fa
Feedback
شـبـاب السـلــفـــيـــيــن

شـبـاب السـلــفـــيـــيــن

رفتن به کانال در Telegram

👉«ሰለፍያ ቀጥተኛ የሀቅ መንገድ ብሎም አይነኬ ፅኑ ተራራ ነው።» ለአስተያዬትና እርማት

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام شـبـاب السـلــفـــيـــيــن

کانال شـبـاب السـلــفـــيـــيــن (@nuredinal_arebi) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 29 087 مشترک است و جایگاه 2 518 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 1 173 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 29 087 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 13 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -341 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 24 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 19.27% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.02% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 603 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 624 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 71 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
👉«ሰለፍያ ቀጥተኛ የሀቅ መንገድ ብሎም አይነኬ ፅኑ ተራራ ነው።» ለአስተያዬትና እርማት

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 14 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

29 087
مشترکین
+2424 ساعت
-647 روز
-34130 روز
آرشیو پست ها
نخبة الفكر في مصطلح أهل الأثر | المتون الإضافية

✍️ለድምፁ ለዛ ቃናው ውበቱ ሲማርክ «የኔ ህዝብ ኩራቴ» ----------------- በተውሒድ ተማማል በሱናው ተራመድ፡ አጥበቅ ጨብጠው የኢማኑን ገመድ፡ አንተ የትም ዝመት ጠላት ይሁን አመድ፡ ፍቅር ነው ታሪክህ የለውም ክርክር፡ ይገለፅ መዝገቡ ታሪክህ ይመስክር፡ ምቀኛህ ይቃጠል ዘላለም ይዳክር፡ አንተ ግን ከፍ በል #በአዛንህ ጠንክር፡ .....ህዝቤ ሆይ.... የፅናት ጥግ የጀግንነት መዳረሻ፡ መስጂዱ ነው የስኬቱ መዳረሻ፡ ተውሒዱ ነው መደበቂያው፡ አዛኑ ነው ማነቃቂያው፡ አሏህ ሲል ነው የሚረካው፡ እሱን ማነው የሚነካው፡ ውብ ታሪኩ ለዘላለም ይዘመራል፡ በእስልምናው እንደፀና ይከበራል፡ አዛኑ ነው የሱ ሰንደቅ፡ ለሐቅ ነው የሚዋደቅ፡ ለኢስላም ነው የሚለፋው፡ በሰላም ነው የሚስፋፋው፡ ጠላቶች ምን ቢጨቆን፡ ምን ቢገድለው ቄስም ዳቆን፡ አንድ እምነቱን አለቀቀም፡ እስከ ዛሬ አልደቀቀም፡ አሏሁ አክበር ይላል ዘልቆ፡ በጎራው ጫፍ በሸለቆ፡ ልብ ይነካል ድምፁ ጠልቆ፡ ይህ ነው የኛ ታሪካችን፡ ቢደበቅም ውብ ስራችን፡ ዛሬም ቦታው ይናገራል፡ ኢስላም ገና ይሞሸራል፡ ህዝቤ ሆይ ታሪክህን አንብቤያለሁ ፅናትህ ነው የኔ ኩራት፡ እመኛለሁ እፎይታህን ላንተ ስኬት እኔ መስራት፡ ልሙትልህ ካንተ በፊት እኔ ልሁን ዋስ ጠበቃ፡ አንተ ፅና በተውሒድህ አዛን አድርግ የትም በቃ፡ ህመምህ ይሰማኛል አንተኮ ነህ ስብራቴ፡ የጨለማ ሻማዬ ነህ ብርሀኔ ውብ መብራቴ፡ ባሞካሽህ ምን አያንስህም ህዝቤ ነህና ኩራቴ፡ ....ኑር የወሎ ህዝብ ልጅ...✍️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

2026-06-13-13-35-36-592_Church.mp32.36 MB

💎ለደዕዋው ድባብ በድምፅ🌷

🎙 በውስጥ እየመጣችሁ ፕሮግራሙ እንደት እንደሚያምር ውይ ኖረህ ቢሆንማ .....የምትሉኝ ወንድሞች እረፉ ...ብያለሁ በቃ እረፉ...ልታሳብዱኝ ነው እንዴ

