uz
Feedback
شـبـاب السـلــفـــيـــيــن

شـبـاب السـلــفـــيـــيــن

Kanalga Telegram’da o‘tish

👉«ሰለፍያ ቀጥተኛ የሀቅ መንገድ ብሎም አይነኬ ፅኑ ተራራ ነው።» ለአስተያዬትና እርማት

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali شـبـاب السـلــفـــيـــيــن analitikasi

شـبـاب السـلــفـــيـــيــن (@nuredinal_arebi) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 29 136 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 2 514-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 1 171-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 29 136 obunachiga ega bo‘ldi.

17 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -249 ga, so‘nggi 24 soatda esa 14 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 17.55% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 9.17% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 5 111 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 670 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 63 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
👉«ሰለፍያ ቀጥተኛ የሀቅ መንገድ ብሎም አይነኬ ፅኑ ተራራ ነው።» ለአስተያዬትና እርማት

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 18 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

29 136
Obunachilar
+1424 soatlar
+307 kunlar
-24930 kunlar
Postlar arxiv
«ሴት ልጅ» ----------- ሴት ልጅ ጌጥ ነች በተለይ ደግሞ በንፁህ አቂዳ ቆማ ፣ተውሒድና ሱናን ቀምማ፣ከለበሰች የኒቃብ ሸማ..የሁለት ሀገር እንቁ፣አስተዋይና ንቁ ማለት #ሴት_ልጅ ነች። ወንድ
«ሴት ልጅ» ----------- ሴት ልጅ ጌጥ ነች በተለይ ደግሞ በንፁህ አቂዳ ቆማ ፣ተውሒድና ሱናን ቀምማ፣ከለበሰች የኒቃብ ሸማ..የሁለት ሀገር እንቁ፣አስተዋይና ንቁ ማለት #ሴት_ልጅ ነች። ወንድ ሆይ በፈለከው ልክ ራስህን ብትንከባከብ ሰውነትህ የሚዋበው ሴት ልጅ ስትመግብህ ነው ...የምትመግበው አካልህን ብቻ ሳይሆን መንፈስህንም ጭምር ነውና ሴት ልጅ በረከት ነች። ደምቀህ እንድትወጣ የምታስጌጥህ፣ ውብ አድርጋ ቀርፃ የምትኩልህ፣ ወንድነትህን ፣ንጉስነትህን በኩራት የምትነግርህ ...ሴት ነች። ሴት ልጅ ማረፊያ ናት። ሀገር ከነግዝፈቷ በሴት ትጠራለች። ዱንያ ሙሉ ከነ በረከቷ በሴት ነው የምትወከለው ይህ የሆነው ማረፊያ መጠለያ ስለሆነች ነው። ⭕️#ሴት_ልጅ ‼️ የልብ ሰላም፣ የአእምሮ ረፍት፣ የጉልበት ብርታት፣ የፅናት ሰንደቅ፣ የአንደበት ለዛ፣ የአነጋገር ቅላፄ ትሰጣለች። ✅ወንድ ልጅ ወንድ ለመሆን ሴት ልጅ ያስፈልገዋል። ሲግል የምታረጋጋው፣ ሲታወክ የምትደግፈው፣ ሲሳሳት ታግሳ የምታልፈው፣ ሲደናቀፍ የምትደጉመው። ሴት ልጅ የወንድ ልጅ #ሁለንተናዊ የስኬት መስመር ነች። በአጠቃላይ ሰው ሰው ለመሆኑ መሰረት የተጣለበት አንዱ መገለጫ በሴት በኩል ማለፍ በመቻሉ ነው። ....አወ ሰው ሰው የሆነው በሴት ነው። ✅ሴቶች ሆይ አደራ ይህን እንቁ ሴትነታችሁን ጠብቁት ሴት ሁኑና ወንድ ቅረፁልን። 👉ወንድን ፀንሳ የወለደች ሴት ትባረክ አሚን። ....የፋሩቅ-አባት...✍️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

