en
Feedback
ማራናታ.....MARANATHA

ማራናታ.....MARANATHA

Open in Telegram

ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደምመስላቸው ጌታ ሰለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንድደርሱ እንጅ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ሰለ እናንተ ይታገሳል።2ኛ ጴጥ 3፥9 ገና በጣም ጥቅት ጊዜ ነው፤ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም። ዕብራ 10፥37 የመወያያ ግሩፕ👇 @Marantawoch Inbox Comment @Thaddyapostolic

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ማራናታ.....MARANATHA

Channel ማራናታ.....MARANATHA (@maranathawoch) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 17 348 subscribers, ranking 4 718 in the Religion & Spirituality category and 1 989 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 17 348 subscribers.

According to the latest data from 02 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 331 over the last 30 days and by 18 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 19.72%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 7.97% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 421 views. Within the first day, a publication typically gains 1 382 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 23.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደምመስላቸው ጌታ ሰለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንድደርሱ እንጅ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ሰለ እናንተ ይታገሳል።2ኛ ጴጥ 3፥9 ገና በጣም ጥቅት ጊዜ ነው፤ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም። ዕብራ 10፥37 የመወያያ ግሩፕ👇 @Marantawoch Inbox Comment @Thaddyapostolic

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 03 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

17 348
Subscribers
+1824 hours
+1067 days
+33130 days
Posts Archive
የማለዳ ትምህርት የጸሎታችን መልስ ለምን ይዘገያል? 11, የጸሎታችን ክብደት በማነስ ጸሎት በእግዚአብሔር ፊት ተመዝኖ የሚታይ ምዛናዊ ንግግር ነው። በዚህ ምድር ላይ በመንገድ ዳር ተቀምጦ የሚለምን ለማኝ እንኳን የሰውን ቀልብ ለመሳብና ሰው እንድራራለት ብሎ እስክደክም ድረስ አቅሙ የሚፈቅደውን ሁሉ አድርጎ ይለምናል። ነገር ግን በመንገድ ላይ ስለተቀመጠ፣ ለማኝ ነው ስለተባለ ብቻ ሰዎች አይራሩለትም። የሚናገረው ንግግር፣ የሚያወጣው ቃላቶች የሰዎችን ሆድና አንጀት የሚበላና የሚላወስ መሆን አለበት፤ ሰዎች አጥብቆ ለለመነ ሰው ነው የሚሰጡት። ለመለመን እውነተኛ ድሃ መሆን ያስፈልጋል። አንዳንድ ለማኞች በመንገድ ላይ ስቀመጡ ለመዝናኛ የተቀመጠ ሰው የሚመስሉም አሉ። ለመለመን ወጥቷሉ ግን የመለመን ዘዴ አላወቁም። አንድ ብርም ሳይወስዱ ማታ ጨርቃቸውን ሰብስበው ወደ ቤት ይመለሳሉ፤ ሌሎች ግን የሰውን አንጀት በቃላቶቻቸው በልተው ብዙ ብር ሰብስበው ይገባሉ። ይህ የልዩነታቸው ምስጥር የቃላቶች ክብደትና ቅለት ላይ የተፈጠረ ነው። በዛውም ልክ እግዚአብሔር የሚያየው አጥብቆ የሚጸልየው ሰው ብቻ ነው። አንዳንድ ሰው በልቡ ሌላ ነገር እያሰበ የአጠገቡ ሰው ሰለተምበረከከ ብቻ ተምበርክኮ ለመንኩ ብሎ መልስ ይጠብቃል። ጸሎቱ ከልቡ የመነጨ ስላልሆነ መልሱን አያገኝም። በእርግጥ የአንድ ሰው የነገሩ ክብደት ሰውዬ እንዳደረገው ይሆናል። ይህ ማለት ለነገሩ ክብደት ሳይሰጥ ቀለል አድርጎ ካዬ ለእሱ ቀላል ነው፤ ከባድ ነው ብሎ value ሰጥቶ ካሰበ ይከብዳል፤ በክብደቱ ልክም ይጸልያል። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙ ቦታ እግዚአብሔር ለጸሎታቸው መልስ የሰጣቸው ሰዎች ስንመለከት በጸሎታቸው ጀርባ "አጥብቀው ጸለዩ፣ አጥብቀው ለመኑ፣አብዝተው ጮኹ፣እምባቸውን አፈሰሱ፣... የሚሉ ቃላቶችን እናገኘዋለን። የዛን ቦታ ደግሞ ጸሎታቸውን ሰማ፣ መለሰላቸው፣ ፈወሳቸው... የሚሉ ቃላቶች አሉ። የጸሎት መልስ ያለው አጥብቆ በመጸለይ ላይ ነው እንጂ በምኞትና እንደ ተራ ነገር አድርገን ከፈለክ ስጠኝ ካልፈለክ ተውው እነደሚባል አይነት ጸሎት በመጸለይ አይደለም። ስፈልግ መጸለይ ካልፈለገ መተው፣ ቀጠሮ እየሰጠ እንደ dim-light ብርሃን ቦግ-ጥርቅም ማለት የጸሎት ባህርይ አይደለም። ያዕ 5፥17-18 የኤልያስ ጸሎት እንመልከት ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥ ሰማዩም ዝናብን ሰጠ ምድሪቱም ፍሬዋን አበቀለች። መልስ ያለው በማጣበቅ ላይ ነው እንጂ ፈዛዛ ጸሎት ጸልየህ ኢየሱስን ጥፋተኛ አታደርግየሃናም በጸሎት እንመልከት፦ ሃና በየአመቱ ሊትጸልይ ወደ ኢየሩሳሌም ትወጣ ነበረች። ነገር ግን ነገሩ ስከብድባትና ስጨንቃት በመጨረሻ ላይ አጥብቃ ጸለየች። የተጠቀመችው ቃላቶችም የሚገርሙና የእግዚአብሔርን ልብ የሚነኩ ናቸው። 1ሳሙ 1፥10-11እርስዋም በልብዋ ትመረር ነበር፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸለየች፥ ጽኑ ልቅሶም አለቀሰች። እርስዋም። አቤቱ፥ የሠራዊት ጌታ ሆይ፥ የባሪያህን መዋረድ ተመልክተህ ብታስበኝ፥ እኔንም ባትረሳ፥ ለባሪያህም ወንድ ልጅ ብትሰጥ፥ ዕድሜውን ሁሉ ለእግዚአብሔር እሰጠዋለሁ፥ ምላጭም በራሱ ላይ አይደርስም ብላ ስእለት ተሳለች። ይህ ንንግሯ ነው የእግዚአብሔርን ሆድ የበላው። በፊትም እግዚአብሔር ጸሎቷን ያቆየው ወደ እርሱ ስላልደረሰ ሳይሆን ከአንደበቷ የፈለገው ቃላቶችና የጸሎት ክብደት አለ ማለት ነው። ማህጸኗንም አውቆ እንደ ዘጋ በቁ.6 ላይ ይናገራል። የጸሎቷ ቃላቶች በክሎ ተመዝኖ ክብደት ካገኘ በኋላ ነው የመለሰላት። እግዚአብሔር የፈለገውን ደረጃ ደርሰን እስክንጸልይ ድረስ የጸሎታችን መልስ እንደማይመልስ ይህ ጥሩ ማሳያ ነው። ዛሬ ለእኛም የትኛው ቃላት ጠብቆ እንዳቆየን መፈለግ አለብን። በሉቃ 18፥35 እና ማር 10፥46 ላይ የተጻፈው የጤሜዎስ ልጅ ዕውሩ በርጠሜወስ አብዝቶ ባይጮኽና ሰዎች ዝም በል ስሉት ዝም ብል እፈወስ ነበረ? ምን አስጮኸው? የችጎሩ ክብደት ስለታየውና ይህ ፈዋሹ አምላክ በአጠገበ ወጥቶ ሳያልፍ እድለን ልሞክር ብሎ ነው። ሁለተኛ ይህንን ዕድል አላገኝም ብሎ ሳይፈራ አብዝቶ ጮኾ ተፈወሰ። መጮህ ማለት ኢየሱስ ሳያልፍ አጠገብህ እያለ ነውና ዛሬ ጮሄህ ተፈወስ ወንድሜ። አብዝቶ መለመንና አብዝቶ መጮህ ለጥያቄ መልስ ይሰጣል። በመሀል gap እየሰጠን የሚንጸለየው ጸሎትና ትዝ ስለን ብቻ ጌታ ሆይ እኔን መቼ ትመለከተኛለህ? ማለት ለጸሎታችን መልስ ያዘገያል፤ እንጠነቀቅ። ሉቃ 18፥1-8 ሳይታክቱም ዘወትር ሊጸልዩ እንዲገባቸው የሚል ምሳሌን ነገራቸው፥ እንዲህ ሲል። በአንዲት ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም የማያፍር አንድ ዳኛ ነበረ። በዚያችም ከተማ አንዲት መበለት ነበረች፥ ወደ እርሱም እየመጣች። ከባላጋራዬ ፍረድልኝ ትለው ነበር። አያሌ ቀንም አልወደደም፤ ከዚህ በኋላ ግን በልቡ። ምንም እግዚአብሔርን ባልፈራ ሰውንም ባላፍር፥ ይህች መበለት ስለምታደክመኝ ሁልጊዜም እየመጣች እንዳታውከኝ እፈርድላታለሁ አለ። ጌታም አለ። ዓመፀኛው ዳኛ ያለውን ስሙ። እግዚአብሔር እንኪያስ ቀንና ሌሊት ወደ እርሱ ለሚጮኹ ለሚታገሣቸውም ምርጦቹ አይፈርድላቸውምን? እላችኋለሁ፥ ፈጥኖ ይፈርድላቸዋል። ነገር ግን የሰው ልጅ በመጣ ጊዜ በምድር እምነትን ያገኝ ይሆንን? ወንድሞችና እህቶች በእግዚአብሔር ፊት መጸለያችን ካልቀረ ሚዛኑን የሚያነሳ ጸሎት እንጸልይ እንጂ ክብደት የሌለውን ጸልየን እግዚአብሔርን አንወቅስ። አንዳንድ ሰው ተቸግሮ አንድ ማታ ከጸለየ 2ኛው ቀን እግዚአብሔር ረሳኝ ጸሎተን አይመልስም ብሎ ለውቀሳ ይቸኩላል። እንኳን ኢየሱስ አንተን ሊረሳና የራስህን ጸጉር ቁጥር ያውቃል። መጀመሪያ ጸሎትህን አስተካክል፤ እረሱ እንደሚፈልግህ ሆነህ ቅረብ። ሐዋ ሥራ 2፥5 ላይ ጴጥሮስ በወህኒ ስታሰር ምዕመናን ወደ ቤተክርስቲያን ገብተው አጥብቀው ጸለዩለት። እጅ እግሩን በሰንሰለት የታሰረውን ጸሎት ብቻ ፈታች። እስክ አንተ/ች አጥብቀህ/ሺ ጸልይ/ዪ ጸሎት እንደማይፈታ ታያለህና/ሺና። ነገር ግን አጥብቀህ/ሺ ሳትጸልይ/ዪ እግዚአብሔርን አትወቅስ/ሺ። ይቀጥል የሚትሉ ወንድሞችና እህቶች በግሩፕ ላይ ብያንስ 10 ሰው add አድርጉ። ይቀጥላል...... @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH INBOX @Thaddyapostolic GROUP @Marantawoch