👉ወሎ ምድር ዛሬ ልዩ ፕሮግራም ⭕️«ወሎ በልጆቿ»⭕️ --------------------- የዑለሞች ምድር የብርሀን ማማ፡ ደምቃ በልጆቿ ኮንቦልቻ ከተማ፡ በሁሉም አቅጣጫ ደዕዋ እየተሰማ፡ ትውልዱ ለእውነት እጁን እየሰጠ፡ ህዝባችን በተውሒድ እየተለወጠ፡ ጠላት እየሟሟ እንደ ጨው ቀለጠ፡ አብሽር የኔ ህዝብ የታሪክ ሰገነት የሞላበት ምድር፡ የፅናት ተምሳሌት የውብ ጀግኖች ስድር፡ የሸጋዎች ሀገር የውበት አውድማ፡ የአሊሞች መፍለቂያ የደጎች ባድማ፡ የፍቅር ተምሳሌት የመውደድ ውብ አርማ፡ የእስልምና ታሪክ የታላቆች ፊርማ፡ ከትናንት እስካሁን ጀግና እማይጠፋብሽ፡ አሊም የሐቅ ሰው ሰው እሚበቅልብሽ፡ የፍቅር የሰላም ፅናት ነው መረብሽ፡ ተውሒድና ሱናን የሚያስተምሩልሽ፡ ከውስጥሽ ተፈጥረው የሚዘምሩልሽ፡ ሐቅን እየሰሙ የማያቃልሉ፡ ሽርክን ለመፋለም ሁሌ እሚታገሉ፡ እውነተኛ አፍቃሪ ምርጥ ልጆች አሉ፡ ከፊሎቹ ዛሬ ደዕዋ ታድመዋል፡ ስለ እውነት ሊሰሙ ኮንቦልቻ ተመዋል፡ የኔ ቢጤ ደግሞ ሔዷል ባህር ማዶ፡ ከሚወዳት ምድር #ከወሎ ተሰዶ፡ ....ተመኘሁ አቦ...!! ምነው ትንሽ ቅፅበት በሆንኩ አብሬያችሁ!? ምነው በተገኘሁ ከመካከላችሁ!? በደስታ ሰክሬ ምነው ባቀፍኳችሁ!? ወንጀል ይሆን እንደ ከናንተ የለየኝ፡ ባህር ማዶ ወስዶ ናፍቆት ያሰቃየኝ፡ ለነፍሴ እንደዛ ነው ለኔ የሚታየኝ፡ ....እውነት ነው!! እርግጥ ቀንቻለሁ አልቅሻለሁ ዛሬ፡ ግን ደግሞ ለእናንተ የ'እውነት ነው ፍቅሬ፡ ንግግሬን ቆጠብኩ እናንተን አክብሬ፡ 👉ለማንኛውም!! ሰለፍያ አ'ቅ'ፋው በውብ አክናፎቿ፡ ለሐቅ አናብስቶች ተከፍተው ቀሮቿ፡ ሒዝብያን አባረው ተፈፅሞ ፍቿ፡ በደዕዋ ደምቃለች ወሎ በልጆቿ፡ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