«ሴት ልጅ» ----------- ሴት ልጅ ጌጥ ነች በተለይ ደግሞ በንፁህ አቂዳ ቆማ ፣ተውሒድና ሱናን ቀምማ፣ከለበሰች የኒቃብ ሸማ..የሁለት ሀገር እንቁ፣አስተዋይና ንቁ ማለት #ሴት_ልጅ ነች። ወንድ ሆይ በፈለከው ልክ ራስህን ብትንከባከብ ሰውነትህ የሚዋበው ሴት ልጅ ስትመግብህ ነው ...የምትመግበው አካልህን ብቻ ሳይሆን መንፈስህንም ጭምር ነውና ሴት ልጅ በረከት ነች። ደምቀህ እንድትወጣ የምታስጌጥህ፣ ውብ አድርጋ ቀርፃ የምትኩልህ፣ ወንድነትህን ፣ንጉስነትህን በኩራት የምትነግርህ ...ሴት ነች። ሴት ልጅ ማረፊያ ናት። ሀገር ከነግዝፈቷ በሴት ትጠራለች። ዱንያ ሙሉ ከነ በረከቷ በሴት ነው የምትወከለው ይህ የሆነው ማረፊያ መጠለያ ስለሆነች ነው። ⭕️#ሴት_ልጅ ‼️ የልብ ሰላም፣ የአእምሮ ረፍት፣ የጉልበት ብርታት፣ የፅናት ሰንደቅ፣ የአንደበት ለዛ፣ የአነጋገር ቅላፄ ትሰጣለች። ✅ወንድ ልጅ ወንድ ለመሆን ሴት ልጅ ያስፈልገዋል። ሲግል የምታረጋጋው፣ ሲታወክ የምትደግፈው፣ ሲሳሳት ታግሳ የምታልፈው፣ ሲደናቀፍ የምትደጉመው። ሴት ልጅ የወንድ ልጅ #ሁለንተናዊ የስኬት መስመር ነች። በአጠቃላይ ሰው ሰው ለመሆኑ መሰረት የተጣለበት አንዱ መገለጫ በሴት በኩል ማለፍ በመቻሉ ነው። ....አወ ሰው ሰው የሆነው በሴት ነው። ✅ሴቶች ሆይ አደራ ይህን እንቁ ሴትነታችሁን ጠብቁት ሴት ሁኑና ወንድ ቅረፁልን። 👉ወንድን ፀንሳ የወለደች ሴት ትባረክ አሚን። ....የፋሩቅ-አባት...✍️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

እህታለም «ጠንካራ ሁኝ ህመምን በፈገግታ መደበቅ ከእናትሽ ተማሪ እሽ!?» t.me/nuredinal_arebi

⭕️«የማይናገሩት ግን የሚያለቅሱበት ድብቁ ዓለም!» ▢ ራስን በራስ የማርካት ምስጢራዊ ቀውስ እና ደረጃ በደረጃ የሚተገበሩ መፍትሔዎች! ----------- ✏️ትርጉም እና ጥንቅር፦አቡ ሱፍያን 📑PDF ቅንብርና ዲዛይን፦ ሙሐመድ አሕመድ ~ t.me/Sle_qelbachn1 t.me/Sle_qelbachn1

ራስን በራስ ማርካት💋 -- ❞سَمِعْتُ أَنَّ قَوْمًا يُحْشَرُونَ وَأَيْدِيهِمْ حَبَالَى، فَأَظُنُّ أَنَّهُمْ هَؤُلَاءِ الَّذِينَ يَسْتَمْنُونَ بِأَيْدِيهِمْ❝ «የሆነ ሰዎች እጆቻቸው አርግዘው (አብጠው) የውመል ቂያማ እንደሚቀሰቀሱ ሰምቻለሁ፤ እነሱም እጆቻቸውን ተጠቅመው ራሳቸውን የሚያረኩት ሳይሆኑ አይቀሩም ብዬ አስባለሁ።» 📜ታላቁ ታቢዒይ ዐጣእ (ረሒመሁላህ)t.me/Sle_qelbachn1

