ማራናታ.....MARANATHA
ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደምመስላቸው ጌታ ሰለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንድደርሱ እንጅ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ሰለ እናንተ ይታገሳል።2ኛ ጴጥ 3፥9 ገና በጣም ጥቅት ጊዜ ነው፤ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም። ዕብራ 10፥37 የመወያያ ግሩፕ👇 @Marantawoch Inbox Comment @Thaddyapostolic
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel ማራናታ.....MARANATHA
Channel ማራናታ.....MARANATHA (@maranathawoch) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 17 446 subscribers, ranking 4 695 in the Religion & Spirituality category and 1 983 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 17 446 subscribers.
According to the latest data from 05 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 389 over the last 30 days and by 26 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 19.10%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.15% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 3 328 views. Within the first day, a publication typically gains 1 420 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 22.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደምመስላቸው ጌታ ሰለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንድደርሱ እንጅ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ሰለ እናንተ ይታገሳል።2ኛ ጴጥ 3፥9 ገና በጣም ጥቅት ጊዜ ነው፤ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም። ዕብራ 10፥37
የመወያያ ግሩፕ👇
@Marantawoch
Inbox Comment @Thaddyapostolic”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 06 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 06 September | +23 | |||
| 05 September | +26 | |||
| 04 September | +28 | |||
| 03 September | +22 | |||
| 02 September | +18 | |||
| 01 September | +20 |
| 2 | የልብ አይን መከፈት
የልብ አይን መከፈት ስንል ምን ማለታችን ነው?
የልብ አይን መከፈት ማለት ከእግዚአብሔር ጋር መገናኘት ማለትም እንደእግዚአብሔር ሀሳብ መሆን ማለት ነው (በልሳን እናወራለን ፣ሀጢያት የሚባሉትን አንነካም(ማስተዋል ስለምንችል ና ባጠቃላይ እግዚአብሔርን እንፈራለን ።
፦አብዛኛውን ጊዜ የልብ አይናችን ስላልተከፈተልን ከእግዛብሄር ሀሳብ እና ፈቃድ ጋር እንጋጫለን ለምሳሌ እኛ ሰዎች ፈተና ሲበዛብን በፈተናው መሀል መውጫ እንደሚዘጋጅልን ረስተን ቶሎ ተስፋ እንቆርጣለን ግን ይሄ ትክክል አይደለም።
በመፅሀፍ ቅዱስ እነኖህን እነአብርሀምን እነዮሴፍን ስናይ በብዙ መከራ ውስጥ በትእግስት የእግዚአብሔር ፈቃድ በሂወታቸው እንዲፈፀም አድርገዋል ይህም የሆነው የልብ አይናቸው ስለበራ እና የእግዚአብሔርን ፈቃድ መመልከት ስለቻሉ ነው።
ስለዚህ ልክ እንደአባቶቻችን ሁሉ የኛም የልብ አይን ተከፍቶ የእግዚአብሔርን ፈቃድና ሀሳብ እያየን በቤቱ እንድንመላለስ እንፀልይ 🙏🙏
እግዚአብሄር የልብ አይኖቻችንን ከፍቶ በማስተዋል እንድንከተል ያድርገን።
አሜን 🙏
@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH | 583 |
| 3 | የማለዳ ትምህርት
የጸሎታችን መልስ ለምን ይዘገያል?
ክፍል 14 በበቀል ስሜት መጸለይ
ይህ ጸሎት በእግዚአብሔር ፊት አስጸያፊ ነው። ምክንያቱም በቀል የእግዚአብሔር ነው እንጂ የሰው አይደለም።
ዕብራ 10፥30 በቀል የእኔ ነው፥ እኔ ብድራትን እመልሳለሁ ያለውን እናውቃለንና፤ ደግሞም። ጌታ በሕዝቡ ይፈርዳል።
ፈራጁና በቀልን የሚመልስ እግዚአብሔር መሆኑን ረስቶ ብዙ ሰው በራሱ ለመበቀል ወደ እግዚአብሔር ይጸልያል። እግዚአብሔር ግን መልስ የሚመልሰው በወንድሙና በእህቱ ላይ ለመበቀል ሳይሆን በቅን ልብ በፉቱ እንድኖር ነው።
አንዳንድ ሰው ከሰው ጋር ከተጣላ እሱን ለመበቀል ወደ ጸሎት ይገባል። ይህ ጸሎት ግን በእግዚአብሔር ፊት አስጸያፊ ነው፤ አይሰማም።
ጸሎት ማለት ለእኔ ብቻ እያልን የሚንጸልየው ሳይሆን ለሚጠሉንም ጭምር እግዚአብሔር እውነተኛ ልብ እንድሰጣቸው መጸለይ ነው። አለበለዚያ ከትዕዛዙ ስለወጣን አስጸያፊ ጸሎት ሆኖ እራሳችንንም መልሶ የሚጎዳ ይሆናል።
ምሳሌ 28፥9 "ሕግን ከመስማት ጆሮውን የሚመልስ ጸሎቱ አስጸያፊ ናት።"
ከመጸለያችን በፊት የእግዚአብሔር ሕግ ምን ይላል የሚለውን ማወቅ አለብን። ለቃሉና ለሕጉ የማይታዘዝ ሰው ስጸልይ ጸሎቱ አስጸያፊ ስለሚሆን።
ሕጉ ምን ይላል?
