ማራናታ.....MARANATHA😍
ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደምመስላቸው ጌታ ሰለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንድደርሱ እንጅ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ሰለ እናንተ ይታገሳል።2ኛ ጴጥ 3፥9 ገና በጣም ጥቅት ጊዜ ነው፤ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም። ዕብራ 10፥37 የመወያያ ግሩፕ👇 @Marantawoch Inbox Comment @Thaddyapostolic
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel ማራናታ.....MARANATHA😍
Channel ማራናታ.....MARANATHA😍 (@maranathawoch) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 16 519 subscribers, ranking 5 163 in the Religion & Spirituality category and 2 034 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 16 519 subscribers.
According to the latest data from 15 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 209 over the last 30 days and by 18 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 20.27%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.00% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 3 349 views. Within the first day, a publication typically gains 1 321 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 30.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደምመስላቸው ጌታ ሰለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንድደርሱ እንጅ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ሰለ እናንተ ይታገሳል።2ኛ ጴጥ 3፥9 ገና በጣም ጥቅት ጊዜ ነው፤ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም። ዕብራ 10፥37
የመወያያ ግሩፕ👇
@Marantawoch
Inbox Comment @Thaddyapostolic”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 16 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.
Title .... ነፍሴ_ሆይ .!ነፍሴ ሆይ ነፍሴ ሆይ እግዚአብሔርን ባርኪ ×2 ውለታውን ፈጽሞ አትርሽ መዝሙር 103 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ነፍሴ ሆይ፥ እግዚአብሔርን ባርኪ፥ አጥንቶቼም ሁሉ፥ የተቀደሰ ስሙን። ² ነፍሴ ሆይ፥ እግዚአብሔርን ባርኪ፥ ምስጋናውንም ሁሉ አትርሺ፤ ³ ኃጢአትሽን ሁሉ ይቅር የሚል፥ ደዌሽንም ሁሉ የሚፈውስ፥ ⁴ ሕይወትሽን ከጥፋት የሚያድናት፥ በምሕረቱና በቸርነቱ የሚከልልሽ፥