يا شباب المسلمين النوم عن صلاة الفجر باستمرار من علامة قسوة القلب ، وعدم التأثر لضياعها من علامة موت القلب በፈጅር ሶላት ወቅት ያለማቋረጥ መተኛት የደነደነ ልብ ምልክት ከመሆኑም በላይ በማለፉ አለመቆጨት ደግሞ ልባችን እንደሞተ አመላካች ነው። ...nur...✍️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

ለሳዑድ እና ለሀቅ ጠላቶች አድርሱልኝ⁉️ «ባንዲራሽ ከፍ ይበል» ተጓዥ በቀጥታ በነብዩ ትውፊት፡ ከፍ ይበል ባንድራሽ በጠላቶችሽ ፊት፡ መነስነስ ባህሪው ነው ሙ,ጂሪምና ወንፊት፡ የሙስሊሙ ረዳት የሚስኪኖች ደራሽ፡ የዑለሞች ምድር የነብያት ወራሽ፡ «ላኢላሀ-ኢለሏህ» ከፍ ይበል ባንድራሽ፡ ግልፅ የሚታይ ክህደት የለብሽምና፡ አሏህ ይጠብቅሽ በተውሒድ በሱና፡ ስራሽን መዘርዘር አያስፈልግም ቃል፡ አንችን ለማመስገን ባንድራሽ ይበቃል፡ በጥላቻ ሰክረው ስምሽን ቢያጠፉት፡ ከካፊር ጋር ቆመው ክብርሽን ቢዘልፉት፡ ዋሽተው ታሪክሽን ጠላት ጋር ቢሰፉት፡ ሲሰድቡሽ ቢውሉ ከሽዓ ወግነው፡ የተውሒድን መርህ ስለማያውቁ ነው፡ ለአህባሽ፣ለኢኽዋን ደግሞም ለሱፍያ፡ ግልፅ ነው ይጠላል ደዕዋ ሰለፍያ፡ የተውሒድ ጠላቶች አወ ይጠሉሻል፡ ግን ትንኝ ዝሆንን መቼ ይረብሻል፡ የነብዩ ኢብራሒም የፀሎት ማድረጊያ፡ የዒስማኢል ድንቅ መረጋጊያ፡ የሙሀመድ አሚን ግሩም መመሸጊያ፡ ጋሻ ጦር ሰይፍ ነሽ የጠላት መዋጊያ፡ አርማወችሽ ናቸው መዲናና መካ፡ ጥላ ሆነው ላንች ገዝፈዋል ከዋርካ፡ ከአሏህ ነው ቅጣቱ አንችን የሚነካ፡ በድርን ጦረኞች በመላክ ያጀበ፡ በጠላቶቹ ላይ እሳት ያዘነበ፡ ዛሬም ይላክበት ጦይረን አባቢል፡ ሊያጠቃሽ ያሰበን ሀቅን ክዶ እቢ-ቢል፡ በተውሒድሽ ፀንተሽ ሁሌም ተከበሪ፡ የአሏህን ጠላት ቅልጥሙንጨስበሪ፡ ጀሊሉ ይገዝሽ እንዳትደፈሪ፡ የአቡ-በክር የዑመር ንግስና መነሻ፡ የዑስማን የአልይ ግሩም መዳረሻ፡ የሀበሻው ቢላል ውብ የአዛን መውጫ፡ የበረከት ምድር የዘምዘም መጠጫ፡ አንች ታሪክ አለሽ በሁሉም አቅጣጫ፡ ሶፋና መረዋ ከዕባ ነው ሀረምሽ፡ አያልቅም