#የሐሰተኞች_ነቢያት_ባሕሪያት 1) እግዚአብሔር ሳይናገር ትንቢት የሚናገሩ ናቸው ሕዝ 22፡28 2) ሳይላኩ የሚሄዱ ናቸው ኤር 23፡1፤የሐዋ-ሥራ 15፡24 3) ይሳካልሃል እያሉ ገዥዎቸንና ባለጠጎችን የሚያታልሉ ናቸው 1ነገሥ 22፡5-6፤የሐዋ.ሥራ 13፡6-12 4) ተሳዳቢዎች ናቸው 2ጴጥ 2፡9-12፣ይሁዳ 1፡10 ራዕይ 13፡5 5) ዳፋሮችና ኩሩዎች ናቸው 2ጴጥ 2፡10 6) ቅንን መንገድ የሳቱ ናቸው 2ጴጥ 2፡15፤ይሁዳ 1፡15 7) ኃጢኣትን የማይተው ናቸው 2ጴጥ 2፡14 8) የሚያጠፋ ኑፋቁ አሾልከው የሚያገቡ ናቸው 2ጴጥ 2፡1 9) ብዙዎችን በመዳራታቸው የሚያስከትሉ ናቸው 2ጰጥ 2፡2 10) ገንዘብን ያአግባብ በመሰብስብ የተጠመዱ ናቸው 2ጴጥ 2፡3 11) ክንቱ የሆነ ከመጠን በላይ ቃል ይናገራሉ 2ጴጥ 2፡18 ራዕይ 13፡5 12) ራሳቸውን ከመጠን በላይ ከፍ ከፍ የሚያድርጉ ናቸው 2ተስሎንቄ 2፡4 13) ውኃ የሌለባቸው ምንጮችና ዝናብ የሌለባቸው ደመናዎች ናቸው 2ጴጥ 2፡17፤ ይሁዳ ቁ-12 14) የሚንከራተቱ ከዋክበት ናቸውጨይሁዳ ቁ- 13 15) የሰይጣን ስህተት አሠራር መሣሪያዎች ናቸው 2ተስሎንቄ 2፡7-12 16) የጥፋት ባሪያዎች ሆነው አርነት ትወጣላችሁ የሚሉ ናቸው 2ጴጥ 2:19 17) ጸጋውን በሴሰኝነት የሚለውጡ ናቸው ይሁዳ 1:4 ቁ.7 2ጴጥ2:18 18) በሀሰተኛ ድንቆችና ታኣምራቶች የታጀቡ ናቸው 2ተሰሎንቄ 2:9-10; ማቴ 24:24; ራዕይ 13:13 19) ያለእውነተኛው ኢየሱስ እውቅና በውሸት አጋንንት የሚያስወጡ ናቸው ማቴ 7:22 20) የእውነተኛ አገልጋዮች መልክ የያዙ ግን በውስጣቸው ነጣቂዎች ናቸው ሜቴ 7:15; 2ቆሮ 11:13 21) እውነተኛውን ኢየሱስን የሚሰብኩ ይመስላሉ ነገር ግን በሥራቸው የካዱ ናቸው ይሁዳ 1:4; ቲቶ 1:16 22) የማይጸኑ ነፍሳትን የሚያታልሉ ናቸው 2ጴጥ 2:14 23) እየሳቱ የሚያስቱ ናቸው 2ጢሞ 3:13 24) ለፍርድ የተመደቡ ናቸው ይሁዳ 1:4 ቁ-14 25) ውሸተኞች ሐዋሪያትና ተንከለኞች ሠራተኞች ናቸው 2ቆሮ 11:13 26) እንደብርሃን መልአክ ራሳቸውን ልለውጡ ይችላሉ 2ቆሮ11 27) ታላቅ ነገርና ስድብ የሚናገሩበት አፍ አላቸው ራዕይ 13:5 28) አጋንንታዊ ግን ማራኪ ትምህርት ያስተምራሉ 1ጢሞ 4:1 29) ዓለምን ሀብትና ክብር ሰይጣን ለኢየሱስ የሰበካውን ይሰብካሉ ማቴ 4:6 30) ያለሥርዓት የሚሄዱና የሚኖሩ ናቸው 2ተሰሎንቄ 3:11 31) ነውረኛ ረብ ለማግኘት የሚተጉ ናቸው ቲቶ 1:11-12 32) የማይታዘዙ፤ከንቱ የሚናገሩና የሚያታልሉ ናቸውቲቶ 1:10 33) እውነተኛውን የእግዚአብሔርን ቃል ገልብጠው የምናገሩ ናቸው ዘፍ 3:4 ፤ቲቶ1:1 34) መንፈሳዊ የሚመስል የተድላ ዘፈን የሚዘፍኑ ናቸው 2ጴጥ 2፡13 35) ከሰማይ እሳት እስኪያወርዱ ታላላቅ ምልክቶችን ሊያደርጉ ይችላሉ ራዕይ 13:13 36) በምዕመናን መካከል ወይም በባልና በሚሰት መካክል መለያያትን የሚዘሩ ናቸው ሮሜ 16፡17፤ቲቶ 3፡10-11 37) ወደምዕመናን መካክል ሾልከው የሚገቡ ናቸው 2ጢሞ 3፡6-7፤ይሁዳ ቁ- 4 38) ክርስቶስን ለመምሰል የሚስማማ ጤናማ ትምህርት የማያስተምሩ ናቸው1ጠሞ 6፡3 39) በትዕቢት የተነፉ ናቸው 1ጢሞ 6፡4 40) እግዚአብሔርን መምሰል ማትረፊያ አድርገው የሚጠቀሙ ናቸው 1ጢሞ 6፡5 41) ለሆድ የተገዙ ናቸው ሮሜ16፡18፤ፊልጵ 3፡19 42) በመልካምና በሚያቆላምጥ ንግግር የሚያታልሉ ናቸውሮሜ 16፡18 43) እውነትን የተቀሙ ናቸው 1ጠሞ 6፡5 44) ቃሉን የሚያጣምሙ ናቸው 2ጼጥ 3:16 45) ዓመፀኞች ናቸው 2ጴጥሮስ 3:17; 2:13 46) ሥልጣን ያላቸውን/መሪዎችን በድፍረት ይሳደባሉ 2ጴጥ 2:10 47) ለመንጋው የማይራሩ ጨካኞች ናቸው የሐዋ 20:29 48) ደቀ መዛሙርትን ወደኃላ የሚስቡ ናቸው የሐዋ 20:30 49) ጠማማ ነገርን የሚናገሩ ናቸው ሐዋ 20:30 50) የተማራችሁትን እውነተኛ ትምህርት የሚቃወሙ ናቸው ሮሜ 16:17 51) መለያየትንና ማሰናከያ የሚያደርጉ ናቸው ሮሜ 16:17 52) በመልካምና በሚያቆላምጥ ንግግር ተንኮል የሌለባቸውን ሰዎች ልብ ያታልላሉ ሮሜ 16:18 53) የዋጃቸውን ጌታ የሚክዱ ናቸው 2ጴጥ 2፡1፤ይሁዳ ቁ-4) 54) ፍጻሜአቸው ግን እንደሥራቸው ይሆናል! 2ቆሮ 11:15 ማጠቃለያ ሮሜ 16:17 ወንድሞች ሆይ እናንተ የተማራችሁትን ትምህርት የሚቃወሙትን መለያየትንና ማሰናከያን የሚያደርጉትን ሰዎች እንድትመለከቱ እለምናችኋለሁ ከነእርሱ ዘንድ ፈቀቅ በሉ። @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH

📌የሙት ባህር ጥቅልሎች (The Dead Sea Scrolls) ⚜በታሪክ፣ በሃይማኖት እናበአርኪኦሎጂ ዘርፍ እጅግ አስፈላጊ እና በዓለም ታዋቂ የሆኑ ጥንታዊ የጽሁፍ ሰነዶች ናቸው። ስለ እነዚህ ጥቅልሎች ማወቅ የሚገቡዎትን ዋና ዋና ነጥቦች እንደሚከተለው አዘጋጅቼላቸዋለሁ፦ 1. 📌ግኝቱ (Discovery)ጥቅልሎቹ የተገኙት በ1947 እና በ1956 መካከል፣ በምዕራብ ባንክ በሚገኘው ቁምራን (Qumran) በተባለ ቦታ አቅራቢያ በሚገኙ ዋሻዎች ውስጥ ነው። በአጋጣሚ የተገኙት በአንድ በዱር በግ እረኛ ወጣት ሲሆን፣ በሸክላ ማሰሮዎች ውስጥ ተጠቅልለው ለዘመናት ሳይበላሹ ቆይተው ነበር። 2. 📌ይዘታቸው (What are they?) በድምሩ ወደ 900 የሚጠጉ የእጅ ጽሁፎች ተገኝተዋል። እነዚህም በዋነኝነት የተጻፉት በዕብራይስጥ፣ በአረማይክ እና በጥቂቱ በግሪክ ቋንቋዎች ነው። ዋና ይዘታቸውም የሚከተሉትን ያጠቃልላል፦ •   የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች፦ ከመጽሐፈ አስቴር በስተቀር፣ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት በሙሉ (ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል) ተገኝተዋል። ከነዚህ መካከል በጣም የታወቀው የኢሳይያስ ትንቢት ሙሉ ጥቅልል ነው። •   የኑሮ መመሪያዎች፦ በቁምራን ይኖሩ የነበሩ ሰዎች (አሴንስ ይባላሉ ተብሎ ይታመናል) ህጎች፣ የጸሎት መጽሐፍት እና የስርዓተ አምልኮ ደንቦች። •   የአፖካሊፕቲክ ጽሁፎች፦ ስለ መጨረሻው ዘመን፣ ስለ ብርሃን እና ጨለማ ልጆች ትግል የሚያወሱ ምስጢራዊ ጽሁፎች። 3. 📌ለምን አስፈላጊ ናቸው? የሙት ባህር ጥቅልሎች በዓለም የሃይማኖት ታሪክ ውስጥ ትልቅ ለውጥ ያመጡበት ምክንያቶች፡- •  📌 የብሉይ ኪዳን አስተማማኝነት፦ እነዚህ ጥቅልሎች ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ250 እስከ ክርስቶስ ልደት በኋላ ባለው ጊዜ የተጻፉ ናቸው። ከነዚህ ጥቅልሎች በፊት የነበሩን የብሉይ ኪዳን ቅጂዎች ከዘጠነኛው ክፍለ ዘመን በኋላ የተጻፉ ነበሩ። በሁለቱ መካከል የሺህ ዓመት ልዩነት ቢኖርም፣ የጽሁፎቹ ይዘት እጅግ ተመሳሳይ መሆኑ የመጽሐፍ ቅዱስ ጽሁፎች በጊዜ ሂደት ሳይለወጡ እንደተጠበቁ የሚያሳይ ጠንካራ ማስረጃ ሆነ። •   የጁዳይዝም እና የክርስትና መነሻ፦ ጥቅልሎቹ በኢየሱስ ክርስቶስ ዘመን የነበረውን የአይሁድ እምነት ሁኔታ፣ አስተሳሰብ እና የኑሮ ሁኔታ በግልጽ የሚያሳዩ ናቸው። የክርስትና መነሻ ከነበረው የአይሁድ ባህል ጋር ያለውን ግንኙነት ለመረዳት ትልቅ ሚና ተጫውተዋል። 4. 📌ማን ጻፋቸው? ምሁራን በአብዛኛው እንደሚያምኑት፣ እነዚህን ጽሁፎች የጻፉት አሴንስ (Essenes) የሚባሉ የአይሁድ ቡድን አባላት ናቸው። እነዚህ ሰዎች ከኢየሩሳሌም ከተማ በመውጣት፣ ከብክለት ለመራቅ እና በንጽህና ለመኖር ወደ በረሃው ገብተው ይኖሩ እንደነበር ይገመታል። 📌 5. አሁን የት አሉ? አብዛኛዎቹ የጥቅልል ክፍሎች የሚገኙት በኢየሩሳሌም በሚገኘው "የመጽሐፍ ቤተ መቅደስ" (Shrine of the Book) ውስጥ ነው። ይህ ህንጻ የተገነባው ጥቅልሎቹ በተገኙበት የሸክላ ማሰሮ ቅርጽ ተመስሎ ነው። @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH

አስተማሪ ታርክ #አንዲነታችን_ይጠበቅ 🐂 የጅቡና የሶስቱ በሬዎች ተረት ከዕለታት አንድ ቀን ነጭ፣ ቀይና ጥቁር የሆኑ ሶስት በሬዎች አብረው ይኖሩ ነበር። አንድነታቸውም ስለጠነከረ አውሬዎች ቢመጡባቸው በአንድነት ይዋጉ ነበር። አንድ ጅብ ግን በሬዎቹን አይቶ፦ “እነዚህን ሶስቱን አብረው እያሉ መብላት አልችልም፤ መከፋፈል አለብኝ” ብሎ አሰበ። ጅቡም በሬዎቹን ከሩቅ እየተመለከተ አንድ ቀን መጣና ነጩን በሬ ነጥሎ፦ “እናንተ ቀይና ጥቁሮች በጨለማ አትታዩም። እኛ ግን ነጩን በሬ ከሩቅ እያየን ነው የምንመጣው። እሱን ብታባርሩት እናንተን አንረብሽም” አላቸው። በሬዎቹም የጅቡን ቃል አምነው፣ ነጩን በሬ ከመካከላቸው አባረሩት። ጅቦቹም ነጩን በሬ ለብቻው አግኝተው በሉት። ከዚያም ጅቡ ወደ ጥቁሩና ቀዩ በሬ ተመልሶ ጥቁሩን፦ “አንተ ጥቁር ስለሆንክ በጨለማ አትታይም፤ ቀዩ ግን ከሩቅ ይታያል። እሱን ብታስወግድ ሰላም ታገኛለህ” ብሎ አሳመነው። በመጨረሻም ቀዩን በሬ ከጥቁሩ በሬ አለያዩት። ጅቦቹም ቀዩን በሬ ለብቻው አግኝተው በሉት። ጥቁሩ በሬ ብቻውን ሲቀር ጅቦቹ በቀላሉ ከበቡት። በዚያን ጊዜ ጥቁሩ በሬ ተንኮሉን ተረዳ፤ ግን በጣም ዘግይቶ ነበር። ስለዚህ “ጠላት አንድነትን ማፍረስ ከቻለ ማሸነፍ ይችላል። ስለዚህ በተለያዩ ምክንያቶች መከፋፈል ሳይሆን አንድነትን መጠበቅ ያስፈልጋል። @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH

ግጥም አገልጋዮች እንሁን 〰〰〰〰〰〰〰 ይድረስ ለወጣቶች በዚ ዘመን ላለን የቅዱስ የእግዚአብሔር ልጆቹ ለሆንን የኢየሱስን ስራ ድቃድቁን ላየን ከጥፋት ሊያድነን በደሙ ለገዛን እግዚአብሔር ለስራው ሰውን ይፈልጋል ወታደር ሊያደርገን ጌታ የሱስ ይሻል ታዲያ ወንድሜ ሆይ አንቺም የኔ እህት ተዘጋጅተን ይሆን ልፈፅም እቅዱን ለእግዚአብሔር ስራ አገልጋይ ለመሆን እግዚአብሔር ሰርቷል ጥንት በነቢያት ህዝቡን አስተምሯል ባባቶች አንደበት በሙሴ ተጠቅሞ ህዝቡን ሲያሶጣ በልጁ በእያሱ አህዛብን ሲቀጣ እንደልቤ ባለው ጎልያድን ሲመታ ደግሞም በኤልያስ በአልን ሲረታ በፈጠረው ፍጥረት ያውም በሰው ልጅ ነው ለቅዱስ አላማ አገልጋይ ያረገው ሐዋሪያትን መርጦ ወንጌልን ሲያሰብክ ከለም ዳር እስከዳር ፍጥረትን ሲማርክ አባቶችም ደግሞ ይህን ተረክበው እዚ አድርሰዋል በአገልግሎት ኖረው እናም በዚ ዘመን አንተን እኔን መርጧል እግዚአብሔር ለስራው ሰውን ይፈልጋል ታዲያ ወንድሜ ሆይ አንቺም የኔ እህት ተዘጋጅተን ይሆን ልፈፅም እቅዱን ለእግዚአብሔር ስራ አገልጋይ ለመሆን የቱ ይጠቅመናል የቱስ ይሻለናል? አለምን ወደናት አገልግሎት ትተን ግያዝን እንሁን ምንወርስ ሀጢያትን ወይስ ካባቶች ጎን ሳጠፋ ሳንለይ መሆን እደ ኤልሳዕ በእጥፍ አገልጋይ እንምረጥ መልካሙን የሂወት ጎዳና አገልጋዮች ያርገን ያዎጣናልና። @MARANATHAWOCH

# አለመፍረድ 🕎ክፉንና ደጉን እንደየስራዉ የምለየዉ ብቸኛው ጌታ እየሱስ ነዉ። አንድ ሰዉ "ሰው "እንደመሆኑ ላጠፋ ይችላል ግን ላጠፋው ጥፋት የምፈርደዉም በደሉን የምሽረዉ እሱ እየሱስ ብቻ ነዉ ምክንያቱም ጻድቅ እሱ ስለሆነ።          ዮሐንስ 8  ፥ 3፤ ጻፎችና ፈሪሳውያንም በምንዝር የተያዘችን ሴት ወደ እርሱ አመጡ በመካከልም እርሱዋን አቁመው፡—4፤ መምህር ሆይ፥ ይህች ሴት ስታመነዝር ተገኝታ ተያዘች።5፤ ሙሴም እንደነዚህ ያሉት እንዲወገሩ በሕግ አዘዘን፤ አንተስ ስለ እርስዋ ምን ትላለህ? አሉት።7፤ መላልሰው በጠየቁት ጊዜ ግን ቀና ብሎ፡— ከእናንተ ኃጢአት የሌለበት አስቀድሞ በድንጋይ ይውገራት፡ አላቸው። 9፤ እነርሱም ይህን ሲሰሙ ሕሊናቸው ወቀሳቸውና ከሽማግሌዎች ጀምረው እስከ ኋለኞች አንድ አንድ እያሉ ወጡ፤ ኢየሱስም ብቻውን ቀረ ሴቲቱም በመካከል ቆማ ነበረች።10፤ ኢየሱስም ቀና ብሎ ከሴቲቱ በቀር ማንንም ባላየ ጊዜ፡— አንቺ ሴት፥ እነዚያ ከሳሾችሽ ወዴት አሉ? የፈረደብሽ የለምን? አላት።11፤ እርስዋም፡— ጌታ ሆይ፥ አንድ ስንኳ አለች። ኢየሱስም፡— እኔም አልፈርድብሽም፤ ሂጂ ከአሁንም ጀምሮ ደግመሽ ኃጢአት አትሥሪ፡ አላት።           የደከመውን ማበርታት የተሳሳተ መንገድ የምሄዱትን እህት ዉንድሞቻችንን መምከር ፤ መመለስ እርስ በርሳችን በመንፈሳዊ ህዉይት በጸሎት መተጋገዝ ነዉ የኛ ስራ መሆን ያለበት ምክንያቱም ስለራሳችንም አናዉቅምና።                ማቴዎስ 7 ፥ 1-2፤ እንዳይፈረድባችሁ አትፍረዱ፤ በምትፈርዱበት ፍርድ ይፈረድባችኋልና፥ በምትሰፍሩበትም መስፈሪያ ይሰፈርባችኋል።3፤ በወንድምህም ዓይን ያለውን ጉድፍ ስለምን ታያለህ፥ በዓይንህ ግን ያለውን ምሰሶ ስለ ምን አትመለከትም?4፤ ወይም ወንድምህን፡— ከዓይንህ ጉድፍ ላውጣ ፍቀድልኝ፡ እንዴትስ ትለዋለህ? እነሆም፥ በዓይንህ ምሰሶ አለ።5፤ አንተ ግብዝ፥ አስቀድመህ ከዓይንህ ምሰሶውን አውጣ፥ ከዚያም በኋላ ከወንድምህ ዓይን ጉድፉን ታወጣ ዘንድ አጥርተህ ታያለህ። እንዳይፈረድብን አንፍረድ እንዳይሰፈርብን አንስፈር ፤ በምትሰፍሩበት መስፈረያም ይሰፈርባችኋና ይላል  ። ፈራጅ  አምለክ ብቻዉን ያለ እየሱስ ስለሆነ ፦        ሮሜ 14  ፥ 10፤ አንተም በወንድምህ ላይ ስለ ምን ትፈርዳለህ? ወይስ አንተ ደግሞ ወንድምህን ስለ ምን ትንቃለህ? ሁላችን በክርስቶስ ፍርድ ወንበር ፊት እንቆማለንና። አቤቱ አምላካችን ሆይ እስከ ዛረ ባለማዉቃችን በድለናል አንተን ብቻ አሳዘንህ፤  ባለማዉቃችን ስላደረግነዉ በደል ሁሉ ይቅር በለን " ማረን"!!!