ማቴ 5፥43-48 "ባልንጀራህን ውደድ ጠላትህንም ጥላ እንደ ተባለ ሰምታችኋል።
እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፥ ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤ እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና።
የሚወዱአችሁን ብትወዱ ምን ዋጋ አላችሁ? ቀራጮችስ ያንኑ ያደርጉ የለምን? ወንድሞቻችሁንም ብቻ እጅ ብትነሡ ምን ብልጫ ታደርጋላችሁ? አሕዛብስ ያንኑ ያደርጉ የለምን? እንግዲህ የሰማዩ አባታችሁ ፍጹም እንደ ሆነ እናንተ ፍጹማን ሁኑ።
ይህ የአምላካችን ሕግ ነው። ይህንን ሕግ ጥሰን የሚጠሉንን ለመበቀል በስሜት ተነሳስተን ጸሎታችንን መልስ የሚንል ሰዎች ከሆንን ጸሎታችን በቁጣ ይመለሳል እንጂ በመልካም አይመለስም። ጸሎት በፍጹምና በቅን ልብ ብቻ ነው።
አንዳንድ ሰዎች እንደው ከሰው ጋር ስጣሉ ለባለጋራው እንድሞት ግደለው እያሉ የሚጸልዩም አሉ። አንዳንድ ሰው ያ ጸሎትም በቤተክርስቲያን አምጥቶ የልቤን መሻት እግዚአብሔር ያውቃልና እግዚአብሔር እንድፈጽምልኝ ጸልዩልኝ የሚልም አለ። ያላወቀ ሰው ግን "እንደ ልብህ ይስጥህ" እያለ ይጸልያል። ልቡ ቅን ካልሆነ ለዘላሀም ጠማማ ሆኖ እንድኖርለት ነው ማለት ነው።
በነገራችን ላይ በዚህ ምድር ላይ ከዲያብሎስ ውጭ የሰው ባለጋራ የለንም።
ኤፈ 6፥12 መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ። ይህንን ያላወቀ ሰው ሰውን እንደ ጠላት ቆጥሮ ይዋጋል። በዚህ ሁኔታ ሰውን ለማሸነፍ ለበቀል ተነሳስታችሁ የሚትጸልዩ ሰውች የጸሎታችሁን መልስ አትጠብቁ።
ይሄ ልባችንን ካላስተካከልን የሚንጸልየው ጸሎት መልሶ ዋጋ ያስከፍለናል እንጅ ዋጋ አይከፍለልንም። ብዙ ሰው ለጸሎተ መልስ አጣሁ፣ እምብ አለኝ የሚለው የጎኑን ሰው አይቶ ስለሚጸልይ ብቻ ነው። የጎኑ ሰው ወይንም ጓደኛው ጥሩ ቤት ካገኘ፣ መኪና ካገኘ፣ ጥሩ ነገር ተሳክቶለት መንቀሳቀስ ስጀምር እሱን አይቶ ለእኔም ስጠኝ፣ አድርግልኝ ብሎ ስለሚጸልይ የምኞት ጸሎትም ስለሆነ ጥያቄው ሄዶ በዛው ይቀራል፤ ለአንዳንዱ ደግሞ ይባስ ብሎ በመቅሰፍት ይመለሳል።
እኛ ግን ቅኖች ከሆንን እግዚአብሔር በራሱ ጊዜ በባለጋራችን የሚበቀል መሆኑን ረስተን እኛ እንሞክራለን። እኛ በራሳችን መሞከር ግን መተላለፍ ነው።
1ተሰሎ 4፥6 አስቀድመን ደግሞ እንዳልናችሁና እንደ መሰከርንላችሁ፥ ጌታ ስለዚህ ነገር ሁሉ የሚበቀል ነውና ማንም በዚህ ነገር አይተላለፍ ወንድሙንም አያታልል።
ስትጸልዩስለ እገለ ብላችሁ የሚትጸልዩት ጸሎት መልስ ያመጣል ብላችሁ አትጠብቁ። ጠላትህ ብሆን እንኳ ለእሱ መልካሙን ተመኝለት፤ ጸልይለት። ይህንን ስታደርግ ለእሱ ማፈርያ ይሆናል ለአንተ ግን ጽድቅ ይሆንልሃል። ይህ ግን ከልብህ የተነሳ መሆን አለበት እንጅ ለቃሉ ለመታዘዝ ብለህ ብቻ ያልተዋጠልህ ምህረት አትጠይቅ።
ሮሜ 12፥17-21 ለማንም ስለ ክፉ ፈንታ ክፉን አትመልሱ፤ በሰው ሁሉ ፊት መልካም የሆነውን አስቡ። ቢቻላችሁስ በእናንተ በኩል ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ።
ተወዳጆች ሆይ፥ ራሳችሁ አትበቀሉ፥ ለቍጣው ፈንታ ስጡ እንጂ፤ በቀል የእኔ ነው፥ እኔ ብድራቱን እመልሳለሁ ይላል ጌታ ተብሎ ተጽፎአልና።
ጠላትህ ግን ቢራብ አብላው፤ ቢጠማ አጠጣው፤ ይህን በማድረግህ በራሱ ላይ የእሳት ፍም ትከምራለህና። ክፉውን በመልካም አሸንፍ እንጂ በክፉ አትሸነፍ።
በአጠቃላይ እኔ በበኩሌ ይህ ስለ ጸሎት የተጀመረ ትምህርት ለሚያነብና አምብቦም ተግባራዊ ለሚያደርግ ሰው በህይወቱ ውስጥ ለውጥ ያመጣል ብዬ አምናለሁ። አውቃለሁ እኔ በራሴ ይህንን ትምህርት ለማቅረብ የሚገባኝ ሰው አይደለሁም። ነገር ግን አንዱን ጽፌ አቆማለሁ ብዬ ስያስብ በየቀኑ ሌላ ትምህርት፣ ሌላ የቃሉ ሙላት እየሰጠኝ ስላስቸገረኝ ነው ለመጻፍ እየሞከርኩ ያለሁትና በቅንነት አምብቡ አትሰለቹ። ማንበብ ብቻ ሳይሆን በህይወታችሁ ውስጥ ተግበራዊ ለማድረግ ሞክሩ ለውጡን ታያላችሁና።
ለጸሎታችሁ መልስ እንድመጣላችሁ ከፈለጋችሁ በፍጹም ልብ ቅረቡ። እግዚአብሔር ለአብርሃም እኔ ኤልሻዳይ ነኝና አንተ ግን በፊቴ ተመላለስ፥ ፍጹምም ሁንብሎዋልና። ፍጹም ለሆነ ልብ ነው እግዚአብሔር የሚሰራው እንጅ በተንኮል ለሚጸልይ ሰው አይመልስም።
ዘፈጥ 17፥1 አብራምም የዘጠና ዘጠኝ ዓመት ሰው በሆነ ጊዜ እግዚአብሔር ለአብራም ተገለጠለትና። እኔ ኤልሻዳይ ነኝ፤ በፊቴ ተመላለስ፥ ፍጹምም ሁን፤ ቃል ኪዳኔንም በእኔና በአንተ መካከል አደርጋለሁ፥ እጅግም አበዛሃለሁ አለው።
እግዚአብሔር ፍጹማን ያድርገን!!