ፕሮግራሙ ተጀምሯል ያ ሰላም የዛሬዋ የኮቻ ውሎ ግን

ልጅነት ሲናፈቅ ----—---------------- «ተነሳሁኝና በድንገት ከእንቅልፌ፡ የልጅነት አለም ናፈቀኝ እቅፌ፡ ከተጋደምኩበት ብንን ስል ድንገት፡ እየወጣሁ ነበር የትዝታን ዳገት፡ የልጅነት እድሜ ኮሽቻ ተሰማኝ፡ ሁሉንም ቃኘሁት ህይወት ፍርድ አቁማኝ፡ .....ገረመኝና አካፈልኳችሁ... ...ይሔው እንካችሁ... ሳላውቀው ሳላቅፈው ያለፈ ዘመኔን፡ አሁን ላይ ሳስበው ይቆጨኛል እኔን፡ ያኔ ህፃን ሳለን ነፃነት ነበረን፡ ያስመኛል ሀሴቱ ልጅ ሆነን በቀረን፡ በነፃነት ዘመን ያለፈ ጨዋታ፡ በልጅነት መንፈስ የነበረ ደስታ፡ ዛሬም በስተርጂና አያጣም ትዝታ፡ ገጠር ከመስኩ ላይ ከልጅነት ጋራ፡ ከብቶች ሲሰማሩ ፀሐይ ስታበራ፡ የሚመጣ አይመስልም የሞት ባላንጋራ፡ ልጅነት ሰላም ነው የነፃነት አለም፡ ልጅነት ፊርማ ነው የማይገፍ ቀለም፡ ችግሩ በሱ ውስጥ አንቆይም ዘላለም፡ ማደግ መከራ ነው በቃ ቻንስ አይደለም፡ ሙሉ ጨረቃዋ ስትፈካ በማታ፡ በጠራው ሰማይ ላይ ስናስተውል ፈክታ፡ ፍርሀት ሳይሰማን እሷን ተከትለን፡ ቤተሰብ ካላየን የትም እንዘምታለን፡ ጨረቃዋም ከኛ ጋር ቁልቁለት አቀበት፡ ድንቡል ቦቃ ስንል በኮልታፋ አንደበት፡ በልጅነት ዜማ እንግባባታለን፡ እሷ አትቀርም ማታ እኛ እንጠብቃለን፡ ጨረቃ ጋር ወሬ ዛሬ ማን ያስባል፡ ለማታ ጨዋታ ማን ይሰባሰባል፡ ልጅ መሆን ሰላም ነው የሩቁን ያቀርባል፡ ልጅነት ቋንቋ ነው ከሁሉ ያግባባል፡ ...ብቻ ግን ልጅነት... የህይወት ወለላ ተንጠፍጥፎ ያልቃል፡ ሰው የመሆን መርህ እጂጉን ይደንቃል፡ ለአንድ ነፍሱ ሲባል ይነሳል ይወድቃል፡ እኔም እመኛለሁ ከሰዎች ለይቶ ህፃናት ባረገኝ፡ ሁሉንም አይቼ የማወራው ባገኝ፡ ሰው እድሜው ቢገፋ እጂግ ቢሸመግል፡ ምን ድካም ቢኖረው በህይወቱ ትግል፡ በምርኩዝ ቢራመድ እጂጉን ቢያረጂም፡ እድሜ ጠገብ ሆኖ ምን ቢገረጂጂም፡ ልክ እንደ ህፃን ልጅ ጨዋታ ይወዳል፡ ቀልድና ቁም ነገር ትዝታ ይወልዳል፡ ብቻ ልጅነት ማለት ደማቅ ብርሀን ነው የተሰጣ ወለል፡ የህይወት ጣዕም ነው የውቅያኖስ ጠለል፡ ልጅነት ስኬት ነው በፅድቅ መማለል፡ ልጅነት ፍሬ ነው ሌላው መንቀዋለል፡ ያ ንፁህ ልጅነት አልፎ ቢቆጨኝም፡ ዛሬም ወዳጂ ነው ከኔ አልተለየኝም፡ ሞት እስከሚመጣ በህይወት እስካለሁ፡ ንፁህ ልጅነቴን አስታውሰዋለሁ፡ ዘመን አቋርጨ ወደ ኋላ ስጓዝ፡ ተጭኘ መጣሁኝ እልፍ የትዝታ ጓዝ፡ ሰላም ግን አገኘሁ በልጅነት ጉዝጓዝ፡ በትውስታ አለም ውስጥ ስስቅ ቆየሁና፡ ከሔድኩበት ቦታ መጣሁ እንደገና፡ ትዝታ ክፉ ነው በዬ ጊዜው ያድጋል፡ ግን ከሰው ነጥሎ ባይተዋር ያደርጋል፡ የያዘኝ ድባቴ በቅፅበት ለቀቀኝ፡ ግን አሁን አድጌ ልጅነት ናፈቀኝ፡ ትዝታ ሲጋጋል በስሎ ሲንፈቀፈቅ፡ በፈገግታ ደምቆ ውስጥ ሲፈቀፈቅ፡ እንደ ሞኝ ያደርጋል ልጅነት ሲናፈቅ፡ ......ልጅ እንደሆኑ ቢቀርስ...⁉️ .....በኑረዲን አል-አረብ..✍️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