# አለመፍረድ 🕎ክፉንና ደጉን እንደየስራዉ የምለየዉ ብቸኛው ጌታ እየሱስ ነዉ። አንድ ሰዉ "ሰው "እንደመሆኑ ላጠፋ ይችላል ግን ላጠፋው ጥፋት የምፈርደዉም በደሉን የምሽረዉ እሱ እየሱስ ብቻ ነዉ ምክንያቱም ጻድቅ እሱ ስለሆነ።          ዮሐንስ 8  ፥ 3፤ ጻፎችና ፈሪሳውያንም በምንዝር የተያዘችን ሴት ወደ እርሱ አመጡ በመካከልም እርሱዋን አቁመው፡—4፤ መምህር ሆይ፥ ይህች ሴት ስታመነዝር ተገኝታ ተያዘች።5፤ ሙሴም እንደነዚህ ያሉት እንዲወገሩ በሕግ አዘዘን፤ አንተስ ስለ እርስዋ ምን ትላለህ? አሉት።7፤ መላልሰው በጠየቁት ጊዜ ግን ቀና ብሎ፡— ከእናንተ ኃጢአት የሌለበት አስቀድሞ በድንጋይ ይውገራት፡ አላቸው። 9፤ እነርሱም ይህን ሲሰሙ ሕሊናቸው ወቀሳቸውና ከሽማግሌዎች ጀምረው እስከ ኋለኞች አንድ አንድ እያሉ ወጡ፤ ኢየሱስም ብቻውን ቀረ ሴቲቱም በመካከል ቆማ ነበረች።10፤ ኢየሱስም ቀና ብሎ ከሴቲቱ በቀር ማንንም ባላየ ጊዜ፡— አንቺ ሴት፥ እነዚያ ከሳሾችሽ ወዴት አሉ? የፈረደብሽ የለምን? አላት።11፤ እርስዋም፡— ጌታ ሆይ፥ አንድ ስንኳ አለች። ኢየሱስም፡— እኔም አልፈርድብሽም፤ ሂጂ ከአሁንም ጀምሮ ደግመሽ ኃጢአት አትሥሪ፡ አላት።           የደከመውን ማበርታት የተሳሳተ መንገድ የምሄዱትን እህት ዉንድሞቻችንን መምከር ፤ መመለስ እርስ በርሳችን በመንፈሳዊ ህዉይት በጸሎት መተጋገዝ ነዉ የኛ ስራ መሆን ያለበት ምክንያቱም ስለራሳችንም አናዉቅምና።                ማቴዎስ 7 ፥ 1-2፤ እንዳይፈረድባችሁ አትፍረዱ፤ በምትፈርዱበት ፍርድ ይፈረድባችኋልና፥ በምትሰፍሩበትም መስፈሪያ ይሰፈርባችኋል።3፤ በወንድምህም ዓይን ያለውን ጉድፍ ስለምን ታያለህ፥ በዓይንህ ግን ያለውን ምሰሶ ስለ ምን አትመለከትም?4፤ ወይም ወንድምህን፡— ከዓይንህ ጉድፍ ላውጣ ፍቀድልኝ፡ እንዴትስ ትለዋለህ? እነሆም፥ በዓይንህ ምሰሶ አለ።5፤ አንተ ግብዝ፥ አስቀድመህ ከዓይንህ ምሰሶውን አውጣ፥ ከዚያም በኋላ ከወንድምህ ዓይን ጉድፉን ታወጣ ዘንድ አጥርተህ ታያለህ። እንዳይፈረድብን አንፍረድ እንዳሰፈርብን አንስፈር ፤ በምትሰፍሩበት መስፈረያም ይሰፈርባችኋና ይላል  ። ፈራጅ  አምለክ ብቻዉን ያለ እየሱስ ስለሆነ ፦        ሮሜ 14  ፥ 10፤ አንተም በወንድምህ ላይ ስለ ምን ትፈርዳለህ? ወይስ አንተ ደግሞ ወንድምህን ስለ ምን ትንቃለህ? ሁላችን በክርስቶስ ፍርድ ወንበር ፊት እንቆማለንና። አቤቱ አምላካችን ሆይ እስከ ዛረ ባለማዉቃችን በድለናል አንተን ብቻ አሳዘንህ፤  ባለማዉቃችን ስላደረግነዉ በደል ሁሉ ይቅር በለን " ማረን"!!!