ከተመቻችሁ ይቀጥላል......
@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH
INBOX @Thaddyapostolic
GROUP @Marantawoch | 953 |
| 4 | Matamoha cubbo'ya taare sample .mp3 | 1 455 |
| 5 | ሰላም ይብዛችሁ የኢየሱስ ልጆች
✍ማንም ሰው በአንቴ/በአንች ምክንያት በእግዘአብሔር ፊት ተንበርክኮ እንዳይለቅስ ተጠንቀቅ::
የፍቅር መገለጫ ቅርበት ሲሆን ወንድማችን እና እህታችን መውደድ ግን የመዳናችን ትልቁ ምስጥር ነው:: | 1 674 |
| 6 | የማለዳ ትምሀርት
የጸሎታችን መልስ ለምን ይዘገያል ?
ክፍል 13 መቅደም ያለበት ነገር አለማስቀደም
የብዙ ሰው ጸሎት የሚያተኩረው በግል ጥቅሙ ላይ ነው እንጂ ለእግዚአብሔር በሚጠቅም ላይ አይደለም። ከዛም አልፎ በዚህ አለም ላይ የራሱን ስም ከፍ ከፍ ለሚያደርጉ ነገሮች ላይ አትኩሮ ይጸልያል። ነገር ግን በዚህ አካሄድ ሰውና እግዚአብሔር አይገናኙም። እግዚአብሔር አስቀድሙ ያለው ለጽድቅና የእግዚአብሔርን መንግስት ነው እንጂ በዚህ ምድር ላይ የሚቀር ጥቃቅን ነገሮችን አይደለም። ይህ እናንተ ተጨነቅን ተብላችሁ የሚትለምኑት ነገር ዋናውን ከፈለጋችሁ የሚጨመርላችሁ ነገር ነው ይላል።
የቀደመውን አስቀድመን እንድንኖር ኢየሱስ ይርዳን።
በእግዚአብሔር ዘንድ ጸሎት ነው ተብሎ ሚዛኑን የሚያነሳ ጸሎት ማለት አስቀድመን ለመንግስቱ ስንጸልይ ነው። እኛ ግን ብዙ ጊዜ የግላችን ጥቅም ለማስከበር፣ በዚህ ምድር ላይ ከእገለ በለጥን ለማለት፣ እገለ ሳልደርስ ሊሞት ነው በማለት ለምድራዊ ነገር ብቻ ያተኮረ ጸሎት እየጸለይን እንቆያለን።
የእግዚአብሔር አላማ በእኛ ላይ ያለው ግን እሱ አይደለም።ይህ እኛ የማንፈልገው ጭራ ነው። ቀንዱን ትተን ጭራን አንለምን! ቀንዱ ጽድቅና የእግዚአብሔር መንግስት ስሆን ጭራ ምድራዊ የሆነ የእኛ ፍላጎት ነው። ስለዚህ ነው እግዚአብሔርን መለመን ያለብንን ነገር ለይተን አውቀን እስክንጸልይ ዝም የሚለን።
በእርግጥ በዚህ ምድር ላይ የጸሎቱን መልስ የማይፈልግ ሰው የለም። ይሁን እንጂ ወደ ጸሎት ሰምው ጋር የመቀራረብ ሁኔታ ብቻ ነው ጸሎትን የሚያቆየው እንጂ። ስለዚህ በዚህ ርዕሰ ጀምረን እየተማርን ያለነው ትምህርቶች ተግባራዊ እያደረገ ለሚጸልይ ሰው መልሱ ቶሎ ይመለሳል ብየ በእርግጠኝነት አምናለሁ።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እግዚአብሔር በሚገርም ሁኔታ ያስቀመጠው፥ ሰው ግን ያልተረዳው የጸሎት መልስ መንገዶች አሉ።
1, የሚንበላውንና የሚንጠጣውን ነገር ከፈለግን አስቀድመን ጽድቅንና የእግዚአብሔርን መንግስት መፈለግ/መጸለይ/ ማቴ 6፥25-33, ሮሜ 14፥17
2, ለህመማችን ፈውስ ከፈለግን አስቀድመን ምህረቱን መጠየቅ። ማር 2፥1, ሉቃ 5፥18, ማቴ 9፥1, ሮሜ 9፥16
3, ሀብታም መሆን ከፈለግን አስቀድመን ጌታን መከተል። ማቴ 19፥27, ማር 10፥28
4, ከእግዚአብሔር አትርፈን መቀበል ከፈለግን ቀድመን ያለንን ለእርሱ መስጠት። ሉቃ 6፥38, ምል 3፥8, 2ቆሮ 9፥6-10
5, በምድር ላይ አርፈን በእረፍት መቀመጥ ከፈለግን ቀምበሩን ተሸክመን እርሱን መከተል። ማቴ 11፥28
እነዚህ ናቸው ማስቀደም ያለብን እንጂ ፍላጎታችን አይደለም። የእኛ ችግር ግን የኋለኛውን ፊት ለፊት ማምጣት ነው። በዚህ ሁኔታ ካልጸለይን መልሳችን አይመጣምና እንጠነቀቅ። ብመለስም እንኳ ለነፍሳችን እረፍት የሚሰጥ አይሆንም። እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩትን ካላደረግን ስጠኝ ማለት እንጅ ምዛኑን አያነሳም።