singer:meseret kejela Title:ጥሶ የሚያስጉዝ ሀይል location : merkato salem atbyaጥሶ የሚያስጉዝ ሀይል ልቤ ይናፍቃል ሰማያት ይከፈቱ ይውረድ እጥፍ እሳቱ የረከሰው እንዲፈወስ እጥፍ ይውረድ ያንተ መንፈስ ተቀብለን ፀጋ ሚበልጥ እንውጣ ሀይልህም ይገለጥ 1)ቀንበርን የሚሰብር ሃጥያትን የሚያስጥል(የሚያስክድ) ላንተ መኖር የሚያስችል ሀይልህ እጥፍ ይውረድ እንለይ ላንተ ክብር እንቀመም በእሳት ጠላትን እያስፈራን እንኑር የክብር ህይወት 2)ጥቂት ዘመን እንዳለው ጠላት ይህንን አውቆ በታላቅ ቁጣ ቢወርድ ቢነሳ እጅግ ታጥቆ ሁሉን የሚበልጥ ፀጋ ማሸንፍያ ቅባት ይውረድ ታላቁ መብረቅ የመንፈስህ እሳት ጠላት ይፍራ ይደንግጥ አይቶ እንዳለን በእሳት ውስጥ የድል ህይወት የድል መንገድ እንድንጓዝ ሀይልህ ይውረድ ይውረድ እሳትህ ይውረድ *3 ይውረድ መንፈስህ ይውረድ *3 3) ቅዱስ ስምህ ይጠራ ፈውስ ይሁን ታምራት ጠላታችን ይንቀጥቀጥ ይርበድበድ ባንተ ፉት በስምህ ከጠራህው ከታላቅ ህዝብ ጋር ውጣ የኛ አምላክ የሱስ ልዩነት ይፈጠር ጠላት ይፍራ.... 3) ዛሬም ቅዱስ መንፈስ በብርቱ እንፈልጋለን ያልተለማመድነውን ፀጋ ይዞ ይምጣልን ሰማያት ይከፈቱ ድንቁ ክብር ይታይ(ሙሉ) ፍጥረት ወድቀው ይስገዱ ንገስ በሁሉ ላይ
✍️ቅድስና ለእግዚአብሔር !◉ ቅዱሳን ወገኖች፦ ቅድስና ለእግዚአብሔር መለየት ፤ ብልቶቻችንን የፅድቅ እቃ ጦር አርጎ ማቅረብ ሲሆን መቼም የማንደራደርበት ጉዳይ ሊሆን ይገባል። ክርስትና እንደ ልባችን አሳብና ፈቃድ እየዋልን እያደርን የምንመላለስበት ህይወት አይደለም ! ዳግመኛ ስንወለድ እርሱን ልንመስል እሱም ህይወታችንን በሞቱና በትንሳኤው ከለወጠ በኋላ በምድር የምንኖረው ኑሮ ስለ እኛ ለሞተውና ለተነሳው መሆን እንዳለበት አስተምሮናል! ሐዋርያ ጳውሎስ "ከክርስቶስ ጋር ተሰቅያለሁ እኔም አሁን ህያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል! በስጋም የምኖረው ህይወት በክርስቶስ ላይ ባለኝ እምነት የምኖረው ነው!" እንዳለው ◉ እርሱን እንድንመስል ተጠርተናል፦ ክርስትና በማስመሰልና በግብዝነት በውጭ መልክ የሚኖር ህይወት አይደለም !ልንኖረው ግድ ይላል!!የእግዚአብሔር መንግስት ጉዳይ ነውና!!። ሞቱን በሚመስል ሞት አሮጌውን ሰው ሰቅለን ትንሳኤውን በሚመስል ትንሳኤ ደግሞ በአዲስ ህይወት ልንመላለስ ይገባል!!! እንዴትስ ደግመን በሀጥያት ባርነት እንያዛለን? ከሀጥያት በታች እየኖርን እንዴት ክርስቲያን (የእግዚአብሔር ቤተሰብ )እንባላለን ??፤ የተቀበልነው መንፈስ የፍቅር ራስን የመግዛት መንፈስ እንጂ የፍርሃት መንፈስ አይደለምና! ◉ እንዴት ራሳችንን እንግዛ ? እንዴትስ በብርሀን እንመላለስ? " ነገር ግን እላለሁ፥ በመንፈስ ተመላለሱ፥ የሥጋንም ምኞት ከቶ አትፈጽሙ። ሥጋ በመንፈስ ላይ መንፈስም በሥጋ ላይ ይመኛልና፥ እነዚህም እርስ በርሳቸው ይቀዋወማሉ፤ ስለዚህም የምትወዱትን ልታደርጉ አትችሉም። ገላ5፥16-17 ይሄ ጥቅስ የሚነግረን "መንፈሳችንን በስጋችን ላይ ማሰልጠን እንዳለብን ያሳየናል" ስጋ በመንፈስ ላይ መንፈስም በስጋ ላይ ይቀዋወማሉ! በክርስቶስ ዳግም ተወልዶ አዲስ ፍጥረት በሆነው ማንነታችንና(መንፈሳችን) ላይ ባልተለወጠውና ፣ አለምን በሚሻው ( በወደቀው ማንነታችን )መሀል ከፍተኛ መቀዋወምና ጦርነት አለ። እኛም በይበልጥ የመገብነው በርሱ ቁጥጥር ስር ያደርገናል !!የመገብነው አይሎ ይሰለጥንብናል!! ወገኖች በህይወታችን ማን አይሏል???? መልሱን ለእናንተ ትቸዋለሁ!! እንዲሁ የወደቀው ማንነታችን እንዳለ ሆኖ ፥ ሰይጣን በሚሰለጥንበትና በወደቀ አለም ስለምንኖር ልንመስላቸው ስለሚስቡን ነው! ሐዋርያ ጳውሎስ ጢሞቲዮስን "እግዚአብሔርን ለመምሰል ራስህን አስለምድ" ይለዋል። ልክ ሰውነትን ለማጎልበትና ለመጠንከር የተመጣጠነ ምግብ መመገብ እና ተገቢ ስፖርት መስራት ግዴታ እንደሆነ ፥ እግዚአብሔርን ለመምሰልም መንፈሳዊ Exercise እንዲሰራ ያዘዋል። ይህ ነው እንግዲህ እግዚአብሔርን ለመምሰል መለማመድ!!