የማለዳ ትምህርት የጸሎታችን መልስ ለምን ይዘገያል? ክፍል 10 ጸሎትን የሚሰማ አምላክ ለይቶ አለማወቅ በዚህ ምድር ላይ ሰው ለሰው ደብዳቤ ስጽፍ የደብዳቤ መነሻና መድረሻ እንዳለው ሁላ ለጸሎትም መነሻና መድረሻ አለው። መነሻ ከዚህ ከሰውዬው ብሆን እንኳ መድረሻው ግን የሚሰማ አምላኬ ነው ብሎ የሚያምን አካል መኖር አለበት። ለብዙ ሰዎች ችግራቸው ግን ማን እንደሚሰማቸው ወደ ማን እንደሚጸልዩ አለማወቅ ነው። ስለዚህ ይህ ጸሎት የሚቀርብለት /የሚደርስለት/ አካል በእውነትም ጸሎታችንን ሰምቶ የሚመልስ አምላክ ነው ወይስ አይደለም የሚለውን ማወቅና ማጣራት ወሳኝ ነጥብ ነው። ሰው አምላኬ ነው ብሎ በተዘዋዋሪ መንገድ አማልክትን ማምለክ ወይም መጸለይ ይችላል። ነገር ግን ለጸሎት መልስ የሚመልሰው አንዱ እውነተኛ አምላክ እንጂ አማልክት አይደሉም ። ጸሎትን የሚሰማ አምላክ ለይቶ ሳያውቅ በየቀኑ መጾምና መጸለይ ሞኝነት ነው። ከጸሎት በፊት ሰምቶ እውነተኛ መልስ የሚሰጥ አምላክ ማወቅ ወሳኝ ነው፤ አለበለዚያ በየቀኑ ወደማይሰማ አምላክ እየጸለየ መኖር ነው። መዝ 115፥4-8 እና 135፥15-18 የአሕዛብ ጣዖታቶች የወርቅና የብር፥ የሰው እጅ ሥራ ናቸው። አፍ አላቸው አይናገሩምም፤ ዓይን አላቸው አያዩምም፤ ጆሮ አላቸው አይሰሙምም፤ አፍንጫ አላቸው አያሸትቱምም፤ እጅ አላቸው አይዳሰሱምም፤ እግር አላቸው አይሄዱምም፤ በጕሮሮአቸውም አይናገሩም። የሚሠሩአቸውም የሚያምኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ። ዛሬም ወደ እኛ ዘመን ብንመጣም በተዘዋዋሪ ሰው ሁሉ ወደማይመለስ አምላክ እየጸለዬ ከኮንፈረንስ ወደ ኮንፈረንስ እየዞረ ይገኛል። አጠገባችን ያሉ ሰዎች ብዙዎችን እንታዘባለን፤ በየቀኑ የት እየጎረፈ ነው ብባል ዛሬ ያቺ ሰፈር ነብዩ እገለ መጥቷል፣ ነገም ያኛው ሰፈር የሆነ ነብይ መጣ፣ ቀጣይ ሳምንትም የሆነ ታላቅ ነብይ ሰፈራችን መጣ፣... ለኮንፈረንስም ደግሞ በየቀኑ ስም ተሰይሟል። አንዴ ነጻ የመውጣት ኮንፈረንስ፣ አንዴ የፋይናንስ ድርመሳ፣ አንዴ ከክብር ወደ ክብር የመለወጥ ኮንፈረንስ፣.... ብቻ የማይወጣላት ስም የለም። እንደዚህ እየሆነ እየባዘነ ዘመኑን እየጨረሰ ነው። ይህንን የሚሆነው ግን አንድ እውነታ አላቸው። የተሸከሙት የችግራቸው ቀምበር ሊያደርጋቸው ይችላል። ግን ቆም ብሎ የሚሰማ አምላክ የት አለ የሚለውን ማየት ተስኖአቸዋል። የእገለ አምላክ፣ የእገለ አምላክ እያሉ በየሳምንቱ አማልክትን የሚጠሩ ሆኑ። በነብያቶች ብዛት የማን አምላክ  እንደሚሰማ እራሱ አያወቁም፣ እራሳቸውን ነብያቶች ነን ብለው የሰየሙት ግን የኔው ይበልጣል፤ የኔው ይበልጣል በሚል ፉክክር በየቀኑ ማስታወቂያ እያወጡ promotion እየሰሩ የህዘብ ልብ ያወካሉ። በእግዚአብሔር ትምህርት ጸንቶ ያልቆመ ትውልድ እረኛ እንደሌላቸው መንጋ በየቀኑ በትምህርት ንፋስ እየተወሰደ ይገኛል። ይህ ምንድነው ብባል አንዳንዶቹ "ብቻ የእግዚአብሔር ቃል የሚናገርበት ቦታ ይሁን እንጅ፣ ብቻ የኔ ችግር የሚያውቅ ነብይ ይሁን እንጅ፣ ብቻ ከዚህ ከችግሬ ይዉጣ እንጂ..." እያሉ አንድም ቀን እረፍት አያገኙም። እንደው አንድ ጊዜ ከአንድ ልጅ ጋር ስለ ሐሰተኛ ነብያቶችና ስለ ስራቸው መንፈሳቸውም የጠንቆላ መንፈስ መሆኑን ስናወራ ልጁ ምን አለኝ መሰላችሁ፦ " ነብዩ የትም የትም ጠንቆላ ሰርቶ ይምጣ፣ 666 አባልም ሆኖ ብሰራ፤ ለእኔ ግን በእግዚአብሔር ቃል ተናግሮ ችግረን የሚፈታ ከሆነ ምንም ችግር የለም እቀበላለሁ" አለኝ። ምን ማለት ፈልገ ነው ሰው በዚህ ልክ ነው ከእውነተኛ አምላክ የሸሸው። ለዚህ ሰውዬ በራሱ የሚሰራ ስንት ተአምራት እያለ የኔ ነገር ከነብዩ እጅ ብቻ ነው ብሎ እንዳመነ አስቡ። በእሱ ቤት የሚሰማ አምላክ ያለው ለነብዩ ብቻ ነው እንጅ ለራሱ የሚሰማ አምላክ የለውም ማለት ነው። ብዙ ሰዎች እንደዛ የሚያስቡ አሉ። ይህ ግን ወደሚሰማ አምላክ መጸለይ ሳይሆን አማልክትን መከተል ነው። እንኳን ሄዶ መጸለይና በቤተ/ያን ውስጥ ሆኖም በልቡ እየከጀለ ልቡን ማከፋፈል፣ የኔ ነገር ነብዩ እገለ ጋር ሄጄ ብጸልይ፣ እገለ ብጸልይልኝ ይቀረፋል መሰለኝ እያለ ልቡን በዛው ሰውጋር ማንልጠል እውነተኛ አምላክ ልቡንና ኩላልቱን ስለሚመረምረው ሀሳቡ እንደተሰረቀ ያውቃልና ለጸሎቱ መልሱ አይመለስለትም። ይህ ሰውዬ በልቡ አምላክ ሳይህን አማልክት እየለመነ ነው። እግዚአብሔርም በምድር ላይ የተደነቀው ነገር ብኖር ሰው ሁሉ ወደገዛ መንገድ ሄዶ የራሱን አምላክ ፈጥሮ ወደ እርሱ /ወደ እውነተኛ አምላክ / የሚማለድ ሰው እንደሌለ ተረድቶ ነው። ፤ ሰውም እንደሌለ አየ፥ ወደ እርሱ የሚማልድ እንደሌለ ተረዳ ተደነቀም፤ ስለዚህ የገዛ ክንዱ መድኃኒት አመጣለት፥ ጽድቁም አገዘው። /ት/ኢሳ 59፥16/ ወደ ምድር ሰውን ስመለከት ከአምላክ ይልቅ የአማልክት ክብር በዝቷል፣ ሰው ሁሉ ይሰማኛል ብሎ በየቀኑ ወደ አማልክት ይማለዳል፤ ወደ እውነተኛ አምላክ የሚማለድ አጣ፣ አየ፣ ተደነቀም። እኛስ ዛሬ ወዴት እየማለድን ነን? በእርግጥ የእኛ ወንድሞችና እህቶች ለዚህ ጉዳይ ጠንቃቃዎች መሆናቸውንና አንዱ እውነተኛ አምላክ እንዳላቸው አምናለሁ። ነገር ግን አልፎ አልፎ በማወቅም ባለማወቅም በሰው ግፊት ሾልከው እናያለን ብለው የሚሄዱ ሊኖሩ ይችላሉ። በአህዛብ በኩል ያላው የሚበልጥና እነርሱ እዚህ ተቀምጠው የተጎዱ የሚመስላቸውም አይጠፉም። ነገር ግን እርግጠኛ ነኝ እንደዚህ አይነት ሰዎች( አምላክንና አማልክትን) የሚትቀላቀሉ ሰዎች በእውነት ለጸሎታችሁ መቼም መልስ አትጠብቁ፤ ይልቅ እግዚአብሔር ከቁጣ ይጠብቃችሁ። ለእኛ ግን ሰምቶ በእሳት የሚመልስ አንዱ እውነተኛ የኤልያስ አምላክ ያለን ህዝብ ነን። ነገር ግን በቤተ/ያን ውስጥ ሆናችሁ በሁለት ሀሳብ አታነክሱ፤ እግዚአብሔር አምላክ ብሆን እርሱን ተከተሉና ወደ እርሱ ጸልዩ፤ በአል/ ነብይ/ አምላክ ብሆን እርሱን ተከተሉና አምልኩ። የሚበልጠውና እናያለን!! 1ኛ ነግ 18፥24-28 እናንተ አምብቡ አደራ። የማን አምላክ መልስ እንደሚሰጥ በግልጽ ተቀምጧል። አምላካችሁን ሳትለዩ እየጸለያችሁ ዘመናችሁን አትጨርሱ። እኛ ግን ጸሎትን ሰምቶ የሚመልስ አንዱን የኤልያስ አምላክ የሚናመልክና ወደ እርሱ የሚንጸልይ የአንዱ ሰዎች ነን። @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH INBOX @Thaddyapostolic GROUP @Marantawoch

ያ-ክብር-ይገለጥAddisaba-sebeka-Apostolic-song.m4a8.45 MB

ይቅር የሚል አምላክ!
ዘወትር ይቅርታ መጠየቅ ንሰሃ መግባት ከኢየሱስ ጋር ያለንን የአብሮነት መንገድ ብሩህ ያደርገዋል።
ማቴዎስ 6፡9-13 12፤ እኛም ደግሞ የበደሉንን ይቅር እንደምንል፥    በደላችንን ይቅር በለን፤ ኢየሱስ በየቀኑ ይቅርታ መጠየቅን ጨምሮ ለሚከተሉት የጸሎት ምሳሌ ሰጥቷቸዋል። አዘውትሮ ንስሐ መግባትና ይቅር በለን ማለት ከእግዚአብሔር ጋር ያለንን ህብረት የምናስተካክልበት ነው። በኢየሱስ ስም ስንጠመቅ ኃጢአታችን ለዘላለም ተሰርዮልናል—ያለፈው፣ የአሁን እና የወደፊት በደሎቻችን እድፍ ይደመሰሳል። የኃጢአት ዝንባሌ ግን የሰው ልጅ ልምምድ አካል ሆኖ ይቆያል፣ ምንም እንኳን ክርስቶስን እየመሰልን በሄድን ቁጥር ተፅዕኖው እየቀነሰ ቢሄድም። ከኢየሱስ በስተቀር ማንም ፍጹም አይደለም። ስለዚህ፣ በምድር ላይ ሳለን ሁላችንም ኃጢአትና መዘዙ ያገኘናል። በየእለቱ ይቅርታን እንድንፈልግ የጌታ ኢየሱስ ማሳሰቢያ ኃጢአታችንን እንድንናዘዝ እና ከኃጥያት እንድንርቅ ነው ይቅር ስለተባልን። የእግዚአብሔር ጸጋ የኃጢአት ፈቃድ አይደለም። ይልቁንም ጽድቅን ያለማቋረጥ ለመከታተል ምክንያት ነው። መጥፎ አመለካከቶች፣ ግድየለሽ ድርጊቶች እና ደግነት የጎደለው ንግግር እኛ በክርስቶስ አዲስ ፍጥረት ለመሆናችን አይመጥኑም። 1ኛ ዮሐንስ 1: 9፤ በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው። እርሱ ይቅር ለማለት ከታመነ እኛ ንሰሃ እየገቡ በየእለቱ ለመፀለይ አንታክት። ኃጥያት እንቅፋት እንዳይሆንብን። መልካምና የተባረከ ምሽት ይሁንላችሁ @MARANATHAWOCH

#ማነው #ሚታመነው ? አንድ ልናስተውል የሚገባን ነገር ቢኖር  እግዚአብሔርን  የምታውቅ እና በእግዚአብሔር የምትታወቅ አንዲት እምነት ሃይማኖት እዳለች ነው ። #አንድ ሃይማኖት ኤፌ  4:5 ስንት ሃይማኖት ❓ #አንድ #ሃይማኖት ማመን መታመን መልካም ገድል ነው። #የሚጠበቅ #የምንፀናበት መጨረስ የሚገባን #እሩጫ #ፅናት ነው " ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ፥ ጎልምሱ ጠንክሩ።" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 16:13) " ወዳጆች ሆይ፥ ስለምንካፈለው ስለ መዳናችን ልጽፍላችሁ እጅግ ተግቼ ሳለሁ፥ ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ።" (የይሁዳ መልእክት 1:3) "መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ፥ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤" (2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 4:7 ስለዚህ  #ማነው #ሚታመነው❓ የሚታመን አንድ እግዚአብሔር ብቻ! ሁለት እግዚአብሔር ወይም ሶስት እግዚአብሔር (ሮች) የሉም። እምነት የሚጀምረው ተመላኪውን በቁጥር እና በስም በማውቅ ነው። #ስንት እግዚአብሔር አለ? ስንልን #በቁጥር                   #አንድ እግዚአብሔር አለ ። " እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ አምላካችን እግዚአብሔር አንድ እግዚአብሔር ነው፤" (ኦሪት ዘዳግም 6:4) ይህን ሁሉም የሚያውቀው ነው አጋንንትም ጭምር #አንድ እግዚአብሔር  ብቻ ነው ያለው " እግዚአብሔር አንድ እንደ ሆነ አንተ ታምናለህ፤ መልካም ታደርጋለህ፤ አጋንንት ደግሞ ያምናሉ ይንቀጠቀጡማል።" (የያዕቆብ መልእክት 2:19) እግዚአብሔር አንድ እንደሆነ አንተም ታምናለህ @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH

የማለዳ ትምህርት የጸሎታችን መልስ ለምን ይዘገያል? ክፍል 9 በጊዜ አለመጸለይ በተለምዶ ሰው ጸሎትና ምልጃ የሚያበዛው በችግር ጊዜ ብቻ ነው። ችግር ስያጋጥመው፣ የመውጫ መንገድ ስያጣ ወደ እግዚአብሔር መጮኽ ከብሉይ ክዳን ከእስራኤል ዘመን ጀምሮ የተለመደ ሆኖ እስከ ዛሬ ድረስ ደርሶዋል። ነገር ግን እግዚአብሔር የሚጸልገው ይሄንን ህይወት አይደለም። በጊዜውም አለጊዜውም መጸለይና መጽናትን ነው። ስለዚህ ቅዱስ ሁሉ በምቹ ጊዜ ወደ አንተ ይለምናል፣ ብዙ የጥፋት ውሃም ወደ እርሱ አይቀርብም  [መዝ 32፥6] ተብሎ ስለተጻፈ ጥፋትና ችግር ወደ እርሱ እንዳይቀርብ ጻድቅ መለመን ያለበት ጊዜ ሳለ ነው እንጅ ፈተና ደርሶ፣ ጥፋት ደርሶ፣ ቀን መሽቶ ብቻ ወደ እግዚአብሔር መጮኽ የጸሎት መልስ አያመጣም። ኢየሱስም ስናገር " ቀን ሳለ የላከኝን ሥራ ላደርግ ይገባኛል፤ ማንም ሊሰራ የማይችልበት ሌሊት ትመጣለች" ይላልና። [ዮሐ 9፥4] ወንድሞችና እህተች መጸለይ ካለብን በጊዜ፣ ማምለክ ካለብን በጊዜ፣ ማልቀሳ ካለብን፣ መጮኽ ካለብን፣ እምባ ማፍሰስም ካለብን በጊዜ ነው እንጅ የፈተና ሰአት ደርሶ "ሠርገኛ መጣ፥ በርበሬ ቀንጥሱ" እንደሚባለው ተረት መሆን የለብንም። ኢየሱስ ከዲያብሎስ በተፈተነ ጊዜ በመጀመሪያ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት በጾም ጸሎት ቆይቶ ነው እንጅ ፈተና ደርሶት አይደለም። ፈተናና ችግር እንደሚደርሰን ካመንን ሥራውን ለማፍረስና ለማሸነፍ ቀድመን መዘጋጀት አለብን። ይህ ማለቴ በችግራችን ጊዜ አንጸልይ፣ አይሰማንም ማለቴ አይደለም። ይሰማናል፤ ነገር ግን በኋላ ከሚመጣው ጥፋት ለማምለጥ በእግዚአብሔር ፊት በምቹ ጊዜ መምበርከክ አለብን። "ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ" ብሎዋል እንጅ ፈተና መጥቷልና ጸልዩ አላለም። ወደ ተና እንዳንገባ የሚያደስገን ፀሎት ቀድመን ፀለይነው ፀሎት ነው እንጅ ተፈትነን የሚንልየው ፀሎት አይደለም። እርሱ ጊዜ ሰጥቶን፣ ሰአት ሰጥቶን፣ ቀን አመቻችቶልን ጸልዩ እያለ እየመከረንእምብ ካልን በኋላ ሰሚ በሌለበት ሰአት በር ተዘግቶ የሚንጸልየው ጸሎት መልስ አይገኝም። ጸሎታችን ለምን ዘገየ እያልን ከመማረርና እግዚአብሔርን ከመወቀስ ውጭ ትስፍ አይኖርም። ምሳ 1፥24-31 በጠራሁ ጊዜ እምቢ ስላላችሁ፥ እጄን በዘረጋሁ ጊዜ ማንም ስላላስተዋለ፥ 25 ምክሬን ሁሉ ግን ቸል ስላላችሁ፥ ዘለፋዬንም ስላልፈቀዳችሁ፤ 26 እኔም ስለዚህ በጥፋታችሁ እስቃለሁ፤ ጥፋታችሁም በመጣ ጊዜ አላግጥባችኃለሁ። 27 ድንጋጤ እንደ ጐርፍ በደረሰባችሁ ጊዜ፥ ጥፋታችሁም እንደ ዐውሎ ነፋስ በመጣ ጊዜ፥ ጭንቅና መከራ በወረደባችሁ ጊዜ። 28 የዚያን ጊዜ ይጠሩኛል፥ እኔ ግን አልመልስም፤ ተግተው ይሹኛል፥ ነገር ግን አያገኙኝም። 29 እውቀትን ጠልተዋልና፥ እግዚአብሔርንም መፍራት አልመረጡምና፤ 30 ምክሬን አልፈቀዱምና፥ ዘለፋዬንም ሁሉ ንቀዋልና፤ 31 ስለዚህ የመንገዳቸውን ፍሬ ይበላሉ፥ ከራሳቸው ምክር ይጠግባሉ። እግዚአብሔር የሚሰማበት ሰአት እምብ ብለን የማይሰማትና ፊቱን በሰወረበት ሰአት መጮኽ መፍትሄ አይሆንም። እግዚአብሔር ከደጃችን ሳያልፍ በደጃችን እያለ ወደ ቤታችን ማስገባት ነው እንጅ አንኳክቶ አጥቶ ከደጅ ካለ በኋላ ፈልገንም አናገኘውም። መ/መ/ ዘሰለሞን 5፥2-7 "እኔ ተኝቻለሁ፥ ልቤ ግን ነቅቶአል የውዴ ቃል ነው፥ እርሱም ደጁን ይመታል እኅቴ፥ ወዳጄ፥ ርግቤ፥ መደምደሚያዬ ሆይ፥ በራሴ ጠል፥ በቈንዳላዬም የሌሊት ነጠብጣብ ሞልቶበታልና ክፈችልኝ። 3 ቀሚሴን አወለቅሁ እንዴት እለብሰዋለሁ? እግሬን ታጠብሁ እንዴት አሳድፈዋለሁ? 4 ውዴ እጁን በቀዳዳ ሰደደ፥ አንጀቴም ስለ እርሱ ታወከ። 5 ለውዴ እከፍትለት ዘንድ ተነሣሁ እጆቼ በደጅ መወርወሪያ ላይ ከርቤን አፈሰሱ፥ ጣቶቼ ፈሳሹን ከርቤ አንጠበጠቡ። 6 ለውዴ ከፈትሁለት፥ ውዴ ግን ፈቀቅ ብሎ አልፎ ነበር። ነፍሴ ከቃሉ የተነሣ ደነገጠች ፈለግሁት፥ አላገኘሁትም ጠራሁት፥ አልመለሰልኝም። 7 ከተማይቱን የሚዞሩት ጠባቂዎች አገኙኝ መቱኝ፥ አቈሰሉኝም ቅጥር ጠባቂዎችም የዓይነ ርግብ መሸፈኛዬን ወሰዱት። በጊዜ አለመክፈትና አለመዘጋጀት የሚያመጣው ችግር አያችሁ? ጸሎቴ የት ጠፋ፣ መልሴ ለምን ዘገየ ከማለት ውጭ ምላሽ አናገኝም። ስለዚህ መጸለይ ያለብን ሰአት ቀድመን እንጸልይ፣ መፈለግ ያለብን ሰአትም ቀድመን እንፈልግ እንጅ የእኛ ቅድሜ ሁኔታ ሳናስተካክል ኢየሱስን ጥፋተኛ አናደርግ። ዮሐ/ ራዕየ 3፥20 እነሆ በደጅ ቆሜ አንኳኳለሁ፤ ማንም ድምፄን ቢሰማ ደጁንም ቢከፍትልኝ፥ ወደ እርሱ እገባለሁ ከእርሱም ጋር እራት እበላለሁ እርሱም ከእኔ ጋር ይበላል። ይህ ሰአት የኢያንዳንዱ ደጅ እያንኳኳ ያለበት ሰአት ነውና ክቡር እንግዳዬ ነህና ና ግባ ብለን እንቀበለው። ሀሳቤ ልክ ከሆነ ቀጥል በሉኝ፤ ልክ ካልሆንኩኝ አቁም በሉኝ ተባረኩ! ይቀጥላል........ @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH INBOX @Thaddyapostolic GROUP @MARANTAWOCH

የመገረም ጥግ.mp311.37 MB

# አድስ ነገር ጌታ እግዚአብሔር እሱን በመጠባበቅ ላይ ላሉት  ታይቶ የማይታወቀውን ልዩና ድንቅ የሆነ ነገር ያደርጋል ፦       1 ቆሮንቶስ 2 ፥ 9፤ ነገር ግን፡— ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀው ተብሎ እንድተጻፈ፥ እንዲህ እንናገራለን።   ጌታ እግዚአብሔር  አንድን ነገር ስሰራ በሰው  ልክ ተገምቶ የተጠበቀውን ብቻ ሳይሆን  ብዙ  የተጠበቁ ነገሮች እያሉ ከዛም  እጥፍ ድርብ  የሆነ   ከፍ ያለ ነገር ያደርጋል ፦             ኢሳይያስ 43 ፥ 19፤ እነሆ፥ አዲስ ነገርን አደርጋለህ፤ እርሱም አሁን ይበቅላል፥ እናንተም አታውቁትምን? በምድረ በዳም መንገድን በበረሀም ወንዞችን አደርጋለሁ።20-21፤ ምስጋናዬን እንዲናገሩ ለእኔ የፈጠርሁት ሕዝብ፥ የመረጥሁትን ሕዝቤን አጠጣ ዘንድ በምድረ በዳ ውኃን በበረሀም ወንዞችን ሰጥቻለሁና የምድረ በዳ አራዊት፥ ቀበሮችና ሰጎኖች፥ ያከብሩኛል።        እኛ ያመንነዉ አምላክ በፊትም ስሰራ የኖረ ያ ታማኝ አምላክ  ዛረም በእኛ በልጆቹ ላይ በሀይሉ ከፍ ያለ ነገር   ድንቅና ታምር ይሰራል፦             ኢዮብ 36  ፥ 22፤ እነሆ፥ እግዚአብሔር በኃይሉ ከፍ ያለውን ነገር ያደርጋል፤ እንደ እርሱስ ያለ አስተማሪ ማን ነው? በማደሪያው ሆኖ ቃል     የገባ  አምላክ       ራእይ 21 ፥ 5፤ በዙፋንም የተቀመጠው፡—   እነሆ፥ ሁሉን አዲስ አደርጋለሁ፡ አለ። በምመጡት ቀናቶች በምመጣዉ    አመት  ሁሉን ቻይ የሆነ አምላክ በአድሱ አመት  " አድስ ነገር    ያድርግልን"   ይደረግልን ይሁንልን!!!!