ለማንኛውም እውነታው ይህ ነው። በነገራችን የህዝብ ቆጠራ ላይ ሆነ ብለው የውሸት ዳታ አስቀምጠው በሙስሊሙ ላይ መዋሸት ዛሬ የጀመሩት አይደለምና አይገርመንም።። ⭕️የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ 30% ⭕️ጴን
ለማንኛውም እውነታው ይህ ነው። በነገራችን የህዝብ ቆጠራ ላይ ሆነ ብለው የውሸት ዳታ አስቀምጠው በሙስሊሙ ላይ መዋሸት ዛሬ የጀመሩት አይደለምና አይገርመንም።። ⭕️የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ 30% ⭕️ጴንጤ ቆስጤ 16.8% ⭕️ካቶሊክ 0.70 % ✅ኢስላም 50% ነው እየመረራችሁ ዋጡት። t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

« እነዚህ ተሸክመን ስለኖርን ብቻ መንግስት የኖቬል ሽልማት ሊሸልመን ይገባል።» 👉ይህ ነው የፋኖ መሪ‼️ አሁንስ አላማቸው አልገባችሁም ወይ እናንተ የኛዎቹ አሞት አልባ መይቶች‼️ ስንቱን ሽፍታ ነኝ ባይ ስንቱን አራሙቻ፡ ስንቱን መሀይማን ስንቱን ጉድ ሙሀቻ፡ ደናቁርቱን ችለን ስለኖርን ብቻ፡ ያለምንም ነገር ያለማመልከቻ፡ ለሀገር ሰላም ብለን ስለኖርን ታመን፡ በመታገሳችን አለም አስደምመን፡ አሁን በዚህ ጊዜ አሁን በዚህ ዘመን፡ የኖቬል ሽልማት መንግስት ይሸልመን፡ «እንደት ግን ሙስሊም መጤ ሆኖ ሳለ ቤተ መንግስት ይገባል?» እያለ ጠቅላይ ሚኒስተሩ ሙስሊም ነውና እንዋጋ የሚለው አርበኛችሁ ነው። አመፅ የሚጠራ መሀይም ወፍ ዘራሽ፡ ድልብ ጦር ናፋቂ የሚባለው አራሽ፡ ወንድነት የሌለው ልክስክስ ትርኳሽ፡ ኦቶዶክስ ያለችው ቀዳሽና ተኳሽ ፡ ከእውቀት የፀዳው በቃ ይህ ነው ፋኖ፡ ራሱን አጠፍቷል አልቋል ተሸንሽኖ፡ የመንጋ ስብስብ የከብቶች ጥርቅም፡ ለሀገር ለወገን ሁሌም የማይጠቅም፡ እንደ ፋኖ ያለ መናፍስት አላቅም፡ የሙስሊሞች ጠላት መሀይም ደንቆሮ፡ ጧት ማታ የሚጮህ ሰገጤ ቆርቆሮ፡ ሁሌ እማይሻሻል ካምናው ለዘንድሮ፡ በደም የሚነግድ ነፍራቃና እንኩሮ፡ ጫካ ነኝ እያለ የሚደፍጥ እጓሮ፡ ዘመኑን የሳቱ በግፍ ተመዝኖ፡ ሰላምን የማይወድ በእምነት ስም ወግኖ፡ የድንጋይ ዘመን ቅርስ በቃ ይህ ነው ፋኖ፡ ✅መንግስት እነዚህን ችለን በመኖራችን ብቻ ሊሸልመን ይገባል ባይ ነኝ‼ አወ ኢትዮጲያ የቆመችው በሙስሊሙ ትዕግስት ነው። t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

⚠️ኮ/ቻ ላይ ኮርስ የሚሰጡን ታላቁ ዐሊም فضيلة الشيخ علي بن أحمد الرازحي - حفظه الله - ይህ ናቸው በደንብ እንዲታውቋቸው ነው የቴሌግራም ቻናላቸውን ተቀላቀሉ https://t.me/AliAlrazihi https://t.me/AliAlrazihi