በቅድስና ለመኖር መንፈሳችንን በመመገብ በስጋችን ላይ እንዲሰለጥን ማድረግ ..... መንፈስን መመገብ ► መንፈሳችንን የምንመግበው የመጀመሪያው ምግብ የእግዚአብሔርን ቃል ነው! “ኢየሱስም፦ ሰው በእግዚአብሔር ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል” ሉቃስ 4፥4 ቃሉን ማንበብ ወሳኙ ነገር ሆኖ ሳለ ፥ ይህን ቃል እስኪዋሀደንና የራሳችን እስኪሆን ድረስ ማሰላሰል ደግሞ ቀጣዩ ቁልፍ ጉዳይ ነው! በዚህ ላይ ብዙዎች የሚስቱት ማንበቡን ያነቡትና ማሰላሰሉ (meditation) ላይ የሉበትም! ቃሉ ደግሞ በማሰላሰል በኩል መንፈሳችንን እንዲቆጣጠር እስካላረግነው ድረስ ጠቀሜታ አይኖረውም! ልክ ምግብ ተመግበን የተመገብነው ምግብ ተፈጭቶ የሚዋሀደው በDigestive system እንደሆነው ሁሉ ቃሉን አንብበን የሚዋሀደን ደግሞ በተደጋጋሚ ስናሰላስለው ነው! ስንወጣ ስንገባ ፤ በምልልሳችን ሁሉ ማሰላሰል ግድ ይለናል። “እጆቼንም ወደ ወደድኋቸው ወደ ትእዛዛትህ አነሣለሁ፤ ሥርዓትህንም አሰላስላሁ።” መዝ 119፥48 ► ሌላኛው የመንፈስ ምግብ ፀሎት ነው! ፀሎት የክርስቲያን አማራጭ የሌለው ህይወቱ መሆን አለበት። ቢደክም ቢበረታ በየትኛውም ሁኔታዎች ውስጥ ከእግዚአብሔር ጋር የጠበቀ ህብረት ሊኖረው ያስፈልገዋል። ፀሎት ማለት፦ ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር ፤ ህብረት ማድረግ ነው። ይህም ሰአት ገድበንለት የምናደርገው ሳይሆን ዘወትር መንፈሳችንን ከእርሱ መንፈስ ጋር የምናገናኝበት የሰማይ ደጅ ነው!! ስንወጣ ፤ ስንሄድ ፤ ስራ ስንሰራ ብንጸልይ.... መንፈሳችን ይጠነክራል ፤ ስጋ የምንጎስምበት አቅም ይሰጠናል። ክፋትን እያሰብን ፤ ሰዎችን እያማን ፤ ለማያንጹን ቃላት ጆሮአችንን እየሰጠን ከአንድበታችንም እያወጣን ውለን የምንፀልየው ፀሎት ትርጉም ይኖረዋልን? ► ሌላኛው የመንፈስ ምግብ በቤተክርስቲያን ውስጥ ህብረት ማድረግና ማገልገል ነው። “በሐዋርያትም ትምህርትና በኅብረት እንጀራውንም በመቍረስ በየጸሎቱም ይተጉ ነበር።” ሐዋ 2፥42 ቅዱሳን የክርስቶስ አካል እንደመሆናችንና ክርስቶስም የኛ ራስ እንደመሆኑ እንደ አካል መስራት መንቀሳቀስ አለብን። እርስ በእርስ መተሳሰብ፣ መተናነፅ ፣ መያያዝ ፣ መደጋገፍ አካሉን ያሳድጋል! በቀረውስ ወገኖቼ እስቲ በዚህ ሚዛን እንመዘን?!የት ጋር ነን?ኑሮችን እንዴት ነው? ለርሱ እየኖርንለት ነው? ጨክን እንቀደስ ፥ የተሻለ ህይወት ይሁንልን! እነሆ በደጅ ቆሟል!!! ለእውነት እንነሳ !እርሱን ለመምሰል ራሳችንን እናስለምድ ክብራችን ነውና!!! በእለት ተእለት ህይወታችን ይህን በማሰላሰልና በማድረግ በቅድስና ለእግዚአብሔር መኖር እንችላለን!! “እኛም ሁላችን በመጋረጃ በማይከደን ፊት የጌታን ክብር እንደ መስተዋት እያብለጨለጭን መንፈስ ከሚሆን ጌታ እንደሚደረግ ያን መልክ እንመስል ዘንድ ከክብር ወደ ክብር እንለወጣለን።” 2ኛ ቆሮ 3፥18 @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH
ክብር አለኝ ለአንተክብር አለኝ ላንተ *2 የማያመጠን*4 ምስክርህ ነኝ ለማዳንህ የሱሴ እኔ አንተን ብዬ አፍሬ አላውቅም በህይወቴ የፍቅርህ ሚዛን እያደላልኝ ወደእኔ አለው በቤትህ ምህረትህ ከቦት ዘመኔን ባመልክህ ያንስብሃል ብዘምር ያንስብሃል በእውነት ግነን ከፍ በል ይታይ ማንነትህ 1) በእውነት ቃል አስበህ ፈጥረህ ይህው አኖርከኝ ዘመኔን በሙሉ ይዘህ እየመራህኝ ምን አለ ያላንተ ያላለፍኩት ነገር ጌታዬ አምላኬ ምስጋናዬ እኮ ነህ ያማረ ዜማ የሚገባህ እየሱስ አለ አለ በፂዮን አለ አለ*2 የማይቋረጥ ምስጋና አምልኮ ለአንተ አለ አለ በፂዮን አለ አለ *2 ይሰማ ያስተጋባ የእልልታው ድምፅ ይውጣ ሰማይ ልዩ ነህ የእኔ ጌታ ከአማልክት ሁሉ ልቀህ ታይ አይነስብህ ከኔ ምስጋና ትልቅ ነህ ትልቅ ልበል ገናና አይነስብህ ከኔ ዝማሬ ለአምላክነትህ ትዋረድ ክብሬ 2) ማረጌ ልበልህ ብርቱ ነህ መጠጊያዬ ማዳንህን ስራህን አይቼዋለው ባይኔ ባመታት መሀል ቃልህ ተፈፀመልኝ ትኑርልኝ ነፍሴ ታመልክሃለች ዘወትር የልቤ ጉልበት (ይንበርከክልህ)*2 ውለታህ አለብኝ ክበር ልበልህ ያበቃልኝን ዘመን አሻግረህ ዛሬን አቆምከኝ ምስጋናን ሞልተህ መዝሙሬ ሀሌሉያ ነው ስጦታዬም ምስጋና ነው ሳመልክህ *3 ብቻ ኖራለው
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