ግጥም እልፍ አርገኝ የልምምድ ኑሮ እዛው ተቀምጦ ከፍታ የሌለው ወደታች ሠምጦ ሁሌ ባለሁበት አዲስ ነገር ሳላይ አንድ አይነት ነገር ሳሎጣ ወደ ላይ በጣም ሰልችቶኛል የለመድኩት ልማድ ከፍታ ሳሎጣ  ሁልጊዜ መራመድ እጄን ዘርግቻለው አንተ እንድትረዳኝ በራሴ ጥሪያለው መውጣት ግን አቃተኝ እባክህ ተመልከተኝ አንዴ ብቻ እየኝ ድካሜ በርትቶ ሀይልን እኮ አሳጣኝ ፊትህን ጋረደኝ ድምፅህ ራቀብኝ ተስፋዎቼ ሁሉ በቃ ጨለሙብኝ ይቅርብኝ ያ ልማድ ድግግሞሽ ይብቃ አልፌ  ልሻገር አሁን  ቶሎ  ልንቃ ወዳለመድኩት ወደ አዲስ ነገር ተሻግሬ ልየው ሁሌ ያንተን ክብር ድንበሩ ላይ ቆሜ ለምንስ ልመልከት ተሻግሬ ልሂድ  በሀይል  በጉልበት እልፍ እልፍ እልፍ አርገኝ መራመድ ይብቃና ወደ ላይ አሶጣኝ ከፍ ከፍ ከፍም አርገኝ ዝቅታ ይብቃና ክብርህን አሳየኝ የዛለው ጉልበቴ በድጋሜ ይታደስ ወደታች የሳበኝ  አሁኑኑ ይበጠስ ተራራውን መዞር ምን ጥቅም ይሰጣል እዛው ባለሁበት በጣም ይሰለቻል ሀይልህ ይምጣና ያውጣኝ ወደላይ ጉልበትን እሻለው ፊትህን እስከማይ መንሳፈፍ ናፈኩኝ በፀጋህ ዙፋን እጅግ የሚያስፈልግ በአሁኑ ዘመን ይፍሰስ በእኔ ላይ ይሄ ቅዱስ መንፈስ እላይ የሚያወጣ ካሰብኩት የሚያደርስ አንድ እርምጃ ብቻ አሁን ካለሁበት እንዳይደጋገም የትላንት ማንነት አሮጌውም ይሻር በአዲስ ይለወጥ ማያስፈልግ ነገር ከህይወቴ ይቆረጥ አብዝቼ ልፈልግህ ወደ አንተ ልሩጥ ተራራው ቢጋረጥ ከቶ እንዳልደነግጥ      ከሰፈር ልውጣና ልለይ ላንተ ክብር ከትላንት ማንነት ዛሬ እንድሻገር ድግግሞሽ በቅቶ የድሮ ልማዴ ከዛ እልፍ ልበል ካለሁበት አንዴ አዲስ ነገር ማየት ነውና መሻቴ አንተን መርጠንሀል እኔ እና ቤቴ እናም እልፍ አርገኝ አሁን ካለሁበት ያየሁትን ነገር ወደ ማልደግምበት አንዴ  ብቻ እልፍ አርገኝ አንድ እርምጃ ፈቀቅ አርገኝ S/r eyael

እልፍ አርገኝ
የልማድ ጉዞ ሁሌ ሲደጋገም ለሊቱ ሲነጋ መልሶ ሲጨልም ወይ ላላልፍ ላልሻገር ቀን ፈጀው ቆሜ ከድንበር ትላንትና ዛሬን ተክቶት ሲያልፍ ዛሬ ነገን ሊደርስ በፍጥነት ሲቀዝፍ ወይ ላላልፍ ላልሻገር ቀን ፈጀው ቆሜ ከድንበር የተጋረጠውን ተራራ እየዞርኩ ያኔ በማልኩበት ስፍራ ዛሬም ስገኝ ወይ ላላልፍ ላልሻገር ቀን ፈጀው ቆሜ ከድንበር ሁሌ አንድ አይነት ህይወት መኖር ሰልችቶኛል ቆርጦ ለመውጣት ጥሮ መውደቅ ስልችቶኛል ባለሁበት መራመድ የትም ላልሄድ ኧረ ምንድነው አንተን ይዞ መንገዳገድ እልፍ አርገኝ እልፍ አርገኝ ካለሁበት እልፍ አርገኝ እልፍ አርገኝ ከቆምኩበት እልፍ አርገኝ እልፍ አርገኝ ጥሼ ልሻገር እልፍ አርገኝ እልፍ አርገኝ ከስጋ ነገር እልፍ አርገኝ የከበደኝን ሚያውከኝን ባንተ ላይ ጥዬ ልሂድ ልሻገር ልለፍ እንጂ ተደላድዬ የስምህን በትር በእጄ ይዤ ለምን ቆማለሁ ዮርዳኖስንም ከፍዬበት እሻገራለሁ እልፍ አርገኝ*2 ካለሁበት እኔን አውጣኝ ዘይቴ ፈሶ ተመርጬ ተቀብቻለሁ ታድያ መንደር ውስጥ ከአለም ጋር ምን እስራለሁ ካልተለየሁኝ ስትለየኝ ስትጠራኝ ስጋ መሻቱን ጥፍር አርጎ እንዳይገዛኝ እልፍ አርገኝ አንድ እርምጃ ካለሁበት አንድ እርምጃ ከቆምኩበት አንጅ እርምጃ እልፍ አርገኝ አንዴ ብቻ ፈቀቅ

Tem(2).mp312.46 MB

"ታሪክህ እንዲቀየር ኢየሱስን ወደ ህይወትህ ጋብዝ" ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።                           -ማቴዎስ 6:33 በአንድ ሀገር አንድ ንጉሥ በየአመቱ እጣ የማውጣት ባህል ነበረው። እንግዲህ ዕጣው ለወጣለት ሰው ንጉሡ ዜጋው የፈለገውን/የጠየቀውን ነገር ያደርጋል። አንዴም ቃል ስለገባ፤  ከዚህ በፊትም እንዲህ አይነት ልምምድ ስላለ ዕጣው ለወጣለት ሰው ያሻውን ያደርግለታል። የሆነ አመት ላይ ዕጣው ለሆኑ በዕድሜ ለገፉ እናት ይወጣላቸዋል። ከዛ በኃላ ንጉሡ የደህንነት አባላቶቹን ዕጣው መድረሱን እንዲያሳውቋትና ጥያቄዋን ለመቀበል ወደ ሴትዮዋ መንደር ይልኳቸዋል። እነዚህ የደህንነት አባላቶቹ ልክ ሰፈሯ ሲደርሱ መንገዱ አስቸጋሪ የሆነ፣ አከባቢው ላይ ያሉ ቤቶች የደካከሙ እና ሊወድቁ ቀናቶች ብቻ የቀሩት፣ ሴትዮዋም ቤት ሲገቡ ቤቷ እርጅት ያለና ቤቷ ውስጥም ምንም የሚበላ እንኳን የሌለ እንደሆነ ተረዱ። የንጉሡ የደህንነት አባላቶቹ ልክ እንደደረሱ "እንኳን ደስ ያሎዎት እማማ፡ የዘንድሮ ዕጣ ለእርሶዎ ነው የወጣሎት፡ ስለዚህ ከዚህ ደቂቃ ጀምሮ የፈለጉትን ነገር ንጉሡን የመጠየቅ መብት አለዎት።" እሳቸውም ቀጥለው " እንግዲህ እግዚአብሔር ፈቅዶ ዕጣው ለኔ ከወደቀ፡ አንድ ጥያቄ ነው ያለኝ። እሱም ንጉሥ ቤቴ መጥቶ እራት እንዲበላ ነው ምፈልገው።" አሉ! የደህንነት አባላቶቹ ያልጠበቁት አይነት ጥያቄ ስለነበር እጅግ ደነገጡ። "እንደዛማ ሊሆን አይችልም እማማ። እስቲ ከሰፈሮት ብንጀምር እንኳን ንጉሡ ልምጣ ቢል መንገዱ አመቺ አይደለም፡ እጅግ አስቸጋሪ ነው። ቤቶቹ ደግሞ የወዳደቁ እና የደካከሙ ናቸው። እስቲ ዞር ብለው ቤቶትን ይዩ ሊወድቅ ቀናቶች የቀረው ነው በዛ ላይ በስነስርዓት የሚበሉት ምግብ የሚጠጡት ነገር የሎትም። በዚህ ሁኔታ እንዴት ነው የአንድ ሀገር ንጉሥ መጥቶ እራት የሚበላው? ይኼ የማይሆን ነገር ነው እማማ!" ሲሏቸው፡ ወይ ፍንክች " እንግዲህ ሀሳቤን አልቀይርም። የኔ ፍላጎት ንጉሥ መጥቶ አብሮኝ እራት እንዲበላ ነው። ሌላ ጥያቄ የለኝም።" አሏቸው። የደህንት አባላቶቹ ግራ ቢገባቸው ጥያቄውን ወደ ንጉሥ ዘንድ ወሰዱ። ንጉሡም ዕጣ የደረሰው ዜጋው የሚጠይቀውን ለማድረግ ከዚህ በፊት ቃል ስለገባ እንዲሁም የማድረግ ልምምዱም ስላለው እምቢ ማለት ቢቸግረው ጃንደረቦቹን ሰበሰበ። ንጉሡ ከ3 ሳምንታት አስቀድሞ ጃንደረቦቹ ወደ ሴትዮዋ መንደር ሄደው ያለውን ነገር እንዲያዩ ላካቸው። ልክ ሰፈሯ ሲደርሱ መንገዱ የተበላሸ፡ መኪና የማያስገባ ስለነበር አስፓልት ይሰራ ተባለ፡ ተሰራ። አከባቢው ላይ የነበሩ ቤቶች የደካከሙ እና ሊወድቁ አንድ ሐሙስ የቀራቸው ስለነበሩ ሁሉም ፈርሶ እንደገና የሚያምር ቤት ይሰራ ተባለ፡ ተሰራ። ቤቷ ሲደርሱ ቤቷም ያረጀ እና ሊወድቅ  ቀናቶች የቀሩት ስለነበረ ፈርሶ ንጉሡን በሚመጥን ልክ ይሰራ ተባለ፡ ተሰራ። እንዲሁም ቤቷ ምንም የሚበላ ነገር ስላልነበረ ንጉሥን በሚመጥን መልኩ ምግብ በየአይነቱ ይሰራ ተባለ፡ ተሰራ። እንግዲህ በዚህ ሁሉ ታሪክ እንድታዩ የፈለኩት በእውነቱ የተሰራውን ነገር አይደለም። ሰው ከምንም ነገር አስቀድሞ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ወደህይወቱ ከጋበዘ በረከት የሚከተል ነገር እንደሆነ እንድትረዱልኝ ነው። እንግዲህ አንድ የሀገር ንገሥ የፈለጉትን ነገር ሊያደርግላቸው ፈቃዱ ሆኖ ሳለ የሳቸው ምላሽ ንጉሡ ወደቤቷ መጥቶ ከእሷ ጋር እራት እንዲበላ መጋበዝ ነበር። ጌታን ወደህይወታችን ስንጋብዝ እኛ ከምናስበው እና ከምንረዳው በላይ ሊያደርግልን ይፈልጋል። የጥያቄ ሁሉ መልስ ኢየሱስ ነው። ታሪክህ/ሽ እንዲቀየር ወደ ህይወትህ/ሽ ኢየሱስን ጋብዝ/ዢው። ልክ ሴትዮዋ ንጉሡን ቤቷ እንዲመጣ ስትጋብዝ ከራሷ አልፋ ለሰፈሯ በረከት እንደሆነችው እኛ ኢየሱስን ወደህይወታችን ስንጋብዝ የኛ ታሪክ ብቻ አይደለም የሚገለበጠው። ለሰዎች የምንተርፍ እንሆናለን። ብቻ ኢየሱስን ወደ እያንዳንዱ ነገራችን እንጋብዘው። አለም ልክ እንደ የደህንነት አባላቶቹ ያልተሳኩ ነገሮቻችንን፡ የወደቅንባቸውን ጊዜያቶች እያመጣ በህሊና ወቀሳ እያሰቃየን፡ አዕምሮአችንን በከንቱ ሀሳብ እየሞላ፡ ማጣታችንን ተጠቅሞ፡ መድከማችንን አይቶ ተስፋ ሊያስቆርጠን ቢሞክርም ንጉሣችንን ኢየሱስን ብቻ ነው ምፈልገው ሌላ ጥያቄ የለኝም ብለን ፀንተን ከቆምን በረከት ይከተለናል።​

የማለዳ ትምህርት የጸሎታችን መልስ ለምን ይዘገያል ? ክፍል 8 ራሱን ከፍ አድርጎ በማየት ጸሎት ማለት ሰውና እግዚአብሔር የሚገናኝበት የስልክ መስመር በመሆኑ መጠን የሚጸልየው ጸሎት በጥንቃቄ መሆን አለበት። ምክንያቱም በስልክ መስመራችን የሚናወራው ወሬአችን ሁሉ በቴሌ እንደሚመዘገብ የጸለይነው ጸሎታችንም እያንዳንዱ ቃላቶች በእግዚአብሔር ፊት የሚመዘገብ ነው። እየቀለድን የሚናወራቸው ቃላቶች እንኳን በአየር ላይ ተቀምጦ በፍርድ ቀን ተሰብስቦ እንደሚመጡብን በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ ስለተጻፈ ሁሉንም ቃላቶቻችን ጥንቃቄ እያደረግን ብናወራ ይሻለናል። ወደ ዋና አላማዬ ስመለስ ስንጸልይ እራሳችንን ማመጻደቅ ሌላውን ግን መኮነን አያስፈልገንም። የሀጥአት ምዛንና የጽድቅ ምዛን ያለው እግዚአብሔር ጋር ነው። ስንጸልይ እራሳችንን አዋርደን በእምባ፣ በለቅሶ እንጅ እኔ ጻድቅ ስለሆንኩኝ ማለት አያስፈልግም። የበታችነት ስሜት ይሰማን፤ ከሐጥአተኞች ዋና ሐጥአተኛ እኔ ነኝ እያልን መጸለይ አለብን። መቼስ የሚለምን እጅ የበታች ነው ይባላልና በታችነት ተሰምቶን መጸለይ አለብን። እኛ ወደ እግዚአብሔር ስንጸልይ እግዚአብሔር ግን ከላያችን ያለው ማንነት ሳይሆን ልባችንን ይመረምራል። መርምሮ ካዬ በኋላ  የተዋረደውን ከፍ ያደርጋል፤ ከፍ ያለውን ዝቅ ያደርጋል። ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። መጠምጠሚያውን አውልቅ፥ ዘውዱንም አርቅ፤ ይህ እንዲህ አይሆንም፤ የተዋረደውን ከፍ አድርግ፥ ከፍ ያለውንም አዋርድ። [ት/ሕዝ 21፥26] ፤ ለዘላለም የሚኖር ስሙም ቅዱስ የሆነ፥ ከፍ ያለው ልዑል እንዲህ ይላል። የተዋረዱትን ሰዎች መንፈስ ሕያው አደርግ ዘንድ፥ የተቀጠቀጠውንም ልብ ሕያው አደርግ ዘንድ፥ የተቀጠቀጠና የተዋረደ መንፈስ ካለው ጋር በከፍታና በተቀደሰ ስፍራ እቀመጣለሁ። [ ት/ ኢሳ 57፥15] የእግዚአብሔር መሥዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው፥ የተሰበርውንና የተዋረደውን ልብ እግዚአብሔር አይንቅም። [መዝ 51፥17] እንግዲህ በጊዜው ከፍ እንዲያደርጋችሁ ከኃይለኛው ከእግዚአብሔር እጅ በታች ራሳችሁን አዋርዱ፤ እርሱ ስለ እናንተ ያስባልና የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት። [1ጴጥ 5፥6-7] ችግራችን።፣ ቀምበራችንን፣ ሸክማችንን ሁሉ የሚንጥለው በትዕብት ተሞልተን፣ ከፍ ከፍ ብለን ሳይሆን በፊቱ ተዋርደን ብቻ ነው። እኛ ከእርሱ በታች ሆነን መዋረድ ስንጀምር እርሱ ከፍ ከፍ ማድረግን ይጀምራል። እርሱ ጸሎታችን ሰምቶ ከፍ ባደረገን ቁጥር እኛ ጨምረን ዝቅ ዝቅ ማለትን መለማመድ አለብን። ኢየሱሰ ለምሳሌ የተጠቀመውን የሁለት ሰዎች ጸሎት እንመልከት፦ የፈረሳዊው ጸሎት፦ ፈሪሳዊም ቆሞ በልቡ ይህን ሲጸልይ። እግዚአብሔር ሆይ፥ እንደ ሌላ ሰው ሁሉ፥ ቀማኞችና ዓመፀኞች አመንዝሮችም፥ ወይም እንደዚህ ቀራጭ ስላልሆንሁ አመሰግንሃለሁ፤ በየሳምንቱ ሁለት ጊዜ እጦማለሁ፥ ከማገኘውም ሁሉ አሥራት አወጣለሁ አለ። የቀራጩ ጸሎት፦ ቀራጩ ግን በሩቅ ቆሞ ዓይኖቹን ወደ ሰማይ ሊያነሣ እንኳ አልወደደም፥ ነገር ግን። አምላክ ሆይ፥ እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ እያለ ደረቱን ይደቃ ነበር። የኢየሱስ ፍርድ፦ እላችኋለሁ፥ ከዚያ ይልቅ ይህ ጻድቅ ሆኖ ወደ ቤቱ ተመለሰ፤ ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳልና፥ ራሱን ግን የሚያዋርድ ከፍ ይላል። አንዱ የራሱን ማንነት እያሳየ ከፍ ከፍ ስል ሌላኛው ግን ከሐጥአቴ ውጭ የሚነግርህ ጽድቅ የለኝም ብሎ ገና ከሩቅ ቆሞ ደረቱን እየደቃ ለመነ። በመጨረሻም ሐጥአተኛ ነው ተብሎ የተፈረጀ ቀራጭ ሐጥአቱን አራግፎ በሠላም ወደ ቤቱ ስመለስ ራሱን ከፍ አድርጎ ጽድቁን ያሳየ ሰውዬ ሐጥአቱን ተሸክሞ ወደ ቤቱ ተመልሰዋል። ዛሬም በእግዚአብሔር ፊት ብልጥ ብልጥ መሆን የሚሰማን ሰዎች አንድ ጊዜ እናስተውልና በፊቱ እንዋረድ፣ ዋና ሐጥአተኛ እኔ ነኝ እንበል። ተዋርደን ጸልየን ከፍ ብለን እንመለስ። አለበለዚያ  በልባችን ትዕቢት እግዚአብሔርን እየወቀስን እንኖራለን። ይቀጥላል....... @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH Comment INBOX  @Thaddyapostolic GROUP @Marantawoch