የስደት መጨረሻው... ~ በስደት አለም የሚኖሩ ብዙ እህቶች ህይወታቸውን፣ ወጣነታቸውንና ጉልበታቸውን መስዋዕት አድርገው ሌት ተቀን ይለፋሉ። ግባቸው አንድ ነው...ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን መለወጥ! ነገር ግን ብዙ ጊዜ ሲታይ የሚደጋገም አንድ ልብ ሰባሪ እውነታ አለ። እህቶቻችን ለአስር እና ከዚያ በላይ አመታት በስደት ኖረው፣ ጥሪት አውጥተው፣ ለቤተሰብ ቤት ሰርተው ወይም የተወሰነ ገንዘብ ይዘው «ተሳካልኝ» በሚል ስሜት ወደ ሀገራቸው ይመለሳሉ። ነገር ግን ሳምንታትና ወራት ሳይነጉዱ የያዙት ገንዘብ ያልቃል፤ ያሰቡት የሀገር ውስጥ ህይወት እንደጠበቁት አይሆንም። በመጨረሻም የገቡበትን የኢኮኖሚ ቀውስ መቋቋም ሲያቅታቸው፣ አማራጭ አጥተው በቁጭትና በእንባ ተመልሰው ወደ ስደት ይመለሳሉ።ምክኒያቱም ገንዘብ ማግኘትና ሀብታም መሆን ይለያያሉና። አወ ብዙ ከመስራት፣ጥቂት መቆጠብና ማስተዳደር ታላቅ ዋጋ አለው።እውነተኛ ሀብታምነትና ስኬት የሚመጣው የሚገኘውን ገንዘብ እንዴት መያዝ፣ መቆጠብና ወደ ስራ መለወጥ (ኢንቨስት ማድረግ) እንዳለብህ ሲገባህ ብቻ ነው። ብዙ እህቶቻችን የስደት ደመወዝ ማግኘቱን እንጂ ያንን ገንዘብ እንዴት አውጥተው፣ አባዝተውና ቆጥበው በሀገራቸው ቋሚ የገቢ ምንጭ እንደሚያደርጉት እውቀቱ የላቸውም ይመስለኛል--ብዙዎቹ--። አንድ ሰው ወደ ሀገር ቤት ከመመለሱ በፊት «ነገ ጠዋት ከምን እኖራለሁ? ምንስ እሰራለሁ?» የሚለውን ጥያቄ በግልጽ መመለስ አለበት ብየ አምናለሁ።በየወሩ ደመወዝ ከመቀበልና ያንን ገንዘብ በቀጥታ ወደ ሀገር ቤት ከመላክ ባለፈ፣ ስለ ነገው ህይወትሽ ምን እያሰብሽ ነው? ነገ ወይም ከነገ ወዲያ ወደ ሀገርሽ ስትመጪ ደግመሽ ወደ ስደት ላለመሄድና በራስሽ እግር ለመቆም ዛሬ ምን እየሰራሽ ነው?? t.me/AbuSufiyan_Albenan t.me/AbuSufiyan_Albenan

