክተኛው ንግግር ነው። ሚዛኑ ረቢዕ ነው የሚል ይሄ ውድቅ ንግግር ነው።" [ከድምፅ ቅጅ የተወሰደ ነው።] ስለዚህ የአልባኒይ፣ የኢብኑ ባዝ፣ የኢብኑ ዑሠይሚን፣ ወዘተ ንግግር በጭፍን እንደማይወሰደው የረቢዕ ንግግርም በጭፍን አይወሰድም። ረቢዕ በሌሎች መሻይኾች ላይ የሚናገሩትም በማስረጃ የተደገፈ ሲሆን ይወሰዳል፣ ካልሆነ ይጣላል። እንጂ ተናጋሪው ረቢዕ በመሆናቸው ብቻ ይወሰዳል ማለት አይደለም። አልባኒያ፣ ባዚያ፣ ዑሠይሚኒያ፣ ፈውዛኒያ፣ ... የሚባል መዝሀብ እንደሌለው መድ'ኸሊያ የሚባል መዝሀብም የለም። ስለዚህ አኢማዎችን በጭፍን የሚከተል ሐነፊይ፣ ማሊኪይ፣ ሻፊዒይ፣ ሐንበሊይ፣ ... መሆን እንደሌለብህ ሁሉ ረቢዕን በጭፍን የሚከተል መድ'ኸሊይ ልትሆንም አይገባም። እዚህ ላይ በቃል ደረጃ ችግር የለም። በተግባር ግን በተለያዩ መሻይኾች ላይ ድንበር ማለፍ ስላለ ጥንቃቄ እንዲኖረን ማስታወስ ነው የፈለግኩት። (ለጥጠው ሌላ ትርጉም ከሰጡ በኋላ በራሳቸው ምናብ ላይ ነብር ሆነው ለረድ የሚነሱ እንደሚኖሩ እጠብቃለሁ።) በተረፈ የኢኽ'ዋን ጀሌዎች እዚህ እንዳትመጡ። የዚህ ፅሑፍ ጭብጥ በቅርብም በሩቅም ከናንተ ጋር የሚገናኝ አይደለም። የኢኽ'ዋን ቡድን ዘንድ የአንጃቸውን ጥመት ከተናገርክ፣ የነ ሐሰን አልበና፣ ሰይድ ቁጥብ፣ ቀርዷዊይ፣ ... ጥፉ አካሄዶች ካስጠነቀቅክ፣ ... በኢኽ'ዋን ቫይረስ በተጠቁ አካላት ዘንድ አንተ መድ'ኸሊይ ወይም ጃ'ሚይ ነህ። ልክ የሙታን አምልኮን፣ በአላህ ሲፋት ላይ ማራቆትን ስታወግዝ "ወሃ'ቢይ" እንደምትባለው ማለት ነው። ለነዚህ ሸይኽ ዒምራን ዐሊይ ሪድዋን አልፋሪሲይ - ረሒመሁላህ - እንዳሉት እንላለን፦ قُـلْ لِلَّذِي اتَّـخَـذَ الـتَّـجَـهُّـمَ مَـرْكَـبًـا وَ رَآهُ دِيـنًـا و ارْتَــضَـاهُ مَـذْهَــــبًـا وَ لِـمَـذهَبِ الأَبـــرَارِ صَارَ مُـكَـذِّبـًـا إنْ كَانَ تَـابِـعُ أَحـمَــــدٍ مُـتَـوَهِّــبًـا *** فَـأَنـا الـمُــــقِـرُّ بِـأَ نَّـنِـي وَهَّـــابِي (ኢብኑ ሙነወር፣ ጥር 17/2016) = * የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

🎈..ለነዛ በጥፋታቸው ለሚዘባበቱት ይድረስ‼️ «ዞሮ ኒቃቢስቷን አትናገሩብን» ----------------------------- እሱ ከሳሽ ሆኖ፤ ላይፈ-ረድለት በሸንጎ ላይካስ፡ ምን አይነት እብደት ነው፤ እንደ ባለሙያ መሸከም ፈ'ረካስ፡ ግን እንደት አስቻለህ⁉️ የሀያሉን አምላክ ውብ ትዕዛዙን መጣስ፡ በእንደዚህ አይነት ሙድ፤ የተገኘው ዝና ቢጠፋ ባይመጣስ...⁉️ ....