ከላይ የተዘረዘሩት ነጥቦች ማቢራርያ ካስፈለገ በተለግራማችን ቻናል ውስጥ በሰፊው አለና "የቀደመውን አስቀድም" ብላችሁ search አድርጉ፤ እዚህ ለማብራራት ጊዜ ይፈጃልና።
ሌላው ደግሞ ከልመናችን በፊት ማስቀደም ያለብን ነገር እርሱ እንደሚፈልገን ሆነን መቅረብ። ለዚህ ሀሳብ መነሻ የሚሆንልን የንግስቲቱ የአስቴር ታርክ ስናነብ፦ አስቴር ስለ ዘሩዋ አይሁድና ስለ መርዶክዮስ ሊትለምን ወደ ባሏ ወደ ንጉሡ አርጤክስስ በገባች ጊዜ ሀሳቧን ከመንገሯ በፊት "ለንጉሡ መልካም ሆኖ ብታይ ንጉሡ ወዳዘጋጀሁለት ግብዣ ከሐማ ጋር ዛሬ ይምጣ" አለች።
አስቴር 5፥3-5 ንጉሡም። ንግሥት አስቴር ሆይ፥ የምትለምኚኝ ምንድር ነው? የምትሺውስ ምንድር ነው? እስከ መንግሥቴ እኵሌታ እንኳ ቢሆን ይሰጥሻል አላት።
አስቴርም። ለንጉሡ መልካም ሆኖ ቢታይ ንጉሡ ወዳዘጋጀሁለት ግብዣ ከሐማ ጋር ዛሬ ይምጣ አለች።
ንጉሡም። አስቴር እንዳለች ይደረግ ዘንድ ሐማን አስቸኵሉት አለ። ንጉሡና ሐማ አስቴር ወዳዘጋጀችው ግብዣ መጡ።
አስቴር ከጥያቄዋ በፊት ግብዣ ነው ያቀረበችው። ምክንያቱም ቀልቡን ለመሳብ፤ የበላና የጠገበ ሰው መቼስ -ve መልስ አይመለስምና። ባሌ ነው፥ ደፍሬ ብጠይቅ ምን ያመጣል አላለችም። ለግብዣ እራሱ በትህትና ነው የጠየቀችው።
እኛም እግዚአብሔር አባታችን ብሆንም እንኳ ልጁ የአባቱን ሆድ ለማረሰረስ ምርቃትን ለመቀበል የማያደርገው ጥረት የለምና በዛው ልክ የቀደመዉን አስቀድመን እንቅረብ።
እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩትን ሳታስቀድሙ ለምናችሁ እግዚአብሔርን ጥፋተኛ ወይንም መልስ የማይመልስ ጨካኝ አምላክ አታደርጉት። እርሱ ምንም ብትሉት ሥርአቱን ጠብቆ የሚሠራ አምላክ ነው እንጅ ያለ ሥርአት ዘው ብሎ አይገባምና። ሰይጣን ብቻ ነው ያለ ሥርአት የሚገባው እንጅ እግዚአብሔር የሥርአት አምላክ ነው።
የቀደመውን አስቀድማችሁ ጠይቁ!!
ከተመቻችሁ ይቀጥላል......
@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH
INBOX @Thaddyapostolic
GROUP @Marantawoch | 2 006 |
| 7 | 6 በሄዱ ጊዜ፥ ዘራቸውን ተሸክመው እያለቀሱ ተሰማሩ፤ በተመለሱ ጊዜ ግን ነዶአቸውን ተሸክመው ደስ እያላቸው ይመጣሉ።
መዝሙር ዳዊት 126*6 | 1 |
| 8 | 🌻🌻 2017 🌻🌻
ዘማሪ ሹሚ ኤልያስ
አሳለፍከኝ ያንን አመት
እንደ ሃጢአቴ ሳትሆንብኝ
በማይዝል ትከሻ የሱስ ተሸክመህ
በምህረት እጆችህ አጠንክረህ ይዘህ
በከፍታዎች ላይ በድል አራመድከኝ
ክፉ እንዳይነካኝ በክንፍህ ከልለህ
አሳለፍከኝ ያንን አመት እንደጥያቴ ሳትሆንብኝ
ክበር ሌላ ምን እላለው
ሞገስ ሆንከኝ አከብርሀለው | 2 592 |
| 9 | 🌼«ለአዲስ ዓመት የምሆን መዝሙር »🌼
ዘማሪ ወንድም በረከት
እግዚአብሔር አሻገርኝ
እግዚአብሔር አሻገርኝ
መከራዬን እየሰረሳኝ
ከፊት ሆኖ እየመራኝ ዛሬን አየሁ ተሻገርከኝ |2×
አልሆንም እንደ ጠላቴ
ቀደምልኝ ደጉ አባቴ
እጄን ይዞ እያሳለፍን
መደገፊያ ጋሻ ሆኖልኝ
ዛሬን አየሁኝ ለዚህ በቃሁ |2×
እኔም ዛሬ ቀን ወቶልኛል
የታመንኩት እዚህ አድርሶኛል
ያልጠፋሁት በምህረቱ ነው
መደገፍያ ጋሻ ሆኖኝ ነው |2×
1| ኢየሱስ ምህረቱን በህይወቴ አብዝቶ ዘመን ዓመትን ሲያሳልፍኝ
የጠላቴን ሀሳብ ከንቱ እያረገ ከፊት ለፊቴ እየመራኝ
ዛሬ ፈቱ ቆመ ሰሙን እንዳከብር አለሁ በህይወት ክንዱ ደግፎኝ
ጉዞ ያስጀመረኝ መልካሙ እረኛዬ በክፉ ቀንም መሸሻግያየ |2×
እኔም ዛሬ ቀን....
2| እረ ማነው እንደኔ ያለ ያመሰግነው ክብር እያለ |2×
እረ ማነው እንደኔ ያለ ያክብርው እልል እያለ |2×
እኔ ነኝ ዛሬ በደስታዬ እኔ ነኝ የሱስን ላመልከው
እኔ ነኝ ጥበቃው በዝቶልኝ በፊቱ ሞገስ ያገኘሁት
እኔ ነኝ የምህረቱ ውጤት እኔ ነኝ በእርሱ መልካምነት
ኤረ እንዴት መልካም እረኛ ነው ብዘምር ይሄም ሲያንሰበት ነው
ይክብር |2× በምስጋናዬ
ይክብር |2× በእልልታዬ
አሻገሬነኝ ኢየሱስ ጌታዬ |2×
እኔም ዛሬ ቀን... | 2 |
| 10 | በማይዝል.... (1).m4a | 2 380 |
| 11 | # የቃሉ ሀይል
የእግዝአብሔር ቃል ሰማይን አጽንቶ ያቆመ በሰማይና በምድር ያሉትን አራዊት ሁሉ ይሁን
ብሎ የፈጠረ ከምንም ነገር በላይ ሀይል
ያለዉ ነዉ፦
ዘፍጥረት 1 ፥ 1፤ በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ።3፤ እግዚአብሔርም፡— ብርሃን ይሁን፡ ኣለ፤ ብርሃንም ሆነ።5፤ እግዚአብሔርም ብርሃኑን ቀን ብሎ ጠራው፥ ጨለማውንም ሌሊት፡ አለው። ማታም ሆነ ጥዋትም ሆነ፥ አንድ ቀን።
6፤ እግዚአብሔርም፡— በውኆች መካከል ጠፈር ይሁን፥ በውኃና በውኃ መካከልም ይክፈል፡ አለ።7፤ እግዚአብሔርም ጠፈርን አደረገ፥ ከጠፈር በታችና ከጠፈር በላይ ያሉትንም ውኆች ለየ፤ እንዲሁም ሆነ።
11፤ እግዚአብሔርም፡— ምድር ዘርን የሚሰጥ ሣርንና ቡቃያን በምድርም ላይ እንደ ወገኑ ዘሩ ያለበትን ፍሬን የሚያፈራ ዛፍን ታብቅል፡ አለ፤ እንዲሁም ሆነ።14፤ እግዚአብሔርም አለ፡— ቀንና ሌሊትን ይለዩ ዘንድ ብርሃናት በሰማይ ጠፈር ይሁኑ፤ ለምልክቶች ለዘመኖች ለዕለታት ለዓመታትም ይሁኑ፤15፤ በምድር ላይ ያበሩ ዘንድ በሰማይ ጠፈር ብርሃናት ይሁኑ፤ እንዲሁም ሆነ።
16፤ እግዚአብሔርም ሁለት ታላላቆች ብርሃናትን አደረገ፤ ትልቁ ብርሃን በቀን እንዲሠለጥን፥ ትንሹም ብርሃን በሌሊት እንዲሰለጥን፤ ከዋክብትንም ደግሞ አደረገ።17፤ እግዚአብሔርም በምድር ላይ ያበሩ ዘንድ በሰማይ ጠፈር አኖራቸው፤
የሆነዉ ነገር ሁሉ በእርሱ ሆነ
የተደረገውንም ሁሉ በቃሉ አደረገ
ዮሐንስ 1 ፥ 3፤ ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም።
የእግዚአብሔር ቃል የሞተዉን ያነሳል
የቃሉ ሀይል እዉሩን ያበራል
ቃሉ ህዉይታችን ያለመልማል
ቃሉ መንፈሳችን ያድሳል
ቃሉ ሀይል አለዉ ።
የእግዝአብሔር ቃል በሀይል ይሰራል
ሁል ግዘ የእግዚአብሔርን ቃል ለመስማት እንትጋ ከምንም ነገር አስበልጠን ተናግረን ብለን ቃሉን ለመስማት እንትጋ
እግዝአብሔር በአንድም በሌላም ይናገራል
ተብሎ ተጽፈዋል ስለዝ ሀል ግዘ ውደፊቱ
ቀርበን የምትናገረው አለና ተናግን እንበል። | 2 295 |
| 12 | አዲሱን አመት አዲሱን ዘመን *2
ያገልግሎት የሰላም የፍቅር ዘመን አድርግልን
ነፍሳት ከያቅጣጫው የሚጎርፉበት
በወንድማማች ፍቅር የምንዋደድበት
ቤተክርስትያን አድጋ እሰይ የምንልበት
ይሁን እየሱሴ አንተ ምትከብርበት
ያገልግሎት...
አዲሱን አመት...
የእያሪኮ ግንብ የሚፈርስበት
ይህ እውነት በአለም ዙሪያ አንድ የሚሆንበት
የሀዋርያት ወንጌል ብቻ ሚሰበክበት
ይሁን እየሱሴ አንተ ምትከብርበት
እሺ ዝቅ እያልን የምንዋደድበት
ወንድሜ ሆይ በርታ አይዞህ የምንልበት
ልብህ ተደስቶ እሰይ የምትልበት
ይሁን የድል አመት አንተ ምትክብርበት
አዲሱን አመት...
በፆምም በፀሎት የምንበረታበት
ሀይልህም ከሰማይ የሚወርድበት
ጥላቻ እርቆ ፍቅር የሚሰፍንበት
ይሁን የድል አመት አንተ ምትነግስበት
@MARANATHAWOCH | 2 024 |
| 13 | የማለዳ ትምህርት
የጸሎታችን መልስ ለምን ይዘገያል?
ክፍል 12 ለተቀበልነው ነገር አለማመስገን
እግዚአብሔር መስጠት ብቻ ሳይሆን መቀበልም የሚገባው አምላክ ነው። ብዙ ጊዜ ሰው ግን ስጠኝ ማለት እንጂ እንካ፥ ተቀበል ማለት ይረሳል። እግዚአብሔር መስጠት እንደሚችል እንዳመንን እንዲሁ መቀበልም እንደሚችል ማመን ወሳኝ ነው።
ከሁሉም ነገር እግዚአብሔር የሚፈልገው ነገር ብኖር ለሰጠው ነገር ሁሉ እንድናመሰግነው ነው። ስላደረገልን ነገር እያመሰገንን እንደገና እንዲያደርግልን ለፈለግነው ነገር መጸለይ አለብን።
በዚህ ምድር ላይ ሰው እንኳ ለተቸገረ ሰው የፈለገውን እርዳታ ሰጥቶ ምላሽ ስያጣ "ይህ ሰው ውለታ ቢስ ነው፤ ምስጋና የለውም " ይላል። እንደገና ተቸግሮ እንዳኝ ስል ለባለፈው ነገር መች አመሰገንከኝና አሁን ሊጨምርልህ የሚል ምላሽ ይሰጣል። በዛውም ልክ ከእግዚአብሔር ለተቀበልነው ነገር ሳናመሰገንን ለመቀበል ብቻ መቸኮል ለጸሎታችን መልስ አያስገኝም።
እኛ አናውቅም እንጅ ያልተሰጠን ነገር ምን አለ? እኛ በእጃችን የሚታይ ንብረትና ገንዘብ አይተን ለማመስገን እንፈልጋለን። ነገር ግን ከገንዘብ የበለጠ ሀብታችን እንዳለን እንረሳለን። ዋና ሀብታችን መዳናችን፣ ሠላማችንና ጤናችን ብቻ ለማመስገን በቂ ምክንያት ነው።
በሰውነታችን ውስጥ ያለውን እያንዳንዱን የሰውነት ክፍላችን ወደ ብር ብንቀይር ስንት ይሆን ነበረ? ለምሳሌ የአንድ ጥርስ ዋጋ ስንት ብር ነው? በ32 አባዙ። የአንዱ ኩላልታችን ዋጋ ስንት ነው? በ2 አባዙ። የአንድ አይናችን ዋጋ ስንት ነው? በ2 አባዙ፤...... የሁሉንም ሰውነታችን አካል ክፍል ወደ ብር ቀይሩ እስቲ። ይህ ሁሉ በሠላም በጤና ተጠብቆ የሚኖር ነገር ግን ለእኛ የማይታይ ሀብታችን ነው።
እኛ ጧት ተነስተን እጃችንና ፊታችን ሊንታጠብ እንሮጣለን፤ ሌላው ግን በየጧቱ ኩላሊቱን ሊታጠብ የሚሮጥ አለ። ከእኛ ውስጥ ብያንስ አንድ ሰውነቱ ክፍል ታምሞ መታከም የሚችል ማነው? መጀመሪያ ላለን ሠላም ሳናመሰግን ገንዘብ ከለከለን ብለን እንወቅሳለን። እርሱ ግን መጀመሪያ ባለህ ነገር አመስግን ይለናል።
ሌላው ብቀር መዳናችን ብቻ በብር የሚተመን ነው? ስንት ቢሊየን ያላቸው ሰዎች ይህንን መዳን ሳያገኙ ይሞታሉ? ለእኛ ግን አንድ ብር ለሌለን ሰዎች ይህንን መዳን በነጻ ሰጥቶን በቤቱ አኑሮናል። ይህ ብቻ የሚናመሰገንበት ትልቅ ምክንያት ነው። "እጅ ያለው ወርቅ እንደ መዳብ ይቆጠራል"
እንደሚባለው ነው ምንም ያልመሰለን እንጅ በእጃችን ያለው ነገር በዋጋ የሚተመን አይደለም።
ዘዳግ 28፥47&48 ሁሉን አብዝቶ ስለ ሰጠህ አምላክህን እግዚአብሔርን በፍሥሐና በሐሤት አላመለክህምና በራብና በጥማት በዕራቁትነትም ሁሉንም በማጣት እግዚአብሔር ለሚልክብህ ለጠላቶችህ ትገዛለህ፤ እስኪያጠፋህም ድረስ በአንገትህ ላይ የብረት ቀንበር ይጭናል።
እስራኤል ለሠራላቸው ተአምራት የማያመሰገኑ ናቸው፥ ነገር ግን ለሚሰጣቸው ነገር ብቻ የሚለምኑ፤ይህ ነገር መጨረሻቸውን አላሳመረላቸውም። ውለታውን ፈጥነውም እየረሱ ስያስቸግሩ የለመኑትንም ሁሉ ሰጣቸው፤ ለነፍሳቸው ግን ክሳትን ላከ ይላል።
መዝ 106፥13-15 "ፈጥነውም ሥራውን ረሱ፥ በምክሩም አልታገሡም። በምድረ በዳም ምኞትን ተመኙ፥ በበረሃም እግዚአብሔርን ተፈታተኑት። የለመኑትንም ሰጣቸው፤ ለነፍሳቸው ግን ክሳትን ላከ።"
እግዚአብሔር የለመንነውን ቶሎ ብመለስልን እንኳ የሰጠን በረከት ለነፍሳችን የማይጠቅም ከሆነ ምን ዋጋ አለን? ለእስራኤል ይህንን የነፍስ ክሳት ያመጣው ውለታውን መርሳት ነው እንጂ አለማመን አይደለም። ሥጋችንን አወፍሮ ነፍሳችንን የሚያከሳ በረከት አሁንም ቤታችን አይግባ።
ስንጸልይ ይህንን የሰጠሄን አንተ ነህና ተመስገን እያልን ምስጋና እየሰጠን አሁንም የቀረውን አንተ ታውቃለህ እንድንል ይፈልጋል እንጂ ለኔ፣ ለኔ፣ ለኔ ብቻ የሚል ጸሎት አይሰማም።
በቆላስ 4፥12 "ከማመስገን ጋር በጸሎት እየነቃችሁ ለእርሱ ትጉ"ይላል። ጸሎት ከምስጋና ጋር ነው እንጂ በእምባና በለቅሶ ጋር ብቻ አይደለም። እንኳን ለተሰጠን ነገርና ላልተሰጠን ነገርም የሚናመሰግን አምላክ ነው። ሰጥቶም ነስቶም እርሱ አምላክ ነውና።
ኢዮብ ይህ ሁሉ ፈተና ደርሶለት እያለ አንድም ቀን እግዘብሔርን አልበደለም። ይልቅ እግዚአብሔር ሰጠ፤ እግዚአብሔር ነሳ፤ የእግዚአብሔር ስም የተባረከ ይሁን"አለ እንጂ። እኛ ዛሬ እንኳን ልጆቻችንና እንስሳቶቻችን ማለቅ ይቅርና 1000 ብር ከክሳችን ወጥቶ ብጠፋ እግዚአብሔር አላወቀኝም፤ እግዚአብሔር እኔን ይጠላል እያልን እስከ ስድብ እንደርሳለን። ልጁ ሞቶበት ማነው እግዚአብሔር ይመስገን የሚል?
እንዲህም አለ። ራቁቴን ከእናቴ ማኅፀን ወጥቻለሁ፥ ራቁቴንም ወደዚያ እመለሳለሁ፤ እግዚአብሔር ሰጠ፥ እግዚአብሔርም ነሣ፤ የእግዚአብሔር ስም የተባረከ ይሁን። ፤ በዚህ ሁሉ ኢዮብ አልበደለም፥ ለእግዚአብሔርም ስንፍናን አልሰጠም።
በእኛ ዘመን እንኳን ትንሽ የታገሰ ሰው ነው የሚንለው ሰው እግዚአብሔር ሰጠ፤እግዚአብሔር ነሳ የሚል ሰው ብኖር ነው። የእግዚአብሔር ስም የተባረከ ይሁን የሚልማ ተፈልጎም አይገኝም። ስለዚህ ለተቀበልነው ነገር አለማመስገን ለሚንቀበለው ነገር መንገድ አይሰጥምና እንጠነቀቅ። መቀበል ብቻ ሳይሆን መስጠትንም እንልመድ።
ፊልጵ 4፥6 ጌታ ቅርብ ነው። በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ።
ይቀጥላል.....
@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH
INBOX @Thaddyapostolic
GROUP @Marantawoch | 2 117 |
| 14 | Adama ACOE
ደቡብ አጥቢያ
New apostolic song
Singer: fechatu
Title: ባንተ ተሻግሬ
ባንተ ተሻግሬ
ባንተ ሁሉን አልፌ
ባንተ ይሄው ቆሜ
ባንተ ዛሬን አይቼ
ላንተ አቀርባለሁ ምስጋናዬን
ላንተ አቀርባለሁ እልልታዬን
ላንተ አቀርባለሁ የድል መዝሙር
ላንተ አቀርባለሁ ይሄው የሱስ
ይሄው/*2 የሱስ/*4
1/ረዳቴ አንተው ነህ እኔን የረዳሄኝ
አቅሜ ሆነኸኝ የሱስ ያሻገርከኝ
ምን ብልህ ይሻላል ምንስ ይመጥናል
ምስጋና አምልኮ ይሄው አፌ ሞልቷል ላንተ
ይሁን ምስጋናዬ
ይሁን አምልኮዬ
ይሁን ለስምህ
ይሁን ክብር ላንተ
ሁሉን ለምትችል
ሁሉን ላደረከው
ኤልሻዳይ ለሆንከው
2/አቀበት ቁልቁለት ስወጣ ተራራውን
በእሳት በሀሩር ውስጥ የነበርክ ከኔጋር
(በሀሩሩ መሀል የነበርክ ከኔጋር)
አይኖቼን አንስቼ አንተን ስመለከት
ነይ ልጄ ብለኸኝ ይዘህ ያራመድከኝ
ረዳቴ ከወዴት ይምጣልኝ
አይኖቼን አንስቼ እየጠበኩ
እኔን የሚረዳኝ የሚያግዝ
ባልኩኝ ስዓት ደረስክ እየሱስ
ረዳኸኝ/*2
አገዝከኝ/*2
ይሄው ለክብር አቆምከኝ
3/ሁሉን የምትችል ክንደ ብርቱ አምላክ
ጉልበት ስልጣን ያለህ በእውነት ምትታመን
የማትለዋወጥ በዘመናት መሀል
ተመስገን እየሱስ ክብር ይገባሀል
እልል/*4
ለስምህ ክብር ይሁንልህ
ኤልሻዳዩ አምላክ እየሱስ
ውዳሴ አምልኮ ይቅረብልህ | 2 442 |
| 15 | የዛሬው ጥያቄና መልስ በጣም ጥሩ ተወዳዳሪዎች የተገኙበት ውድድር ነው። ይሁን እንጅ አብዘኞቹ AI ,App በመጠቀም ነው የሠሩት። ስለዚህ ለወደፊት ጥንቃቄ አድርጉ ማለት እወዳለሁ።
ካልሆነ ይህንን ፕሮግራም አቆማለሁ።
የሁሉንም ውጤት ለማጣራት ሞክረያለሁ ከእነዚህ ውስጥ ያለ AI ከሠሩት ውስጥ
1, እህት Tina 10/10
አብዘኞቹ ግን 9/10 ናቸው። ስለዚህ የፈለገችውን PDF የሚትሸለመው እህት Tina ነች ማለት ነው
በዚህ ከቀጠላችሁ የጥያቀና መልስ ፕሮግራም ይቆማል። ይህ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ምን ያህል እየተከታተልኩ ነኝ የሚለውን ማሳያ ነው እንጅ ከክፍል ወደ ክፍል ማለፊያ አይደለም። app መስራት የመጽሐፍ ቅዱስ እውቀት መለክያ አይደለም። | 2 091 |
| 16 | አሁን መልስ ተለቋል አቁሙ | 437 |
| 17 | መልስ
1, ጓጉንቸሮች። ዘፀዓት 8፥13 እግዚአብሔርም ሙሴ እንዳለ አደረገ፤ ጓጕንቸሮቹም ከቤት ከወጀድም ከሜዳም ሞቱ።
14 እንደ ክምርም አድርገው ሰበሰቡአቸው፤ ምድርም ገማች።
2, 7 ቀን። ዘፀዓት 7፥25 እግዚአብሔርም ወንዙን ከመታ በኋላ ሰባት ቀን ተፈጸመ።
3, 12 ወራት ነው። አሥር 2፥12 የመንጻታቸውም ወራት ስድስት ወር ያህል በከርቤ ዘይት፥ ስድስት ወርም በጣፋጭ ሽቱና በልዩ ልዩም በሚያነጻ ነገር ይፈጸም ነበርና እንደ ሴቶች ወግ አሥራ ሁለት ወር እንዲሁ ከተደረገላት በኋላ ወደ ንጉሡ ወደ አርጤክስስ ለመግባት የአንዳንዲቱ ቆንጆ ተራ በደረሰ ጊዜ፥......
4, ሄጌ ይባላል። አስተር 2፥3 ሴቶችን ከሚጠብቅ ከንጉሡ ጃንደረባ ከሄጌ እጅ በታች እንዲያደርጓቸው መልከ መልካሞቹን ደናግል ሁሉ ወደ ሱሳ ግንብ ወደ ሴቶች ቤት ይሰበስቡአቸው ዘንድ ንጉሡ በመንግሥቱ አገሮች ሁሉ ሹማምቶችን ያኑር፤ ቅባትና የሚያስፈልጋቸውም ይሰጣቸው፤
5, የሙሴ ሦስት ሲፓራም። 25 ሲፓራም ሚስቱ ባልጩት ወሰደች፥ የልጅዋንም ሸለፈት ገረዘች፥ ወደ እግሩም ጣለችው፡— አንተ ለእኔ የደም ሙሽራ ነህ አለች።
6, የሞከብ ንጉሥ ዔግሎም።
መጻፍ 3፥17 ለሞዓብም ንጉሥ ለዔግሎም ግብሩን አቀረበ፤ ዔግሎምም እጅግ ወፍራም ሰው ነበረ።
7, ሐ ሠለሞን
2ዜና 9፥17 እና 1ነግ 10፥18ንጉሡም ደግሞ ከዘሆን ጥርስ ታላቅ ዙፋን አሠራ፥ በጥሩ ወርቅም ለበጠው።
8, ሐ ዕዝራ። ዕዝራ 7፥6 የእስራኤልም አምላክ እግዚአብሔር በሰጠው በሙሴ ሕግ ፈጣን ጸሐፊ ነበረ፤ የአምላኩም የእግዚአብሔር እጅ በእርሱ ላይ ነበረችና ንጉሡ የሻውን ሁሉ ሰጠው።
9, ለ
10, ሀ
ለ9&10 የራዕይ ትርጉም መጽሐፍ አምብቡ
@MARANATHAWOCH
አስተያየት @Thaddyapostolic ላይ ጻፉ | 2 126 |
| 18 | +10 ደቂቃ | 323 |
| 19 | ጥያቄና መልስ
መልስ @Thaddyapostolic ላይ ብቻ inbox አድርጉልኝ አደራ።
#ማሳሰቢያ፦ ከ1-6 ላለው ጥያቄ ከነ ቃሉ ጥቅስ ማስረጃ ጋር መልሱ። ካልሆነ መልሱ ትክክል ብሆንም ግማሽ ይሰጣል።
የተሰጠ ሰአት 30 ደቂቃ ነው
1, የግብፅ ምድር ሙሉ የገማው መች ነው ማለትም የትኛው መቅሰፍት በወረደ ጊዜ ነው?
2, በፈርኦን ልብ ደንዳናነት ምክንያት በግብፅ ምድር ውሀ ወደ ደም ተለውጦ ስንት ቀን ቆየ?
3, በንጉሡ አርጠክስስ ዘመን የነበሩ ሴቶች ወደ ንጉሡ ለመቅረብ እራሳቸውን እያስዋቡ በተመረጠ ቤት ውስጥ ምን ያህል ቆዩ?
4, ለንጉሡ አርጠክስስ የሚሆኑ ሴቶች መርጦ ቅባትና የሚያስፈልጋቸውን ሁሉ እየሰጣቸው ሴቶችን የሚያይዋብ የንጉሡ ጀንደረባ ማነው?
5, በመጽሐፍ ቅዱስ ታርክ ውስጥ የራሷን ልጅ በባልጩት የገረዘች ሴት ማን ነች?
6, ከሞአብ ህዝብ ሁሉ እጅግ ወፍራም ሰው ማን ነበረ?
7, ከዝሆን ጥርስ የተሰራ ታላቅ ዙፋን የነበረው ንጉሥ ማነው?
ሀ ዳዊት ለ ናቡከድናፆር ሐ ሰለሞን መ ሙሴ
8, የአምላኩ የእግዚአብሔር እጅ ከእርሱ ጋር ነበረች የተባለለት ፈጣን ፀሐይ ማን ይባላል?
ሀ ያቤጽ ለ አሳፍ ሐ ዕዝራ መ ኤርምያስ
9, ከሰባቱም አብያተ ቤተክርስቲያናት ውስጥ የአመንዝራ ቤተክርስቲያን ምሳሌ የሆነች ቤተክርስቲያን የትኛው ነች?
ሀ ሰርደስ ለ ቲያጥሮን ሐ ጰርጋመን መ ሎዶቂያ
10, "የጥንቱ ሀይማኖት ሰጠን" ተብሎ የተዘመረው በየትኛው ቤተክርስቲያን ዘመን ነው?
ሀ ፍላደልፍያ ለ ኤፈሶን ሐ ሰርደስ መ ሎዶቂያ
@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH
መልስ @Thaddyapostolic ላይ ብቻ መልሱልኝ | 2 015 |
| 20 | ማሳሰብያ፦ ሐሙስ የጥያቄና መልስ ምሽት
ውድ የማራናታ ተለግራም ቻናል ቤተሰብ እንደምን ቆያችሁ?
ዛሬ ማታ ማለትም ሐሙስ ምሽት ልክ 2: 00 ላይ የጥያቄና መልስ ውድድር ይኖረናል። በጊዜ ገብታችሁ እንድትሳተፉ አሳስባችኋለሁ። አንደኛ ለወጣ ተወዳዳሪ ከታች ከተዘረዘሩት pdf የፈለገውን pdf እንሸልማለን።
pdf
1, የዘፍጥረት እንቁዎች ብሾፕ ዳዊት ጦሼ
2 ገንዘብና መንፈሳዊ ህይወት ብሾፕ አንዱአለም
3 የመዳን እውቀት መፅሐፍ ብ/ ደጉ
4 በሥርአት ታነፁ ብሾፕ ተ/ማሪያም
5 የራዕይ ትርጉም pdf ብሾፕ ደጉ
6, የእውነት ወንጌል ጥሪ ፓስተር በረከት
7 ኢየሱስን ማን ይሉታል ብሾፕ ተ/ማርያም
8 ቃሉ ይናገር ብሾፕ ተ/ማርያም
10 የሥላሴ አጠያያቂ ምስጥር ቄስ ኤልያስ ሸባባው
11 የንስር መንገድ
12 መፅሐፍ ቅዱስ ትምህርት ለጀማሪዎች ብሾፕ ተክሌ
13 ህይወት የሚገኝበት ትምህርት ብሾፕ ደጉ
14 ወደ መዳን የሚያደርስ እውነት ብሾፕ ደጉ
15 መንፈሳዊ ወጣት
16 እውነት እና ምህረት
17 እምነት በእግዚአብሔር ቃል
18 የመዳናችን ምስጥር
19 የመልዕክቶች አጠቃላይ ትምህርት ብሾፕ ተክሌ
20 Eschatology Final destiny of humanity ብሾፕ ጌታሁን
21 የአንድ አምላክ ልጆች ይለይ
22 መሠረታዊ የክርስትና ትምህርቶች
.
.
.
ከእነዚህና ሌሎችንም መርጦ #አንዱን ይወስዳል። ለጓደኞቻችሁ ሼር አድርጉ።
ልብ በሉ ! መልስ @Thaddyapostolic ላይ ብቻ ይመለሳል
@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH | 1 714 |