ቢቀዳ ይደንቃል ዘምዘምሽ፡ ድንቅ ነው ተግባርሽ በአለም የሚሰማ፡ ሁሉም ይጠብቃል የአዛንሽን ዜማ፡ ኢስላም ነው ውበትሽ አብረቅራቂ ግርማ፡ ላኢላ-ኢለሏህ ተደርጎልሽ አርማ፡ ልዩ አሻራችን ነሽ የሙስሊሞች ፊርማ፡ አንችን የሚጠላ ይሆናል ቄጠማ፡ ሙናፊቁ ሁሉ በአንች ቢረባረብ፡ ልጋጋሙ ሁሉ ምንም ቢዝረበረብ፡ ማንም ቢቀጥፍብሽ በሚዲያ ተረብ፡ ቢንጫጫ ቢወራጭ አጀም ቢሆን አረብ፡ ጋሻ ነው ኸይራትሽ የተውሒድሽ መረብ፡ የሰከረው ሁሉ ነገር እየበላ፡ ጥፋትሽን ለሚመኝ መሀይም ወደላ፡ ተደብቆ እሚፅፍ ስሙን የማያሳይ፡ የአቂዳ ጠላት የሚዲያ አስመሳይ፡ ከእውቀት የነፃ በዘር የሚባላ፡ ሲቀጥፍ የሚውል በቃለ-መሀላ፡ ዋጋ የሌለው ነው ሰላላ-መላላ፡ ከሽርክ የፀዳሽው የሙስሊሞች ሀገር፡ ደስታ ይሰማኛል ስለ አንች ስናገር፡ ወደብ ነሽ ለሁሉ የትም ለመሻገር፡ ጣዖት አምላኪወች ከየትም ቢጠሉሽ፡ ስምሽን አጥቁረው ምንም ነገር ቢሉሽ፡ ዋጋ እሚከፍሉልሽ ጀግና አሊሞች አሉሽ፡ እነ ፈውዛን ናቸው አንችን የወከሉሽ፡ ማህፀንሽ ለምለም መክኖ አያውቅም ጭራሽ፡ ነብይ ፈልቆበታል የኢብራሒም ወራሽ፡ ደዕዋው ተሰራጭቷል በአለም አዳራሽ፡ እናከብርሻለን አንሰማም ወፍ ዘራሽ፡ ዘምዘምን ሀጀራ እንደገደበቻት፡ የጠቢባን ምድር ሳዑዲያ ይቻት፡ የማያልቅ ኒዕማ የሚፈልቀው ውሀ፡ አለም ያስደመመች አረቢያን በረሀ፡ ጠላቶች የሚሏት የበረሀ ገነት፡ ተናገር አዳሜ ይህን መራር እውነት፡ ግርማዋ የሆነ የዑሁድ ተራራ፡ ጋሻ ሰንደቅ ሆኗት የአረፋ ጎራ፡ አሏህ አሳምሯት በሚደንቅ ስራ፡ ሙናፊቅ ምን ይበል ከሀዲ ምን ያውራ‼️
ሙሽራው ነብዩ ሶሀባው ሰርገኛ፡ የጀነት ተራራ የዑሁድ መገኛ፡ ቅድስት ነች ምድሯ ምን እናድርግ እኛ፡
የውብ ዘምዘም ውሀ የወህዩ መፍለቂያ፡ የመሀመድ አሚን የህይወት መድመቂያ፡ ባንድራሽ ይበቃል ለአማኝ ማነቃቂያ፡ ለቁጥር ያደክማል ቢነገር ኸይራትሽ፡ ያንች መታወቂያ ይህ ነው ምልክትሽ፡ ላኢላሀ-ኢለሏህ እንደት ይደበቃል፡ የሚውለበለበው ባንድራሽ ይበቃል፡ ✍️በኑረዲን አል-ዓረብ     http://t.me/nuredinal_arebi http://t.me/nuredinal_arebi