የመስቀሉ ስር ቁማርተኞች! ~ እነዚህ አካላት ሃይማኖትን በሽፋንነት የሚጠቀሙ አሸ^ባሪዎች ናቸው። 1. አመሰራረታቸውና አደረጃጀታቸው በሞ0 ተዋህዶ ነው። 2. እንቅስቃሴያቸው በካህናት የሚደገፍ ነው። 3. ያለመሸማቀቅ ሃይማኖታዊ ዓላማ አንግበው እንደወጡ ደጋግመው ገልፀዋል። 4. በቤተ ክርስቲያናት ውስጥ የጦር መሳሪያ እያስቀመጡ በሚዲያ ወጥቶ አይተናል። 5. በቤተ ክርስቲያናት ውስጥ ስልጠና ሲያካሂዱ ታይተዋል። 6. በተደጋጋሚ እምነት እየለዩ ሙስሊሞችንና መስጂዶችን አጥቅተዋል። ይሄ ሁሉ ሆኖም በሽብር አልተፈረጁም። ለምን? የሚገርም ነው። እየተፈፀመ ያለው ክርስቲያናዊ ሽብ^ርተኝነት ነው። ይሄው ከሰሞኑ አዲስ አበባ ውስጥ ሁለት ሙስሊሞችን እጅግ ሰቅጣጭ በሆነ መልኩ አር^ደዋል። የሰሞኑ ጩኸታቸው ዓላማም ይሄው ነው። አራት ኪሎን ለመቆጣጠር ሲሉ የዘሩንም፣ የሃይማኖቱንም ሁሉንም ዓይነት መንገድ ይጠቀማሉ። አሁንም በጊዜ ጠንካራ እርምጃ ካልተወሰደ ጎንደር ላይ ያለው ሁኔታ አስጊ ነው። ውጥረት አለ። እገታዎች ሙስሊሞች ላይ ከወትሮው ጨምረዋል። ችግሩን ውስብስብ የሚያደርገው በመንግስት መዋቅር ውስጥ ሆነው ለነሱ ያደሩ መረጃ አቀባይና ሽፋን ሰጪ መኖራቸው ነው። ስጋቱ ያጠላው በሙስሊሞች ላይ ሆኖ ሳለ ጫናው አንድ ነገር ቢደርስ ማላከከያ ሰበብ የሚፈለግላቸው እነሱው ናቸው። ነፍስ ሳይጠፋ፣ የከፋ ነገር ሳይደርስ መንግስት የፈጠነ ስራ ሊሰራ ይገባዋል። ሹመኞች ኃላፊነታቸውን ባግባቡ ሳይወጡ ሲቀሩ አስተማሪ እርምጃ ካልተወሰደ አጥፊዎችን የልብ ልብ ይሰጣል። እውነት ለመናገር የሚደርሱት ጥቃቶች ከአቅም በላይ አይደሉም። የሚፈልገው ቁርጠኛ የሆነ አያያዝ ነው። የሚፈልገው በየ መዋቅሩ ያሉ ኃላፊዎች ላይ ሀቀኛ ምርመራና በማካሄድ ተጠያቂነት እንዲሰፍን ማድረግ ነው። አጥቂዎቹ የውስጥ ድጋፍ ይዘው ነው መሀል ከተማ ላይ የሚርመሰመሱት። ከዚህ በፊት በጎንደር፣ ደባርቅ፣ እስቴ፣ ብቼና፣ ሞጣ፣ ወፍጠጌ፣ እንፍራንዝ፣ ... በደረሱ ነውረኛ ተግባራት ኃላፊነታቸውን ባልተወጡ ሹማምንት ላይ ህጋዊ እርምጃ አለመወሰዱ የክልሉ መንግስት ለጉዳዩ ብዙም ደንታ እንደሌለው ያሳየ ነበር። ጥቃቶቹን ተከትሎ በአንዳንድ ቦታ ላይ የነበረው ድንገተኛ አፈሳም በሚያሳዝን ሁኔታ ተጎጂዎች ላይ ያነጣጠረ መሆኑ ወሮበላዎቹ ምን ያህል በመንግስት መዋቅር ውስጥ የተሰገሰጉ እንደሆኑ ያሳየና ተስፋ አስቆራጭ ነበር። ዛሬም የባሰ ሳይመጣ ሳይቃጠል በቅጠል!! = የቴሌግራም ቻናል :- https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

پیام صوتی00:25

پیام صوتی00:28

ሀገሬን ላስቃኛችሁ ዛሬ የተወለድኩበት ያደኩበት ቦታ፡ ትዝ ይለኛል ሁሌ በጧትም በማታ፡ ራቀኝ ሰፈሬ ናፈቀኝ መንደሩ፡ በአይኔ ውል አለብኝ ጋራው ሸንተረሩ፡ በየት ነው መንገዱ ውስብስብ አለብኝ፡ ስደት
+3
ሀገሬን ላስቃኛችሁ ዛሬ የተወለድኩበት ያደኩበት ቦታ፡ ትዝ ይለኛል ሁሌ በጧትም በማታ፡ ራቀኝ ሰፈሬ ናፈቀኝ መንደሩ፡ በአይኔ ውል አለብኝ ጋራው ሸንተረሩ፡ በየት ነው መንገዱ ውስብስብ አለብኝ፡ ስደትና ናፍቆት እየጨፈረብኝ፡ ....ኑር..... t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

شـبـاب السـلــفـــيـــيــن - آمار و تحلیل کانال تلگرام @nuredinal_arebi