አታንሷት በክፉ...!! ለማንኛውም ግን፤ የታሪኬን አካል ሰንደቅ ምልክቴን፡ የደስታየን አውታር፤ ደወል ሆና ማንቂያ አላርም ስስቴን፡ ያችን ልዩ ወጣት፤ በተውሒድ የፀናች ጀግናዋን እህቴን፡ ሱናን የተረዳች፤ ደዕዋ እምታዳምጥ ኒቃቢስት እናቴን፡ ጥፋት ለመደበቅ፤ በቃላት ስንጠቃ ስትደጋገፉ፡ ያችን ጀግና ወጣት፤ በፍፁም በጭራች አታንሷት በክፉ፡ .....ኒቃቢስቷ ሆይ...‼️ ይጥላሽ ያፊዝብሽ ፍሬዝ ሱሪ ለባሽ፡ ዱሮም አይወድሽም ላንችም አይገባሽ፡ ጀግና ለጀግና ነው የሚፈላለገው፡ ፍሬዝ ጨፋሪ ነው ልቡ እሚፈልገው፡ አንችን ያጠንክርሽ እነሱን ያቅናቸው፡ መልካሙን ሁሉ ነው የምመኝላቸው፡ ግና ማንም ቢሆን ስህተትን ሲሰራ፡ ሲቀልድ ሲያላግጥ ቪዲዎ እያበራ፡ በጥፋቱ መጠን መልስ ይከተለዋል፡ እኛ እናደርሳለን አሏህ ያክመዋል፡ ምንም ወንጀላችን በዝቶ ቢከብደንም፡ ከሐቁ አቋማችን ማንም አይንደንም፡ ከኒቃቢስት ውጭ ፈላጊ አይደለንም፡ ፀጉሯን እያሳዬች የምትጨፍርን ሴት፡ መክሮና አስተምሮ ማግባቱ በሀሴት፡ የተከለከለ ባይሆንም ከጥንቱ፡ ሀራም ባይባልም ከስር መሰረቱ፡ የትናንቱ ጥፋት ዛሬ እንዳይደገም፡ ጥሩ ሆኖ ሳለ ራስን መገምገም፡ በጥፋት ላይ ይበልጥ የሚያበረታ ቃል፡ ዑስታዝ ነኝ ከሚል ሰው በጣም ያሳቅቃል፡ ሀዲስ ከሚናገር ይሔ ይጠበቃል⁉️ አሏህ ይመልሰን እጂጉን ይደንቃል፡ አስተውሎ ላየው ይህ ነገር ይጨንቃል፡ አላዋቂ እህቴን መናገር ባልደፍርም፡ አሏህ ይመልስሽ ይሔ ባንች አያምርም፡ አንተም ልክ እንደ ወንድ ቆፍጠን በልና፡ ፀጉርህን ተቆርጠህ ሱሪ አሳጥረህ ና፡ በርታ ጀገን በል በነብዩ ሱና፡ ዑስታዝ ብሎ ማለት እንደዚህ ነው ጀግና፡ .....እናማ..ንቃ... አስተምራት እንጂ ተውሒድና ሱና፡ ጭፈራ እንድታቆም በሐቅ እንድትፀና፡ ማስታወቂያ አትስራ ያንተ ሚስት ሆና፡ ሐፍረትና ፀባይ ሐያዕ የጎደላት፡ የሴትነት ግርማ ሰኪና የሌላት፡ እንደዚህ ሆናችሁ እሽ ምን እንበላት⁉️ ደበቅ አድርግና ከሰዎች እይታ፡ በፍቅር አባብለህ ገስፀህ በደስታ፡ ተውሒድ አስተምረህ በጧትም በማታ፡ ኒቃቢስት አድርጋት ሷሊህ ትሁንልህ፡ ስሜት አትከተል እውቅና አይሸንግልህ፡ «......ዞሮ ያም ሆነ ይህ......» በአሏህ ይሁንብኝ አይከጅልም ልቤ፡ የተምታታባት ሴት አትመጣም ባሳቤ፡ ምንም ትሁን ምንም ውስጤ ውልም አይለኝ፡ 🎈የሚመናቀር ሴት ወንድ ነው ሚመስለኝ‼️ ምንም መልኳ ቢያምር ለኔ አትታየኝም፡ እንኳን ልትማርከኝ ሴትም አትመስለኝም፡ ከኒቃቢስት ውጭ ልቤ አይደነግጥም፡ ከዛች ኮከብ ውጭ መንፈሴ እጅ አይሰጥም፡ እሷን ካላደነቅኩ ግጥምም አልገጥም፡ እሷ ነች በውስጤ የነገሰችብኝ፡ እሷ ነች ከሁሉም ለኔ እምትበልጥብኝ፡ ♦️ከኒቃቢስት ውጭ አሏህም አይሻብኝ፡ የወንድነቴ ጌጥ የልቤ ላይ ኮከብ፡ የጉዞዬ ጋሻ የመንገዴ መርከብ፡ ደምቃ የተዋበች በተውሒድ በሱና፡ እኔ እወዳታለሁ ኒቃቢስቷን ጀግና፡ የምድር ኮከብ ነች በኒቃቧ ደምቃ፡ ፕላኔት ነች እሷ ሀያዕ ላይ ተጣብቃ፡ የኔ አንደኛ ምርጫ ይህች ሴት ነች በቃ፡ በርቀት አይቻት ውስጤ ይረበሻል፡ 🎈የሱና እህቴ ነች የኔ ፊልድ ማርሻል፡ ምን ቢሳለቅብሽ ዱርዬና ቦርኮ፡ ያላየሽ ውበትሽን አያውቀውምኮ፡ እውቅናዬ ይርገፍ ይብጠልጠል ዝናዬ፡ ኒቃቢስት እህቴ እሷ ነች ጀግናዬ፡ አንችን ከማንም ጋር አላወዳድርም፡ ወላሒ በአንች ላይ አልደራደርም፡ የልቤ ላይ አርማ የአዕምሮዬ ሰንደቅ፡ ቃል አለኝ በግሌ ለክብርሽ ልዋደቅ፡ ስምሽን በክፉ ለሚያነሱሽ ውሾች፡ ፂም ለሚጋጥጡ ፋራና ቆሻሾች፡ ከማንም በስተፊት እኔ ነኝ ጠበቃሽ፡ 🎈ኒቃብሽ ብቻውን ለመመረጥ በቃሽ፡ የአሏህ አደራ ማህተም ነው ልብስሽ፡ አንችን እኔ እያለሁ ማነው የሚከስሽ!? እስኪ ማነው ወንዱ ስምሽን የሚጠራው፡ 🎈እኔ ነኝ ወንድምሽ በእህቴ እምኮራው፡ ህይወት እስካለሁ ካንች ልከላከል፡ በፅናት ላስጥልሽ ከውሾች መካከል፡ አለሁልሽ ልልሽ ቃል አለኝ ላምላኬ፡ አንች ነሽ የኔነት ውበትና መልኬ፡ ከማንም በስተፊት እኔ አከብርሻለሁ፡ የናቀሽን ሁሉ መልስ እሰጠዋለሁ፡ ባንች ከመጡብኝ አልፈራም እውቅና፡ አንችን ከነኩብኝ የለኝም ልቅና፡ ስሜት የሚከተል የጭብጨባ ካዝና፡ ልቡን ላሳበጠው የቲክቶክ ላይ ዝና፡ በእህቴ እየመጡ የምን ሙዋዘና፡ አውርድበታለሁ ግጥም ዘነዘና፡ ኒቃብ ልበሽ ብሎ ኢስላም ነው ያፈካሽ፡ እስኪ ማነው ወንዱ አንችን የሚነካሽ፡ ሱሪ ገታች እና የቲክቶክ ርካሽ፡ ኒቃቢስት እህቴን ሊዘልፏት አልፈቅድም፡ በህይወት እስካለሁ ይህንን አሎድም፡ እህቴን የሚንቅ አላስተናግድም፡ ማነው ከቶ ባንች የሚዘባበተው፡ ማነው ህሌና ቢስ ሰው መሆን ያቃተው፡ ኒቃቢስት እያለ በጂምላ እሚሳደብ፡ የማነው ልበ-ቢስ ያለፈብሽ ገደብ፡ ንገሪኝ ስም ጠርተሽ የናቀሽ ይቀንደብ፡ ካላመመው በቀር ካላቅለበለበው፡ ህሌናው ተምታቶ ስሜት ካልጋለበው፡ ኒቃቢስት እህቴን በክፉ እሚያስበው⁉️ በሉ እስኪ ንገሩኝ እኔ ልለብልበው፡ ቢሻው በሚኒሽር ሲፈልግ በጓንዴ፡ ሲፈልግ በሽጉጥ ቢመዝም ጎራደ፡ ለእምነቴ እና ላንች ዝግጁ ነው ክንዴ፡ ወንድ ልጅ ለእህቱ መፋለም ካቃተው፡ ወኔው ካልተነሳ ድፍረት ካልሸተተው፡ እሱ ወንድ አይደለም ከቁጥርም አይገባ፡ ፈሪ ቦቅቧቃ ነው እበት ነው አዛባ፡ እንደዛ ነው በቃ ምንም ሳይዛባ፡ ፋሬው ተነስቶለት የቀረ ገለባ፡ አትፎክት አትሟጭር ሳይበላ ለሚያክህ፡ በሐቁ ላይ ፅና ወንድ ሁን እባክህ፡ እንደዚህ አይደለም ያንተነቱ መልክህ፡ መሆንም የለበት መ'ገለጫ ልክህ፡ ምንም የሚንጫጫው ቲፎዞ ቢበዛም፡ ወላሒ አጨብጫቢ አንድ ኸይር አይገዛም፡ ይልቅ ተስተካከል ነገ ዛሬ አትበል፡ ስሜትክን ተቃረን እውነቱን ተቀበል፡ አረፉ አሽቃባጮች ነገር አራጋቢ፡ የፊትና ማገዶ ብርድ ልብስ ጋቢ፡ እህቴን አትስጧት ሰድቦ ለሰዳቢ፡ አንችም ተረጋጊ በቃ ተዓደቢ፡ ሐቁን መናገር ነው በኛ ላይ ያለብን፡ በተረዳነው ልክ አንድ ሳይቀርብን፡ ዞሮ ያም ሆነ ይህ ኒቃቢስቷን ኮከብ አትናገሩብን፡ ....በኑረዲን አል-አረብ..✍️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi