es
Feedback
شـبـاب السـلــفـــيـــيــن

شـبـاب السـلــفـــيـــيــن

Ir al canal en Telegram

👉«ሰለፍያ ቀጥተኛ የሀቅ መንገድ ብሎም አይነኬ ፅኑ ተራራ ነው።» ለአስተያዬትና እርማት

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram شـبـاب السـلــفـــيـــيــن

El canal شـبـاب السـلــفـــيـــيــن (@nuredinal_arebi) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 29 001 suscriptores, ocupando la posición 2 496 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 1 174 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 29 001 suscriptores.

Según los últimos datos del 10 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -96, y en las últimas 24 horas de -23, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 14.42%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 7.78% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 183 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 255 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 49.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
👉«ሰለፍያ ቀጥተኛ የሀቅ መንገድ ብሎም አይነኬ ፅኑ ተራራ ነው።» ለአስተያዬትና እርማት

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 11 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

29 001
Suscriptores
-2324 horas
-467 días
-9630 días
Archivo de publicaciones
ቲክቶክ ላይ ኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር ሀፊዞሁሏህ ተጀምሯል https://vt.tiktok.com/ZS9MaGfAG2Kja-KRNEk/
ቲክቶክ ላይ ኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር ሀፊዞሁሏህ ተጀምሯል https://vt.tiktok.com/ZS9MaGfAG2Kja-KRNEk/

«ወንጀልን መፎከት» በልተን ሆድ አንሞላ ጠጥተን አንረካም፡ ታግለን ድል የለንም ፕላን አናሳካም፡ ከአሏህ የሚያቃርብ ስራ የለን መልካም፡ በወንጀል ቫይረሶች ሆነናል እከካም፡ ከእውነት እርቀን ጨርሰን ታመናል፡ ሞራላችን ላሽቆ ከውስጥ ደክመናል፡ ወንጀግ እየበላን መፎከት ይዘናል፡ አሏህ ይመልሰን እከካም ሆነናል፡ የኛን ግፍ ደብቀን የሌላ መመልከት፡ በራሳችን ሰንፈን በሌሎች መታከት፡ ሱስ ሆነብን በቃ ወንጀልን መፎከት፡ ...ኑር....✍️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

Mensaje de voz00:22

2026-07-10_11'56'36'.mp32.13 MB

በጣም ጥፍጥ የሚል ሙሀዶራ

«ኹጥባ» --------- خطبة شهيرة في التاريخ الإسلام لسحبان الوائل. ይህ ጠቢብ ሰው በንግግር ምጥቀቱና በአነጋገር ለዛው በኢስላም የታሪክ ገፆች ላይ ስሙ በደማቅ ሰፍሯል።
«ኹጥባ» --------- خطبة شهيرة في التاريخ الإسلام لسحبان الوائل. ይህ ጠቢብ ሰው በንግግር ምጥቀቱና በአነጋገር ለዛው በኢስላም የታሪክ ገፆች ላይ ስሙ በደማቅ ሰፍሯል። 👉ሰህባን አል-ዋኢሊ «ሰህባን ኢብን ዘፍር አል-ዋኢሊ አል-ባሂሊ) በቅድመ-እስልምና ዘመን የኖረና እስልምናን የተቀበለ «ሙኸድረም» ሲሆን በ54ኛው አመተ-ሂጅራ የሞተ ታዋቂ አረባዊ የንግግር ጥበብን ከለዛ ጋር የተቸረው #ጀግና ነበር። በአንደበተ ርቱዕነቱ እና በማራኪ ምትዓታዊ አገላለፁ ይታወቃል። ይህ የሰህባን የቅልጥፍና እና የንግግር ብቃት ብልም የአገላለፅ ችሎታ በታሪክ ውስጥ ልዩ የተሰጦ ምልክት«ፓራጎን» እንደሆነ ይነገራል። የዚህ ሰው አንደበተ ርቱዕነት ምሳሌ እስከመሆን ደርሷል፡- "ከሰህባን ዋኢሊ የበለጠ አንደበተ ርቱዕ ከየት ይመጣል እስከመባል የደረሰ የግሩም አነጋገር የጣፋጭ አንደበት ባለፀጋ እንደሆነ የኢስላም የታሪክ ድርሳናት ይጠቁማል"። ከላይ ያያዝኩት ግሩም ገለፃ የዚህ ታላቅ ኮከብ #ንግግሮች አንዱ እንደሆነ ይታመናል። የዛሬ ጁሙዓ ግሩም ኹጥባ ከተደረገ በውስጥ ብትልኩልኝ እመኛለሁ 👉ሶለዋት እያወረድን ጁሙዓን እናድምቀው‼️ ....ኑር....✍️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

ስትናደድ ዝምታን ምረጥ። ለአንድ ደቂቃ ንዴት… የዓመታት ዋጋ አትክፈል። ቁጣህን ተቆጣጠር

..ሰለፍያዬ .ወላሒ እወድሻለሁኮ..‼️ ⭕️....አትንኳት መንሀጀን...✍️ ❝ሞቴን በሰለፍያ ላይ ጌታዬ እስኪ በዱዓችሁ❞ ስላንች እያዜምኩኝ አንገቴ ቢበጠስ፡ እጅ እግሬ ቢታሰር ወይም ቢቀነጠስ፡ ምስጋና አቀርባለሁ ልክ እንደማስነጠስ፡ በህግሽ ፀንቼ በመርህሽ ቆሜ፡ ብታሰር ብሰቀል ብሞት ደጋግሜ፡ ስጋዬ ቢሰበር ቢፈስልሽ ደሜ፡ ስላንች ከሆነ አልፈራም አለሜ፡ ስምሽን ስጠራው ውስጤ ይደሰታል፡ ሰላም ይሰማኛል ነፍሴ ይሰስታል፡ ሰለፍይ ነው ስባል መንፈሴ ይረካል፡ ተስፋዬ ተሟልቶ እቅዴ ይሳካል፡ .....ወላሒ እወድሻለሁክ... ሞቴን ቢያደርግልኝ ያንችን ቃል በመጥቀስ፡ አንችን እያፀናሁ ሁሌ ብንቀሳቀስ፡ ሽርኩን ቢዲዓውን ጥመቱን በመውቀስ፡ እኮራለሁ እንጂ አላፈገፍግም፡ ካንች በላይ ስኬት ወላሒ አልፈልግም፡ .....ሰለፍያ......‼️ አንች ነሽ ሚስጥሬ አንች ነሽ ወዳጄ፡ ያንችን ውዴታ ነው የጨበጥኩት በእጄ፡ አንች ነሽ ልሳኔ አንች ነሽ መንሀጄ፡ .......ሰለፍያዬ....‼️ ላንች የማልመጥን ክፉ ነኝ አውቃለሁ፡ ግን ከነወንጀሌም አንችን እወዳለሁ፡ ሲነኩሽ ያመኛል እኔ ምን አውቃለሁ፡ ስምሽን በክፉ ሲጠሩት ስሰማ፡ ውስጤ ይረበሻል ያመኛል እኔማ፡ .....መንሀጄ...‼️ ለዋሹብሽ ሁሉ መረጃ ሰጥቼ፡ አልሰማም ያለውን ጋሻ ጦር አዝምቼ፡ በቀጠፋብሽ ላይ ለመውሰድ እርምጃ፡ አልሰማም ያለውን ደሊልም መረጃ፡ ይዘምታል ወኔዬ የነካኝን እንጃ፡ ....ሰለፍያዬ...‼️ በመጥፎ ሲያነሳሽ ደንቆሮ ፈላስፋው፡ ሲሳለቅ በስምሽ ዱዳና ወልካፋው፡ ደስ ይለኝ ነበረ ይዤ ደም ባስተፋው‼️ ሰው በስነ-መግባር ካልተከባበረ፡ ውሸትን ቀምሞ ሀቅን ለቀበረ፡ ሁሉም አንችን ሊዘልፍ ከተነባበረ፡ ላንች ስል ብጋደል ደስ ይለኝ ነበረ፡ ....እህህህህ....ሰለፍያዬ...‼️ እታገሰዋለሁ ማንም ቢበድለኝ፡ ክብሬ ቢንቋሸሽም ለኔ ግድም የለኝ፡ አንችን ሲነኩሽ ግን ውስጤ ይረበሻል፡ ፊቴ ይቀየራል ወኔዬ ይጓሻል፡ መላው ሰውነቴ አንችን ይወድሻል፡ ላንች ስል ብሰዋም ላንች ያንስብሻል፡ ......ሰለፍያዬ.....‼️ እናትና አባቴ ፊዳ ይሁኑልሽ፡ አሏህ ይወፍቀኝ እኔም ልሙትልሽ፡ ሚስትና ልጆቼ ካንች አይበልጡብኝም፡ በክፉ ሲጠሩሽ እኔ አያስችለኝም፡ ......መንሐጄ...‼️ አዜምልሻለሁ ልሳኔ እስኪዘጋ፡ ሁሌ አልሰለችሽም ቀን መሽቶ ቢነጋ፡ ያኮራኛል ስምሽ በቆላም በደጋ፡ አውቀዋለሁና የሐቅሽን ዋጋ፡ አቃጥሉት አብሽሩ አፈራርሱን ደጀን፡ እግሬንም አንገቴን ገነጣጥሉት እጀን፡ ግን ልለምናችሁ አትንኳት መንሀጀን፡ ....በኑረዲን አል-ዓረብ...✍️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

ለሰለፍዮች የትም ሁኑ የት #በሰለፍያ_መንሀጅ ላይ ያላችሁ #ወንድም #እህቶቼ በገጠር በከተማ በስደትም ህነ በሀገር ያላችሁ ጀግኖቼ ሆይ...ከነችግራችሁ ከነስህተታችሁ አንድ ወንድማችሁ እጂግ ይወዳችኋል እሽ። ሁሌም አስባችኋለሁ፣ እሳሳላችኋለሁ...ትናፍቁኛላችሁ። 👉እንድታውቁት እፈልጋለሁ ወላሒ ልቤ ለናንተ ልዩ ቦታ አለው ። ...ኑር... t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

قال جرير: «ما رآني النبي ﷺ منذ أسلمت إلا تبسَّم في وجهي». 📚 الإخوان لابن أبي الدنيا (١٣١) t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

እውነተኛ ወንድነት የት ገባ‼️ -------------------------- ​በየቀኑ የምንሰማቸው ታሪኮች ሁሉ ተመሳሳይ ዜማ አላቸው የለቅሶ፣ የክህደት እና የቁስል ዜማ። ሶሻል ሚዲያውን ስንከፍተው አንዷ «ባሌ በደለኝ» ስትል፣ ሌላኛዋ «የህልሜ መስሎኝ የህይወቴ ጠባሳ ሆነብኝ» እያለች በከባድ እንባ ስትናገር እንሰማለን። ሁልጊዜም ከሚያለቅሱ ሴቶች ጀርባ የወንዶች የበደል ታሪክ ብቻ ይደመጣል። ​ግን ለመሆኑ... "እውነተኛ ወንድነት" በዚህ ዘመን የት ገባ? ​መቼ ነው ስለ ወንድ ልጅ መልካም ታሪክ፣ ስለ ታማኝነቱ እና ስለ ጀግንነቱ የምንሰማው? ትዳር ትርጉሙ ጠፍቶ "ትዳር ይቅርብኝ" የሚያስብል ትውልድ ውስጥ እየኖርን ይመስላል። ​የሴት ልጅ ክብር፣ መጠለያና ጋሻ መሆን ምን ማለት እንደሆነ ለማወቅ ወደ ኋላ መለስ ብሎ ማየት ይበቃል። የአላህ መላክተኛ ነቢዩ ሙሐመድ ﷺስለ ሴቶች መልካም አያያዝ ያስተማሩትና በተግባር ያሳዩት መንገድ የትግስት፣ የክብር እና የፍቅር ጥግ ነበር። ​"ከእናንተ መካከል በላጭ ማለት ለቤተሰቡ (ለባለቤቱ) መልካም የሆነው ነው..."በማለት አስተምረዋል። ​እውነተኛ ጀግንነት ሴትን ልጅ ማልቀስ ሳይሆን፣ ከማንኛውም አስከፊ ነፋስ ሊጠብቃት ጋሻና መከታ መሆን ነበር። እውነተኛ ወንድነት ሴትን ልጅ ሰብሮ "እኔ ወንድ ነኝ" ማለት ሳይሆን፣ ደክማ ስትገኝ ድጋፍ፣ አዝና ስትገኝ መጽናኛ መሆን ነበር። ●ትዳር ለምን አስፈሪ ሆነ⁉️ ​ዛሬ ላይ ብዙ ሴቶች ትዳርን እንደ ህይወት ማደሻ ሳይሆን እንደ "እስር ቤት" ወይም "የስቃይ መጀመሪያ" አድርገው እንዲፈሩት ተደርገዋል። ፍቅር በጥቅም፣ ታማኝነት በክህደት እየተተካ በመጣበት በዚህ ዘመን፣ "መቼ ነው እንደ ነቢዩ ﷺ አስተምህሮ ሴትን ልጅ የሚያከብር፣ የሚንከባከብና ዋስትና የሚሆን ጀግና ወንድ ታሪክ የምንሰማው?" የሚለው ጥያቄ የብዙዎች የውስጥ እምባ ሆኗል። ​✨መልእዕክቴ ይድረስልኝ ለነገው ጀግና! ​የወንድ ልጅ መልካም ታሪክ አልጠፋም፣ ሊጠፋም አይገባም! ● ወዳጄ ​የአንድ ሴት መጠጊያ ሁን፦ የሴት ልጅን ክብር መጠበቅ የደካማነት ሳይሆን የትልቅነት እና የንፁህ ማንነት መገለጫ ነው። ●​ጠባሳ አትሁን፦ በአንተ ምክንያት አንዲት ሴት እጆቿን ወደ ሰማይ ዘርግታ እንባዋን እንድታፈስ አታድርግ። ይልቁንም በአንተ ሰላምና ደስታ አግኝታ የምታመሰግንህ የህይወቷ ንጉስ ሁን። ​በየማእዘኑ የምንሰማው የበደል ታሪክ አብቅቶ፣ "እንደዚህ አይነት መልካም ወንድና ደስ የሚል ትዳር አለ!" ተብሎ የሚወራበት፣ የጠፋው ፍቅርና መከባበር የሚመለስበት ዘመን ይሁንልን አሚን። 🤲 t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

Mensaje de voz00:19

መተዋወቅ ነው ያናናቀን ምናልባት መራራቅ ደግሞ ያከባብረን ይሆናል።

Mensaje de voz01:42

በአሏህ ስም ልጠራ የሚል የጥመት ሰው፡ መገረፉ ቢቀር መዘቅዘቅ ይነሰው⁉️ .....ኑር...✍️ t.me/nuredinal_arebi

ከቴሌግራም ትንሽ ጠፋ ብልም።በቲክታክ አንዳንድ እንቅስቃሴዎችን እያደረግን ነው በተለይ ከአህባሾች ብዥታ ጋር ተያይዞ ስለሆንም ቲክታክ አካውንት ያላችሁ follow & share በማድረግ አበራቱን ለማለት ነው።ባረከሏሁ ፊኩም https://www.tiktok.com/@abu.oubeida3?_r=1&_t=ZS-97pJ2HkpGEx

«እነዚህ ናቸው ሰለፍዮችን የሚሳደቡት» «ዋጋዋን የማታውቅ ዑማ» هؤلاء من يسبون السلفيين .. هؤللء من ينبزونهم بالمداخلة... هؤلاء من ينبزونهم بالوهابي
+2
«እነዚህ ናቸው ሰለፍዮችን የሚሳደቡት» «ዋጋዋን የማታውቅ ዑማ» هؤلاء من يسبون السلفيين .. هؤللء من ينبزونهم بالمداخلة... هؤلاء من ينبزونهم بالوهابية.... እነዚህ ናቸው #ሰለፍዮችን ሲሳደቡ የሚውሉት!! እነዚህ ናቸው #በመዳኺላ የሚሰይሙን!! እነዚህ ናቸው በሌለንበት የሚያሙን!! እነዚህ ናቸው #ውሀብያ እያሉ የሚተቹን!! هؤلاء من ينبزونهم بعباد السلاطين... هؤلاء من يريدون تحرير فلسطين.. . እነዚህ ናቸው የባለ-ስልጣን አገልጋይ የሚሉን!! 🛑እነዚህ ናቸው #ፍልስጤንን ነፃ እናወጣለን የሚሉን!! هؤلاء من يسبون الحكام لأجل فشلهم في حياتهم... እነዚህ #ድንዙዛኖች የራሳቸው ህይወት በራሳቸው ጥፋት በተመሰቃቀለ ቁጥር ለውድቀታቸው ሙስሊም መሪወችን በመሳደብና በማንቋሸሽ የተጠመዱ ናቸው። هؤلاء من يتهمون السعودية بأنها تدفع الجزية لأمريكا. . وأنها عميلة لهم ... እነዚህ ሰዎች ናቸው #ሳዑዲ ለአሜሪካ ጂዝያ ትከፍላለች የሚሉን እሷ የነሱ ወኪል መሆኗ ግን አይነገርም። هؤلاء هم سبب تسلط الأعداء على للأمة ووهنها.... እነዚህ #አስመሳዮች በሙስሊሙ ዑማ ላይ ጠላት እንድጠራራባቸው ግንባር ቀደም የውርደት ምልክቶች ናቸው። #أمة_ضاعت_قيمها ብቻ ዋጋችንን ያጣን ህዝቦች መሆናችን ያሳዝነኛል። ...ኑር....✍️ t.me/nuredinal_arebi t.me/nuredinal_arebi

«ባለገ ትውልዱ» ስሜን አያቁትም አሏህ ብለው ጠሩኝ፡ ደስ ይለኛል በቃ ይህንን ሲነግሩኝ፡ እያለ በንቀት በደስታ ያወራል፡ አሁን ይህ ብልግና ለማን ይነገራል!? የብልግናህ መጠን አለፈ ድንበሩን፡ እስኪ እንደ ሰው እፈር ተወው መከበሩን፡ ንቀትህ በአሏህ ላይ ምላሱን ዘረጋ፡ አልገባህም ገና የቅጣቱ ዋጋ፡ ሸይጧን እንኳ እንዳንተ አልተደፋፈረም፡ ህሌናህ ሲያስበው ለምን አላፈረም⁉️ ስዳደግነትህ ልክ አለፈ እያደር፡ ማነው ያሳደገህ ከየትኛው መንደር⁉️ አባት የለህም ወይ ማነው ያሳደገህ፡ እስከዚህ ደረጃስ ማነው ያባለገህ፡ ሰው በአምላኩ ክብር እንደት ይሳለቃል፡ በአሏህ ስም ሲጠራስ ምን ብሎ ይስቃል? ወንጀል ከዚህ በላይ አለ ግን ማን ያውቃል? ምን አይነት ከባድ ቃል እንደምትናገር፡ ተቀምጠህ ቢሆን ፍትህ ባላት ሀገር፡ መገደሉ ቢቀር ትገረፍ ነበረ፡ ግና በዛች ሀገር ፍትህ ተቀበረ፡ ልንገርህ አሁንም ህሌናህ ከቆጨው፡ ያንን ቪዲወ አጥፋ በቃ አታሰራጨው፡ እጂግ ያሳምማል ተረጭቷል እንደ ጨው፡ በአለሙ ጌታ በስሙ ተጠራህ⁉️ መሸማቀቅ ቀርቶ እየሳቅክ አወራህ፡ ሰው ነህ እንስሳ ነህ ምንድን ነበር ስራህ!? ማነው ለዚህ ጥመት ያበቃህ ኮትኩቶ፡ ምን አይነቱ በግ ነህ ምን አይነቱ እንኩቶ፡ አዕምሮ የለህም አስተዋይ ህሌና!? ከዚህ በላይ ውርደት ምን አለ ብልግና፡ ምን አይነት አዕምሮ ነው የተሸከምከው፡ እንደትስ አሏህን እስከዚህ ደፈርከው፡ ለምን ክብር ስሙን ቀየርከው በስምህ፡ ተውበት ካላደረክ ጠብቅ እስኪያከስምህ!! የመከነ ትውልድ በየቦታው በዛ፡ ጀለ-ተጃጃለ ወጣት ጠነዛ፡ በማያውቀው ነገር ምላስ እያበዛ፡ አሏህን አመፀ ጭራሽ ቀለደበት፡ ስሙን ስም አድርጎ አፊዞ ሳቀበት፡ በአሏህ ላይ መዳፈር ማፌዝ ሆነ ቀልዱ፡ በዘግናኝ ሁኔታ ባለገ ትውልዱ፡ ....Nur..✍️ t.me/nuredinal_arebi

ኢና ሊላሂ ወኢናኢለይሒ ራጂዑን አሏህ ብለው ይጠሩኛል እኔም ዘወር እላለሁ ...ይላል። እሽ ምን እንበል በአሏህ⁉️ t.me/nuredinal_arebi

የናቁን ሳይጠፉ ሳይሞቱ የሚያሙን፡ ከስኬት ላይ ቆመን እፎይ ስንል ይስሙን፡ አሚን በሉ