✅ውሀ-ልክህን ጠብቅ‼️ -------------------------- ህይወት ተራ ነገር ነች እናም ለመኖር የብዙ ሰዎች ተሞክሮ ሳይሆን የሚያስፈልግህ የራስህ ውሀ ልክ ነው። ብዙ ሰዎች ጀምረው የሚፈርስ
✅ውሀ-ልክህን ጠብቅ‼️ -------------------------- ህይወት ተራ ነገር ነች እናም ለመኖር የብዙ ሰዎች ተሞክሮ ሳይሆን የሚያስፈልግህ የራስህ ውሀ ልክ ነው። ብዙ ሰዎች ጀምረው የሚፈርስባቸው copy እያደረጉ ነው።ከሰማኸኝ የከበደ ልብስ ለከበደ እንጀ ለኑረዲን አይሆንም። ...ራስህን ከሆንክ በራስህ ልክ ትቆማለህ። ...በራስህ ልክ ትቀመጣለህ። ...በራስህ ልክ ትኖራለህ። ⭕️አስተውል‼️ ❝ድንችን እሳት ይፈረካክሰዋል።❞ «እንቁላልን ግን እሳት ያጠነክረዋል።❞ ጀግንነቱ ራስህን መለየት ላይ ነው። ድንች ነህ⁉️ ወይስ እንቁላል⁉️ .....ኑረዲን አል-አረብ.... t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

👉ለምንድነው እንደዚህ የማዝነው የወንድሞቼን ችግር እኔ ብሸከምላችሁኮ እመኝ ነበር ....‼️ ወንድ ልጅ ሲከፋው ------------------- ለፍቶ ደግሞ ሲዝል መሔጃ ሲጠፋው፡ ብቻውን ተክዞ ችግሩ ሲገፋው፡ ወዳጅ ያማክራል ወንድ ልጅ ሲከፋው፡ የጭንቀትን መጠን አውቀዋለሁ እኔ፡ አይቸዋለሁኝ ተጨማትሮ ጎኔ፡ ግን ተረባርቦልኝ የዋሁ ወገኔ፡ ዛሬ አልሀምዱ ሊላህ ለዚህ በቅቻለሁ፡ ቅርብ ነው ትዝታው ጠንቅቄ አውቀዋለሁ፡ ......የሐቅ ሰው.... ወንድ ልጅ ካልከፋው አማራጭ ካላጣ፡ በችግር በረሀብ በእዳ ካልተቀጣ፡ ወይም ደግሞ ታሞ ደክሞ ካልተሰጣ፡ እንኳን ሚዲያ ላይ ካገሩም አይወጣ‼️ .....ብችልበትማ‼️ አማናን መቀበል ያላሀሳብ መቀርጠፍ፡ ብችልማ ኖሮ.. እንደ ሰው ቃል ማጠፍ፡ መቼ ስጨናነቅ መቼ ስንጠፈጠፍ፡ .....እ... ሰላም ቢኖርማ #እዳን ተሸክሞ፡ ሰው አያብድም ነበር ከጤንነት ደክሞ፡ ከሀሳብ ወንድ ልጅ አይድንም ታክሞ፡ የሰው ደይን ጦር ነው ህሌናን ይወጋል፡ እንቅልፍ አያስተኛም እጂጉን ያሰጋል፡ ግን አማራጭ ጠፋ እንደት ይደረጋል፡ የሰው ልጅ መዳኒት ሰው ነበረ ዱሮ፡ አሁን በሽታ ነው ሰው ተቀይሮ፡ ችግርን መረዳት መተጋገዝ ጠፍቷል፡ ጭካኔና በደል አውሬነት በርክቷል፡ ብችልበትማ ያለኝን መደበቅ፡ ውስጤ ቢኖርማ የጭካኔ ለበቅ፡ መች እፈልግ ነበር የሰወችን መላ፡ ለጊዜያዊ ህይወት ለሚፈርስ ገላ፡ ለጥቅም ያደረ ቢኖረኝ ህሌና፡ ድሀ አልሆንም ነበር አሎጣም ጎዳና፡ አልዘረጋም ነበር እጀን ለልመና፡ ማይፈታ ገመድ ጠንካራ ሰንሰለት፡ የእድሜ ልክ ፀፀት ሀራራና ግለት፡ እሳት ነው ይፋጃል የሰው ልጅ ፊት ማለት፡ የአርሹ ባለቤት ሲለመን ይወዳል፡ የሰው ልጅ ግን ደግሞ ስታጣ ይከዳል፡ በህይወት ስንኖር ኑሮ በኛ ከትማ፡ ከሰው ፊት አቁማን በችግር አትማ፡ ደስታና ሀዘንን ስንት ነገር አየን፡ ጠላት መሳይ ወዳጅ፤ ወዳጅ መሳይ ጠላት ስንት ሰዎች ለየን፡ ካልተጠበቀ ሰው፤ ክፉ ነገር ሰምተን ስንቴ ተሰቃየን፡ ሁሉን ጠጥተነው፤ በፈገግታ አልፈነው ስንት ዘመን ቆየን፡ ...ብቻ አልሀምዱ ሊላህ... ለጊዜው ነው እንጂ ሁሉም ነገር ያልፋል፡ መልካሙም መጥፎውም ልብ ላይ ይፃፋል፡ አብሽሩ ወገኖች እዳ ያለባችሁ፡ ከሰው መመለስ መክፈል ያልቻላችሁ፡ አሏህ ክፉ አይሰራም አብሽሩ አይዟችሁ፡ የአለማት እዝነት የሁሉ ሙረቢ፡ የሰላሙ አለቃ የሁላችን ዋቢ፡ ተበድረው ነበር ተቸግረው ነቢ፡ እናም መጥፎ አይደለም ተበድሮ መስራት፡ ነግዶ ለማትረፍ ህይወትን ለመምራት፡ በቀን ስራ መድከም ወይም በኩንትራት፡ እስኪ እንጠጋገን በተቻለን አቅም፡ ነገ የኛም ክስተት ምን ይሁን አናውቅም፡ ለተጨነቀች ነፍስ በፀሎት እንጠንክር፡ እስኪ እንተዛዘን ነገር ሳናሳክር፡ ነውርኮ አይደለም ችግረኛን መርዳት፡ ለተጠማ ፍጡር ንፁህ ውሀ መቅዳት፡ የወኔድምን ችግር ለሌሎች ማስረዳት፡ .....ነውርኮ አይደለም.... መንፈሱ ሲጨነቅ መሔጃ ሲጠፋው፡ ግልፅ አይናገርም ወንድ ልጅ ሲከፋው፡ 🌷አሏህ ይፈርጂህ ወንድማለም አብሽር በተቻለን አብረንህ ነን ያንተ ችግር ችግራችን ነው። ....በኑረዲን አል-አረብ http://t.me/nuredinal_arebi http://t.me/nuredinal_arebi

ምነው በኖረኝና ከመፃፍህ በፊት አንተ ሳታውቅ ከፍየልህ ቢሆን....አይ...ወንድ ልጅ (በተለይ የሱና ሰው)ከሰው ፊት የሚወጣው ችግሩ ከምን ደረጃ ሲደርስ እንደሆነ አውቀዋለሁ ግና.....

ከሰሞኑ በውስጥ መስመር ከደረሱኝ እጅግ ልብ የሚነኩ መልእክቶች መካከል፣ ከላይ የምትመለከቱት የወንድማችን መልእክት አንዱ ነው። ይህ ወንድማችን በዚህ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ በበጎ ተሳትፎው የምናውቀው
ከሰሞኑ በውስጥ መስመር ከደረሱኝ እጅግ ልብ የሚነኩ መልእክቶች መካከል፣ ከላይ  የምትመለከቱት የወንድማችን መልእክት አንዱ ነው። ይህ ወንድማችን በዚህ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ በበጎ ተሳትፎው የምናውቀው ሰው ነው። ነገር ግን ዱኒያ ፈታኝ ናትና፣ የልጆች አልባሳት ቡቲክ ስራ ውስጥ ገብቶ በደረሰበት ከባድ ኪሳራ ምክንያት አሁን ላይ እጅግ ከባድ የዕዳ ሸክም ወድቆበታል። በአሁኑ ሰዓት የሰው ዕዳ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴውን አግቶት፣ የቤት ኪራይ መክፈያና የልጆቹን ቀለብ ማቅረቢያ እንኳ አጥቶ በእጅጉ ተጨንቋል። ዱኒያህ ይህችው ናት...ዛሬ እኛ መርዳት የምንችልበት አቅም ሲኖረን፣ ነገ የእኛ መድረሻ ምን እንደሚሆን አናውቅም። 📌 የባንክ አካውንት ንግድ ባንክ (CBE) 1000340662583 አቢሲኒያ ባንክ 10686369 አዋሽ ባንክ 014250816807603 የአካውንቱ ስም፦MEHAMMED BEDIRU NASIR 📌 እሱን ቀጥታ አግኝታችሁ ለማነጋገር፦ 0900076123 @AbuMeryem

የልብህን ሰዎች ሁሉ ለአደባባይ አታቅርብ‼️ --------------------------------------- ውድ ነገሮች ጫጫታን አይወዱም። ወርቅ በመሬት ውስጥ ይገኛል፤ ዕንቁ በባሕር ጥልቀት ውስጥ እንደሚገኝ ሁሉ እውነተኛ ፍቅርም በልብ ውስጥ ታትሞ ይኖራል። የኔ ትውልድ ግን ሁሉን ነገር ለአደባባይ ማቅረብን እንደ ድፍረት እያስተማረን ነው፤ ሁሉን መናገርን እንደ ታማኝነት፣ ሁሉን ማሳየትን እንደ ፍቅር እያስለመደን ነው። ይህ ፈፅሞ ስህተት ነው ብዬ አምናለሁ። የምትወደው ሰው የነፍስህ የውስጥህ ሐሴት እንጂ የሚታይ ወይም የሚሸጥ ዕቃ አይደለም። የውስጥ ሰላምና ሀሴት ደግሞ በሚስጥር የሚቆለፍ እንጂ በየመንገዱ ለሚያልፍ ሰው ሁሉ የሚታይ ርካሽ ሳይሆን በክብር የሚጠበቅ እንቁ ነው። #አስታውስ...‼️ የሚጠላህ ሰው በጥንካሬህ ላይ አያተኩርም፤ ልብህ በሚያምበት ቦታ ላይ ያነጣጥራል። የሰው ትልቁ ድክመቱ ገንዘቡ ወይም ሥልጣኑ ሳይሆን፣ ከልቡ የሚወዳቸው ሰዎች ናቸው። ሁሉም ፈገግ የሚልልህ ወዳጅህ አይደለም፤ ሁሉም የሚያጨበጭብልህ በደስታህ የተደሰተ አይደለም። አንዳንዶች የሚቀርቡት የልብህን በር ለመክፈት ሳይሆን..... የሚያቆስሉህን መስኮት ለማግኘት ነው። ስለዚህ ጸጥ ብለህ ውደድ። በጥልቅ ጠብቅ። የቤትህን በር ቁልፍ ለማንኛውም ሰው እንደማትሰጥ ሁሉ..ለሁሉም ሰው የልብህን ካርታ አትስጥ። የነፍስህን ቁልፍ በጥንቃቄ ጠብቅ። አንዳንድ ፍቅሮች የሚያምሩት በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ስለተለጠፉ አይደለም...ከክፉ ዓይን ተጠብቀው ስለኖሩ ነው። አንዳንድ ግንኙነቶች የሚጸኑት በብዙ ምስክሮች ፊት ሳይሆን፣ በጸጥታ ውስጥ ስለተገነቡ ነው። ሰው ሁሉ የደስታህን ምንጭ ማወቅ አያስፈልገውም፤ ሰው ሁሉ የእንባህን ምክንያት ማወቅም አያስፈልገውም። የልብህን ቅዱስ ስፍራ ለሚያከብሩት ብቻ ክፈተው። ምክንያቱም የምትወዳቸውን ሰዎች መደበቅ ፍቅርን መንፈግ አይደለም፤ ፍቅርን መጠበቅ ነው። 👉 የሚያምረው ነገር ሁሉ ለአደባባይ አይወጣም፤ አንዳንድ ውበቶች በዝምታ ውስጥ እንጂ በጩኸት ውስጥ አያብቡም። 👉ይህ የእኔ እይታ ነው። ....ኑር....✍️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

👉ሙሀረም ወር እንፁም لقول النبي ﷺ: (أفضلُ الصِّيامِ بعد شهرِ رمضانَ، شَهرُ اللهِ المُحرَّمُ). ከረመዷን ውጭ ካሉት ወራቶች ሁሉ የሙሀረም ወር መፆም እጂግ በላጭነት አለው። t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

2026-06-16-22-53-31-751_Church.mp36.62 MB

Repost from Dr. Seid Musa
☞ ልዩ የደውራና (ኮርስ) ፕሮግራም በቡታጅራ ከተማ! = ⏱ እነሆ የፊታችን ጁሙዓ ቀን 12/09/2018 ከዐስር ሰላት በኋላ በይፋ የሚጀምርና ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሚቀጥል የኮርስ ፕሮግራም ተሰና
   ልዩ የደውራና (ኮርስ) ፕሮግራም                    በቡታጅራ ከተማ! = ⏱ እነሆ የፊታችን ጁሙዓ ቀን 12/09/2018 ከዐስር ሰላት በኋላ በይፋ የሚጀምርና ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሚቀጥል የኮርስ ፕሮግራም ተሰናድቶ ይጠብቀዎታል። 🎤 ኮርሱን የሚሰጡት ታላቁ ሸይኽ፦ #ሸይኽ_ዐሊይ_ቢን_አሕመድ_አርራዚሒይ መሆናቸው ፕሮግራሙን ለየት ያደርገዋል። እንዲሁም በእለቱ ከተለያየ የሀገሪቱ ክፍል ጥሪ የተደረገላቸው መሻይኾችና ጠለበተል ዒልም ኮርሱን ለመታደም ይገኛሉ። በመሆኑም ከተለያዩ አካባቢ ከሚመጡ የሱና ወንድሞች ጋር ትውውቅ የምናደርግበት ትልቅ አጋጣሚ ይሆናል ብለን እንጠብቃለን!! 📚 ለኮርሱ የተመረጡ ኪታቦች በቦታው ተዘጋጅተው የሚታደሉ ይሆናል። ታዲያ ይህንን ታሪካዊ ፕሮግም እንዳያመልጣችሁ ከወዲሁ ፕሮግራማችሁን ቡታጅራ እንድታደርጉ ስንል በአክብሮት እንገልፃለን።         ለበለጠ መረጃ፦        ስልክ፦ 0939003858 0916270905 https://t.me/butajira_Qirat_daewa_group

መድረኩ ሳይዘጋ እንዳነቧት አድርሱላቸው ቤተሰብ

ባገሬ ወሎ ላይ የየመን እርግቦች፡ ተከበዋል አሉ በሀበሻ ንቦች፡ በተውሒድ ደዕዋ ላይ ማር እያመረቱ፡ ተውበዋል አሉ ጠላት እየረቱ፡ ሽርክ ቢዲዓ ላይ ሰርክ እየዘመቱ፡ ......ኑር... t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi